#በፍቅር_ላይ_ሾተላይ
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ሁለት
፡
፡
#ድርሰት_በትክክል_ገና
“ጤና ይስጥልኝ ወይዘሪት እንዳሻው በቀለ.... እባላለሁ እራሱን በሚገባ አስተዋወቀ። እሷም ስሟን ሰጠችው። ፈርጣማ ወጠምሻ ነው።
“ምን ያህል ጊዜ ሆነሽ ሥራ ከጀመርሽ?” ድዱን እየገለፈጠ
“እንድ ሳምንት ሆኖኛል” በር በሩን እያየች::
“በስመአብ ይህንን ያክል ቀን ስትቆዪ ያለመምጣቴ ደደብ ያሰኘኛል”
“ለምን? ይኸው አሁን ተዋወቅን አይደል? ምን ልዩነት አለው?”
“ተይ እንጂ! ጊዜ እኮ የውጤት አብራክ ነው” ትንሽ እየተውረገረገ።
“እንዴት ማለት?”
“ከአንድ ውጤት ላይ ለመድረስ ድርጊት የሚወሰነው በጊዜ ውስጥ ነው
ማለቴ ነው” ሊፈላሰፍባት ሞከረ፡፡
“አልገባኝም?”::
እንደሻው በልቡ “ተይ እንጂ ቆንጂት? አንድ ሳምንት እኮ ለጥብስ የምትበቂበት ጊዜ ነበር፡፡ አሁን ግን ገና ጥሬ ነሽ፡፡ አንድ
ተጨማሪ የማብሰያ ሳምንት ሳትወስጅብኝ አትቀሪም” አለ፡፡
“ማለቴ ይሄኔ በደንብ ተዋውቀን፣ ተግባብተን፤ ሞቅ ያልን ጓደኛሞች መሆን የምንችልበት ጊዜ ነበር ማለቴ ነው”
ወደ ወ/ሮ አረጋሽ በቆረጣ ተመለከተ።
ወ/ሮ አረጋሽ በዕድሜ ጠና ያለች በዚህ ሱቅ ውስጥ ለረጅም አመታት ተቀጥራ ያገለገለች ቅጥር ሠራተኛ ናት።
ልክ እሱ እሷን ሲያይ፤ እሷም ቀስ ብላ በቆረጣ አየችውና ጠቀሰቸው፡፡
“በኔ ተማመኝ አሁን ነው የማቀላጥፋት በሚል ስሜት
ከንፈሩን ወደ ጎን አጣሞ የግራ ዐይኑን ጨፈን አደረገው። ተግባቡ።
እንደ እውነቱ ከሆነ እንደሻው እዚህም እዚያም እያለ ከሚልከሰከስ፤ ይህችን የመሰለች ልጅ መቀላጠፍ ብቻ ሳይሆን ቢያገባት የወ/ሮ አረጋሽ ምኞች ነበር፡፡ በዚህ የተጀመረው ትውውቅ ቀጠለ፡፡ አበራ በዚያን ዕለት አልነበረም፡፡ እንደሻው ድሮ ወደዚያ ሱቅ ዝር እንደማይል ሁሉ ትህትናን ካየ በኋላ ያንን የጫማ ሱቅ እንደ ቤተ ክርስቲያን ሳይሳለም ወደራሱ
ሱቅ መሄድ አቆመ፡፡
ምንም እንኳን እግሩ እስከሚቀጥንድረስ ቢመላለስም መጀመሪያ አይቷት እንደገመተው ግን አልሆነችለትም፡፡
“እንደሻው በዚህ በኩል ያለህ ሃሳብ ቢለወጥና ጥሩ ወንድሜ ሆነህ ጓደኝነታችን ቢቀጥል ደስታውን አልችለውም:: ከማንም አንሰህ
ሳይሆን፤ የግሌ በሆነ ምክንያት ብቻ ጥያቄህን ለመቀበል ስለማልችል
እባክህን ይቅርታ አድርግልኝ?” ብላ ለመነችው። -
“ምንድነው የግል ችግርሽ?” ሲል ደጋግሞ ጠየቃት፡፡
“እጮኛ አለኝ” ስትል ቁርጡን ነገረችው፡፡
እንደሻው ግን እንኳን እጮኛ ባሏ ቢሆን ደንታ የሌለው አጥር ዘላይ መሆኑን
አላወቀችም ብትለምነው ብትማፀነው
እሷን ካልቀመሰ እንደሚሞት ሁሉ እሺ ካላለችው፤ ከስራ እንድትባረር ከማድረግ ወደ ኋላ እንደማይል እየገለጸ፤ ያስፈራራት፤ ጀመር፡፡
ይህ ጊዜያዊ ስሜቱ ቀስ በቀስ እንደሚለወጥና፤ ልመናዋን እንደሚቀበላት ተማምና፤በምታገኘው ጊዜ ሁላ በጸባይ ትቀርበው ነበር።
እንደሻው እንዳስበው ሳይሳካለት መቅረቱን ሲያውቅ አማላጅ አድርጐ የላካት ወ/ሮ አረጋሽ ትህትናን ለብቻዋ ጠራቻትና...ትሁት በእጅ የያዙት ወርቅ ከመዳብ ይቆጠራል አይነት ሆንሽብኝ እኮ!
ምንም ትንሽ ልጅ ብትሆኝ አመለካከትሽ ብስል መሆኑን ከተረዳሁት ውዬ አድሬአለሁ። አሁን ግን ሳይሽ ልጅነትሽ የለቀቀሽ አልመስል አለኝ፡፡
ሰማሽ የኔ ልጅ? ዕድል እጅ ላይ የምትወድቀው አንድ ጊዜ ብቻ ነው።
እንደገባችም ካልተጠቀሙባትና አንዴ ካለፈች ደግሞ በፀፀት ትጎዳለች እንጂ
ተመልሳ አትገኝም። በዚህ በቁንጅና ወቅት በዚህ በልጅነት ጊዜ ችላ
የተባለ እድል ደግሞ በእኛ ዕድሜ ላይ ከደረሱ በኋላ ና! ብለው ቢለምኑት፤ ቢጣሩት፤ ተመልሶ አይመጣም፡፡እንደታኘከ የሸንኮራ አገዳ መመጠጥና የትም ተጥሎ መቅረት ነው ትርፉ። ልብሽ ልብ ይበል!፡፡ ዛሬ የደነደነው ልብሽ ነግ ደም እንዳያለቅስ?። እግዚአብሔር ከዚህ የሀብት ባህር ውስጥ አምጥቶ ሲጥልሽ፤ በየወሩ አፍንጫዬ ላይ የሚወረወርልኝ
ሳንቲም ይበልጥብኛል ብለሽ ይህንን ሁሉ ሀብት ንብረት ብትገፊ፧
ዕድልሽ የተገፋ ነው የሚሆነው :: እወቂበት፡፡ የዚህ ቤት የሽማግሌው
አጠቃላይ ንብረት ወራሽ እንደሻው መሆኑን አትዘንጊ!! የጠየቀሽን
አድርገሽ ልጥፍ፤ ጥብቅ፧ ነው ልጄ ዋእ...!”
ያልደሰኮረችላት ዲስኩር አልነበረም፡፡ ትህትና ወይ ንቅንቅ!
“አመሰግናለሁ እትዬ አረጋሽ፡፡ ያለሽ ቀና አመለካከት፣ ምክርሽም ሁሉ ለኔ ጥሩ በመመኘት፣ እኔ ጥሩ ደረጃ ላይ እንድደርስ በማስብ እስከሆነ
ድረስ ከልቤ ነው የማመሰግንሽ :: እንደሻው ቢበዛብኝ እንጂ አንሶኝ
እንዳልሆነ አምናለሁ፡፡ በሁሉም ረገድ ከኔ የበለጠች ማግኘት የሚችል ሲሆን እኔ ግን ለሱ የማልገባ እዚህ ግቢ የማልባል መናጢ ደሀ መሆኔንም አልዘነጋሁትም፡፡ ይህንን ሁሉ ደግሞ ለሱ ነግሬዋለሁ። እትዬ አረጋሽ የማፈቅረው ጓደኛ አለኝ፡፡ በሱ ላይ ደርቤ ማፍቀር አልችልም፡፡
እባክሽን ይቅርታ እንዲያደርግልኝና ሀሳቡን እንዲለውጥ ለምኝልኝ?”
በማለት እግሯ ላይ ወድቃ እያለቀሰች ለመነቻት፡፡
ወ/ሮ አረጋሽ በልጅቷ ንግግር ልቧ ቢነካም፤ ጉልበተኛው እንደሻው ያጋጨኛል ብላ ስለፈራች! የአደራ መልዕክቱን ለእንደሻው ሳታደርስላት ቀረች፡፡
የወይዘሮ አረጋሽ አማላጅነት
በቀጠሮ እየተጓተተ ውጤት የማይታይበት ሆኖ በመገኘቱ እንደሻው ተናደደና አበራን አማከረው::
“ይህቺ ጭንጋፍ አሮጊት ያነጋገረቻት አልመሰለኝም፡፡በንዴት መንጋጭላዋን ከማውለቄ በፊት ምን አለበት ብትገላግለኝ?!” ሲል ለአበራ ጥያቄ አቀረበለት፡፡
“እንዴት ማለት?”
“ትህትናን በጣም አፍቅሬአታለሁ፡፡ በተደጋጋሚ አነጋግሬአታላሁ፡፡ፈቀደኛ አልሆነችም፡፡ እሺ ብትላት ብዬ አበራሽን አማላጅነት ልኬባት ነበር፡፡ ለሷም እሺ ያለቻት አልመሰለኝም፡፡ አንተ አለቃዋ ስለሆንክ ልትፈራህ ትችላለች፡፡ በእውነት ነው የምልህ አበራ የወደድኳት፡፡ በቀላሉ አገኛታለሁ ብዬ ነበር የገመትኩት፡፡ እንደገመትኩት አልሆነም፡፡ ልታግባባልኝ የምትችለው የመጨረሻው ሰው አንተ ብቻ ነህ፡፡” ለመነው፡፡ እንደሻው እንደተስገበገበባት ከሁኔታው ተገነዘበ፡፡
አበራና እንደሻው ፍቅራቸው በከፈቱት ንግድ ምክንያት እየጠበቀ የሄደ
ሽሪኮች ስለሆኑ እምቢ ሊለው አልፈለገም።
“አይዞሽ! እንደሻው ሁሉንም ነገር ለኔ ተይው! እኔ እጨርሰዋለሁ! በኔ ተማመኝ!” ጀርባውን ቸብ፤ ቸብ፤ በማድረግ ተስፋ በተስፋ አደረገው። አበራ ሙሉ በሙሉ ተማምኖ የእሺታ ቃሏን ለመቀበል ብቻ ያነጋገራት
“ልሸኝሽ በማለት በመኪና ውስጥ ካስገባት በኋላ ነበር፡፡
ስሚ ትህትና!” ፊት ለፊት እየተመለከተና መሪውን እያስተካከለ።
“አቤት ጋሽ አበራ” አንድ የሚነግራት ነገር እንዳለ በመጠራጠር ስሜት ወደጐን እያየችው፡፡
“እንደሻው አነጋግሮሽ ነበር መሰለኝ” መሪውን በእጁ እየመታ።
“ስለምኑ?”
“ያው ነዋ!! እንደሚወድሽ” ፍርጥ አደረገው፡፡ ምን ዙሪያ ጥምጥም
መሄድ ያስፈልጋል?።
ትንሽ እንደማፈር አለችና በኃይል መምታት የጀመረው ልቧ ሲረጋጋላት፡-
“አነጋገርኳት አለ እንዴ?” አለችው፡፡
“ከዚያም አልፎ አረጋሽንም እንደላከብሽ ሳይደብቅ አጫውቶኛል” እየሳቀ።
“
አዎን እንደሱ ነው”ውጭ ውጭውን በመስታወቱ አሻግራ እየተመለከተች፡፡
“ታዲያ ምን መልስ ሰጠሽው?”
“ያው እንደነገረህ ነዋ ጋሽ አበራ?” የሰጠችውን መልስ እያወቀ
እንደሚጠይቃት ገብቷታል።
" መልሱ ያንቺ መሆኑ አጠራጥሮኝ ነው እኮ የምጠይቅሽ?” የአለቅነት ስሜቱ እየታገለው ነበር፡፡በዚህ ላይ ደግሞ ስራውን ምን ያህል እንደምትፈልገውና ችግረኛ መሆኗን በሚገባ ያውቃል፡፡
“ምንም አያጠራጥርም ጋሼ አበራ፡፡ በእርግጥ እንደሻው የሚጠላ ወይንም
ለኔ የሚያንስ ልጅ ሆኖ አይደለም። እንደኔ ያለች ደሃ እሱን
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ሁለት
፡
፡
#ድርሰት_በትክክል_ገና
“ጤና ይስጥልኝ ወይዘሪት እንዳሻው በቀለ.... እባላለሁ እራሱን በሚገባ አስተዋወቀ። እሷም ስሟን ሰጠችው። ፈርጣማ ወጠምሻ ነው።
“ምን ያህል ጊዜ ሆነሽ ሥራ ከጀመርሽ?” ድዱን እየገለፈጠ
“እንድ ሳምንት ሆኖኛል” በር በሩን እያየች::
“በስመአብ ይህንን ያክል ቀን ስትቆዪ ያለመምጣቴ ደደብ ያሰኘኛል”
“ለምን? ይኸው አሁን ተዋወቅን አይደል? ምን ልዩነት አለው?”
“ተይ እንጂ! ጊዜ እኮ የውጤት አብራክ ነው” ትንሽ እየተውረገረገ።
“እንዴት ማለት?”
“ከአንድ ውጤት ላይ ለመድረስ ድርጊት የሚወሰነው በጊዜ ውስጥ ነው
ማለቴ ነው” ሊፈላሰፍባት ሞከረ፡፡
“አልገባኝም?”::
እንደሻው በልቡ “ተይ እንጂ ቆንጂት? አንድ ሳምንት እኮ ለጥብስ የምትበቂበት ጊዜ ነበር፡፡ አሁን ግን ገና ጥሬ ነሽ፡፡ አንድ
ተጨማሪ የማብሰያ ሳምንት ሳትወስጅብኝ አትቀሪም” አለ፡፡
“ማለቴ ይሄኔ በደንብ ተዋውቀን፣ ተግባብተን፤ ሞቅ ያልን ጓደኛሞች መሆን የምንችልበት ጊዜ ነበር ማለቴ ነው”
ወደ ወ/ሮ አረጋሽ በቆረጣ ተመለከተ።
ወ/ሮ አረጋሽ በዕድሜ ጠና ያለች በዚህ ሱቅ ውስጥ ለረጅም አመታት ተቀጥራ ያገለገለች ቅጥር ሠራተኛ ናት።
ልክ እሱ እሷን ሲያይ፤ እሷም ቀስ ብላ በቆረጣ አየችውና ጠቀሰቸው፡፡
“በኔ ተማመኝ አሁን ነው የማቀላጥፋት በሚል ስሜት
ከንፈሩን ወደ ጎን አጣሞ የግራ ዐይኑን ጨፈን አደረገው። ተግባቡ።
እንደ እውነቱ ከሆነ እንደሻው እዚህም እዚያም እያለ ከሚልከሰከስ፤ ይህችን የመሰለች ልጅ መቀላጠፍ ብቻ ሳይሆን ቢያገባት የወ/ሮ አረጋሽ ምኞች ነበር፡፡ በዚህ የተጀመረው ትውውቅ ቀጠለ፡፡ አበራ በዚያን ዕለት አልነበረም፡፡ እንደሻው ድሮ ወደዚያ ሱቅ ዝር እንደማይል ሁሉ ትህትናን ካየ በኋላ ያንን የጫማ ሱቅ እንደ ቤተ ክርስቲያን ሳይሳለም ወደራሱ
ሱቅ መሄድ አቆመ፡፡
ምንም እንኳን እግሩ እስከሚቀጥንድረስ ቢመላለስም መጀመሪያ አይቷት እንደገመተው ግን አልሆነችለትም፡፡
“እንደሻው በዚህ በኩል ያለህ ሃሳብ ቢለወጥና ጥሩ ወንድሜ ሆነህ ጓደኝነታችን ቢቀጥል ደስታውን አልችለውም:: ከማንም አንሰህ
ሳይሆን፤ የግሌ በሆነ ምክንያት ብቻ ጥያቄህን ለመቀበል ስለማልችል
እባክህን ይቅርታ አድርግልኝ?” ብላ ለመነችው። -
“ምንድነው የግል ችግርሽ?” ሲል ደጋግሞ ጠየቃት፡፡
“እጮኛ አለኝ” ስትል ቁርጡን ነገረችው፡፡
እንደሻው ግን እንኳን እጮኛ ባሏ ቢሆን ደንታ የሌለው አጥር ዘላይ መሆኑን
አላወቀችም ብትለምነው ብትማፀነው
እሷን ካልቀመሰ እንደሚሞት ሁሉ እሺ ካላለችው፤ ከስራ እንድትባረር ከማድረግ ወደ ኋላ እንደማይል እየገለጸ፤ ያስፈራራት፤ ጀመር፡፡
ይህ ጊዜያዊ ስሜቱ ቀስ በቀስ እንደሚለወጥና፤ ልመናዋን እንደሚቀበላት ተማምና፤በምታገኘው ጊዜ ሁላ በጸባይ ትቀርበው ነበር።
እንደሻው እንዳስበው ሳይሳካለት መቅረቱን ሲያውቅ አማላጅ አድርጐ የላካት ወ/ሮ አረጋሽ ትህትናን ለብቻዋ ጠራቻትና...ትሁት በእጅ የያዙት ወርቅ ከመዳብ ይቆጠራል አይነት ሆንሽብኝ እኮ!
ምንም ትንሽ ልጅ ብትሆኝ አመለካከትሽ ብስል መሆኑን ከተረዳሁት ውዬ አድሬአለሁ። አሁን ግን ሳይሽ ልጅነትሽ የለቀቀሽ አልመስል አለኝ፡፡
ሰማሽ የኔ ልጅ? ዕድል እጅ ላይ የምትወድቀው አንድ ጊዜ ብቻ ነው።
እንደገባችም ካልተጠቀሙባትና አንዴ ካለፈች ደግሞ በፀፀት ትጎዳለች እንጂ
ተመልሳ አትገኝም። በዚህ በቁንጅና ወቅት በዚህ በልጅነት ጊዜ ችላ
የተባለ እድል ደግሞ በእኛ ዕድሜ ላይ ከደረሱ በኋላ ና! ብለው ቢለምኑት፤ ቢጣሩት፤ ተመልሶ አይመጣም፡፡እንደታኘከ የሸንኮራ አገዳ መመጠጥና የትም ተጥሎ መቅረት ነው ትርፉ። ልብሽ ልብ ይበል!፡፡ ዛሬ የደነደነው ልብሽ ነግ ደም እንዳያለቅስ?። እግዚአብሔር ከዚህ የሀብት ባህር ውስጥ አምጥቶ ሲጥልሽ፤ በየወሩ አፍንጫዬ ላይ የሚወረወርልኝ
ሳንቲም ይበልጥብኛል ብለሽ ይህንን ሁሉ ሀብት ንብረት ብትገፊ፧
ዕድልሽ የተገፋ ነው የሚሆነው :: እወቂበት፡፡ የዚህ ቤት የሽማግሌው
አጠቃላይ ንብረት ወራሽ እንደሻው መሆኑን አትዘንጊ!! የጠየቀሽን
አድርገሽ ልጥፍ፤ ጥብቅ፧ ነው ልጄ ዋእ...!”
ያልደሰኮረችላት ዲስኩር አልነበረም፡፡ ትህትና ወይ ንቅንቅ!
“አመሰግናለሁ እትዬ አረጋሽ፡፡ ያለሽ ቀና አመለካከት፣ ምክርሽም ሁሉ ለኔ ጥሩ በመመኘት፣ እኔ ጥሩ ደረጃ ላይ እንድደርስ በማስብ እስከሆነ
ድረስ ከልቤ ነው የማመሰግንሽ :: እንደሻው ቢበዛብኝ እንጂ አንሶኝ
እንዳልሆነ አምናለሁ፡፡ በሁሉም ረገድ ከኔ የበለጠች ማግኘት የሚችል ሲሆን እኔ ግን ለሱ የማልገባ እዚህ ግቢ የማልባል መናጢ ደሀ መሆኔንም አልዘነጋሁትም፡፡ ይህንን ሁሉ ደግሞ ለሱ ነግሬዋለሁ። እትዬ አረጋሽ የማፈቅረው ጓደኛ አለኝ፡፡ በሱ ላይ ደርቤ ማፍቀር አልችልም፡፡
እባክሽን ይቅርታ እንዲያደርግልኝና ሀሳቡን እንዲለውጥ ለምኝልኝ?”
በማለት እግሯ ላይ ወድቃ እያለቀሰች ለመነቻት፡፡
ወ/ሮ አረጋሽ በልጅቷ ንግግር ልቧ ቢነካም፤ ጉልበተኛው እንደሻው ያጋጨኛል ብላ ስለፈራች! የአደራ መልዕክቱን ለእንደሻው ሳታደርስላት ቀረች፡፡
የወይዘሮ አረጋሽ አማላጅነት
በቀጠሮ እየተጓተተ ውጤት የማይታይበት ሆኖ በመገኘቱ እንደሻው ተናደደና አበራን አማከረው::
“ይህቺ ጭንጋፍ አሮጊት ያነጋገረቻት አልመሰለኝም፡፡በንዴት መንጋጭላዋን ከማውለቄ በፊት ምን አለበት ብትገላግለኝ?!” ሲል ለአበራ ጥያቄ አቀረበለት፡፡
“እንዴት ማለት?”
“ትህትናን በጣም አፍቅሬአታለሁ፡፡ በተደጋጋሚ አነጋግሬአታላሁ፡፡ፈቀደኛ አልሆነችም፡፡ እሺ ብትላት ብዬ አበራሽን አማላጅነት ልኬባት ነበር፡፡ ለሷም እሺ ያለቻት አልመሰለኝም፡፡ አንተ አለቃዋ ስለሆንክ ልትፈራህ ትችላለች፡፡ በእውነት ነው የምልህ አበራ የወደድኳት፡፡ በቀላሉ አገኛታለሁ ብዬ ነበር የገመትኩት፡፡ እንደገመትኩት አልሆነም፡፡ ልታግባባልኝ የምትችለው የመጨረሻው ሰው አንተ ብቻ ነህ፡፡” ለመነው፡፡ እንደሻው እንደተስገበገበባት ከሁኔታው ተገነዘበ፡፡
አበራና እንደሻው ፍቅራቸው በከፈቱት ንግድ ምክንያት እየጠበቀ የሄደ
ሽሪኮች ስለሆኑ እምቢ ሊለው አልፈለገም።
“አይዞሽ! እንደሻው ሁሉንም ነገር ለኔ ተይው! እኔ እጨርሰዋለሁ! በኔ ተማመኝ!” ጀርባውን ቸብ፤ ቸብ፤ በማድረግ ተስፋ በተስፋ አደረገው። አበራ ሙሉ በሙሉ ተማምኖ የእሺታ ቃሏን ለመቀበል ብቻ ያነጋገራት
“ልሸኝሽ በማለት በመኪና ውስጥ ካስገባት በኋላ ነበር፡፡
ስሚ ትህትና!” ፊት ለፊት እየተመለከተና መሪውን እያስተካከለ።
“አቤት ጋሽ አበራ” አንድ የሚነግራት ነገር እንዳለ በመጠራጠር ስሜት ወደጐን እያየችው፡፡
“እንደሻው አነጋግሮሽ ነበር መሰለኝ” መሪውን በእጁ እየመታ።
“ስለምኑ?”
“ያው ነዋ!! እንደሚወድሽ” ፍርጥ አደረገው፡፡ ምን ዙሪያ ጥምጥም
መሄድ ያስፈልጋል?።
ትንሽ እንደማፈር አለችና በኃይል መምታት የጀመረው ልቧ ሲረጋጋላት፡-
“አነጋገርኳት አለ እንዴ?” አለችው፡፡
“ከዚያም አልፎ አረጋሽንም እንደላከብሽ ሳይደብቅ አጫውቶኛል” እየሳቀ።
“
አዎን እንደሱ ነው”ውጭ ውጭውን በመስታወቱ አሻግራ እየተመለከተች፡፡
“ታዲያ ምን መልስ ሰጠሽው?”
“ያው እንደነገረህ ነዋ ጋሽ አበራ?” የሰጠችውን መልስ እያወቀ
እንደሚጠይቃት ገብቷታል።
" መልሱ ያንቺ መሆኑ አጠራጥሮኝ ነው እኮ የምጠይቅሽ?” የአለቅነት ስሜቱ እየታገለው ነበር፡፡በዚህ ላይ ደግሞ ስራውን ምን ያህል እንደምትፈልገውና ችግረኛ መሆኗን በሚገባ ያውቃል፡፡
“ምንም አያጠራጥርም ጋሼ አበራ፡፡ በእርግጥ እንደሻው የሚጠላ ወይንም
ለኔ የሚያንስ ልጅ ሆኖ አይደለም። እንደኔ ያለች ደሃ እሱን
👍1🔥1
#በፍቅር_ላይ_ሾተላይ
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ሶስት
፡
፡
#ድርሰት_በትክክል_ገና
ሻምበል ብሩክና ትህትና ድንበሩ ከተዋወቁ ዛሬ ልክ አንድ ወራቸው፡፡ የፍቅራቸው ወርሃዊ ልደት ውል የሚበጅበት ቀን በመሣሣም ደረጃ የቆየው ፍቅር ዛሬ ወደ አካላዊ ውህደት ሊሸጋገር እቅድ ተይዞለታል። ሻምበል ብሩክም ሆነ ትህትና የዛሬውን ቀን በልዩ ጉጉት ነው የጠበቁት።
እሁድ ዕለት አሥመራ መንገድ በሚገኘው በሻምበል ብሩክ ቤት ለማደር የወሰነችበት ቀን ነበር፡፡ ወደ ዶክተር ባይከዳኝ ቀጠሮ ስትሄድ የሚሰማት ስሜት ከቀጠሮው በስተጀርባ ባለው ምክንያት አስገዳጅነት እንጂ በፍቅር አስገዳጅነት አልነበረም፡፡
ከዶክተር ባይከዳኝ ጋር የምትፈጽማቸው ግንኙነቶች እውነተኛ ስሜቷን የምትገልጽባቸው ሳይሆኑ፤ በተላበሰችው ጭምብል እውነተኛ ማንነቷን ደብቃ፤ በመድረክ ላይ ትያትር የምትሰራ ተዋናይ ሆና ነው የምትውለው፡፡ በሻምበል ብሩክ ፍቅር ግን ሰውነቷ እንደሻማ እየቀለጠ፣
ልቧ በዕልልታ እየጨፈረች፤ ሁለንተናዋን አሳልፋ የምትሰጠው በደስታ ስሜት ሰክራ ነው፡፡ በተለይ የመጀመሪያዋ በሆነው የወንድ ልጅ ፍቅር የተረታችለት ሰው፤ እንደዘመኑ ወጣቶች በአንድ ነገር ላይ ብቻ ትኩረት የሚሰጥ ሳይሆን በሷ ቦታ ሆኖ ሁሉን ነገር የሚያስብላትና፤
የሚያጽናናት፤ ሆኖ በመገኘቱ ፈጣሪዋን ታመሰግናለች፡፡
ብቻ አንዳንድ ጊዜ የሰው ልጅ ሥጋ ለባሽ ፍጡር ነውና፣ ሰው ተላላና ደካማ ፍጡር ነውና፤ ሰው ሰው ነውና፤ ይህ ሁሉ ፍቅር ድንገት ብን ብሎ ጠፍቶ፣ ሻምበል ብሩክም ተለውጦ፣ እንዳይከዳት ልቧ
መጠርጠሩ አልቀረም፡፡
እንደዚያ ታስብና ደግሞ አስተሳሰቧ ትክክል ባለመሆኑ እራሷን ወቅሳ “ብሩኬ አይለወጥም”
በማለት መልሳ መጽናናትን ታሳድራለች፡፡ በዛሬው ዕለት ሻምበል ብሩክ ቤት ለማደር ቀጠሮውን በልቧ የወሰደችው በከፍተኛ ደስታ ነው። ምናልባት የዛሬው አዳር ደግሞ ያንን ተንከባክባ ያቆየችውን የልጃገረድነት ወግ፣ ብር አምባሯን የምትፈተሽበት ወቅት ሊሆን ይችላል፡፡ ከዚያ በኋላ “ዞር በይ” ቢላትስ? ልቧ
በመጠራጠርና፤ ባለመጠራጠር፤ስሜት መሀል ገብቶ ሲዋዥቅ ከዋለ በኋላ
አንድ ነገር አሰበች።
ለሻምበል ብሩክ ልጃገረድ መሆኗን ገልጻለት፤ እንደ ወጉ፤ እንደ ሥርዐቱ፤ በጫጉላ ቤት ብር አምባሯን ልትሰጠው ያላትን ምኞች የሱን ስሜትና ፍላጐት ከተረዳች በኋላ ካሳወቀችውና በአጠቃላይ ስለማንኛውም ነገር አብረው በጋራ መወሰን እንደሚችሉ ገምታ፤ በዚሁ ሃሳብ ፀናች።
“እማይዬ ዛሬ አዜቢና ጋ ነው የማድረው ፓርቲ አዘጋጅታለች' በማለት እናቷን ዋሸቻት።
“ባርቲ ደግሞ ምንድነው ትሁቴ?” እናት በመጠራጠር ስሜት፡፡
“ያው ነዋ! ጓደኞቿ ተሰባስበን ስንጫወት ማደር ማለት ነዋ!” እየሳቀች፡፡
አደራሽን የኔ እራስሽን ጠብቂ!!” እናቷ ዐይን ዐይኖቿን እያየቻት።የውጭ አዳር የተሰማው ገና ዛሬ ነው፡፡
“ምንም ችግር የለም:: ማሚ ሙች!” ጉንጫን ሳመቻት፡፡ እናቷ በልቧ
ዝግጅቷን አሰበችው፡፡ በጠዋት ተነስቶ መተጣጠቡ፣ ቀኑን ሙሉ ሲመረጥ የተዋለው ልብስ፣ ሦስት ጊዜ አውልቃ ቀይራለች። መስተዋቱ ሥራ አልፈታም፡፡ መኳኳሉ ሁሉ ያልተለመደ ነበር።
በልቧ ወደ ሻምበል ብሩክ እንደምትሄድ ብታውቀውም የሰጠቻትን ምክንያት ይሁን ብላ ተቀበለቻት፡፡
ዛሬ ሻምበል ብሩክ ጋ የምታድር መሆኗን ለአንዱአለም ስለነገረችው በጊዜ ወደቤት እንዲገባ ተስማምተዋል። በዚህ ላይ የቤት ሰራተኛዋ እታፈራሁ ታክላበት እናቷን በመንከባከብ በኩል ኃላፊነቱን
ስለሚወስዱ የሚያስጨንቃት ነገር አልነበረም፡፡ ሁሉንም አጥብቃ አደራ
ብላ፤ ከቤት የወጣችው ከቀኑ አሥራ ሁለት ሰዓት ላይ ነበር።
ሻምበል ብሩክ ዛሬ ሽር ጉድ ሲል አርፍዷል። አልጋው ቦታ ሲመረጥለት፤ ሲንከራተት፤ የቤቱ ቁሳቁሶች በሙሉ በአዲስ መልክ አንዴ በጭንቅላታቸው፧ አንዴ በእግራቸው፤ ሲቆሙ፤ ቦታ ሲመረጥላቸው ነው የተዋለው፡፡
በዛሬው የቤት ዝግጅት ላይ ሠራተኛዋ ብቻ ሳትሆን ሁለቱም ታናናሽ ወንድሞቹ አብረውት ቤቱን ሲያተራምሱት ነው የዋሉት፡፡
በመጨረሻ ላይ ግን ከዚያ በፊት ያልታየበት ዓይነት ሥርዓትና መልክ ይዞ ሲያይ ሻምበል ብሩክ ተደነቀ፡፡
በእርግጥም ይህ ሁሉ የሆነው በትህትና ምክንያት መሆኑን ሲያስብ፤ የትዳር ውጥኑ አግባብ መሆኑን አመነ። በዚያ በቤቱ ሥርዓት ተማርኮ ወደሌላ ሃሳብ ውስጥ ገባ፡፡
ባለፋቸው መጥፎ ጊዜያቶች ውስጥ የተጐዳ ልቡ፣ በትህትና የወደፊት የትዳር እመቤቱ አማካይነት ሊታደስና፤ ሲታነጽ፤ ታየው።
እናም የትዳር መዓዛ በርቀት ሸተተው፡፡ ይህ በርቀት የሚሸተው የትዳር መዓዛ ቀርቦ እንዲያውደው ተመኘ፡፡
ትህትና እስከምትመጣለት የቀጠሮው ሰዓት እስከሚደርስ ድረስ ተንቆራጠጠ።
ዛሬ የሚነግራት ትልቅ ጉዳይ አለው። እሷም እንደሱ በጉዳዩ
ላይ ፈቃደኛ ከሆነች ጉዳዩ የምሥራች ይሆናል። እሷን የፈለጋት ጊዜያዊ
ፍቅረኛ እንድትሆነው ሳይሆን፤ ዘላቂ የትዳር ጓደኛው እንድትሆን ነው::
ይህ እሱ የጓጓለትን በፀጋ ከተቀበለችለት ደስታው እጥፍ ድርብ ይሆናል፡፡
“ትሁት.. ትሁት.. ትሁት.. ስሟን ደጋገመው። በልቡ፡፡
ልክ ከምሽቱ አንድ ሰዓት ላይ ታላቋ እንግዳ የዱር ጽጌረዳ መስላ አምራና፤ ደምቃ ከች! አለች፡፡ ቤቱን ከዚህ ቀደም አንድ ሁለት ጊዜ አይታዋለች፡፡ የዛሬውን ልዩ የሚያደርገው ለማደር ወስና የመጣችበት ዕለት በመሆኑ ነው፡፡
ሻምበል ብሩክ ከደጅ ወጥቶ እየተጠባበቃት ነበር። በሁለመናው
አቅፎ ተቀበላት፡፡
ከዚያም አጥሩን ዘልቀው እየተሳሳቁ፣ እጅ ለእኛ ተያይዘው ወደ ቤት ገቡ፡፡
የሻምበል ብሩክ ሁለት ታናናሽ ወንድሞቹ ሰላምታ አቅርበውላት ትንሽ ከተጫወቱ በኋላ የግል ነፃነት ሊሰጧቸው ወጡ።
ዛሬ የሻምበል ብሩክ ቤት ልዩ ሆናለች:: ትህትናም ከዚያ በፊት ያየቸው ቤት መሆኑ እስከሚያጠራጠራት ድረስ የቤት ዕቃዎቹ አቀማመጥ አስደንቋታል፡፡
ሻምበል ብሩክ የትዳር ምኞቱን ሊገልጽላት ሲያሰላስል፤ እሷ ደግሞ ሌላ የምትገልጽለት እጹብ ድንቅ የሆነ የምስራች ነበራት። ሻምበል ብሩክ በፍቅር ቢወድቅላትም፤ ከዚህ ሁሉ በላይ ደግሞ ያልገመተውን ገፀ በረከት ልታቀርብለት ማሰቧን ቢያውቅ ኖሮ ምንኛ ደስተኛ ይሆን ነበር?፣
ቀለል ያለ እራት ከበሉ በኋላ ይሄንን የቀዘቀዘ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቢራቸውን
መኮምኮም ቀጠሉ። ዛሬ ቢራው አልመረራትም። የፍቅር ስኳር
ተጨምሮበት ነው መሰል፤ ከምትወደው ሰው ጋር በፍቅር እየቀለጡ፤ ሲኮመኩሙት ማር ሆነና ቁጭ አለ፡፡ ከዶክተር ባይከዳኝ ጋር ሆና ስትጠጣው የግራዋ ጭማቂ ያህል ነበር የሚመራት። አሁን ግን ጣፈጣት፡፡
አንዱን ቢራ ጨረስችና በህይወቷ ለመጀመሪያ ጊዜ ሁለተኛውን የቢራ ጠርሙስ ጨበጠች፡፡ ሻምበል ብሩክ የወደፊት የትዳር ጓደኛው ከምትሆን ቆንጆ ጋር እያሳለፈ ባለው ጊዜ እጅግ ከመደሰቱም በላይ ከረጅም ዓመታት በፊት እጮኛው ከነበረችው በድሏ ጋር ያሳልፉ የነበረውን ዓይነት ልዩ ስሜት አጫረበትና፤ ጨዋታውን በሰፊው ቀጠለ። እየተቃቀፉ መላላሱ ፤ መሳሳሙ፤ ሁሉ ለጉድ ነበር፡፡
ከምሽቱ ሦስት ሰዓት ሲሆን ወደ መኝታ ክፍላቸው መሄድ ፈለጉ።
የመኝታ ክፍሏ በንጽህና የተጠበቀች ናት። እንደገቡ በነጭ ስስ የመጋረጃ ጨርቅ የተሸፈነውን ባለመስታወት መስኮት ሲገልጡት ፍንትው ብላ ደምቃ የወጣችው ጨረቃ ብርሃኗን ወደመኝታ ክፍላቸው ውስጥ አዘለቀችላቸው...
ያንን የጨረቃ ውበት ሲያስተውሉ፤ መብራቱን አጠፉት በዚያች ክፍል
ውስጥ ጨረቃና ፍቅር ነገሱ ከዚያም ልብሳቸውን እንደለበሱ አልጋቸው ላይ ጋደም ብለው መላፋታቸውን ቀጠሉ....
የትህትና ሁኔታ የተለየ ነበር ከዚያ በፊት ለወንድ ልጅ የነበራት ስሜት ምን እንደ ነበረና አሁን ምን እየሆነች እንዳለች
ስታስበው
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ሶስት
፡
፡
#ድርሰት_በትክክል_ገና
ሻምበል ብሩክና ትህትና ድንበሩ ከተዋወቁ ዛሬ ልክ አንድ ወራቸው፡፡ የፍቅራቸው ወርሃዊ ልደት ውል የሚበጅበት ቀን በመሣሣም ደረጃ የቆየው ፍቅር ዛሬ ወደ አካላዊ ውህደት ሊሸጋገር እቅድ ተይዞለታል። ሻምበል ብሩክም ሆነ ትህትና የዛሬውን ቀን በልዩ ጉጉት ነው የጠበቁት።
እሁድ ዕለት አሥመራ መንገድ በሚገኘው በሻምበል ብሩክ ቤት ለማደር የወሰነችበት ቀን ነበር፡፡ ወደ ዶክተር ባይከዳኝ ቀጠሮ ስትሄድ የሚሰማት ስሜት ከቀጠሮው በስተጀርባ ባለው ምክንያት አስገዳጅነት እንጂ በፍቅር አስገዳጅነት አልነበረም፡፡
ከዶክተር ባይከዳኝ ጋር የምትፈጽማቸው ግንኙነቶች እውነተኛ ስሜቷን የምትገልጽባቸው ሳይሆኑ፤ በተላበሰችው ጭምብል እውነተኛ ማንነቷን ደብቃ፤ በመድረክ ላይ ትያትር የምትሰራ ተዋናይ ሆና ነው የምትውለው፡፡ በሻምበል ብሩክ ፍቅር ግን ሰውነቷ እንደሻማ እየቀለጠ፣
ልቧ በዕልልታ እየጨፈረች፤ ሁለንተናዋን አሳልፋ የምትሰጠው በደስታ ስሜት ሰክራ ነው፡፡ በተለይ የመጀመሪያዋ በሆነው የወንድ ልጅ ፍቅር የተረታችለት ሰው፤ እንደዘመኑ ወጣቶች በአንድ ነገር ላይ ብቻ ትኩረት የሚሰጥ ሳይሆን በሷ ቦታ ሆኖ ሁሉን ነገር የሚያስብላትና፤
የሚያጽናናት፤ ሆኖ በመገኘቱ ፈጣሪዋን ታመሰግናለች፡፡
ብቻ አንዳንድ ጊዜ የሰው ልጅ ሥጋ ለባሽ ፍጡር ነውና፣ ሰው ተላላና ደካማ ፍጡር ነውና፤ ሰው ሰው ነውና፤ ይህ ሁሉ ፍቅር ድንገት ብን ብሎ ጠፍቶ፣ ሻምበል ብሩክም ተለውጦ፣ እንዳይከዳት ልቧ
መጠርጠሩ አልቀረም፡፡
እንደዚያ ታስብና ደግሞ አስተሳሰቧ ትክክል ባለመሆኑ እራሷን ወቅሳ “ብሩኬ አይለወጥም”
በማለት መልሳ መጽናናትን ታሳድራለች፡፡ በዛሬው ዕለት ሻምበል ብሩክ ቤት ለማደር ቀጠሮውን በልቧ የወሰደችው በከፍተኛ ደስታ ነው። ምናልባት የዛሬው አዳር ደግሞ ያንን ተንከባክባ ያቆየችውን የልጃገረድነት ወግ፣ ብር አምባሯን የምትፈተሽበት ወቅት ሊሆን ይችላል፡፡ ከዚያ በኋላ “ዞር በይ” ቢላትስ? ልቧ
በመጠራጠርና፤ ባለመጠራጠር፤ስሜት መሀል ገብቶ ሲዋዥቅ ከዋለ በኋላ
አንድ ነገር አሰበች።
ለሻምበል ብሩክ ልጃገረድ መሆኗን ገልጻለት፤ እንደ ወጉ፤ እንደ ሥርዐቱ፤ በጫጉላ ቤት ብር አምባሯን ልትሰጠው ያላትን ምኞች የሱን ስሜትና ፍላጐት ከተረዳች በኋላ ካሳወቀችውና በአጠቃላይ ስለማንኛውም ነገር አብረው በጋራ መወሰን እንደሚችሉ ገምታ፤ በዚሁ ሃሳብ ፀናች።
“እማይዬ ዛሬ አዜቢና ጋ ነው የማድረው ፓርቲ አዘጋጅታለች' በማለት እናቷን ዋሸቻት።
“ባርቲ ደግሞ ምንድነው ትሁቴ?” እናት በመጠራጠር ስሜት፡፡
“ያው ነዋ! ጓደኞቿ ተሰባስበን ስንጫወት ማደር ማለት ነዋ!” እየሳቀች፡፡
አደራሽን የኔ እራስሽን ጠብቂ!!” እናቷ ዐይን ዐይኖቿን እያየቻት።የውጭ አዳር የተሰማው ገና ዛሬ ነው፡፡
“ምንም ችግር የለም:: ማሚ ሙች!” ጉንጫን ሳመቻት፡፡ እናቷ በልቧ
ዝግጅቷን አሰበችው፡፡ በጠዋት ተነስቶ መተጣጠቡ፣ ቀኑን ሙሉ ሲመረጥ የተዋለው ልብስ፣ ሦስት ጊዜ አውልቃ ቀይራለች። መስተዋቱ ሥራ አልፈታም፡፡ መኳኳሉ ሁሉ ያልተለመደ ነበር።
በልቧ ወደ ሻምበል ብሩክ እንደምትሄድ ብታውቀውም የሰጠቻትን ምክንያት ይሁን ብላ ተቀበለቻት፡፡
ዛሬ ሻምበል ብሩክ ጋ የምታድር መሆኗን ለአንዱአለም ስለነገረችው በጊዜ ወደቤት እንዲገባ ተስማምተዋል። በዚህ ላይ የቤት ሰራተኛዋ እታፈራሁ ታክላበት እናቷን በመንከባከብ በኩል ኃላፊነቱን
ስለሚወስዱ የሚያስጨንቃት ነገር አልነበረም፡፡ ሁሉንም አጥብቃ አደራ
ብላ፤ ከቤት የወጣችው ከቀኑ አሥራ ሁለት ሰዓት ላይ ነበር።
ሻምበል ብሩክ ዛሬ ሽር ጉድ ሲል አርፍዷል። አልጋው ቦታ ሲመረጥለት፤ ሲንከራተት፤ የቤቱ ቁሳቁሶች በሙሉ በአዲስ መልክ አንዴ በጭንቅላታቸው፧ አንዴ በእግራቸው፤ ሲቆሙ፤ ቦታ ሲመረጥላቸው ነው የተዋለው፡፡
በዛሬው የቤት ዝግጅት ላይ ሠራተኛዋ ብቻ ሳትሆን ሁለቱም ታናናሽ ወንድሞቹ አብረውት ቤቱን ሲያተራምሱት ነው የዋሉት፡፡
በመጨረሻ ላይ ግን ከዚያ በፊት ያልታየበት ዓይነት ሥርዓትና መልክ ይዞ ሲያይ ሻምበል ብሩክ ተደነቀ፡፡
በእርግጥም ይህ ሁሉ የሆነው በትህትና ምክንያት መሆኑን ሲያስብ፤ የትዳር ውጥኑ አግባብ መሆኑን አመነ። በዚያ በቤቱ ሥርዓት ተማርኮ ወደሌላ ሃሳብ ውስጥ ገባ፡፡
ባለፋቸው መጥፎ ጊዜያቶች ውስጥ የተጐዳ ልቡ፣ በትህትና የወደፊት የትዳር እመቤቱ አማካይነት ሊታደስና፤ ሲታነጽ፤ ታየው።
እናም የትዳር መዓዛ በርቀት ሸተተው፡፡ ይህ በርቀት የሚሸተው የትዳር መዓዛ ቀርቦ እንዲያውደው ተመኘ፡፡
ትህትና እስከምትመጣለት የቀጠሮው ሰዓት እስከሚደርስ ድረስ ተንቆራጠጠ።
ዛሬ የሚነግራት ትልቅ ጉዳይ አለው። እሷም እንደሱ በጉዳዩ
ላይ ፈቃደኛ ከሆነች ጉዳዩ የምሥራች ይሆናል። እሷን የፈለጋት ጊዜያዊ
ፍቅረኛ እንድትሆነው ሳይሆን፤ ዘላቂ የትዳር ጓደኛው እንድትሆን ነው::
ይህ እሱ የጓጓለትን በፀጋ ከተቀበለችለት ደስታው እጥፍ ድርብ ይሆናል፡፡
“ትሁት.. ትሁት.. ትሁት.. ስሟን ደጋገመው። በልቡ፡፡
ልክ ከምሽቱ አንድ ሰዓት ላይ ታላቋ እንግዳ የዱር ጽጌረዳ መስላ አምራና፤ ደምቃ ከች! አለች፡፡ ቤቱን ከዚህ ቀደም አንድ ሁለት ጊዜ አይታዋለች፡፡ የዛሬውን ልዩ የሚያደርገው ለማደር ወስና የመጣችበት ዕለት በመሆኑ ነው፡፡
ሻምበል ብሩክ ከደጅ ወጥቶ እየተጠባበቃት ነበር። በሁለመናው
አቅፎ ተቀበላት፡፡
ከዚያም አጥሩን ዘልቀው እየተሳሳቁ፣ እጅ ለእኛ ተያይዘው ወደ ቤት ገቡ፡፡
የሻምበል ብሩክ ሁለት ታናናሽ ወንድሞቹ ሰላምታ አቅርበውላት ትንሽ ከተጫወቱ በኋላ የግል ነፃነት ሊሰጧቸው ወጡ።
ዛሬ የሻምበል ብሩክ ቤት ልዩ ሆናለች:: ትህትናም ከዚያ በፊት ያየቸው ቤት መሆኑ እስከሚያጠራጠራት ድረስ የቤት ዕቃዎቹ አቀማመጥ አስደንቋታል፡፡
ሻምበል ብሩክ የትዳር ምኞቱን ሊገልጽላት ሲያሰላስል፤ እሷ ደግሞ ሌላ የምትገልጽለት እጹብ ድንቅ የሆነ የምስራች ነበራት። ሻምበል ብሩክ በፍቅር ቢወድቅላትም፤ ከዚህ ሁሉ በላይ ደግሞ ያልገመተውን ገፀ በረከት ልታቀርብለት ማሰቧን ቢያውቅ ኖሮ ምንኛ ደስተኛ ይሆን ነበር?፣
ቀለል ያለ እራት ከበሉ በኋላ ይሄንን የቀዘቀዘ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቢራቸውን
መኮምኮም ቀጠሉ። ዛሬ ቢራው አልመረራትም። የፍቅር ስኳር
ተጨምሮበት ነው መሰል፤ ከምትወደው ሰው ጋር በፍቅር እየቀለጡ፤ ሲኮመኩሙት ማር ሆነና ቁጭ አለ፡፡ ከዶክተር ባይከዳኝ ጋር ሆና ስትጠጣው የግራዋ ጭማቂ ያህል ነበር የሚመራት። አሁን ግን ጣፈጣት፡፡
አንዱን ቢራ ጨረስችና በህይወቷ ለመጀመሪያ ጊዜ ሁለተኛውን የቢራ ጠርሙስ ጨበጠች፡፡ ሻምበል ብሩክ የወደፊት የትዳር ጓደኛው ከምትሆን ቆንጆ ጋር እያሳለፈ ባለው ጊዜ እጅግ ከመደሰቱም በላይ ከረጅም ዓመታት በፊት እጮኛው ከነበረችው በድሏ ጋር ያሳልፉ የነበረውን ዓይነት ልዩ ስሜት አጫረበትና፤ ጨዋታውን በሰፊው ቀጠለ። እየተቃቀፉ መላላሱ ፤ መሳሳሙ፤ ሁሉ ለጉድ ነበር፡፡
ከምሽቱ ሦስት ሰዓት ሲሆን ወደ መኝታ ክፍላቸው መሄድ ፈለጉ።
የመኝታ ክፍሏ በንጽህና የተጠበቀች ናት። እንደገቡ በነጭ ስስ የመጋረጃ ጨርቅ የተሸፈነውን ባለመስታወት መስኮት ሲገልጡት ፍንትው ብላ ደምቃ የወጣችው ጨረቃ ብርሃኗን ወደመኝታ ክፍላቸው ውስጥ አዘለቀችላቸው...
ያንን የጨረቃ ውበት ሲያስተውሉ፤ መብራቱን አጠፉት በዚያች ክፍል
ውስጥ ጨረቃና ፍቅር ነገሱ ከዚያም ልብሳቸውን እንደለበሱ አልጋቸው ላይ ጋደም ብለው መላፋታቸውን ቀጠሉ....
የትህትና ሁኔታ የተለየ ነበር ከዚያ በፊት ለወንድ ልጅ የነበራት ስሜት ምን እንደ ነበረና አሁን ምን እየሆነች እንዳለች
ስታስበው
👍2🔥2❤1