#ህመም_ያዘለ_ፍቅር
፡
፡
#
#ክፍል_ሰላሳ_አራት
፡
፡
#በክፍለማርያም
...ፍፁም ለማምለጥ እየሞከረ ነዉ
ቤዛዊት በተቀመጠችበት ቦታ በሀሳብ እሩቅ ተጉዛ ስለ ፍፁም መቅረት ትብከነከናለች
"ምን ሆኖ ቀረ?"
በአይምሮዋ የሚመላለስ ጥያቄ ነዉ።
ሀሳቧ ሁለት ፅንፍ ይዞ ይጋጫል
"ይመጣል አይቀርም"
የሚል የመፅናኛ እና የጤነኝነት ሀስብ በተቃራኒዉ
"አይመጣም ቀርቷል"
የሚል በህመም የገነነ ዉጥረት ባላቸዉ ጥያቄወች ተዉጣ በቀኝ እጇ አገጯን ደገፍ አርጋ
አይኖቿን አሁንም ፊት ለፊቷ አሻግራ ተስፋ ባለነቁረጥ የፍፁምን መምጣት በጉጉት ስትጠባበቅ
ቆይታ አሉታዊዉ ሀሳቧ የፍፁምን መቅረት አሳምኗት ከተቀመጠችበት በፍጥነት ዘላ ተነስታ እንደወታደራዊ አቋቋም በተጠንቀቅ ከቆመች በኋላ ለመራመድ መንቀሳቀስ ስትጀምር
በርቀት ሁኔታዋን ሲታዘቡት የነበሩት እማማ ስንቅነሽ ፈጠን እያሉ ተራምደዉ አስቆሟት
"የት ልትሄጂ ነዉ ልጄ?"
በእድሜ ብዛት የደከመ በሚመስል አሳዛኝ የእናትነት ድምፅ
የቤዛዊትን እጆች ለመያዝ እጃቸዉን እየሰደዱ
"ቀረ በቃ አይመጣም"
ቆጣ ብላ እጆቿን እያወናጨፈች ሊይዟት የቀረቡትን የእማማ ስንቅነሽን እጅ እየገፋች
"ማን ..."
ካሉ በኋላ እማማ ስቅነሽ ይመጣል እየጠበኩት ነው ያለቻቸዉን አስታዉሰዉ
"ፍፁምን ነዉ ምን አለ ትንሽ ብትጠብቂዉ ታድያ ልጄ ወዴት ልትሄጂ ነው የተነሳሽዉ.."
ከጎናቸዉ እንዳትርቅ እየፈለጉ ቤዛዊትን ማባበል ጀመሩ
የት እንደምትሄድ ያላረጋገጠችዉ ቤዛዊት ግን የእማማን ተማፅኖ ከቁብ ሳትቆጥር
ሂጂ ሂጂ የሚላትን ስሜት እየተከተለች እማማን
"እመለሳለሁ እመለሳለሁ እሺ"
እያለች በእርጅናና በህይወት የጎበጠ ትከሻቸዉን በእጇ ዳበስ አርጋ
እማማ ስንቅነሽን ወደ ኋላ ትታ እስዋ ወደ ፊት መራመድ ጀመረች።
ፍፁም ፍቃዱን አመልጣለሁ ብሎ ዘዉ ብሎ የገባበት ቤት መኖርያ ቤት መስሎት እየተሳቀቀ የያዝኩትን ክራንች ማነከሴንም አይተዉ ያዝኑልኛል ብሎ ሰተት እንዳለ
ቤቱ ዉስጥ በቁጥር የሚቆጠሩ ሰወች ሰብሰብ ብለዉ ስላየ በፍርሀት እና ተመልሼ ልዉጣ አልዉጣ እያለ በቆመበት
ሲያስብ አንዲት ደርባባ ሴትዮ ከቤቱ ዉስጠኛ ክፍል መጋረጃ ገልጣ ስትወጣ ፊት ለፊት ሲገጣጠሙ ፍፁም እንደምንም ብሎ
"ሰላም ዋልሽ"
አንገቱን ለሰላምታ ያክል ዝቅ እያረገ
ሴትየዋ ፊት ለፊቷ አይታዉ የማታዉቀዉ ሰዉ በማየቷ ጥቂት ተገርማ ክራንቹን አቋቋሙን ፊቱን በገረፍታ አይታዉ ፊቷ ላይ ፈገግታ እየተነበበ
"እንዴ ምን አስቆመህ አረፍ በል እነጂ..."
በአይኖቿ ሰወቹ ከተቀመጡበት አግዳሚ ወንበር ክፍት ቦታ እያሳየችዉ መቀመጡን ስታይ ተመልሳ ወደ ጓዳዋ ፈጠን እያለች ገባች
ፍፁም የተቀመጡትን ሰወች ቃኛቸዉ የራሳቸዉ ጨዋታ ላይ ናቸዉ ሁሉም እግራቸዉ ስር ንኬል ተቀምጧል መሀል ላይ ጆግ ሙሉ ጠላ መኖሩን አስተዋለ ወድያዉ ሴትየዋ በጣሳ ዉሉ ጠላ ይዛ መጥታ ፊት ለፊቱ አስቀመጠች
ጠላ ቤት መግባቱ ስለገባዉ ፈገግ እያለ አመስግኖ ተቀብሎ መጠጣት ጀመረ።
ቤዛዊት የመንገዱን ጠርዝ ይዛ በለሆሳስ እያወራች ከንፈሮቿ እየተንቀሳቀሱ አንዴ ቆም
ብላ እያሰበች ሲላት ፈጠን ፈጠን እያለች እየተራመደች ነዉ
"ቀረ !!"
አንገቷን ከግራ ወደ ቀኝ እያንቀሳቀሰች
"ቤቱ ለምን አልሄድም እንደዉም እሄዳለሁ"
እጇን ከንፈሯ ላይ ጣል አርጋ ትንፋሽ እየሳበች አሰበች
"ይሄኔ ከእህቴ ጋር ይሆናል"
ንዴቷ እየጨመረ ሄዶ እጆቿን ለቡጢ በሚመስል አኩዋሀን ጨበጠቻቸዉ
ወደ ፍፁም ቤት ሄዳ ፍፁም እና እህቷን አብረዉ ሆነዉ ስታገኛቸዉ ምን ልታረግ እንደምትችል እያሰበች
"ኪኪኪኪኪ ኪኪኪኪ ኪኪኪኪኪ"
እየተንከተከተች ስትስቅ መንገደኛ ሰዉ አይቷት እጆቹን ለማማተብ አንዴ ግንባሩን ቀጥሎ ወደ ሆዱ በስተመጨረሻ ሁለቱን ትከሻወቹን አስነክቶ እየዞረ እያያት ሲያልፍ ሳቋን አቁማ ኮስተር ለማለት እየሞከረች ወደ ፍፁም ቤት አመራች።
ፍቃዱ በንዴት ብዛት ተበሳጭቷ ባዶ ሜዳ ላይ ቆሞ ይዉረገረጋል
"እንዴት ይሄ ያመልጠኛል የት ሊገባ ይችላል"
እያለ በቆመጠት ዙርያዉን ይቃኛል ነገር ግን ፍፁምን ማየት ስላልቻለ እና ፀሀይዋም አቅም አሳጥታዉ ስለደከመዉ ለመመለስ እያሰበ ጥቂት ወደ ኋላ ሲራመድ
አንድ ጎልማሳ ሰዉዬ የጣሳ ምልክት ከተሰቀለበት ቤት በመጠኑ ገድገድ እያለ ሲወጣ ተመልክቶ ቆመ።
💫ይቀጥላል💫
ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ መልካም ምሽት። 🙏
፡
፡
#
#ክፍል_ሰላሳ_አራት
፡
፡
#በክፍለማርያም
...ፍፁም ለማምለጥ እየሞከረ ነዉ
ቤዛዊት በተቀመጠችበት ቦታ በሀሳብ እሩቅ ተጉዛ ስለ ፍፁም መቅረት ትብከነከናለች
"ምን ሆኖ ቀረ?"
በአይምሮዋ የሚመላለስ ጥያቄ ነዉ።
ሀሳቧ ሁለት ፅንፍ ይዞ ይጋጫል
"ይመጣል አይቀርም"
የሚል የመፅናኛ እና የጤነኝነት ሀስብ በተቃራኒዉ
"አይመጣም ቀርቷል"
የሚል በህመም የገነነ ዉጥረት ባላቸዉ ጥያቄወች ተዉጣ በቀኝ እጇ አገጯን ደገፍ አርጋ
አይኖቿን አሁንም ፊት ለፊቷ አሻግራ ተስፋ ባለነቁረጥ የፍፁምን መምጣት በጉጉት ስትጠባበቅ
ቆይታ አሉታዊዉ ሀሳቧ የፍፁምን መቅረት አሳምኗት ከተቀመጠችበት በፍጥነት ዘላ ተነስታ እንደወታደራዊ አቋቋም በተጠንቀቅ ከቆመች በኋላ ለመራመድ መንቀሳቀስ ስትጀምር
በርቀት ሁኔታዋን ሲታዘቡት የነበሩት እማማ ስንቅነሽ ፈጠን እያሉ ተራምደዉ አስቆሟት
"የት ልትሄጂ ነዉ ልጄ?"
በእድሜ ብዛት የደከመ በሚመስል አሳዛኝ የእናትነት ድምፅ
የቤዛዊትን እጆች ለመያዝ እጃቸዉን እየሰደዱ
"ቀረ በቃ አይመጣም"
ቆጣ ብላ እጆቿን እያወናጨፈች ሊይዟት የቀረቡትን የእማማ ስንቅነሽን እጅ እየገፋች
"ማን ..."
ካሉ በኋላ እማማ ስቅነሽ ይመጣል እየጠበኩት ነው ያለቻቸዉን አስታዉሰዉ
"ፍፁምን ነዉ ምን አለ ትንሽ ብትጠብቂዉ ታድያ ልጄ ወዴት ልትሄጂ ነው የተነሳሽዉ.."
ከጎናቸዉ እንዳትርቅ እየፈለጉ ቤዛዊትን ማባበል ጀመሩ
የት እንደምትሄድ ያላረጋገጠችዉ ቤዛዊት ግን የእማማን ተማፅኖ ከቁብ ሳትቆጥር
ሂጂ ሂጂ የሚላትን ስሜት እየተከተለች እማማን
"እመለሳለሁ እመለሳለሁ እሺ"
እያለች በእርጅናና በህይወት የጎበጠ ትከሻቸዉን በእጇ ዳበስ አርጋ
እማማ ስንቅነሽን ወደ ኋላ ትታ እስዋ ወደ ፊት መራመድ ጀመረች።
ፍፁም ፍቃዱን አመልጣለሁ ብሎ ዘዉ ብሎ የገባበት ቤት መኖርያ ቤት መስሎት እየተሳቀቀ የያዝኩትን ክራንች ማነከሴንም አይተዉ ያዝኑልኛል ብሎ ሰተት እንዳለ
ቤቱ ዉስጥ በቁጥር የሚቆጠሩ ሰወች ሰብሰብ ብለዉ ስላየ በፍርሀት እና ተመልሼ ልዉጣ አልዉጣ እያለ በቆመበት
ሲያስብ አንዲት ደርባባ ሴትዮ ከቤቱ ዉስጠኛ ክፍል መጋረጃ ገልጣ ስትወጣ ፊት ለፊት ሲገጣጠሙ ፍፁም እንደምንም ብሎ
"ሰላም ዋልሽ"
አንገቱን ለሰላምታ ያክል ዝቅ እያረገ
ሴትየዋ ፊት ለፊቷ አይታዉ የማታዉቀዉ ሰዉ በማየቷ ጥቂት ተገርማ ክራንቹን አቋቋሙን ፊቱን በገረፍታ አይታዉ ፊቷ ላይ ፈገግታ እየተነበበ
"እንዴ ምን አስቆመህ አረፍ በል እነጂ..."
በአይኖቿ ሰወቹ ከተቀመጡበት አግዳሚ ወንበር ክፍት ቦታ እያሳየችዉ መቀመጡን ስታይ ተመልሳ ወደ ጓዳዋ ፈጠን እያለች ገባች
ፍፁም የተቀመጡትን ሰወች ቃኛቸዉ የራሳቸዉ ጨዋታ ላይ ናቸዉ ሁሉም እግራቸዉ ስር ንኬል ተቀምጧል መሀል ላይ ጆግ ሙሉ ጠላ መኖሩን አስተዋለ ወድያዉ ሴትየዋ በጣሳ ዉሉ ጠላ ይዛ መጥታ ፊት ለፊቱ አስቀመጠች
ጠላ ቤት መግባቱ ስለገባዉ ፈገግ እያለ አመስግኖ ተቀብሎ መጠጣት ጀመረ።
ቤዛዊት የመንገዱን ጠርዝ ይዛ በለሆሳስ እያወራች ከንፈሮቿ እየተንቀሳቀሱ አንዴ ቆም
ብላ እያሰበች ሲላት ፈጠን ፈጠን እያለች እየተራመደች ነዉ
"ቀረ !!"
አንገቷን ከግራ ወደ ቀኝ እያንቀሳቀሰች
"ቤቱ ለምን አልሄድም እንደዉም እሄዳለሁ"
እጇን ከንፈሯ ላይ ጣል አርጋ ትንፋሽ እየሳበች አሰበች
"ይሄኔ ከእህቴ ጋር ይሆናል"
ንዴቷ እየጨመረ ሄዶ እጆቿን ለቡጢ በሚመስል አኩዋሀን ጨበጠቻቸዉ
ወደ ፍፁም ቤት ሄዳ ፍፁም እና እህቷን አብረዉ ሆነዉ ስታገኛቸዉ ምን ልታረግ እንደምትችል እያሰበች
"ኪኪኪኪኪ ኪኪኪኪ ኪኪኪኪኪ"
እየተንከተከተች ስትስቅ መንገደኛ ሰዉ አይቷት እጆቹን ለማማተብ አንዴ ግንባሩን ቀጥሎ ወደ ሆዱ በስተመጨረሻ ሁለቱን ትከሻወቹን አስነክቶ እየዞረ እያያት ሲያልፍ ሳቋን አቁማ ኮስተር ለማለት እየሞከረች ወደ ፍፁም ቤት አመራች።
ፍቃዱ በንዴት ብዛት ተበሳጭቷ ባዶ ሜዳ ላይ ቆሞ ይዉረገረጋል
"እንዴት ይሄ ያመልጠኛል የት ሊገባ ይችላል"
እያለ በቆመጠት ዙርያዉን ይቃኛል ነገር ግን ፍፁምን ማየት ስላልቻለ እና ፀሀይዋም አቅም አሳጥታዉ ስለደከመዉ ለመመለስ እያሰበ ጥቂት ወደ ኋላ ሲራመድ
አንድ ጎልማሳ ሰዉዬ የጣሳ ምልክት ከተሰቀለበት ቤት በመጠኑ ገድገድ እያለ ሲወጣ ተመልክቶ ቆመ።
💫ይቀጥላል💫
ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ መልካም ምሽት። 🙏
👍2
#ሰመመን
፡
፡
#ክፍል_ሰላሳ_አራት
፡
፡
#ድርሰት_በሲሳይ_ንጉሱ
...የከተማው ዋና ዋና መንገዶች በዩኒቨርስቲው ተማሪዎች መወረር ጀምረዋል ። የአራት ኪሎና እካባቢዋ ቡና
ቤት አሳላፊዎች፥ ለተማሪ ሻይ ቡና በማቅረብ ተዋክበዋል ። የተማሪዉ አንሶላዎች'ልብሶች በየሥርቻው ተወርውረው የከረሙ የእግር ሹራቦች ከውሃ በመታረቅ ላይ ናቸው ሕሜት ፥ ውረፋ ፡ ዘለፋና ቀልድ ጊዚአቸውን
ጠብቀው ተመልሰዋል በሴሚስተሩ ውስጥ በዩኒቨርስቲው የተደረገች አንዳች ነገር ሳትቀር እየተነሳች መብጠልጠያዋ ጊዜ ነው።
ይህ ሁሉ ፈተና ማለቁን የሚያበሥር ነው የፈተና ውጤት ቀርቦ ማዕበሉ ማንን ጠርጎ ማንን እንደ ተወ እስኪታወቅ ድረስ ለሁለት ሳምንቱ የዕረፍት ቀናት አብዛኛው ተማሪ ከዚህ ክልል አይወጣም ።
እቤልና እስክንድርም የመጨረሻውን ፈተና እንደ ተፈተኑ ግቢውን ለቀው ወጥተዋል ። የተዝረከረኩ ዕቃዎች
ለማስተካከል እንኳ፥ ወደ መኝታ ክፍላቸው አልተመለሱም።ተያይዘው በቀጥታ ወደ እስክንድር እናት ቤት ተክለ ሃይማኖት አካባቢ ሔዱ። አቤል ለአውደ አመትና አልፎ አልፎም ለዕረፍት እነ እስክንድር ቤት መሔድ የጀመረው ገና የሁለተኛ ዓመት ተማሪ ሳለ ከእስክንድር ጋር እንደተዋወቁ ነው።አንዳንዴ አብረው ይሔዱና የተገኘውን ቀማምሰው ተጫውተው ይመለሳሉ ። ዘንድሮ ግን አቤል ቤታቸው ሳይሔድ ቆይቷል ።
የጠፋው ሰው እንደ ምን አላችሁ ልጆቼ ?
እሁና እናትየዋ ፥ ሁለቱን አቅፈው ሳሙዋቸው ።
“ አቤል ፣ ምነው እንዲህ ጠፋህ ልጄ ?”
ምን እባክዎን ፥ ጥናት በዝቶ ነው
“ ቢሆንስ ታዲያ ፥ አንዳንዴ መቼስ እናት ቤት ብቁ ተብሎ የተገኘውን ቀማምሶ ይኬዳል ። አሀን ፈተና ጨረሳችሁ አይደለም ? ”
“ አዎ መቼስ"
“ እንግዲህ አንድ ፈተና ነዋ የቀራችሁ ? የፊታችን ሰኔ መመረቂያችሁ አይደለም ?
አቤል ዝም አለ ። እስክንድር ስሜቱ ስለ ገባው ቶሎ ብሎ ጣልቃ ገባ ።
“ አዎ ! አይዞሽ ደርሰናል ” አላቸው « እጁ ላይ ሲጋራ መኖሩን ያዩት ይሄኔ ነበር ።
« ይኼንን ሲጋራህን ምናለ ብትተወው እስክንድር ? አቤል ጓደኛህን አትመክረውም ? ! ”
ብዙ ዓመት የተናገሩት ነገር ነው ። ሆኖም ዐይናቸው ባየ ቁጥር ዝም ማለት አይችልም ። አቤል ከመቅለስለስ ልላ
ምንም አልመለሰም።
“አይዞሽ ፡ በቅርቡ አቆማለሁ” አላቸው እስክንድር ራሱ ። እሳቸው ሣቁ ሁሌም
የሚላቸው ነገር ስለሆነ።
ማዘር ሙች አቆማለሁ ። አራት ወር ያህል
ብቻ ታገሽኝ ብቻ አላቸው።
ከልቡ ለማቆም ቆርጦ ነበር እናትየው ግን ጊዜው ደርሶ እስካሳዩ ድረስ ሊያምኑት አይችሉም ።
“ምግብ አቀረቡላቸው ከበላሉ በኋላ ሲጫወቱ ቆይተው ሲመሻሽ እስክንድርና አቤል ሊሔዱ ሲሉ፡-
ዛሬ ለምን ከዚሁ ስትጫወቱ አታድሩም ” እሉ እናትየዋ ።
“ አአይ እንሔዳለን ። እዚያው ካምፓችን ይሻለናል አለ እስክንድር እሳቸው በሚናገሩት አይነት ፣
እስክንድር በዕረፍቱ ሰሞን አቤልን ጥሎ ቤት መክረም አልፈለገም። አብረው እንዳይሆኑ ደግሞ ቤቱ አይበቃም።
ሁለት መኝታ ብቻ ነው ያለው “ አንዱ የናትየዋ ነው " በአንዱ መኝታ ላይ ከታናሽ ወንድሙ ጋር ሦስት ሆነው ተጨናንቀው መክረሙን ኣልፈለገም ። በዚያ ላይ እናትየዋ ለእነሱ የሚያቀርቡትን ምግብ ጣፈጠ አልጣፈጠልኝ ብለው ሲጨነቁ እንዲከርሙ አይፈልግም " ከአሁን በፊትም ቢሆን ትልቁ የክረምት ዕረፍት ላይ ካልሆነ የገናወን ዕረፍት ቤቱ አሳልፎ አያውቅም ። እዚያው ዩኒቨርስቲ
ውስጥ የሚከርመው ። እናትየውም ይህንኑ ስለሚያውቁ ብዙም አላግደረደሩት "
ተሰናብተዋቸው ከውጭው በር እንደ ደረሱ። እናትየው እስክንድርን ወደ ኋላ አስቀሩትና አንድ ነገር እጁ ውስጥ
ሽጉጥ አደረጉለት።
“ ምንድነው እሱ ? ” አላቸው ፡ ምን እንደሆን ልቡ እያወቀ።
“ ያዘው ለዚያ ለምናምንቴ ለሱስህ ይሆንሃል አሉት ። የዐሥር ብር ኖት ነበር ።
እኔ ከሌላ ቦታ አላጣም እባክሽ ። ይሄ ለራስሽ ይሁንሽ ” አላቸው ።ለመግደርደር ያህል ሳይሆን ከልቡ ነበር ።
ምን ጊዜም ከእናቱ ገንዘብ ሲወስድ ልቡ ያዝናል ። እንደ ሲጋራ ሱሰኝነቱ አይቅበዘበዝም ።
ያዘው ግድ የለህም” ። እኔ አለኝ ። አንድ አረርባ ብር የመንደር ዕቁብ ነበረችኝ ፤እሷ ወጥታልኝ ነው ” አሉት ።
አመስግኖ ብሯን ኪሱ ከተተ ወዲያው ማርታ በሀሳቡ መጣችበት ግን በዐሥር ብር ምን ሊኮን ?
“ አቤል ፡ በል እንግዲህ ብቅ እያላችሁ ጠይቁኝ ። አሁን ዕረፍት ናችሁ ” አሉት እናትየዋ « አቤልን ቅር እንዳይለው
ከእናቱ ተለይተው ከሔዱ በኋላ እስክንድር ስለ ድህነትና የእናት አንጀት ተቃራኒ ሁኔታ እያብሰለሰለ ነበር
ድህነት እጅዋን ሊያስራት ይሞክራል ፤ እናት እጅን ለልጅዋ ለመዘርጋት ትፍጨረጨራለች ፡፡ ምኞቷና አድራጎቷ እኩል አይሆንም “ በፍቅር ወደ ልጅዋ ስትንጠራራ
ድህንት ጨምድዶ ይይዛታል ግን ያም ሆኖ እትረታም አትሽንፍም እንደ ምንም ተፍጨርጭራ የልጅዋን እጅ
ትነካለች።
“ አሁን ወዴት ነን ?” አለ አቤል " ትንሽ እንደተጓዙ
“ አንድ ቤት ጎራ ብለን ደርቆ የከረመ ጉሮሮአችንን እናርጥብ እንጂ ! ” አለ እስክንድር ።
አቤል ገንዘብ መቆጠብ የማይችለው የእስክንድር እጅ አስግርምት ሳቀ ። ከእናቱ የተቀበላትን ገንዘብ ለማጥፋት
እንደ ቸኮለ ገባው።
“ ይልቅ ቦታ ምረጥ የት ይሻለናል ? ” አለው እስክንድር
“ ወደ ሠፈራችን አቅራቢያ አይሻልም ? ” አለ አቤል ።መቼም ከዩኒቨርስቲው አካባቢ ርቆ መቆየት አይሆንለትምና።
“ ስድስት ኪሎ ደኅና ቡና ቤት የለማ ! ከጠጣን አይቅር ትንሽ ትርምስ ብጤ ያለበት ይሻለናል ። የጠርሙስ ካካታ ! ”
" አራት ኪሎ እንሒዳ! በዚያው ወደ ካምፓስ ለመግባት ይቀርበናል ”
በዚሁ ተስማምተው ወዶ አራት ኪሎ እመሩ ።
እዚያ ሲደርሱ ከምሽቱ አንድ ሰዓት ተኩል ገደማ ሆኖ ነበር እስክንድር ቻቻታ ያለበትን ቦታ መምረጥ ስለፈለገ ከቡና ቤት ቡና ቤት ሲዘዋወሩ በብዛት የሚያገጥማቸው የዩኒቨርስቲ ተማሪ ነበር ። ተማሪው ታስሮ እንደተፋታ ሆኖአል ንኮኒ ትተደግፎ የሚጠጣው የሴት አሳላፊዎችን ዳሌ የሚዳብሰው በቡድን ተቀምጦ እየጠባ የሚንቻቻው ተሜ ነው። ከወላጅ ከዘመድ የተላከ ከወዲያ ወዲህ ተጠራቅሞ ተቀብሮ የቆየ ገንዘብ መውጫው ዕለት ነዉ። በፈተና ማግሥት ሰክሮ መጥቶ ግቢው ውስጥ መደንፋት ፡ የማይጠጡ ተማሪዎችን መረበሽ ። ወይም ሰክሮ በየበረንዳው አድሮ
ጠዋት “ ጀብድ ” አርጎ ማውራት በዩኒቨርስቲ ውስጥ እየተለመደ የመጣ ይመስላል በተለይ ይህ ሁኔታ አይሎ
የሚታየው ከገጠር በወጡ ተማሪዎች ላይ ነው ። የአዲስ አበባው ተማሪ የቡና ቤቱን ትርምስ ከማዘውተር “ የኖርንበት ነው ” በማለት ዐይነት ቆጠብ ይላል ። ገንዘቡንም ቢሆን ከገጠረ እንደ መጡት አጠራቅሞ ማቆየት አይችልም ። አንዳንዱ እንደ ቱሪስት አስጐብኝ ገጠሬዎቹን ይዞ የከተማውን
ምርጥ ቡና ቤቶች በማስተዋወቅ የጋራ “ ጀብድ ” ይፈጽማል
እስክንድር አንድ ሞቅ ያለ ቡና ቤት አግኝተዉ ገቡ አንድ አንድ ቢራ ይዘው ቁጭ ከማለታቸው ፡ ሳምሶን ጉልቤው ዝንጥ ብሎ መጣ ሁሉም አራት ኪሎ መጠጣት የመረጡት ማታ ወደ መኝታ ቤታቸው ለመግባት እንዲቀርባቸው ይመስላል ።
ሳምሶን እስክንድርና አቤልን ሲያገኛቸው ደስ አለው ።በተለይ አቤልን መጋበዝ፤ ይፈልግ ነበር ።ጠዋት የለበሰውን
ቀያይሮ አፍላ ጉልበቱን ወጣጥሮ በሚያሳይ መሉ ጅንስ ሽክ ብሎአል ።
"ከመቼው ተሠየማችሁ ? አላቸው ፡ አጠግባቸው ለመቀመጥ መንበር እየሳበ
“ አንተም ደህና ጊዜ ደርሰሃል ፤ ቁጭ በል አለው እስክንድር።
ሳምሶንም ቢራ አዝዞ
፡
፡
#ክፍል_ሰላሳ_አራት
፡
፡
#ድርሰት_በሲሳይ_ንጉሱ
...የከተማው ዋና ዋና መንገዶች በዩኒቨርስቲው ተማሪዎች መወረር ጀምረዋል ። የአራት ኪሎና እካባቢዋ ቡና
ቤት አሳላፊዎች፥ ለተማሪ ሻይ ቡና በማቅረብ ተዋክበዋል ። የተማሪዉ አንሶላዎች'ልብሶች በየሥርቻው ተወርውረው የከረሙ የእግር ሹራቦች ከውሃ በመታረቅ ላይ ናቸው ሕሜት ፥ ውረፋ ፡ ዘለፋና ቀልድ ጊዚአቸውን
ጠብቀው ተመልሰዋል በሴሚስተሩ ውስጥ በዩኒቨርስቲው የተደረገች አንዳች ነገር ሳትቀር እየተነሳች መብጠልጠያዋ ጊዜ ነው።
ይህ ሁሉ ፈተና ማለቁን የሚያበሥር ነው የፈተና ውጤት ቀርቦ ማዕበሉ ማንን ጠርጎ ማንን እንደ ተወ እስኪታወቅ ድረስ ለሁለት ሳምንቱ የዕረፍት ቀናት አብዛኛው ተማሪ ከዚህ ክልል አይወጣም ።
እቤልና እስክንድርም የመጨረሻውን ፈተና እንደ ተፈተኑ ግቢውን ለቀው ወጥተዋል ። የተዝረከረኩ ዕቃዎች
ለማስተካከል እንኳ፥ ወደ መኝታ ክፍላቸው አልተመለሱም።ተያይዘው በቀጥታ ወደ እስክንድር እናት ቤት ተክለ ሃይማኖት አካባቢ ሔዱ። አቤል ለአውደ አመትና አልፎ አልፎም ለዕረፍት እነ እስክንድር ቤት መሔድ የጀመረው ገና የሁለተኛ ዓመት ተማሪ ሳለ ከእስክንድር ጋር እንደተዋወቁ ነው።አንዳንዴ አብረው ይሔዱና የተገኘውን ቀማምሰው ተጫውተው ይመለሳሉ ። ዘንድሮ ግን አቤል ቤታቸው ሳይሔድ ቆይቷል ።
የጠፋው ሰው እንደ ምን አላችሁ ልጆቼ ?
እሁና እናትየዋ ፥ ሁለቱን አቅፈው ሳሙዋቸው ።
“ አቤል ፣ ምነው እንዲህ ጠፋህ ልጄ ?”
ምን እባክዎን ፥ ጥናት በዝቶ ነው
“ ቢሆንስ ታዲያ ፥ አንዳንዴ መቼስ እናት ቤት ብቁ ተብሎ የተገኘውን ቀማምሶ ይኬዳል ። አሀን ፈተና ጨረሳችሁ አይደለም ? ”
“ አዎ መቼስ"
“ እንግዲህ አንድ ፈተና ነዋ የቀራችሁ ? የፊታችን ሰኔ መመረቂያችሁ አይደለም ?
አቤል ዝም አለ ። እስክንድር ስሜቱ ስለ ገባው ቶሎ ብሎ ጣልቃ ገባ ።
“ አዎ ! አይዞሽ ደርሰናል ” አላቸው « እጁ ላይ ሲጋራ መኖሩን ያዩት ይሄኔ ነበር ።
« ይኼንን ሲጋራህን ምናለ ብትተወው እስክንድር ? አቤል ጓደኛህን አትመክረውም ? ! ”
ብዙ ዓመት የተናገሩት ነገር ነው ። ሆኖም ዐይናቸው ባየ ቁጥር ዝም ማለት አይችልም ። አቤል ከመቅለስለስ ልላ
ምንም አልመለሰም።
“አይዞሽ ፡ በቅርቡ አቆማለሁ” አላቸው እስክንድር ራሱ ። እሳቸው ሣቁ ሁሌም
የሚላቸው ነገር ስለሆነ።
ማዘር ሙች አቆማለሁ ። አራት ወር ያህል
ብቻ ታገሽኝ ብቻ አላቸው።
ከልቡ ለማቆም ቆርጦ ነበር እናትየው ግን ጊዜው ደርሶ እስካሳዩ ድረስ ሊያምኑት አይችሉም ።
“ምግብ አቀረቡላቸው ከበላሉ በኋላ ሲጫወቱ ቆይተው ሲመሻሽ እስክንድርና አቤል ሊሔዱ ሲሉ፡-
ዛሬ ለምን ከዚሁ ስትጫወቱ አታድሩም ” እሉ እናትየዋ ።
“ አአይ እንሔዳለን ። እዚያው ካምፓችን ይሻለናል አለ እስክንድር እሳቸው በሚናገሩት አይነት ፣
እስክንድር በዕረፍቱ ሰሞን አቤልን ጥሎ ቤት መክረም አልፈለገም። አብረው እንዳይሆኑ ደግሞ ቤቱ አይበቃም።
ሁለት መኝታ ብቻ ነው ያለው “ አንዱ የናትየዋ ነው " በአንዱ መኝታ ላይ ከታናሽ ወንድሙ ጋር ሦስት ሆነው ተጨናንቀው መክረሙን ኣልፈለገም ። በዚያ ላይ እናትየዋ ለእነሱ የሚያቀርቡትን ምግብ ጣፈጠ አልጣፈጠልኝ ብለው ሲጨነቁ እንዲከርሙ አይፈልግም " ከአሁን በፊትም ቢሆን ትልቁ የክረምት ዕረፍት ላይ ካልሆነ የገናወን ዕረፍት ቤቱ አሳልፎ አያውቅም ። እዚያው ዩኒቨርስቲ
ውስጥ የሚከርመው ። እናትየውም ይህንኑ ስለሚያውቁ ብዙም አላግደረደሩት "
ተሰናብተዋቸው ከውጭው በር እንደ ደረሱ። እናትየው እስክንድርን ወደ ኋላ አስቀሩትና አንድ ነገር እጁ ውስጥ
ሽጉጥ አደረጉለት።
“ ምንድነው እሱ ? ” አላቸው ፡ ምን እንደሆን ልቡ እያወቀ።
“ ያዘው ለዚያ ለምናምንቴ ለሱስህ ይሆንሃል አሉት ። የዐሥር ብር ኖት ነበር ።
እኔ ከሌላ ቦታ አላጣም እባክሽ ። ይሄ ለራስሽ ይሁንሽ ” አላቸው ።ለመግደርደር ያህል ሳይሆን ከልቡ ነበር ።
ምን ጊዜም ከእናቱ ገንዘብ ሲወስድ ልቡ ያዝናል ። እንደ ሲጋራ ሱሰኝነቱ አይቅበዘበዝም ።
ያዘው ግድ የለህም” ። እኔ አለኝ ። አንድ አረርባ ብር የመንደር ዕቁብ ነበረችኝ ፤እሷ ወጥታልኝ ነው ” አሉት ።
አመስግኖ ብሯን ኪሱ ከተተ ወዲያው ማርታ በሀሳቡ መጣችበት ግን በዐሥር ብር ምን ሊኮን ?
“ አቤል ፡ በል እንግዲህ ብቅ እያላችሁ ጠይቁኝ ። አሁን ዕረፍት ናችሁ ” አሉት እናትየዋ « አቤልን ቅር እንዳይለው
ከእናቱ ተለይተው ከሔዱ በኋላ እስክንድር ስለ ድህነትና የእናት አንጀት ተቃራኒ ሁኔታ እያብሰለሰለ ነበር
ድህነት እጅዋን ሊያስራት ይሞክራል ፤ እናት እጅን ለልጅዋ ለመዘርጋት ትፍጨረጨራለች ፡፡ ምኞቷና አድራጎቷ እኩል አይሆንም “ በፍቅር ወደ ልጅዋ ስትንጠራራ
ድህንት ጨምድዶ ይይዛታል ግን ያም ሆኖ እትረታም አትሽንፍም እንደ ምንም ተፍጨርጭራ የልጅዋን እጅ
ትነካለች።
“ አሁን ወዴት ነን ?” አለ አቤል " ትንሽ እንደተጓዙ
“ አንድ ቤት ጎራ ብለን ደርቆ የከረመ ጉሮሮአችንን እናርጥብ እንጂ ! ” አለ እስክንድር ።
አቤል ገንዘብ መቆጠብ የማይችለው የእስክንድር እጅ አስግርምት ሳቀ ። ከእናቱ የተቀበላትን ገንዘብ ለማጥፋት
እንደ ቸኮለ ገባው።
“ ይልቅ ቦታ ምረጥ የት ይሻለናል ? ” አለው እስክንድር
“ ወደ ሠፈራችን አቅራቢያ አይሻልም ? ” አለ አቤል ።መቼም ከዩኒቨርስቲው አካባቢ ርቆ መቆየት አይሆንለትምና።
“ ስድስት ኪሎ ደኅና ቡና ቤት የለማ ! ከጠጣን አይቅር ትንሽ ትርምስ ብጤ ያለበት ይሻለናል ። የጠርሙስ ካካታ ! ”
" አራት ኪሎ እንሒዳ! በዚያው ወደ ካምፓስ ለመግባት ይቀርበናል ”
በዚሁ ተስማምተው ወዶ አራት ኪሎ እመሩ ።
እዚያ ሲደርሱ ከምሽቱ አንድ ሰዓት ተኩል ገደማ ሆኖ ነበር እስክንድር ቻቻታ ያለበትን ቦታ መምረጥ ስለፈለገ ከቡና ቤት ቡና ቤት ሲዘዋወሩ በብዛት የሚያገጥማቸው የዩኒቨርስቲ ተማሪ ነበር ። ተማሪው ታስሮ እንደተፋታ ሆኖአል ንኮኒ ትተደግፎ የሚጠጣው የሴት አሳላፊዎችን ዳሌ የሚዳብሰው በቡድን ተቀምጦ እየጠባ የሚንቻቻው ተሜ ነው። ከወላጅ ከዘመድ የተላከ ከወዲያ ወዲህ ተጠራቅሞ ተቀብሮ የቆየ ገንዘብ መውጫው ዕለት ነዉ። በፈተና ማግሥት ሰክሮ መጥቶ ግቢው ውስጥ መደንፋት ፡ የማይጠጡ ተማሪዎችን መረበሽ ። ወይም ሰክሮ በየበረንዳው አድሮ
ጠዋት “ ጀብድ ” አርጎ ማውራት በዩኒቨርስቲ ውስጥ እየተለመደ የመጣ ይመስላል በተለይ ይህ ሁኔታ አይሎ
የሚታየው ከገጠር በወጡ ተማሪዎች ላይ ነው ። የአዲስ አበባው ተማሪ የቡና ቤቱን ትርምስ ከማዘውተር “ የኖርንበት ነው ” በማለት ዐይነት ቆጠብ ይላል ። ገንዘቡንም ቢሆን ከገጠረ እንደ መጡት አጠራቅሞ ማቆየት አይችልም ። አንዳንዱ እንደ ቱሪስት አስጐብኝ ገጠሬዎቹን ይዞ የከተማውን
ምርጥ ቡና ቤቶች በማስተዋወቅ የጋራ “ ጀብድ ” ይፈጽማል
እስክንድር አንድ ሞቅ ያለ ቡና ቤት አግኝተዉ ገቡ አንድ አንድ ቢራ ይዘው ቁጭ ከማለታቸው ፡ ሳምሶን ጉልቤው ዝንጥ ብሎ መጣ ሁሉም አራት ኪሎ መጠጣት የመረጡት ማታ ወደ መኝታ ቤታቸው ለመግባት እንዲቀርባቸው ይመስላል ።
ሳምሶን እስክንድርና አቤልን ሲያገኛቸው ደስ አለው ።በተለይ አቤልን መጋበዝ፤ ይፈልግ ነበር ።ጠዋት የለበሰውን
ቀያይሮ አፍላ ጉልበቱን ወጣጥሮ በሚያሳይ መሉ ጅንስ ሽክ ብሎአል ።
"ከመቼው ተሠየማችሁ ? አላቸው ፡ አጠግባቸው ለመቀመጥ መንበር እየሳበ
“ አንተም ደህና ጊዜ ደርሰሃል ፤ ቁጭ በል አለው እስክንድር።
ሳምሶንም ቢራ አዝዞ
👍1