#ለኀጥአን_የመጣ
#የታዳጊው_ወታደር_ትዝታ
#ክፍል_ሶስት
#በኢስማኤል_ቤህ
#ክፍለእየሱስ_አበበ_እንደተረጎመው
የምታውቅ ይመስላል።
..ቀጥሎ በጥይት የተበሳሱ ወንዶች እና
ሴቶች መጡ፡፡ አንዳንዶቹ ሰዎች እንደ ቆሰሉ እንኳ አያውቁም ነበር፡፡ አንዳንዶቹ ራሳቸውን ሳቱ ሌሎቹ ደግሞ አስታወኩ። አቅለሸለሸኝ ራሴም ዞረብኝ መሬት ሲሽከረከር ፤ የሰዎች ድምጸ ሩቅ ሁኖ ይሰማኛል።
በቀኑ መጨረሻ ያየነው ሌላው ጉዳት በጀርባዋ ህጻን ልጅ ያዘለች አንዲት ሴት ናት። ደም በልብሷ ከላይ እስከ ታች
ወርዶ በጀርባዋ መስመር ሰርቷል። ልጆዋ በጥይት ተመቶ ሙቷል። ቁማ ልጅዋን አውርዳ አስቀመጠቻት። በኋላ ወደ
ልጅዋ ቀርባ ወዘወዘቻት። በብዙ ስቃይ እና ድንጋጤ ውስጥ ስለነበረች አለቀሰች።
ጅኒየር፣ታሎ እና እኔ ተያየን ወደ ማታሩ ጆንግ መመለስ እንዳለብን ገባን። ማግቦ ከእንግዲህ ቤታችን እንደማይሆን ወላጆቻችንንም ከዛ ሊሆኑ እንደማይችሉ
ተገነዘብን፡፡ አንዳንድ የቆሰሉ ሰዎች ካባቲ ቀጣይ የአማጺዎች መዳረሻ እንደሚሆን ይናገራሉ። አማጺዎች እንዲያገኙን
አንፈልግም:: በደንብ መራመድ እንኳ ማይችሉ ሰዎች ከካባቲ ለመውጣት የቻሉትን ሁሉ እያረጉ ነው:: ወደ ማታሩ ጆንግ ስንመለስ የዛች ሴትዮዎ እና የልጅዋ ሁኔታ አእምሮየን አስጨነቅው:: ጉዞው ብዙም አልተሰማኝም። ውሃ ጠምቶኝ ጠጥቼ እንኳ ምንም ጥሩ ስሜት ሊሰማኝ አልቻለም፡፡ ያቺ ሴት
ወደመጣችበት መመለስ አልፈልግም ፤ ሁሉም ነገር እንደጠፋ የልጅዋ አይን ይናገራል።
"አንተ ነጌትቭ አስራ ዘጠኝ አመትህ ነው” ይለኝ ነበር ባባ።አባቴ ከ ነጻነት በኋላ በ1961 የሴራሊዎን ሕይወት ምን
እንደምትመስል ስጠይቀው ሁሌም መልሱ ይሄ ነበር፡፡ ምኑ ይገባሃል የሚል ምፀት ያለው መልስ! ከ1808 ዓ/ም ጀምሮ ሴራሊዮን የብሪታንያ ግዛት ነበረች::
ሚልተን ማርጋይ የመጀመሪያው ጠቅላይ ሚኒስቴር በመሆን የሴራሊዮንን ህዝብ ከዚህ አለም በሞት እስከ አረፈበት 1964 ድረስ ሃገሪቱን መርቷል::
ወንድሙ አልበርት ማርጋይ እሱን ተከትሎ እስከ 1967 ማለትም በሲያካ ስቲቨን በምርጫ እስከ ተሸነፍበት ደረስ መምራት ቻለ፡፡ ሲያካ ስቲቨን ወዲያው መፈንቅለ መንግስት ቢያጋጥመውም በ1968 እንደገና ወደ ስልጣን ተመለሰ። ከብዙ
አመታት በኋላ ሃገሪቱ የአንድ ፓርቲ ብቻ ሃገር እንደሆነች አወጀ:: የሁሉም ህዝቦች ኮንግረስም የሃገሪቱ ብቸኛው ህጋዊ
ፓርቲ ሆነ። የ”ፖለቲካው መበላሸት የሚጀመረው ከዚህ ጊዜ ጀምሮ ነው ይል ነበር አባቴ።ስለዚህ ጦርነቱ ምን እያለ ይሆን?! አዋቂዎች አቢዮታዊ ጦርነት እንደሆነ እና ህዝቡን ከሙሰኛ
መንግስት ነጻ ለማውጣት የ ሚደረግ ጦርነት እንደሆነ ሲያወሩ ሰምቻለሁ፡፡ የትኛው የነጻነት እንቅስቃሴ ነው ንጹሃንን ህጻናትን የሚገድል? ይህንን የሚመልስ ማንም የለም::ባየሁት ነገር ልቤን ይከብድዋል ያስጨንቀኛል!
የሚታየውን ተራራ ዱሩን ሁሉ ፈራሁ።
በጣም ከመሽ ማታሩ ጆንግ ደረስኩ፡፡ ጅኒየር ና ታሎ ያየነው አስከፊና አስቃቂ ክስተት በሙሉ ለጓደኞቻችንን ነገሩዋቸው። እኔ ግን ያየሁትን ማመን ስላልቻልኩ ዝምታን መረጥኩ። ማታ ማንቀላፋት ስጀምር በህልሜ ጎኔን በጥይት ተመትቼ ቆስዬ ሰዋች ምንም ሳይረዱኝ የራሳቸውን ህይወት ለማትረፍ አልፈውኝ ሲሮጡ አየሁ።
ተንፏቅቄ ወደ ዱር ለመግባት ስሞክር ከየት እንደመጣ የማይታወቅ ሰው ራሴ ላይ መሳሪያ ደቅኗል። ተኮሰ፡፡ባትቼ ከእንቅልፌ ተነሳሁ፡፡በጥርጣሬ ጎኔን ነካሁ። ፈራሁ! ህልም እና እውነታን መለየት ስላቃተኝ ፈራሁ።
ሁሌም ጥዋት ጎህ ሲቀድ ስለ ቤተሰቦቻችን ወሬ ካለ ለመስማት ወደ ማታሩ ጆንግ ባህር ዳርቻ እንወርዳለን።
ከሳምንት በኋላ ወደ ማታሩ ጆንግ የሚመጡ ስደተኞች ቁጥር ቀነሰ። ስለ ቤተሰቦቻችን ምንም ወሬ የለም። ድጋሚ የውሃ ሽታ ሆኑብን! የመንግስት ወታደሮች በማታሩ ጆንግ ተሰማርተው ኬላዎችን በባህር ዳርቻ እና በከተማው ዋና ዋና አቅጣጫዎች አቁመዋል::
ወታደሮቹ ከባድ መሳሪያዎችን አዘጋጅተው አማጺዎቹን ለመምታት ይጠባበቃሉ። አማጺዎቹ በባህር ዳርቻው በኩል እንደሚመጡ ገምተዋል። ህዝቡ በጊዜ እንዲገባ የስዓት እላፊ ከምሽቱ አንድ ስዐት በኋላ መንግስት አውጇል። ከባድ ምሽት ነበር፤ መተኛት አልቻልንም:: ሁላችንም በጊዜ ተሰባሰብን ከበን
ማውራት ጀመርን፡፡
ይሄ ነገር፦ ይሄ እብደት መቼ ይሆን የሚያበቃው? "በጥቂት ጊዜ ውስጥ የሚያበቃም አይመስለኝም፡፡" አለ ጅኒ የር ”ምን አልባት ለአንድ ና ሁለት ወር ይቆይ ይሆናል።” አለ ታሎ ጣሪያ ጣሪያ እያየ።
ገብሪላ ደግሞ ወታደሮች አመጺዎችን ከማዕድን ቦታ ለማባረር እየገሰገሱ እንደሆነ ሰምቻለሁ አለ። ጦርነቱ ወደ
የፍጻሜው ምዕራፍ ላይ እንዳለ እና ከሶስት ወር በላይ እንደማይቆይ ተማመን፡፡
ጅኒየር፣ታሎ እና እኔ ነገሮችን ለመርሳት ራፕ ሙዚቃ ማደመጥ ጀመርን፡፡ የ ሙዚቃ ካሴቶች እና ልብሶቻችንን ብቻ
ይዘን ነበር ከቤት የወጣነው:: ከቤት ደጃፍ ላይ ተቀምጨ Now That We Found Love ” ፍቅርን አሁን አገኘነው” የሚለውን የሄንሪ ዲ እና ዘ ቦይዝ ሳዳምጥ ትዝ አለኝ ። አይኔን ጨፈንኩ። ካባቲ ያየሁዋቸው አሰቃቂ ነገሮች ሁሉ
በአዕምሮዬ መጡ። ምስሎቹን ከአዕምሮዬ ለማውጣት የድሮውን
በሰላሙን ጊዜ የነበረችውን ካባቲ ማሰብ ጀመርኩ።
በአያቴ መንደር ባንድ በኩል ጥቅጥቅ ያለ ደን ሲኖር በሌላው ደግሞ የቡና እርሻ ነበር፡፡ በጫካው በኩል የሚመጣው ወንዝ ሰፈሩ ዳር፣ በወይራ ዛፎች አደርጎ ወደ ረግረጉ ይገባል። ከረግረጉ በላይ የሙዝ ማሳው እስከዛኛው አድማስ ይታያል። ብዙ ሰው ከቤቱ ጀርባ የማንጎ ዛፎች አለው።
ጥዋት ከጫካው በስተጀርባ ፅሐይ ትወጣለች። መጀመሪያ ጨረሯ በቅጠሎች መሃል ያልፋል። ከዛ አውራ ደሮ ይጮሃል፤ ድንቢጥ ወፎች በዝማሬ አዲስ ቀንን ሲያውጁ ወርቃማ ፅሐይ
ከጫካው ራስ ላይ ጉብ ብላ ትታያለች። ምሽት ላይ ዝንጀሮዎች ወደ ማደሪያቸው ለመመለስ ከዛፍ ዛፍ ሲዘሉ ይታያል። በቡናው ማሳ ደሮዎች ጫጩቶቻቸውን ከጭልፊት ይሸሽጋሉ። ከማሳው
ወዲያ ማዶ ደግሞ የወይን ዛፎች በንፋስ ሲወዛወዙ ይታያል።
አንዳንዴ የወይን ፍሬ ለቃሚ ዛፎች ላይ ወጥቶ ይታያል።
ምሽቱ በዛፎች ውዝዋዜ ድምጽ ( ቀ ቀ ቀ ቀ ) እና በሩዝ መውቀጥ ድምጽ (ድው ዱ ዱ) ታጂቦ ይገባደዳል። ድምጹ በመንደሩ ያስተጋባል። ወፎች በጥንቃቄ እንዲበሩ፣ ዶሮዎች፣እንቁራሪቶች ጉጉቶችም ወደ ማደሪያቸው እንዲመለሱ ያደርጋል። የመንደር ሰዎች ፋኖስ ወይም የተቀጣጣለ እንጨት እያበሩ ከ እርሻ ማሳቸው ይመለሳሉ፡፡
"እንደ ጨረቃ ለመሆን እንትጋ” ይላል አንድ ሽማግሌ ሰውየ ውሃ ሲቀዳ፣ ለአደን ሲሄድ ወይም የወይን ፍሬ ዛፎቹ ላይ ሲቆርጥ። አንድ ቀን አያቴን ምን ማለት እንደሆነ ጠየኳት። አባባሉ ሰዎች ሁሌም ጥሩ እንዲሆኑ እና ለሌሎች መልካም እንዲሆኑ ያስታውሳል። ስዎች የፅሐይን ግለት ፤ ከባድ ዝናብን እና ብርድን ያማርራሉ። ነገር ግን ጨረቃ ስትወጣ
ማንም አያጉረመርምም፡፡ ሁሉም ደስተኛ ነው፤ እንደየራሳቸው ሁኔታ ጨረቃን ያደንቃሉ። ህጻናት ጥላቸውን ያያሉ፤ ሰዎች ተሰባስበው ይጫወታሉ ለሊቱን በጭፈራ ያሳልፋሉ። ጨረቃዋ
ስታበራ ደስታ ይሆናል። ለዛ ነው እንደ ጨረቃ ለመሆን የምንተጋው።
።።
አየሩ ደም ደም እና የተቃጠለ ስጋ በሚሸትበት ከተማ መሐል የዛገ ካሬታ እየገፋሁ ነበር። : ንፋሱ የሲቃ ድምጾችን ያመጣል::
ተመሰቃቅለው በወደቁ ሬሳዎች መካከል ሳልፍ እጃቸውን እና እግራቸውን ያጡ ሰዎች፤ ሆዳቸው ውስጥ ቅልሃ ገብቶ
አንጀታቸው የተዘረገፈ እና በአፍንጫቸው በጆሮቻቸው ደም የፈሰሳቸውን አየሁ። በራሪዎች
#የታዳጊው_ወታደር_ትዝታ
#ክፍል_ሶስት
#በኢስማኤል_ቤህ
#ክፍለእየሱስ_አበበ_እንደተረጎመው
የምታውቅ ይመስላል።
..ቀጥሎ በጥይት የተበሳሱ ወንዶች እና
ሴቶች መጡ፡፡ አንዳንዶቹ ሰዎች እንደ ቆሰሉ እንኳ አያውቁም ነበር፡፡ አንዳንዶቹ ራሳቸውን ሳቱ ሌሎቹ ደግሞ አስታወኩ። አቅለሸለሸኝ ራሴም ዞረብኝ መሬት ሲሽከረከር ፤ የሰዎች ድምጸ ሩቅ ሁኖ ይሰማኛል።
በቀኑ መጨረሻ ያየነው ሌላው ጉዳት በጀርባዋ ህጻን ልጅ ያዘለች አንዲት ሴት ናት። ደም በልብሷ ከላይ እስከ ታች
ወርዶ በጀርባዋ መስመር ሰርቷል። ልጆዋ በጥይት ተመቶ ሙቷል። ቁማ ልጅዋን አውርዳ አስቀመጠቻት። በኋላ ወደ
ልጅዋ ቀርባ ወዘወዘቻት። በብዙ ስቃይ እና ድንጋጤ ውስጥ ስለነበረች አለቀሰች።
ጅኒየር፣ታሎ እና እኔ ተያየን ወደ ማታሩ ጆንግ መመለስ እንዳለብን ገባን። ማግቦ ከእንግዲህ ቤታችን እንደማይሆን ወላጆቻችንንም ከዛ ሊሆኑ እንደማይችሉ
ተገነዘብን፡፡ አንዳንድ የቆሰሉ ሰዎች ካባቲ ቀጣይ የአማጺዎች መዳረሻ እንደሚሆን ይናገራሉ። አማጺዎች እንዲያገኙን
አንፈልግም:: በደንብ መራመድ እንኳ ማይችሉ ሰዎች ከካባቲ ለመውጣት የቻሉትን ሁሉ እያረጉ ነው:: ወደ ማታሩ ጆንግ ስንመለስ የዛች ሴትዮዎ እና የልጅዋ ሁኔታ አእምሮየን አስጨነቅው:: ጉዞው ብዙም አልተሰማኝም። ውሃ ጠምቶኝ ጠጥቼ እንኳ ምንም ጥሩ ስሜት ሊሰማኝ አልቻለም፡፡ ያቺ ሴት
ወደመጣችበት መመለስ አልፈልግም ፤ ሁሉም ነገር እንደጠፋ የልጅዋ አይን ይናገራል።
"አንተ ነጌትቭ አስራ ዘጠኝ አመትህ ነው” ይለኝ ነበር ባባ።አባቴ ከ ነጻነት በኋላ በ1961 የሴራሊዎን ሕይወት ምን
እንደምትመስል ስጠይቀው ሁሌም መልሱ ይሄ ነበር፡፡ ምኑ ይገባሃል የሚል ምፀት ያለው መልስ! ከ1808 ዓ/ም ጀምሮ ሴራሊዮን የብሪታንያ ግዛት ነበረች::
ሚልተን ማርጋይ የመጀመሪያው ጠቅላይ ሚኒስቴር በመሆን የሴራሊዮንን ህዝብ ከዚህ አለም በሞት እስከ አረፈበት 1964 ድረስ ሃገሪቱን መርቷል::
ወንድሙ አልበርት ማርጋይ እሱን ተከትሎ እስከ 1967 ማለትም በሲያካ ስቲቨን በምርጫ እስከ ተሸነፍበት ደረስ መምራት ቻለ፡፡ ሲያካ ስቲቨን ወዲያው መፈንቅለ መንግስት ቢያጋጥመውም በ1968 እንደገና ወደ ስልጣን ተመለሰ። ከብዙ
አመታት በኋላ ሃገሪቱ የአንድ ፓርቲ ብቻ ሃገር እንደሆነች አወጀ:: የሁሉም ህዝቦች ኮንግረስም የሃገሪቱ ብቸኛው ህጋዊ
ፓርቲ ሆነ። የ”ፖለቲካው መበላሸት የሚጀመረው ከዚህ ጊዜ ጀምሮ ነው ይል ነበር አባቴ።ስለዚህ ጦርነቱ ምን እያለ ይሆን?! አዋቂዎች አቢዮታዊ ጦርነት እንደሆነ እና ህዝቡን ከሙሰኛ
መንግስት ነጻ ለማውጣት የ ሚደረግ ጦርነት እንደሆነ ሲያወሩ ሰምቻለሁ፡፡ የትኛው የነጻነት እንቅስቃሴ ነው ንጹሃንን ህጻናትን የሚገድል? ይህንን የሚመልስ ማንም የለም::ባየሁት ነገር ልቤን ይከብድዋል ያስጨንቀኛል!
የሚታየውን ተራራ ዱሩን ሁሉ ፈራሁ።
በጣም ከመሽ ማታሩ ጆንግ ደረስኩ፡፡ ጅኒየር ና ታሎ ያየነው አስከፊና አስቃቂ ክስተት በሙሉ ለጓደኞቻችንን ነገሩዋቸው። እኔ ግን ያየሁትን ማመን ስላልቻልኩ ዝምታን መረጥኩ። ማታ ማንቀላፋት ስጀምር በህልሜ ጎኔን በጥይት ተመትቼ ቆስዬ ሰዋች ምንም ሳይረዱኝ የራሳቸውን ህይወት ለማትረፍ አልፈውኝ ሲሮጡ አየሁ።
ተንፏቅቄ ወደ ዱር ለመግባት ስሞክር ከየት እንደመጣ የማይታወቅ ሰው ራሴ ላይ መሳሪያ ደቅኗል። ተኮሰ፡፡ባትቼ ከእንቅልፌ ተነሳሁ፡፡በጥርጣሬ ጎኔን ነካሁ። ፈራሁ! ህልም እና እውነታን መለየት ስላቃተኝ ፈራሁ።
ሁሌም ጥዋት ጎህ ሲቀድ ስለ ቤተሰቦቻችን ወሬ ካለ ለመስማት ወደ ማታሩ ጆንግ ባህር ዳርቻ እንወርዳለን።
ከሳምንት በኋላ ወደ ማታሩ ጆንግ የሚመጡ ስደተኞች ቁጥር ቀነሰ። ስለ ቤተሰቦቻችን ምንም ወሬ የለም። ድጋሚ የውሃ ሽታ ሆኑብን! የመንግስት ወታደሮች በማታሩ ጆንግ ተሰማርተው ኬላዎችን በባህር ዳርቻ እና በከተማው ዋና ዋና አቅጣጫዎች አቁመዋል::
ወታደሮቹ ከባድ መሳሪያዎችን አዘጋጅተው አማጺዎቹን ለመምታት ይጠባበቃሉ። አማጺዎቹ በባህር ዳርቻው በኩል እንደሚመጡ ገምተዋል። ህዝቡ በጊዜ እንዲገባ የስዓት እላፊ ከምሽቱ አንድ ስዐት በኋላ መንግስት አውጇል። ከባድ ምሽት ነበር፤ መተኛት አልቻልንም:: ሁላችንም በጊዜ ተሰባሰብን ከበን
ማውራት ጀመርን፡፡
ይሄ ነገር፦ ይሄ እብደት መቼ ይሆን የሚያበቃው? "በጥቂት ጊዜ ውስጥ የሚያበቃም አይመስለኝም፡፡" አለ ጅኒ የር ”ምን አልባት ለአንድ ና ሁለት ወር ይቆይ ይሆናል።” አለ ታሎ ጣሪያ ጣሪያ እያየ።
ገብሪላ ደግሞ ወታደሮች አመጺዎችን ከማዕድን ቦታ ለማባረር እየገሰገሱ እንደሆነ ሰምቻለሁ አለ። ጦርነቱ ወደ
የፍጻሜው ምዕራፍ ላይ እንዳለ እና ከሶስት ወር በላይ እንደማይቆይ ተማመን፡፡
ጅኒየር፣ታሎ እና እኔ ነገሮችን ለመርሳት ራፕ ሙዚቃ ማደመጥ ጀመርን፡፡ የ ሙዚቃ ካሴቶች እና ልብሶቻችንን ብቻ
ይዘን ነበር ከቤት የወጣነው:: ከቤት ደጃፍ ላይ ተቀምጨ Now That We Found Love ” ፍቅርን አሁን አገኘነው” የሚለውን የሄንሪ ዲ እና ዘ ቦይዝ ሳዳምጥ ትዝ አለኝ ። አይኔን ጨፈንኩ። ካባቲ ያየሁዋቸው አሰቃቂ ነገሮች ሁሉ
በአዕምሮዬ መጡ። ምስሎቹን ከአዕምሮዬ ለማውጣት የድሮውን
በሰላሙን ጊዜ የነበረችውን ካባቲ ማሰብ ጀመርኩ።
በአያቴ መንደር ባንድ በኩል ጥቅጥቅ ያለ ደን ሲኖር በሌላው ደግሞ የቡና እርሻ ነበር፡፡ በጫካው በኩል የሚመጣው ወንዝ ሰፈሩ ዳር፣ በወይራ ዛፎች አደርጎ ወደ ረግረጉ ይገባል። ከረግረጉ በላይ የሙዝ ማሳው እስከዛኛው አድማስ ይታያል። ብዙ ሰው ከቤቱ ጀርባ የማንጎ ዛፎች አለው።
ጥዋት ከጫካው በስተጀርባ ፅሐይ ትወጣለች። መጀመሪያ ጨረሯ በቅጠሎች መሃል ያልፋል። ከዛ አውራ ደሮ ይጮሃል፤ ድንቢጥ ወፎች በዝማሬ አዲስ ቀንን ሲያውጁ ወርቃማ ፅሐይ
ከጫካው ራስ ላይ ጉብ ብላ ትታያለች። ምሽት ላይ ዝንጀሮዎች ወደ ማደሪያቸው ለመመለስ ከዛፍ ዛፍ ሲዘሉ ይታያል። በቡናው ማሳ ደሮዎች ጫጩቶቻቸውን ከጭልፊት ይሸሽጋሉ። ከማሳው
ወዲያ ማዶ ደግሞ የወይን ዛፎች በንፋስ ሲወዛወዙ ይታያል።
አንዳንዴ የወይን ፍሬ ለቃሚ ዛፎች ላይ ወጥቶ ይታያል።
ምሽቱ በዛፎች ውዝዋዜ ድምጽ ( ቀ ቀ ቀ ቀ ) እና በሩዝ መውቀጥ ድምጽ (ድው ዱ ዱ) ታጂቦ ይገባደዳል። ድምጹ በመንደሩ ያስተጋባል። ወፎች በጥንቃቄ እንዲበሩ፣ ዶሮዎች፣እንቁራሪቶች ጉጉቶችም ወደ ማደሪያቸው እንዲመለሱ ያደርጋል። የመንደር ሰዎች ፋኖስ ወይም የተቀጣጣለ እንጨት እያበሩ ከ እርሻ ማሳቸው ይመለሳሉ፡፡
"እንደ ጨረቃ ለመሆን እንትጋ” ይላል አንድ ሽማግሌ ሰውየ ውሃ ሲቀዳ፣ ለአደን ሲሄድ ወይም የወይን ፍሬ ዛፎቹ ላይ ሲቆርጥ። አንድ ቀን አያቴን ምን ማለት እንደሆነ ጠየኳት። አባባሉ ሰዎች ሁሌም ጥሩ እንዲሆኑ እና ለሌሎች መልካም እንዲሆኑ ያስታውሳል። ስዎች የፅሐይን ግለት ፤ ከባድ ዝናብን እና ብርድን ያማርራሉ። ነገር ግን ጨረቃ ስትወጣ
ማንም አያጉረመርምም፡፡ ሁሉም ደስተኛ ነው፤ እንደየራሳቸው ሁኔታ ጨረቃን ያደንቃሉ። ህጻናት ጥላቸውን ያያሉ፤ ሰዎች ተሰባስበው ይጫወታሉ ለሊቱን በጭፈራ ያሳልፋሉ። ጨረቃዋ
ስታበራ ደስታ ይሆናል። ለዛ ነው እንደ ጨረቃ ለመሆን የምንተጋው።
።።
አየሩ ደም ደም እና የተቃጠለ ስጋ በሚሸትበት ከተማ መሐል የዛገ ካሬታ እየገፋሁ ነበር። : ንፋሱ የሲቃ ድምጾችን ያመጣል::
ተመሰቃቅለው በወደቁ ሬሳዎች መካከል ሳልፍ እጃቸውን እና እግራቸውን ያጡ ሰዎች፤ ሆዳቸው ውስጥ ቅልሃ ገብቶ
አንጀታቸው የተዘረገፈ እና በአፍንጫቸው በጆሮቻቸው ደም የፈሰሳቸውን አየሁ። በራሪዎች
👍2🥰1
#ለኀጥአን_የመጣ
#ክፍል_አራት
#የታዳጊው_ወታደር_ትዝታ
#በኢስማኤል_ቤህ
#ክፍለእየሱስ_አበበ_እንደተረጎመው
እንደርስበታለን ብለን ከገመትነው ስዓት በፊት ማታሩ ጆንግ ደረሰን፡፡ ስለ ቤተሰቦቻችን ምንም ዜና የለም። በተስፋ ከመጠበቅ እና ደህንነታቸውን ከመመኘት ውጪ ምን ማድረግ እንዳለብን አናውቅም::
አማጺዎች ከ ማታሩ ጆንግ ሃያ ኪሎ ሜትር እና ከዛ በላይ በምትርቀው ሱምብያ ከተማ መሰፈራቸውን ሰማን። ቀጥሎ አማጺዎች ደብዳቤ እንደላኩና ደብዳቤው የነሱም መምጣት፤ ስለ
እኛ እየታገሉ እንደሆነ እና የእንኳን ደህና መጣችሁ አቀባበል እንደሚፈልጉ ያትታል። መልዕክተኛው ወጣት ነው፡፡ ሰውነቱ ላይ የአማጺዎችን ስም እና አጸርሆተ ቃል ማለትም (አአግ
አብዮታዊ የአንድነት ግንባርን ተነቅሷል። ከአውራ ጣቱ ውጪ ሁሉንም ጣቶቹን ቆርጠውበታል። አውራ ጣት በብዙ ሰወች
የተለመደ የፍቅር ምልክት ነበር።
መልዕክቱ እንደደረስ ሰዎች ወደ ጫካ መሸሸግ ጀመሩ። የካሊሎ ቤተሰብ ግን እንድንቆይ እና ስንቅ ይዘን እነሱን
እንድንከተል ጠየቁን። ቆየን፡፡
ያ ምሽት በህይወቴ ለመጀመሪያ ጊዜ የከተማን ህይወት የሚሰጠው የሰዎች መኖር እና መንፈሳቸው እንደሆነ ተረዳሁ። የሰዎች አለመኖር ከተማውን አስፈሪ አደረገው። ድቅድቅ ጨለማ እና ከባድ ጸጥታ! የዶሮዎች እና የወፎች ዝማሬ
እንኳ የለም። ጨለማ ፈጥኖ መጣ፤ ጨረቃም የለችም። አየሩ ከብዷል፡፡ ተፈጥሮ ራሷ የሚመጣውን የፈራች ትመስላለች።
ሰዎች ለሳምንት ያህል ተሸሸጉ። አማጺዎች ግን አልመጡም።በኋላ ሌላ መልዕክተኛ ላኩ፡፡ መልዕክተኛው ታዋቂ የካቶሊክ ካህነ ነበር፡፡ ከማስፈራራት ውጪ ካህኑን ምንም አላደረጉትም።
ቃሉን ተቀብሎ ህዝቡ ወደ ጫካ ተመልሶ ገባ። አስር ቀናት አለፉ አማጺዎች ግን አልመጡም፡፡ ነዋሪው ወደ ከተማ መመለስ ጀመረ። ትምህርት ቤቶች ተከፈቱ፤ ሰዎች ወደ ዕለት ተዕለት
ኑሯቸው ተመለሱ፡፡ አምስት ቀናት በሰላም አለፉ፡፡
በመጨረሻ አማጺዎች ሲመጡ ቀላል የተኩስ ድምጽ ሰማን፡፡
ጅኒ የር፣ታሉ፣ ካሎኮ፣ ገብሬላ፣ ካሊሎ እና እኔ ቤት ውስጥ ነበረን
"ሰማቹህ?” ብለው ጠየቁ። ወታደሮች ናቸው የተኮሱት ወይስ ሌላ አካል እያልን በማሰብ ደርቀን ቆምን።
ከደቂቃዎች በኋላ ሶስት ጊዜ ተተኮሰ። አሁን ሁላችንም ፈራን።ከተማው ጸጥ ረጭ አለ። ተኩሱ ሲቀጥል። ሁሉም ተደናገጠ።በጥቂት ሰከንዶች ውስጥ ሰዎች መጮህ እና ወደ ተለያዩ
አቅጣጫዎች መሮጥ ጀመሩ። ሰዎች ተገፋፉ፣ አንዱ በአንዱ ላይ ወደቀ የወደቁ ሰዎችን ረግጦ ያልፋል። እናቶች ልጆቻቸውን አጡ፤ ቤተሰብ ተለያየ፤ የከተማው ነዋሪዎች ለዘመናት
የለፉበትን ጥሪት ትተው ሮጡ። ልቤ በፍጥነት ይመታል።
ወደ ማታሩ ጆንግ ለመግባት ሁለት መንገዶች አሉ።የመኪና መንገድ እና በወንዙ በማቋረጥ :: አማጺዎች ግን በየብስ በኩል እያጠቁ ሲገሰገሱ ሰዎች ወደ ወንዝ እንዲሮጡ ተገደዱ። ብዙ
ሰዎች በፍርሃት ወንዝ ውስጥ ገቡ። እስኪደክማቸው ድረስ ዋኙ:: ወታደሮቹ በቁጥር መበለጣቸውን ሲያውቁ ቀድመው ነበር ከተማውን ለቀው የወጡት :: ህዝብ ሁሉ የተመመበት
አንድ ማምለጫ መንገድ ብቻ ነበር፡፡ ተከተልናቸው። መንገዱ ጭቃ ነበር፡፡ ጭቃ የያዛቸውን አካል ጉደተኞች ማንም
አልረደቸውም፡፡ ማንም ሊረደቸው የሚፈልግ የራሱን ህይወት አደጋ ላይ ይጥላል፡፡ አማጺዎቹ ወደ ሰው መተኮስ ጀመሩ። ሰው ከተማውን ለቆ እንዲወጣ አልፈለጉም። ነዋሪውን በተለይ
ሴቶችን እና ህጻናትን ምሽግ በማድረግ ከመከላከያ ጥቃት መዳን ይፈልጋሉ፡፡
እንደምንም ግን ወደ ማምለጫው መንገድ ስንዳረስ አማጺዎች ቀጥታ ወደ እኛ መተኮስ ጀመሩ። ሁሉንም የመሳሪያ አይነቶች ተጠቀሙ።ጥይት አዘነቡ፤ ሮኬት ና መትረየስ ተኮሱ ቦምብ ወረወሩ። እኛ ምንም አላመነታነም:: መያዝ የከፋ እንደሚሆን እናውቃለን፡፡ ከተያዝን እንመለመላለን : በጋለ ጩቤ አእግ
ብለው ደስ ያላቸው ቦታ ላይ ይጻፉብናል። ስለዚህ ማምለጥ ግድ ነው። ብዙ ኪሎ ሜትሮችን ሳናርፍ በፍጥነት ሮጥን::
አማጺዎች ተስፋ ቆርጠው ወደ ማታሩ ጆንግ ተመለሱ። እኛ ግን መሮጣችንን ቀጠልን፡፡
ለብዙ ቀናት ስድስታችን ጅኒየር ታሎ ካሎኮ፣ ገብሬላ፣ ካሊ እና እኔ በቀጭን መንገድ ጥቅጥቅ ባለ ጫካ መሃል ተጓዝን፡፡ሁላችንም ሃሳብ ላይ እንመስላለን። ማውራት የለም፤ መሄድ
ብቻ:: ስለ ቤተሰቦቼ ደግሜ ላያቸው እችላለሁ ብየ አሰብኩ፡፡ማልቀስ ፈለኩ በጣም ስለ ራበኝ ግን አቅም አልነበረኝም ::
በተተወ መንደር ውስጥ ባዶ መሬት ላይ ተኛን።በሚቀጥለው ቀን ሙዝ፣ብርቱካን እና ኮኮናት ዛፍ በሚገኝበት መንደር አለፍን፡፡ ሙዙ ጥሬ ስለሆነ ቀቅለን ነበር የበላነው። ከዛ ትንሽ ብርቱካን እና ኮኮናት በላን። በቂ ምግብ ግን ማግኘት
አልቻልንም። ከቀን ቀን ረሃባችን እየተባባሰ መጣ። ስለዚህ ወደ
ማታሩጆንግ ተደብቀን በመግባት ምግብ መግዣ ገንዘብ ማግኘት አለብን፡፡ ከዚህ ውጭ ሌላ ምንም አማራጭ አልነበረንም።
በመንገዳችን ጸጥ ረጭ ባለ በተከዳ ከተማ ስናልፍ አስክሬን፣የተበላሸ ምግብ ፣ የእንጨት ስራዎች፣ ልብስ እና ሌሎች
እቃዎች በየቦታው ወድቆ አየን። አስክሬን ተቆራርጦ እጅ፣ እግር እና ሌሎች የሰውነት ክፍሎች በየቦታው ወድቋል። ይሄን ሳይ አዞረኝ፤ አቅለሸለሸኝ። የነ ካሊሎ ቤት በከተማ እንዳሉ ሌሎች
ቤቶች በሩ ተሰብሯል ተቃጥሏል። የጥይት ቀዳዳ በበሩ በኩል ሲታይ ስታር ቢራ እና ሲጋራ መጠቅለያ ደግሞ ድጃፍ ላይ ወድቋል።
ገንዘቡን ባስቀመጥኩት ቦታ ሳይነካ አገኘሁት። ገንዘቡን ካልሴ ውስጥ ከትቼ ወደ ረግረጉ ወረድን፡፡ አማጺዎች ባህር ዳርቻው አካባቢ ማማ ላይ ወጥተው ይጠብቁ ስለነበር መንፏቀቅ ነበረብን፡፡ ከመካከላችን አንድ ልጅ ትልቅ ቦርሳ አንግቶ ስለነበር ጠባቂዎች አይትውት ተኩስ ከፈቱ።ከጠባቂዎች እስክንርቅ
ድረስ በፍጥነት ሮጥን።አመሻሽ ላይ ብዙ ሰዎች ያሉበት መንደር ውስጥ ገባን፡፡
ገንዘብ ስለያዝን ምግብ ይሸጡልናል የሚል ተስፋ ነበረን።
ነገር ግን አንዳንዶቹ ለክፉ ጊዜ ምግብ መቆጠብ ስለምንፈልግ አንሸጥም ሲሉ ሌሎቹ ደግሞ ያለ ምንም ምክንያት አንሸጥም አሉ። ራሳችንን ወቀስን፡፡ የጦርነት ወቅት እንዲህ ተለዋዋጭ
ነው። ማንም አይቆጣጠረውም፡፡ ነገሮችን በፍጥነት መረዳትና
የመትረፌያ መንገዶችን መቀየስ ነበረብን። ያን ምሽት አማራጭ
ስላልነበረን ሰዎች ወደ መኝታ ሲሄዱ ምግብ ሰርቀን በላን::
ምግብ እና ውሃ ሳናገኝ ብዙ ስለቆየን
ጉሮራችን ተንቃቃ፣ ሆድ ቁርጠትም ተሰማን። ከንፈራችን ተጣበቀ መገጣጠሚያችንም ዝሏል። ምግብ የት እንደምናገኝ ግራ ገባን። በመጨረሻ ረሃብ ወደ ማታሩ ጆንግ እንደገና
መለሰን።
የበጋ ወቅት ስለ ነበር ሳር ቅጠሉ ቢጫ ሁኗል። በሳር መሃል እየሄድን ድንገት አማጺዎች መጡብን። ገብሬላ ላይ ሽጉጥ ደቀኑ፤ እኔ ላይ ደግሞ ጩቤ ሰነዘሩ፡ "ደንግጧል" ብሎ ከት ብሎ
ሳቀ፡፡ አልፈን ወደመጣንበት መንደር መለሱን፡፡ አማጺዎቹ እጅጌ ጉርድ ቲሽርት፣ ጂንስ ጃኬት እና ሱሪ ለብሰዋል እና አዲዳስ ጫማም ተጫምተዋል። እጃቸው ላይ ውድ ስዐቶች አስረዋል።
ሁሉም በጉልበት የተቀሙ ወይም የተዘረፍ ናቸው።
ፈራሁ! እጆቼ እና እግሬዎቼ ተንቀጠቀጡ።አማጺዎች ትንሽም እንኳ ለመንቀሳቀስ ከሞከርን እንደሚገሉን ዝተዋል።ከጓደኞቼ እንዱ ወይም ወንድሜ ቢንቀሰቀስ ለማምለጥ ቢሞክርና ቢገሉንስ ብየ ሰግቻለሁ።
በአቅራቢያው ወዳለ መንደር ስንደርስ የመንደሩን ነዎሪዎች ሴቶች ህጻናት ሳይሉ ሁሉንም አሰለፉ። መጀመሪያ ካሊሎ
ቀጥሎ እኔን እና ሌሎች ወንዶችን መረጠው ወደ ፊት እንድንመጣ አዘዙ።
"ጠንካራ ወታደሮችን እንፈልጋለን” በማለት ጅኒየር
#ክፍል_አራት
#የታዳጊው_ወታደር_ትዝታ
#በኢስማኤል_ቤህ
#ክፍለእየሱስ_አበበ_እንደተረጎመው
እንደርስበታለን ብለን ከገመትነው ስዓት በፊት ማታሩ ጆንግ ደረሰን፡፡ ስለ ቤተሰቦቻችን ምንም ዜና የለም። በተስፋ ከመጠበቅ እና ደህንነታቸውን ከመመኘት ውጪ ምን ማድረግ እንዳለብን አናውቅም::
አማጺዎች ከ ማታሩ ጆንግ ሃያ ኪሎ ሜትር እና ከዛ በላይ በምትርቀው ሱምብያ ከተማ መሰፈራቸውን ሰማን። ቀጥሎ አማጺዎች ደብዳቤ እንደላኩና ደብዳቤው የነሱም መምጣት፤ ስለ
እኛ እየታገሉ እንደሆነ እና የእንኳን ደህና መጣችሁ አቀባበል እንደሚፈልጉ ያትታል። መልዕክተኛው ወጣት ነው፡፡ ሰውነቱ ላይ የአማጺዎችን ስም እና አጸርሆተ ቃል ማለትም (አአግ
አብዮታዊ የአንድነት ግንባርን ተነቅሷል። ከአውራ ጣቱ ውጪ ሁሉንም ጣቶቹን ቆርጠውበታል። አውራ ጣት በብዙ ሰወች
የተለመደ የፍቅር ምልክት ነበር።
መልዕክቱ እንደደረስ ሰዎች ወደ ጫካ መሸሸግ ጀመሩ። የካሊሎ ቤተሰብ ግን እንድንቆይ እና ስንቅ ይዘን እነሱን
እንድንከተል ጠየቁን። ቆየን፡፡
ያ ምሽት በህይወቴ ለመጀመሪያ ጊዜ የከተማን ህይወት የሚሰጠው የሰዎች መኖር እና መንፈሳቸው እንደሆነ ተረዳሁ። የሰዎች አለመኖር ከተማውን አስፈሪ አደረገው። ድቅድቅ ጨለማ እና ከባድ ጸጥታ! የዶሮዎች እና የወፎች ዝማሬ
እንኳ የለም። ጨለማ ፈጥኖ መጣ፤ ጨረቃም የለችም። አየሩ ከብዷል፡፡ ተፈጥሮ ራሷ የሚመጣውን የፈራች ትመስላለች።
ሰዎች ለሳምንት ያህል ተሸሸጉ። አማጺዎች ግን አልመጡም።በኋላ ሌላ መልዕክተኛ ላኩ፡፡ መልዕክተኛው ታዋቂ የካቶሊክ ካህነ ነበር፡፡ ከማስፈራራት ውጪ ካህኑን ምንም አላደረጉትም።
ቃሉን ተቀብሎ ህዝቡ ወደ ጫካ ተመልሶ ገባ። አስር ቀናት አለፉ አማጺዎች ግን አልመጡም፡፡ ነዋሪው ወደ ከተማ መመለስ ጀመረ። ትምህርት ቤቶች ተከፈቱ፤ ሰዎች ወደ ዕለት ተዕለት
ኑሯቸው ተመለሱ፡፡ አምስት ቀናት በሰላም አለፉ፡፡
በመጨረሻ አማጺዎች ሲመጡ ቀላል የተኩስ ድምጽ ሰማን፡፡
ጅኒ የር፣ታሉ፣ ካሎኮ፣ ገብሬላ፣ ካሊሎ እና እኔ ቤት ውስጥ ነበረን
"ሰማቹህ?” ብለው ጠየቁ። ወታደሮች ናቸው የተኮሱት ወይስ ሌላ አካል እያልን በማሰብ ደርቀን ቆምን።
ከደቂቃዎች በኋላ ሶስት ጊዜ ተተኮሰ። አሁን ሁላችንም ፈራን።ከተማው ጸጥ ረጭ አለ። ተኩሱ ሲቀጥል። ሁሉም ተደናገጠ።በጥቂት ሰከንዶች ውስጥ ሰዎች መጮህ እና ወደ ተለያዩ
አቅጣጫዎች መሮጥ ጀመሩ። ሰዎች ተገፋፉ፣ አንዱ በአንዱ ላይ ወደቀ የወደቁ ሰዎችን ረግጦ ያልፋል። እናቶች ልጆቻቸውን አጡ፤ ቤተሰብ ተለያየ፤ የከተማው ነዋሪዎች ለዘመናት
የለፉበትን ጥሪት ትተው ሮጡ። ልቤ በፍጥነት ይመታል።
ወደ ማታሩ ጆንግ ለመግባት ሁለት መንገዶች አሉ።የመኪና መንገድ እና በወንዙ በማቋረጥ :: አማጺዎች ግን በየብስ በኩል እያጠቁ ሲገሰገሱ ሰዎች ወደ ወንዝ እንዲሮጡ ተገደዱ። ብዙ
ሰዎች በፍርሃት ወንዝ ውስጥ ገቡ። እስኪደክማቸው ድረስ ዋኙ:: ወታደሮቹ በቁጥር መበለጣቸውን ሲያውቁ ቀድመው ነበር ከተማውን ለቀው የወጡት :: ህዝብ ሁሉ የተመመበት
አንድ ማምለጫ መንገድ ብቻ ነበር፡፡ ተከተልናቸው። መንገዱ ጭቃ ነበር፡፡ ጭቃ የያዛቸውን አካል ጉደተኞች ማንም
አልረደቸውም፡፡ ማንም ሊረደቸው የሚፈልግ የራሱን ህይወት አደጋ ላይ ይጥላል፡፡ አማጺዎቹ ወደ ሰው መተኮስ ጀመሩ። ሰው ከተማውን ለቆ እንዲወጣ አልፈለጉም። ነዋሪውን በተለይ
ሴቶችን እና ህጻናትን ምሽግ በማድረግ ከመከላከያ ጥቃት መዳን ይፈልጋሉ፡፡
እንደምንም ግን ወደ ማምለጫው መንገድ ስንዳረስ አማጺዎች ቀጥታ ወደ እኛ መተኮስ ጀመሩ። ሁሉንም የመሳሪያ አይነቶች ተጠቀሙ።ጥይት አዘነቡ፤ ሮኬት ና መትረየስ ተኮሱ ቦምብ ወረወሩ። እኛ ምንም አላመነታነም:: መያዝ የከፋ እንደሚሆን እናውቃለን፡፡ ከተያዝን እንመለመላለን : በጋለ ጩቤ አእግ
ብለው ደስ ያላቸው ቦታ ላይ ይጻፉብናል። ስለዚህ ማምለጥ ግድ ነው። ብዙ ኪሎ ሜትሮችን ሳናርፍ በፍጥነት ሮጥን::
አማጺዎች ተስፋ ቆርጠው ወደ ማታሩ ጆንግ ተመለሱ። እኛ ግን መሮጣችንን ቀጠልን፡፡
ለብዙ ቀናት ስድስታችን ጅኒየር ታሎ ካሎኮ፣ ገብሬላ፣ ካሊ እና እኔ በቀጭን መንገድ ጥቅጥቅ ባለ ጫካ መሃል ተጓዝን፡፡ሁላችንም ሃሳብ ላይ እንመስላለን። ማውራት የለም፤ መሄድ
ብቻ:: ስለ ቤተሰቦቼ ደግሜ ላያቸው እችላለሁ ብየ አሰብኩ፡፡ማልቀስ ፈለኩ በጣም ስለ ራበኝ ግን አቅም አልነበረኝም ::
በተተወ መንደር ውስጥ ባዶ መሬት ላይ ተኛን።በሚቀጥለው ቀን ሙዝ፣ብርቱካን እና ኮኮናት ዛፍ በሚገኝበት መንደር አለፍን፡፡ ሙዙ ጥሬ ስለሆነ ቀቅለን ነበር የበላነው። ከዛ ትንሽ ብርቱካን እና ኮኮናት በላን። በቂ ምግብ ግን ማግኘት
አልቻልንም። ከቀን ቀን ረሃባችን እየተባባሰ መጣ። ስለዚህ ወደ
ማታሩጆንግ ተደብቀን በመግባት ምግብ መግዣ ገንዘብ ማግኘት አለብን፡፡ ከዚህ ውጭ ሌላ ምንም አማራጭ አልነበረንም።
በመንገዳችን ጸጥ ረጭ ባለ በተከዳ ከተማ ስናልፍ አስክሬን፣የተበላሸ ምግብ ፣ የእንጨት ስራዎች፣ ልብስ እና ሌሎች
እቃዎች በየቦታው ወድቆ አየን። አስክሬን ተቆራርጦ እጅ፣ እግር እና ሌሎች የሰውነት ክፍሎች በየቦታው ወድቋል። ይሄን ሳይ አዞረኝ፤ አቅለሸለሸኝ። የነ ካሊሎ ቤት በከተማ እንዳሉ ሌሎች
ቤቶች በሩ ተሰብሯል ተቃጥሏል። የጥይት ቀዳዳ በበሩ በኩል ሲታይ ስታር ቢራ እና ሲጋራ መጠቅለያ ደግሞ ድጃፍ ላይ ወድቋል።
ገንዘቡን ባስቀመጥኩት ቦታ ሳይነካ አገኘሁት። ገንዘቡን ካልሴ ውስጥ ከትቼ ወደ ረግረጉ ወረድን፡፡ አማጺዎች ባህር ዳርቻው አካባቢ ማማ ላይ ወጥተው ይጠብቁ ስለነበር መንፏቀቅ ነበረብን፡፡ ከመካከላችን አንድ ልጅ ትልቅ ቦርሳ አንግቶ ስለነበር ጠባቂዎች አይትውት ተኩስ ከፈቱ።ከጠባቂዎች እስክንርቅ
ድረስ በፍጥነት ሮጥን።አመሻሽ ላይ ብዙ ሰዎች ያሉበት መንደር ውስጥ ገባን፡፡
ገንዘብ ስለያዝን ምግብ ይሸጡልናል የሚል ተስፋ ነበረን።
ነገር ግን አንዳንዶቹ ለክፉ ጊዜ ምግብ መቆጠብ ስለምንፈልግ አንሸጥም ሲሉ ሌሎቹ ደግሞ ያለ ምንም ምክንያት አንሸጥም አሉ። ራሳችንን ወቀስን፡፡ የጦርነት ወቅት እንዲህ ተለዋዋጭ
ነው። ማንም አይቆጣጠረውም፡፡ ነገሮችን በፍጥነት መረዳትና
የመትረፌያ መንገዶችን መቀየስ ነበረብን። ያን ምሽት አማራጭ
ስላልነበረን ሰዎች ወደ መኝታ ሲሄዱ ምግብ ሰርቀን በላን::
ምግብ እና ውሃ ሳናገኝ ብዙ ስለቆየን
ጉሮራችን ተንቃቃ፣ ሆድ ቁርጠትም ተሰማን። ከንፈራችን ተጣበቀ መገጣጠሚያችንም ዝሏል። ምግብ የት እንደምናገኝ ግራ ገባን። በመጨረሻ ረሃብ ወደ ማታሩ ጆንግ እንደገና
መለሰን።
የበጋ ወቅት ስለ ነበር ሳር ቅጠሉ ቢጫ ሁኗል። በሳር መሃል እየሄድን ድንገት አማጺዎች መጡብን። ገብሬላ ላይ ሽጉጥ ደቀኑ፤ እኔ ላይ ደግሞ ጩቤ ሰነዘሩ፡ "ደንግጧል" ብሎ ከት ብሎ
ሳቀ፡፡ አልፈን ወደመጣንበት መንደር መለሱን፡፡ አማጺዎቹ እጅጌ ጉርድ ቲሽርት፣ ጂንስ ጃኬት እና ሱሪ ለብሰዋል እና አዲዳስ ጫማም ተጫምተዋል። እጃቸው ላይ ውድ ስዐቶች አስረዋል።
ሁሉም በጉልበት የተቀሙ ወይም የተዘረፍ ናቸው።
ፈራሁ! እጆቼ እና እግሬዎቼ ተንቀጠቀጡ።አማጺዎች ትንሽም እንኳ ለመንቀሳቀስ ከሞከርን እንደሚገሉን ዝተዋል።ከጓደኞቼ እንዱ ወይም ወንድሜ ቢንቀሰቀስ ለማምለጥ ቢሞክርና ቢገሉንስ ብየ ሰግቻለሁ።
በአቅራቢያው ወዳለ መንደር ስንደርስ የመንደሩን ነዎሪዎች ሴቶች ህጻናት ሳይሉ ሁሉንም አሰለፉ። መጀመሪያ ካሊሎ
ቀጥሎ እኔን እና ሌሎች ወንዶችን መረጠው ወደ ፊት እንድንመጣ አዘዙ።
"ጠንካራ ወታደሮችን እንፈልጋለን” በማለት ጅኒየር
👍1