አንድ ባለቀለም ጉርድ ፎቶግራፍ ብቻ ነበር ውስጡ ያኘሁት፤አንዲት እድሜዋ ሦስት ዓመት የሚሆናት ቆንጅዬ ሕጻን ልጅ ፎቶ፡፡ከፎቶው ጀርባ
በእንግሊዝኛና አማርኛ ቅልቅል እንዲህ የሚል ጽሁፍ ተጽፏል የሎዛ የእጅ ጽሁፍ ነው፡፡
hello,uncle! guess what ...My name is "ማምሻ ዳግማዊ!!
ሟርት ነው አልኩ ለራሴ፡፡ ግን ደግም አይገርምም፣ ሎዛ እብድ ናት እብድ ቤተሰብ
መመስረትም ትችላለች፡፡ እናም ዓለም ፈውሷን ለመቀበል የሎዛ ዓይነት ብዙ እብዶች ሳያስፈልጓት አይቀም፡፡
✨ጨረስን✨
አረ ተዉ #MUTE ያደረጋቹ #UNMUTE አድርጉ ምንም አልሰማም አላችሁ እኮ😡 ምን ይሻለኛል ወይ እስቲ ስለድርሰቱ አስተያየት ስሰጡ #UNMUTE የማታደርጉበትን ምክንያት ምንድን ነው??? እባካችሁ ንገሩኝ..Post የሚደረጉትን ብዙ ሰው የማያነበው ከሆነ ማዘጋጀቱም ይደብራል..ሌላ ድርሰት ለመጀመር ወይም ለማቆም አስተያየታችሁን (ምክንያታችሁን) እፈልጋለው...በዛሬው ቀን ብቻ እንኳን #381 ሰው ቻናሉን #MUTE አድርጓል አስተያየት ይስጡ
@atronosebot ን ይጠቀሙ
በእንግሊዝኛና አማርኛ ቅልቅል እንዲህ የሚል ጽሁፍ ተጽፏል የሎዛ የእጅ ጽሁፍ ነው፡፡
hello,uncle! guess what ...My name is "ማምሻ ዳግማዊ!!
ሟርት ነው አልኩ ለራሴ፡፡ ግን ደግም አይገርምም፣ ሎዛ እብድ ናት እብድ ቤተሰብ
መመስረትም ትችላለች፡፡ እናም ዓለም ፈውሷን ለመቀበል የሎዛ ዓይነት ብዙ እብዶች ሳያስፈልጓት አይቀም፡፡
✨ጨረስን✨
አረ ተዉ #MUTE ያደረጋቹ #UNMUTE አድርጉ ምንም አልሰማም አላችሁ እኮ😡 ምን ይሻለኛል ወይ እስቲ ስለድርሰቱ አስተያየት ስሰጡ #UNMUTE የማታደርጉበትን ምክንያት ምንድን ነው??? እባካችሁ ንገሩኝ..Post የሚደረጉትን ብዙ ሰው የማያነበው ከሆነ ማዘጋጀቱም ይደብራል..ሌላ ድርሰት ለመጀመር ወይም ለማቆም አስተያየታችሁን (ምክንያታችሁን) እፈልጋለው...በዛሬው ቀን ብቻ እንኳን #381 ሰው ቻናሉን #MUTE አድርጓል አስተያየት ይስጡ
@atronosebot ን ይጠቀሙ
የሚላት፣የሆነ ቀን ቡና ልትገዛ መጥታ
ያስደነበረችኝን ልጅ ነው፡፡ በጣም ወጣትና ቆንጆ ነች፡፡ አገር ቤት የመድረክ ቲያትር ስትሠራ፣ አውቃትም አደንቃትም ስለነበር፣ ከረዥም ጊዜ በኋላ ሳያት ደስ ብሉኝ፣ ፈገግ ብዬ ሰላም አልኳት! ኮስተር እንዳለች አንገቷን ብቻ ቀለስ እድርጋ ዝም አለች፡፡ “ይቅርታ አገር ቤት አውቅሻለሁ የእንባ ቀብድ የሚል ቲያትር ስትሠሪ…” ብዬ ከመጀመሬ፣ ፊቷ ተቀያይሮ “ይቅርታ! የኔ ወንድም ሥራ የለህም?” ብላ ኩም አደረገችኝ፡፡ ትንሽ ክብደት
ከመጨመሯ በቀር፣ አሁንም ቆንጆ ናት፡፡ ፊቷ ግን አስፈሪ ነበር፡፡ አሁን ገና የአባቷን ሞት ያረዷት ይመስል፣ ደህና ዋልሽ? ሲሏት የሚዘረገፍ የሚመስል እንባ ያረገዘ ሐዘንተኛ ፊት፣ ምን ስበብ አግኝቼ ባለቀስኩ የሚል ፊት፡፡ ብዙ አታወራም። ከዚያ ቀን በኋላም ብዙ ጊዜ ወደዚህ ሱቅ ስትመጣ፡ ኮስተር እንዳለች የምትፈልገውን ገዝታ ነው የምትሄደው።..........
አንብበው ጨርሰዋል አሁን ደሞ ከዚሁ ሳይወጡ #UNMUTE አድርገው ይውጡ አመሰግናለው
✨ይቀጥላል✨
ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ
ለወዳጆ #Share እያደረጉ
ያስደነበረችኝን ልጅ ነው፡፡ በጣም ወጣትና ቆንጆ ነች፡፡ አገር ቤት የመድረክ ቲያትር ስትሠራ፣ አውቃትም አደንቃትም ስለነበር፣ ከረዥም ጊዜ በኋላ ሳያት ደስ ብሉኝ፣ ፈገግ ብዬ ሰላም አልኳት! ኮስተር እንዳለች አንገቷን ብቻ ቀለስ እድርጋ ዝም አለች፡፡ “ይቅርታ አገር ቤት አውቅሻለሁ የእንባ ቀብድ የሚል ቲያትር ስትሠሪ…” ብዬ ከመጀመሬ፣ ፊቷ ተቀያይሮ “ይቅርታ! የኔ ወንድም ሥራ የለህም?” ብላ ኩም አደረገችኝ፡፡ ትንሽ ክብደት
ከመጨመሯ በቀር፣ አሁንም ቆንጆ ናት፡፡ ፊቷ ግን አስፈሪ ነበር፡፡ አሁን ገና የአባቷን ሞት ያረዷት ይመስል፣ ደህና ዋልሽ? ሲሏት የሚዘረገፍ የሚመስል እንባ ያረገዘ ሐዘንተኛ ፊት፣ ምን ስበብ አግኝቼ ባለቀስኩ የሚል ፊት፡፡ ብዙ አታወራም። ከዚያ ቀን በኋላም ብዙ ጊዜ ወደዚህ ሱቅ ስትመጣ፡ ኮስተር እንዳለች የምትፈልገውን ገዝታ ነው የምትሄደው።..........
አንብበው ጨርሰዋል አሁን ደሞ ከዚሁ ሳይወጡ #UNMUTE አድርገው ይውጡ አመሰግናለው
✨ይቀጥላል✨
ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ
ለወዳጆ #Share እያደረጉ
👍1
ዕድሜው፣ ዘለግ ያለች ሴት ይፈልጋል: ያውም ቆንጆ፣ ያውም ጨዋ፣ ያውም ልጅ እግር! መቼም ደግ ኑሮ ይዞት እንጂ ዕድሜው ስድሳን ሳይሻገር አይቀርም::
ታዲያ በዚያ ሰሞን ትልቅ መነጽሩን ይሰካና፣ ፌስቡክ እና ኢንስታግራም ላይ ሴት ሲያስስ ይውላል! አንድ የተረዳሁት ነገር፣ አሜሪካ ያሉ አንዳንድ ወንዶች፣ በተለይ ትንሽ ጥሩ ሥራና ገንዘብ ቢጤ ካላቸው፣ ድፍን የኢትዮጵያ ሴት አሜሪካ ያለ ወንድ ላግባሽ ካላት፣ ትዳር ቢኖራት እንኳ ጣጥላው የምትመጣ ይመስላቸዋል፡፡ ልከራከር ሞክሬ ነበር ገና አዲስ ነህ ዝም በል” ተባልኩ፡፡ ትዕቢት ያጠየመው በራስ መተማመናቸው የሚገርም ዓይነት ነው። እናም የዶክተር ጓደኞች (በእርሱ ዕድሜ የሚሆኑ) በየሳምንቱ
ቅዳሜ ከሰዓት ቁርጥ ሲበሉና ሲያወሩ ወደ ሱቋ ጎራ ሲሉ፣ ልክ እንደ ምግብ ቤት ሜኑ ኮራ ብለው በየስልኮቻቸው ሴት ይመርጣሉ፡፡ ቀፋፊ አስተያየት ሲሰጡ በግርምት እመለከታለሁ።
“ይቺ ጥሩ ናት ዶክተር” ይላል አንዱ፣ ፌስቡክ ላይ የአንዷን ፎቶ እያሳየ፡፡
"አይ!" ዛላዋ ከባድ ነው የግድ ይዛው ነው እንጂ አንድ ስትወልድ ዝርግፍግፍ ውድቅድቅ ነው የምትለው"
܀
“ይችኛይቱስ?"
“አይ! ይች ሥራዋ ፎቶ መለጠፍ ብቻ ነው እንደ ጉሊት ፌስቡከ ላይ ተሰጥታ የምትውል ላግባ እንዴ ደሞI?”
እሽ፣ ይች ምን ይወጣላታል? አፈር ስሆን ተመልከታት! ባላገባ ኑሮ አለቃትም ነበር
ሃሃሃሃሃ"
“ይች? እስቲ ከኋላዋ የሚያሳይ ፎቶ ካላት…ዋው ቢዩቲፉል! እስቲ እጇን ጠጋ አድርገው እስቲ እግሯ ….! ልቅም ያለች! እንዲህ ያለችዋን ነው ያልኩህ! የሳቀችበት ፎቶ የለም? ዋናው ፊት ነው ከፍትፍቱ ፊቱ ሃሃሃሃሃሃሃ..አቤት ጥርስ! አቤት ውበት
ምኑን ብትበላው ነው ባክህ? ይኼ ጤፍ እኮ ታምሩ ብዙ ነው! ሃሃሃ! እኔኮ የሚገርመኝ፣
ኢትዮጵያ አሥራ ሦስት ወር ሙሉ ፀሐይና አቧራ ሲከካቸው እየከረመ፣ እንዴት ነው ቆዳቸው እንዲህ የሚጠራው? ደሞ ቅላቷ! ማነው ስሟ? ፊደላዊት… ስሟ ራሱ ማማሩ እሷ ራሷ የግዜር የእጅ ጽሑፍ አይደል እንዴ የምትመስለው! ፓ! ስሟ አፍ ላይ መጣፈጡ ምራቁን ዋጠ ዶክተር፡፡ ትንሽ ስልኩን እየጎረጎረ ቆዬና “አይይይይይይ" አለ
"ምነው?"
ተይዛለች ኢን ርሌሽንሽፕ ይላል ስታተሷ…ወንዱ መች ተኝቶ ያድራል “
ሃሃ…ይችን ይችን ለኛ ተዋት… ዝም ብለህ ጻፍላት…” በየአፋቸው እየተንጫጩ አበረታቱት !ዶክተር ጻፈላት!.....
አንብበው ጨርሰዋል አሁን ደሞ ከዚሁ ሳይወጡ #UNMUTE አድርገው ይውጡ አመሰግናለው
✨ይቀጥላል✨
ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ
ለወዳጆ #Share እያደረጉ
ታዲያ በዚያ ሰሞን ትልቅ መነጽሩን ይሰካና፣ ፌስቡክ እና ኢንስታግራም ላይ ሴት ሲያስስ ይውላል! አንድ የተረዳሁት ነገር፣ አሜሪካ ያሉ አንዳንድ ወንዶች፣ በተለይ ትንሽ ጥሩ ሥራና ገንዘብ ቢጤ ካላቸው፣ ድፍን የኢትዮጵያ ሴት አሜሪካ ያለ ወንድ ላግባሽ ካላት፣ ትዳር ቢኖራት እንኳ ጣጥላው የምትመጣ ይመስላቸዋል፡፡ ልከራከር ሞክሬ ነበር ገና አዲስ ነህ ዝም በል” ተባልኩ፡፡ ትዕቢት ያጠየመው በራስ መተማመናቸው የሚገርም ዓይነት ነው። እናም የዶክተር ጓደኞች (በእርሱ ዕድሜ የሚሆኑ) በየሳምንቱ
ቅዳሜ ከሰዓት ቁርጥ ሲበሉና ሲያወሩ ወደ ሱቋ ጎራ ሲሉ፣ ልክ እንደ ምግብ ቤት ሜኑ ኮራ ብለው በየስልኮቻቸው ሴት ይመርጣሉ፡፡ ቀፋፊ አስተያየት ሲሰጡ በግርምት እመለከታለሁ።
“ይቺ ጥሩ ናት ዶክተር” ይላል አንዱ፣ ፌስቡክ ላይ የአንዷን ፎቶ እያሳየ፡፡
"አይ!" ዛላዋ ከባድ ነው የግድ ይዛው ነው እንጂ አንድ ስትወልድ ዝርግፍግፍ ውድቅድቅ ነው የምትለው"
܀
“ይችኛይቱስ?"
“አይ! ይች ሥራዋ ፎቶ መለጠፍ ብቻ ነው እንደ ጉሊት ፌስቡከ ላይ ተሰጥታ የምትውል ላግባ እንዴ ደሞI?”
እሽ፣ ይች ምን ይወጣላታል? አፈር ስሆን ተመልከታት! ባላገባ ኑሮ አለቃትም ነበር
ሃሃሃሃሃ"
“ይች? እስቲ ከኋላዋ የሚያሳይ ፎቶ ካላት…ዋው ቢዩቲፉል! እስቲ እጇን ጠጋ አድርገው እስቲ እግሯ ….! ልቅም ያለች! እንዲህ ያለችዋን ነው ያልኩህ! የሳቀችበት ፎቶ የለም? ዋናው ፊት ነው ከፍትፍቱ ፊቱ ሃሃሃሃሃሃሃ..አቤት ጥርስ! አቤት ውበት
ምኑን ብትበላው ነው ባክህ? ይኼ ጤፍ እኮ ታምሩ ብዙ ነው! ሃሃሃ! እኔኮ የሚገርመኝ፣
ኢትዮጵያ አሥራ ሦስት ወር ሙሉ ፀሐይና አቧራ ሲከካቸው እየከረመ፣ እንዴት ነው ቆዳቸው እንዲህ የሚጠራው? ደሞ ቅላቷ! ማነው ስሟ? ፊደላዊት… ስሟ ራሱ ማማሩ እሷ ራሷ የግዜር የእጅ ጽሑፍ አይደል እንዴ የምትመስለው! ፓ! ስሟ አፍ ላይ መጣፈጡ ምራቁን ዋጠ ዶክተር፡፡ ትንሽ ስልኩን እየጎረጎረ ቆዬና “አይይይይይይ" አለ
"ምነው?"
ተይዛለች ኢን ርሌሽንሽፕ ይላል ስታተሷ…ወንዱ መች ተኝቶ ያድራል “
ሃሃ…ይችን ይችን ለኛ ተዋት… ዝም ብለህ ጻፍላት…” በየአፋቸው እየተንጫጩ አበረታቱት !ዶክተር ጻፈላት!.....
አንብበው ጨርሰዋል አሁን ደሞ ከዚሁ ሳይወጡ #UNMUTE አድርገው ይውጡ አመሰግናለው
✨ይቀጥላል✨
ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ
ለወዳጆ #Share እያደረጉ
#የእንባ_ቀብድ
፡
፡
#ክፍል_ሶስት(የመጨረሻ ክፍል)
፡
፡
#በአሌክስ_አብርሃም
ተይዛለች ኢንሪሌሽንሽፕ ይላል ስታተሷ…ወንዱ መች ተኝቶ ያድራል “
ሃሃ…ይችን ይችን ለኛ ተዋት… ዝም ብለህ ጻፍላት…” በየአፋቸው እየተንጫጩ
አበረታቱት !ዶከተር ጻፈላት!
1
2
3ቀን
መለሰች፡፡ መልሶ ጻፈላት
4..
5...
መለሰችለት፡፡ የጻፈውን ጮክ ብሎ ያነብልናል፡፡ የመለሰችውንም እንደዛው :: በግልጽ ፎቶዎችሽን አይቼ ደስ ስላሉኝ መተዋወቅ ፈለኩ፡፡ ብችልና ስልከሽን ብትሰጭኝ ደውዬ ብናወራ ደስ ይለኛል”ብሎ ጻፈላት ስልኳን ትልካለች፣ አትልከም፣ ውርርዱ ቀለጠ፡፡
ጭራሽ ከየዋሌታቸው የመዘዙትን የውርርድ ገንዘብ፣ እኔው ያዥ ሁኜ አረፍኩ፡፡ ትንሽ
ውስጤን ጸጸተኝ! አንዲት ነገር ዓለሙን የማታውቅ፣ በአዲሰ አበባ ብልጣብልጥነት፣
የሕይወትን ማሳለጫ የምታቋርጥ በመሰላት ሚስኪን የአገሬ ቆንጆ ላይ፣ ዕጣ ሲጣጣሉ
ማስጣሉ ሲቀር፣ የውርርድ ገንዘብ ያዥ መሆኔ፣ ውስጤን እንደ አንድ ነገር ሲያቃጥለው
ይሰማኛል፡፡ የወጋሪዎቹን ልብስ ጠባቂ ሆንኩ፡፡
7..8... 9 ስልኳን ላከችለት፡፡
የውርርዱ ገንዘብ ጥሬ ሥጋ ተቆረጠበት፡፡ ውስኪ ወረደበት፡፡
“አብርሃም ና እንጂ …”
“ጥሬ ሥጋ አልበላም
“ማነሽ ጥለሽለት”
“ያዝ ውስኪ
አልጠጣም
"ለስላሳ አምጭለት …”
11..12….13….14 ምን እንዳላት እንጃ…ምን እንዳወሩ እግዜር ይወቅ፣ ዶክተር በደፈናው
“ስለቁም ነገር እያወራን ነው” አለ፡፡ ከዛን ቀን ጀምሮ የዶክተር ጓደኞች ስለልጅቱ ሲያወሩ
ቆጠብ ማለት እንደጀመሩ አስተዋልኩ፡፡
15.. 16….17…18.…19..20 ቀናት አለፉ፡፡ ገርሞኝ የፊደላዊትን የፌስቡክ አካውት በዓይነቁራኛ እከታተላለሁ ትሰጥፈዋለች ይኼን ፎቶ! በምኞት የሰከረ ወንድ ከሚያጎርፈው ላይክ መኻል፣ ዓይኔ ዶክተርን ይፈልጋል፡፡ አገኘዋለሁ! “ላይክ ያደርጋል፡፡ ፈገግታዋ አንዳች የሚነዝር ውበት አለው፡፡ አንድ ወር..ሁለት ወር..ዓይኔ
ነው ወይስ ..እስከምል የፊደላዊት የፌስቡከ ስታተስ' ተቀይሮ አረፈው::
"relationship" የነበረው ወደ "open relationship" ተቀይሯል።
የሽማግሌዎቹ ባሕሪ ቁማር ነበር፡፡
“ተከፈተ! ሃሃሃሃ… አላልኩህም! ገና ሲንግል ትሆናለች” አለ አንዱ ሽማግሌ፡፡ ሌላው ይቀበላል…
"ሲንግል ምን አላት? ገና ድንግል ትሆናላች፡፡ አሜሪካኮ ነው 'ብራዘር …ሃሃሃሃሃ ኡሁ!
ኡሁ ሳል የቀላቀለ የሽማግሌዎች ሳቅ
ፋሲልን “ይችን ልጅ ማስጠንቀቅ አለብኝ” አልኩት፡፡
“አንተ ምን ቤት ነህ? አርፈህ ተቀመጥ!”
“ምንም አይሰማህም? ይች ልጅ ነገ መጥታ እንደ እነሯ የስቃይ ሕይዎት ውስጥ ብትገባስ?
እዚህ እንድ ሐሙስ የቀረው ሽማግሌ ጋር ምንድነው የምትሆነው?”
ለምን ግማሽ ሐሙስ አይቀረውም! …ሲጀመር ልጅቱ ራሷ ምቀኛ ነው የምትልህ፡፡ ወር እንኳን ሳይሞላት፣ በሯን ስትከፍት አይገባህም እንዴ? አዲስ ነህ! እንዲህ ዓይነት ነገር ውስጥ ጣልቃ አትግባ! እነዚህ በተንኮል ጥርሳቸውን የነቀሉ ሽማግሌዎች አንዴ ከጠመዱህ፣ጥሩ አይደለም. ወዲህም ገባያዬን እንዳትዘጋው… ሄደው አንዲት ቃል ቢተነፍሱ ሐበሻ እዚህ ሱቅ ዝር አይልም” ዝም አልኩ፡፡
ፊደላዊት ደወለች! ደወለች… ደወለች ቤቢ…… ደወለች…" ጎበጥ ጎበጥ እያለ ወደ ውጭ ይወጣል ዶከተር፡፡ አይመለስም! ለሰዓታት ስልክ ላይ ነው! ቀናት ሄዱ፣ ወራት ተከተሉ፣ ሁለት፣ ሦስት፣ አራት ወር፡፡
ምናገባኝ ብዬ መከታተሌን ትቸ ከርሜ አንድ ቀን ሳላየው የቆየሁትን የፊደላዊትን አካውንት ተመለከትኩ፡፡ ጭር ብሏል፡፡ የለጠፈቻቸውን ፎቶዎች ሁሉ አንስታቸው ነበር፡፡ ምን መጣ ብዬ መመልከቴን ቀጠልኩ፡፡ ከረዥም ቀናት መዘናጋት በኋላ ስመለስ፣ ስታተሏ ሲንግል” ሆኗል። ደነገጥኩ! ፍቅረኛዋ በአደጋ ሞቶ መሆን አለበት አልኩ ለራሴ፡፡ ዝግመተ ለውጥ እንዲህም ፈጥኖ አያውቅ:: አዎ ዝግመተ ለውጥ፡፡ እንዲህ ነበር ዝንጀሮ መሰል ፍጥረት ቀስ በቀስ ወደ ሰው ተቀየረ ያሉን፡፡ መሆን አለበት:: ቀን ከተለጠው፣ ዝንጀሮም ሰው፣ ሰውም ዝንጀሮ መሆን ሳይችል አይቀርም: ሰው የአገርህ ልጆች በረሃ አቋርጠው ተሰደዱ ሲባል ከንፈር ይመጣል፡፡ እግርማ በረሃን አቋርጦ ካለፈ እሰዬው ነው፡፡ እንዲህ ልቦቻችን ውስጥ ያቆጠቆጠውን ሰውነት፣ ፍቅር፣ እውነት፣
ጨፍጭፈን ዘላለም የማንሻገረውን በረሃ ልባችን ውስጥ ከመፍጠር የባስ፣ ከንፈርየሚያስመጥጥ ምን ሰቆቃ አለ?
አንድ ምሽት ድንገት ዶክተር ደወለና “ወደ አገር ቤት የምትልከው ቀለል ያለ ነገር ካለ፣ ነገ ይዘህ ና፣ መሄዴ ነው አለኝ
“የት?”
አገሬ ነዋ! ጕዳይ አለኝ” አልጠየኩም፣ ጉዳዩ እንዲሁ ይገባኛል!
ቀናት ተቆጠሩ፡፡ ዶክተር ወደ ኢትዮጵያ ከሄደ ከሃያ ቀናት በኋላ የፊደላዊትን የፌስቡክ አካውንት” ተመለከትኩ፡፡
“ሰው ዝም ብሎ እግዚአብሔርን ተስፋ ቢያደርግ መልካም ነው ከሚል ጥቅስ ጋር ረዥም ቬሎ ለብሳ ፣ብቻዋን የተነሳችው የሚያምር ፎቶ ተለጥፏል። ቬሎዋን ሳይ ያንን ትኩስ ሰውነት በበረዶ ያጀሎት ዓይነት ሰውነቴ ቅዝቅዝ ሲል ተሰማኝ፡፡ እጅግ በጣም ብዙ የእንኳን ደስ አለሽ አስተያየት ጎርፎላታል።
እግዚአብሔር የቅኖች አምላክ ነው?”
“ይገባሻል የኔ ቆንጆ?”
“የእብርሃም የሣራ....በሳምንቱ ከቤተሰቦቿ ጋር በወርቃማ ጥልፍ ያበደ ጥቁር ካባ ለብሳ፣ በሹሩባዋ ሳይ ወርቃማ አከሊል ደፍታ፣ የማላውቃትን ንግሥተ ሳባ መስላ
(ለምን እንደሆን እንጃ እንደዚያ መሰለችኝ) የተነሳችውን የምላሽ ፎቶ ለጠፈች፡፡ በጣም
ውብ ልጅ ነት፡፡ ያንለታውኑ ከአሥር በላይ የሚሆኑ ተደጋጋሚ የሰርግ ፎቶዎቿን
ለጠፌች፡፡ መንፈስ ያገባች ይመስል አንዱም ላይ የባሏ ፎቶ የለም።
ፋሲል እየሳቀ እና የአንድ ሽማግሌ ፎቶ፣ ባል ብላ ለጥፋ ሐበሻ ለብር ነው ለቪዛ ነው እያለ፣ አዛ ያድርጋት እንዴ? ዋናው ማግባቷ ነው፣ በቃ!” አለቀ፡፡ ከሠርግ የመጀመሪያ ቀን ጀምሮ፣የእኔ ባሉት ነገር እየታፈረ እንዴት ይኖራል?… እያልኩ ፎቶዎቹን እመለከታለሁ፡፡
ዓይኔ አንዱ ፎቶዋ ላይ አረፈ፡፡ ዓይኖቿ እንባ ሞልተው፣ በሚያማምሩ ጣቶቿ አፏን
እፍና፣ እናትና አባቷ ፊት ለስንብት ቆማለች፡፡ ፋሲልን አሳየሁት፡፡“ወግ ነው ሲዳሩ ማልቀስ!” ብሎ እንደሚተርት እርግጠኛ ነበርኩ፡፡ ግን እንደዚያ አላለም፡፡ ቅሬታ ይሁን ሐዘን ባረበበት ፊት፣
“የእንባ ቀብድ! ብሎ ዝም አለ፡፡
የዶክተርን አካውት ተመለከትኩ፡፡ ጭር ባለው የፌስቡክ አካውንቱ ላይ፣ አንዲት ዐረፍተ ነገር በጎሉ እንግሊዝኛ ፊደላት ተለጥፋለች፡፡
love never gets old"
ፍቅር አያረጅምህ!
አንብበው ጨርሰዋል አሁን ደሞ ከዚሁ ሳይወጡ #UNMUTE አድርገው ይውጡ አመሰግናለው
✨ጨረስን✨
ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ
ለወዳጆ #Share እያደረጉ
፡
፡
#ክፍል_ሶስት(የመጨረሻ ክፍል)
፡
፡
#በአሌክስ_አብርሃም
ተይዛለች ኢንሪሌሽንሽፕ ይላል ስታተሷ…ወንዱ መች ተኝቶ ያድራል “
ሃሃ…ይችን ይችን ለኛ ተዋት… ዝም ብለህ ጻፍላት…” በየአፋቸው እየተንጫጩ
አበረታቱት !ዶከተር ጻፈላት!
1
2
3ቀን
መለሰች፡፡ መልሶ ጻፈላት
4..
5...
መለሰችለት፡፡ የጻፈውን ጮክ ብሎ ያነብልናል፡፡ የመለሰችውንም እንደዛው :: በግልጽ ፎቶዎችሽን አይቼ ደስ ስላሉኝ መተዋወቅ ፈለኩ፡፡ ብችልና ስልከሽን ብትሰጭኝ ደውዬ ብናወራ ደስ ይለኛል”ብሎ ጻፈላት ስልኳን ትልካለች፣ አትልከም፣ ውርርዱ ቀለጠ፡፡
ጭራሽ ከየዋሌታቸው የመዘዙትን የውርርድ ገንዘብ፣ እኔው ያዥ ሁኜ አረፍኩ፡፡ ትንሽ
ውስጤን ጸጸተኝ! አንዲት ነገር ዓለሙን የማታውቅ፣ በአዲሰ አበባ ብልጣብልጥነት፣
የሕይወትን ማሳለጫ የምታቋርጥ በመሰላት ሚስኪን የአገሬ ቆንጆ ላይ፣ ዕጣ ሲጣጣሉ
ማስጣሉ ሲቀር፣ የውርርድ ገንዘብ ያዥ መሆኔ፣ ውስጤን እንደ አንድ ነገር ሲያቃጥለው
ይሰማኛል፡፡ የወጋሪዎቹን ልብስ ጠባቂ ሆንኩ፡፡
7..8... 9 ስልኳን ላከችለት፡፡
የውርርዱ ገንዘብ ጥሬ ሥጋ ተቆረጠበት፡፡ ውስኪ ወረደበት፡፡
“አብርሃም ና እንጂ …”
“ጥሬ ሥጋ አልበላም
“ማነሽ ጥለሽለት”
“ያዝ ውስኪ
አልጠጣም
"ለስላሳ አምጭለት …”
11..12….13….14 ምን እንዳላት እንጃ…ምን እንዳወሩ እግዜር ይወቅ፣ ዶክተር በደፈናው
“ስለቁም ነገር እያወራን ነው” አለ፡፡ ከዛን ቀን ጀምሮ የዶክተር ጓደኞች ስለልጅቱ ሲያወሩ
ቆጠብ ማለት እንደጀመሩ አስተዋልኩ፡፡
15.. 16….17…18.…19..20 ቀናት አለፉ፡፡ ገርሞኝ የፊደላዊትን የፌስቡክ አካውት በዓይነቁራኛ እከታተላለሁ ትሰጥፈዋለች ይኼን ፎቶ! በምኞት የሰከረ ወንድ ከሚያጎርፈው ላይክ መኻል፣ ዓይኔ ዶክተርን ይፈልጋል፡፡ አገኘዋለሁ! “ላይክ ያደርጋል፡፡ ፈገግታዋ አንዳች የሚነዝር ውበት አለው፡፡ አንድ ወር..ሁለት ወር..ዓይኔ
ነው ወይስ ..እስከምል የፊደላዊት የፌስቡከ ስታተስ' ተቀይሮ አረፈው::
"relationship" የነበረው ወደ "open relationship" ተቀይሯል።
የሽማግሌዎቹ ባሕሪ ቁማር ነበር፡፡
“ተከፈተ! ሃሃሃሃ… አላልኩህም! ገና ሲንግል ትሆናለች” አለ አንዱ ሽማግሌ፡፡ ሌላው ይቀበላል…
"ሲንግል ምን አላት? ገና ድንግል ትሆናላች፡፡ አሜሪካኮ ነው 'ብራዘር …ሃሃሃሃሃ ኡሁ!
ኡሁ ሳል የቀላቀለ የሽማግሌዎች ሳቅ
ፋሲልን “ይችን ልጅ ማስጠንቀቅ አለብኝ” አልኩት፡፡
“አንተ ምን ቤት ነህ? አርፈህ ተቀመጥ!”
“ምንም አይሰማህም? ይች ልጅ ነገ መጥታ እንደ እነሯ የስቃይ ሕይዎት ውስጥ ብትገባስ?
እዚህ እንድ ሐሙስ የቀረው ሽማግሌ ጋር ምንድነው የምትሆነው?”
ለምን ግማሽ ሐሙስ አይቀረውም! …ሲጀመር ልጅቱ ራሷ ምቀኛ ነው የምትልህ፡፡ ወር እንኳን ሳይሞላት፣ በሯን ስትከፍት አይገባህም እንዴ? አዲስ ነህ! እንዲህ ዓይነት ነገር ውስጥ ጣልቃ አትግባ! እነዚህ በተንኮል ጥርሳቸውን የነቀሉ ሽማግሌዎች አንዴ ከጠመዱህ፣ጥሩ አይደለም. ወዲህም ገባያዬን እንዳትዘጋው… ሄደው አንዲት ቃል ቢተነፍሱ ሐበሻ እዚህ ሱቅ ዝር አይልም” ዝም አልኩ፡፡
ፊደላዊት ደወለች! ደወለች… ደወለች ቤቢ…… ደወለች…" ጎበጥ ጎበጥ እያለ ወደ ውጭ ይወጣል ዶከተር፡፡ አይመለስም! ለሰዓታት ስልክ ላይ ነው! ቀናት ሄዱ፣ ወራት ተከተሉ፣ ሁለት፣ ሦስት፣ አራት ወር፡፡
ምናገባኝ ብዬ መከታተሌን ትቸ ከርሜ አንድ ቀን ሳላየው የቆየሁትን የፊደላዊትን አካውንት ተመለከትኩ፡፡ ጭር ብሏል፡፡ የለጠፈቻቸውን ፎቶዎች ሁሉ አንስታቸው ነበር፡፡ ምን መጣ ብዬ መመልከቴን ቀጠልኩ፡፡ ከረዥም ቀናት መዘናጋት በኋላ ስመለስ፣ ስታተሏ ሲንግል” ሆኗል። ደነገጥኩ! ፍቅረኛዋ በአደጋ ሞቶ መሆን አለበት አልኩ ለራሴ፡፡ ዝግመተ ለውጥ እንዲህም ፈጥኖ አያውቅ:: አዎ ዝግመተ ለውጥ፡፡ እንዲህ ነበር ዝንጀሮ መሰል ፍጥረት ቀስ በቀስ ወደ ሰው ተቀየረ ያሉን፡፡ መሆን አለበት:: ቀን ከተለጠው፣ ዝንጀሮም ሰው፣ ሰውም ዝንጀሮ መሆን ሳይችል አይቀርም: ሰው የአገርህ ልጆች በረሃ አቋርጠው ተሰደዱ ሲባል ከንፈር ይመጣል፡፡ እግርማ በረሃን አቋርጦ ካለፈ እሰዬው ነው፡፡ እንዲህ ልቦቻችን ውስጥ ያቆጠቆጠውን ሰውነት፣ ፍቅር፣ እውነት፣
ጨፍጭፈን ዘላለም የማንሻገረውን በረሃ ልባችን ውስጥ ከመፍጠር የባስ፣ ከንፈርየሚያስመጥጥ ምን ሰቆቃ አለ?
አንድ ምሽት ድንገት ዶክተር ደወለና “ወደ አገር ቤት የምትልከው ቀለል ያለ ነገር ካለ፣ ነገ ይዘህ ና፣ መሄዴ ነው አለኝ
“የት?”
አገሬ ነዋ! ጕዳይ አለኝ” አልጠየኩም፣ ጉዳዩ እንዲሁ ይገባኛል!
ቀናት ተቆጠሩ፡፡ ዶክተር ወደ ኢትዮጵያ ከሄደ ከሃያ ቀናት በኋላ የፊደላዊትን የፌስቡክ አካውንት” ተመለከትኩ፡፡
“ሰው ዝም ብሎ እግዚአብሔርን ተስፋ ቢያደርግ መልካም ነው ከሚል ጥቅስ ጋር ረዥም ቬሎ ለብሳ ፣ብቻዋን የተነሳችው የሚያምር ፎቶ ተለጥፏል። ቬሎዋን ሳይ ያንን ትኩስ ሰውነት በበረዶ ያጀሎት ዓይነት ሰውነቴ ቅዝቅዝ ሲል ተሰማኝ፡፡ እጅግ በጣም ብዙ የእንኳን ደስ አለሽ አስተያየት ጎርፎላታል።
እግዚአብሔር የቅኖች አምላክ ነው?”
“ይገባሻል የኔ ቆንጆ?”
“የእብርሃም የሣራ....በሳምንቱ ከቤተሰቦቿ ጋር በወርቃማ ጥልፍ ያበደ ጥቁር ካባ ለብሳ፣ በሹሩባዋ ሳይ ወርቃማ አከሊል ደፍታ፣ የማላውቃትን ንግሥተ ሳባ መስላ
(ለምን እንደሆን እንጃ እንደዚያ መሰለችኝ) የተነሳችውን የምላሽ ፎቶ ለጠፈች፡፡ በጣም
ውብ ልጅ ነት፡፡ ያንለታውኑ ከአሥር በላይ የሚሆኑ ተደጋጋሚ የሰርግ ፎቶዎቿን
ለጠፌች፡፡ መንፈስ ያገባች ይመስል አንዱም ላይ የባሏ ፎቶ የለም።
ፋሲል እየሳቀ እና የአንድ ሽማግሌ ፎቶ፣ ባል ብላ ለጥፋ ሐበሻ ለብር ነው ለቪዛ ነው እያለ፣ አዛ ያድርጋት እንዴ? ዋናው ማግባቷ ነው፣ በቃ!” አለቀ፡፡ ከሠርግ የመጀመሪያ ቀን ጀምሮ፣የእኔ ባሉት ነገር እየታፈረ እንዴት ይኖራል?… እያልኩ ፎቶዎቹን እመለከታለሁ፡፡
ዓይኔ አንዱ ፎቶዋ ላይ አረፈ፡፡ ዓይኖቿ እንባ ሞልተው፣ በሚያማምሩ ጣቶቿ አፏን
እፍና፣ እናትና አባቷ ፊት ለስንብት ቆማለች፡፡ ፋሲልን አሳየሁት፡፡“ወግ ነው ሲዳሩ ማልቀስ!” ብሎ እንደሚተርት እርግጠኛ ነበርኩ፡፡ ግን እንደዚያ አላለም፡፡ ቅሬታ ይሁን ሐዘን ባረበበት ፊት፣
“የእንባ ቀብድ! ብሎ ዝም አለ፡፡
የዶክተርን አካውት ተመለከትኩ፡፡ ጭር ባለው የፌስቡክ አካውንቱ ላይ፣ አንዲት ዐረፍተ ነገር በጎሉ እንግሊዝኛ ፊደላት ተለጥፋለች፡፡
love never gets old"
ፍቅር አያረጅምህ!
አንብበው ጨርሰዋል አሁን ደሞ ከዚሁ ሳይወጡ #UNMUTE አድርገው ይውጡ አመሰግናለው
✨ጨረስን✨
ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ
ለወዳጆ #Share እያደረጉ
👍4❤1
ሴቶች በጧት ሰፈራችን ወዳለው መድኃኒያለም ቤተክርስቲያን እንዲወስዷቸው አደረግን፤አንዳንዴ እንደዛ እናደርግ ነበር ቤተክርስቲያን እንወስዳቸውና እዛው ሲጸበሉና ጸሎት ሊያደርሱ ውለው ማታ እንመልሳቸዋለን፤ የዛን ቀንም እማማ እዛው ዋሉ እኛም ተባብረን የቤታቸውን ጣራ ከማደስ አልፎ ምን የመሰለ ነጭ የ ማዳበሪያ ኮርኒስ ሰራንላቸው፡፡ ቤቱን አጸዳድተን ደጅ ፀሐይ ላይ የዋለ አልጋቸውን አስገባብተን ካነጠፍን በኋላ የሰፈር ሴቶች ቡና አፍልተው በድምቀት እማማን ተቀበልናቸው፤ እማማ እቤት እንደገቡና አልጋቸው ላይ እንዳረፉ ወደጣራው ባለማመን እየተመለከቱ፣ ዓይኔ ነው… ወይስ ያችን ሽንቁር ደፍናችኋታል!?” ብለው ጠየቁ። አጠያየቃቸው
ከደስታም ይሁን ምስጋና ይልቅ ወደ ቅሬታ ያመዘነ ነበር፡፡የተደረገውን ሁሉ አንድ በአንድ ነገር ናቸው፡፡ ቀጥሞና ሲያዳምጡን ቆዩና ዓይናቸውን ነጩ ኮርኒስ ላይ ሲያንከራትቱ ቆይተው ፊታቸው ቅጭም እንዳለ፣ “ደህና!” አሉ: ከዚች ቃል ውጭ ምንም አልተናገሩም፤ በዛው እንቅልፍ ወሰዳቸው። መቼም ሰው የፈለገ ለነፍሱ ቢሰራ በጎ ስራው ምስጋና መሻቱ አይቀርምና በዚህ የእማማ ዝምታ ቅሬታ ተሰምቶኝ ነበር፡፡ጓደኞቸም እንደዛው፡፡
በቀጣዩ ቀን ጧት አንድ የሰፈራችን ልጅ ሲሮጥ እቤት መጣና እማማ እያለቀሱ የሰፈሩ
ሰው ሁሉ ተሰብስቦ እያባበላቸው ነው አለኝ፡፡
ምነው አመማቸው እንዴ?”
እንጃ! ለምን የጣራውን ሽንቁር ዴፈናችሁብኝ? ብለው ነው እሉ ደነገጥኩ::
ምን ? ከምርህ ነው?” አልኩት እየቀለደ መስሎኝ ነበር::
ከምሬ ነው! እንደዛ አሉ እየተባለ ነው።
ተየይዘን እማማ ቤት ስንደርስ የሰፈሩ ሰው ቤቱን ሞልቶ እማማ ይጮኻሉ፣
✨ነገ ያልቃል✨
#UNMUTE #UNMUTE # UNMUTE
አሁንም #UNMUTE👇 ሰምታችኋል።
ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ
ለወዳጆ #Share እያደረጉ
ከደስታም ይሁን ምስጋና ይልቅ ወደ ቅሬታ ያመዘነ ነበር፡፡የተደረገውን ሁሉ አንድ በአንድ ነገር ናቸው፡፡ ቀጥሞና ሲያዳምጡን ቆዩና ዓይናቸውን ነጩ ኮርኒስ ላይ ሲያንከራትቱ ቆይተው ፊታቸው ቅጭም እንዳለ፣ “ደህና!” አሉ: ከዚች ቃል ውጭ ምንም አልተናገሩም፤ በዛው እንቅልፍ ወሰዳቸው። መቼም ሰው የፈለገ ለነፍሱ ቢሰራ በጎ ስራው ምስጋና መሻቱ አይቀርምና በዚህ የእማማ ዝምታ ቅሬታ ተሰምቶኝ ነበር፡፡ጓደኞቸም እንደዛው፡፡
በቀጣዩ ቀን ጧት አንድ የሰፈራችን ልጅ ሲሮጥ እቤት መጣና እማማ እያለቀሱ የሰፈሩ
ሰው ሁሉ ተሰብስቦ እያባበላቸው ነው አለኝ፡፡
ምነው አመማቸው እንዴ?”
እንጃ! ለምን የጣራውን ሽንቁር ዴፈናችሁብኝ? ብለው ነው እሉ ደነገጥኩ::
ምን ? ከምርህ ነው?” አልኩት እየቀለደ መስሎኝ ነበር::
ከምሬ ነው! እንደዛ አሉ እየተባለ ነው።
ተየይዘን እማማ ቤት ስንደርስ የሰፈሩ ሰው ቤቱን ሞልቶ እማማ ይጮኻሉ፣
✨ነገ ያልቃል✨
#UNMUTE #UNMUTE # UNMUTE
አሁንም #UNMUTE👇 ሰምታችኋል።
ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ
ለወዳጆ #Share እያደረጉ
ተንተርሳ የደረቱን ጠጉር እያፍተለተለች በወጣትነት ትኩስ ገላው ውስጥ እንደ ቅቤ ለመቅለጥ... እንደ ውሃ ለመፍሰስ... በእጅጉ ጓጉታለች፡፡
ከምሽቱ ሁለት ሰዓት ሆነ፡፡ ጌትነት በዚያ ከጥጥና ሲባጎ በተሰራ ምቹ ሶፋ ወንበር ላይ በጀርባው ተለጥጦ እየተዝናና ጠላውን መኮምኮሙን ቀጥሏል። ሸዋዬ ሁኔታውን ስትመለከት ፈነጠዘች። ጠላዋ ስራውን በሚገባ በመስራት ሃላፊነቱን እየተወጣ መሆኑን አረጋገጠች። ሁሉም
ነገር በእቅዷ መሰረት እየተቀላጠፈ ነው። ሚስኪኑ ባጠመደችለት ወጥመድ ውስጥ ያለችግር ሰተት እያለ በመግባት ላይ መሆኑን እንዳወቀች ያንን ከተዳፈነበት ተቆስቁሶ እንደ ነበልባል ሲለበልባት የቆየ፣ ውስጥ ውስጡን ያሰቃያትን፣ ቀን ከለሊት እረፍት ያሳጣትን ችግሯን ለማስወገድ ቸኮላች፡፡ የወሲበ ክብሪቷን ጭራበት በዚያ እንደ ፈረሰኛ ውሃ ሽቅብ በሚጋልበው ዳሌዋ ላይ አፈናጣ እያስጋለበች በጭኖቿ መካከል አስገብታ ልቡ እስከሚጠፋ ድረስ ልታሸውና ትኩስ የወንድነት ወኔውን ጨምቃ ልታጣጥመው ተጣደፈች፡፡
“እጅህን ታጠብ ጌቱ?” ከፊት ለፊቱ ከሞላ ጎደል ዳንስ በሚመስል ሁኔታ እየተውረገረገች የእጅ ማስታጠቢያውን አስጠጋችለት። ድሮ ጌትነት ብላ ነበር የምትጠራው።ዛሬ ግን ከወዲሁ ስሜቱን ለመስረቅ ለየት ያለ ስሜት ልታሳድርበት ፈለገችና ጌቱ ብላ አቆላመጠችው። በዚያ ላይ ደግሞ አድርጋ የማታውቀውን እጁን ልታስታጥበው ተነሳች። ጌትነት ድንግር
ግር አለው፡፡ “እንዴ! ጋሼ ቶሎሳ ሳይመጣ እራት ልበላ?”በፈዘዙ ዐይኖቹ ሽቅብ እየተመለከታት ጠየቃትና ማስታጠቢያውን ከእጇ ሊቀበል ሞከረ።
“ውይ አልነገርኩህም ለካ! የነገርኩህ መስሎኝ፡፡ ስልክ ደወለልኝ እኮ! የጓደኛዬ ልጅ ሞታ ቀብር አለብኝ እያስተዛዘንኩት ነው ብሎ ደወለልኝ”
አምሽቶ ስልክ የደወለ አስመስላ ነገረችው። ጌትነት ቅር ቢለውም እጁን
ለመታጠብ የወንበሩን መደገፊያ ተመርኩዞ ብድግ ሊል ሞከረ።
“እስቲ ለዛሬ ክብሩ ይቅርብኝና ቁጭ ብለህ ታጠብ” ከመቀመጫው እንዳይነሳ በግራ ክርኗ ትከሻውን ወደ ታች ደገፍ አድርጋ አስታጠበችው። እጁን ካስታጠበች በኋላ እንጀራ የተጉዘጉዘበት ሰፊ ትሪ አመጣች። ያንን ሰፊ ትሪ ደግሞ በጥልፍ ባሸበረቀው ትልቁ ሌማት ላይ
ካስቀመጠች በኋላ ያንን በቅመምና በቅቤ ያበደ የዶሮ ወጥ ልታመጣ
ተመልሳ ወደ ጓዳ ገባች። ወጡን ይዛ ስትገባ ረሃብ የሽረሽረው ሆዱ በነጎድጓድ ድምጽ አፍ አውጥቶ ጩኽቱን አቀለጠው..!! የወጡ ሽታ መጣፈጥ
ለጉድ ነበር። ሽዋዬ ጊዜ አላጠፋችም። በፍጥነት ከዋንዛ እንጨት የተሰራውን ኩርሲ ሳብ አድርጋ ከጐኑ ልጥፍ ብላ ተቀመጠችና በአፍ በአፉ ትለቅበት ጀመር፡፡ የጉርሻዋ ክብደት አይጠየቅም፡፡ 'ፍቅርና ጉርሻ ሲያስጨንቅ ነው ባይዋ ሸዋዬ በላይ በላዩ እየጠቀለለች ባጎረሰችው ጉርሻ ሆዱ ተወጠረ። የእራት ሥነ ሥርዐት ጨዋታው በአንድ ቋሚ የጉርሻ ተቀባይና በአንድ ቋሚ አጉራሽ መካከል ሲካሄድ ከቆየ በኋላ“ወደ ማሳረጊያው ላይ ለኔስ አታጎርሰኝም እንዴ?” አለችው እንደማቀፍ እየቃጣት።
“ማጉረስ ስለማልችል እኮ ነው እትዬ ሸዋዬ?” ከመፍዘዛቸው ብዛት ያንቀላፉ የሚመስሉ ዐይኖቹን በግድ ከፍቶ ዐይን ዐይኖቿን ሽቅብ እየተመለከተ።
“ሂድ! ጉረኛ! ይሄኔ የምትወዳት ውሽማህ ብትሆን ኖሮ በጉልበትህ ተንበርክከህ አደግድገህ ነበር የምታጎርሳት” በመቀመጫዋ ጎሽም አደረገችው።
ጌትነት አፈረና አንገቱን አቀረቀረ።
“ምን አንገትህን ትደፋለህ?! አንገት ደፊ አገር አጥፊ አሉ?! እኔ እንደሆንኩ እሳት መሆንህን ያወቅኩት ገና እንዳየሁህ ነው። ነቃሁብ አይደል?” አሁንም በመቀመጫዋ ቡጢዋን ደገመችው። ጌትነት ግራ
ተጋባ፡፡ ያከብራትና ይፈራት የነበረችው ሸዋዬ መሆኗን ተጠራጠረ፡፡ ከሷ
እንደዚህ ያለውን አቀራረብና ቅብጠት ፈፅሞ ያልጠበቀው ነበር። ስሜቱ
በመጠኑ ተረበሽ፡ ወደ መጨረሻ ላይ በግድ ልታጐርሰው ስትታገለው “በቃኝ”ብሉ እጆቿን ይዞ ተማፀናት። ከሚገባው በላይ ሲሆን እህልም ዱላ
ነው። በቁንጣን እንዳይታመም ፈራ።
“ጌቱ ይህቺን ብቻ በሞቴ!!” ሄዳ አንገቱን እቅፍ አድርጋ በግድ አጎረሰችው። የመጨረሻው ጉርሻ እንኳን ሆን ብላ አንገቱን ለማቀፍ እንጂ እንደጠገበ ሳይገባት ቀርቶ አልነበረም፡፡ በአንድ ቋሚ አጉራሽና በአንድ ቋሚ ጎራሽ መካከል ሲካሄድ የቆየው ጨዋታ አብቅቶ ገበታው ሲነሳ ከምሽቱ ሶስት ሰዓት ሆኖ ነበር፡፡
አንድ ሰዓት ሙሉ የፈጀ የእራት ሥነ
ሥርአት... ከገበታው በኋላ ሸዋዬ ለራሷም ጠላ በዋንጫ ሞላችና ኩርሲውን የበለጠ አስጠግታ ልጥፍ አለችበት።......
✨ይቀጥላል✨
እባካችሁ #MUTE አድርጋችሁ የምትጠቀሙ #UNMUTE አድርጉ በየቀኑ የሚለቀቁትን መከታተል አትችሉም
በድርሰቶቹ ላይም ያለውን አስተያየታችሁን በመወያያ ግሩፑ @dertogadaa እና @atronosebot ላይ ማስፈር ትችላላችሁ
ከምሽቱ ሁለት ሰዓት ሆነ፡፡ ጌትነት በዚያ ከጥጥና ሲባጎ በተሰራ ምቹ ሶፋ ወንበር ላይ በጀርባው ተለጥጦ እየተዝናና ጠላውን መኮምኮሙን ቀጥሏል። ሸዋዬ ሁኔታውን ስትመለከት ፈነጠዘች። ጠላዋ ስራውን በሚገባ በመስራት ሃላፊነቱን እየተወጣ መሆኑን አረጋገጠች። ሁሉም
ነገር በእቅዷ መሰረት እየተቀላጠፈ ነው። ሚስኪኑ ባጠመደችለት ወጥመድ ውስጥ ያለችግር ሰተት እያለ በመግባት ላይ መሆኑን እንዳወቀች ያንን ከተዳፈነበት ተቆስቁሶ እንደ ነበልባል ሲለበልባት የቆየ፣ ውስጥ ውስጡን ያሰቃያትን፣ ቀን ከለሊት እረፍት ያሳጣትን ችግሯን ለማስወገድ ቸኮላች፡፡ የወሲበ ክብሪቷን ጭራበት በዚያ እንደ ፈረሰኛ ውሃ ሽቅብ በሚጋልበው ዳሌዋ ላይ አፈናጣ እያስጋለበች በጭኖቿ መካከል አስገብታ ልቡ እስከሚጠፋ ድረስ ልታሸውና ትኩስ የወንድነት ወኔውን ጨምቃ ልታጣጥመው ተጣደፈች፡፡
“እጅህን ታጠብ ጌቱ?” ከፊት ለፊቱ ከሞላ ጎደል ዳንስ በሚመስል ሁኔታ እየተውረገረገች የእጅ ማስታጠቢያውን አስጠጋችለት። ድሮ ጌትነት ብላ ነበር የምትጠራው።ዛሬ ግን ከወዲሁ ስሜቱን ለመስረቅ ለየት ያለ ስሜት ልታሳድርበት ፈለገችና ጌቱ ብላ አቆላመጠችው። በዚያ ላይ ደግሞ አድርጋ የማታውቀውን እጁን ልታስታጥበው ተነሳች። ጌትነት ድንግር
ግር አለው፡፡ “እንዴ! ጋሼ ቶሎሳ ሳይመጣ እራት ልበላ?”በፈዘዙ ዐይኖቹ ሽቅብ እየተመለከታት ጠየቃትና ማስታጠቢያውን ከእጇ ሊቀበል ሞከረ።
“ውይ አልነገርኩህም ለካ! የነገርኩህ መስሎኝ፡፡ ስልክ ደወለልኝ እኮ! የጓደኛዬ ልጅ ሞታ ቀብር አለብኝ እያስተዛዘንኩት ነው ብሎ ደወለልኝ”
አምሽቶ ስልክ የደወለ አስመስላ ነገረችው። ጌትነት ቅር ቢለውም እጁን
ለመታጠብ የወንበሩን መደገፊያ ተመርኩዞ ብድግ ሊል ሞከረ።
“እስቲ ለዛሬ ክብሩ ይቅርብኝና ቁጭ ብለህ ታጠብ” ከመቀመጫው እንዳይነሳ በግራ ክርኗ ትከሻውን ወደ ታች ደገፍ አድርጋ አስታጠበችው። እጁን ካስታጠበች በኋላ እንጀራ የተጉዘጉዘበት ሰፊ ትሪ አመጣች። ያንን ሰፊ ትሪ ደግሞ በጥልፍ ባሸበረቀው ትልቁ ሌማት ላይ
ካስቀመጠች በኋላ ያንን በቅመምና በቅቤ ያበደ የዶሮ ወጥ ልታመጣ
ተመልሳ ወደ ጓዳ ገባች። ወጡን ይዛ ስትገባ ረሃብ የሽረሽረው ሆዱ በነጎድጓድ ድምጽ አፍ አውጥቶ ጩኽቱን አቀለጠው..!! የወጡ ሽታ መጣፈጥ
ለጉድ ነበር። ሽዋዬ ጊዜ አላጠፋችም። በፍጥነት ከዋንዛ እንጨት የተሰራውን ኩርሲ ሳብ አድርጋ ከጐኑ ልጥፍ ብላ ተቀመጠችና በአፍ በአፉ ትለቅበት ጀመር፡፡ የጉርሻዋ ክብደት አይጠየቅም፡፡ 'ፍቅርና ጉርሻ ሲያስጨንቅ ነው ባይዋ ሸዋዬ በላይ በላዩ እየጠቀለለች ባጎረሰችው ጉርሻ ሆዱ ተወጠረ። የእራት ሥነ ሥርዐት ጨዋታው በአንድ ቋሚ የጉርሻ ተቀባይና በአንድ ቋሚ አጉራሽ መካከል ሲካሄድ ከቆየ በኋላ“ወደ ማሳረጊያው ላይ ለኔስ አታጎርሰኝም እንዴ?” አለችው እንደማቀፍ እየቃጣት።
“ማጉረስ ስለማልችል እኮ ነው እትዬ ሸዋዬ?” ከመፍዘዛቸው ብዛት ያንቀላፉ የሚመስሉ ዐይኖቹን በግድ ከፍቶ ዐይን ዐይኖቿን ሽቅብ እየተመለከተ።
“ሂድ! ጉረኛ! ይሄኔ የምትወዳት ውሽማህ ብትሆን ኖሮ በጉልበትህ ተንበርክከህ አደግድገህ ነበር የምታጎርሳት” በመቀመጫዋ ጎሽም አደረገችው።
ጌትነት አፈረና አንገቱን አቀረቀረ።
“ምን አንገትህን ትደፋለህ?! አንገት ደፊ አገር አጥፊ አሉ?! እኔ እንደሆንኩ እሳት መሆንህን ያወቅኩት ገና እንዳየሁህ ነው። ነቃሁብ አይደል?” አሁንም በመቀመጫዋ ቡጢዋን ደገመችው። ጌትነት ግራ
ተጋባ፡፡ ያከብራትና ይፈራት የነበረችው ሸዋዬ መሆኗን ተጠራጠረ፡፡ ከሷ
እንደዚህ ያለውን አቀራረብና ቅብጠት ፈፅሞ ያልጠበቀው ነበር። ስሜቱ
በመጠኑ ተረበሽ፡ ወደ መጨረሻ ላይ በግድ ልታጐርሰው ስትታገለው “በቃኝ”ብሉ እጆቿን ይዞ ተማፀናት። ከሚገባው በላይ ሲሆን እህልም ዱላ
ነው። በቁንጣን እንዳይታመም ፈራ።
“ጌቱ ይህቺን ብቻ በሞቴ!!” ሄዳ አንገቱን እቅፍ አድርጋ በግድ አጎረሰችው። የመጨረሻው ጉርሻ እንኳን ሆን ብላ አንገቱን ለማቀፍ እንጂ እንደጠገበ ሳይገባት ቀርቶ አልነበረም፡፡ በአንድ ቋሚ አጉራሽና በአንድ ቋሚ ጎራሽ መካከል ሲካሄድ የቆየው ጨዋታ አብቅቶ ገበታው ሲነሳ ከምሽቱ ሶስት ሰዓት ሆኖ ነበር፡፡
አንድ ሰዓት ሙሉ የፈጀ የእራት ሥነ
ሥርአት... ከገበታው በኋላ ሸዋዬ ለራሷም ጠላ በዋንጫ ሞላችና ኩርሲውን የበለጠ አስጠግታ ልጥፍ አለችበት።......
✨ይቀጥላል✨
እባካችሁ #MUTE አድርጋችሁ የምትጠቀሙ #UNMUTE አድርጉ በየቀኑ የሚለቀቁትን መከታተል አትችሉም
በድርሰቶቹ ላይም ያለውን አስተያየታችሁን በመወያያ ግሩፑ @dertogadaa እና @atronosebot ላይ ማስፈር ትችላላችሁ
👍1