#ቆንጆዎቹ
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ሁለት
፡
፡
#ድርሰት_ሰርቅ_ዳ
“እና ደግሞ ጭራ
“የምን ጭራ? "
“ጭራ ነዋ፤ የዝንብ ማባረሪያ ጭራ፡፡”
ደግሞ ጭራ ምን ይሰራልሃል?
“ነገርኩሽኮ፡፡ ቄስ መምሰል ነው የምፈልገው::
ወር ሆነው ዘውዲቱ ቤት ዘግቶ ከተቀመጠ፡፡ ድንገት ሲሰወር
ደብዛው ሲጠፋ አውሬው እያጓራ በየስርቻው እንደሚያነፈንፍ ገምቷል፡፡
ቢሆንም አንድ ቦታ አድብቶ ጊዜ እስከወሰደ ድረስ መልሰው ጭራውን
ለመያዝ ይቸገራሉ። በዛ ጊዜ ውስጥ ራሱን ለመቀየር ጊዜ ያገኛል።
ከውዲቱ ጋር በሂሣብ ተስማምተው እዛው ሰነበተ:: . አብሯት የሚያድር ደንበኛ ያገኘች ሌሊት እፎይ ብሎ አንዴ በጀርባው አንዴ በደረቱ እየተገላበጠ ደልቶት እየተኛ ያልቀናት : ሌሊት ደግሞ የማታ ማታ እየተጎተተች መጥታ በዛችው ጠባብ ታጣፊ አልጋ ላይ እየተጋፉ ወር
አለፈ ፤ እንደምንም::
ገና ቤቷን በተከራየ በአራተኛው ቀን ነበር አላስችል ብሏት የጠየቀችው:: የጠበቀው ጥያቄ ነበር! መምጣቱ አላስደነገጠውም
አላስበረገገውም:: ተዘጋጅቷል፤ ምን እንደሚመልስላት ያውቅ ነበር፡፡
"ጺምህን ለምን አትላጨውም? ደግሞ ለምን ወጣ አትልም? ከጠዋት ጀምረህ እስከ ማታ በር ዘግተህ ምንድነው? የጤና ነው?” አለችው ጠዋት ከደንበኛ ጋር ኣድራ አረፋፍንዳ ስትመጣ ቤት ስታገኘው፡፡
“አዎ፡፡” አላት ነገሩን በአጭሩ ለመቅጨት፡፡
“ምን ማለት ነው አዎ?” አለች የምታበጥረውን ፀጉሯን ለቃ
ቁለቁል በተቀመጠበት እየተመለከታችሁ
“አዎ ነዋ፡፡” አለ ይበልጥ ገፍታ ገፍታ እስክትመጣ ወጥራ እስክትይዘው፡፡
ሁኔታው እንዳላማራት በግልጽ ታስታውቃለች። ቀሚሷን በጭንቅላቷ አውልቃ አልጋው ላይ ወርወር አደረገችውና ከፊት ለፊቷ
ያለውን ቁም ሳጠን ከፈተች፡፡
“እየው ወንድም” አለች ከቁም ሳጥኑ ውስጥ የታሰቀላ ልብስ ማውረዷን ሳታቋርጥ ፊቷን ወደሱ መልሳ፡፡ «እየው ወንድም ብሬ እስካልተቋረጠ ድረስ ዓመትም ተግተህ ብትቆይ ግድ የለኝም:: ግን ደግሞ ችግር አልፈልግም፡፡ ከፖሊስ ነው የተደበቅኽው አይደል?”
“ምን ማለትሽ ነው? እንዴት ከፖሊስ?” ደነገጠ፡፡
ተው ባክህ አለች ከቁምሳጥኗ ያወረደችውን ቀሚስ እያጠለቀች፡፡ “አሁን ማን ይሙት ዓለም በቃኝ ብለህ እኔ ጎጆ ውስጥ ሱባዔ የገባኸው ለነፍስህ ነው?”
የሚለው ጠፍቶት ዝም ብሎ ተመለከታት፡፡
“ሰርቀህ ነው! አይደል? ሰርቀህ ነው የተደሰቅኸው?“
“አይደለም… አይደለም::” አለ ፈጠን ብሎ፡፡ ለፖሊስ እንዳታሳጣው
ሰጋ፡፡
“ታዲያ ምንድነው? ወይስ ፍቅር ያዘህ ከኔ!” አለች ድንገት ስቃ፡፡
“እየው እኔ ግድ የለኝም:: ሌባ ቀርቶ የፈለከውን መሆን ትችላለህ፡፡ ግን
ልምከርህ፡፡ ከፖሊስ ከሆነ የተደበቅኸው እዚህ ተከተህ አታመልጣቸውም፡፡
አንድ ቀን ወጣ ያልክ ቀን ጋማህን ያብቱሃል፡፡ ራቅ ብለህ ሂድ፡፡ ድሬድዋ
ወይ ጅማ! እንደገንዘቡ እንደሰረቅከው ገንዘብ ብዛት፡፡”
ከተቀመጠበት ኣልጋ ላይ ተነስቶ
“ሰርቄ አይደለም ዘውዲቱ በጠባቧ ክፍል ጎርደድ ማለት ያዘ፡፡
“ታዲያ እኔ ቤት ውስጥ እናትህን ቀብረሃል? ”እይኖቿ አብረው
እየተንጎራደዱ ወገቧን ይዛ ጠየቀችው፡፡
ጊዜው እንደሚደርስ ቀድሞውኑም ገብቶታል፡፡ እንደምትጠይቀው ወጥራ እንደመትይዘው ገብቶታል፡፡የሚያሳምን ምክንያት መስጠት እንዳለበትም ተረድቷል፡፡ አለበለዚያ ለሳምንታት ቤቷ ውስጥ ተደብቆ ሊቆይ አይችልም፡፡ በአጭሩ የቤትሽን ኪራይ እስካላቋረጥኩ ድረስ አያገባሽም፡፡ ብሎ ዝም ሊያሰኛት ይችላል። ግን ደግሞ ልትፈራ ትችላለች! ወንጀል ፈጽሞ ከቤቷ የተሸሸገ ሊመስላት ይችላል:: “ውጣ!” ብትለውስ? ፖሊስ ይዛ
ከተፍ ብትልስ?ለዚህ ነው ቀደም ብሎ የሚላትን ያዘጋጀው፡፡ “ሊያስደነግጣት
አይገባም፡፡ ግን ደግሞ ልታዝንለት ይገባል። ችግሩን ተረድታ ልትረዳው
ፈቃደኛ መሆን አለባት፡፡ ቀስ ብሎ ማግባባት አለበት፡፡
“ምን መሰለሽ ዘውድዬ.…አለ ቀረብ ብሎ ግራ ክንፏን ያዝ አደረገና፡፡ “ግን አደራ…”
አይ ይሄን ያህል የሚያስጨንቅህ ከሆነ አትንገረኝ፡፡ ምን መሰለህ ከብዬ በሰላም መኖር ስለምፈልግ ብቻ ነው፡፡ ገላዬን ሽጨ የኖርኩት አንሶኝ ተባበርሽ ምንትስዬ ተብዬ ዘብጥያ መውረድ አልፈለግም፡፡ ይገባሃል አይደል?ልጅ አለኝ፡፡ የምወደው የምቀልበው ወንድ ልጅ፡፡ነገ የሚሸረሙጥ” ፈገግ አለች፡፡
ልታስከፋው እንዳልፈለገች ከሁኔታዋ ያስታውቃል፡፡ባለፉት ቀናቶች
ሳይታወቃቸው በመሃላቸው የመግባባት ስሜት ተፈጥሯል፡፡ስሙን ስትጠይቀው 'ከበደ' ብሎ እንደዋሻት ብትረዳም አላስጨነቀችውም፤ ስቃ ተወችው
ተወችው።ተከትለዋት እቤቷ ድረስ መጥተው ተጨማልቀው አጨማልቀዋት
ሳንቲም ወርውረውላት እንደሚሄዱ ደንበኛቿ እንዳልሆነ ግን ተረድታዋለች፡፡
የመጀመሪያው ማታ አብሬሽ
አልተኛም ሲላት ለይስሙላ ነበር የመሰላት፡፡ አጋጥመዎታላ! የገዛ ገንዘባቸውን ከፍለው መጥተው ተለማመጡን የሚሉ፤ ካላንቆለጳጰሳችሁን የሚሉ፤ “ያው የገዛችሁት ዕቃ” ሲባሉ የሚግደረደሩ።
ያን ቀን ማታ በል የውስጥ ልብሴን አቀብለኝ ብላው ያለችውን አቀብሏት : መብራቱን አጥፍቶ ከጎኗ አልጋው ውስጥ ሲገባ ይዘግይ እንጅ ያው እንደ አውሬ ወንድሞቹ የማታ የማታ ዘሎ እንደሚያንቃት አልተጠራጠረችም ነበር፡፡ አልጋዋ ወስጥ ገብቶ በጀርባው ተኝቶ
አንጋለወት እንደሄዱ ህፃን ጣሪያ ጣሪያውን ሲመለከት በጨለማው ውስጥ
ስታየው ደነቃት፣ቢሆንም አላመነችውም፡፡ ዘግይቶ ሊጓጉር ነው ብላ ደህና እደር አለችና በደረቷ ተገልብጣ ተኛች፡፡ እንቅልፍ ሊወስዳት ግን አልቻለም፡፡ ሰውነቷ አላርፍልሽ አላት:: . 'ከአሁን አሁን ዘሎ.. እያለች እላይ እታች የሚለውን ትንፋሹን ተከተለችው::
እንቅልፍ፡ እንዳልወሰደው እርግጠኛ ነበረች፡፡ እንዳሰበችው ሃሳቡን
ሳያቀያር ዘገየባት፡፡ ሲያነቃቃውና በጊዜ ብገላገል ብላ በእንቅልፍ ልቧ
እንዳለች ሁሉ ተወራጨችና በብርድ ልብሱ ውስጥ ክንዷን ሰድዳ አንድ
እጇን ጭኑ ላይ ጣል አደረገችው:: ተፈታተነች፡፡ ሲሸማቀቅ ተሰማት።
እጁን ሰድዶ እጇን ከላዩ ላይ አነሳና በቀስታ እራቅ አድርጎ አስቀመጠው፡፡
በእንቅልፍ ልቧ ያለች ሳይመስለው አልቀረም። ጃውሳው! በጉ! ተረጋጋች፡፡
ሳታውቀው ድብን ያለ አንቅልፍ ይዟት ጭልጥ አለ፡፡
በተከተሉት ቀናት ሳትጠይቀው ቀድሞ የተስማሙበትን የወር የቤት ኪራይ ሂሳብ ሰጣት፡፡ ከዛ በተረፈ ሆቴል እንድታመጣለት ገንዘብ እየሰጣት እራሱን ብቻ ሳይሆን እሷንም እየቀለበ ተቀመጠ፡፡ ተገኝቶ ነው?፡፡ ግን ደግሞ አቤት ብቅ አለማለቱ የተደበቀ ሰው አስመስሎታል፡፡ አንድ ክፍል ቤቷ ውስጥ ዘግቶ መቀመጥ ምን ማለት ነው? . ታዲያ ይና ዝም
ብሎ ማለፍ ይቻላል? እህእ ነገ አንዱ መርቶበት ቢያስይዘው አብራ መውረዷ እደደለም? የተካፈለች አብራ የገመጠች ይመስል ሆ!
“ልክ ነሽ! ልክ ነሽ! ይገባኛልኮ፡፡ ግን ሠርቄ አይደለም፡፡” አላት የያዛቸውን ክንዶቿን ለቆ አልጋው ላይ እየተቀመጠ፡፡
“እሺ ምንድነው ታድያ? ”
“እደው ምን መሰለሽ…” ያጠነጠነውን ይተረትር ጀመር፡፡ አራት ቀን መሉ ብቻውን በሚሆን ሰዓት እየተንጎራደደ ያጠናውን የተለማመደውን ዲስኩር ጀመረ፡፡
“በምስራበት መሥሪያ ቤት ውስጥ ረዳት የሂሣብ ክፍል ኃላፊ ሆኜ ነው የማገለግለው ዘውድዬ እኔ ትዳር ያለኝ ሰው ነኝ፤ የሁለት ልጆች አባት ነኝ:: ነገር አልሻም፤ በሠላም ሰርቼ ከቤቴ መግባት ከባለቤቱና ከልጆቼ ጋር ያገኘሁትን ተቋድሼ ማደር ነው የምሻ:: ምን መሰለሽ…” ትክ ብለው ቁልቁል የሚያዩት አይኖቿ ሰርስረውት ገቡ፡፡ ግንባሩን የምታነብ መሰሰው፡፡ሁለት እጆቹን አንስቶ ለአንድ አፍታ በመዳፎቹ ውስጥ ደበቀው ሰባራ ሳንተም አላነሳሁም ግን
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ሁለት
፡
፡
#ድርሰት_ሰርቅ_ዳ
“እና ደግሞ ጭራ
“የምን ጭራ? "
“ጭራ ነዋ፤ የዝንብ ማባረሪያ ጭራ፡፡”
ደግሞ ጭራ ምን ይሰራልሃል?
“ነገርኩሽኮ፡፡ ቄስ መምሰል ነው የምፈልገው::
ወር ሆነው ዘውዲቱ ቤት ዘግቶ ከተቀመጠ፡፡ ድንገት ሲሰወር
ደብዛው ሲጠፋ አውሬው እያጓራ በየስርቻው እንደሚያነፈንፍ ገምቷል፡፡
ቢሆንም አንድ ቦታ አድብቶ ጊዜ እስከወሰደ ድረስ መልሰው ጭራውን
ለመያዝ ይቸገራሉ። በዛ ጊዜ ውስጥ ራሱን ለመቀየር ጊዜ ያገኛል።
ከውዲቱ ጋር በሂሣብ ተስማምተው እዛው ሰነበተ:: . አብሯት የሚያድር ደንበኛ ያገኘች ሌሊት እፎይ ብሎ አንዴ በጀርባው አንዴ በደረቱ እየተገላበጠ ደልቶት እየተኛ ያልቀናት : ሌሊት ደግሞ የማታ ማታ እየተጎተተች መጥታ በዛችው ጠባብ ታጣፊ አልጋ ላይ እየተጋፉ ወር
አለፈ ፤ እንደምንም::
ገና ቤቷን በተከራየ በአራተኛው ቀን ነበር አላስችል ብሏት የጠየቀችው:: የጠበቀው ጥያቄ ነበር! መምጣቱ አላስደነገጠውም
አላስበረገገውም:: ተዘጋጅቷል፤ ምን እንደሚመልስላት ያውቅ ነበር፡፡
"ጺምህን ለምን አትላጨውም? ደግሞ ለምን ወጣ አትልም? ከጠዋት ጀምረህ እስከ ማታ በር ዘግተህ ምንድነው? የጤና ነው?” አለችው ጠዋት ከደንበኛ ጋር ኣድራ አረፋፍንዳ ስትመጣ ቤት ስታገኘው፡፡
“አዎ፡፡” አላት ነገሩን በአጭሩ ለመቅጨት፡፡
“ምን ማለት ነው አዎ?” አለች የምታበጥረውን ፀጉሯን ለቃ
ቁለቁል በተቀመጠበት እየተመለከታችሁ
“አዎ ነዋ፡፡” አለ ይበልጥ ገፍታ ገፍታ እስክትመጣ ወጥራ እስክትይዘው፡፡
ሁኔታው እንዳላማራት በግልጽ ታስታውቃለች። ቀሚሷን በጭንቅላቷ አውልቃ አልጋው ላይ ወርወር አደረገችውና ከፊት ለፊቷ
ያለውን ቁም ሳጠን ከፈተች፡፡
“እየው ወንድም” አለች ከቁም ሳጥኑ ውስጥ የታሰቀላ ልብስ ማውረዷን ሳታቋርጥ ፊቷን ወደሱ መልሳ፡፡ «እየው ወንድም ብሬ እስካልተቋረጠ ድረስ ዓመትም ተግተህ ብትቆይ ግድ የለኝም:: ግን ደግሞ ችግር አልፈልግም፡፡ ከፖሊስ ነው የተደበቅኽው አይደል?”
“ምን ማለትሽ ነው? እንዴት ከፖሊስ?” ደነገጠ፡፡
ተው ባክህ አለች ከቁምሳጥኗ ያወረደችውን ቀሚስ እያጠለቀች፡፡ “አሁን ማን ይሙት ዓለም በቃኝ ብለህ እኔ ጎጆ ውስጥ ሱባዔ የገባኸው ለነፍስህ ነው?”
የሚለው ጠፍቶት ዝም ብሎ ተመለከታት፡፡
“ሰርቀህ ነው! አይደል? ሰርቀህ ነው የተደሰቅኸው?“
“አይደለም… አይደለም::” አለ ፈጠን ብሎ፡፡ ለፖሊስ እንዳታሳጣው
ሰጋ፡፡
“ታዲያ ምንድነው? ወይስ ፍቅር ያዘህ ከኔ!” አለች ድንገት ስቃ፡፡
“እየው እኔ ግድ የለኝም:: ሌባ ቀርቶ የፈለከውን መሆን ትችላለህ፡፡ ግን
ልምከርህ፡፡ ከፖሊስ ከሆነ የተደበቅኸው እዚህ ተከተህ አታመልጣቸውም፡፡
አንድ ቀን ወጣ ያልክ ቀን ጋማህን ያብቱሃል፡፡ ራቅ ብለህ ሂድ፡፡ ድሬድዋ
ወይ ጅማ! እንደገንዘቡ እንደሰረቅከው ገንዘብ ብዛት፡፡”
ከተቀመጠበት ኣልጋ ላይ ተነስቶ
“ሰርቄ አይደለም ዘውዲቱ በጠባቧ ክፍል ጎርደድ ማለት ያዘ፡፡
“ታዲያ እኔ ቤት ውስጥ እናትህን ቀብረሃል? ”እይኖቿ አብረው
እየተንጎራደዱ ወገቧን ይዛ ጠየቀችው፡፡
ጊዜው እንደሚደርስ ቀድሞውኑም ገብቶታል፡፡ እንደምትጠይቀው ወጥራ እንደመትይዘው ገብቶታል፡፡የሚያሳምን ምክንያት መስጠት እንዳለበትም ተረድቷል፡፡ አለበለዚያ ለሳምንታት ቤቷ ውስጥ ተደብቆ ሊቆይ አይችልም፡፡ በአጭሩ የቤትሽን ኪራይ እስካላቋረጥኩ ድረስ አያገባሽም፡፡ ብሎ ዝም ሊያሰኛት ይችላል። ግን ደግሞ ልትፈራ ትችላለች! ወንጀል ፈጽሞ ከቤቷ የተሸሸገ ሊመስላት ይችላል:: “ውጣ!” ብትለውስ? ፖሊስ ይዛ
ከተፍ ብትልስ?ለዚህ ነው ቀደም ብሎ የሚላትን ያዘጋጀው፡፡ “ሊያስደነግጣት
አይገባም፡፡ ግን ደግሞ ልታዝንለት ይገባል። ችግሩን ተረድታ ልትረዳው
ፈቃደኛ መሆን አለባት፡፡ ቀስ ብሎ ማግባባት አለበት፡፡
“ምን መሰለሽ ዘውድዬ.…አለ ቀረብ ብሎ ግራ ክንፏን ያዝ አደረገና፡፡ “ግን አደራ…”
አይ ይሄን ያህል የሚያስጨንቅህ ከሆነ አትንገረኝ፡፡ ምን መሰለህ ከብዬ በሰላም መኖር ስለምፈልግ ብቻ ነው፡፡ ገላዬን ሽጨ የኖርኩት አንሶኝ ተባበርሽ ምንትስዬ ተብዬ ዘብጥያ መውረድ አልፈለግም፡፡ ይገባሃል አይደል?ልጅ አለኝ፡፡ የምወደው የምቀልበው ወንድ ልጅ፡፡ነገ የሚሸረሙጥ” ፈገግ አለች፡፡
ልታስከፋው እንዳልፈለገች ከሁኔታዋ ያስታውቃል፡፡ባለፉት ቀናቶች
ሳይታወቃቸው በመሃላቸው የመግባባት ስሜት ተፈጥሯል፡፡ስሙን ስትጠይቀው 'ከበደ' ብሎ እንደዋሻት ብትረዳም አላስጨነቀችውም፤ ስቃ ተወችው
ተወችው።ተከትለዋት እቤቷ ድረስ መጥተው ተጨማልቀው አጨማልቀዋት
ሳንቲም ወርውረውላት እንደሚሄዱ ደንበኛቿ እንዳልሆነ ግን ተረድታዋለች፡፡
የመጀመሪያው ማታ አብሬሽ
አልተኛም ሲላት ለይስሙላ ነበር የመሰላት፡፡ አጋጥመዎታላ! የገዛ ገንዘባቸውን ከፍለው መጥተው ተለማመጡን የሚሉ፤ ካላንቆለጳጰሳችሁን የሚሉ፤ “ያው የገዛችሁት ዕቃ” ሲባሉ የሚግደረደሩ።
ያን ቀን ማታ በል የውስጥ ልብሴን አቀብለኝ ብላው ያለችውን አቀብሏት : መብራቱን አጥፍቶ ከጎኗ አልጋው ውስጥ ሲገባ ይዘግይ እንጅ ያው እንደ አውሬ ወንድሞቹ የማታ የማታ ዘሎ እንደሚያንቃት አልተጠራጠረችም ነበር፡፡ አልጋዋ ወስጥ ገብቶ በጀርባው ተኝቶ
አንጋለወት እንደሄዱ ህፃን ጣሪያ ጣሪያውን ሲመለከት በጨለማው ውስጥ
ስታየው ደነቃት፣ቢሆንም አላመነችውም፡፡ ዘግይቶ ሊጓጉር ነው ብላ ደህና እደር አለችና በደረቷ ተገልብጣ ተኛች፡፡ እንቅልፍ ሊወስዳት ግን አልቻለም፡፡ ሰውነቷ አላርፍልሽ አላት:: . 'ከአሁን አሁን ዘሎ.. እያለች እላይ እታች የሚለውን ትንፋሹን ተከተለችው::
እንቅልፍ፡ እንዳልወሰደው እርግጠኛ ነበረች፡፡ እንዳሰበችው ሃሳቡን
ሳያቀያር ዘገየባት፡፡ ሲያነቃቃውና በጊዜ ብገላገል ብላ በእንቅልፍ ልቧ
እንዳለች ሁሉ ተወራጨችና በብርድ ልብሱ ውስጥ ክንዷን ሰድዳ አንድ
እጇን ጭኑ ላይ ጣል አደረገችው:: ተፈታተነች፡፡ ሲሸማቀቅ ተሰማት።
እጁን ሰድዶ እጇን ከላዩ ላይ አነሳና በቀስታ እራቅ አድርጎ አስቀመጠው፡፡
በእንቅልፍ ልቧ ያለች ሳይመስለው አልቀረም። ጃውሳው! በጉ! ተረጋጋች፡፡
ሳታውቀው ድብን ያለ አንቅልፍ ይዟት ጭልጥ አለ፡፡
በተከተሉት ቀናት ሳትጠይቀው ቀድሞ የተስማሙበትን የወር የቤት ኪራይ ሂሳብ ሰጣት፡፡ ከዛ በተረፈ ሆቴል እንድታመጣለት ገንዘብ እየሰጣት እራሱን ብቻ ሳይሆን እሷንም እየቀለበ ተቀመጠ፡፡ ተገኝቶ ነው?፡፡ ግን ደግሞ አቤት ብቅ አለማለቱ የተደበቀ ሰው አስመስሎታል፡፡ አንድ ክፍል ቤቷ ውስጥ ዘግቶ መቀመጥ ምን ማለት ነው? . ታዲያ ይና ዝም
ብሎ ማለፍ ይቻላል? እህእ ነገ አንዱ መርቶበት ቢያስይዘው አብራ መውረዷ እደደለም? የተካፈለች አብራ የገመጠች ይመስል ሆ!
“ልክ ነሽ! ልክ ነሽ! ይገባኛልኮ፡፡ ግን ሠርቄ አይደለም፡፡” አላት የያዛቸውን ክንዶቿን ለቆ አልጋው ላይ እየተቀመጠ፡፡
“እሺ ምንድነው ታድያ? ”
“እደው ምን መሰለሽ…” ያጠነጠነውን ይተረትር ጀመር፡፡ አራት ቀን መሉ ብቻውን በሚሆን ሰዓት እየተንጎራደደ ያጠናውን የተለማመደውን ዲስኩር ጀመረ፡፡
“በምስራበት መሥሪያ ቤት ውስጥ ረዳት የሂሣብ ክፍል ኃላፊ ሆኜ ነው የማገለግለው ዘውድዬ እኔ ትዳር ያለኝ ሰው ነኝ፤ የሁለት ልጆች አባት ነኝ:: ነገር አልሻም፤ በሠላም ሰርቼ ከቤቴ መግባት ከባለቤቱና ከልጆቼ ጋር ያገኘሁትን ተቋድሼ ማደር ነው የምሻ:: ምን መሰለሽ…” ትክ ብለው ቁልቁል የሚያዩት አይኖቿ ሰርስረውት ገቡ፡፡ ግንባሩን የምታነብ መሰሰው፡፡ሁለት እጆቹን አንስቶ ለአንድ አፍታ በመዳፎቹ ውስጥ ደበቀው ሰባራ ሳንተም አላነሳሁም ግን
👍3
#የፍቅር_ሰመመን
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ሁለት
፡
፡
#ድርሰት_ሲዲኒ_ሼልደን
፡
፡
#ትርጉም_ብርሃኑ_በላቸው
መርማሪ ፖሊስ ሚክ ጆንሰን ካርተር በርክሌ ውድ ሽሚዙን በደንብ ማኒኩየር በተሰራው ጣቶቹ በደንብ አድርጎ አስተካከለው:: የዶክተር ሮበርትስ
ታካሚ የሆነው የኢንቨስትመንት ባንከሩ ካርተር በርክሌ ሁሉ ነገሩ ውዷ ነው፡፡ ምርጥ መኖሪያ ቤት፣ ምርጥ ምርጥ የቪንቴጅ ጃንዋር ስፖርት መኪኖች እና ሁሉም ቁጭ ያሉበት በምርጥ ሁኔታ ፈርኒሽድ የተደረገው የቤት ውስጥ ቢሮው እራሱ በጣም ውድ ነው፡፡ እንኳን እቃዎቹ ሲያወራ የሚጠቀምባቸው ቃላቶች ሁሉ በጣም የተመረጡ ናቸው፡፡
እዚህ ቢሮ ውስጥ ቁጭ ብለው እያወሩ እያሉ ካርተር ትላንትና ማታ መኝታ ቤቱ ውስጥ የሆነ ሰው ሊያስፈራራው በማሰብ የሞተ አይጥ አስቀምጦ እንደነበር እየነገረው ነበር። የሞተ አይጥን ማስቀመጣቸው የማፍያዎች ማስፈራሪያ ስልት እንደሆነ ጭምር እያስረዳው ነበር፡፡
“ይሄን ነገር ያደረጉት በእርግጥም እኔን ሊያስፈራሩ አስበው ነው፡፡ደግሞም ተሳክቶላቸዋል። ባይገርምህ መርማሪ ፖሊስ ጆንሰን እናንተ ወደ እኔ ባትመጡ እንኳን እኔ እራሴ ጉዳዩን ለማመልከት ወደ እናንተ መምጣቴ አይቀርም ነበር።
ጆንሰንም ራሱን በአዎንታ በመነቅነቅ የቤቱን ዙሪያ ሲመለከት ዕቃዎቹ
በደንብ ከመወልወልም በላይ የመፅሀፍ መደርደሪያው ሼልፍም ራስን
በመገንባት ላይ እና በፋይናንስ ዙሪያ በተፃፉ መፅሀፍት በሥርዓት
ተጠቅጥቀዋል። አሁን ላይ ካርተር በርክሌይን እየተመለከተው ያለው ጆንሰን
ዶክተር ሮበርትስ ስለ ካርተር ከማስታወሻዋ ላይ ከፃፈችው ነገር ጋር
በመስማማቱ ተናደደ፡፡
ጆንሰን ካርተርን አስመልክታ ኒኪ የፃፈችውን ሲያነብ “መቀወሱ
ያልተረጋገጠ በከንቱ ስሜት ውስጥ የሚናውዝ የሜክሲኮ ወንጀለኞች
ሊገድሉት እንደሚያሳድዱት የሚናገር (ለዚህ ምንም ማረጋገጫ የሌለው)
ለረዥም ጊዜ በጭንቀት ውስጥ የኖረ። ምናልባት በልጅነቱ በደረሰበት ስቃይ
ምክንያት ሊሆን ይችላል? (ወይንም ደግሞ ሜክሲኮ ውስጥ በጉርምስናው
ዘመን ኖሯልና ምናልባት እዚያ የሆነ ነገር ተከስቶ ይሆን?) ውስጡ ያላደገ
ቋሚ የሆነ ፆታዊ ግንኙነት የሌለው እና በግንኙነት አብረውት ያሉ ሰዎችንም በጣም አድርጎ የሚቆጣጠር ነው።” ይላል ማስታወሻው፡፡
ዶክተር ሮበርትስ ካርተር በርክሌን የገለፀችበት መንገድ በሙሉ የተቀበለው ቢሆንም አንድ ነገር ረስታለች እሱም “የሰዎች አትኩሮትን (ታይታን) የሚፈልግ ባህሪ ያለው መሆኑ ነው። ይህንን ደግሞ በእሱ ላይ ያላየችው እሷም የዚህ ልክፍት ስላለባት ነው ብሎ አሰበ፡፡ ለዚህም ነው
ካርተር ከዚህ በፊት በተካሄዱት ግድያዎች ውስጥ ዋነኛ ተፈላጊ ሰው መሆኑን ለማሳየት ያጫወተውን የአይጥ ታሪክ ፈጥሮ ለጆንሰን የተናገረው።
ይሄ ቀሽም ሰው ራሱን እንደተፈላጊ ሰው ያያል ወይንም ደግሞ የሆነ እሱ ስለግድያው የሚያውቀውን ነገር እንዳላውጣጣው እያዘናጋኝ ነው
ብሎም አሰበ፡፡
“ቤትህ ውስጥ ጠባቂዎች አሉህ መሰለኝ?” ብሎ ቅድም ወደ ቤቱ ሲገባ
የተመለከታቸውን ብዙም ስልጠና እንደሌላቸው የሚያስታውቁትን የጥበቃ
ሰዎቹን አልፎ እንደገባ አስታውሶ ካርተርን ጠየቀው። ቤቱ ውስጥ ሲገባ ከጠባቂዎቹ ሌላም የሲ.ሲ.ቲቪ
ካሜራዎችንም አይቶዐካሜራዎችንም በየቦታው ገጥመሃል አይደል እንዴ?”
“አዎን ቤቱ ጥበቃ ስለሚያስፈልገው በጠባቂዎችም፣ በካሜራም ነው
የሚጠበቀው። ግን ዋናው መኝታ ቤቴ ውስጥ ካሜራ አልገጠምኩኝም” ብሎ
መለሰለት፡፡
ጆንሰንም “ለምን ዋናው መኝታ ቤትህ ውስጥ ካሜራ አላስገጠምክም?
ብሎ ጠየቀው፡፡
ባንከሩም እንዴት ይሄ አይገባህም በሚል ሀሳብ ይመስል የጎረምሳ ፈገግታ ከለገሰው በኋላ “እዚህ ጋር የተማረ ሰው ግምት ይኖርሃል ብዬ አስባለሁ። ጠባቂዎቼ ከሁሉም ካሜራዎች በቀጥታ መረጃዎች ይደርሳቸዋል።እኔ ደግሞ በግሌ የማደርጋቸውን ነገሮች ማንም እንዲያውቅብኝ አልፈልግም። ለዚያም ስል ነው በዋናው መኝታ ክፍሌ ውስጥ ካሜራ ያላስገጠምኩት፡፡ በሁሉም ወደ ቤቴ በሚያስገቡ በሮች ላይ ካሜራ
ተገጥሞባቸዋል። እሱ ላይ ብቻ ሳይሆን ፎቅ ላይም ካሜራዎችን
አስገጥሜያለሁ። ስለ እዚህ ወደ እዚህ ቤት የሚገባም ሆነ የሚወጣ ሰው
በካሜራው መታየት ይችላል” ብሎ መለሰ፡፡
“መልካም” አለና ጆንሰን በመቀጠልም “የሞተውን አይጥ መኝታ ቤትህ
ተቀምጦ ካገኘህ በኋላ መቼስ ካሜራዎቹ የቀረፁትን ቪዲዩዎች ተመልክተሀቸዋል አይደል?” ብሎ ጠየቀው፡፡
“አዎን አይቻቸዋለሁ”
“ግን ማንም ሰው አላየህም?”
ቤቴ ውስጥ ከሚሰሩ ሰዎች በስተቀር አንድም ሰውን አላየሁም። ይሄ ታዲያ አይገርምም?” ብሎ የሸሚዙን ኮሌታ በሀይል ጎተተው።
“እና እንዴት ነው ይሄ አንተ የማፍያዎች የማስፈራሪያ መንገድ ነው ብለህ ያሰብከውን የሞተውን አይጥ መኝታ ቤትህ ድረስ ሊያስቀምጡ የቻሉት?” ብሎ ጆንሰን ጠየቀ፡፡
ካርተርም ፊቱ ላይ ግራ የመጋባት ፊት እያሳየው “እኔ ይሄንን በምን አውቃለሁ? መርማሪ ፖሊሱ እንግዲህ አንተ ነህ አይደል? አንተው ንገረኝ
እንጂ” ብሎ መለስ፡፡
“እና ቪድዮው ላይ አዲስ ሰው እስካላየህ ድረስ ቤት ውስጥ የሚሰራ
ሰው ነው አይጡን መኝታ ቤትህ ያስቀመጠው ማለት ነው፡፡ አይመስልህም?”ብሎ ጠየቀው እኔ ጋር አለ ብሎ ባልጠበቀው የራሱ ትዕግስት ጭምር እየተገረመ፡፡
“ይሄማ ሊሆን አይችልም፡፡ ምክንያቱም እኔ እነዚህን ሰዎች ስቀጥር
የበፊት ህይወታቸውን በሚገባ አስጠንቼ እና ተጠንቅቄ ነው፡፡ ስለሆነም
አሁን አንተ የተናገርከው ነገር ሊሆን አይችልም...”
ብሎ ያሰበውን ነገር ተናግሮ ሳይጨርስ ጆንሰን አቋረጠው እና ምናልባት አይጡን ልታሳየኝ ትችላለህ? ስለዚህ አይጡን አንስቼ ምርመራ እንዲደረግበት ማድረግ እችላለሁ” አለው ከወንበሩ ላይ ተነሳ፡፡
“አይጡን ላሳይህ አልችልም” ብሎ መለሰለት፡፡ ጆንሰንም የካርተርን
መልስ ሲሰማ ዶክተር ሮበርትስ “ዝም ብሎ የቅዠት ሀሳብ የሚፈጥር ብላ
የተናገረችው ነገር ትክክል እንደሆነ አወቀ።
ለምንድነው አይጡን የማታሳየኝ?” ብሎ ኮስተር ብሎ ጠየቀው እና ለእንደዚህ አይነት ሰው ዶክተር ሮበርትስ እንዴት በየቀኑ የቴራፒስት ህክምና ልትሰጥ እንደምትችል ራሱን ጠየቀ፡፡ እንደዚህ አይነቶቹ ቴራፒስቶች አፍንጫቸው መመታት የለበትም ታዲያ?
“ትላንትና ማታ ነው አይጡን ያገኘሁት እሱን ደግሞ ነግሬሀለሁ አይደል?” ብሎ ካርተር ክርክሩን በመቀጠል “ቤቴን የምታፀዳው ሴት ደግሞ እስከጠዋቱ ሁለት ሰዓት ድረስ አልመጣችም ነበር፡፡ እሷ እስክትመጣ ድረስ ደግሞ አይጡን ክፍሌ ውስጥ ልተወው አልችልም፡፡ ምክንያቱም አይጡ ምን አይነት በሽታ ይዞ እንደመጣ ማንም አያውቅም፡፡” ብሎ መለሰለት።
“እና መረጃ የሚሆነንን ነገር ነው የጣልከው?”
“መጣል ነበረብኝ”
“አይጡን ከክፍልህ ስታስወግድ ያየህ ሰው አለ?”
የለም ያው እንዳልኩህ በጣም መሽቶ ነበር” ብሎ ሲመልስለት የጆንሰን
ትዕግስት ተሟጥጦ ስላለቀ አሁንም ከተቀመጠበት ወንበር ላይ ተነሳ፡፡
የታለ ቆሻሻ የምትጥልበት የቆሻሻ ማስቀመጫህ? ምናልባት አይጡ
እዚያው ቆሻሻ መጣያው ውስጥ ይኖር ይሆናል ይሄኔ” አለው ጆንሰን
ይህንን የጆንሰን ጥያቄ ሲሰማ ቢያንስ ካርተር ማፈር ነበረበት፤ ግን እሱ
ይበልጥ ድርቅ ብሎ “አሁን ላይ በእርግጠኝነት ባዶ ነው የሚሆኑት። ቆሻሻ የሚሰበስቡ ሰዎች ዛሬ በጠዋት ነው ያለወትሮ የመጡት። ያንን አስቢ
አይጡን ሌላ ቦታ ማስቀመጥ ነበረብኝ፡፡ ወይም በጣም ነው ያጠፋሁት.”ጆንሰን ወደ ዋናው የፖሊስ ማዘዣ ጣቢያ ለመመለስ መኪናውን በተጨናነቀ መንገድ ላይ ሲያሽከረክር ከአንድ ሰዓት በላይ ፈጅቶበታል ጣቢያውም የደረሰው በሚያስጠላ
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ሁለት
፡
፡
#ድርሰት_ሲዲኒ_ሼልደን
፡
፡
#ትርጉም_ብርሃኑ_በላቸው
መርማሪ ፖሊስ ሚክ ጆንሰን ካርተር በርክሌ ውድ ሽሚዙን በደንብ ማኒኩየር በተሰራው ጣቶቹ በደንብ አድርጎ አስተካከለው:: የዶክተር ሮበርትስ
ታካሚ የሆነው የኢንቨስትመንት ባንከሩ ካርተር በርክሌ ሁሉ ነገሩ ውዷ ነው፡፡ ምርጥ መኖሪያ ቤት፣ ምርጥ ምርጥ የቪንቴጅ ጃንዋር ስፖርት መኪኖች እና ሁሉም ቁጭ ያሉበት በምርጥ ሁኔታ ፈርኒሽድ የተደረገው የቤት ውስጥ ቢሮው እራሱ በጣም ውድ ነው፡፡ እንኳን እቃዎቹ ሲያወራ የሚጠቀምባቸው ቃላቶች ሁሉ በጣም የተመረጡ ናቸው፡፡
እዚህ ቢሮ ውስጥ ቁጭ ብለው እያወሩ እያሉ ካርተር ትላንትና ማታ መኝታ ቤቱ ውስጥ የሆነ ሰው ሊያስፈራራው በማሰብ የሞተ አይጥ አስቀምጦ እንደነበር እየነገረው ነበር። የሞተ አይጥን ማስቀመጣቸው የማፍያዎች ማስፈራሪያ ስልት እንደሆነ ጭምር እያስረዳው ነበር፡፡
“ይሄን ነገር ያደረጉት በእርግጥም እኔን ሊያስፈራሩ አስበው ነው፡፡ደግሞም ተሳክቶላቸዋል። ባይገርምህ መርማሪ ፖሊስ ጆንሰን እናንተ ወደ እኔ ባትመጡ እንኳን እኔ እራሴ ጉዳዩን ለማመልከት ወደ እናንተ መምጣቴ አይቀርም ነበር።
ጆንሰንም ራሱን በአዎንታ በመነቅነቅ የቤቱን ዙሪያ ሲመለከት ዕቃዎቹ
በደንብ ከመወልወልም በላይ የመፅሀፍ መደርደሪያው ሼልፍም ራስን
በመገንባት ላይ እና በፋይናንስ ዙሪያ በተፃፉ መፅሀፍት በሥርዓት
ተጠቅጥቀዋል። አሁን ላይ ካርተር በርክሌይን እየተመለከተው ያለው ጆንሰን
ዶክተር ሮበርትስ ስለ ካርተር ከማስታወሻዋ ላይ ከፃፈችው ነገር ጋር
በመስማማቱ ተናደደ፡፡
ጆንሰን ካርተርን አስመልክታ ኒኪ የፃፈችውን ሲያነብ “መቀወሱ
ያልተረጋገጠ በከንቱ ስሜት ውስጥ የሚናውዝ የሜክሲኮ ወንጀለኞች
ሊገድሉት እንደሚያሳድዱት የሚናገር (ለዚህ ምንም ማረጋገጫ የሌለው)
ለረዥም ጊዜ በጭንቀት ውስጥ የኖረ። ምናልባት በልጅነቱ በደረሰበት ስቃይ
ምክንያት ሊሆን ይችላል? (ወይንም ደግሞ ሜክሲኮ ውስጥ በጉርምስናው
ዘመን ኖሯልና ምናልባት እዚያ የሆነ ነገር ተከስቶ ይሆን?) ውስጡ ያላደገ
ቋሚ የሆነ ፆታዊ ግንኙነት የሌለው እና በግንኙነት አብረውት ያሉ ሰዎችንም በጣም አድርጎ የሚቆጣጠር ነው።” ይላል ማስታወሻው፡፡
ዶክተር ሮበርትስ ካርተር በርክሌን የገለፀችበት መንገድ በሙሉ የተቀበለው ቢሆንም አንድ ነገር ረስታለች እሱም “የሰዎች አትኩሮትን (ታይታን) የሚፈልግ ባህሪ ያለው መሆኑ ነው። ይህንን ደግሞ በእሱ ላይ ያላየችው እሷም የዚህ ልክፍት ስላለባት ነው ብሎ አሰበ፡፡ ለዚህም ነው
ካርተር ከዚህ በፊት በተካሄዱት ግድያዎች ውስጥ ዋነኛ ተፈላጊ ሰው መሆኑን ለማሳየት ያጫወተውን የአይጥ ታሪክ ፈጥሮ ለጆንሰን የተናገረው።
ይሄ ቀሽም ሰው ራሱን እንደተፈላጊ ሰው ያያል ወይንም ደግሞ የሆነ እሱ ስለግድያው የሚያውቀውን ነገር እንዳላውጣጣው እያዘናጋኝ ነው
ብሎም አሰበ፡፡
“ቤትህ ውስጥ ጠባቂዎች አሉህ መሰለኝ?” ብሎ ቅድም ወደ ቤቱ ሲገባ
የተመለከታቸውን ብዙም ስልጠና እንደሌላቸው የሚያስታውቁትን የጥበቃ
ሰዎቹን አልፎ እንደገባ አስታውሶ ካርተርን ጠየቀው። ቤቱ ውስጥ ሲገባ ከጠባቂዎቹ ሌላም የሲ.ሲ.ቲቪ
ካሜራዎችንም አይቶዐካሜራዎችንም በየቦታው ገጥመሃል አይደል እንዴ?”
“አዎን ቤቱ ጥበቃ ስለሚያስፈልገው በጠባቂዎችም፣ በካሜራም ነው
የሚጠበቀው። ግን ዋናው መኝታ ቤቴ ውስጥ ካሜራ አልገጠምኩኝም” ብሎ
መለሰለት፡፡
ጆንሰንም “ለምን ዋናው መኝታ ቤትህ ውስጥ ካሜራ አላስገጠምክም?
ብሎ ጠየቀው፡፡
ባንከሩም እንዴት ይሄ አይገባህም በሚል ሀሳብ ይመስል የጎረምሳ ፈገግታ ከለገሰው በኋላ “እዚህ ጋር የተማረ ሰው ግምት ይኖርሃል ብዬ አስባለሁ። ጠባቂዎቼ ከሁሉም ካሜራዎች በቀጥታ መረጃዎች ይደርሳቸዋል።እኔ ደግሞ በግሌ የማደርጋቸውን ነገሮች ማንም እንዲያውቅብኝ አልፈልግም። ለዚያም ስል ነው በዋናው መኝታ ክፍሌ ውስጥ ካሜራ ያላስገጠምኩት፡፡ በሁሉም ወደ ቤቴ በሚያስገቡ በሮች ላይ ካሜራ
ተገጥሞባቸዋል። እሱ ላይ ብቻ ሳይሆን ፎቅ ላይም ካሜራዎችን
አስገጥሜያለሁ። ስለ እዚህ ወደ እዚህ ቤት የሚገባም ሆነ የሚወጣ ሰው
በካሜራው መታየት ይችላል” ብሎ መለሰ፡፡
“መልካም” አለና ጆንሰን በመቀጠልም “የሞተውን አይጥ መኝታ ቤትህ
ተቀምጦ ካገኘህ በኋላ መቼስ ካሜራዎቹ የቀረፁትን ቪዲዩዎች ተመልክተሀቸዋል አይደል?” ብሎ ጠየቀው፡፡
“አዎን አይቻቸዋለሁ”
“ግን ማንም ሰው አላየህም?”
ቤቴ ውስጥ ከሚሰሩ ሰዎች በስተቀር አንድም ሰውን አላየሁም። ይሄ ታዲያ አይገርምም?” ብሎ የሸሚዙን ኮሌታ በሀይል ጎተተው።
“እና እንዴት ነው ይሄ አንተ የማፍያዎች የማስፈራሪያ መንገድ ነው ብለህ ያሰብከውን የሞተውን አይጥ መኝታ ቤትህ ድረስ ሊያስቀምጡ የቻሉት?” ብሎ ጆንሰን ጠየቀ፡፡
ካርተርም ፊቱ ላይ ግራ የመጋባት ፊት እያሳየው “እኔ ይሄንን በምን አውቃለሁ? መርማሪ ፖሊሱ እንግዲህ አንተ ነህ አይደል? አንተው ንገረኝ
እንጂ” ብሎ መለስ፡፡
“እና ቪድዮው ላይ አዲስ ሰው እስካላየህ ድረስ ቤት ውስጥ የሚሰራ
ሰው ነው አይጡን መኝታ ቤትህ ያስቀመጠው ማለት ነው፡፡ አይመስልህም?”ብሎ ጠየቀው እኔ ጋር አለ ብሎ ባልጠበቀው የራሱ ትዕግስት ጭምር እየተገረመ፡፡
“ይሄማ ሊሆን አይችልም፡፡ ምክንያቱም እኔ እነዚህን ሰዎች ስቀጥር
የበፊት ህይወታቸውን በሚገባ አስጠንቼ እና ተጠንቅቄ ነው፡፡ ስለሆነም
አሁን አንተ የተናገርከው ነገር ሊሆን አይችልም...”
ብሎ ያሰበውን ነገር ተናግሮ ሳይጨርስ ጆንሰን አቋረጠው እና ምናልባት አይጡን ልታሳየኝ ትችላለህ? ስለዚህ አይጡን አንስቼ ምርመራ እንዲደረግበት ማድረግ እችላለሁ” አለው ከወንበሩ ላይ ተነሳ፡፡
“አይጡን ላሳይህ አልችልም” ብሎ መለሰለት፡፡ ጆንሰንም የካርተርን
መልስ ሲሰማ ዶክተር ሮበርትስ “ዝም ብሎ የቅዠት ሀሳብ የሚፈጥር ብላ
የተናገረችው ነገር ትክክል እንደሆነ አወቀ።
ለምንድነው አይጡን የማታሳየኝ?” ብሎ ኮስተር ብሎ ጠየቀው እና ለእንደዚህ አይነት ሰው ዶክተር ሮበርትስ እንዴት በየቀኑ የቴራፒስት ህክምና ልትሰጥ እንደምትችል ራሱን ጠየቀ፡፡ እንደዚህ አይነቶቹ ቴራፒስቶች አፍንጫቸው መመታት የለበትም ታዲያ?
“ትላንትና ማታ ነው አይጡን ያገኘሁት እሱን ደግሞ ነግሬሀለሁ አይደል?” ብሎ ካርተር ክርክሩን በመቀጠል “ቤቴን የምታፀዳው ሴት ደግሞ እስከጠዋቱ ሁለት ሰዓት ድረስ አልመጣችም ነበር፡፡ እሷ እስክትመጣ ድረስ ደግሞ አይጡን ክፍሌ ውስጥ ልተወው አልችልም፡፡ ምክንያቱም አይጡ ምን አይነት በሽታ ይዞ እንደመጣ ማንም አያውቅም፡፡” ብሎ መለሰለት።
“እና መረጃ የሚሆነንን ነገር ነው የጣልከው?”
“መጣል ነበረብኝ”
“አይጡን ከክፍልህ ስታስወግድ ያየህ ሰው አለ?”
የለም ያው እንዳልኩህ በጣም መሽቶ ነበር” ብሎ ሲመልስለት የጆንሰን
ትዕግስት ተሟጥጦ ስላለቀ አሁንም ከተቀመጠበት ወንበር ላይ ተነሳ፡፡
የታለ ቆሻሻ የምትጥልበት የቆሻሻ ማስቀመጫህ? ምናልባት አይጡ
እዚያው ቆሻሻ መጣያው ውስጥ ይኖር ይሆናል ይሄኔ” አለው ጆንሰን
ይህንን የጆንሰን ጥያቄ ሲሰማ ቢያንስ ካርተር ማፈር ነበረበት፤ ግን እሱ
ይበልጥ ድርቅ ብሎ “አሁን ላይ በእርግጠኝነት ባዶ ነው የሚሆኑት። ቆሻሻ የሚሰበስቡ ሰዎች ዛሬ በጠዋት ነው ያለወትሮ የመጡት። ያንን አስቢ
አይጡን ሌላ ቦታ ማስቀመጥ ነበረብኝ፡፡ ወይም በጣም ነው ያጠፋሁት.”ጆንሰን ወደ ዋናው የፖሊስ ማዘዣ ጣቢያ ለመመለስ መኪናውን በተጨናነቀ መንገድ ላይ ሲያሽከረክር ከአንድ ሰዓት በላይ ፈጅቶበታል ጣቢያውም የደረሰው በሚያስጠላ
👍2