#በፍቅር_ላይ_ሾተላይ
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ሰባት
፡
፡
#ድርሰት_በትክክል_ገና
....መንፈሷ ላይድን ቆስሎ፧ ሃሣቧ እዚህም እዚያም እየባከነ፤በተኛችበት ሆና በእንባ እየታጠበች ሁለት ቀን በጓደኛዋ ቤት ካሳለፈች በኋላ፤ ተነሣች፡፡
አካሏ ጠንካራ ቢመስልም፤ መንፈሷ ግን ደካማና የተረበሽ ነበር።በዚህች በሁለት ቀን ውስጥ ከዚህ ዓለም የተገለለች ዓይነት ሰሜት ይስማታል፡፡
የእናቷ፡ የወንድሟና፤ የሻምበል ብሩክ ሁኔታ ከፊቷ ድቅን ይልባታል፡፡
እናቷን ለሁለት ቀን ሳታያት በመቅረቷ ሁለት ዓመት የተለያቻት ያህል በናፍቆት ተቃጥላለች፡፡
“እንዴት ሆና ይሆን?” እያለች ሌሊቱን ስትጨነቅ ነው ያደረችው፡፡እናቷን በህልሟ አይታታለች፡፡ በዚያው ጐን ለጐን የሻምበል ብሩክ ጉዳይ አለ፡፡ ዛሬ እሁድ ስለሆነ ሻምበል ብሩክ እየጠበቃት ነው፡፡ ስለዚህ እሱን ማግኘት አለባት፡፡ ካላየችው ጤነኛ የምትሆን አልመሰላትም፡፡ልቧ ከውስጥ ደም ቢያለቅስም፤ ጥርሶቿ ግን እውነተኛ ስሜቷን በመደበቃቸው፤አዜብ ተጽናናች፡፡
“በቃ እንሂድ”አለቻት ለአዜብ ልብሷን ለባብሳ እንደጨረሰች፡፡
እሺ ትሁት፡፡ መጣሁ ጠብቂኝ” አለችና ሄዳ የታክሲ ገንዘብ ይዛ መጣች፡፡ ከቤት ሲወጡ ከቀኑ ስምንት ሰዓት ተኩል ሆኖ ነበር፡፡ ዕለቱ እሁድ ነው :: ተያይዘው በታክሲ ወደ የካቲት አስራ ሁለት ሆስፒታል በረሩ...
በዚህ ቀን ሻምበል ብሩክ ከአሁን አሁን ትመጣለች በማለት በጉጉት እየተጠባበቃት ነበር፡፡ ትዕግስት መራራ ነች ፍሬዋ ግን ጣፋጭ ነው የሚለውን ብሂል በሃሣቡ እያውጠነጠነ ፣ትዕግስት አልባ በመሆን ስህተት እንዳይፈጽም ከራሱ ጋር እየተሟገተ ይገኛል፡፡
ከዚህ በፊት ከትዕግስት ውጭ በመሆን ከሱ የማይጠበቅ ድርጊት በመፈጸሙ ተፀፅቶ፤ ለራሱ የገባውን ቃል ዘነጋና፤ ባለፈው ስልክ የደወለችለት ዕለት፤ በድጋሚ ስህተት ፈጸመ፡፡በዚያን ሰዓት ትህትና በሁኔታው ተደናግጣ...
ምን ሆነሃል ብሩኬ?“ ነበር ያለችው፡፡ በአነጋገሩ የድሮው ሻምበል ብሩክ መሆኑ ፍጹም አጠራጥሯት፡፡
ሻምበል ብሩክ እንደበረዶ ቀዝቅዞ ነበር ያነጋገራት :: ይህንን ስህተት መፈጸሙን ያወቀው ግን ስልኩን ከዘጋ በኋላ ነው፡፡
ስልኩን አንስቶ ሲያነጋግራትና፤ሲሰናበታት በነበረው ሁኔታ ተደናግጣ ተደናግጣ “ምን ሆነብኝ?“ በማለት ተጨንቃ፤ ምን እንዳጋጠመው ለማወቅ ፤ እሁድ
አልደርስልሽ አላት፡፡ ሻምበል ብሩክም ስልኩን ከዘጋ በኋላ ምን ያደርግ እንደነበር ሲረዳ ተደናገጠና፤ የሚይዝ የሚጨብጠው ጠፋው፡፡
“ ምን ዐይነት እራሴን መቆጣጠር የማልችል ደደብ ነኝ?” ሲል በራሱ አማረረ
"እሺ አሁን ምን ይሻላል?“ በሚል ጭንቀት ተውጦ ለፈፀመው ስህተት ምክንያት ሲፈልግ አንድ ሃሣብ መጣለት፡፡
ሻምበል ስሜቱ በሁለት ተቃራኒዎች መካከል መዋዠቅ ጀምሯል፡፡ወደር የሌለው ፍቅር በአንድ በኩል፤ የጥላቻ ስሜት በሌላ በኩልእንደከበሮ ወጥረው ይሞግቱታል፡፡
በቃላት ሊገልጸው በማይችለው ሁኔታ ያፈቅራታል፡፡ የዚያን ዕለቱ ከዶክተር ባይከዳኝ ጋር እጅ ለእጅ ተቆላልፋ ወደ ቤቱ ይዟት ሲገባ የነበረው ሁኔታዋ
ከፊቱ ላይ ድቅን ሲልበት ደግሞ፤ ከአንጀቱ ይጠላታል፡፡
ለማንኛውም ይህ ፍቅሩ ጥላቻውን የሚያጠፋበት፣አሊያም ጥላቻው
ፍቅሩን ከውስጡ ጠራርጉ የሚያስወግድበት፤ እውነተኛው ሰዓት
እስከሚደርስ ድረስ በትዕግስት ለመቆየትና የዚያ የውሽት ልጃገረድነት
ጭምብል ወልቆ እውነተኛው ማንነቷ የሚረጋገጥበትን ጊዜ በጉጉት
መጠባበቁን መረጠ፡፡
በሱ እምነትና ግምት ያ ቀን እሁድ እለት እንዲሆን ወስኗል፡፡ሻምበል እሁድ ዕለት ደርሶለት ይሄ ጥርጣሬና ጥላቻው አንድም የሚወገድበት፤አሊያም ከትህትና ጋር የሚቆራረጥበት ዕለት በመሆኑ የአሁኑ እሁድ ከምንግዜውም የበለጠ ናፈቀው፡፡
ትህትና ደግሞ በበኩሏ ሻምበል ብሩክ እንደዚያ ቅዝቅዝ ብሎና ተለውጦ በስልክ ሲያነጋግራት ተረብሻ፣የመገናኛቸው ዕለት ደርሶላት ሄዳ ምን እንደሆነ እስከምትጠይቀው ድረስ ቸኩላ፤ እሁድን እየተጠባበቀች ነበር፡፡
ሁለት ልቦች በየግል ምክንያቶቻቸውን አምቀው፤ ሰዓቱን በመጠባበቅ ላይ ቢሆኑም፤ ሰዎች በፈለጉት መንገድ ሳይሆን፤ ጊዜ በራሱ ህግና ስርዓት የሚመራ ነውና፤ እሁድ የራሱን አዲስ ክስተት ይዞ ብቅ አለ፡፡
ሰው በጊዜ ቢያቅድም ጊዜ የሰው ተጐታች አይደለምና የታቀደ ሁሉ
አይሳካም :: በተገላቢጦሽ ደግሞ ሰው የጊዜ ተጉታች ነውና፤ አንዳንድ የሰዎች ዕቅድ ጊዜው ካልፈቀደ በዕቅድነቱ ይቀርና ጊዜ የራሱን አዲስ ክስተት ይዞ ይመጣል፡፡
ትህትና ድንበሩ በአበራና በአለሌው እንደሻው አማካይነት በተቀነባበረ ሴራ፤ በአካሏ ላይ ጉዳት ስለደረሰባትና ፤በቀሪ ህይወቷ ላይ ጥቁር ነጥብ የሚጥል ወንጀል ስለተለፈፀመባት፤ በናፍቆት የተጠባበቀችው እሁድ ቢመጣም ያ ቀን ከደረሰባት ዱላና አስገዳጅ የግብረ ሥጋ ግንኙነት ጉዳት ያገገመችበት ቀን ሆኖ ዋለ፡፡
እንደዚያ የምታፈቅረው ጓደኛዋ ናፍቋት፤ እናቷን ለሁለት ቀናት ያህል ስትለያት የምታደርገው ጠፍቷት፤ በእንባ እየታጠበች በዚያች በሁለት ቀን ውስጥ ወዟ ምጥጥ ብሎ፤ አካሏ ጠውልጉና ውበቷ ተገፍፎ ስትታይ፤ ትህትና ነች ብሎ ለመናገር አስቸጋሪ ነበር፡፡ውበት የስሜት
ነጸብራቅ የመሆኑ እውነታ ከፊቷ ይነበብ ነበር፡፡
ለዚያውም አዜብ ከአጠገቧ ሳትለይ በማንኛውም ረገድ ባታፅናናትና
ባትንከባከባት ኖሮ፤ ጉዳቷ ከዚህም የከፋ ይሆን ነበር፡፡ከዚህ ሁሉ በኋላ በሁለተኛው ቀን ላይ ሰውነቷን ተጣጥባ፤ በቅባት ፊቷን አባብሳ፤ የአዜብን ምርጥ ቀሚስ ለብሳ ፤ ሰው መስላ ተነሣች፡፡
ሞራሏ እንዳይነካና ያለፈውን እንድትረሣ አዜብ ያላደረገችላት ጥረት አልነበረም፡፡ ትህትናም ጓደኛዋን ለማስደሰት ያህል ብቻ ልቧ ከውስጥ ደም እያለቀስ፤ ከላይ ከላይ ፈገግታ እያሳየቻት ተነሳች፡፡
በተለይም በዚያን ዕለት ጨረቃዋ በመኝታ ክፍላቸው ውስጥ ብርሃኗን ስትፈነጥቅ፤ ከሻምበል ብሩክ ጋር ባሳለፈችው አስደሳች ምሽት የተናገረችው ትዝ ይላትና እረፍት ይነሳታል፡፡ ያንን የሚያሰቃይ ስሜቷን ውጣ በፍጹም ጤነኛና ደሰተኛ መስላ ልብሷን ለባብሳ እንደጨረሰች...
"እንሂድ አዜቢና” አለቻት፡፡
እናቷ ይህችን ሁለት ቀን ልጇ ሳትመጣ በመቅረቷ እዚያ ሆስፒታል ውስጥ በእንባ እየታጠበች አንዱአለምን ካልወለድካት እያለች ስታስጨንቀው፤ በሁለተኛው ቀን ላይ የት እንዳለች ቁርጡን ነገራት፡፡
አንዱዓለም እህቱ የት እንዳለች የሰማው ከአዜብ ነው፡፡
• ትሁት ሻምበል ጋ ነች፡፡ ሁለት ቀን እዚያ ስለምትቆይ አንተ ከእናትህ እንዳትለይ አደራህን” ብላ በሚስጥር ስለነገረችው፤ አንዱአለም ዜናውን በደስታ ተቀብሎ ለደቂቃ ከእናቱ እንደማይለይ በገባላት ቃል መሠረት ከዚያ አካባቢ ውልፍት ሳይል ነው የቆየው፡፡
ትህትና በዚህች በሁለት ቀን ውስጥ ሁለት ዓመት እንደተለያቻች ሁሉ ናፍቃት፤ ሆስፒታል ስትደርስ እየሮጠች ሄዳ እናቷ ላይ ድፍት ብላ አለቀሰች፡፡ አዜብ የጓደኛዋን ሁኔታ ስትመለከት አንጀቷ ተላወሰ፡፡አልቻለችም፡፡ አብራት አለቀሰች፡፡
እናቷም ልጇ ላይ ጥምጥም ብላ በስስት እያገላበጠች ሣመቻትና..
በጤናሽ ነው ትሁቴ? አለሽልኝ የኔ እናት? ” ዐይን ዐይኖቿን በጉጉት እያየች፡፡
“ደህና ነኝ እማይዬ አንቺስ እንዴት ነሽ?” እናቷን እያሻሸች በዐይኗ አንዱአለምን ስትፈልግ እሱም የሆነ ነገር ሊነግራት ፈልጐ ምልክት ሲሰጣት አየችና ልትስመው ሄደች.....
“ሻምበል ጋ እንደነበርሽ ነግሬአታለሁ” አላት ድምፁን ዝቅ አድርጉ፡፡
ትንሽ ሣቅ ብላ......
“እሺ" አለችው::
ከዚያም በኋላ ከእናቷ አጠገብ የተኙትን በሽተኛ አዛውንት ጤንነታቸውን ጠይቀው፣ እናቷን ከበው ተቀመጡ፡፡ እናቷ የልጇን
ዐይን፤ዐይን፤በስስት ስትመለከት ሆዷ ቡጭ ቡጭ
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ሰባት
፡
፡
#ድርሰት_በትክክል_ገና
....መንፈሷ ላይድን ቆስሎ፧ ሃሣቧ እዚህም እዚያም እየባከነ፤በተኛችበት ሆና በእንባ እየታጠበች ሁለት ቀን በጓደኛዋ ቤት ካሳለፈች በኋላ፤ ተነሣች፡፡
አካሏ ጠንካራ ቢመስልም፤ መንፈሷ ግን ደካማና የተረበሽ ነበር።በዚህች በሁለት ቀን ውስጥ ከዚህ ዓለም የተገለለች ዓይነት ሰሜት ይስማታል፡፡
የእናቷ፡ የወንድሟና፤ የሻምበል ብሩክ ሁኔታ ከፊቷ ድቅን ይልባታል፡፡
እናቷን ለሁለት ቀን ሳታያት በመቅረቷ ሁለት ዓመት የተለያቻት ያህል በናፍቆት ተቃጥላለች፡፡
“እንዴት ሆና ይሆን?” እያለች ሌሊቱን ስትጨነቅ ነው ያደረችው፡፡እናቷን በህልሟ አይታታለች፡፡ በዚያው ጐን ለጐን የሻምበል ብሩክ ጉዳይ አለ፡፡ ዛሬ እሁድ ስለሆነ ሻምበል ብሩክ እየጠበቃት ነው፡፡ ስለዚህ እሱን ማግኘት አለባት፡፡ ካላየችው ጤነኛ የምትሆን አልመሰላትም፡፡ልቧ ከውስጥ ደም ቢያለቅስም፤ ጥርሶቿ ግን እውነተኛ ስሜቷን በመደበቃቸው፤አዜብ ተጽናናች፡፡
“በቃ እንሂድ”አለቻት ለአዜብ ልብሷን ለባብሳ እንደጨረሰች፡፡
እሺ ትሁት፡፡ መጣሁ ጠብቂኝ” አለችና ሄዳ የታክሲ ገንዘብ ይዛ መጣች፡፡ ከቤት ሲወጡ ከቀኑ ስምንት ሰዓት ተኩል ሆኖ ነበር፡፡ ዕለቱ እሁድ ነው :: ተያይዘው በታክሲ ወደ የካቲት አስራ ሁለት ሆስፒታል በረሩ...
በዚህ ቀን ሻምበል ብሩክ ከአሁን አሁን ትመጣለች በማለት በጉጉት እየተጠባበቃት ነበር፡፡ ትዕግስት መራራ ነች ፍሬዋ ግን ጣፋጭ ነው የሚለውን ብሂል በሃሣቡ እያውጠነጠነ ፣ትዕግስት አልባ በመሆን ስህተት እንዳይፈጽም ከራሱ ጋር እየተሟገተ ይገኛል፡፡
ከዚህ በፊት ከትዕግስት ውጭ በመሆን ከሱ የማይጠበቅ ድርጊት በመፈጸሙ ተፀፅቶ፤ ለራሱ የገባውን ቃል ዘነጋና፤ ባለፈው ስልክ የደወለችለት ዕለት፤ በድጋሚ ስህተት ፈጸመ፡፡በዚያን ሰዓት ትህትና በሁኔታው ተደናግጣ...
ምን ሆነሃል ብሩኬ?“ ነበር ያለችው፡፡ በአነጋገሩ የድሮው ሻምበል ብሩክ መሆኑ ፍጹም አጠራጥሯት፡፡
ሻምበል ብሩክ እንደበረዶ ቀዝቅዞ ነበር ያነጋገራት :: ይህንን ስህተት መፈጸሙን ያወቀው ግን ስልኩን ከዘጋ በኋላ ነው፡፡
ስልኩን አንስቶ ሲያነጋግራትና፤ሲሰናበታት በነበረው ሁኔታ ተደናግጣ ተደናግጣ “ምን ሆነብኝ?“ በማለት ተጨንቃ፤ ምን እንዳጋጠመው ለማወቅ ፤ እሁድ
አልደርስልሽ አላት፡፡ ሻምበል ብሩክም ስልኩን ከዘጋ በኋላ ምን ያደርግ እንደነበር ሲረዳ ተደናገጠና፤ የሚይዝ የሚጨብጠው ጠፋው፡፡
“ ምን ዐይነት እራሴን መቆጣጠር የማልችል ደደብ ነኝ?” ሲል በራሱ አማረረ
"እሺ አሁን ምን ይሻላል?“ በሚል ጭንቀት ተውጦ ለፈፀመው ስህተት ምክንያት ሲፈልግ አንድ ሃሣብ መጣለት፡፡
ሻምበል ስሜቱ በሁለት ተቃራኒዎች መካከል መዋዠቅ ጀምሯል፡፡ወደር የሌለው ፍቅር በአንድ በኩል፤ የጥላቻ ስሜት በሌላ በኩልእንደከበሮ ወጥረው ይሞግቱታል፡፡
በቃላት ሊገልጸው በማይችለው ሁኔታ ያፈቅራታል፡፡ የዚያን ዕለቱ ከዶክተር ባይከዳኝ ጋር እጅ ለእጅ ተቆላልፋ ወደ ቤቱ ይዟት ሲገባ የነበረው ሁኔታዋ
ከፊቱ ላይ ድቅን ሲልበት ደግሞ፤ ከአንጀቱ ይጠላታል፡፡
ለማንኛውም ይህ ፍቅሩ ጥላቻውን የሚያጠፋበት፣አሊያም ጥላቻው
ፍቅሩን ከውስጡ ጠራርጉ የሚያስወግድበት፤ እውነተኛው ሰዓት
እስከሚደርስ ድረስ በትዕግስት ለመቆየትና የዚያ የውሽት ልጃገረድነት
ጭምብል ወልቆ እውነተኛው ማንነቷ የሚረጋገጥበትን ጊዜ በጉጉት
መጠባበቁን መረጠ፡፡
በሱ እምነትና ግምት ያ ቀን እሁድ እለት እንዲሆን ወስኗል፡፡ሻምበል እሁድ ዕለት ደርሶለት ይሄ ጥርጣሬና ጥላቻው አንድም የሚወገድበት፤አሊያም ከትህትና ጋር የሚቆራረጥበት ዕለት በመሆኑ የአሁኑ እሁድ ከምንግዜውም የበለጠ ናፈቀው፡፡
ትህትና ደግሞ በበኩሏ ሻምበል ብሩክ እንደዚያ ቅዝቅዝ ብሎና ተለውጦ በስልክ ሲያነጋግራት ተረብሻ፣የመገናኛቸው ዕለት ደርሶላት ሄዳ ምን እንደሆነ እስከምትጠይቀው ድረስ ቸኩላ፤ እሁድን እየተጠባበቀች ነበር፡፡
ሁለት ልቦች በየግል ምክንያቶቻቸውን አምቀው፤ ሰዓቱን በመጠባበቅ ላይ ቢሆኑም፤ ሰዎች በፈለጉት መንገድ ሳይሆን፤ ጊዜ በራሱ ህግና ስርዓት የሚመራ ነውና፤ እሁድ የራሱን አዲስ ክስተት ይዞ ብቅ አለ፡፡
ሰው በጊዜ ቢያቅድም ጊዜ የሰው ተጐታች አይደለምና የታቀደ ሁሉ
አይሳካም :: በተገላቢጦሽ ደግሞ ሰው የጊዜ ተጉታች ነውና፤ አንዳንድ የሰዎች ዕቅድ ጊዜው ካልፈቀደ በዕቅድነቱ ይቀርና ጊዜ የራሱን አዲስ ክስተት ይዞ ይመጣል፡፡
ትህትና ድንበሩ በአበራና በአለሌው እንደሻው አማካይነት በተቀነባበረ ሴራ፤ በአካሏ ላይ ጉዳት ስለደረሰባትና ፤በቀሪ ህይወቷ ላይ ጥቁር ነጥብ የሚጥል ወንጀል ስለተለፈፀመባት፤ በናፍቆት የተጠባበቀችው እሁድ ቢመጣም ያ ቀን ከደረሰባት ዱላና አስገዳጅ የግብረ ሥጋ ግንኙነት ጉዳት ያገገመችበት ቀን ሆኖ ዋለ፡፡
እንደዚያ የምታፈቅረው ጓደኛዋ ናፍቋት፤ እናቷን ለሁለት ቀናት ያህል ስትለያት የምታደርገው ጠፍቷት፤ በእንባ እየታጠበች በዚያች በሁለት ቀን ውስጥ ወዟ ምጥጥ ብሎ፤ አካሏ ጠውልጉና ውበቷ ተገፍፎ ስትታይ፤ ትህትና ነች ብሎ ለመናገር አስቸጋሪ ነበር፡፡ውበት የስሜት
ነጸብራቅ የመሆኑ እውነታ ከፊቷ ይነበብ ነበር፡፡
ለዚያውም አዜብ ከአጠገቧ ሳትለይ በማንኛውም ረገድ ባታፅናናትና
ባትንከባከባት ኖሮ፤ ጉዳቷ ከዚህም የከፋ ይሆን ነበር፡፡ከዚህ ሁሉ በኋላ በሁለተኛው ቀን ላይ ሰውነቷን ተጣጥባ፤ በቅባት ፊቷን አባብሳ፤ የአዜብን ምርጥ ቀሚስ ለብሳ ፤ ሰው መስላ ተነሣች፡፡
ሞራሏ እንዳይነካና ያለፈውን እንድትረሣ አዜብ ያላደረገችላት ጥረት አልነበረም፡፡ ትህትናም ጓደኛዋን ለማስደሰት ያህል ብቻ ልቧ ከውስጥ ደም እያለቀስ፤ ከላይ ከላይ ፈገግታ እያሳየቻት ተነሳች፡፡
በተለይም በዚያን ዕለት ጨረቃዋ በመኝታ ክፍላቸው ውስጥ ብርሃኗን ስትፈነጥቅ፤ ከሻምበል ብሩክ ጋር ባሳለፈችው አስደሳች ምሽት የተናገረችው ትዝ ይላትና እረፍት ይነሳታል፡፡ ያንን የሚያሰቃይ ስሜቷን ውጣ በፍጹም ጤነኛና ደሰተኛ መስላ ልብሷን ለባብሳ እንደጨረሰች...
"እንሂድ አዜቢና” አለቻት፡፡
እናቷ ይህችን ሁለት ቀን ልጇ ሳትመጣ በመቅረቷ እዚያ ሆስፒታል ውስጥ በእንባ እየታጠበች አንዱአለምን ካልወለድካት እያለች ስታስጨንቀው፤ በሁለተኛው ቀን ላይ የት እንዳለች ቁርጡን ነገራት፡፡
አንዱዓለም እህቱ የት እንዳለች የሰማው ከአዜብ ነው፡፡
• ትሁት ሻምበል ጋ ነች፡፡ ሁለት ቀን እዚያ ስለምትቆይ አንተ ከእናትህ እንዳትለይ አደራህን” ብላ በሚስጥር ስለነገረችው፤ አንዱአለም ዜናውን በደስታ ተቀብሎ ለደቂቃ ከእናቱ እንደማይለይ በገባላት ቃል መሠረት ከዚያ አካባቢ ውልፍት ሳይል ነው የቆየው፡፡
ትህትና በዚህች በሁለት ቀን ውስጥ ሁለት ዓመት እንደተለያቻች ሁሉ ናፍቃት፤ ሆስፒታል ስትደርስ እየሮጠች ሄዳ እናቷ ላይ ድፍት ብላ አለቀሰች፡፡ አዜብ የጓደኛዋን ሁኔታ ስትመለከት አንጀቷ ተላወሰ፡፡አልቻለችም፡፡ አብራት አለቀሰች፡፡
እናቷም ልጇ ላይ ጥምጥም ብላ በስስት እያገላበጠች ሣመቻትና..
በጤናሽ ነው ትሁቴ? አለሽልኝ የኔ እናት? ” ዐይን ዐይኖቿን በጉጉት እያየች፡፡
“ደህና ነኝ እማይዬ አንቺስ እንዴት ነሽ?” እናቷን እያሻሸች በዐይኗ አንዱአለምን ስትፈልግ እሱም የሆነ ነገር ሊነግራት ፈልጐ ምልክት ሲሰጣት አየችና ልትስመው ሄደች.....
“ሻምበል ጋ እንደነበርሽ ነግሬአታለሁ” አላት ድምፁን ዝቅ አድርጉ፡፡
ትንሽ ሣቅ ብላ......
“እሺ" አለችው::
ከዚያም በኋላ ከእናቷ አጠገብ የተኙትን በሽተኛ አዛውንት ጤንነታቸውን ጠይቀው፣ እናቷን ከበው ተቀመጡ፡፡ እናቷ የልጇን
ዐይን፤ዐይን፤በስስት ስትመለከት ሆዷ ቡጭ ቡጭ
👍1
#ቆንጆዎቹ
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ሰባት
፡
፡
#ድርሰት_ሰርቅ_ዳ
....ታክሲው ውስጥ የሚጮኸው ሙዚቃ ጭንቅላቱን በጠበጠው፡፡ማታ እንቅልፍ አልወስድህ ብሎት ሲጨነቅ ነበር ያደረው::
“ምንድነው የሆንከው? ለምን አትነግረኝም?” አለች ዘውዲቱ
ከሆቴል ገዝታ ካመጣችው ምግብ እያጎረሰችው፡፡ “ምስኪን አሁንስ ሚስትህ
ናፈቀችሁ መሰለኝ::
ያጎረሰችውን እያላመጠ ዝም አላት:: ወሬ አላሰኘውም:: ምግቡም እንዳያስከፋት ብሎ ነው እንጅ ቢቀርበት በወደደ፡፡
እራት በልተው ተጣጥበው መብራቱን አጥፍተው አልጋ ላይ ከወጡ በኋላ ናትናኤል በጀርባው እንደተንጋለለ አያኖቹን ጣሪያው ላይ ተክሎ ቀረ፡፡
ምን ሆና ይሆን? እንዴት ሁለት ቀን ሙሉ ስራ ሳትገባ ትቀራለች በጤናዋ ባትሆን ነው እንጅ:: ደግሞ ምህረት እቤቷ: ደወዬ
የሚያነሳ አጣሁ ማለቷ ምን ማለቷ ነው? ቤቷን ዘግታ የት ትሄዳለች? ምናልባት አሟት ወላጆቿጋ ሄዳ ይሆን እንዴ? የወላጆቿን ቤት ደግሞ አያውቀውም ! ጉለሌ እንደሆኑ ነግራዋለች፡፡ ግን በደፈናው ጉለሌ ተብሎ አይኬድ፡፡ ቤቷ ሄዶ ይሞክር ይሆን?
ሌሊቱን ሲጨነቅ አደረ፡፡ አሁን ደግሞ ታክሲው ውስጥ ያለው ሙዚቃ አይሉት ጩኽት
“ሲጋራ ፋብሪካ ነው ያሉኝ?” አለው ባለታክሲው፡፡
“እ? አዎ የኔ ልጅ፡፡ ከዚህ ይበቃኛል፡፡” ናትናኤል የታክሲውን በር ከፍቶ ወረደ፡፡
“አባ ገንዘበስ?!” ባለታክሲው የመኪናውን ጥሩንባ ተጭኖ ጮኹ፡፡
“ይቅርታ! ይቅርታ!” አለ ናትናኤል ከሄደበት ተመልሶ ከጋቢው ስር
ከደረት ኪሱ ገንብ እያወጣ “ይቅርታ የኔ ልጅ፡፡ ሃሳብ ገብቶኝ ተዘንግቶኝ
ነው::” ገንዘቡን ለባለታክሲው አቀበለው
ዘውዲቱ የገዛችላት ላስቲክ ቦት ጫማ መንገደኛ ቢያስመስለውም እላይ ከፈፉ እግሩን ከርክሮት ክፉኛ አቁስሎታል። በተራመደ ቁጥር የጫማው ክፈፍ ቁስሉን ሲነካበትና ሲፈትግበት ይለበልበዋል፡፡
ከመንገዱ ባሻገር የአፍሪካ አንድነት ድርጅት ህንፃ ብቻውን ተገትሯል ... ሥራ ፈት፡፡ ናትናኤል ይህንን ፎቅ ሲመለከት ምንም ትርጉም አይሰጠውም በፎቁ ቅርፅ ውስጥ መልዕክት ካለ አንድ የሚል መሆን አለበት ቀጥ ያለ ፎቅ እንድ፡፡
ናትናኤል አይኖቹን ከፎቁ ላይ ነቅሎ ሃሳቡን አሰባሰሰ፡፡ ለጥያቄው መፍትሄ የሚያገኝለት ካልቨርትን ቢያገኝ ብቻ እንደሆነ ከተረዳ ቆይቷል፡፡
ካልቨርትን : እግኝቶ የአውሬውን ማንነት ይፋ እስካላወጣ ድረስ የተደበቀውንና የተሸሸገውን ምሥጢር እስካላዝረከረከው ድረስ አንድ ቀን ከአንዱ ጥግ ነው የሚደፉት፡፡አብርሃምን እንደደፉት፡፡
ይህ ከመሆኑ በፊት ካልቨርትን ማግኘት አለበት፡፡ ግን ካልቨርትን ለማግኘት ከየት ሀ ብሎ እንደሚጀምር እንቆቅልሽ ሆነበት::
መረጃ የውስኪ ጠርሙስ ሾፌር ቤላ
መጠጥ ቤት…ሴት ሞሳድ ኤም አይ
ስድስት…ካዛንቺስ ወዳጁ ቤት… የሴት ልብስ ለብሶ ተሰወረ::
ቁልፉ የግድ እዚህ ውስጥ መሆን አለበት መፍትሄው እዚህ ውስጥ ከሌለ ካልቨርትን ሊያገኘው አይችልም:: ምክንያቱም እሱ የሚያውቀው ይህን ብቻ ነው አብርሃም የነገረውን፡፡
ያለጥርጥር ካልቨርት እንዲሰወር የካዛንቺሷ ወዳጁ ረድታዋለች፡፡ በመጨረሻ የታየው ከእሷ ቤት ሲወጣ ነው፡፡ ምናልባት የት እንደሚገኝም
ታውቅ ይሆናል፡፡ በተቻለው መንገድ ሴትየዋን ማግኘት አለበት:: ካልቨርትን
ለረዳው እንደሚፈልግ ሊያሳምናት ይገባል፡፡ ትጠረጥረው ይሆናል፡፡ ግን
ሊያሳምናት ከቻለና ካልቨርት ያለበትን ቦታ ከነገረችው ድብብቆሹ አበቃ ማለት ነው፡፡ ያን ጊዜ ያለጥርጥር አውሬውን መረቡ ውስጥ ይከተዋል፡፡
ካልቨርት የሚያውቀው ነገር እንደሌለስ? ማወቅ አለበት ምንም የማያውቅ ከሆነ ለምን ተሸሽገ? ያውቃል፡፡ ለሕይወቱ የሚያሰጋው ምሥጢር ይዟል፡፡ ያንን ምስጢር ማግኘት አለበት፡፡ ካልቨርትን ለማግኘት ደግሞ መጀመሪያ የካዛንቺሷን ሴት አግኝቶ ማሳመን፤ ማግባባት ማሽነፍ፡፡፡ እሷ ብቻ ነች ዕድሉ፡፡
ግን አውሬው ለምን ሴትየዋን አቆያት? ያለጥርጥር ወደ ካልቨርት
የምትመሪ መንገድ ነች:: ይህንን ደግሞ አውሬው ሳያውቀው የሚቀር አያደለም:: ታዲያ ለምን አሰነበታት? ለምን አስገድዶም በሆን የካልቨርትን
እድራሻ አላወጣጣትም? ወያም ለማንኛውም ወገን ምሥጢሩን የካልቨርትን አድራሻ እንዳትጠቁም ለምን እንደ አብርሃም አሳስወገዳትም?
ምናልባት ሴትየዋ ራሷ ወጥመድ እንደሆነችስ? የካልቨርትን አድራሻ የሚያነፈንፍ፡ አይጥ ወደ ካዛንቺስ እንዲመጣና ከወጥመድ እንዲገባ
የተንጠለጠለች የሥጋ ቁራጭ እንደሆነችስ? ካዛንቺስ ከመድረሱ እንገቱን ቆርጠው ቢጥሉትስ?'፡ ናትናኤል ሰጋ:ዠ ኣብርሃም ያለው ትዝ አለው
“… ሁለቱን የክትትል ሰዎች ባሰማራን በሶስተኛው ቀን አንደኛው ሰዋችን በስለት ታርዶ እዛው ካዛንቺስ ቱቦ ውስጥ ተጥሎ ተገኘ.…”
ህ! “እዛው ካዛንቺስ” ወጥመድ
ያለጥርጥር ካዛንቺስ ወጥመድ ተጠምዶለታል፡፡ ቢሆንም ምርጫ
የለውም፡፡ ወደ ካልቨርት ሊቀርብ የሚችለው የካዛንቺሏን ሴት ሲያገኝ ብቻ
ነው:: የግድ ካዛንቺስ መሄድ አለበት፡፡
'ካዛንቺስ፡፡ ካዛንቺስ ምኑጋ? ካዛንቺስ ስንት አውራ መንገዶች አሉ?… ካዛንቺስ ስንት መጠጥ ቤቶች አሉ? የትኛዋ ነች የካልቨርት ወዳጅ? “የፈጣሪ ያለህ!' የካዛንቺስ ስፋቱና የቀሚስ ለባሹ ብዛት ታየው::
ሌላ ጥያቄ! እንዴት ሊያገኛት ይችላል? ማን ሊመራው ይችላል? አብርሃም ምንድነው ያለው.…?
የቅብብሎሹን ሠንሠለት መስበር ነው
ካልቨርት የሰረቀውን መረጃ…በውስኪ ጠርሙሶች…በሾፌርነት ለማያገለግል ኢትዮጵያዊ ያቀብላል..ሹፌሩ ቤላ መጠጥ ቤት ላላት.…”
ሹፌሩ ሹፌሩ ሌላ መጠጥ ቤት ያላትን ሴት ያውቃታል ማለት ነው፡፡ የካዛንቺሷንስ? ሊያውቃት ይችላል? ምናልባት ካልቨርት የሚቀርበው ከሆነ ሊያውቃት ያችላል፡፡ ያለው ምርጫ ሾፌሩ ነው:: ሾፌሩን አአግኝቶ የካዛንቺሷን ሴት እድራሻ እንዲሰጠው መጠየቅ::
ሾፌሩ የኛ ሰወ ነው በእሱ በኩል ነው
መረጃውን የምናገኘው...” ነበር ያለው
አብርሃም::
ሌላ ወጥመድ፡፡ ሾፌሩም አደገኛ ነው፡፡ ካዛንቺስ ያለችውን የካልቨርትን ወዳጅ ሆቴል ኣሳየኝ።” ሲለው መቼም መጠራጠሩ አይቀርም፡፡
“እሺ ና” ብሎ ገመድ አንገቱ ቢያስገባለትስ? መሬት ለመሬት እያንሻተተና እየጎተተ ቢያስይዘውስ? እርግጥ ያለው ምርጫ ወደ ካዛንቺሷ እመቤት የሚደርሰው ብቸኛ መንገድ የላይቤርያው ኤምባሲ ሾፌር ብቻ ነው:: ለይቶ የሚያውቀው አድራሻ የእርሱን ብቻ ነዋ! ቢሆንም ሰውየውን በአካል
መገናኘት የለበትም፡፡አንድ ዘዴ መፍጠር አለበት፡፡ ናትናኤል ለበርካታ ቀናቶች ሲያወጣ ሲያወርድ መልስ ሲሻለት የቆየው ጥያቄ ይህ ነበር፡፡መልሱን
አግኝቷል። አቅዶ ወጥኖ ጨርሷል፡፡ ትከሻው ላይ አላርፍልህ ያለውን ጋቢ
እያስተካከለ ከመንገድ ወዳለ ትንሽ ቁርስ ቤት ገባ፡፡
“የኔ ልጅ እባክሽ ስልክ ታስደውይኝ…እከፍላለሁ::ችግር አጋጥሞኝ ነው ልጅ ታማብኝ፡፡” አላቸው እናቱ የሚሆኑትን የቁርስ ቤቷን ባለቤት ጠጋ ብሎ። ያቀደውን ደረጃ በደረጃ ይፈጽም ጀመር፡፡
ሴትየዋ ስልክ ማስደወሉን ባይወዱትም ከቄስ ጋር! ከእግዚኣብሄር ሰው ጋር ክፉ መነጋገሩን አልፈለጉትም፡፡ ከባልኮኒው ስር አንድ ሰማያዊ ስልክ አውጥተው ቄሱ ፊት ቆለሉትና “ያው” ብለው ፊታቸውን አዙረው ሄዱ፡፡ · ደረታቸው ላይ የተቆለለው የጡት ተራራ የዘውዲቱን ጋራ
ያስንቃል፡፡
ናትናኤል ሴትየዋ ዞር እንዳሉለት የስልኩን መነጋገሪያ አንስቶ በመጀመሪያ ወደ ማዞሪያ ደውሎ የላይቤርያ ኤምባሲን የስልክ ቁጥር ከጠየቀና ካገኘ በኋላ ወደ ኤምባሲው ደወለ። በላይቤርያው ኤምባሲ ውስጥ ከአንድ በላይ ሾፌር ሊኖር ይችላል የትኛውን አቅርቡልኝ ሊል ነው? ብቻ ማናቸውም ቢሆኑ የካልቨርት
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ሰባት
፡
፡
#ድርሰት_ሰርቅ_ዳ
....ታክሲው ውስጥ የሚጮኸው ሙዚቃ ጭንቅላቱን በጠበጠው፡፡ማታ እንቅልፍ አልወስድህ ብሎት ሲጨነቅ ነበር ያደረው::
“ምንድነው የሆንከው? ለምን አትነግረኝም?” አለች ዘውዲቱ
ከሆቴል ገዝታ ካመጣችው ምግብ እያጎረሰችው፡፡ “ምስኪን አሁንስ ሚስትህ
ናፈቀችሁ መሰለኝ::
ያጎረሰችውን እያላመጠ ዝም አላት:: ወሬ አላሰኘውም:: ምግቡም እንዳያስከፋት ብሎ ነው እንጅ ቢቀርበት በወደደ፡፡
እራት በልተው ተጣጥበው መብራቱን አጥፍተው አልጋ ላይ ከወጡ በኋላ ናትናኤል በጀርባው እንደተንጋለለ አያኖቹን ጣሪያው ላይ ተክሎ ቀረ፡፡
ምን ሆና ይሆን? እንዴት ሁለት ቀን ሙሉ ስራ ሳትገባ ትቀራለች በጤናዋ ባትሆን ነው እንጅ:: ደግሞ ምህረት እቤቷ: ደወዬ
የሚያነሳ አጣሁ ማለቷ ምን ማለቷ ነው? ቤቷን ዘግታ የት ትሄዳለች? ምናልባት አሟት ወላጆቿጋ ሄዳ ይሆን እንዴ? የወላጆቿን ቤት ደግሞ አያውቀውም ! ጉለሌ እንደሆኑ ነግራዋለች፡፡ ግን በደፈናው ጉለሌ ተብሎ አይኬድ፡፡ ቤቷ ሄዶ ይሞክር ይሆን?
ሌሊቱን ሲጨነቅ አደረ፡፡ አሁን ደግሞ ታክሲው ውስጥ ያለው ሙዚቃ አይሉት ጩኽት
“ሲጋራ ፋብሪካ ነው ያሉኝ?” አለው ባለታክሲው፡፡
“እ? አዎ የኔ ልጅ፡፡ ከዚህ ይበቃኛል፡፡” ናትናኤል የታክሲውን በር ከፍቶ ወረደ፡፡
“አባ ገንዘበስ?!” ባለታክሲው የመኪናውን ጥሩንባ ተጭኖ ጮኹ፡፡
“ይቅርታ! ይቅርታ!” አለ ናትናኤል ከሄደበት ተመልሶ ከጋቢው ስር
ከደረት ኪሱ ገንብ እያወጣ “ይቅርታ የኔ ልጅ፡፡ ሃሳብ ገብቶኝ ተዘንግቶኝ
ነው::” ገንዘቡን ለባለታክሲው አቀበለው
ዘውዲቱ የገዛችላት ላስቲክ ቦት ጫማ መንገደኛ ቢያስመስለውም እላይ ከፈፉ እግሩን ከርክሮት ክፉኛ አቁስሎታል። በተራመደ ቁጥር የጫማው ክፈፍ ቁስሉን ሲነካበትና ሲፈትግበት ይለበልበዋል፡፡
ከመንገዱ ባሻገር የአፍሪካ አንድነት ድርጅት ህንፃ ብቻውን ተገትሯል ... ሥራ ፈት፡፡ ናትናኤል ይህንን ፎቅ ሲመለከት ምንም ትርጉም አይሰጠውም በፎቁ ቅርፅ ውስጥ መልዕክት ካለ አንድ የሚል መሆን አለበት ቀጥ ያለ ፎቅ እንድ፡፡
ናትናኤል አይኖቹን ከፎቁ ላይ ነቅሎ ሃሳቡን አሰባሰሰ፡፡ ለጥያቄው መፍትሄ የሚያገኝለት ካልቨርትን ቢያገኝ ብቻ እንደሆነ ከተረዳ ቆይቷል፡፡
ካልቨርትን : እግኝቶ የአውሬውን ማንነት ይፋ እስካላወጣ ድረስ የተደበቀውንና የተሸሸገውን ምሥጢር እስካላዝረከረከው ድረስ አንድ ቀን ከአንዱ ጥግ ነው የሚደፉት፡፡አብርሃምን እንደደፉት፡፡
ይህ ከመሆኑ በፊት ካልቨርትን ማግኘት አለበት፡፡ ግን ካልቨርትን ለማግኘት ከየት ሀ ብሎ እንደሚጀምር እንቆቅልሽ ሆነበት::
መረጃ የውስኪ ጠርሙስ ሾፌር ቤላ
መጠጥ ቤት…ሴት ሞሳድ ኤም አይ
ስድስት…ካዛንቺስ ወዳጁ ቤት… የሴት ልብስ ለብሶ ተሰወረ::
ቁልፉ የግድ እዚህ ውስጥ መሆን አለበት መፍትሄው እዚህ ውስጥ ከሌለ ካልቨርትን ሊያገኘው አይችልም:: ምክንያቱም እሱ የሚያውቀው ይህን ብቻ ነው አብርሃም የነገረውን፡፡
ያለጥርጥር ካልቨርት እንዲሰወር የካዛንቺሷ ወዳጁ ረድታዋለች፡፡ በመጨረሻ የታየው ከእሷ ቤት ሲወጣ ነው፡፡ ምናልባት የት እንደሚገኝም
ታውቅ ይሆናል፡፡ በተቻለው መንገድ ሴትየዋን ማግኘት አለበት:: ካልቨርትን
ለረዳው እንደሚፈልግ ሊያሳምናት ይገባል፡፡ ትጠረጥረው ይሆናል፡፡ ግን
ሊያሳምናት ከቻለና ካልቨርት ያለበትን ቦታ ከነገረችው ድብብቆሹ አበቃ ማለት ነው፡፡ ያን ጊዜ ያለጥርጥር አውሬውን መረቡ ውስጥ ይከተዋል፡፡
ካልቨርት የሚያውቀው ነገር እንደሌለስ? ማወቅ አለበት ምንም የማያውቅ ከሆነ ለምን ተሸሽገ? ያውቃል፡፡ ለሕይወቱ የሚያሰጋው ምሥጢር ይዟል፡፡ ያንን ምስጢር ማግኘት አለበት፡፡ ካልቨርትን ለማግኘት ደግሞ መጀመሪያ የካዛንቺሷን ሴት አግኝቶ ማሳመን፤ ማግባባት ማሽነፍ፡፡፡ እሷ ብቻ ነች ዕድሉ፡፡
ግን አውሬው ለምን ሴትየዋን አቆያት? ያለጥርጥር ወደ ካልቨርት
የምትመሪ መንገድ ነች:: ይህንን ደግሞ አውሬው ሳያውቀው የሚቀር አያደለም:: ታዲያ ለምን አሰነበታት? ለምን አስገድዶም በሆን የካልቨርትን
እድራሻ አላወጣጣትም? ወያም ለማንኛውም ወገን ምሥጢሩን የካልቨርትን አድራሻ እንዳትጠቁም ለምን እንደ አብርሃም አሳስወገዳትም?
ምናልባት ሴትየዋ ራሷ ወጥመድ እንደሆነችስ? የካልቨርትን አድራሻ የሚያነፈንፍ፡ አይጥ ወደ ካዛንቺስ እንዲመጣና ከወጥመድ እንዲገባ
የተንጠለጠለች የሥጋ ቁራጭ እንደሆነችስ? ካዛንቺስ ከመድረሱ እንገቱን ቆርጠው ቢጥሉትስ?'፡ ናትናኤል ሰጋ:ዠ ኣብርሃም ያለው ትዝ አለው
“… ሁለቱን የክትትል ሰዎች ባሰማራን በሶስተኛው ቀን አንደኛው ሰዋችን በስለት ታርዶ እዛው ካዛንቺስ ቱቦ ውስጥ ተጥሎ ተገኘ.…”
ህ! “እዛው ካዛንቺስ” ወጥመድ
ያለጥርጥር ካዛንቺስ ወጥመድ ተጠምዶለታል፡፡ ቢሆንም ምርጫ
የለውም፡፡ ወደ ካልቨርት ሊቀርብ የሚችለው የካዛንቺሏን ሴት ሲያገኝ ብቻ
ነው:: የግድ ካዛንቺስ መሄድ አለበት፡፡
'ካዛንቺስ፡፡ ካዛንቺስ ምኑጋ? ካዛንቺስ ስንት አውራ መንገዶች አሉ?… ካዛንቺስ ስንት መጠጥ ቤቶች አሉ? የትኛዋ ነች የካልቨርት ወዳጅ? “የፈጣሪ ያለህ!' የካዛንቺስ ስፋቱና የቀሚስ ለባሹ ብዛት ታየው::
ሌላ ጥያቄ! እንዴት ሊያገኛት ይችላል? ማን ሊመራው ይችላል? አብርሃም ምንድነው ያለው.…?
የቅብብሎሹን ሠንሠለት መስበር ነው
ካልቨርት የሰረቀውን መረጃ…በውስኪ ጠርሙሶች…በሾፌርነት ለማያገለግል ኢትዮጵያዊ ያቀብላል..ሹፌሩ ቤላ መጠጥ ቤት ላላት.…”
ሹፌሩ ሹፌሩ ሌላ መጠጥ ቤት ያላትን ሴት ያውቃታል ማለት ነው፡፡ የካዛንቺሷንስ? ሊያውቃት ይችላል? ምናልባት ካልቨርት የሚቀርበው ከሆነ ሊያውቃት ያችላል፡፡ ያለው ምርጫ ሾፌሩ ነው:: ሾፌሩን አአግኝቶ የካዛንቺሷን ሴት እድራሻ እንዲሰጠው መጠየቅ::
ሾፌሩ የኛ ሰወ ነው በእሱ በኩል ነው
መረጃውን የምናገኘው...” ነበር ያለው
አብርሃም::
ሌላ ወጥመድ፡፡ ሾፌሩም አደገኛ ነው፡፡ ካዛንቺስ ያለችውን የካልቨርትን ወዳጅ ሆቴል ኣሳየኝ።” ሲለው መቼም መጠራጠሩ አይቀርም፡፡
“እሺ ና” ብሎ ገመድ አንገቱ ቢያስገባለትስ? መሬት ለመሬት እያንሻተተና እየጎተተ ቢያስይዘውስ? እርግጥ ያለው ምርጫ ወደ ካዛንቺሷ እመቤት የሚደርሰው ብቸኛ መንገድ የላይቤርያው ኤምባሲ ሾፌር ብቻ ነው:: ለይቶ የሚያውቀው አድራሻ የእርሱን ብቻ ነዋ! ቢሆንም ሰውየውን በአካል
መገናኘት የለበትም፡፡አንድ ዘዴ መፍጠር አለበት፡፡ ናትናኤል ለበርካታ ቀናቶች ሲያወጣ ሲያወርድ መልስ ሲሻለት የቆየው ጥያቄ ይህ ነበር፡፡መልሱን
አግኝቷል። አቅዶ ወጥኖ ጨርሷል፡፡ ትከሻው ላይ አላርፍልህ ያለውን ጋቢ
እያስተካከለ ከመንገድ ወዳለ ትንሽ ቁርስ ቤት ገባ፡፡
“የኔ ልጅ እባክሽ ስልክ ታስደውይኝ…እከፍላለሁ::ችግር አጋጥሞኝ ነው ልጅ ታማብኝ፡፡” አላቸው እናቱ የሚሆኑትን የቁርስ ቤቷን ባለቤት ጠጋ ብሎ። ያቀደውን ደረጃ በደረጃ ይፈጽም ጀመር፡፡
ሴትየዋ ስልክ ማስደወሉን ባይወዱትም ከቄስ ጋር! ከእግዚኣብሄር ሰው ጋር ክፉ መነጋገሩን አልፈለጉትም፡፡ ከባልኮኒው ስር አንድ ሰማያዊ ስልክ አውጥተው ቄሱ ፊት ቆለሉትና “ያው” ብለው ፊታቸውን አዙረው ሄዱ፡፡ · ደረታቸው ላይ የተቆለለው የጡት ተራራ የዘውዲቱን ጋራ
ያስንቃል፡፡
ናትናኤል ሴትየዋ ዞር እንዳሉለት የስልኩን መነጋገሪያ አንስቶ በመጀመሪያ ወደ ማዞሪያ ደውሎ የላይቤርያ ኤምባሲን የስልክ ቁጥር ከጠየቀና ካገኘ በኋላ ወደ ኤምባሲው ደወለ። በላይቤርያው ኤምባሲ ውስጥ ከአንድ በላይ ሾፌር ሊኖር ይችላል የትኛውን አቅርቡልኝ ሊል ነው? ብቻ ማናቸውም ቢሆኑ የካልቨርት
👍3❤2🥰1