አትሮኖስ
286K subscribers
118 photos
3 videos
41 files
568 links
╔╦╦╦═╦╗╔═╦═╦══╦═╗
║║║║╩╣╚╣═╣║║║║║╩╣
╚══╩═╩═╩═╩═╩╩╩
ግጥሞች አዳዲስና ቆየት ያሉ የታዋቂ ደራሲያን መፅሐፍቶችን በ PDF እንዲሁንም
ያልተነበቡ ድርሰቶችን ግጥሞችን ታሪኮችን ያገኙበታል።


Contact. @atronosebot
please dont touch the leave button.😔😳😳
Download Telegram
#ሰመመን


#ክፍል_አርባ_አንድ


#ድርሰት_በሲሳይ_ንጉሱ


ተማሪ አንዱ በአንዱ ላይ እየተንጠራራ ከሰሌዳው ላይ የመለያ ቁጥሩን መፈለግ
ጀመረ።

እነ እስክንድር ግርግሩ መሀል ሲደርሱ እነ ማርታ ውጤታቸውን ለማየት ስለ ተበታተኑ ተሰወሩባቸው ። የአንደኛና የሁለተኛ ዓመት ተማሪዎች ውጤት ብቻ ነበር የወጣው ።

የአራተኛ ዓመቶች ውጤት አልደረሰም እንዴ ? ”
አለው እስክንድር ውጤቱን የለጠፈውን ሰውዬ ሲመለስ አግኝቶት።

"ከሰዓት በኋላ ” ብሎት ሰውዬው እየተደፈ ሐደ ።

“ እስቲ እኔም ጉዴን ልመልከት ”አለ ሳምሶን አስደንጋጭ ድምፁ ስልት አጥቶ እየተንቀጠ።

“ ቆይ ምን አስቸኮለህ ? ግርግሩ ተግ ይበልልህ! ” አለው እስክንድር ።

ሳምሶን አረ ባክህ ! ” ብሎት " ተማሪውን እየገፈታተረ ወደ ልለተኛ ዓመቶች የውጤት ሰሌዳ አመራ።

እቤልና እስክንድር ከግርግሩ መሀል ወጥተው ብቻ ቸውን ቆመው ቀሩ አንዳች ነገር ተጫጭኗቸዋል አይነጋገረም።

ግርግሩን አትረው ይመለከቱ ጀመር » ማንኛውም ነገር ውስጡ ሲሆኑበትና ከውጭ ሲታዘቡት የተለያየ ገፅታ አለው የፈተና ውጤት ግዜ እንዲህ ከሩቅ ሆነው ሲያዩት አሳዛኝ ትርኢት ይታይበታል ውጤቱ የድካም ውጤት ሳይሆን የብሔራዊ ሎተሪ እጣ ይመስላል አንዳንዱ እየሳቀ ሄዶ ውጤቱን አይቶ ሲመለስ ፊቱ ኮሶ ይመስላል በፍርሃት
እየተንቀጠለጠ ሔዶ እየቦረቀ የሚመለስም አለ ውጤቱ አስደንግጦት የቆመበት ዘፍ የሚልም አይታጣም አብዛኛው ተማሪ ስለ ራሱ የነበረው ግምትና አሁን ያገኘው ውጤት እየተራራቀበት ፊቱን አጨማዶ ሲመለስ ነው የሚታየው።
እኔስ ከየትኛው ዐይነት እሆን ? ” ሲል እስክንድር ራሱን ጠየቀ ። የውጤት ጊዜን ሁኔታ እንዲህ በሩቅ ታዝቦ አያውቅም ነበር ።

አንዲት ልጃገረድ በጓደኞቿ ተደግፋ እያለቀሰች በኣጠገባቸው ስታልፍ አይተው የአቤልም የእስክንድርም ልብ
አብሮ አለቀሰ።
አይዞሽ ፡ ዩኒቨርስቲ የሕይወት መጨረሻ አይደለም ” አላት እስክንድር ቀስ ብሎ።

ቀና ብላ አላየችውም ጓደኞቿ ግን ያሾፈባት መስሏቸው ዞረው ገላመጡት ። ግልምጫ ከዐፈር የሚደባልቅ ቢሆን የማይተዋወቁት ሰው ግልጫ ኦሆሆ ! ቶሎ ብሎ ዐይኑን ከአይናቸን አሸሸ ።

ዘወር ሲል ሚስተር ሆርስ ከሶስት ልጆች ጋር ሆኖ ቅልጥሙን እጥፍ እያረገ ፌቱ ፈክቶ ሲያልፍ አየው ።

“ እንዴት ነው ውጤት? ፊትህ ሁሉ ጥርስ ሆኖአል” አለው በሩቁ ከአኳኋኑ ማለፉን ተረድቶ

“ አልሞትንም ፤ ተርፈናል ። የዩኒቨርስቲ ሕይወታችንን አራዝመናል።

« እንኳን ደስ ያለህ ! ” አለውና ፥ “ በቀላሉ የሚደሰት ተፈጥሮ ጥሩ ነው ” አለ በልቡ በድንግት የአቤል ድምፅ አስደነገጠው።

“ ያቻት ትዕግስት"

አቤል ከርቀት ትዕግሥትንና ማርታን ሲያይ ሳያስበው ነው ስሟ ያመለጠው ። በድንጋጤ ስሟን ከመጥራቱ ሌላ
የሚጨምርበት ነገር አልነበረም ።

“ እህ ?” አለው እስክንድርም ደንግጦ "

አቤል ምንም አልመለሰም ። ፊቱ በቅጽበት ተለዋውጦ ከሰል መሰለ ከንፈሩ ተጣብቆ አልላቀቅ አለው ዐይኑ
ፈዞ ቀረ።

እስክንድርም መልስ አልጠበቀም ፥ የአቤልን ዐይን ተከትሎ ትዕግሥትንና ማርታን ተመለከታቸው ውጤታቸውን
አይተው በመመለስ ላይ ነበሩ ። ፊታቸው ዳምኗል ።በኀዘን ተውጠው አንዳችም ቃል ሳይለዋወጡ መሬት መሬት እያዩ ነው የሚሔዱት ። ለእነ አቤል ደግሞ የባሰ
ዳምነውና ተክዘው ታዩአቸው ።

ትዕግሥትና ማርታ እነ አቤልን ሲያዩዋቸውመንገዱቸውን አሳብረው በሌላ በኩል ሔዱ። በማርታ ግፊት ነበር
ይህ የተደረገው። ማንም ሳያያት ወደ መኝታ ክፍሏ መሔድ ነው የፈለገችው ።

አቤል መቆም ኣልቻለም ። ወገቡ የተቀነጠሰ መሰለው። ትዕግሥት ወድቃለች ማለት ነው ? ከዩኒቨርስቲው ልትባረርና ሊያጣት? ስለ ራሱ ውጤት አንዴም አላሰበ መለየት የሞት ያህል ሆኖ ታየው ።

ቃላት መተንፈስ ፈለገ ግን ከንፈሮቹ አልላቀቅ አሉት እርዳታ በሚጠይቅ አመለካከት እስክንድርን አየው ። ከተረታ ወይም ከደከመ ልብ ብቻ ነው የዚያን
ዐይነት እይታ የሚመነጨው።

“ ምን ልርዳህ ? ” አለው እስክንድር ' ሁኔታው ስለ ገባው።

አቤል ምንም ሳይመልስለት ፡ በሚስለመለም ዐይኖቹ እያየው ቀስ ብሎ አጠገቡ ያገኘው ነገር ላይ ቁጭ አለ።

እስክንድር በሐሳቡ አሁን ምን በወቅንና ነው ? ” አለ ። “ ምናልባት እነዚህ ልጆች ሳይወድቁ በዝቅተኛ ማርክ ብቻ እንደሆነስ የተከዙት ? ለምን ተከትዬአቸው ሔጂ አልጠይቃቸውም ? እነሱ ቢሸሹኝ ተናደው ይሆናል። እኔ
ግን ሔጄ ጠይቄአቸው ወድቀውም ከሆነ ማጽናናት አለብኝ ካለዚያ የመተዋወቅ ትርጕሙ ምንድን ነው ? ” አለና አቤልን የተቀመጠበት ትቶት ሔደ ።

ከሁለቱም ከማዘኑ ሌላ የእንድም ቀን የጫዋታ ትዝታ ቢሆን መጥፎ ነውና ከማርታ ጋር የመለያየቱ ነገር እሱንም ቅር ብሎት ነበር ።

ፈጥኖ ሔደ። ሲደርስባቸው ቀድማ ያየችው ትዕግሥት ነበረች ። በደካማ ፈገግታ ሰላምታ ሰጠችው ። ማርታም
እሷን ተከትላ ዘወር ስትል አየችው ። ሰላምታ ልትሰጠው ብትፈልግም ፈገግ ማለት አልቻለችም ።

እስክንድር አጠገባቸው ከደረሰ በኋላ ስለ ውጤታቸው መጠየቅ ፈርቶ ከንፈሩ ይንቀጠቀጥ ጀመር ።

“ እንዴት ነው ? ” አላቸው ፡ ሰላምታ ከተለዋወጡ በኋላ ፥ አንዴ ወደ ማርታ አንዴ ወደ ትዕግሥት እየተመለከተ ።

“ ዩኒቨርስቲያችሁን ለቀቅኩላችሁ እናንተው ኑሩበት!” አለችው ማርታ ቀድማ መንፈሷ ቢደክምም ምላሷ አልሞትም ነበር ።

“ ምነው ? ውጤቱ መጥፎ ነው እንዴ ? ”
ኤጭ ! ”
ከንፈሩን መጠጠና ወደ ትዕግሥት ዞሮ ' “ የአንቺስ ውጤት እንዴት ነው ? ” ሲል ጠየቃት ።

ጥሩ ነው ። በመካከለኛ ውጤት አልፌአለሁ ” አለችው በፈገግታ ።

“ እንኳን ደስ ያለሽ ! ዋናው ማለፍሽ ነው!!” አለና እሱም ፈገግ ብሎ እንደገና ጨበጣት ።

ማርታ ሁለቱንም በቅናት አስተያየት ላጠቻቸው "ዐይን የሚገድል ቢሆን ሁለቱም የቆሙበት ክው ብለው ቀርተው ነበር ።

እስክንድር ደስታና ኀዘን መሐል ገብቶ ወደ የትኛዋ 'እንደሚሆን ግራ ገባው ። “ ግማሽ ፊትን አጥቁሮ፡ ግማሽ ፊትን ማሣቅ ቢቻል እንዴት ጥሩ ነበር !” አለ በልቡ ።

ማርታን ፊት ለፊት ሊያያት አልደፈረም ። ቀስ ብሎ በስርቆሽ ተመለከታት የጠወለገች አበባ መስላለች ለካ ውበት የስሜት ነጸብራቅ ነው?” አለ በሐሳቡ ። ስሜቷ ከውስጥ ሲንድ ፡ሲቃጠል ሲብከነከን ታየው ድርብ የከንፈር ቀለሟ በመጠውለጉ ፊቷ ላይ ጎልቶ ምናምን
የላሰች አይጥ አስመስሏታል ። ቅንድቧ ብቻ እንደ ወትሮው ይርገበገባል ።

እስክንድር የቅንድቧን መርገብገብ አይቶ ወሬ እንደምትፈልግ ዐወቀ ። ግን ምን ዐይነት ወሬ ? በእሷ መውደቅ ምክንያት ተማሪውንና አስተማሪውን ማማት መቦጨቅ ? አይዞሽ ማርታ ዩኒቨርስቲ የሕይወት መጨረሻ አይደለም ” አላትና ፡ አንድ ቀን ያጫወተችውን አስታውሶ : “ ደሞም ከዚህ ወጥተሽ ስኮላርሽፕ መጠበቅ ትችያለሽ ” አላት ።

“እኔ ማርታ ጉዳዬም አይደል ! ብቻ እንኳን ዩኒቨርስቲ የምትሉትን አየሁላችሁ !
እስክንድር በልቡ “ እኛ ደሞ ምን አደረግንሽ ? " ብሎ ጭጭ።

“ የማትስ አስተማንሪኮ ነው ጉድ ያረገኝ ” አለች ትንሽ ቆየችና።

“ እሱ "F" ባይሰጠኝ ኖሮ ሌላ ትምህርት አልጎዳኝም ነበር።

“ ማነው እሱ? ” አላት ያስተዛዘናት መስሎት

“አቶ ኃይሉ የሚሉት አንድ ሽማግሌ አለ " ላውጣሽ ብሎኝ ስለ ዘጋሁት ቁጭቱን ተወጣብኝ ”

“ ያሳዝናል ! ” አለ እስክንድር ፡ ውሸቷ ኮርኩሮት በህዱ እየሳቀ።

ደሞ ከእሱ ጋር ልውጣ እንዴ? ቅሌታም ሽማግሌ ! ”፥

እስክንድር እንደገና ከንፈሩን
1
#በፍቅር_ላይ_ሾተላይ


#ክፍል_አርባ_አንድ


#ድርሰት_በትክክል_ገና

....አዜብና አንዱአለም አጠገቡ ናቸው፡፡ ከኪሱ ውስጥ የሆነ ነገር አወጣ፡፡ በትንሽ የፕላስቲክ ሳጥን ውስጥ የተቀመጠች..ውድ ነገር:: በመጠን በጣም ትንሽ፤ በቁም ነገር ግን እዚያ እላይ!! ቀለበት. የቃል ኪዳን ቀለበት ... ስለ እውነተኛ ፍቅር የተዘጋጀች ፤ የትዳር መጠንሰሻ:
የቃል መተሳሰሪያ፤ ቀለበት... በምህጻረ ቃል የሱና የሷ ስም የተጻፈበትን
ቀለበት አወጣና......

“በመንፈሰ ጠንካራነትሽ ለሰጠሽኝ ትልቅ ትምህርት፡ ለእውነተኛ ፍቅር ስትይ ለከፈልሽው መስዋዕትነት፣ በታማኝነት ፀንተሽ ኣብረን ለቆየንባቸው ጊዜያቶች ሁሉ ማስታወሻ እንድትሆን፡ ይህቺ ሁለት ዓመት ለቀሪ ህይወትሽ ትምህርት የምታገኝበት፣ እኔ ደግሞ ለሠርጋችንም ሆነ ከሠርጋችን በኋላ የትዳር ህይወታችንን በሰላም ለመምራት እንዲያስችለን የምዘጋጅበት እንዲሆንና፤ የማረፊያ ቤት ቆይታሽ፤ መጪውን ብሩህ
ተስፋ አሻግረሽ የምትመለከችበት የዕረፍት ጊዜ እንዲሆንልሽ በመመኘት፤
ያዘጋጀኋትን ገፀ በረከት፤ ይህችን የቃል ኪዳን ቀለበት፣ እንድትቀበይኝ” አለና ከጉልበቱ በርከክ ብሎ ሽቅብ ተመለከታት፡፡ ከዚያም ፍዝዝ ባለችበት
እንባዋ ጉንጮቿን እያቋረጠ፤ ቁልቁል መውረድ ሲጀምር፤ ቀልጠፍ ብሎ
የግራ እጇንና ቀለበቷን ወደ ላይ ከፍ አደረጋቸው፡፡

ከዚያ የከበበው ሰው በሙሉ በደስታና በሆታ አጨበጨበላቸው፡፡ ዕልልታውን አቀለጠላቸው፡፡ አንዱዓለምና አዜብ ተቃቀፉ፡ ሚስጥሩን የምታውቀው አዜብ ብቻ ነበረች፡፡ ቀለበቱንም የመረጠችለት እሷ ናት።
ለአንዱአለም ግን ሁኔታው ድንገተኛ ነበር፡፡ በፍርድ ቤቱ ቅጽር ግቢ ውስጥ ሌላ ተዓምር፡፡ ቃል ኪዳን ......ከዚያም
ቀለበቷን በጣቷ ውስጥ ሲያጠልቅ፤ አዜብና አንዱአለም በደስታ ሲቃ ተውጠው፤ እልልታቸውን፤ አቀለጡት፡፡
ያቺን ቀለበት በዚህ በዛሬው ዕለት ሊያደርግላት የወሰነበት ምክንያት ነበረው፡፡ ይህቺ የውሣኔ ዕለት፣ ይህቺ የፍርድ ቀን፡ በነፃ የምትለቀቅበት ሳይሆን፡ የህግ እስረኛ ሆና በማረፊያ ቤት እንድትቆይ የሚወሰንበት ዕለት መሆኗን አስቀድሞ ስለሚያውቅ፣ በዚህች ቀን የህግ እስረኛ በመሆንዋ፤ የመገለል ስሜት እንዳይሰማትና፤ የሞራል ውድቀት
እንዳይደርስባት፣ መታሰር ማለት፤ ከዚህ ዓለም መገለል ማለት ያለመሆኑን ተረድታ፤ በጥንካሬና በጽናት የእስር ዘመኗን እንድትጨርስ ለማድረግ፣ በዚያች የውሣኔ ዕለት፤ እስረኛ ብቻ ሳትሆን፤ የታጨች ሙሽራ መሆኗን ጭምር እንድታውቅ፣ የህይወት አጋር ፤የትዳር
ጓደኛው ! ከሷ ሌላ ማንም እንደሌለው ሊያረጋግጥላት፡፡ ሊያበረታታት፡፡
ስለወሰነ፤ የቀለበት ስነ ሥርዓቱን ባልጠበቀችው በዚያ ሁኔታ ሲፈጽምና
ቀለበቷን በጣቷ ላይ ሲያኖርላት፣ በደስታ ሲቃ ተውጣ፣ እስረኛ መሆኗን ፍጹም ረስታ፤ በሳቅ እየተፍለቀለቀች፣ ሻምበልን አንገቱ ላይ ተጠመጠመችበት፡፡ ሻምበል አደራውን ተወጣ! የፈራረሰ በድን አካሏ በወደቀበት ስፍራ በመቃብሯ ላይ ሳይሆን፤ ያቺን ውብ የፍቅር ጽጌረዳ
አበባ፤ አለንጋ በሚመስለው የቀለበት ጣቷ ላይ እና፤ በፍቅሩ ምክንያት ታላቅ ጉዳትና ስብራት በደረሰበት ልቧ ውስጥ በክብር አስቀመጠላት ::
ዶክተር ባይከዳኝ በዚያ በሚያየው ነገር ተደናግጦ እና ተገርሞ አፉን በሰፊው ከፍቶ በመቅረቱ ምክንያት፤ እጆቹን ማራገብ እንኳ ተስኖት!በተከፈተው አፉ
ውስጥ ይመላለሱ የነበሩ ዝንቦች ፤ ያለከልካይ ተዝናኑበት፡፡ ከዚያም እንደምንም ብሎ ከሰመመኑ ሲመለስ፤ የሆነ የቅናት መንፈስ ሰውነቱን ውርር አደረገው :: ያንን ያልጠበቀውን
ትእንግርት እያየ፤ አፉን ከፍቶ በቀረበት ቅጽበት ሌላ ነገር ተደገመ
“እኛ ደግሞ ለዛሬ የወርቅ ቀለበት ያላዘጋጀን ቢሆንም፧ ልክ አንቺ ከማረፊያ ቤት ወጥተሽ፤ የጋብቻ ስነ ስርዓታችሁን ስትፈጽሙ ፤
እኔና አዜቢና ደግሞ፧ የቃል ኪዳን ቀለበታችንን የምናስርበት ዕለት
ለመሆኑ ማረጋገጫው፤ የቃል ኪዳን ማህተሙ፤ ይኸው!” አለና ወንድሟ
አዜብን፡ የምታፈቅራት ጓደኛዋን፡ ወደ ደረቱ ሳብ፤ እቅፍ፤ አድርጉ አንገቷን ቀና በማድረግ፤ ከንፈሯን ግጥም አድርጎ ሲስማት፡ ይህ ሁሉ ተአምር በፍጹም ያልጠበቀችው ነበርና፤ ትህትና ከደስታዋ ብዛት የምትሆነውን አጣች፡፡ ያቺ ከልጅነት እስከ እውቀት፤ በሀዘንና፤ በችግሯ
አንድም ጊዜ ተለይታት የማታውቅ፤ እንደነፍሷ የምትወዳት ጓደኛዋ፤
ይሄውና የወንድሟ ሚስት ልትሆን፡ የሚወልዱዋቸው ልጆች የአክስቴ ፡
የአጎቴ፡ ልጅ ሊባባሉ ነው፡፡ የጓደኝነት ፍቅራቸው ወደ ስጋ ዝምድና ሊሸጋገር ነውና፤ አልቻለችም፡፡እንባዋ በድጋሜ ኮለል ብሎ ሲወርድ አሁንም ህዝቡ
ጭብጨባውን አቀለጠላቸው......

በሚያየው ተደጋጋሚ ትርኢት ተደንቆ፤ በሳቅ እያውካካ ዶክተር ባይከዳኝ ከህዝቡ ፈንጠር ብሎ ቆሞ ነበር፡፡ ያንን ሁሉ ትርኢት ተመልክቶ ካበቃ በኋላ ግን፤ የቅናት ስሜቱ እየተገፈፈ ሄዶ፤በምትኩ የደስታ ስሜት ይሰማው ጀመር፡፡ ምንም እንኳ የዛሬው የሻምበል እድል የሱ እንደነበረ ቢሰማውም፤ በራሱ ጥፋት እድሉን አበላሽቷልና፤ ይህቺ ለሱ ፍቅር ስትል ትልቅ ዋጋ የከፈለች ቆንጆ ልጅ
ከዚያ ሁሉ ችግር በኋላ ከጐኗ ቆሞ አይዞሽ የሚላት አጋር በማግኘቷ
ተደሰተ :: ትህትና ምንም በደል ያላደረሰችበት ልጅ መሆኗን ህሊናው
ደጋግሞ ስለጨቀጨቀው ይቅርታ ሊጠይቃትና እንኳን ደስ አለሽ ሊላት
ፈለገ፡፡ ከዚያም ጠጋ አለና.....
“ለተፈጸመው ስህተት ሁሉ አዝናለሁ፡፡ ላደረስኩብሽ በደልም ከልብሽ ይቅርታ እንድታደርጊልኝ እለምናለሁ :: በሰላም የእስር ዘመንሽን እንድትጨርሺና! መልካም የቀለበት ስነ ስርአት እንዲሆንልሽም ከልብ እመኝልሻለሁ
አላት፡፡
አንተም ፈቃደኛ ሆነህ እዚህ በመገኘትህና እውነቱን በማወቅህ
እኔም በጣም ተደስቻለሁ፡፡ አመሰግንሃለሁ፡፡ ያለፈውን ሁሉ
እረስቼዋለሁ፡፡ላንተም መልካሙ
ሁለ እንዲገጥምህ እመኝልሃለሁ፡፡ አዲስ ቀን ይመጣል : አዲስ ህይወት ይቀጥላል.በማለት አጸፋውን መለሰችለትና፣ ሻምበልን አየችው፡፡ ሻምበልም አያት::ከዚያም ሶስቱም እርስ በርሳቸው ተያይተው ፈገግ ሲሉ፤ አዜብም
ዶክተር ባይከዳኝን እያየች ፈገግ አለች፡፡ ሰራሁልህ ማለቷ ይሆን?

ለጊዜው ቢደብቋትም፤ ውሎ እያደር ለቅሶዋ ቢበዛና ውትወታዋ ቢያስጨንቃቸው፤ እውነቱን ነገሯት፡፡ እንደፈራችውም ልጇ በጤናዋ
እንዳልጠፋች ካወቀች ዕለት ጀምሮ፤ በበሽታዋ ላይ ሌላ በሽታ ተጨመረባት፡፡ ትህትና ከሆስፒታል ድና ብትወጣም እስር ቤት መግባቷን ሰማች፡፡ መርዶ... ትንሹ ልጇ አንዱአለም ደግሞ በእንጭጭነቱ ተለይቷት ለመሄድ መዘጋጀቱን ሰማች፡፡ ሌላ የልብ ስብራት... ያንን የምትወደው ባለቤቷን የነጠቀባት ጦርነት፤ አሁን ደግሞ ሮጦ ያልጠገበ አንድ ፍሬ ልጇን እንዳይነጥቅባት በሥጋት ተውጣ፤
ጠዋትና ማታ እዬዬ ብቻ ሆነ፡፡ሁለቱንም አለኝታዎቿን ከጐኗ ስታጣቸው፤ የወላድ መካን የሆነች መሰላት፡፡ ትህትና ከሆስፒታል ከወጣች በኋላም እቤቷ እንድትገባ ሳይሆን፤ ፍርድ ቤቱ በማረሚያ ቤት እንድትቆይ መወሰኑን ስትሰማ
ከዛሬ ነገ በነፃ ትለቀቅልኛለች ብላ በጉጉት እየተጠባበቀች ጭል፤ ጭል፤ትል የነበረች ተስፋዋ ድርግም ብላ ጠፋች፡፡
ይህ የጨለማ ህይወት ፍጹም ልትወጣው የማትችለው ሆነባት።የቤት ሰራተኛዋ እታፈራሁ የልጅ ያክል ብትንከባከባትና፤ ሻምበል ብሩክና አዜብም ልጆቿን ሊተኩላት ከጐኗ ሳይለዩ
ደፋ ቀና ቢሉም፤ሳይሆንላቸው ቀረ፡፡
ከዚህ በኋላ በሽታው በአንድ ወገን፤ የልጆቿ ናፍቆት በሌላው ወገን ሆነው፤ እየተጋገዙ፤ ስጋዋን እኝከው በመጨረስ፤ የሞት ድግሷን ያፋጥኑት ጀመር..
ትህትና ማረሚያ ቤት በቆየችበት ጊዜ ብቸኝነት፣ መታከት ተስፋ መቁረጥና
👍1