#ሰመመን
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ስምንት
፡
፡
#ድርሰት_በሲሳይ_ንጉሱ
አቤል ወላጆቹን ትቶ ወደ ትዕግሥት በሐሳቡ መጓዝ ስለጀመረ ዐይኑን ቦዘዝ እንዳደረገ ዝም አለ ።
ምነው ? ”አሉ ዮናታን ፥ አንዳች ስሜቴን የሚጎዳ ነገር የተናገሩ መስሎአቸው ተደናግጠው ። ሐሳባቸው ዘሎ
ያረፈው እናቱ ወይም አባቱ ሞተዋል ከሚል ግምት ላይ ነበር ። ይህን ደግሞ ከአሁን በፊት አልነገራቸውም ፡ ግራ ተጋቡ።
“ ምንም አይደለም ”አላቸው ከሐሳቡ ባነነና ። እርስዎ ለእኔ ያለዎት ክብርና ፍቅር እየታሰበኝ ነው ።ለእኔ መድከምዎ አንሶ ወላጆቼን ሊረዱልኝ ሲያስቡ ... ”
“ ይህ ውለታ ሆኖ ካሳሰበህ ተሳስተሃል ” አሉት ዮናታን “ይህ ማንኛውም ዜጋ ሊያደርገው የሚገባ ነገርም ነው ። ማስተማር ለእኔ ግዴታ ሳይሆን ፥ የመንፈስ ክብርና ኩራት የሚሰጠኝ መስክ ነው ። እናም ጥሩ ተማሪዬን ጥሩ
ቦታ ወይም የሙያ ዘርፍ ላይ ለማየት እንጂ የማስተማር ግዴታዩን ለመወጣት ብቻ አይደለም የማስተምረው ። መረዳዳት ያስፈልጋል ። ደግሞም አጥብቀን አናስበውም እንጂ
ከመረዳዳት ውጪ የሆነ እንቅስቃሴ ምን ታገኛለህ ? ሁሉም የግል ጎጆ ቢቀልስም፡ የሕይወት እንቅስቃሴው የጋራ ነው። ማኅ
በረሰብ ከሌለ ግለሰብ የሚባል ነገር የለም " ምኑን ከምን አርጎ ሊንቀሳቀስ ? ነገሩ ይህ ሆኖ ሳለ ከግል ኑሮአችን በመነሳት የምናደርገው፥ ማኅበራዊ ግንኙነት ከመረዳዳት እንጻር
አጉልተን አናየውም እንጂ ኑሮአችን በመረዳዳት የተሳሰረ ነው።
ዮናታን ከልባቸው እየተመሰጡ ንግግራቸው እየጎላና እየረቀቁ ሲሔድ ፥ የአቤልን እንባ አደረቀው ። አፉን ከፍቶ
ነበር የሚያዳምጣቸው ።
“እሺ እንግዲህ 'እንዳሉት 'አሁን ያለኝ ምርጫ ትምህርቴን ማቋረጥ ነው ። እናም አቋርጠዋለሁ ” አለ የሜዝት
በሚመስል ጉልህ ድምፅ "
«« አዎ ! ቆራጥነት ያስፈልጋል አሉ ዮናታን
“ቆራጥ ካልሆንክና ውሳኔ መውሰድ ካልቻልክ ሕይወትህ የተመሰቃቀለ ይሆንብሃል ። አብዛኛውን ጊዜ ሕይወት የባለ ቤቷን ቆራጥነት ትፈታተናለች የቆራጥነትና ወሳኝነት ትርጉም የሚገባህ ውጤቱን ካየህ በሁዋላ ነው ። አይዞህ
በአንተም ሆነ በወላጆችህ ላይ የሚደርስ ጊዜያዊ ችግር ቢኖር በጋራ እንወጣዋለን አንተም ነገ ትልቅ ሰው እንደምትሆን
አትጠራጠር ። ”
በፊት ያንዣብብ የነበረው የጭንቀት ደመና ከአቤል ፊት ሳይ እየጠፋ መሔዱን ሲመለከቱ ዮናታን ደስታ ተሰማቸው
ጥረታቸው ዋጋ እንዳገኘ እድርገው ገመቱ።
“ እሺ ፤ ለማቋረጥ የሚያስፈልጉኝን ነገሮች ላሟላ ”ብሎ አቤል ከተቀመጠበት ተነሣ ።
“ ግሩም ! ” አሉ ዮናታን ሐሳቡን በመደግፍ ለማቋረጡ ተግባር የምረዳህ ነገር ካለ ብቅ ብለህ አማክረኝ ፡
አቤል እጅ ነሥቶ ሲወጣ በቆራጥነት ስሜት ግንባሩን አኮማትሮ ነበር ። በሐሳቡ የታየው ነገር ይህን “ የሥቃይ
ግቢ ” በአስቸኳይ ለቅቆ መውጣት ብቻ ነበር ። አንድ የሆነ ተቃራኒ ስሜት ጭንቅላቱን ቢከብደውም እስኪወጣ ድረስ ቀውል አልተከሠተለትም ።
ዮናታን ከደስታቸው ብዛት የሚይዙ የሚለቁትን አትተው ፊታቸው የተቀመጡትን ወረቀቶች ያለ ምንም ዓላማ ወዲያ ወዲህ ያገላብጡ ጀመር ፡ አቤል ሐሳባቸውን መቀበሉን የመጀመሪያው ደረጃ አድርገው ወሰዱት የዕቅዳቸው መጀመሪያ እንደ ተሳካ አድርገው በመገመት በጥረታቸው ረኩ ።
“ እሺ እንግዲህ ፡ ትምህርቱን አቋረጠ ። ከዚያ በኋላስ ምን መደረግ አለበት?” በማለት ዮናታን ፥ አቤልን ከተጠመደበት የዐይን ፍቅር ሕመም ለማዳን የሚቀጥለው ደረጃ ምን መሆን እንዳለበት ማሰብ ጀመሩ ። ይህን ሐሳብ በማውጣትና በማውረድ ላይ እንዳሉ በሩ ተከፈተ ።
ቀና ሲሉ አቤል ነው ፊቱ ከስሏል ዐይኖቹ ቀልተዋል በሆነ ስሜት ከራሱ ጋር የተጣላ ይመስላል ከኋላ እንደ ተባረረ ሰው እየቻኮለ ነበር በሩን የከፈተው።
ይቅርታ ያድርጉልኝ ለምን እንደ ዋሸሆዎት አላውቅም። ምናልባት ፈርቼዎት ይሆናል ትምህርቴን ማቋረጥ የለብኝም ብሞክርም አልችልም አላቸው ወደ ውስጥ ሳይገባ በሩ ላይ ቆሞ።
ዮናታን ግር አላቸው ምን ሰይጣን ነው በአንዴ ሐሳቡን ያስቀለበሰው ለጊዜው
የሚመልሱትም ሆነ የሚጠይቁት ነገር እልነበራቸውም።
አቤል ሐሳቡን የቀየረው በሩን ወጥቶ ገና ጥቂት እንኳን ሳይራመድ ነው ። ክፍል ውስጥ ሆኖ ከዮናታን ጋር ሲስማማ ከውስጡ ሲጫጫነውና ሲከብደው የነበረው ተቃራኒ ስሜት ገና ከመውጣ እውነት አሁን ትምህርትህን አቋርጠክ ይህን ትእግስት ያለችበትን ግቢ ልትለቅ ነው? እውነት ከትእግስት ጋር ሳትተያይ ውለህ ማደር የምትችል ይመስልሃል?
የዐይን ፍቅረኛህን ትተህ የት ልትደርስ? እያለ እንደ ጥላ ተከተለው ። አቋርጣለሁ እያለ ቀድሞ ሲፎክር የነበረው ሁሉ ባዶ ጩህት ሆኖ አገኘው ትእግሥትን ጥሎ
ወዴት ?
ለዮናታን ቃል መግባታ አሳዝነው ። እንዴት እንደሚያስተባብላቸወ በማሸበ ቆሞ ተጨነቀ። ሆኖም ዮናታን ያቋርጣል በሚል ተስፋ ልባቸውን ሞልተው እንዳይቀመጡ ቶሎ ተመልሶ ማስተባበል
ነበረበት እራሱን እየረገመ ነው የተመለሰው ምነው? ተስማምተን አልሔድክም እንዴ? ምን ነካህ? ” አሉት ዮናታን በተደናገጠ ስሜት።
አዎ በሃሳቦዎ ተስማምቼ ነበር የወጣሁት ነገር ግን አርቄ ሳስባት ፈተና ተፈትኜ ዕድሌን መሞከር አለብኝ ?” አላቸውና መልስ ሳይጠብቅ ፊቱን አዙሮ ሔደ።
«ስማኝ እንጂ አቤል ! ቆይ እስቲ ?” አሉት ዮናታን ከተቀመጡበት ተነስተው ሊከተሉት እየሞከሩ ዝም ብሏቸው ካጠገባቸው መጭ አለ።
ዮናታን በብስጭት ፈዘው ቀሩ ለሰም ሰው እኔ ምን አስጨነቀኝ ? ” የሚል ተፈታታኝ ሐሳብ መጣባቸው
ተስፋ የመቁረረጥ ስሜት ተስማቸው አኳኋኑ አናደዳቸው ግን ሁኔታን ባስታወሱ ጊዜ ልባቸው ሊጨክን አልቻለም ። እድራጎቱ አንድም የልጅነት አሊያም የፍቅር ቡሶት ነው ደመደሙ።
ቢሮእቸውን ቆልፈው ቀጥታ ወደ አቶ ቢልልኝ ቢሮ አመሩ አረማመዳቸው የሩጫ ያህል ነበር ። በመንገዳቸው
ላይ ሦስት ያህል የሚያውቋቸው ሰዎች ሰላምታ ሳይሰጡ ማለፋቸው አልታወቃቸውም።
ከከባቢልልኝ ቢሮ እንደ ደረሱ ሰላምታ እንኳን ሳይለዋወጡ አረእስተ ጉዳያቸውን አነሱ።
«ቢልልኝ የዚያን ልጅ ጉዳይ ሁላችሁም ቸል ማለታችሁ ነው ?
አቶ ቢልልኝ ! የዮናታን አርእስቱ ስለ አቤል ጉዳይ መሆኑ ለመገመት ጊዜ አልወሰደባቸውም።
የአቤልን ነገር ነው ?...ችላ ማለት አይደለም ኮ እኔ በበኩሌ የዐቅሜን እየመበከርኩ ነው። ሆኖም የልጁ ሁንታ
አስቸኳይ መፍትሔ የሚገኝለት አልሆነም።
"እንዴት ? ” አሉ ዮናታን ፡ ለመቀመጥ ወንበሩን እየሳቡ።
እስቸኳይ መፍትሔ ለማግኘት ልጁ ምቹ አይደለም ቢልልኝ ወደ ጉዳዩ ጠልቀው ሲገቡ ፊታቸው እየተለዋወጠ አዎ አቤል ግልጽ አይደለም ። አንዳንዱ ሰው ሰላፈቀራት ሴት ላገኘው ሰው ሁሉ በየደቂቃው ካላወራ አይሆንለትም ፤ ሌላ አርዕስት የለውም ። ሁሌ ሰው ለሰ
ፍቅር መፍትሔ የሚፈልግለት ይመስለዋል አንዳንዴ ደግሞ ለማንም ሳያዋይ ፍቅሩን ራሱ ዋጥ አርጎ ውስጥ ውስጡን
መቃጠል ይመርጣል ። ሌላ ሰው ለሱ ፍቅር ጤናማ አመለካከት ያለው አይመስለውም የአቤል በደረጃ ከመለየቱ በቀር ይሄኛውን ይመስላል ሁሉም አይነት ግን አስተዳደግና አካባቢን የተመረኮዘ መሠረት ይኖረዋል።
"ታዲያ አሁን የአቤል ነገር እንዴት ይሻላል ?” አሉ ዮናታን ፥ በተጨነቀና በተቻኮለ ስሜት ።
“ የጊዜ ጉዳይ ነው እንጂ ችግሩ መፍትሔ ያገኛል ” አሉ ቢልልኝ፡ “ ጊዜ ! ጊዜ ይወስዳል ። የሥነ ልቡና ጥናት
ሥራ ዘዴና ትዕግሥት ይጠይቃል አቤል ፥ ሌላው ቀርቶ የግል የሕይወት ታሪኩን ለመናገር ፈቃደኛ አልሆነም
ስለዚህ ሥራችን
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ስምንት
፡
፡
#ድርሰት_በሲሳይ_ንጉሱ
አቤል ወላጆቹን ትቶ ወደ ትዕግሥት በሐሳቡ መጓዝ ስለጀመረ ዐይኑን ቦዘዝ እንዳደረገ ዝም አለ ።
ምነው ? ”አሉ ዮናታን ፥ አንዳች ስሜቴን የሚጎዳ ነገር የተናገሩ መስሎአቸው ተደናግጠው ። ሐሳባቸው ዘሎ
ያረፈው እናቱ ወይም አባቱ ሞተዋል ከሚል ግምት ላይ ነበር ። ይህን ደግሞ ከአሁን በፊት አልነገራቸውም ፡ ግራ ተጋቡ።
“ ምንም አይደለም ”አላቸው ከሐሳቡ ባነነና ። እርስዎ ለእኔ ያለዎት ክብርና ፍቅር እየታሰበኝ ነው ።ለእኔ መድከምዎ አንሶ ወላጆቼን ሊረዱልኝ ሲያስቡ ... ”
“ ይህ ውለታ ሆኖ ካሳሰበህ ተሳስተሃል ” አሉት ዮናታን “ይህ ማንኛውም ዜጋ ሊያደርገው የሚገባ ነገርም ነው ። ማስተማር ለእኔ ግዴታ ሳይሆን ፥ የመንፈስ ክብርና ኩራት የሚሰጠኝ መስክ ነው ። እናም ጥሩ ተማሪዬን ጥሩ
ቦታ ወይም የሙያ ዘርፍ ላይ ለማየት እንጂ የማስተማር ግዴታዩን ለመወጣት ብቻ አይደለም የማስተምረው ። መረዳዳት ያስፈልጋል ። ደግሞም አጥብቀን አናስበውም እንጂ
ከመረዳዳት ውጪ የሆነ እንቅስቃሴ ምን ታገኛለህ ? ሁሉም የግል ጎጆ ቢቀልስም፡ የሕይወት እንቅስቃሴው የጋራ ነው። ማኅ
በረሰብ ከሌለ ግለሰብ የሚባል ነገር የለም " ምኑን ከምን አርጎ ሊንቀሳቀስ ? ነገሩ ይህ ሆኖ ሳለ ከግል ኑሮአችን በመነሳት የምናደርገው፥ ማኅበራዊ ግንኙነት ከመረዳዳት እንጻር
አጉልተን አናየውም እንጂ ኑሮአችን በመረዳዳት የተሳሰረ ነው።
ዮናታን ከልባቸው እየተመሰጡ ንግግራቸው እየጎላና እየረቀቁ ሲሔድ ፥ የአቤልን እንባ አደረቀው ። አፉን ከፍቶ
ነበር የሚያዳምጣቸው ።
“እሺ እንግዲህ 'እንዳሉት 'አሁን ያለኝ ምርጫ ትምህርቴን ማቋረጥ ነው ። እናም አቋርጠዋለሁ ” አለ የሜዝት
በሚመስል ጉልህ ድምፅ "
«« አዎ ! ቆራጥነት ያስፈልጋል አሉ ዮናታን
“ቆራጥ ካልሆንክና ውሳኔ መውሰድ ካልቻልክ ሕይወትህ የተመሰቃቀለ ይሆንብሃል ። አብዛኛውን ጊዜ ሕይወት የባለ ቤቷን ቆራጥነት ትፈታተናለች የቆራጥነትና ወሳኝነት ትርጉም የሚገባህ ውጤቱን ካየህ በሁዋላ ነው ። አይዞህ
በአንተም ሆነ በወላጆችህ ላይ የሚደርስ ጊዜያዊ ችግር ቢኖር በጋራ እንወጣዋለን አንተም ነገ ትልቅ ሰው እንደምትሆን
አትጠራጠር ። ”
በፊት ያንዣብብ የነበረው የጭንቀት ደመና ከአቤል ፊት ሳይ እየጠፋ መሔዱን ሲመለከቱ ዮናታን ደስታ ተሰማቸው
ጥረታቸው ዋጋ እንዳገኘ እድርገው ገመቱ።
“ እሺ ፤ ለማቋረጥ የሚያስፈልጉኝን ነገሮች ላሟላ ”ብሎ አቤል ከተቀመጠበት ተነሣ ።
“ ግሩም ! ” አሉ ዮናታን ሐሳቡን በመደግፍ ለማቋረጡ ተግባር የምረዳህ ነገር ካለ ብቅ ብለህ አማክረኝ ፡
አቤል እጅ ነሥቶ ሲወጣ በቆራጥነት ስሜት ግንባሩን አኮማትሮ ነበር ። በሐሳቡ የታየው ነገር ይህን “ የሥቃይ
ግቢ ” በአስቸኳይ ለቅቆ መውጣት ብቻ ነበር ። አንድ የሆነ ተቃራኒ ስሜት ጭንቅላቱን ቢከብደውም እስኪወጣ ድረስ ቀውል አልተከሠተለትም ።
ዮናታን ከደስታቸው ብዛት የሚይዙ የሚለቁትን አትተው ፊታቸው የተቀመጡትን ወረቀቶች ያለ ምንም ዓላማ ወዲያ ወዲህ ያገላብጡ ጀመር ፡ አቤል ሐሳባቸውን መቀበሉን የመጀመሪያው ደረጃ አድርገው ወሰዱት የዕቅዳቸው መጀመሪያ እንደ ተሳካ አድርገው በመገመት በጥረታቸው ረኩ ።
“ እሺ እንግዲህ ፡ ትምህርቱን አቋረጠ ። ከዚያ በኋላስ ምን መደረግ አለበት?” በማለት ዮናታን ፥ አቤልን ከተጠመደበት የዐይን ፍቅር ሕመም ለማዳን የሚቀጥለው ደረጃ ምን መሆን እንዳለበት ማሰብ ጀመሩ ። ይህን ሐሳብ በማውጣትና በማውረድ ላይ እንዳሉ በሩ ተከፈተ ።
ቀና ሲሉ አቤል ነው ፊቱ ከስሏል ዐይኖቹ ቀልተዋል በሆነ ስሜት ከራሱ ጋር የተጣላ ይመስላል ከኋላ እንደ ተባረረ ሰው እየቻኮለ ነበር በሩን የከፈተው።
ይቅርታ ያድርጉልኝ ለምን እንደ ዋሸሆዎት አላውቅም። ምናልባት ፈርቼዎት ይሆናል ትምህርቴን ማቋረጥ የለብኝም ብሞክርም አልችልም አላቸው ወደ ውስጥ ሳይገባ በሩ ላይ ቆሞ።
ዮናታን ግር አላቸው ምን ሰይጣን ነው በአንዴ ሐሳቡን ያስቀለበሰው ለጊዜው
የሚመልሱትም ሆነ የሚጠይቁት ነገር እልነበራቸውም።
አቤል ሐሳቡን የቀየረው በሩን ወጥቶ ገና ጥቂት እንኳን ሳይራመድ ነው ። ክፍል ውስጥ ሆኖ ከዮናታን ጋር ሲስማማ ከውስጡ ሲጫጫነውና ሲከብደው የነበረው ተቃራኒ ስሜት ገና ከመውጣ እውነት አሁን ትምህርትህን አቋርጠክ ይህን ትእግስት ያለችበትን ግቢ ልትለቅ ነው? እውነት ከትእግስት ጋር ሳትተያይ ውለህ ማደር የምትችል ይመስልሃል?
የዐይን ፍቅረኛህን ትተህ የት ልትደርስ? እያለ እንደ ጥላ ተከተለው ። አቋርጣለሁ እያለ ቀድሞ ሲፎክር የነበረው ሁሉ ባዶ ጩህት ሆኖ አገኘው ትእግሥትን ጥሎ
ወዴት ?
ለዮናታን ቃል መግባታ አሳዝነው ። እንዴት እንደሚያስተባብላቸወ በማሸበ ቆሞ ተጨነቀ። ሆኖም ዮናታን ያቋርጣል በሚል ተስፋ ልባቸውን ሞልተው እንዳይቀመጡ ቶሎ ተመልሶ ማስተባበል
ነበረበት እራሱን እየረገመ ነው የተመለሰው ምነው? ተስማምተን አልሔድክም እንዴ? ምን ነካህ? ” አሉት ዮናታን በተደናገጠ ስሜት።
አዎ በሃሳቦዎ ተስማምቼ ነበር የወጣሁት ነገር ግን አርቄ ሳስባት ፈተና ተፈትኜ ዕድሌን መሞከር አለብኝ ?” አላቸውና መልስ ሳይጠብቅ ፊቱን አዙሮ ሔደ።
«ስማኝ እንጂ አቤል ! ቆይ እስቲ ?” አሉት ዮናታን ከተቀመጡበት ተነስተው ሊከተሉት እየሞከሩ ዝም ብሏቸው ካጠገባቸው መጭ አለ።
ዮናታን በብስጭት ፈዘው ቀሩ ለሰም ሰው እኔ ምን አስጨነቀኝ ? ” የሚል ተፈታታኝ ሐሳብ መጣባቸው
ተስፋ የመቁረረጥ ስሜት ተስማቸው አኳኋኑ አናደዳቸው ግን ሁኔታን ባስታወሱ ጊዜ ልባቸው ሊጨክን አልቻለም ። እድራጎቱ አንድም የልጅነት አሊያም የፍቅር ቡሶት ነው ደመደሙ።
ቢሮእቸውን ቆልፈው ቀጥታ ወደ አቶ ቢልልኝ ቢሮ አመሩ አረማመዳቸው የሩጫ ያህል ነበር ። በመንገዳቸው
ላይ ሦስት ያህል የሚያውቋቸው ሰዎች ሰላምታ ሳይሰጡ ማለፋቸው አልታወቃቸውም።
ከከባቢልልኝ ቢሮ እንደ ደረሱ ሰላምታ እንኳን ሳይለዋወጡ አረእስተ ጉዳያቸውን አነሱ።
«ቢልልኝ የዚያን ልጅ ጉዳይ ሁላችሁም ቸል ማለታችሁ ነው ?
አቶ ቢልልኝ ! የዮናታን አርእስቱ ስለ አቤል ጉዳይ መሆኑ ለመገመት ጊዜ አልወሰደባቸውም።
የአቤልን ነገር ነው ?...ችላ ማለት አይደለም ኮ እኔ በበኩሌ የዐቅሜን እየመበከርኩ ነው። ሆኖም የልጁ ሁንታ
አስቸኳይ መፍትሔ የሚገኝለት አልሆነም።
"እንዴት ? ” አሉ ዮናታን ፡ ለመቀመጥ ወንበሩን እየሳቡ።
እስቸኳይ መፍትሔ ለማግኘት ልጁ ምቹ አይደለም ቢልልኝ ወደ ጉዳዩ ጠልቀው ሲገቡ ፊታቸው እየተለዋወጠ አዎ አቤል ግልጽ አይደለም ። አንዳንዱ ሰው ሰላፈቀራት ሴት ላገኘው ሰው ሁሉ በየደቂቃው ካላወራ አይሆንለትም ፤ ሌላ አርዕስት የለውም ። ሁሌ ሰው ለሰ
ፍቅር መፍትሔ የሚፈልግለት ይመስለዋል አንዳንዴ ደግሞ ለማንም ሳያዋይ ፍቅሩን ራሱ ዋጥ አርጎ ውስጥ ውስጡን
መቃጠል ይመርጣል ። ሌላ ሰው ለሱ ፍቅር ጤናማ አመለካከት ያለው አይመስለውም የአቤል በደረጃ ከመለየቱ በቀር ይሄኛውን ይመስላል ሁሉም አይነት ግን አስተዳደግና አካባቢን የተመረኮዘ መሠረት ይኖረዋል።
"ታዲያ አሁን የአቤል ነገር እንዴት ይሻላል ?” አሉ ዮናታን ፥ በተጨነቀና በተቻኮለ ስሜት ።
“ የጊዜ ጉዳይ ነው እንጂ ችግሩ መፍትሔ ያገኛል ” አሉ ቢልልኝ፡ “ ጊዜ ! ጊዜ ይወስዳል ። የሥነ ልቡና ጥናት
ሥራ ዘዴና ትዕግሥት ይጠይቃል አቤል ፥ ሌላው ቀርቶ የግል የሕይወት ታሪኩን ለመናገር ፈቃደኛ አልሆነም
ስለዚህ ሥራችን
#በፍቅር_ላይ_ሾተላይ
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ስምንት
፡
፡
#ድርሰት_በትክክል_ገና
.....ሻምበል ብሩክ ይመስላታል፡፡
የሆነ ደስ የሚል መናፈሻ ውስጥ እጅ ለእጅ ተያይዘው፣ ሲንሸራሸሩ ከቆዩ በኋላ፤ ወደ ኣንድ ጥላው ቀዝቀዝ ያለ፣ ንፁህ አየር ወደሚነፍስበት የወይን ዛፍ ሥር
ይመጡና ከሥሩ ካለው ለምለም ሣር ላይ ጋደም ይላሉ::
በዚህ ጊዜ እሷ እሱን ትራስ አድርጋ፣ ፀጥ ያለውን ኣካባቢ እየቃኙ የተፈጥሮ ውበትን ሲያደንቁ፤ የሁለቱም ዐይኖች ከፊት
ለፊታቸው በሚያዩዋት የጽጌዳ ቅርንጫፍ ላይ ባለችው እንቡጥ ጽጌረዳ አበባ ተማርኮ፤ ጽጌረዳዋን ሲመለከቱ ከቆዩ በኋላ፤ ስለዚያች ጽጌረዳ ለመናገር በአንድ ጊዜ “ እንዴ ” ብለው ይጀምራሉ፡፡
"ምን ልትል ነበር?” ትለዋለች እየሣቀች::
“አንቺስ ምን ልትይ ነበር?” ይላታል እሱም እየሳቀ::
“እንዴት ታምራለች ልል ነበር” ስትለው..
“እኔም እንደሱ ልል ነበር:: ከማማሯም በላይ ደግሞ ልክ የሁለታችንን ፍቅር ትመስላለች ልልሽ ነበር” ይልና ቁልቁል ወርዶ ከንፈሯን ይስማታል፡፡
“ማማሯስ እሺ የሁለታችንን ፍቅር እንዴት ነው የምትመስለው?” ትለዋለች:: ስለፍቅራቸው የበለጠ እንዲያወራላት
ጓጉታ::
“ያልፈነዳ እንቡጥ ጽጌረዳ በአበባነት ደረጃ ላይ ካለው ፍቅራችን ጋር ይመሳሰላል” ይላታል፡፡
“አበባው ፍሬ የሚሆነው መቼ ነው ብሩኬ?” አይን፤ ዐይኑን ሽቅብ እያየች ትጠይቀዋለች::
ወፎች የሚዘምሩ ይመስላታል፡፡ ንፋሱ ሽውው ይላል፡፡ዛፎች ይደንሣሉ፡፡ሰማዩ የጠራ ነው፡፡ሌላ ዓለም፡: ልዩ ዓለም.....
“የሠርጋችን ዕለት በዚያ በጫጉላ ቤት ውስጥ አሀዱ ብለን ትዳርን ስንቀድሰው፡፡ አይመስልሽም ትሁቲና? ቆይ እንዲያውም ይህችን ጽጌረዳ ስለፍቅራችን ገፀበረከት ላቅርብልሽ” ይልና ብድግ ብሎ ያቺን የምታምር እንቡጥ ጽጌረዳ አበባ ቀጥፎ ያመጣና
ይሰጣታል::
“በሠርጋችን ዕለት? .... በጫጉላ ቤት? .... አሀዱ ብለን?... ስንቀድሰው?
ምን ዐይነት ጣጣ ነው? የሆነውን ሁሉ
ብነግረውስ? የጫጉላ ቤቱ ዕቅዳችን መፍረሱን፣ እንደሻው አስገድዶ ክብረ ንፅህናዬን መድፈሩን፤ ብገልጽለትስ?
አያምነኝ ይሆን?
በቃሽኝ አታላይ ነሽ ይለኝ ይሆን? ልንገረው? እያለቀስኩ ልግለጽለት
ወይንስ ልተወው? ወይኔ አምላኬ ምን ጣጣ ውስጥ ከተትከኝ? ወይኔ
ብሩኬ በዚህ ምክንያት እንለያይ ይሆን?...” በስጋት ተዋጠች፡፡
ይህንን ፍርሃቷን በልቧ አምቃ በጭንቀት እንደተዋጠች፤
ሻምበል ብሩክ ቀጥፎ የሰጣትን ጽጌረዳ እንባ በጋረዳቸው ዐይኖቿ ትኩር ብላ መመልከቷን ቀጠለች::
ያቺ የምታምር ጽጌረዳ፣ ያንን የመሰለ ማራኪ ውበት የተላበሰች ለምለም እንቡጥ አባባ፣ ቀስ በቀስ እየጠወለገች፣
እየጠወለገች፣እየደረቀች ሄደችና፣ በእጇ ላይ እንዳለች እርር ብላ ተንኮሻኩሻ ደቀቀች::
በዚህ ጊዜ ትህትና በድንጋጤ ተወራጭታ ከገባችበት አስደንጋጭ የህልም ዓለም ስትወጣ፤ ሰውነቷ ሁሉ በላብ ተዘፍቆ
መንቀጥቀጥ ጀመረች::
ቀስ ብላ ያየችውን ህልም ስትመረምር ፍርሃት ነገሰባትና፤ ሆድ ብሷት “በቃ ልክ ነው:: ህልሜ ትክክል ነው:: ብሩኬን አጣሁት ማለት ነው፡፡ ወይኔ ወይኔ” እያለች ስቅስቅ ብላ ዐይኖቿ
እስከሚያብጡ ድረስ አለቀሰች፡፡
ሻምበል ብሩክ ልጃገረድ ያለመህኗን ሲያውቅ፤ ውሸታም ባለጌ አድርጐ እንደሚገምታት፤ በቃሽኝ እንደሚላት፤ ጠርጥራ ልቧ በሀዘን ተሰበረ::
በዚህ መጥፎ ስሜት ውስጥ ገብታ በሃሣብ ስትዋዥቅ ከቆየች በኋላ፤ ሻምበል ብሩክን የራሷ አድርጋ ለማስቀረት የሚያስችላትን ዘዴ ማውጠንጠን ጀመረች፡፡ በመጨረሻም የሆነ ሃሣብ መጣላት::
“ማን ያውቃል? ዛሬም እንደበፊቱ ሁሉ ልጃገረድ የመሆኔ ምልክቱ ሙሉ ለሙሉ ላይጠፋ ይችላልና የማያስታውቅ ከሆነ ለምን አንድ ሙከራ አላደርግም?” ስትል አሰበች። በመጨረሻም ከሻምበል
ብሩክ ጋር ከመገናኘቷ በፊት ራሷን በዶክተር ልትፈትሽ ወሰነች::
አንዴ ላይታፈስ የፈሰሰ ውሃ፤ በድጋሚ የሚገኝ መስሏት ከዶክተር ባይከዳኝ ጋር ቀጠሮ ያዘች::
ከመቸኮሏ የተነሳ አርብ ዕለት ከዶክተር ባይከዳኝ ጋር በያዘችው ቀጠሮ መሠረት
ወደ ቤት እንደደረሱ ተያይዘው ወደ ቤት እንደደረሱ ሠራተኛዋን አገላብጣ ሣመቻት::
ምነው ፍቅርሽ በዛ?” አለቻት ሠራተኛዋ በልቧ፡፡ ትህትና ከዶክተር ባይከዳኝ ጋር ካሳለፈችው ጊዜ ሁሉ ለየት ያለው የዛሬው ነው:: ለዛሬው ግንኙነታቸው የራሷ ምክንያት ስለአላት፤ የሚሆነውን ቶሎ ለማወቅ፤ ቶሎ ወደ አልጋ ለመሄድ
ቸኮለች፡፡
ቢሆንም ግን ይህንን መቸኮሏን
ዶክተር እንዲያውቅባት አላደረገችም::
እንደተለመደው ሁሉ ዶክተር እራሱን ሊፈትሽ፤ እሷም የልጃገረድነት ሚስጥሯን ልትፈትሽ፤ ተፈላልገውና፤ ተግባብተው፤
ተያይዘው፤ ወደ መኝታ ክፍል ገቡ::
ዶክተር በዚያ ረገድ በራሱ ላይ እምነት እያጣ ስለሄደ በውስጡ የነበረው ጉጉት ቀዝቅዟል፡፡ ሆኖም እንደተለመደው የማይጠገብ ውብ የልጅነት ገላዋ የሚያመነጨውን ሙቀት ለመቋደስ ያህል ብቻ መፍጨርጨሩን ቀጠለ፡፡
......
እሷ ደግሞ በሥጋት እንደተዋጠች ከአሁን አሁን
“ምን ዐይነት ሁኔታ ይፈጠር ይሆን? ልጃገረድ በመሆንና ባለመሆን መካከል ያለው ልዩነት ምን ይመስል ይሆን? በማለት ቁርጧን ለማወቅ ልቧ ትር፤
ትር፤ እያለች የሚያደርገውን
እያንዳንዷን እንቅስቃሴ በንቃት ትከታተላለች፡፡
ቀስ በቀስ አካሉ ከአካሏ ጋር እየተሟሟቀ ፤እየተዋሀደ፣ እየተግባባ፤ መጣና የሷ ገላ እሾህ አመኬላውን አስወግዶ ሊያስተናግደው ዝግጁ መሆኑን ሳያውቅ፣ በሀይል ሲታገላት፤ባልጠበቀው መንገድ ተቀብሎ ያስተናግደው ጀመር፡፡
ትህትና ያንን ሁኔታ ስትመለከት ቅስሟ ስብር ብሎ፤ በሃሣብ ጭልጥ ብላ ሄዳ ሌላ ዓለም ውስጥ ገባች፡፡ ዶክተር ባይከዳኝ ደግሞ በዚያ ባጋጠመው አዲስ ሁኔታ ተደንቆ ጉድ ነው!” አለና ለጊዜው ከገባበት ስሜታዊ ረመጥ ወጥቶ እፎይታ ለማግኘት ያህል ጉልበቱን
እንደድሮው እንደአፍላ የጉርምስና ዘመኑ አድርጐ መጫወቱን ቀጠለ፡፡
በቀላሉ ሊበርድ አልቻለም፡፡ ሰፋ ያለ ጊዜ ወስዶ ተጫወተ፡፡
ይህቺ ሰው ጨው አላት መሰለኝ” እያለ በሚያደርገው ነገር ሁሉ እየተደነቀ ነበር፡፡
ነበር፡፡
እሱ እንደዚያ በደስታ ሲቃ ተውጦ ሲቦርቅ ፣እሷ ግን በድን አካሏን ከሥሩ አጋድማ ዐይኖቿ በከፈቱት ቧንቧዎች እየታጠበች
ዶክተር የልቡ ሲደርስ ቀስ በቀስ ከዚያ ከሚናጥበት የስሜት ማዕበል ወጥቶ የሆነውን ነገር እንደ አዲስ ያስበው ጀመር፡፡
በዚህ ጊዜ የሆነ የቅናት ስሜት ተለኮሰበትና ገላው በንዴት እየተቃጠለ ይጨስ ጀመር፡፡በወሲብ በኩል እርካታን ቢያገኝም፣ ልቡ በዚያው ልክ የምሬት
ደም ሲረጭ ተሰማው::
የልቡ ከደረሰ በኋላ ንጽህናዋን የወሰደው እሱ ባለመሆኑ፤የሆነ የቅናትና የዝቅተኝነት ስሜት አእምሮውን ሰርስሮት ገባ፡፡
መጀመሪያ ካገኛት ቀን ጀምሮ እስከዛሬ ድረስ ያደረገው ድካሙ ሁሉ ከንቱ መቅረቱን ሲያስታውሰው፤ ያንን ውብ ገላዋን ለሌላ ሰው አሳልፋ መስጠቷን ሲያሰላስለው፣ በንዴት እያረረ፣ ጨጓራው ተቀቅሎ እንደገነተረ ሥጋ ሲገነትር ተሰማው:: የተናቀ የተተፋ መሰለው፡፡
የዚያን ጊዜ የልቡን በልቡ አድርጐ.....
“ትህትና እንደዚህ የማደርገው እኮ ስለምጠብቅሽ ነው” ያላት ቀን
“ይገባኛል ዶክተር” ነበር ያለችው:: ግን ዋሸችው:: እሱ ሲጠብቃት እሷ ከዳችው።
እሱ ተንከባክቦ ያቆየውን ውድ ነገር ለሌላ አስረክባቸው መጣች:: ዶክተር ሁሉም ነገር እንደሰንሰለት ተያይዞ በሃሣቡ
መጣበት:: ደካማነቱ የራሱ ሆኖ ሳለ ራሷን አሳልፋ የሰጠችውን ልጅ ሞራሏን
ሊነካው ፈለገ፡፡የሱ ሞራል ተነክቷል፤ ቅስሙ ተሰብሯልና፤ አጥንት በሌለው ምላሱ አጥንት የሚሰብር ንግግር ሊናገራት ፈልጎ ... ጠጋ አላትና
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ስምንት
፡
፡
#ድርሰት_በትክክል_ገና
.....ሻምበል ብሩክ ይመስላታል፡፡
የሆነ ደስ የሚል መናፈሻ ውስጥ እጅ ለእጅ ተያይዘው፣ ሲንሸራሸሩ ከቆዩ በኋላ፤ ወደ ኣንድ ጥላው ቀዝቀዝ ያለ፣ ንፁህ አየር ወደሚነፍስበት የወይን ዛፍ ሥር
ይመጡና ከሥሩ ካለው ለምለም ሣር ላይ ጋደም ይላሉ::
በዚህ ጊዜ እሷ እሱን ትራስ አድርጋ፣ ፀጥ ያለውን ኣካባቢ እየቃኙ የተፈጥሮ ውበትን ሲያደንቁ፤ የሁለቱም ዐይኖች ከፊት
ለፊታቸው በሚያዩዋት የጽጌዳ ቅርንጫፍ ላይ ባለችው እንቡጥ ጽጌረዳ አበባ ተማርኮ፤ ጽጌረዳዋን ሲመለከቱ ከቆዩ በኋላ፤ ስለዚያች ጽጌረዳ ለመናገር በአንድ ጊዜ “ እንዴ ” ብለው ይጀምራሉ፡፡
"ምን ልትል ነበር?” ትለዋለች እየሣቀች::
“አንቺስ ምን ልትይ ነበር?” ይላታል እሱም እየሳቀ::
“እንዴት ታምራለች ልል ነበር” ስትለው..
“እኔም እንደሱ ልል ነበር:: ከማማሯም በላይ ደግሞ ልክ የሁለታችንን ፍቅር ትመስላለች ልልሽ ነበር” ይልና ቁልቁል ወርዶ ከንፈሯን ይስማታል፡፡
“ማማሯስ እሺ የሁለታችንን ፍቅር እንዴት ነው የምትመስለው?” ትለዋለች:: ስለፍቅራቸው የበለጠ እንዲያወራላት
ጓጉታ::
“ያልፈነዳ እንቡጥ ጽጌረዳ በአበባነት ደረጃ ላይ ካለው ፍቅራችን ጋር ይመሳሰላል” ይላታል፡፡
“አበባው ፍሬ የሚሆነው መቼ ነው ብሩኬ?” አይን፤ ዐይኑን ሽቅብ እያየች ትጠይቀዋለች::
ወፎች የሚዘምሩ ይመስላታል፡፡ ንፋሱ ሽውው ይላል፡፡ዛፎች ይደንሣሉ፡፡ሰማዩ የጠራ ነው፡፡ሌላ ዓለም፡: ልዩ ዓለም.....
“የሠርጋችን ዕለት በዚያ በጫጉላ ቤት ውስጥ አሀዱ ብለን ትዳርን ስንቀድሰው፡፡ አይመስልሽም ትሁቲና? ቆይ እንዲያውም ይህችን ጽጌረዳ ስለፍቅራችን ገፀበረከት ላቅርብልሽ” ይልና ብድግ ብሎ ያቺን የምታምር እንቡጥ ጽጌረዳ አበባ ቀጥፎ ያመጣና
ይሰጣታል::
“በሠርጋችን ዕለት? .... በጫጉላ ቤት? .... አሀዱ ብለን?... ስንቀድሰው?
ምን ዐይነት ጣጣ ነው? የሆነውን ሁሉ
ብነግረውስ? የጫጉላ ቤቱ ዕቅዳችን መፍረሱን፣ እንደሻው አስገድዶ ክብረ ንፅህናዬን መድፈሩን፤ ብገልጽለትስ?
አያምነኝ ይሆን?
በቃሽኝ አታላይ ነሽ ይለኝ ይሆን? ልንገረው? እያለቀስኩ ልግለጽለት
ወይንስ ልተወው? ወይኔ አምላኬ ምን ጣጣ ውስጥ ከተትከኝ? ወይኔ
ብሩኬ በዚህ ምክንያት እንለያይ ይሆን?...” በስጋት ተዋጠች፡፡
ይህንን ፍርሃቷን በልቧ አምቃ በጭንቀት እንደተዋጠች፤
ሻምበል ብሩክ ቀጥፎ የሰጣትን ጽጌረዳ እንባ በጋረዳቸው ዐይኖቿ ትኩር ብላ መመልከቷን ቀጠለች::
ያቺ የምታምር ጽጌረዳ፣ ያንን የመሰለ ማራኪ ውበት የተላበሰች ለምለም እንቡጥ አባባ፣ ቀስ በቀስ እየጠወለገች፣
እየጠወለገች፣እየደረቀች ሄደችና፣ በእጇ ላይ እንዳለች እርር ብላ ተንኮሻኩሻ ደቀቀች::
በዚህ ጊዜ ትህትና በድንጋጤ ተወራጭታ ከገባችበት አስደንጋጭ የህልም ዓለም ስትወጣ፤ ሰውነቷ ሁሉ በላብ ተዘፍቆ
መንቀጥቀጥ ጀመረች::
ቀስ ብላ ያየችውን ህልም ስትመረምር ፍርሃት ነገሰባትና፤ ሆድ ብሷት “በቃ ልክ ነው:: ህልሜ ትክክል ነው:: ብሩኬን አጣሁት ማለት ነው፡፡ ወይኔ ወይኔ” እያለች ስቅስቅ ብላ ዐይኖቿ
እስከሚያብጡ ድረስ አለቀሰች፡፡
ሻምበል ብሩክ ልጃገረድ ያለመህኗን ሲያውቅ፤ ውሸታም ባለጌ አድርጐ እንደሚገምታት፤ በቃሽኝ እንደሚላት፤ ጠርጥራ ልቧ በሀዘን ተሰበረ::
በዚህ መጥፎ ስሜት ውስጥ ገብታ በሃሣብ ስትዋዥቅ ከቆየች በኋላ፤ ሻምበል ብሩክን የራሷ አድርጋ ለማስቀረት የሚያስችላትን ዘዴ ማውጠንጠን ጀመረች፡፡ በመጨረሻም የሆነ ሃሣብ መጣላት::
“ማን ያውቃል? ዛሬም እንደበፊቱ ሁሉ ልጃገረድ የመሆኔ ምልክቱ ሙሉ ለሙሉ ላይጠፋ ይችላልና የማያስታውቅ ከሆነ ለምን አንድ ሙከራ አላደርግም?” ስትል አሰበች። በመጨረሻም ከሻምበል
ብሩክ ጋር ከመገናኘቷ በፊት ራሷን በዶክተር ልትፈትሽ ወሰነች::
አንዴ ላይታፈስ የፈሰሰ ውሃ፤ በድጋሚ የሚገኝ መስሏት ከዶክተር ባይከዳኝ ጋር ቀጠሮ ያዘች::
ከመቸኮሏ የተነሳ አርብ ዕለት ከዶክተር ባይከዳኝ ጋር በያዘችው ቀጠሮ መሠረት
ወደ ቤት እንደደረሱ ተያይዘው ወደ ቤት እንደደረሱ ሠራተኛዋን አገላብጣ ሣመቻት::
ምነው ፍቅርሽ በዛ?” አለቻት ሠራተኛዋ በልቧ፡፡ ትህትና ከዶክተር ባይከዳኝ ጋር ካሳለፈችው ጊዜ ሁሉ ለየት ያለው የዛሬው ነው:: ለዛሬው ግንኙነታቸው የራሷ ምክንያት ስለአላት፤ የሚሆነውን ቶሎ ለማወቅ፤ ቶሎ ወደ አልጋ ለመሄድ
ቸኮለች፡፡
ቢሆንም ግን ይህንን መቸኮሏን
ዶክተር እንዲያውቅባት አላደረገችም::
እንደተለመደው ሁሉ ዶክተር እራሱን ሊፈትሽ፤ እሷም የልጃገረድነት ሚስጥሯን ልትፈትሽ፤ ተፈላልገውና፤ ተግባብተው፤
ተያይዘው፤ ወደ መኝታ ክፍል ገቡ::
ዶክተር በዚያ ረገድ በራሱ ላይ እምነት እያጣ ስለሄደ በውስጡ የነበረው ጉጉት ቀዝቅዟል፡፡ ሆኖም እንደተለመደው የማይጠገብ ውብ የልጅነት ገላዋ የሚያመነጨውን ሙቀት ለመቋደስ ያህል ብቻ መፍጨርጨሩን ቀጠለ፡፡
......
እሷ ደግሞ በሥጋት እንደተዋጠች ከአሁን አሁን
“ምን ዐይነት ሁኔታ ይፈጠር ይሆን? ልጃገረድ በመሆንና ባለመሆን መካከል ያለው ልዩነት ምን ይመስል ይሆን? በማለት ቁርጧን ለማወቅ ልቧ ትር፤
ትር፤ እያለች የሚያደርገውን
እያንዳንዷን እንቅስቃሴ በንቃት ትከታተላለች፡፡
ቀስ በቀስ አካሉ ከአካሏ ጋር እየተሟሟቀ ፤እየተዋሀደ፣ እየተግባባ፤ መጣና የሷ ገላ እሾህ አመኬላውን አስወግዶ ሊያስተናግደው ዝግጁ መሆኑን ሳያውቅ፣ በሀይል ሲታገላት፤ባልጠበቀው መንገድ ተቀብሎ ያስተናግደው ጀመር፡፡
ትህትና ያንን ሁኔታ ስትመለከት ቅስሟ ስብር ብሎ፤ በሃሣብ ጭልጥ ብላ ሄዳ ሌላ ዓለም ውስጥ ገባች፡፡ ዶክተር ባይከዳኝ ደግሞ በዚያ ባጋጠመው አዲስ ሁኔታ ተደንቆ ጉድ ነው!” አለና ለጊዜው ከገባበት ስሜታዊ ረመጥ ወጥቶ እፎይታ ለማግኘት ያህል ጉልበቱን
እንደድሮው እንደአፍላ የጉርምስና ዘመኑ አድርጐ መጫወቱን ቀጠለ፡፡
በቀላሉ ሊበርድ አልቻለም፡፡ ሰፋ ያለ ጊዜ ወስዶ ተጫወተ፡፡
ይህቺ ሰው ጨው አላት መሰለኝ” እያለ በሚያደርገው ነገር ሁሉ እየተደነቀ ነበር፡፡
ነበር፡፡
እሱ እንደዚያ በደስታ ሲቃ ተውጦ ሲቦርቅ ፣እሷ ግን በድን አካሏን ከሥሩ አጋድማ ዐይኖቿ በከፈቱት ቧንቧዎች እየታጠበች
ዶክተር የልቡ ሲደርስ ቀስ በቀስ ከዚያ ከሚናጥበት የስሜት ማዕበል ወጥቶ የሆነውን ነገር እንደ አዲስ ያስበው ጀመር፡፡
በዚህ ጊዜ የሆነ የቅናት ስሜት ተለኮሰበትና ገላው በንዴት እየተቃጠለ ይጨስ ጀመር፡፡በወሲብ በኩል እርካታን ቢያገኝም፣ ልቡ በዚያው ልክ የምሬት
ደም ሲረጭ ተሰማው::
የልቡ ከደረሰ በኋላ ንጽህናዋን የወሰደው እሱ ባለመሆኑ፤የሆነ የቅናትና የዝቅተኝነት ስሜት አእምሮውን ሰርስሮት ገባ፡፡
መጀመሪያ ካገኛት ቀን ጀምሮ እስከዛሬ ድረስ ያደረገው ድካሙ ሁሉ ከንቱ መቅረቱን ሲያስታውሰው፤ ያንን ውብ ገላዋን ለሌላ ሰው አሳልፋ መስጠቷን ሲያሰላስለው፣ በንዴት እያረረ፣ ጨጓራው ተቀቅሎ እንደገነተረ ሥጋ ሲገነትር ተሰማው:: የተናቀ የተተፋ መሰለው፡፡
የዚያን ጊዜ የልቡን በልቡ አድርጐ.....
“ትህትና እንደዚህ የማደርገው እኮ ስለምጠብቅሽ ነው” ያላት ቀን
“ይገባኛል ዶክተር” ነበር ያለችው:: ግን ዋሸችው:: እሱ ሲጠብቃት እሷ ከዳችው።
እሱ ተንከባክቦ ያቆየውን ውድ ነገር ለሌላ አስረክባቸው መጣች:: ዶክተር ሁሉም ነገር እንደሰንሰለት ተያይዞ በሃሣቡ
መጣበት:: ደካማነቱ የራሱ ሆኖ ሳለ ራሷን አሳልፋ የሰጠችውን ልጅ ሞራሏን
ሊነካው ፈለገ፡፡የሱ ሞራል ተነክቷል፤ ቅስሙ ተሰብሯልና፤ አጥንት በሌለው ምላሱ አጥንት የሚሰብር ንግግር ሊናገራት ፈልጎ ... ጠጋ አላትና
👍2