አትሮኖስ
280K subscribers
110 photos
3 videos
41 files
462 links
╔╦╦╦═╦╗╔═╦═╦══╦═╗
║║║║╩╣╚╣═╣║║║║║╩╣
╚══╩═╩═╩═╩═╩╩╩
ግጥሞች አዳዲስና ቆየት ያሉ የታዋቂ ደራሲያን መፅሐፍቶችን በ PDF እንዲሁንም
ያልተነበቡ ድርሰቶችን ግጥሞችን ታሪኮችን ያገኙበታል።


Contact. @atronosebot
please dont touch the leave button.😔😳😳
Download Telegram
#ከዕለታት_ግማሽ_ቀን


#ክፍል_አንድ


#በአሌክስ_አብርሃም

የዛሬ አሥራ ሦስት ዓመት እግዚእብሔርን ለመሆን ተመኝቼ ነበር፤ አልተሳካልኝም፡፡ .
እግዚእብሐርን መሆን ስላልተሳካልኝ “በቃ ለምን ሰይጣን አልሆንም?” የሚል ሐሳብ
ውል ብሎብኝ፡ ሰይጣን ለመሆን ሞከርኩ እሱም ቢሆን እንዲህ እንደሚወራው ቀላል አልነበረም(ክፋት በሰይጣን እጅ ያምር፤ሲይዙት ያደናግር) እንግዲህ ሁለቱንም ካልሆንኩ ራሴን ልሁነውና የመጣውን ልጋፈጠው” ብዬ እግዜርነትንና ሰይጣንነት ልለካ አውልቄ ያስቀመጥኩትን እኔነት ፍለጋ ዙሪያዬን ባስስ ራሴም የለሁም፡፡ ይሄ ደግሞ ማነው?” እስክል ራሴን ፈጽሞ የማላውቀው አዲስ ፍጡር ሆኖ አገኘሁት፡፡ይኼው እስራ ሦስት ዓመት ጊዜ ፈጣን ነው፡፡ እንደ ደራሽ ጎርፍ ጠራርጎ የማይወሰድብን እያግበሰበሰም አምጥቶ የማይጭንብን ጉድ የለም፡፡

የአሥራ ሁለተኛ ክፍል የማትሪክ ውጤት የተነገረበት ሰሞን ነበር፤ ከብዙዎች ተመርጠን ወደ ዩኒቨርስቲ መግቢያ ከፍተኛ ውጤት ስላመጣን “በምድር ላይ መከፈት የማንችለው በር የለም! የሚል የወጣትነት የዋህ ትዕቢት፣ ወጣት ልባችንን የሞላበት ጊዜ፣ የሰፈሩ
ወጣት ሴቶች እናተ ልጆች ያሻችሁን ጠይቁን” በሚል ዘወርዋራ ፈገግታ፡ የዕድሜ እኩያ እንዳልገንን ሁሉ ለትልቅ ሰው ከሚሰጥ አክብሮት ጋር ይሽኮረመሙልን የነረበት ጊዜ( ለእናተ ያልሆነ ሴትነት ዓይነት) ትምህርት ላይ ደከም ያሉ የሰፈራችን ልጆች
በወላጆቻቸው እንደነሱ አትሆኑም?” እየተባሉ ስማችን ከኩርኩም ዝናብ በፊት
እንደመብረቅ ጆሯቸው ላይ ይንባረቅባቸው የነበረበት ጊዜ “ምነው እነዚህን ልጆት ከዚህ ሰፈር በነቀለልን”ብለው በሆዳቸው ሳይረግሙን አልቀሩም (መማር ባይሆንላቸው
መራገም አያቅታቸው) አላፊ አግዳሚው በኩራት ፈገገ ይልልን በነበረበት ጊዜ ይኼም ፈገግታ ትምህርት ሚንስቴር እውቅና ሰጥቶቷቸው ከፈተነን “ኬሚስትሪና ማተማቲክስ ምናምን 'ሰብጀክቶች በላይ፡ የሰፈሩ ሰው በአደራ ሰጥቶን በከፍተኛ ውጤት ላለፍነው
“በጎ አርአያነት ነፍሳችን ካርድ ላይ የሚያስቀምጠው “A” በነበረ ጊዜ
ያ ጊዜ ሕይወት ያለ የሌለ እንደ በረዶ የነጣ ጥርሷን ፈገግ ብላ ታሳየን የነበረችበት የክረምት ወር ነበር፡፡ ለእኔና ለጓደኛዩ መሐሪ! “ምን ጓደኛ ናቸው እነዚህ፣ ወንድማማች እንጂ እማምላክንም ይሉ ነበር የሚያውቁን ሁሉ፡፡ አልተጋነነም፡፡ አንድ ሰፈር ነው
ተወልደን ያደግነው፡፡ በቤታችንና በቤታቸው መሃል ያሉት አንድ አምስት ቤቶችና፣የሰፈሩ ልጆች ኳስ የምንጫወትበት አቧራማ ሜዳ ብቻ ነበሩ የመሃሪ እናት ዝንጥ ያለች የቢሮ ሠራተኛ ነበረች፡ ማሚ የምንላት መልከመልካም እናት፤ አገር ምድሩ እትዬ ሮሚ” የሚላት፡ ዘርፋፋ ባለ ከሸከሽ ቀሚስ በመቀነት ሸብ አድርገው ነጠላ በሚያጣፉ እናቶች መሃል ጉልበቷ ድረስ ያጠረ ቀሚስ የምትለብስ፣ ቀጥ ያለ አቋም ያላትና ጸጉሯን ባጭሩ የምትቆረጥ በእውቅ የተቀረጹ ዓምዶች በመሳሰሉ ውብ ጠይም እግሮቿ በተራመደች ቁጥር፣ እንደ ሙዚቃ በተመጠነ ርቀት ቋ ቋ ቋ የሚል ድምፅ በሚያወጣ ባለረዥም ተረከዝ ጫማ የምትውረገረግ ዘመናዊ እናት፡፡ ባሏ የጸሐፊነት ሥራዋን እንድታቆም አድርጓት በኋላ ተወችው እንጂ፡ በፊት በፊት መሐሪን ጧት እቤታችን አምጥታ ለእናቴ ትተወውና ወደ ሥራዋ ትሄዳለች፤ ስትመለስ ትወስደዋለች።አብረን ነው ያደግነው፡፡ ነገሩ ዋጋ ተቆርጦለት የልጅ ጠባቂነት አይሁን እንጂ፡ ለቤተሰቦቼ
በሰበብ አስባቡ ገንዘብም ቁሳቁስም መደገፏ አይቀርም ነበር፡፡ ከዚያ
ዕድሜያችን ጀምሮ እኔም ሆንኩ መሐሪ ሌሎች የመንደሩ ልጆች ጋር ቅርበታችን
እምብዛም ነበር፡፡

ማሚ ሁለታችንንም ግራና ቀኝ ይዛን ቄስ ትምህርት ቤት ስትወስደን ትዝ ይለኛል፡፡
በሕፃንነት ዕድሜያችን (አምስት ዓመት ቢሆነን ነው) ያኔ መንገድ ላይ ሰላም ያሏትን ሰዎች ስም ዝርዝር ብባል፣ አንድ ባንድ አስታውሳቸዋለሁ፤ በተለይ ወንዶቹ
የሚያሽቆጠቁጣቸው ነገር ነበር!

ታዲያ መምሬ ምስሉ ለተባሉ ፊደል አስቆጣሪ ስታስረክበን፣ በሹክሹክታ እንዲህ ስትላቸው ሰማኋት"የኔታ አንድ ላይ ከተቀመጡ መላም የለው፧ አነጣጥለው ያስተምሯቸው መሐሪ ግን እንዲህ ስትል አልሰማኋትም አለኝ፡ አቋቋማችን እኮ ከእኔ ይልቅ እሱ ይቀርብ ነበር፡፡ ስንት ዓመት አልፎ፣ ካደግን በኋላ፣ ማሚን ስንጠይቃት “ውይ! በምን አስታወስከው ልጄ?” ብላ በሳቅ ፍርስ አለችና ብያቸዋለሁ እውነትህን ነው ብላ አመነች። መሐሪ እየሳቀ የሆነ ሼባ ነገር ነው ነገር አይረሳም አለ ሁልጊዜም
ዝንጉቱን የሚያስተባብለው፤ እኔን ነገር ከነከስኩ የማለቅ ሽማግሌ በማድርግ ነበር፡፡
ጎን ለጎን ተቀምጠን ሰዎቸ ለሁለታችንም ያወሩልንን አለፍ ስንል “ምናሉ? ብሎ
የሚጠይቅበኝ ጊዜ ብዙ ነው ለዙሪያው ቸልተኛ ነበር!

መምሬ ምስሉ የማሚን አደራ ለመጠበቅ በቁጣም በአለንጋም ሊነጣጥሉን ብለው
ብለውን አልሆን ስላላቸው እኒህ ልጆች፣ እንደ ዳዊትና የዮናታንን ጓደኝነት ነብሳቸው አብሮ የተሰፋ ነው!” ከሚል ምሳሌ ጋር እንደ ፍጥርጥራችሁ ብለው ተውን፡፡ ለረዥም ጊዜ ዳዊትና ዮናታን ረባሽ የቄስ ትምህርት ቤት ሕፃናት ይመስሉኝ ነበር፣ ሮሐ ናት በኋላ በመፅሐፍ ቅዱስ ውስጥ ያሉ ጓደኛሞች መሆናቸውን የነገረችን (ሰንበት ትምህርት
ቤት ተማርኩ ብላ) ይኼንንም የነገረችን ቀን አብረን ሰምተን ዞር ስትል መሐሪ
ምናለች” ብሎኛል፣ አድጎም አልለቀቀው! ከዚያን ጊዜ ጀምሮ አስራ ሁለተኛ ክፍል
እስክንደርስ እኔና መሐሪ ተነጣጥለን አናውቅም።አንድ ክፍል፣ አንድ ወንበር፣ አልፎ አልፎ ጎን ለጎን ያሉ ክፍሎች፡ ግን አንድ ትምህርት ቤት ነበር ያሳለፍነው።

ዐሥረኛ ክፍል ስንደርስና መሐሪ ሮሐ ከምትባል ልጅ ፍቅር ሲጀማምረው ነበር፣ ሦስተኛ ሰው አብሮን የታየው፤ያኔ ታዲያ ሮሐን ወደድኩ ሲል (ባይወዳት ነበር የሚገርመኝ ሁለታችንም ብርክ ያዘን፤ ነገሩ ጋሼ ጋር ከደረሰ ሁለታችንንም ከገጸ-ምድር ያጠፋናል የሚል ፍርሃት ነበር ያራደን፡፡ ጋሼ የምንለው የመሐሪን አባት ነው፡፡ ጋሽ ዝናቡ ዶፍ ቢሉት ይሻል ነበርኮ” እንባባላለን እኔና መሐሪ ስናማው። ጋሽ ዝናቡ ሲቆጣ፣ ቁጣው ልክ እንደ ርዕደ መሬት ከሰው አልፎ የቤቱን እቃዎችና የግቢውን ዛፎች የሚያንዘፈዝፍ ይመስል ነበር፡፡ ፊቱ የማይፈታ፣ ረዥም ቦክሰኛ የሚመስል ሰው ነበር፡፡ ዳኛ ስለሆነ ነው መስል ቤታቸው ፍርድ ቤት ነበር የሚመስለኝ፡፡ መሐሪም፣ ማሚም ተሽቆጥቁጠው ነው
የሚኖሩት፡፡ ደግነቱ ቁጣው በየአራት ዓመት አንዴ የሚከለት የተፈጥሮ አደጋ ዓይነት ነበር፡፡ ያንን መሬት አንቀጥቅጥ ቁጣውን ያስነሳሉ ተብለው በቤተሰቡ የታወቁ እና ቤተሰቡ እንደተላጠ የኤሌክትሪክ ሽቦ ላለመንካት የሚጠነቀቃቸው፣እንደ ዐሠርቱ
ትዕዛዛት ከቤተሰቡ አልፎ በእኔም ልብ በፍርሃት ፊደላት የተቀረጹ ምክንያቶች ቢበዙ ከሦስት አይበልጡም ነበር

የመጀመሪያው ምክንያት ዝርዝሩ አይገባኝም እንዲሁ እቤታቸው ጎራ ባልኩበት ጊዜ ሁሉ ከለቃቀምኩት ደመ ነፍሳዊ መረጃ ገባኝ ያልኩት ወደ እውነት የሚጠጋ ጥርጣሬ ነው በማሚ(በሚስቱ) እንደሚበሳጭ ይገባኝ ነበር …ነገረ ሥራዋ ያበሳጨዋል! ምንጊዜም እቤት ሲገባ አጋጣሚ ቤት ውስጥ ከሌለች በቁጣ ይጠይቃል “የት ሄደች?” መሐሪ በፍርሃት እየተንተባተበ ማሚ የሄደችበትን ያስረዳል፡፡ ብዙ ጊዜ ወይ የታመመ
ልትጠይቅ፣ አልያም ለቅሶ ልትደርስ ነው የሚሆነው መልሱ! ጋሽ ዝናቡ ታዲያ “የሷ ለቅሶ አያልቅም!” ይላል! ድምፁ ውስጥ መነጫነጭ አለ! ጋሽ ዝናቡ እንዲህ ይጠይቅ እንጂ፣ ማሚን እቤት ቢያገኛት ደግሞ፣ ሰላም እንኳን ሳይላት አልፎ ነበር የሚገባው…ብዙ ጊዜ እንደባልና ሚስት ፈታ ብለው አይነጋገሩም
1👍1
#ከዕለታት_ግማሽ_ቀን


#ክፍል_ሁለት


#በአሌክስ_አብርሃም


የሌላውን ተማሪ እንጃ፣ እኔ ግን ብርድ ብርድ ነበር የሚለኝ።ነገረ ስራዋ ሁሉ የሚሸክክ ሴትዮ።በፊቷ ላይ ሳቅም ቁጣም የለም፣ ድምፁዋ ዝቅም ከፍም አይል። እራሷ አጅብሰም ምናምን ተፈልፍላ የተሰራች እጅ ሥራ ነገር ነበር የምትመስለኝ።ገና በመጀመሪያው ቀን የእጅ ሥራ የሚባለውን ትምህርት ስንጀምር፣ ሰላም ! ከሰፈነበት ክፍላችን አሰልፋ የእግር ኳስ ሜዳውን ተሻግሮ ወደ ሚገኘው “የእጅ ሥራ ክፍሉ ወደሚባል ሕንፃ ወሰደችን፡፡ ከትልልቅ ጥርብ ድንጋዮች የተሠራና ግራጫ የሸክላ ጣሪያ
የተደፋበት ግብ ቤት ነው፡፡ በድንጋዮቹ መጋጠሚያ ላይ እረንጓዴ ሻጋታ እንደ
አረንጓዴ ሽበት የጋገረበት ጣሪያው ላይ ብዙ ሣር ያበቀለበት፣ ለሞላ የወፍ ዘር
ድብርታም ዋነሶች ብቻ የሚሰፍሩበት ዕድሜ ጠገብ ግንብ ቤት ነው፡፡ ዱሮ ጣሊያን ሰዎችን እያሰረ የሚያሰቃይበት
እስር ቤት ነበር ይባላል! በመስኮቱ ትክክል በዕድሜ ብዛት የዛገ የ በ ቅርጽ ያለው የብረት ጎል አለ፡፡እስረኞችን ከዚህ ክፍል እያወጡ እዚህ ብረት ላይ በስቅላት ይቀጧቸው ነበር፡፡ ሆነ ብለው ነው በመስኮቱ ትክክል የሰሩት፡፡
እስረኞቹ ሰው ሲሰቀል በመስኮት በኩል አሻግረው እንዲመለከቱና ሞትን ፈርተው
ጣልያንን እንዲተባበሩ፡፡ ነገሩ ነበር ብቻ ሳይሆን፣ ምስክር ያለው ታሪክም ነው።

አፈሩ ይቅለላቸውና፣ ከዓመት እስከ ዓመት የጊዮርጊስ ቤተክርስቲያን ጥበቃ ሆነው ይሠሩ የነበሩ፣ በየዓመቱ የአርበኞች ቀን ሲከበር ደረቱ ላይ ግራና ቀኝ ብዙ ሜዳሊያ የተደረደረበት የአርበኛ ካኪ ልብሳቸውን ለብሰውና፤ ወርቃማ የዘንባባ ጥልፍ ያለበት ባርኔጣቸውን ደፍተው፣ አሮጌ ጦር እየሰበቁ (በኋለኛው ዘመን እርጅናው ተጭኗቸው ተውት እንጂ ትልቅ ጋሻም ነበራቸው) በቴሌቪዥን የሚቀርቡት ሰውዬ ታሪክ ሲናገሩ
በጆሮዬ ሰምቻቸዋለሁ “ጥሊያን አርበኞቹ በዱር በገደል ሲያስቸግሯት፣ የአርበኞች
ቤተሰቦች ማሰቃየት ጀመረች እዚህ ታች አሁን “አጤ ብልጣሶር ተማሪ ቤት” የተባለው ውስጥ፣ የግንብ እስር ቤት ሠርታ ሰውን ሁሉ እየሰበሰበች ማጎር፣ ጠቁሙ እያለች መግረፍ፣ መስቀል ጀመረች እስከ አሁን ያ እስር ቤት ተማሪ ቤቱ ውስጥ አለ” ሲሉ ሰምቻለሁ፡፡ “ዓፄ ብልጣሶር አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት” ማለት እንግዲህ፣ የኛ ትምህርት ቤት ነው።

ያች አስተማሪ ታዲያ አሰልፋ የወሰደችን ወደዚያ ከፍል ነበር፡፡ ውስጡ በጠራራ ፀሐይ እንኳን የሚያንዘፈዝፍ ብርድ ያለበት ሰፊ አዳራሽ፣ የንብረት ማስቀመጫ ሆኖ በመከረሙና ተጸድቶ ባለማወቁ፣ እምክ እምክ የሚሸትና በአቧራ የተሸፈነ ነበር።ግማሽ የሚሆነው የአዳራሹ ክፍል ተማሪዎች ከወረቀት፣ ከካርቶን፣ ከጣውላና ከብዙ ዓይነት ቁሳቁስ በሠሯቸው የእንስሳትና ሰው ቅርጻ ቅርጾች፣ በተሰባበሩ ወንበሮች፡
በተከመሩ እሮጌ መጻሕፍትና ገና ባልተከፈቱ ብዙ ካርቶን ጠመኔዎች የተሞላ ነበር

እንግዲህ በመጀመሪያ ከፍለ ጊዜ ስሟን እንኳን በወጉ ሳታስተዋውቀን በዚያ ቅዝዝ ባለ ድምፅ ይሄን አዳራሽ አፅዱ!” አለችን፡፡ ከዚያን ቀን ጀምሮ ያ ክፍል እኔም መሐሪም ማየት ራሱ ያንገሸግሸን ነበር፡፡ ከስንት ዓመት በኋላ ትምህርት ቤቱ ሙሉ ለሙሉ ፈርሶ ሲታደስ፣ ያ…የድንጋይ ከፍል ቅርስ ነው!” ተብሎ እንዳለ ነበር የተተወው፡፡ በኋላ እኔና መሀሪ አስራ ሁለተኛ ክፍል እንደጨረስን ሮሐን በመሀላችን አድርገን በሩ ላይ ፎቶ ተነስተናል፡፡ እሷ እንዳካበዳትሁት አይደለም ያምራል” አለች! ተያይተን በሳቅ ፈረስን!

የዚች አስተማሪ ሌላው አስገራሚ ሥራ፣ አንድ ቀን ከቀንም ቀን ቅዳሜ ቀን ጧት
ትምህርታዊ ጉብኝት እናደርጋለን፡፡” ብላ ጠራችን፡፡ ቅዳሜን በሚያህል ቀን ትምህርት ቤት መጠራታችን ሳያንስ፤ልታስጎበኘን የወሰደችብን ቦታ ይኼው ሩብ ክፍለ ዘመን ሊሆነው ተቃርቦ እንኳን ትዝ ሊለኝ ይዘገንነኛል፡፡ ያው እንግዲህ እሷ እንደምትለውና ድሮ እጅ ሥራ ደብተሬ የመጀመሪያ ገጽ ላይ ጽፌው እንደተኘው የእጅ ሥራ ትምህርት መሠረታዊ ዓላማው የተማሪዎችን የፈጠራ ክህሎት እና የአምራችነት ፍላጎት
ከፍ በማድረግ አምራች ዜጋ ማፍራት ነው" ይህን ከህሎት ያዳበሩና ለእኛ አርአያ ሊሆኑን የሚችሉ የእጅ-ሥራ ጥበብ ባለሙያዎች ወደሚገኙበት ቦታ ነበር ለጉብኝት የወሰደችን፡፡ የከተማው ማረሚያ ቤት! ከጣሊያን እስር ቤት ወደ ሐበሻ እስር ቤት፡፡

የማረሚያ ቤቱ የግንብ አጥር የተሠራበት ድንጋይ የትምህርት ቤታችን የእጅ-ሥራ ክፍል ከተሠራበት ጋር ተመሳሳይ ነው፡፡ ድንጋዩ ብቻ ሳይሆን፣ አሰካኩም አንድ ዓይነት ነበር፤ ወይ ይኼንንም ጣሊያን ሠርቶታል አልያም ከጣሊያን እግር ሥር ቁጭ ብለው የተማሩ የአበሻ መሐንዲሶች አንጸውታል፤ መቼስ ደግደጉን መማር ባንዳነት አያስብል፡፡ የማማው ከፍታ ደመናውን ሰንጥቆ የገባ ነበር የሚመስለው፡፡ ከብዙ ፍተሻ ሰኋላ ከባዱ
ተንሸራታች የብረት በር በሁለት መሣሪያ በታጠቁ ወታደሮች እየተገፋና ሲጢጢጢ እያለ ሲከፈት፣ የሚያለቅስ ይመስል ነበር… በሰሩ መንሸራተቻ የብረት ሃዲድ ላይ የተደፈደፈው የጆሮ ኩክ የመሰለ ግራሶ እንደእንባ ግራ ቀኝ ቀልጦ ይፈስሳል፡፡

ወደ ግቢው በሰልፍ ስንገባ፣ በሕይወቴ ይኖራል ብዬ የማላስበው ዓለም፣ ፊት ለፊቴ ተጋረጠ… መጨረሻቸው የማይታይ፣ በጣም ብዙ እሮጌ የቆርቆሮ ቤቶች ከስንትና ከስንትና ዓመታት በፊት ፋሽናቸው ነፍሶበት ወደ ቅርስነት የሚያዘግሙ፣ የተረሱ የድሮ ፎቶዎች
ላይ ብቻ የማውቃቸውን ልብሶች የለበሱ ታራሚዎች ግቢውን ሞልተውታል።

እንዳንዶቹ አቧራው እንደ ደመና የሚነሳ ሜዳ ላይ እየተጯጯሁ መረብ ኳስ ይጫወታሉ።ግቢው ራሱ ይኼ ነው የማይባል የተለየ ሽታ ነበረው።ለምንም ነገር ግድ የሌላቸው የሚመስሉ ታራሚዎች፣ በቸልታ ያዩናል …ደግሞ ለከፋቱ ገና በሩ ላይ እንደደረስን የአእምሮ ሕመምተኛ የሆነ ታራሚ ፊት ለፊታችን ገጠመን፡፡ ልብሱ እላዩ ላይ አልቋል፣ በባዶ እግሩ ነበር … ልጋጉ ይዝረበረባል፣ እግርና እጁ የታሰረበትን ከባድ ሰንሰለት እያቅጨለጨለ ሳያቋርጥ ቻው ቻው ቻው መውጣት የለም ቻው በቃ ገባችሁ፣ መውጣት የለም …” ይለናል ያ ድምፅ እስከ ዛሬ ጆሮዬ ላይ አለ።

እንደተሰለፍን በእስረኞች መሃል አልፈን፣ የእደ ጥበብ ክፍል ወደሚባለው ትልቅ የቆርቆሮ አዳራሽ ተወሰድን፡፡ ወደ ውስጥ ስንገባ ብዙ የሽመና ሥራ የሚሰሩ
ታራሚዎች እግራቸውን ጉድጓድ ውስጥ ቀብረው ነጠላ ጋቢ ይሰራሉ…አንዳንዶቹ
ረዣዥም የክር ድር እዚያና እዚህ ግድግዳ ላይ በተሰኩ ሚስማሮች ላይ ያደራሉ።ግርግሩ ለጉድ ነው፣ ጫጫታው ይጨንቃል፡፡ አስተማሪያችን ሰብሰብ አደረገችንና “ወደሚሰሩት ሰዎች እየሄዳችሁ፣ ምን እንደሚሰሩ? እንዴት እንደሚሰሩ? የመሥሪያ መሣሪያዎቻቸው ስም ምን እንደሚባል እየጠየቃችሁ ማስታወሻ ያዙ:” አለችን፡፡ግራ
እንደገባን እኔና መሐሪ ወደ አንዱ ጸጉሩን ወደተላጨ ሸማኔ ጠጋ ብለን ከግራ ወደቀኝ ከቀኝ ወደግራ የሚወረውራትን፣ ውስጧ የሚተረተር ነጭ ክር ያለባትን መወርወሪያ ስንመለከት፣ ሸማኔው ድንገት በዜማ፤

ተማሪ ውሻ ቀባሪ ውሻ ሲቀብር… አነቀው ነብር…” አለና ልክ እንደ ነብር ጥፍር
ጣቱን ለቀልድ እንጨፍርሮ ሲቃጣን፤ ደንግጠን ወደኋላ ስናፈገፍግ ሌሎቹ በሳቅ አውካኩ።

ወይ የዘንድሮ ተማሪ ቤት ….እንደያው እሁን ምን ሊያስተምሩ እዚህ ሲኦል
አመጧችሁ?” አለን፣ ለራሱ በሚመስል አነጋገር፡፡ ትኩስ የተላጨው ሞላላ አናቱ ላይ አልፎ አልፎ ቋቁቻና ጠባሳ ነገር አለው፡፡

“ለምንድነው የታሰርከው” አልኩት ድንገት፡፡ ያልጠበቀው ጥያቄ ስለሆነ የገረመው ይመስል፣ አንዴ እኛን፣ አንዴ ጓደኞቹን ተመለከተና፣
👍3