አትሮኖስ
279K subscribers
110 photos
3 videos
41 files
458 links
╔╦╦╦═╦╗╔═╦═╦══╦═╗
║║║║╩╣╚╣═╣║║║║║╩╣
╚══╩═╩═╩═╩═╩╩╩
ግጥሞች አዳዲስና ቆየት ያሉ የታዋቂ ደራሲያን መፅሐፍቶችን በ PDF እንዲሁንም
ያልተነበቡ ድርሰቶችን ግጥሞችን ታሪኮችን ያገኙበታል።


Contact. @atronosebot
please dont touch the leave button.😔😳😳
Download Telegram
#ሰመመን


#ክፍል_ሰላሳ_ሦስት


#ድርሰት_በሲሳይ_ንጉሱ

...የጠዋት ፀሐይ ከመቼውም ይልቅ ፏ ብላ ወጥታለች ።
"እኔንም አንዳንዴ አስታውሱኝ ፤ ስለእኔ ውበት ድምቀትና ሙቀት ተወያዩ ” የምትል ትመስላለች ሆኖም ቀና ብሎ የሚያደንቃት ወይም ከልቡ ሆኖ የሚሞቃት ተማሪ አልነበረም ። ሁሉም በየፊናው ይሯሯጣል ። ዛሬ የጠዋት እንቅልፍ የሚያሸንፈው ተማሪ የለም ፡

ማዕበሉ በግቢው ውስጥ ተነሥቷል ። ተማሪው ከግፊቱ ለመዳን ይተራመሳል " ድምፅ የለሽ ትርምስ ይተራመሳል ።
ወደ ፈተና ሲገቡ የሚያኾ ትጥቅን ለማሟላት ! እርሳስ ላጲስ ማስምሪያ

አንዳንዱ ሶባኤ ገብቶ የከረመ ይመስል ሞግጓል ።ጾም ጸሎት እንደ ጎዳው ሁሉ ትንፋሽ አጥሮታል « አጎንብሶ በአንገት ሰላምታ እየተለዋወጡ መተላለፍ ብቻ የሁሉም ልብ የፍርህት ደወል ይደውላል በጭንቀት ተወጥሮ ይነጥራል ።

የመፈተኛ አዳራሾቹ እንደ መቃብር አፋቸውን ከፍተው ይጠብቃሉ ቀድሞ የሚገባባቸው ተማሪ የለም ።ሁሉ ዙሪያውን ከብቦ የመጨረሻዋን ደወል ይጠባበቃል ።አንዳንዱ የሰዓቱንና የልቡን ትርታ ያነጻጽራል "እነዚህን የሚውጠው ትልቁ ደወል እስኪደወል ድረስ ! ...

የመፈተኛው እዳራሾች አቅራቢያ የሚገኙት ሽንት ቤቶች በወረፋ ተጨናንቀዋል ። የገባው ቶሎ አይወጣም
የሌለውን በግድ ያምጣል ። ከብዙ ምጥ በኋላ ትንሽ ጭርር አርጎ ይወጣል ። ከውጭ ያለው ያልጐመማል ። ይሳደባል ግን እሱም ሲገባ ያው ነው የፈተና ምጥ !

ቤተልሔም እንደ ልማዷ ሽንት ቤቱን አንቃ ይዛለች። በወረፋ ያገኘችውን መጸዳጃ ቤት በቀላሉ ልትለቀው አልፈለገችም ። ባለ በሌለ ኃይሏ እያማጠች ወስጧን ፈተሸችው ።ጠብ ያለ ነገር አልነበረም” ። በሸቀች ። ምናልባት ድንገተኛ አደጋ ተፈጥሮ እንደሆን ለማረጋገጥ የውስጥ ሱሪዋን መረመረች ቀይ ነገር የለም ።

እንግኒህ ታቃለህ ኢየሱስዬ ! ” አለች የውስጥ ሱሪዋን ታጥቃ ቀሚሷን ቁልቁል እየለቀቀች ።

በሩን ከፍታ ስትወጣ የወረፋ ጠባቂቹን ልጃገረዶች ዐይን ማየት አፍራ አንገቷን ሰብራ ያለፈቻቸው ። ከዚያ ቀጥሉ የታያት የማርታ ዘለፋ ነው። ፀባይዋ እንደሆነ ብታውቅም ሳትለክፋት አታልፍም ። “ .
ያንቺ ሽንት ደግሞ ለምን ፖፖ ይዘሽ አትዞሪም ? ወይም የፕላስቲክ ከረጢት
ብታጠልቂ ይሻላል ።

ዛሬሳ አልለክፈቻትም ። ዝም አለቻት ። ልዩ የምጥ ቀን በመሆኑና ችግሩ በእሷም ላይ ስለሚታይ ከትዕግሥት ጋር ውጪ ቆመው እየጠበቋት ነበር።

ይሄ ሁሉ ትጥቅ ምን ይሠራልሻል ? ” አለቻት ትዕግሥት ቤተልሔምን ፡ ይዛላት የቆየችውን የጽሕፈት መሳርያ ስትመለከት

ማን ያውቃል? ለክፉም ለደጉም" አለችና ቤተልሄም እየሣቀች ተቀበለቻት።

ትጥቋ ብዙ ነው ሁለት እርሳሰና አንድ ብዕር ሁለት ላጲስ ፥ አንድ ቀይ አንድ ጥቁር : ሁለት እስክሪፕቶ አንድ የፕላስቲክና አንድ የእንጨት ፥ ሁለት አጫጭር ማስመሪያ . . . ማን ያውቃል ጭንቅላት እምቢ ያለውን ትጥቁ ይመልሰው እንደሆን?

አንቺ የዛሬት ፈተና ተሰርቆ ወጥቶአል ሲባል ሰማው“ኮ” አለች ማርታ የቤተልሔምን ዐይን ዐይን እያየች

"የማን? የእናንተ ወይስ የእኛ? ” አለች ቤተልሔም ብዙም ባልተደነቀ ስሜት
“ ኧረ የኛ ? ”
“ ማን ነገረሽ ? ?

“ እሁን አንቺ ሽንት ቤት እንደ ገባሽ አንዲት ልጅ ስታወራ ሰማሁ ። ”

"ውሸት ነው እባክሽ ፈተና በወጣ ቁጥር
የሚወራ ወሬ ነው አለች ቤተልሔም።

“አረ እባክሽ ማን ያውቃል ? ሊሰረቅ ወይም በዘመድ አዝማድ ሊወጣ ይችላል ” አለች ማርታ ከጥርጣሬ ይልቅ እምነት በሞላበት ስሜት ።

“ እንሒድ እባክሽ ማርታ ” ስትል ትዕግሥት አቋረጠቻቸው። እሷና ማርታ የሚፈተኑበት ክፍል ቤተልሄም ከምትፈተንበት ራቅ ይል ነበር።

"ገና ኮ ነው"

“ አምስት ደቂቃ ነው፡ የቀረው ብንሔድ ይሻላል ” አለችና ትእግስት በቆራጥ ስሜት ተነቃነቀች።

“ መልካም ዕድል ! ” እየተባባሉ ተለያዩ ።

ትዕግሥት ከቤተልያም መለየት የፈለገችው በአቅራቢያዋ ያሉት ወንዶች ሲጠቋቁሙባት አይታ ነው። ምክንያቱ ምን እንደሆነ ይገባታል። አቤል አማኑኤል ሆስፒቲል ደርሶ ከተመለሰ ወዲህ የግቢው ወሬ ስለ እሶ እና ስለ እሱ ሆኗል ል ። “ ጎበዙዙን ተማሪ ያሳበደችው ኝ ” ትዕግሥትን" ትእግስትን ለማየት የማይጓጓ ተማሪ አልነበረም። እሷም በአንድ በኩል ይኸንኑ ፈርታ ፥ በሌላ ደግሞ የጥናት ሰሞን በመሆኑ ፥ መኝታ
ክፍሏ ውስጥ መሽጋ ነው የከረመችው ። የግድ ነውና አሁን ብትወጣ የተማሪው ሹክሹክታ የመንፈስ ዕረፍት ነሳት።

ቤተልሄም ከትዕግሥት እንደ ተለየች ሳምሶን ጉልቤውን አገኘችው የመፈተኛ ክፍሉን ለማወቅ አንደ ተጣደፈ ነበር።

“ ወዴት ነው ሩጫው ?” አለችው ። ልብ ብሎ አልተመለከታትም ነበር ። ድምጿን ሲሰማ ልቡ ተረጋጋ ።

“ መፈተኛ ክፍላችንን አይተሻል ? ” አላት ፡ ከቁጣ ባልተለየ ኃያል ድምፅ።

“ አዎ እዚህ 104 ውስጥ ነው ” አለችና በጣቷ አመለከተችው ።

ወደዚያው ቀረብ እንበላ !”

“ እሺ ቆይ መጣሁ” ብላው ባለችበት ቆመች ። “ ሁለተኛው አምላክ” ወደ እሷ ሲመጣ ተመልክታው ነበር ። ።በዛሬው ዕለት በቁም የምትፈልገው ሰው ነው ። እሱን ሳትሳለም ወደ ፈተና አትገባም ። እሱም ምልምሎቹን እየተዟዟረ በማጽናናት ተዋክቧል ።

“ እንደምን አደርክ ? ” አለችው ' አጠገቧ ሲደርስ
“ እግዚአብሔር ይመስገን፡ ደኅና ነኝ ። ”
እንግዲህ ወደ ፈተና መግባቴ ነው ።

“ አይዞሽ ፡ እግዚአብሔር ካንቺ ጋር ይሁን ብሏት ሄደ።

እሷም ይኽንኑ እንዲላት ነበር የፈለገችው የግዜርን የራሱን ድምፅ የሰማች ያህል ተጽናናች ። የፈተና ሰሞን ሁሉ አምላኳ ነው ።በተጠየቀችው ሐይማኖት ሁሉ እሺ
ነው ። ከጀህባውም ፡ ከጴንጤውም፥ ከባሀዪም ከሁሉም ጋር የግዜርን ቃል” ትሰማለች ። አንዱ ካንዱ ጋር ሲያያት
ዐይኑ እንደሚቀላ አልተገነዘበችም ። በእሷ ቤት ለሦስት ኣምልኮት መቆሟን ብልጠትና ዘዴ አርጋዋለች ። አንዱ አምላክ ቢስት ሌላው አይስትም ነው ጥበቧ ። በዚያ ላይ ደግሞ ስድስት ኮርስ ነው የምትፈተነው ። አንዱን ኮርስ በለማ
ላይ ጥላዋለች ። የተቀሩትን አምስት ኮርሶች በአንድ አምላክ ላይ መጣሉ ይከብዳል ። እና ሦስቱ “ አምላኮች”
ተከፋፍለው ቢሸከሙት ? መልማዮቿ ልቧን ከፍተው እንዳያዩባት እንጂ ጥሩ ዘዴ ነው ።

አቤልና እስክንድርም ከአንድ ጥግ ስፍራ ሆነው የመግቢያው ደውል እስኪደወል ድረስ ትርምሱን ይታዘባሉ ለፈተና ጊዜ የሚያደረገው ግርግርና ሽብር በተለይ እስክንድርን ሁልጊዜም ያበሽቀዋል ። ፈተና እንዲህ ተማሪውን የሚያርበደብድ ነገር ከሆነ የዕውቀት መለኪያነቱ ያጠራጥራል እያለ ለብቻው ውስጥ ውስጡን ያሰላስላል ።

አቤል የተማሪውን ዐይን ለመሸሽ የሚገባበት ጉድጓድ እጥቷል ። ተማሪዉ እሱ ላይ ሲጠቋቆቻምበትና ሲንሾካሾኩበት ይመለከታል ከትዕግሥትም ላይ እንዲሁ የማያውቁት ተማሪዎች አቤል ማለት የትኛው እንደሆነ ለማወቅ ነበር የሚጠቋቆሙት አቤልን ያስገረመው ግን በፊት የሚያውቁትም ተማሪዎች እንደ እንግዳ ሆነው እየሰረቁ
መመልከታቸው ነው "

“ፊቴ ላይ ምን ለውጥ ለማየት ፈልገው ነው ? ወይስ ግንባሬ ላይ የሚያነቡት ነገር አለ ?” ሲል እሰበ ። በተማሪዉ
አስተያየት በሽቅ ።

የተማሪው ሹክሹክታና የስርቆት እይታ ራሱ ሳያብዱ ያሳብዳል ። “ጥናት ቢወጥረው " ምን ፈተና ቢያስጨንቀው
እንዲህ ዐይነቱን ወሬ ማነፍነፉ አይቀርም የስነ ልቦና ጥናት በስሎ አቶ ቢልልኝና የመሃበራዊ ሥራ ባልደረቦች ከአቤል ጋር በቀጥታም ሆና በተዘዋዋሪ ግኑኝነት አላቸው ብለው የገመቷቸውን ተማሪዎች
#ሰመመን


#ክፍል_ሰላሳ_አራት


#ድርሰት_በሲሳይ_ንጉሱ

...የከተማው ዋና ዋና መንገዶች በዩኒቨርስቲው ተማሪዎች መወረር ጀምረዋል ። የአራት ኪሎና እካባቢዋ ቡና
ቤት አሳላፊዎች፥ ለተማሪ ሻይ ቡና በማቅረብ ተዋክበዋል ። የተማሪዉ አንሶላዎች'ልብሶች በየሥርቻው ተወርውረው የከረሙ የእግር ሹራቦች ከውሃ በመታረቅ ላይ ናቸው ሕሜት ፥ ውረፋ ፡ ዘለፋና ቀልድ ጊዚአቸውን
ጠብቀው ተመልሰዋል በሴሚስተሩ ውስጥ በዩኒቨርስቲው የተደረገች አንዳች ነገር ሳትቀር እየተነሳች መብጠልጠያዋ ጊዜ ነው።

ይህ ሁሉ ፈተና ማለቁን የሚያበሥር ነው የፈተና ውጤት ቀርቦ ማዕበሉ ማንን ጠርጎ ማንን እንደ ተወ እስኪታወቅ ድረስ ለሁለት ሳምንቱ የዕረፍት ቀናት አብዛኛው ተማሪ ከዚህ ክልል አይወጣም ።

እቤልና እስክንድርም የመጨረሻውን ፈተና እንደ ተፈተኑ ግቢውን ለቀው ወጥተዋል ። የተዝረከረኩ ዕቃዎች
ለማስተካከል እንኳ፥ ወደ መኝታ ክፍላቸው አልተመለሱም።ተያይዘው በቀጥታ ወደ እስክንድር እናት ቤት ተክለ ሃይማኖት አካባቢ ሔዱ። አቤል ለአውደ አመትና አልፎ አልፎም ለዕረፍት እነ እስክንድር ቤት መሔድ የጀመረው ገና የሁለተኛ ዓመት ተማሪ ሳለ ከእስክንድር ጋር እንደተዋወቁ ነው።አንዳንዴ አብረው ይሔዱና የተገኘውን ቀማምሰው ተጫውተው ይመለሳሉ ። ዘንድሮ ግን አቤል ቤታቸው ሳይሔድ ቆይቷል ።

የጠፋው ሰው እንደ ምን አላችሁ ልጆቼ ?
እሁና እናትየዋ ፥ ሁለቱን አቅፈው ሳሙዋቸው ።

“ አቤል ፣ ምነው እንዲህ ጠፋህ ልጄ ?”
ምን እባክዎን ፥ ጥናት በዝቶ ነው
“ ቢሆንስ ታዲያ ፥ አንዳንዴ መቼስ እናት ቤት ብቁ ተብሎ የተገኘውን ቀማምሶ ይኬዳል ። አሀን ፈተና ጨረሳችሁ አይደለም ? ”
“ አዎ መቼስ"

“ እንግዲህ አንድ ፈተና ነዋ የቀራችሁ ? የፊታችን ሰኔ መመረቂያችሁ አይደለም ?

አቤል ዝም አለ ። እስክንድር ስሜቱ ስለ ገባው ቶሎ ብሎ ጣልቃ ገባ ።

“ አዎ ! አይዞሽ ደርሰናል ” አላቸው « እጁ ላይ ሲጋራ መኖሩን ያዩት ይሄኔ ነበር ።

« ይኼንን ሲጋራህን ምናለ ብትተወው እስክንድር ? አቤል ጓደኛህን አትመክረውም ? ! ”

ብዙ ዓመት የተናገሩት ነገር ነው ። ሆኖም ዐይናቸው ባየ ቁጥር ዝም ማለት አይችልም ። አቤል ከመቅለስለስ ልላ
ምንም አልመለሰም።

“አይዞሽ ፡ በቅርቡ አቆማለሁ” አላቸው እስክንድር ራሱ ። እሳቸው ሣቁ ሁሌም
የሚላቸው ነገር ስለሆነ።

ማዘር ሙች አቆማለሁ ። አራት ወር ያህል
ብቻ ታገሽኝ ብቻ አላቸው።

ከልቡ ለማቆም ቆርጦ ነበር እናትየው ግን ጊዜው ደርሶ እስካሳዩ ድረስ ሊያምኑት አይችሉም ።

“ምግብ አቀረቡላቸው ከበላሉ በኋላ ሲጫወቱ ቆይተው ሲመሻሽ እስክንድርና አቤል ሊሔዱ ሲሉ፡-

ዛሬ ለምን ከዚሁ ስትጫወቱ አታድሩም ” እሉ እናትየዋ ።

“ አአይ እንሔዳለን ። እዚያው ካምፓችን ይሻለናል አለ እስክንድር እሳቸው በሚናገሩት አይነት ፣

እስክንድር በዕረፍቱ ሰሞን አቤልን ጥሎ ቤት መክረም አልፈለገም። አብረው እንዳይሆኑ ደግሞ ቤቱ አይበቃም።
ሁለት መኝታ ብቻ ነው ያለው “ አንዱ የናትየዋ ነው " በአንዱ መኝታ ላይ ከታናሽ ወንድሙ ጋር ሦስት ሆነው ተጨናንቀው መክረሙን ኣልፈለገም ። በዚያ ላይ እናትየዋ ለእነሱ የሚያቀርቡትን ምግብ ጣፈጠ አልጣፈጠልኝ ብለው ሲጨነቁ እንዲከርሙ አይፈልግም " ከአሁን በፊትም ቢሆን ትልቁ የክረምት ዕረፍት ላይ ካልሆነ የገናወን ዕረፍት ቤቱ አሳልፎ አያውቅም ። እዚያው ዩኒቨርስቲ
ውስጥ የሚከርመው ። እናትየውም ይህንኑ ስለሚያውቁ ብዙም አላግደረደሩት "

ተሰናብተዋቸው ከውጭው በር እንደ ደረሱ። እናትየው እስክንድርን ወደ ኋላ አስቀሩትና አንድ ነገር እጁ ውስጥ
ሽጉጥ አደረጉለት።

“ ምንድነው እሱ ? ” አላቸው ፡ ምን እንደሆን ልቡ እያወቀ።

“ ያዘው ለዚያ ለምናምንቴ ለሱስህ ይሆንሃል አሉት ። የዐሥር ብር ኖት ነበር ።
እኔ ከሌላ ቦታ አላጣም እባክሽ ። ይሄ ለራስሽ ይሁንሽ ” አላቸው ።ለመግደርደር ያህል ሳይሆን ከልቡ ነበር ።
ምን ጊዜም ከእናቱ ገንዘብ ሲወስድ ልቡ ያዝናል ። እንደ ሲጋራ ሱሰኝነቱ አይቅበዘበዝም ።

ያዘው ግድ የለህም” ። እኔ አለኝ ። አንድ አረርባ ብር የመንደር ዕቁብ ነበረችኝ ፤እሷ ወጥታልኝ ነው ” አሉት ።

አመስግኖ ብሯን ኪሱ ከተተ ወዲያው ማርታ በሀሳቡ መጣችበት ግን በዐሥር ብር ምን ሊኮን ?

“ አቤል ፡ በል እንግዲህ ብቅ እያላችሁ ጠይቁኝ ። አሁን ዕረፍት ናችሁ ” አሉት እናትየዋ « አቤልን ቅር እንዳይለው

ከእናቱ ተለይተው ከሔዱ በኋላ እስክንድር ስለ ድህነትና የእናት አንጀት ተቃራኒ ሁኔታ እያብሰለሰለ ነበር
ድህነት እጅዋን ሊያስራት ይሞክራል ፤ እናት እጅን ለልጅዋ ለመዘርጋት ትፍጨረጨራለች ፡፡ ምኞቷና አድራጎቷ እኩል አይሆንም “ በፍቅር ወደ ልጅዋ ስትንጠራራ
ድህንት ጨምድዶ ይይዛታል ግን ያም ሆኖ እትረታም አትሽንፍም እንደ ምንም ተፍጨርጭራ የልጅዋን እጅ
ትነካለች።

“ አሁን ወዴት ነን ?” አለ አቤል " ትንሽ እንደተጓዙ

“ አንድ ቤት ጎራ ብለን ደርቆ የከረመ ጉሮሮአችንን እናርጥብ እንጂ ! ” አለ እስክንድር ።

አቤል ገንዘብ መቆጠብ የማይችለው የእስክንድር እጅ አስግርምት ሳቀ ። ከእናቱ የተቀበላትን ገንዘብ ለማጥፋት
እንደ ቸኮለ ገባው።

“ ይልቅ ቦታ ምረጥ የት ይሻለናል ? ” አለው እስክንድር

“ ወደ ሠፈራችን አቅራቢያ አይሻልም ? ” አለ አቤል ።መቼም ከዩኒቨርስቲው አካባቢ ርቆ መቆየት አይሆንለትምና።

“ ስድስት ኪሎ ደኅና ቡና ቤት የለማ ! ከጠጣን አይቅር ትንሽ ትርምስ ብጤ ያለበት ይሻለናል ። የጠርሙስ ካካታ ! ”

" አራት ኪሎ እንሒዳ! በዚያው ወደ ካምፓስ ለመግባት ይቀርበናል ”

በዚሁ ተስማምተው ወዶ አራት ኪሎ እመሩ ።

እዚያ ሲደርሱ ከምሽቱ አንድ ሰዓት ተኩል ገደማ ሆኖ ነበር እስክንድር ቻቻታ ያለበትን ቦታ መምረጥ ስለፈለገ ከቡና ቤት ቡና ቤት ሲዘዋወሩ በብዛት የሚያገጥማቸው የዩኒቨርስቲ ተማሪ ነበር ። ተማሪው ታስሮ እንደተፋታ ሆኖአል ንኮኒ ትተደግፎ የሚጠጣው የሴት አሳላፊዎችን ዳሌ የሚዳብሰው በቡድን ተቀምጦ እየጠባ የሚንቻቻው ተሜ ነው። ከወላጅ ከዘመድ የተላከ ከወዲያ ወዲህ ተጠራቅሞ ተቀብሮ የቆየ ገንዘብ መውጫው ዕለት ነዉ። በፈተና ማግሥት ሰክሮ መጥቶ ግቢው ውስጥ መደንፋት ፡ የማይጠጡ ተማሪዎችን መረበሽ ። ወይም ሰክሮ በየበረንዳው አድሮ
ጠዋት “ ጀብድ ” አርጎ ማውራት በዩኒቨርስቲ ውስጥ እየተለመደ የመጣ ይመስላል በተለይ ይህ ሁኔታ አይሎ
የሚታየው ከገጠር በወጡ ተማሪዎች ላይ ነው ። የአዲስ አበባው ተማሪ የቡና ቤቱን ትርምስ ከማዘውተር “ የኖርንበት ነው ” በማለት ዐይነት ቆጠብ ይላል ። ገንዘቡንም ቢሆን ከገጠረ እንደ መጡት አጠራቅሞ ማቆየት አይችልም ። አንዳንዱ እንደ ቱሪስት አስጐብኝ ገጠሬዎቹን ይዞ የከተማውን
ምርጥ ቡና ቤቶች በማስተዋወቅ የጋራ “ ጀብድ ” ይፈጽማል

እስክንድር አንድ ሞቅ ያለ ቡና ቤት አግኝተዉ ገቡ አንድ አንድ ቢራ ይዘው ቁጭ ከማለታቸው ፡ ሳምሶን ጉልቤው ዝንጥ ብሎ መጣ ሁሉም አራት ኪሎ መጠጣት የመረጡት ማታ ወደ መኝታ ቤታቸው ለመግባት እንዲቀርባቸው ይመስላል ።

ሳምሶን እስክንድርና አቤልን ሲያገኛቸው ደስ አለው ።በተለይ አቤልን መጋበዝ፤ ይፈልግ ነበር ።ጠዋት የለበሰውን
ቀያይሮ አፍላ ጉልበቱን ወጣጥሮ በሚያሳይ መሉ ጅንስ ሽክ ብሎአል ።

"ከመቼው ተሠየማችሁ ? አላቸው ፡ አጠግባቸው ለመቀመጥ መንበር እየሳበ

“ አንተም ደህና ጊዜ ደርሰሃል ፤ ቁጭ በል አለው እስክንድር።

ሳምሶንም ቢራ አዝዞ
👍1