አትሮኖስ
286K subscribers
118 photos
3 videos
41 files
567 links
╔╦╦╦═╦╗╔═╦═╦══╦═╗
║║║║╩╣╚╣═╣║║║║║╩╣
╚══╩═╩═╩═╩═╩╩╩
ግጥሞች አዳዲስና ቆየት ያሉ የታዋቂ ደራሲያን መፅሐፍቶችን በ PDF እንዲሁንም
ያልተነበቡ ድርሰቶችን ግጥሞችን ታሪኮችን ያገኙበታል።


Contact. @atronosebot
please dont touch the leave button.😔😳😳
Download Telegram
#ትኩሳት


#ክፍል_አንድ


#በስብሐት_ገብረ_እግዚአብሔር


ስብሃት ለትምህርት ወደ ፈረንሳይ በተላከበት ጊዜ ከጓደኞቹ ጋር በፓሪስ ያሳለፈውን ጊዜ የሚተርክ። በእውነተኛ ታሪክ ላይ ተመስርቶ የተጻፈ ከኢትዮጵያ ባህልና ስርአት ወጣ ያለ ልቦለድ ነው በርግጥ ከላይ ከላይ ለሚያነበው ከወሲብ ቀስቃሽ መፅሀፍነት ላይዘል ይችላል ነገር ግን በማስተዋል ብናነበው የብዙ ነገር ትኩሳቶች ያነሳልና ስናነብ በጥሞና ይሁን ያው ሁሉንም ይመቻል ተብሎ አይጠበቅምና ከዚህ ውጪ ወደ ላይ ብዙ ድርሰቶች አሉና ያላነበባችሁ ከሆነ እስከዚያው በነሱ አሳልፉ። አሁን ወደ #ትኩሳት እንሂድ።👇
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።

ከውብ ሰማይ በታች

ባህራም
ከሩቅ

ይሄ ሁሉ የሆነውና የተደረገው ኤክስ ውስጥ ነበር.....
ኤክስ (ኤክስ-አን-ፕሮቫንስ) በፈረንሳይ ደቡብ ከማርሴይ አጠገብ የምትገኝ ትንሽ የዩኒቨርሲቲ ከተማ ናት፡ ህዝቧ ግማሽ በግማሽ ተማሪ ነው
የኤክስ ሰማይ አብዛኛውን ጊዜ ብሩህ ሰማያዊ ነው፡ አንዳንድ
ጊዜ ውሀ አረንጓዴ ይሆናል፣ ወደ ማታ ላይ እንደ ልጃገረዶቹ
ጉንጭ ይቀላል።

የኤክስ አየር ጠባይ የተመሰገነ በመሆኑ፣ ሀብታም በሽተኞችና
ሽማግሌዎች በሐኪም ምክር ወደ ኤክስ መጥተው ይኖራሉ፡፡ ስለዚህ
«ኩር ሚራቦ» የተባለው የኤክስ ዋና ጎዳና ላይ ሽማግሌዎች፣
አሮጊቶችና ባለሻኛዎች
እግራቸው ረዣዥም ቀጫጭን የሆነ፣የተነፋ ደረታቸው ውስጥ አንገታቸው የተቀበረ ባለሻኛ ሰዎች በቀስተኛ እርምጃቸው ሲዘዋወሩ ይታዩበታል። ባቡር መንገድ ዳር የተደረደሩት አግድም ወምበሮች ላይ የአሮጊትና የሽማግሌ መአት ቁጭ ብሎ ሹራብ እየሰራ ወይም ጋዜጣ እያነበበ ፀሀይ ይሞቃል፡
ወይም ዝም ብሎ ባዶ ብርጭቆ መሳይ ፈዛዛ አይኑን አተኩሮ (ምን
ያይ ይሆን?) ከንፈሩን ያለማቋረጥ ያንቀሳቅሳል (ምን ይል ይሆን?)

በጣም ይቀፋሉ የፈረንጅ ሽማግሌዎችና አሮጊቶች። ጨምጻዳ ቆዳቸው የተሰነጣጠቀ ደረቅ ሰም ይመስላል። ቀጥቃጣዎች::ዝምተኞች። አገጫቸው ተገንጥሎ ወደታች የወደቀ፣ ከንፈራቸው
የተንጠለጠለ፣ ጥርሳቸው የፈራረሰ ሽማግሌዎች፡፡ ጥርሳቸው አልቆ አፋቸው ወደ ውስጥ የጎደጎደ ፂማም አሮጊቶች፡፡ የመኖር ጊዜያቸው
አልፎ፤ የሞት ጊዜያቸውን ዘመናዊ ህክምና ከልክሏቸው፤ ታችኛው
ከንፈራቸውን እንደ ጡጦ እየጠቡ ሞትን ሲጠብቁ ሚውሉ
የህይወት ኦናዎች። ዝምተኞች፡፡ ለአይን ብቻ ሳይሆን ላፍንጫም
ይቀፋሉ፡፡ የልዩ ልዩ መድሀኒት፣ የእርጅና፣ የሞት ሽታ
ሳይቀበር መግማት የጀመረ ስጋ

ደሞ መብዛታቸው ከተማሪው እኩል ሳይሆኑ ይቀራሉ? ማታ
መቸስ ፀህይዋ ሙቀቷን ይዛ ስትሄድ ወደየአልጋቸው ይከተታሉ።
ቀን ግን የትም ይገኛሉ፣ ኤክስን ይወሯታል። ኩር ሚራ ግዛታቸው ነው፡ ዩኒቨርሲቲው አጠገብ ያለው መናፈሻ ቤት መንግስታቸው ነው! ካፌዎቹ ቅኝ ሀገራቸው ናቸው። ቀን ሲኒማ የገባህ እንደሆነህ በጭለማው ሳይታወቅህ፣ ሳይተኛ ከሚያንኰራፉ ሽማግሌ፣ ወይም በየሶስት ሰከንዱ አክ!» ከምትል አሮጊት አጠገብ ትቀመጣለህ. . .

ደግነቱ ይሄ ታሪክ ስለአሮጊቶችና ስለሽማግሌዎች አይደለም።
ስለኛ ስለወጣቶቹ ነው፤ ስለባህራም፣ ስለኒኮል፣ ስለሲልቪ ስለሉልሰገድ፣ ስለሌሎችም ወጣቶች ....

ጥሩ ነው ወጣት መሆን። ገንዘብ ባይኖርህም ጤና ይኖርሀል፡ መልክ ባይኖርህም አንጎል
ይኖርሀል! እውቀት ባይኖርህም ጉራ ይኖርሀል፡ ፍቅር ባይኖርህም
ተስፋ ይኖርሀል፤ ደስታ ባይኖርህም ንዴት ይኖርሀል መጨቆን ቢበዛብህ ሪቮሉሽን ታነሳለህ. .. መኖር ቢያስጠላህ ወይም ቢያቅትህ ራስህን ትገድላለህ....ሰው ባያውቀውም ቅሉ ታሪክ ይኖርሀል፤ወጣት ነህና

የኤክስ የበጋ ሙቀት እየከበደኝ አላስራ ስለሚለኝ የከሰአት
በኋላውን ተኝቼ ውልና ሌሊት ስሰራ ለማደር 'ሞክራለሁ።
አንዳንድ ሌሊት ስራው እምቢ ሲለኝ፣ ከሆቴሌ ወጥቼ በእግሬ
እዘዋወራው ደስ ይለኛል በሌሊቱ ኤክስን መዞር፡፡ ትንሽ ከተማ
ስለሆነች ሰባት ሰአት ሲደርስ ሁሉ ነገር ተዘግቷል (ከካፌ «ሰንትራ»
እና ከላ ፓሌት ናይት ክለብ በቀር) በቀን ጠባቦቹን መንገዶች
የሚያስጨንቃቸው ህዝብ በሙሉ ተኝቷል፡ እነዚያ የሚያስፈሩኝ፣ መምጫቸው የማይታወቅ እብድ ፈረንሳይ ነጂዎች
በየአልጋቸው ተከተዋል! ኤክስ-አን-ፕሮቫንስ ሰላም ነው፡፡ ቤቶቹ ሁሉ ጨልመው፣ የመንገድ መብራት በርቶ፣ በፀጥታው የጫማዬን ድምፅ ብቻ እየሰማሁ ስራመድ፣ ባዶ ከተማ ውስጥ እንዳለሁ ሆኖ ይሰማኛል። አልፎ አልፎ በየአደባባዩ የሚገኙት ሰው ሰራሽ ምንጮች ወደ ኮከቦቹ በኩል እየዘለሉ ከሌሊቱ ጋር ይንሾካሾካሉ

አንድ ሌሊት ወደ ስምንት ሰአት ላይ አንዱን መንገድ ይዤ
ስራመድ ቆይቼ ወደ ግራ በኩል ስታጠፍ፣ ከፊቴ አራት የሚታገሉ
ፈረንጆች ድንገት ብቅ አሉ። ብቅ ያልኩትስ እኔ ነበርኩ፣ ግን እነሱ
ብቅ ያሉብኝ መሰለኝ፡፡ በበጋው ሙቀት ምክንያት አራቱም በሽሚዝ ናቸው፣ ይታገላሉ። በሌሊቱ ፀጥታ ጫማዎቻቸው ከአስፋልቱ ጋር ሲፋተጉና ትንፋሻቸው ሲቆራረጥ ይሰማል። ለጊዜው ማን ከማን ጋር
እንደሚታገል ለማወቅ አልቻልኩም። ዝም ብዬ ስመለከት፣ ሶስት ግዙፍ ሰዎች አንዱን ደቃቃ ብጤ ገጥመውት ኖሮ፣ ከጥቂት ትግል በኋላ ሁለቱ በቀኝና በግራ በኩል ያዙት። ሶስተኛው ከፊቱ ቆመ::
ሁሉም ቁና ቁና ይተነፍሳሉ፡፡ ደቃቃው ሰውዬ ይፍጨረጨራል፣
ግን ድምፅ አያሰማም፡፡ ለምን ኡ ኡ እንደማይል እንጃለት

ከፊት የቆመው ግዙፍ አንዴ በጥፊ መታውና፣ ዘወር ብሎ አጠገባቸው ካለው ግድግዳ ስር አንድ ትንሽ ነገር አንስቶ መጥቶ፣ በዚህ
በጨበጠው ነገር የትንሹን ሰውዬ ግምባር ፈተገው። ትንሹ ሰውዬ
ተፋበት። ግዙፉ በሹክሹክታ እየተሳደበ ወይም እየተራገመ ከሱሪ ኪሱ መሀረብ አውጥቶ ፊቱን ጠረገና ሲያበቃ፣ ደቃቃውን አንድ ቃሪያ ጥፊ አላሰው፡፡ ጥፊው ጧ ሲል ቀሰቀሰኝ፣ ገና አሁን ከመፍዘዜ ነቃሁ። ዘወር ስል፣ አጠገቤ ለመንገድ መጠገኛ ይሁን ለቤት ማስሪያ የተከመረ ኮረት አየሁ። በፍጥነት አንድ ሰባት ከባድ ጠጠር አነሳሁና
እያነጣጠርኩ ሰዎቹ ላይ መወርወር ጀመርኩ (ስወረውር የሀበሻ ነገር!» የሚል ሀሳብ በሀይል አሳቀኝ) ከት ከት ብዬ እየሳቅኩ የወረወርኩት ድንጋይ (ሶስተኛዋ) በጥፊ ተማቺውን ሰውዬ ደረቱን ደለቀችው፣ አራተኛዋ የአንዱን ትክሻ መታች። ድንጋዩና ሳቁ አስደንግጧቸው፣ ትንሹን ሰውዬ ለቀቁትና ተፈተለኩ፡፡ ለምራቂ ያህል እጄ ውስጥ የቀሩትን ድንጋዮች ወረወርኩባቸው። በድንጋዮቼ
ሸኚነት ጥቂት እንደሮጡ ወደ ቀኝ በኩል ታጠፉ፣ ጠፉ።

ሳቄም ድንገት ጠፋ። የፍርሀት ሳቅ ኖሯል። አጠገባችን ምንጭ
ሰማሁ። ገና አሁን ሰማሁት! ለካስ «ፕላስ ዴ ካትር ዶፈን» እተባለው
አደባባይ ውስጥ ነን

ትንሹ ሰውዬ ግራ ገብቶት መንገዱ ጋር ቆሞ አኔን ያየኛል
እጄን እያራከፍኩ ወደሱ ሄድኩ።
ይህን ያህልም ደቃቃ አደለም ከኔ ትንሽ ተለቅ ይላል። ደቃቃ የመሰለኝ ጠላቶቹ በጣም ግዙፍ ስለነበሩ መሆን አለበት።

«Bon soir» አልኩት (ቦን ሷር)
«Bon soir! አንተ ነህ እንዴ? ሀለላሲ ሙት!» አለኝ እየሳቀ

ባህራም ነው፡፡ ከዚህ በፊት ከሀበሾቹ ጋር ብዙ ጊዜ
አይቼዋለሁ። ግን ያን ጊዜ ያገሬን ልጆች በብዙ ስለማልጠጋቸው፣
ይህን ባህራም ተዋውቄው ወይም አናግሬው አላውቅም ነበር።

ድምፁ ወፍራም ሆኖ ለጆሮ ደስ ይላል ፈረንሳይኛው የፈረንሳዮቹ አይደለም፣ መልኩ ግን ትንሽ የደቡብ ፈረንሳዮችን ይመስላል። ፊቱ እንደ ፈረንጅ ነጭ ሳይሆን፡ ፀጉሩ በጣም ጥቁር ነው:: «ሀለሰላሴ ሙት!» ያለኝ ሀበሻ መሆኔን ስላወቀ ነው።
አብሯቸው የሚሄድ ሀበሾች ብዙ ጊዜ ሀይለስላሴ ይሙት!» ሲሉ
ሰምቷል
👍371
#ምንዱባን


#ክፍል_አንድ


#ትርጉም_ከዬሐንስ_ገፃዲቅ

ቀና ሰው

በ1815 መሴ ቻርለስ ብየንቬኑ መሪል የሞንቴስ ሱር ሞንቴስ ሀገረ ስብከት ጳጳስ ነበሩ፡፡ እድሜያቸው 75 ሲሆን የሞንቴስ ሱር ሞንቴስ ሀገረ ስብከት ጳጳስ ሁነው የተሾሙት በ1806 ዓ.ም ነበር፡፡ ጳጳሱ ወደ ሀገረ
ስብከታቸው ሲመጡ እህታቸው ወ/ት ባፕቲስታን አብረዋቸው ነበር
የመጡት:: እህትዬዋ ምንም እንኳን ትዳር ባይዙም እድሜ የጠገቡ ሲሆኑ ወንድማቸውን በአሥር ዓመት ይበልጧቸዋል፡፡

ከጳጳሱ ቤት ውስጥ ሌላም ሴት ነበሩ፡፡ እኝህ ሴት የወ/ት ባፕቲስታን እኩያ ናቸው:: ሴትዬዋ ወ/ሮ ማግልዋር ይባላሉ:: ሴትዮዋ ቀደም ሲል የሌላ ሰው አገልጋይ ሆነው ሠርተዋል፡፡ አሁን ደግሞ የወ/ት ባፕቲስታንና
የጳጳሱ ቤት ጠባቂ ሁነው ተቀጥረው ይሠራሉ፡፡

ጳጳሱ ከሀገረ ስብከታቸው እንደደረሱ በሀገሩ ደምብ መሠረት ከፊልድ ማርሻል ቀጥሎ ያለውን ሹመት ይሰጣቸዋል፡፡ የክፍለ ሀገሩ መሪና የማዘጋጃ ቤቱ ሹም ከቤታቸው ሄደው «እንኳን ደህና መጡ» በማለት እጅ ይነስዋቸዋል፡፡ አቡኑም በተራቸው ከዚያ ለተገኙ ከፍተኛ ባለሥልጣኖች ቡራኬ ይሰጣሉ፡፡ የከተማው ሕዝብ በአጠቃላይ አዲስ የተሾሙለትን ጳጳስ
ለማየት በጉጉት ሲጠባበቅ ነበር፡፡

የጳጳሱ ቤት ከአንድ ሆስፒታል አጠገብ ሲሆን ቤቱ እጅግ በጣም
ሰፊና ያማረ ነው:: ሆስፒታሉ ይገኝ የነበረው ከረባዳ ሥፍራ ላይ ሲሆን ግቢው እንደ ጳጳሱ ቤት አይሰፋም:: ጳጳሱ ወደዚያ ሲሄዱ በሦስተኛው ቀን ሆስፒታሉን ይጎበኛሉ:: ከጉብኝቱ በኋላ የሆስፒታሉ አስተዳዳሪ ከቤታቸው
ድረስ መጥቶ እንዲያነጋግራቸው ይጋብዙታል:: አስተዳዳሪው ከጳጳሱ ቤት ይሄዳል::

በሆስፒታሉ ውስጥ «ስንት በሽተኞች አሉ? » ሲሉ አስተዳዳሪው ጠየቁ::

«ሃያ ስድስት» ሲል መለሰላቸው::

«ልክ እኔ እንደቆጠርኳቸው ናቸው አልተሳሳትክም» አሉ ጳጳሱ::
ጳጳሱ የቤታቸውን አዳራሽ በዓያናቸው ቃኙ:: አመለካከታቸው
አዳራሹን በዓይነ ሕሊናቸው የሚለኩና የሚያከፋፍሉ ይመስሉ ነበር ።

«ይህ ክፍል ብቻ ሀያ አልጋ ይይዛል» አሉ እርስ በራሳቸው? ሲነጋገሩ።
ከዚያም ድምፃቸውን ከፍ አድርገው የሚቀጥለውን ተናገሩ::

«ወዳጄ የምለውን አጢነህ ስማኝ፡፡ እዚህ ቦታ አንድ ስህተት የተፈጸመ ይመስላል፡፡ እናንተ አምስት ወይም ስድስት ጠባብ ክፍሎች ናቸው ያሏችሁ::
ከዚያ ውስጥ ሃያ ስድስት ሰዎች ይተኛሉ፡፡ እኛ እዚህ ሦስት ሰዎች ብቻ ነን፡፡ ያለው ቦታ ግን ለስልሣ ሰው የሚበቃ ነው:: ታዲያ ይህ የአደላደል ስህተት አይመስልህም? የእኔን ቤት አንተ ብትወስድ ፤ የአንተን ደግሞ እኔ
ብወስድ ይሻላል፡፡›

በሚቀጥለው ቀን ሃያ ስድስቱ በሽተኞች ወደ ጳጳሱ ቤት ተዛወሩ፡፡
ጳጳሱም ሆስፒታሉን ተረከቡ:: ወሬው በከተማው ተነዛ፡፡ በጥቂት ቀናት ውስጥ የጳጳሱን በጎ ምግባር በመከተል ለበጎ ተግባር የሚውል እርዳታ ይጎርፍ ጀመር፡፡ በየቀኑ ከጳጳሱ ቤት በር የሚያንኳኳ ሰው ቁጥር እየበዛ
ሄደ፡፡ ሆኖም የሚመጣው ሰው ሁሉ እርዳታ ለማድረግ ብቻ ሳይሆን ምፅዋት ለመቀበልም ነበር፡፡ ዓመት ባልሞላ ጊዜ ውስጥ ጳጳሱ የብዙ ችግረኞች ቀላቢ፣ ምፅዋት ሰጪና ገንዘብ ሰብሳቢ ሆነ፡፡ ብዙ ገንዘብም ከጳጳሱ እጅ እየገባ ለድሃ ይሰጥ ጀመር:: የሚገኘው ገቢ ግን ልክ ከደረቀ
አፈር ላይ እንደሚፈስ ውሃ ገና ከመገኘቱ ወጪ ሆኖ በቶሎ ያልቃል፡፡ጳጳሱ ገንዘብ ቢያገኙም ከተገኘው ገቢ ጥቂቱን እንኳን ለራሳቸው ወደኋላ አላሉም፡፡ እንዲያውም ከነአካቴው የራሳቸውንም ይዞ ይሄድ ጀመር፡፡
ጳጳሳትን ከስማቸው አስቀድሞ ንጽህናቸውን ለማረጋገጥ ብፁዕ ወቅዱስ እያሉ መጥራት የተለመደ ቢሆንም በዚያ አካባቢ ይገኙ የነበሩት ነዳያን ፍቅራቸውንና ቅርበታቸውን ለመግለጽና የጳጳሱን ደግነት ለማውሳት ብፁዕ ወቅዱስ በማለት ፈንታ «አባ ደጉ» እያሉ ይጠርዋቸዋል፡፡

እኚህ ደግ ሰው በ1815 ዓ.ም ምንም እንኳን 75 ዓመት ቢሞላቸወም ከስልሣ ዓመት በላይ የሆናቸው አይመስሉም ነበር:: ቁመታቸው እጅግም ረጅም ሳይሆን መጠነኛ ሆኖ ሰውነታቸው ደልዳላ ነው:: ክብደታቸውን
ለመቆጣጠር በእግር መሄድ ያዘወትራሉ:: ሲራመዱ መሬት በኃይል እየረገጠ ከወገባቸው ትንሽ ጎበጥ ይላሉ::

የልጅ ፈገግታ በተጎናጸፈ አንደበት ሲናገሩ ከግርማ ሞገሳቸው ብዛት
የሰማቸው ሁሉ የመንፈስ እርካታን ያገኛል:: ከመላ ሰውነታቸው ደስታ
የሚንፀባረቅ ይመስላል፡፡ ደግነት የተቆራኘው አካላቸውና ወተት የመሰለው ጥርሳቸው ፈገግ ሲል እኚያ «ጨዋ ሰው ፤ እድሜ የተቸረ ሽማግሌ፤ ደግ ሰው» በማለት ለደጋግ ሰዎች የምንሰጠው ቅጻል ሁሉ በእኚህ ሰው ላይ ጎልቶ ይታያል፡፡ ለመጀመሪያ ጊዜ ላያቸው እንኳን ስለብቃታቸውና
ስለደግነታቸው አይጠራጠርም:: ነገር ግን አንድ ሰው ለጥቂት ሰዓት ከጳጳሱ ጋር ቢቆይና በአሳብ ባህር ተወጠው ቢያያቸወ ቀስ በቀስ
መለወጣቸውን ይገነዘባል፡: ግርማ ሞገሳቸው በቃላት ለመግለጽ በማይቻል ሁኔታ ያስፈራል፡፡ ሰፊውና ኮስታራው ፊታቸው እንዲሁም ሻሽ የመሰለው
ፀጉራቸው ክብር የተጎናጸፈ ለመሆነ በግልጽ ይታያል:: ግርማ ሞገስ ከውስጣቸው እየፈለቀ ሲወጣ የሚያልቅ ቢመስልም የእንዐባራቂነት ኃያል
እንዳለው አያጠራጥርም:: እንዲያውም አንድ ሰው ሁኔታቸውን በጥሞና ሲመለከት «አንድ መልአክ በፈገግታ አጊጦ ያየኛል» የሚል ስሜት
ያድርበታል፡፡ እኚህ ሰው የሚያሰላስሉት ስለ ክቡር ጉዳይ እንጂ ስለርካሽ ነገር ላለመሆኑ ጥርጣሬ አይገባውም::

ጸሎት ማድረስ፤ ምፅዋት መስጠት፧ የመንፈስ ስቃይ የደረሰበትን ማጸናናት፤ ወንድማማችነትን መስበክ፤ ራስን ለሌሎች መስዋዕት ማድረግ፤
በእምነት ራስን መግራት የጳጳሱ የእለት ተዕለት ኑሮ ሲሆን ይህም ኑር በበጎ አሳብ፤ በምርጥ ቃላትና በበጎ ተግባር የተሞላ ነበር፡፡

ክረምት ይሁን በጋ ሁለቱ ሴቶች ሲተኙ ብፁዕነታቸው ወደ ጓሮ
ሄደው አትክልት ውስጥ ለአንድ ወይም ለሁለት ሰዓት ፈጣሪያቸውን በማሰብ ከዚያ ካልቆዩ ኑሮአቸው የተሟላ አይመስላቸውም:: አሳባቸውን
ሰብስበውና የመንፈስ እርጋታን አግኝተው የምሽቱን ሰላምና ፀጥታ ከሰዎች የመንፈስ እርካታ ጋር እያነፃፀሩ የከዋክብትን ብዛት በመመልከት ከአትክልቱ
ውስጥ ይንሸራሸራሉ፡፡

በዚያች ሰዓት አበቦች ያለመስገበገብ የሚለግሱትን መልካም መዓዛ እየማጉ ጥቅጥቅ ካለ ጨለማ ውስጥ እንደበራ ሻማ ብቻቸውን በፍጥረታት
መካከል በደስታ የተዋበው ነፍሳቸውን ዘርግተው ይቆማሉ:: አእምሮአቸው ውስጥ ምን እንዳለ ራሳቸውን ቢጠይቁ መልሱን አያውቁትም:: ሆኖም ከሰውነታቸው ውስጥ አንድ ነገር ወጥቶ እንደሚሄድና አንድ ነገር ደግሞ ከሰውነታቸው ላይ እንደሚያርፍ ይሰማቸዋል ፤ አንድ ዓይነት ምሥጢር መከናወኑን ይገነዘባሉ::

እኚህ እድሜ የጠገበና ፈጣሪያቸውን የቀረበ ሰው የእረፍት ጊዜያቸውን የሚያጠፉት ቀን ቀን አትክልት በመኮትኮት ሲሆን ማታ ማታ ደግሞ ፈጣሪያቸውን በጸሎት በማመስገን ስለሆነ ሌላ የሚፈልጉት
ነገር አልነበረም:: ምድሩ በአበባ ፤ ሰማዩ ከከዋክብት በማጌጡ የመንፈስ እርካታ ይሰጣቸዋል::

ውድቀት

ጊዜው 1815 ዓ.ም ወሩ ጥቅምት ነው:: ፀሐይዋ ልትጠልቅ አንድ ሰዓት ያህል ሲቀራት አንድ በእግሩ የሚጓገዝ ሰው ወደ ሞንቴስ ሱር ሞንቴስ
👍47😁3👏2👎1🔥1
#ገረገራ


#ክፍል_አንድ


#በታደለ_አያሌው

“እኔ እምልሽ” አለች እናቴ፣ ሆድ ሆዴን እያየች።

“እመት እመዋ?” አልኋት፣ ዳር ዳርታዋ ያልገባኝ ይመስል።

“እምታዋዩኝ ጉዳይ የለሽም ወይ?”

"እ"

በቃ፣ አዉቃብኛለች። ለነገሩማ እንዲህ ሆዴን ገፍጥጬ እንዴት
አይታወቅብኝ? እመዋ አይደለች እንዴ ሴትዮዋ? ለመዋሸትም ለማመንም እያመነታሁ የምንተፍረቴን ሰረቅ አድርጌ ሳያት፣ አሁንም ዓይኗን ከሆዴ
ላይ አልነቀለችውም። በአዛኝቷ! ከቅድሙ ይልቅ አሁን ደግሞ እንዴት ነው ዓይኗ የደፈራረሰው? ጥርሶቿን ልትፈለቅቅ ብትሞክርም፣ እምቢ
እንዳላት ግን ታውቆኛል። እንዲሁ መግቢያ ስታሳጣኝ፣ ዝም ብዬ ወደ ኋላ ሸሽቼ ገረገራውን ተደገፍሁና፣ ኹለተኛ እንኳን የሌለውን የቤተ ክርስቲያኑን ጉልላት ደጋግሜ መቁጠር ጀመርሁ። እንደ ሁኔታዬማ
የተደገፍሁትን ሁሉ ገፍቼ አለመጣሌ አስደንቆኛል።

“ግድየለም ተዬው እሺ፤ ባሰኘሽ ጊዜ ራስሽ ትነግሪኝ አልነበር
እንዲያዉስ? ተዪው በቃ”

“አይ” አልሁ፣ እጄን በዓይኗ እና በሆዴ መካከል ማድረጉን እንደ ተሻለ አማራጭ እየሞከርሁት፡፡ “ጊዜ እየጠበቅሁ ነዉ እንጂ፣ መደበቁን ፈልጌው አልነበረም እኮ እመ። ልደብቀውስ ብል ከእንግዲህ እየገፋ እንጂ እየጠፋ አይኼድልኝ ነገር! መቼስ ጉዴ ፈልቶ የለም አንዴ?”

“እንግዲያው እማትነግሪኝ፤ ንገሪኛ”

“እረ እመዋ ስሞትልሽ”

አንጀቷን ሳልበላው አልቀረሁም። ዓይኖቿን ወደ ዓይኖቼ አምጥታ
በርኅራኄ ስታየኝ ቆየች። እንዲያዉም ለምን እንደሆነ ባይገባኝም፣ ሳቅ ሳቅ እያላት መጣ። ቆይታማ ጭራሽ ስቃ ልታስቀኝ ጭምር ምንም
አልቀራት። እንዲህ ስትሆን ደግሞ እንዲያዉም ከነጭራሹ ያዘነችብኝም አልመስልሽ እያለችኝ መጣች።

“ተንግዲህ አያት መሆኔም አይደል?”

ዝም አልኋት። አያት መሆን የምትጀምረዉ በእኔ ይመስል፣ እንደ ብርቅ ማየቷ አልተዋጠልኝም። እንኳንስ ታላላቆቼ፣ ታናናሾቼ ጭምር አያት
አድርገዋት የለም'ንዴ? ያልሰማሁ መስዬ፣ ዝም አልኋት።

“ሆድሽን አይቼ አንቀጽዋን ልገምት?”

አሁንም ዝም።

“ሴት ናት፤ አይደለችም?”
"ጭጭ"
“ስም ላውጣላት?”
እርጭ፡፡
“ቱናት" ብያታለሁ። ደስ ይል የለ? በቃ ሴት ብትሆንልኝስ፣ ቱናት ነው
እምላት እኔ”

ዓይናማ ድንጋይ እንደ መሰልሁ ቀረሁ፣ በፊቷ። የምለው ቸግሮኝ
እየተንተባተብሁ ሳለ፣ ቄስ ገበዙ ወዳለንበት ቀርበው ሰላምታ አቀረቡልንና ከጉድ አተረፉኝ፡፡ ደራሽ መልአክ መስለዉ ነዉ የታዩኝ። ጎንበስ ቀና እያሉ
በረዥሙ ጤንነታቸውን ከተጠያየቁ በኋላ፣ እመዋን አበመኔቱ እንደሚፈልጓት ነግረዋት ተመለሱ። ወዲያውኑ ፈቃድ እየጠየቀችኝ በሚመስል ሁኔታ፣ ለዐመል ያህል ወደኔ አይታ መልከኛዋን የሥዕል ቤት ኪዳነ ምሕረትን እና ባለ ሞገሱን የበዓታ ለማርያም ገዳም ሕንጻ
ወደሚከፍለው ሰፊ አደባባይ ገባች። እሷ ገና ትንሽ ፈቀቅ ከማለቷ፣ አጭር መልእክት ሲመጣልኝ የእጅ ስልኬ የሚያሰማውን ጺዉጺዉታ
አሰማኝ።

ወጣ አድርጌ ስመለከተዉ፣ ከባልቻ መሆኑን አወቅሁ።

ባልቻ፣ በአሁኑ ጊዜ የሲራክ ፯ ዋና ኃላፊ ሲሆን፣ የላከልኝ መልእክት
(አሁኑኑ እዚያዉ ይላል። በአስቸኳይ ስፈለግ የሚመጣልኝ እንዲህ ያለ መልእክት ነው። የምፈለገው ድንገተኛ ለሆነ አጭር ስብሰባ ወይም ለአንዳች ተልእኮ ወይም ለሌላ ለምንም ጉዳይ ሊሆን ይችላል። ምንም
ቢሆን ምን ግን፣ እንዲህ ያለ መልእክት በደረሰኝ በዐሥር ደቂቃዎች ውስጥ መድረስ ይኖርብኛል። በተለይም የተፈለግሁት እንደ አሁኑ በባልቻ
ከሆነ፣ እኔን የሚፈልግ እጅግ አስቸኳይ ጉዳይ ተፈጥሯል ማለት ነው።ስለዚህ፣ እመዋ አበመኔቱን አነጋግራ እስከምትመለስ ድረስ ለመጠበቅ ቀርቶ፣ በስመ አብ እንኳን የምልበት ጊዜ አይኖረኝም፡፡ ይልቁንስ
አሁኑኑ መሮጥ አለብኝ። ያለበለዚያማ የእመዋ ሰላምታ ብቻውን ጉዞ ፍትሐት ያስጨርሳል። በዚያ ላይ አበመኔቱ የፈለጓት እንዲሁ ለማነጋገር ብቻም ላይሆን እኮ ይችላል። አይበለውና እኔ እዚሁ ከአሁን አሁን መጣች
እያልሁ እሷን ስጠባበቅ፣ ምንጣፎችን እንድታጥብ ወይ ደግሞ የተግባር ቤት ሥራ ቢያዝዟትስ ምን ይዉጠኛል?

ኧረረረ! መሰናበት አለብኝ፡፡ አሁኑኑ።

“እመዋ” አልኋት፣ እንደ መሮጥ ብዬ ከኋላዋ ስደርስባት።
“ምነዉ ምሆንሽ?”
“በቃ ከሰሞኑ ብቅ እላለሁ”
“ምን ልትሆኝ ነው አሁን? ቆዬኝ ይልቅስ ደርሼ መጣሁ”
“አይ፤ ሥራ ቦታ ቶሎ ነይ ተባልሁኝና
“ኤድያ! ያንቺ ሥራ ደሞ። ወይ እንዲህ ነዉ አይሉት፣ ወይ ለእናት
የሚተርፍ ጊዜ አይሰጥ”
“ሰሞኑን እኮ እመጣለሁ”
“ጭራሽ?” አለች ቆጣ ብላ፣ ከቤት እንደ ወጣሁ ማደር ማብዛቴን ጭምር እንደ ከነከናት በሚያስታዉስ ሁኔታ።

“ያዉ የሥራ ነገር አይደል፣ ምን ላድርግ ብለሽኝ ነዉ?”

“እኮኮኮሽ! ብትሄጅስ እዉነት እሱን ሳትነግሪኝ ልትሄጅ ነወይ?”

“የቱን እመ?”

ሆዴ ላይ ዓይኗን ጣለች። ገባኝ፡

“ምን ላድርግ ብለሽኝ ነዉ እመ፤ ያዉ እንጀራ አይደል?”

“ይሁን እሺ። ባይሆን ቶሎ እቤት አትመጭም? ከሥራሽ መልስ?”
አለችኝ፣ በስስት እና በቅያሜ ትንሽ ካስተዋለችኝ በኋላ፡፡

“እሺ” አልኋት፣ ሳላቅማማ። እኔ እንዲያዉም አብሪያት ሆኜ
እየዳበሰችኝም ጭምር፤ ታሳሳኛለች። ለቅጽበት እንኳን የሚለየን ባይኖር ደስታዉን አልችለዉም።

“እሺ እመጣለሁ” አልኋት።

“ትመጫለሽ? በይ ደሞ እንደ ሠለስትናዉ እመጣለሁ ብለሽ ቅሪ አሉሽ።በይ ደህና ዋይ። መኪናሽን ይዘሽ የለ? ቀስ እያልሽ ንጂ ደሞ። ጥድፍ ጥድፍ ትይና ወዮልሽ!”
በዓይኔ ትንሽ ሸኝቻት ሰዓቴን ስመለከት፣ ሦስቱ ደቂቃ እዚሁ ወድሟል።
ቢሆንም የቀረኝ ሰባት ደቂቃ፣ በቂዬ እንደሆነ እያሰብሁ ወደ ግቢዉ መዉጫ በር ዘወር ስል እንደገና ጠራችኝ

"እመት እመዋ?”

“ይቺን ነገር...” ብላ፣ ወደ ጉንፏ እየዳበሰች ወደኔ መለስ ስትል፣ ወደ እሷ ተሽቀዳድሜ ሮጬ ተቀበልኋት። ነገርዮዋ በእራፊ ጨርቅ ስለተጠቀለለች ምን እንደሆነች ላውቃት አልቻልሁም፡፡ የእምነት አፈር ልትሆን እንደምትችል ግን ገምቻለሁ።

“ምን ላድርጋት እመዋ?”

“እቤት አድርሰሽልኝ እለፊማ”

እንደገና በስስት ተሰነባበትንና፣ ወደ ሥዕል ቤት ኪዳነ ምሕረት መለስ ብዬ ተሳለምሁ። ጨርሼ እየወጣሁ፣ ልክ በወንዶች መግቢያ በኩል ስደርስ፣ አንድ ሰዉ በትከሻዬ ትክክል ድንገት በኃይል አስነጠሰብኝ። ሰአሊ
ለነ! ከየት ነዉ እንዴ? ድምፁን ተከትዬ ቀና ብል፣ መትረየስ በበሩ
ትክክል ካነጣጠረ አንድ ወታደር ዓይን ጋር በዓይኔ ገጠምሁ። ክዉ ብዬ ነዉ የቀረሁ። ምንም እንኳን ቅጽረ ቤተ ክርስቲያኑ ከቤተ መንግሥቱ ግቢ ጋር አጥር ብቻ የሚከፍላቸዉ ቢሆንም፣ ጥበቃዉን ግን በዚህ ደረጃ
አልጠበቅሁትም። ቆይ ምንድነዉ የሚጠብቀዉ? ማን ላይ ነዉ እንዲህ ያነጣጠረዉ? ካልጠፋ ቦታ እስከ ታቦቱ መቀመጫ የመቅደስ ክፍል ድረስ
በሚያሳይ ቅርበት ላይ እንዲህ ያለ ማማ? በዚያም ላይ ያጠመደ ወታደር?ስንት ጊዜ እዚህ ስመላለስ፣ ያለ ዛሬ አስተዉየዉ አላዉቅም። የግንብ
አጥሩን ተከትዬ ዙሪያዉን ስመለከት፣ ተመሳሳይ ወታደሮች በተመሳሳይ አኳኋን ዓይናቸዉን የሰጎን ዓይን አስመስለዉ ቆመዉባቸዋል። በሁሉም
የቤተ መንግሥቱ ወሠንተኛ አብያተ ክርስቲያናት እንደዚሁ ነዉ። ልክ እንደ ኪዳነ ምሕረት ሁሉ ወደ ታዕካ ነገሥትም ወረድ ብዬ አየሁ፣ ወደ ግቢ ገብርኤልም አለፍ ብዬ አስተዋልሁ። በሪፐብሊኩ ጠባቂዎች
ተከቧል።
👍582🥰2👏2😁1😱1
#ሳቤላ


#ክፍል_አንድ


#ድርሰት_ሚሲስ_ሔንሪ_ውድ

ዊልያም ቪን በከተማ ውስጥ ከሚገኘው ቤቱ፡ በተለይም ከሚያምረው ሰፊ ቤተ መጻሕፍት ውስጥ በምቹ ወንበር ላይ ተቀምጧል "

አንደኛው እግሩን በወፍራሙ በታጠፈ ጨርቅ ግጥም አርጎ አስሮ ከአንድ
ለስላሳ ትራስ ላይ አሳርፎ ሕመሙን ያዳምጣል ። ገና ዐርባ ዘጠኝ ዓመቱን እንኳን ሳይደፍን ጸጉሩ ሽብቶ ሰፊው ግንባሩ ተጨማዶ ዱሮ ያምር የነበረው ፊቱ ምጥጥ ድርቅ ብሎ ያለ ዕድሜው አርጅቶ ሽማግሌ ሆኗል ።

ዊሊያም ቬን በፖለቲካ ሰውነቱ ወይም በጦር መሪነቱ ወይም በላቀ የሕዝብ አስተዳዳሪነቱ ወይም የሕግ መወሰኛ ምክር ቤት አባል እንደ መሆኑ መጠን
በኃይለኛ ተናጋሪነቱና በንቁ ተከራካሪነቱ፡ ሳይሆን በገንዘብ አባካኝነቱ፡በቁማርተኛነቱ በዕለት ደስታ ፈላጊነቱና በደንታ ቢስነቱ፡ በሁሉም ዘንድ የታወቀ ነበር ፡፡

በፊት ኻያ አምስት ዓመት እስኪሞላው ድረስ ዋዛ ፈዛዛ የማያውቅ የያዘውን ተግባር ከዳር ሳያደርስ የማይለቅ ትጉሕና ቁም ነገረኛ ነበር ። ሕግ ሲያጠና
በነበረበት ጊዜ ከትምህርት ቤቱ የሚጠበቅበትን ግዴታ በሚገባ ለመወጣት ሲል አምሽቶ እየተኛ ማልዶ እየተነሣ ተግቶ ማጥናትን የዘወትር ተግባሩ አደረገወዉ ፡፡ ትዕግሥት የሞላበት ጥረቱን የተመለከቱ፡ ጀማሪ የሕግ ተማሪዎች የሆኑ ጓደኞቹ « ዳኛው ቬን » የሚል የቅጽል ስም አወጡለት ። ወጣቱ፡ ዊልያም ቬን ልቡ ሰማይ ነበርና የደረጃ ዕድገቱና የታዋቂነት ምኞቱ ሊሳካለት የሚችለው ዝንባሌውንና ተሰጥዎውን በጥረቱ በማጠናከር መሆኑን ስለተገነዘበ ባልንጀሮቹ ወደ ዕለታዊ ደስታና ወደ ቦዘኔነት ሊመልሱት ያደረጉት ሙከራ ሁሉ ሳይዝላቸው ቀርቷል
ዊልያም ከመልካም ቤተሰብ የተወለደና በዚያን ጊዜ ሽማግሌ ለነበረው የማውንት
እስቨርን ኧርል ወራሽ ዘመድ ቢሆንም ለራሱ ግን ምንም የሌለው ድሀ ነበር ። የሽማግሌው ወራሽ ሆኖ በእግሩ እንዳይተካ እንኳን በዝምድናቸው ቅርበት መሠረት የቅድሚያ መብት የነበራቸው ሌሎች ሦስት ጤናቸው የተሟላ ዘመዶች ነበሩት ።ከሦስቱ ውስጥ ደግሞ በተለይ ሁለቱ፡ ገና ወጣቶች ስለነበሩ ውርሱን በሞት የመልቀቃቸው ተስፋ የመነመነ ነበር ። እሱም ቢሆን : ከነዚያ ሁሉ ዐልፍ ይደርሰኛል የሚል ተስፋ በሕልሙም ሆነ በውኑ መጥቶበት አያውቅም። ነገር ግን ሦስቱም ተከታትለው አለቁ ። አንዱን የሚጥል በሽታ ገደለው ። ሁለተኛዉ ወደ አፍሪካ እንደ ሔደ በንዳድ ሞተ። ሦስተኛዉ ባገሩ በኦክስፎርድ አካባቢ በጀልባ ሲጓዝ ተገልብጦ ሰጠመ። በዚህ ምክንያት፡ የሕግ ተማሪው ዊሊያም ቬን ሳያስበውና ሳያልመውን በድንገተኛ አጋጣሚ የማውንት እስቨርን ኧርልን ማዕረግና ሀብት ወረሰና ! የስልሳ ሺ ፓውንድ ያመት ገቢ ሕጋዊ ባለመብት ሆነ

በመጀመሪያ ሲያስበው ያን ያህል ገንዘብ በየዓመቱ ከገባለት እንዴት አንደ ሚጠቀምበት ጨንቆት ነበር ። ነገር ግን ገና ሳይጀምር ትንሹም ትልቁም የሱ አወዳሽና አሞጋሽ ሆኑ ። በዚያ ሁሉ አንፋሽ አከንፋሽ ብዛት ጭንቅላቱ፡ ያለመዞሩ ያስገርም ነበር ዊልያም በውርሱ ባገኘው ማዕረግና ሀብት ብቻ ሳይሆን ቀድሞውንም የሚያምር መልክና የሚስብ ጠባይ ስለ ነበረው፡ የደመቀና የተደነቀ ሰው ሆነ ።ነገር ግን ያን ምስኪን የሕግ ተማሪ ከትምህርት ቤቱ፡ ብቸኛ ክፍሎች ውስጥ ጠብቆ ይዞት የነበረው አስተዋይነት እርግፍ አድርጐ ከዳውና ሕይወቱን ቅጥ አምባር በሌለው ጥድፊያ ሲመራው የተመለከቱት አንዳንድ አስተዋዮች አንድ ቀን በግንባሩ ተደፍቶ እንደሚቀር ይናገሩ ነበር ። ቢሆንም በዓመት ከፍተኛ ገቢ ያለው ሰው
በቀላሉ ጨርሶ አይወድቅምና እነሆ በጎ ኗሪ መስሎ ከቤተ መጻሕፍቱ ተቀምጧልም የአእምሮ ሰላም የነሡትን ሕይወቱን በቋፍ ያንጠለጠሉትንና እንደማይነቀሉ ሆነው የተጣቡትን ችግሮች ግን አገር ስምቷቸዋል ። ካገር በበለጠም የቅርብ ወዳጆቹ ከነሱ ይልቅ ደግም ባለዕዳዎች ደህና አድርገው ዐውቀዋቸዋል ወደ ዕብደቱ የሚያጣድፈው ሥቃዩ ብቻ የግሉ ድርሻ ስለሆነ ከራሱ በቀር ማንም አላወቀለትም ሊያውቅለትም አይችልም ከብዙ ዓመት በፊት የነገሩን አጀማመር ተመልክቶ
አዝማሚያውን አስተውሎ: መጨረሻው ምን ሊሆን እንደሚችል ለማሰብ ትኩረት
ሰጥቶ ገንዘብ አወጣጡን በቅጡ ለማድረግ ቢሞክር ኖሮ ፡ ክብሩን ለማደስ ይቻላው ነበር ። እሱ ግን ብዙ ብጤዎቹ የዚህ ዐይነቱ ነገር ሲደርስባቸው እንደሚያደርጉት ያቺን እንድ ጊዜ ደርሳ ማጋለጧ የማይቀር ቀን ላልተወሰነ የጊዜ ገደብ ወደ ጐን በመተው በዕዳ ላይ ዕዳ መጨመሩን ቀጠለበት ። ቁርጠኝነቱ የውርደትና የውድቀት ሰዓት ግን ጉዞዋን አላቆመችም ። እየቀረበች መጣች ።

ዊልያም ቬን ከዚህ ምዕራፍ መግቢያ እንደ ተመለከትነው : ከቤተ መጻሕፍት
ተቀምጦ የሚተክዘው ከፊቱ ካለው ጠረጴዛ ላይ ምስቅልቅል ብሎ የተቆለለውን የብዙ ልዩ ልዩ ዕቃዎች ሰነድ እየተመለከተ ይሆናል ።

እንደዚያ ተቀምጦ ሲተክዝ የጋብቻው ሁኔታ ታወሰው “ ግሬትና ግሪን ከሚ
ባለው ቦታ የፈጸመው ጋብቻ ምንም እንኳን ሴትዮዋ የፍቅር አቻው ብትሆንም' አፈፃፀሙ ያልታሰበበትና ምንም ዐይነት ማመዛዘን ያልታከለበት ነበር ። ቢሆንም ሚስቲቱ ያሳያት ከነበረው ቸልታና ይፈጸመው ከነበረው ዕብደት በላይ ትወደው ነበር ። አንዲት ሴት ልጅ ወለደችለት ። ልጁ ዐሥራ ሦስት ዓመት እስኪሞላት ድረስ እናቷ በደንብ ካሳደገቻት በኋላ ሁለተኛ ልጅ ሳትወልድለት ሞትች ። ወንድ ልጅ ለመውለድ ቢታደል ኖሮ ዊልያም ሲመኘው ' ሲመኘው ሳያገኘው የቀረው ነገር ትዝ ሲለው ' እንደማቃሰት ብሎ በረጅሙ ተነፈሰ ከገባበት የችግር ማጥ የሚወጣበትን መንገድ አያጣለትም ነበር ። ልጁ አድጎ፡ ለአቅመ አዳም ሲደርስ ይህን ባባቱ ላይ የወደቀውን የኑሮ ጣጣ ለማስወገድ አብሮት ተሰልፎ....

« ጌቶች » አለ አንድ አሽከር ወደ ውስጥ ገብቶ የጌታውን ከንቱ ምኞት በማቋረጥ። « ከእርስዎ ጋር ለመገናኘት የሚፈልግ እንግዳ መጥቷል ። »

« ማነው እሱ ? » አለው ኮስተር ብሎ " አሽከሩ ከፊቱ ያኖረለትን የስም ካርድ
ልብ አላለውም ። ማንም ሰው ቢሆን እንደ ውጭ አገር አምባሳደር ለብሶና ትልቅ ሰው መስሎ ቢመጣም ሥነ ሥርዓት ሳይጠብቅ ሎርድ (የማዕረግ ስም) ዊልያም ቬን ዘንድ ሰተት ብሎ ይገባል ማለት ዘበት ነበር ። አሽከሮቹም ገንዘባቸው እንዲከፈላቸው ለመጠየቅ ከሚመላለሱት ብዙ ባለዕዳዎች ጋር የረጅም ጊዜ ልምድ ስለ ነበራቸው ትእዛዙን ተጠንቅቀው ነበር የሚያከብሩለት

« ካርዱ እኮ እሱውና ጌታዬ » ዌስት ሊን ያለው ሚስተር ካርላይል ነው "

« ሚስተር ካርላይል ? » እለ ዊልያኛ ቬን እግሩን ሲቆረጥመው እያቃሰት
« ምን ይፈልጋል ? እስኪ አስገባው ። » አሽከሩ እንደታዘዘው እንግዳውን አስገባው ሚስተር ካርላይል ግርማ ሞገስ ያለው የኻያ ሰባት ዓመት ሰው ነው። አጠር ካለ ሰው ጋር ሲነጋገር ራሱን ወደ ሰውየው ዘንበል የማድረግ ልማድ አለው ። የእጅ መንሣት ልማድ ቢባልም ስሕተት አይሆንም ። አባቱም እንደዚሁ ያደርግ ነበር ።ሰዎች ስለዚህ ነገር ሲያነሡበት እንደ መሣቅ ይልና ለራሱ ምንም እንደማይታወቀው ይናገር ነበር ። ሚስተር ካርላይል ፡ ፊቱ ገርጣ ብሎ ጥርት ያለ ጸጉሩ ጥቁር ሽፋሺፍቱ ግጥም ያለ ባጠቃላይ የዐይነ ግቡነቱንና ያስደሳችነቱን ያህል መልከ መልካም ነው ባይባልም፡ ወንዶችም ሴቶችም ሊያዩት የሚፈልጉት ፡ የሚያስከብርና የቅንነት መለኪያ የመሰለ ገጽታ አለው። የካርላይል አባት፡ ትልቁ ካርላይል ጠበቃ ነበርና ልጁም ባባቱ እግር ተተክቶ ጠበቃ ሆነ ። ነገር ግን እንደገጠር ሰው
👍382
#የጣሪያ_ስር_አበቦች


#ክፍል_አንድ


#ትርጉም_ሀኒም_ኤልያስ


ደሃና ሁን አባዬ

የእኛ ህይወት የተጀመረው ደስ በሚል አይነት ስለነበረ፣ በጣም ትንሽ ልጅ ሳለሁ ጀምሮ ህይወት ሁሉ እንደ አንድ ደስ የሚል ረጅም ብሩህ ቀን እንደሆነ አድርጌ አምን ነበር። የልጅነታችንን ጊዜ በተመለከተ በጣም ጥሩ
ጊዜ ነበር ከማለት በስተቀር ልለው የምችለው እምብዛም የሆነ ነገር የለም በኑሯችን ሀብታምም፣ ደሀም አልነበርንም፧ እኛ ያሉንን ነገሮች ሌሎች ካሏቸው ጋር ሳወዳድር፣ አስፈልጎን ያጣነውንም ሆነ በቅንጦት ያገኘነውን ነገር አላስታውስም:: በዚያ ላይ በመካከለኛ የኑሮ ደረጃ ላይ ያሉ ሰዎች በሚኖሩበት በእኛ አካባቢ ማንም ሰው ብዙም ሆነ ትንሽ አልነበረውም በሌላ አነጋገር፣ ተራና የተለየ ነገር ያልነበረን ልጆች ነበርን።

አባታችን በፔንሲልቫንያ፣ ግላድስተን ውስጥ በሚገኝ 12,602 ሰዎች ባሉበት
ግዙፍ የኮምፒውተር ማምረቻ ውስጥ የህዝብ ግንኙነት ሰራተኛ ሆኖ ይሰራ ነበር የአባታችን አለቃ አብዛኛውን ጊዜ ከእኛ ጋር እራት ይበላ ስለነበርና አባታችንን “ክሪስ በዚህ ማራኪ ባህርይህና በመልከ መልካም ፊትህ ማን አስተዋይ ሰው ሊቋቋምህ ይችላል?” እያለ ያደንቀው ስለነበር በአባታችን
ደስተኞች ነበርን።

በዚህ አባባሉ እኔም ከልቤ እስማማለሁ አባታችን እንከን የለሽ ነው: ዘንካታ ቁመና ያለው ሲሆን ከቁመቱ ጋርም ተመጣጣኝ ውፍረት ታድሏል። ፀጉሩ
ጥቅጥቅ ያለና ወርቃማ ነው፡ ሰማያዊ አይኖቹ ለመኖርና ለመደሰት ያለውን ትልቅ ፍቅር የሚያንፀባርቁ ናቸው። አፍንጫው ቀጥ ያለና ረጅምም አጭርም
ያልሆነ… ተመጥኖ የተሰጠው ነው። ቴኒስና ጎልፍ መጫወትና መዋኘት ይወዳል፡ ሁልጊዜ እኛን ከእናታችን ጋር ትቶን ለስራ ጉዳይ ከካሊፎርኒያ ወደ ፍሎሪዳ ወይም ወደ ሌላ ውጪ ሀገር ይሄድና በሳምንቱ መጨረሻ ላይ ይመለሳል ዘወትር አርብ ከሰዓት በኋላ ወደ ቤት መጥቶ በፊት ለፊቱ በር በመግባት ደስ የሚል ትልቅ ፈገግታውን ፈገግ ሲልልን ስናይ፣ ዝናብ ቢጥልም ሆነ በረዶ ቢዘንብ ለእኛ ግን ፀሀይ ይሆንልን ነበር ሻንጣውን ወለሉ ላይ ጣል አድርጎ ሰላምታ ይጀምራል። “የሚወደኝ መጥቶ ይሳመኝ::
ይለናል።

ልክ ይህንን ሲናገር እኔና ወንድሜ ከተደበቅንበት ወንበር ወይም ሶፋ ስር እየሮጥን ወጥተን እቅፉ ውስጥ እንወድቃለን፡ እሱም አጥብቆ ያቅፈንና ጉንጮቻችንን ጥብቅ አድርጎ በመሳም ያሞቀናል። አርብ ሁልጊዜ አባታችንን መልሶ ወደ እኛ ስለሚያመጣልን ከሁሉም ቀናት የበለጠ ምርጥ ቀናችን
ነበር፡

አባታችን በመጣ ቁጥር በኪሱ ውስጥ ይዞልን የሚመጣውን ትንንሽ ስጦታዎች ከሰጠን በኋላ ሻንጣው ውስጥ ያሉትን ትልልቆቹን ስጦታዎች ለመቀበል
ደግሞ እኛ ሰላምታችንን እስክንጨርስ ድረስ በትዕግስት የምትጠብቀውን እናታችንን ሰላም ብሎ እስኪጨርስ እንጠብቃለን
እኔና ክሪስቶፈር ኪሱ ውስጥ የያዛቸውን ትንንሽ ስጦታዎች ካገኘን በኋላ፣እናታችን የአባታችንን አይኖች እንዲያበሩ የሚያደርገውን የእንኳን ደህና
መጣህ ፈገግታዋን ተላብሳ ወደ እሱ በቀስታ ስትራመድ እንመለከታታለን፡

አባታችንም እጆቹን ዘርግቶ ያቅፋትና ቢያንስ ለዓመት ያህል ያላያት በሚመስል ሁኔታ ፍዝዝ ብሎ ቁልቁል በናፍቆት ይመለከታታል።

እናታችን ዘወትር አርብ ሽቶ ባለው የመታጠቢያ ዘይት በተቀላቀለበት ውሀ ገላዋን ስትታጠብ፣ ጸጉሯን ስትሰራና ጥፍሮቿን ስታሳምር ነው ግማሹን ቀን የምታሳልፈው። እኔም እስክትጨርስ ድረስ በመልበሻ ክፍሏ ውስጥ ቁጭ ብዬ በጉጉት እጠብቃለሁ። ራሷን ከቆንጆ ሴት እጅግ ውብና እውን ወደማትመስል ሴት ስትቀይር የምታደርገውን እያንዳንዷን ነገር በጉጉት አስተውላለሁ።

የሚገርመኝ ነገር አባታችን በተፈጥሮ አስደናቂ ውበት እንዳላትና ፊቷን ምንም እንደማትቀባባ ማሰቡ ነው።

እኛ ቤት ከመጠን በላይ የሚደመጥ ቃል ቢኖር ፍቅር የሚለው ቃል ነው።
“እኔ በጣም አፈቅርሻለሁ አንቺስ ታፈቅሪኛለሽ? ናፍቄሽ ነበር? ቤት
በመምጣቴ ደስ ብሎሻል? እዚህ የሌለሁ ጊዜ ስለእኔ ታስቢ ነበር? በየምሽቱ እየተገላበጥሽ አጠገብሽ ሆኜ እንዳቅፍሽ ተመኝተሸ ነበር? እንደዚያ ካልሆነ
ካሪን… የእውነት ብሞት ይሻለኛል።” ይላታል። እናታችን ለእንደዚህ አይነት ጥያቄዎች እንዴት በአይኖቿ በለስላሳ
ሹክሹክታዋና በመሳም መመለስ እንዳለባት በትክክል ታውቅ ነበር።

በአንድ ክረምት ላይ እኔና ክሪስቶፈር ከትምህርት ቤት ወደ ቤት ተመልሰን እየተቻኮልን በፊት ለፊቱ በር ገባን፡ እናታችን ሳሎን ውስጥ ከምድጃው ፊት ለፊት ተቀምጣ ለአሻንጉሊት የሚሆን ነጭ ሹራብ እየሰፋች ነበር።
ከአሻንጉሊቶቼ ለአንዷ የሚሆን የገና ስጦታ እንደሆነ አስቤ ደስ አለኝ በተቀመጠችበት ሆና “ወደዚህ ከመግባታችሁ በፊት ጫማችሁን በሩ ጋ አውልቁና አስቀምጡት!” አለችን፡

ቦት ጫማዎቻችንና ወፍራም ኮቶቻችንን እንዲሁም ኮፍያችንን አስቀምጠን በካልሲ ብቻ በመሆን ነጭ ምንጣፍ ወደተነጠፈበት ክፍል አመራን አብዛኛውን ጊዜ ነጭ ምንጣፍ በተነጠፈበት ክፍል በሚያማምሩት ሶፋዎችና
ወንበሮች ላይ እንደልባችን ለመሆን ስለማይፈቀድልን የተዋበው የእናታችን ክፍል ለእኛ ምርጫችን አይደለም የአባታችን ክፍል ግን ጠቆር ያለ ቀለም
ያለው በመሆኑና ምንም ነገር እናበላሻለን ብለን ስለማንሳቀቅ ጠንካራው ሶፋ ላይ እንደልባችን መላፋትና መታገል ስለምንችል ክፍሉን በጣም እንወደው
ነበር።

እግሯ ስር ተቀምጬ እንዲሞቀኝ እግሮቼን ወደ እሳቱ እየዘረጋሁ “እማዬ… ሳይክሎቻችንን እየነዳን ወደ ቤት ስንመጣ ዛፎቹ ሁሉ በበረዶ ተሸፍነው ሲታዩ እንዴት ደስ እንደሚሉ ብታይ። ደሞ እማዬ ውጪውን ብታይው ተረት ተረት ላይ ያለውን ቦታ ነው የሚመስለው: ግን ብርዱ አይቻልም ያም ሆኖ ደስ ይላል እኔ በበኩሌ መቼም ቢሆን በረዶ የማይጥልበት ደቡብ አካባቢ መኖር አልፈልግም” አልኳት።

ክሪስቶፈር ሁለት ዓመት ከአምስት ወር ስለሚበልጠኝና ሁልጊዜ ከእኔ የተሻለ ብልህ መሆኑን ማሳየት ስለሚፈልግ ስለ አየር ሁኔታውና በረዶው ስለፈጠረው
ውበት ምንም አልተናገረም ልክ እንደኔ የቀዘቀዘውን እግሩን በእሳት እያሞቀ በጭንቀት ተኮሳትሮ የእናታችንን ፊት አፍጥጦ እየተመለከተ ነበር እንደዚያ አይነት ጭንቀት እንዲሰማው ያደረገው ምን አይቶ እንደሆነ ለማወቅ ፈልጌ እኔም ቀና ብዬ አየኋት᎓

“እማዬ ደህና ነሽ?” ሲል ጠየቃት።

ስስና ደስ የሚል ፈገግታ እያሳየችው “አዎ በጣም ደህና ነኝ” ብላ መለሰችለት።

“የደከመሽ ትመስይኛለሽ” አላት።

የምትሰራውን ትንሽ ሹራብ ወደጎን አስቀመጠችና የክሪስቶፈርን ፅጌረዳ
የሚመስሉ ቀዝቃዛ ጉንጮች ለመዳበስ ወደፊት ዘንበል ብላ “ዛሬ ሀኪም ቤት
ሄጄ ነበር” አለች:

“አሞሻል እንዴ እማዬ?” ሲል በድንጋጤ ጮኸ፡

በስሱ ሳቅ አለችና ጥቅጥቅ ያለውን ወርቃማ ጸጉሩን ቀጫጭንና ረጃጅም
በሆኑ ጣቶቿ እያሻሸች “ክሪስቶፈር ዶላንጋንገር፣ የሆነ ነገር ጠርጥረህ
እያሰብክ ነው አይደል? መቼም ምን ሆኜ እንደሆነ ሳትገምት አትቀርም አለችው ከዚያ እጁን ያዘችና የእኔንም አንዱን እጄን ጎትታ ሁለቱንም ሆዷ ላይ አስቀመጠቻቸው

ሚስጥራዊና ደስ የሚል አስተያየት ፊቷ ላይ እየተነበበ “የሆነ ነገር
አልተሰማችሁም?” ስትል ጠየቀችን፡
ክሪስቶፈር በፍጥነት እጁን መነጨቃት እኔ ግን ምን እንደሆነ በመጠበቅ
እጄን እዚያው ላይ ተውኩት።

“ምን ተሰማሽ ካቲ?”
👍62🥰21
#ጠላፊዎቹ


#ክፍል_አንድ


#በኬንፎሌት


#ትርጉም_በወንዳየሁ_ንጉሴ


ጦርነቱ የፈነዳው በአንዱ ፀሐያማ እሁድ ቀን ነበር፡
አይሮፕላኑ እስካሁን ከተሰሩት ሁሉ የተለየ ነው፡፡ ጦርነቱ የታወጀ ቀን ስድስት ሰዓት ከሰላሳ ላይ አይሮፕላኑ ብቅ ይል ይሆን እያለ ቶም ሉተር ልቡ ተሰቅሎ ወደ ሰማይ አንጋጦ እየጠበቀ ነው።

ቶም ወሬ ለማየት ባሰፈሰፉ ሰዎች ተከቧል፡ የፓን አሜሪካን ኩባንያ ንብረት የሆነው ባህር ላይ ማረፍና መነሳት የሚችለው አይሮፕላን ሳውዝ ሃምፕተን ወደብ ላይ ሲያርፍ ይህ ዘጠነኛው ጊዜ ቢሆንም አሁንም ማራኪነቱ አልደበዘዘም፡፡ ይህ አይሮፕላን አስደናቂ በመሆኑ አገሪቱ ጦርነት
ባወጀችበት ቀን እንኳን ሰዎች እሱን ለማየት ወደሚያርፍበት ቦታ
እየተንጋጉ ነው፡፡ በዚሁ ወደብ ዳርቻ አንዳች የሚያካክሉ ሁለት መርከቦች መልህቃቸውን ጥለው ቢቆሙም እነሱን ነገሬ ያለ የለም፡፡

ታዲያ አይሮፕላኑን እየጠበቁም ቢሆን ሰዎች የሚያወሩት ስለጦርነቱ
ነው ወንዶቹ ስለታንክና መድፎች ሲያወሩ ሴቶቹ በአርምሞ ይመለከታሉ፤
ከፍቷቸዋል። ሉተር አሜሪካዊ እንደመሆኑ ፍላጎቱ ሀገሩ በጦርነቱ እጇን እንዳታስገባ ነው፡፡ ጦርነቱ የእሷ ጉዳይ አይደለም፡፡ ከዚህም በላይ ናዚዎች በኮሚኒስቶች መጨከናቸው ተገቢ ነው፡፡

ሉተር በንግድ ሥራ የሚተዳደር ሲሆን የልብስ ስፌት ፋብሪው ውስጥ የሚሰሩት ኮሚኒስቶች አንድ ወቅት ላይ ችግር ፈጥረውበት ሊያጠፉት ሁሉ ምንም አልቀራቸውም ነበር፡፡ ትዝ ሲለው በንዴት
ይንቀጠቀጣል፡፡ የአባቱ የልብስ መሸጫ መደብር በይሁዳውያን ተቀናቃኞች
አፈር ድሜ ሊበላ ነበር፡፡ ሉተር ሬይ ፓትሪያርካን በጡት አባትነት ሲይዝ
ግን ህይወቱ ባንድ ጊዜ ተለወጠ የፓትሪያርካ ሰዎች እዚህም እዚያም
አደጋ በመፍጠር ኮሚኒስቶችን ልክ ማስገባት ያውቃሉ አንዱ ከውካዋ
ኮሚኒስት እጁ በማዳወሪያ ማሽን ውስጥ ተወትፎ እንዲቀር ተደረገ፡፡ የሰራተኛ ማህበር ቀስቃሽ አባል በመኪና ተገጭቶ ህይወቱ አለፈ፡ በፋብሪካ ውስጥ ስላለው የደህንነት ደምብ መጣስ ቅሬታ ያቀረቡ ሁለት ሰዎች ቡና ቤት ውስጥ በተፈጠረ ጠብ ቆስለው የአልጋ ቁራኛ ሆኑ፡ አንዷ ችግር ፈጣሪ ቤቷ በእሳት እንዲጋይ በመደረጉ በኩባንያው ላይ ያቀረበችውን ክስ ለማንሳት
ተገደደች፡፡ ከዚህ በኋላ ሰላም ሰፈነ፡፡ ፓትሪያርካ ሂትለር የሚያውቀውን
ያውቃል፡፡ ኮሚኒስቶችን ልክ ለማስገባት እንደ በረሮ መንጋ መደምሰስ ነው::

ሉተር ይህን እያሰላሰለ እግሩን ወለሉ ላይ ይጠበጥባል፡፡ አንዲት ጀልባ
አይሮፕላኑ የሚያርፍበት የባህር ክፍል አካባቢ ለማረፍ ችግር የሚፈጥርበት
አንዳች የተንሳፈፈ ነገር እንዳለ ለማየት ወደ ቦታው በረረች፡፡ የተሰበሰበው
ሰው ይህን ሲያይ በጉጉት አጉተመተመ አይሮፕላኑ እየመጣ ነው ማለት
ነው፡፡

አይሮፕላኑን ቀድሞ ያየው አንድ ትንሽ ልጅ ነው፡፡ አጉልቶ የሚያሳይ
መነጽር ባይዝም ‹‹ያውላችሁ!›› ሲል ጮኸ፡፡ ‹‹ባህር ላይ የሚያርፈው
አይሮፕላን መጣ!›› በማለት ወደ ምዕራብ አቅጣጫ ሲያመለክት ሁሉም
ዓይኑን ወደዚያው ወረወረ፡፡ ሉተር በመጀመሪያ አሞራ የመሰለ ነገር ደብዘዝ
ብሎ ታየው፡፡ በኋላ እየጎላ መጣ ‹‹ልጁ እውነቱን ነው! እውነቱን ነው!››በማለት የተሰበሰበው ህዝብ አውካካ፡፡

ፓን አሜሪካን አየር መንገድ ሰዎችን በምቾት አሳፍሮ አትላንቲክ ውቅያኖስን ማቋረጥ የሚችል ቦይንግ B 134 የተሰኘ አይሮፕላን በቦይንግ ኩባንያ አሰርቷል፤ ግዙፍ፣ ማራኪና ጉልበቱ ከፍተኛ የሆነ የአየር ላይ ቤተ መንግስት፡፡ አየር መንገዱ ስድስት አይሮፕላኖችን ያስመጣ ሲሆን ሌሎች ስድስት ደግሞ እንዲሰሩለት አዟል። በምቾትና በማራኪነት በወደቡ ላይ ከቆሙት የመንገደኛ መርከቦቹ አይተናነሱም፡፡ ነገር ግን መርከቦቹ አትላንቲክን ለማቋረጥ አራት ወይም አምስት ቀን ሲወስድባቸው ይህ ባህር ላይ ማረፍና ከባህር ላይ መነሳት የሚችል አይሮፕላን ግን ይህን ጉዞ በሃያ አራት ወይም በሰላሳ ሰዓት ያጠናቅቀዋል፡፡

ልክ ክንፍ ያለው ዓሳ ነባሪ ይመስላል› አለ ሉተር በሆዱ አይሮፕላኑ እየቀረበ ሲመጣ፡፡ ከወደ ፊቱ ሾል ያለ ግዙፍ ነው፡፡ ክንፎቹ ውስጥ ኃይለኛ
ሞተሮች ተሰክተዋል፡ አይሮፕላኑ ውሃ ላይ ሲያርፍ ሚዛኑን እንዲጠብቅ
የሚያስችሉት ከክንፎቹ በታች አጠር ወፈር ያሉ ትናንሽ ክንፎች
ተገጥመውለታል፡፡ የአይሮፕላኑ የታችኛው ክፍል እንደ ፈጣን ጀልባ
ውሃውን መሰንጠቅ እንዲያስችለው ጫፉ እንደ ቢላ የሰላ ነው፡፡

አይሮፕላኑ ፎቅና ምድር አለው፡ ሉተር ባለፈው ሳምንት ስለመጣበት
የአይሮፕላኑን ውስጣዊና ውጫዊ ገጽታ በሚገባ ያውቀዋል፡ የላይኛው ፎቅ
ፓይለቶቹንና የዕቃ ማስቀመጫ ክፍሎችን የያዘ ሲሆን የታችኛው ክፍል
ተሳፋሪዎች የሚቀመጡበት ነው፡፡ ተሳፋሪዎች የሚቀመጡባቸው ክፍሎች
በመደዳ በተደረደሩ የእንግዳ ማረፊያ ሶፋዎች የተሞሉ ናቸው፡፡ በመብል ጊዜ እነዚህ ክፍሎች ወደ መብል ቤትነት የሚለወጡ ሲሆን በመኝታ ጊዜ ደግሞ
ሶፋዎቹ እንደ አልጋ ይዘረጋሉ፡

ተሳፋሪዎቹን ከሙቀትና ከብርድ ለመጠበቅ አይሮፕላኑ ውስጡ
ተለብጧል፡ ወለሉ ወፋፍራም ምንጣፍ የተነጠፈበት ሲሆን ክፍሉ ዓይን የማይወጉ መብራቶች ተገጥመውለታል፡፡ በሃር ጨርቅ የተሸፈኑ ሶፋዎቹ
ድሎታቸው ልክ የለውም፡ የአይሮፕላኑ ግድግዳ ላይ የተገጠመው ድምጽ
ማፈኛ የሞተሮቹን ድምጽ ይውጣል፡ የአይሮፕላኑ ካፒቴን የአዛዥነት ባህሪ
የተላበሰ ሲሆን ባልደረቦቹ ደግሞ ጸዳ ያለና ማራኪ የፓን አሜሪካን አየር
መንገድ ዩኒፎርም ለብሰዋል፡፡ አስተናጋጆቹ የተሳፋሪዎቹን ፍላጎት ለማርካት ተፍ ተፍ ይላሉ፡ ምግብና መጠጥ ያለማቋረጥ ይጋዛል፡፡ ተሳፋሪዎች የጠየቁት ነገር በሙሉ ልክ በአስማት የሚመጣ እንደሆነ ሁሉ እፊታቸው ዱብ ይላል፡ እንዲህ አይነት ድሎት በቀላል ዋጋ አይገኝም፡ ተሳፋሪዎቹ አብዛኛውን ጊዜ የንጉሣውያን ቤተሰቦች፣ የፊልም ተዋናዮች፣ የትላልቅ ኮርፖሬሽኖች ኃላፊዎች እና የአገር መሪዎች ናቸው፡፡ ቶም ሉተር ከእንደነዚህ አይነት ሰዎች ጋር የሚመደብ አይደለም፡ ሀብታም ቢሆንም እዚህ ደረጃ ለመድረስ ብዙ የለፋ በመሆኑ ለድሎት ሲል ብቻ ገንዘቡን አይረጭም: ቢሆንም ራሱን ከአይሮፕላኑ ጋራ ለማለማመድ ፈልጓል፡፡
አንድ ኃያል ሰው በጣም ኃያል የሆነ አንድ አደገኛ ተግባር እንዲፈጽምለት
ውለታ ጠይቆታል፤ ለዚህ ስራው ሉተር የሚከፈለው ነገር የለም፡ ነገር ግን
ለዚህ ሰው ውለታ መዋል ከገንዘብ ይልቃል፡

ይሄ ዕቅድ ምናልባት ይሰረዝ ይሆናል፡ ሉተር ‹‹ስራውን ቀጥል››
የሚለውን የመጨረሻውን ትዕዛዝ እየጠበቀ ነው፡፡ ይህም ሆኖ ግን አዕምሮው
ዕቅዱን ቶሎ ለመፈጸም በመጓጓትና ምነው ባልሰራሁት! ብሎ በመመኘት መካከል ይዋልልበታል፡

አይሮፕላኑ ከአፍንጫው ከፍ ከጭራው ዝቅ እያለ ወደ መሬት እየወረደ
ነው፡፡ አሁን ለማረፍ ተቃርቧል፡ ሉተር በአይሮፕላኑ እንደአዲስ ተደንቋል፡፡

ለአፍታ ያህል አይሮፕላኑ እየተንሳፈፈ ይሆን እየወደቀ ሳይለይ አንዳንዴ ደግሞ ወደ ላይ ከፍ እያለ በመጨረሻም ባህር ላይ እንደተወረወረ ዝይ እዚህም እዚያም እየነጠረና ውሃውን ሁለት ቦታ እየከፈለ ፍጥነቱን በመቀነስ ውሃው ላይ አረፈና እንደ ጀልባ ይሄድ ጀመር፡

ሉተር ትንፋሹን ውጦ ቆይቶ ስለነበር በእፎይታ ለቀቀው፡ አይሮፕላኑ ወደ መቆሚያው ተጠግቶ ቆመ፡ ሉተር ከሳምንት በፊት እዚህ ቦታ ላይ ነው ከአይሮፕላኑ የወረደው:፡ ከአፍታ በኋላ አይሮፕላኑ ከፊትና ከኋላ
በገመድ ከወደቡ ምሰሶ ጋር ይታሰራል፡
👍593👎1🔥1
#ከቡስካ_በስተጀርባ
#ድንግል_ውበት


#ክፍል_አንድ


#በፍቅረማርቆስ_ደስታ


ባኞ ቤቱ ውስጥ ጠብ ጠብ ከሚለው የውኃ ድምፅ በተጨማሪ ላይ ላይ የምትተነፍስ ሴት ድምፅ ይሰማል" የመታጠቢያ ገንዳው ውኃ እስከ ወገቡ የደረሰ ሲሆን ካርለት ውኃው ውስጥ ጋደም ብላ
ቀኝ እግሯን ገንዳው ከንፈር ላይ በማስቀመጥ ከግርጌዋ ያለውን የውኃ ማሞቂያ በተመስጦ ትመለከታለች" ከውኃ ገንዳው በስተቀኝ የእጅ መታጠቢያው ከፍ ብሎ ደግሞ በክፍሉ ሙቀት ሳቢያ የሚያዠው መስተዋት አለ የመታጠቢያ ክፍሉ ጠበብ ያለ ቢሆንም ንጹሕና ዘመናዊ ነው ከመግቢያው በር በስተግራ ካለው የቆሻሻ ልብስ ማጠራቀሚያ ቅርጫት ካኔተራ፣ ሱሪና ጃኬት ተቀምጧል። ከሱ በላይ ሰፋና ረዘም ያለ በነጭና ሐምራዊ ቀለም የተዥጎረጎረ ፎጣ
ተንጠልጥሏል።

ካርለት የገንዳውን ውኃ ቀይራ ሰውነቷን በንጹሕ ውኃ ከተለቃለቀች በኋላ ከገንዳው ውስጥ ወጥታ በጥቁርና ነጭ ቀለም
የአጥር ሥዕል ከተሣለበት ጸጕራማ ምንጣፍ ላይ ቆመች" እርጥቡ ጸጕሯ ትከሻዋና ደረቷ ላይ ተለጥፏል" ከጸጕሯ ወደ ግንባሯ እየተንኳለለ የሚወርደው ውኃ በቅንድቧ ሥር እየሰረገ ተለቅና
ሰርጐድ ያለውን ዓይኗን ያራጥባል” በደረትና ትከሻዋ አካባቢ ቁጥር ቁጥር ያለ የውኃ እንክብል ከመታየቱም ባሻገር ከሴት ብልቷ ላይ ካለው ስስ ጸጕር ላይ ደግሞ በውርጭ ሰሞን ሳር ላይ የሚታየውን የመሰለ ትንንሽ የውኃ ነጠብጣብ ይታያል"

ካርለት ወደ መስተዋቱ ቀረብ እንዳለች ገፅታዋ ከሚያዠው መስተዋት ውስጥ ተከፋፍሎ ታያት። መስተዋቱን ተወት አድርጋ
በእጆቿ ጡቶቿን ጨበጥ ጨበጥ አደረገቻቸው" ቀኝ እጇ ቀኝ ጡቷ ላይ ሲቀር ግራ እጇ ግን ወደ ታች እየተንከላወሰ ጕዞ ጀመረ ወደ ሴት ብልቷ" እጇ የደረሰበትን በዓይኗ ተመለከተችው
ከሰፊው የመስተዋት መስኮትና ላዩ ላይ ከተንጠለጠለው ነጭና
ቡና ዓይነት መጋረጃ አልፎ አልፎ ዧ ብሎ የሚያልፍ የመኪና ድምፅ ይሰማል" ክፍሉ ውስጥ ካሉት ሁለት አልጋዎች መካከል አንድ
ኮመዲኖ አለ። ኮመዲኖው ላይ «ሶኒ» የሚል ምልክት ካለበት ሬዲዮ ካሴት ውስጥ ከዛሬ ሁለት መቶ ሃምሳ ዓመት በፊት በሞዛርት የተቀነባበረው ፒያኖ ሶናታ የሙዚቃ ስልት ድምፁን ሰለምለም
ሞቅ ሞቅ ሰለምለም...እያደረገ ይንቆረቆራል ከመስኮቱ ጠርዝ አካባቢ ሁለት ሶፋና አንድ ጠረጴዛ ያለ ሲሆን ጠረጴዛው ላይ ከግማሽ
በላይ የተጠጣለት የማር አረቄ ይታያል"

ስቲቭ ማርቲን የአደረው «የዞረ ድምር» ዓይኖቹን ከርቸም ያለ እንቅልፍ አጋድሞታል በአዲስ አበባው ሒልተን ሆቴል
በተዘጋጀው የቡፌ ግብዣ ላይ ሦስት ወንበር እንዲያዝላቸው በማዘዝ ሁለቱ የፍቅር ጓደኛሞች ከከሎ ሆራ ጋር በመሆን ምሽቱን ከምግብ ጕዝጓዙ በኋላ መጎንጨቱንና በአፍሪቃውያን ሙዚቃ መውረግረጉን
እስከ እኩለ ሌሊት ሲያስኬዱት ቆይተው ነው ሁለቱ ፍቅረኛሞችና
ከሎ ሆራ «መሥመርህን ለይ» የተባባሉት"

ካርለት እና ስቲቭ የሥራ ቦታቸው በጣም የተራራቀና
የትራንስፖርትም ችግር ያለበት በመሆኑ ተመልሶ ለመገናኘት ቢያንስ የሦስት ወር ጊዜ ያስፈልጋቸዋል" በፍቅር አባዜ ለተያዙት ለእነዚህ ወጣቶች ደግሞ ጊዜው የትየለሌ ነው ሩቅ። ስለ መለያየታቸው እንጂ ስለ መገናኘታቸው የማይተማመኑት ፍቅረኛሞች በወሲብና በፍቅር ጨዋታ ሰዓታቸውን በሚገባ ለመጠቀም በአንድ ወጥ ስሜት ጥረዋል" ድብቅነት በሌለው ንጹሕ የፍቅር ጨዋታ ልባቸውን
ስልትና ቃናው በሚጣፍጥ ቅላፄ እያስጨፈሩ ራሳቸውን በመሆን በፍቅር ባሕር ከመዋኘት አልፈው ዘቅጠውበት አድረዋል።

ካርለት እንደምንም በድኗን ከስቲቭ እቅፍ መንጭቃ ተነሥታ ወደ ባኞ ክፍሉ በመሄድ ገላዋን ተጣጥባ ስትጨርስና በፎጣ ገላዋን
ስታደራርቅ ከስቲቭ ረዘም ላለ ጊዜ የመለየቷን፣ የፍቅርና ወሲብ ጥመኛ የመሆኗን ትርዒት በእዝነ ልቦናዋ ስትቃኝ ፍርሃትና ጭንቀት መንፈሷን ሰንገው ያዙት ተፈጥሯዊ ስሜቷ መኪና አይቶ እንደማያውቅ ፈረስ አእምሮዋን ጥሎ በረገገባት"
አንገቷን ዘንበል በማድረግ መጀመሪያ ጡቶቿን ከዚያም
እምብርቷንና ሰርጓዳ ወገቧን፣ ለስላሳ ጭኖቿን ስትመለከት ስሜቷን
በአእምሮዋ ለመቆጣጠር ተሳናት" ካርለት ስሜቷን ልትጫነው ስላልፈለገች በግዴለሽነት የመታጠቢያ ከፍሉን በር በርግዳ ስትወጣ ስቲቭ ቀኝ እግሩን አጠፍ አድርጎ ጭኖቹን በመበርገድ ተንጋሎ ተኝቷል።

ካርለት ስቲቭን ስታየው የሆነ ስሜት በመላ አካሏ ቅጽበታዊ መተረማመስ ፈጠረና ፍቅር አመንጭ ሕዋሳቶቿ ተከፋፍተው ወደ ፊት ገፈተሯት አእምሮዋም በስቲቭ አካል ላይ ቀስቱን ደገነ የልግጠም፣ ይውጋኝ ፍልሚያ። «ግንኮ የስቲቭ ስሜት እንደኔ ላይሆን ይችላል? ስሜቴን መቆጣጠር መቻል አለብኝ" ሊደከመውም እኮ ይችላል!» ብላ አሰበች" ታስብ እንጂ መንቀሳቀሷን አላቆመችም የሚገፋፋት ስሜት ወደፊት አዳፋት ተጠጋችው» ካርለት ያሰቡትን ለማድረግ መወሰን የሚሳንበት ወቅት መሆኑ ገብቷታል"

«ስቲቭ» አለች የእጅ ጣቶቿን ወደ ቡናማው ጸጕሩ እየሰገሰገች።
ቦንብ ቢፈነዳ እንኳን የሚነቃ የማይስለው ፍቅረኛዋ የእሷን ውብ ድምፅ ሰምቶ ዓይኖቹን ሲገልጥ የሚወደው ምስል እርቃነ ሥጋውን ከአጠገቡ ቆሞ ሲያይ፣ «ኦ...» ብሎ ዓይኖቹን ገለጠ።

«ፍቅር የሚጣፍጠው ሲልሱት ሳይሆን ሲግጡት፣ ኩርሽምሽም አድርገው ሲውጡት፣ ከአካል ጋር ሲዋሐድ፣ የተፈጥሮ ቦታውን
ሲይዝ፣ ደባቂና ተደባቂ ሲሆን እንጂ በቃላት ድርደራ አይደለም»ብላ የምታምነው ካርለት ለስቲቭ፣ «ና» የሚል ምልክት በእጇ አሳየችው ያ እጇ ሁሌም ከሚያስደስተው አካሏና ውስጣዊ እሷነቷ
እንደሚያደርሰው ያውቃልና ተከተለው።

በጣም ደክሞታል፤ ከካርለት እጆችና የፈገግታ ኃይል ግን ራሱን ሊለይ አልተቻለውም። ስለዚህ ወደ ተጠራበት አቅጣጫ ተጓዘ ጒዞው ራቀበት ከተጠራበት አካል ቶሎ ደርሶ ለመደሰት በጣም ጓጕቷል ካርለት ባኞ ቤት ውስጥ እንደገቡ ገፍትራ ለብ ካለው ውኃ
ውስጥ ከተተችው ሣቀ ሣቀች ሁለመናቸው ተሣሣቀ
ጭኖቿን ተመርኵዞ አንጋጦ ሲያይ የገነትን በር ያየ መሰለው ታዲያ የዚያን ውብ ስፍራ በር ከፍቶ የማይገባ ማን አለ? በየጅማቱ ሥር ተበታትኖ የነበረው ኃይል ዘቅዝቆ ወደ ብልቱ ሲንዶለዶል
ተሰማው" ያ የተበታተነ ኃይል እንኳን የተፈቀደለትን፣ ሌላ ጠንካራ በር እንኳ ጥሶ የሚያስገባ ኃይል እንዳለው አመነ።

«እወድሃለሁI ፍቅርህን አልጠግብምI ስግብግብ ነኝ እንድትለቀኝ አልፈልግም...» የሚል ድምፅ የሰማ መሰለው
የቃላት ምልልስ ወቅቱ አለመሆኑን በመረዳቱ ግን እግሮቿን እየዳሰሰ
ተነሣ ሁለቱ አካሎች ተዋሐዱ ፍጡር ካለ ክንፍ ወደሚንሳፈፍበት ወደ ሰማየ ሰማያት ተነጥቆ የገነትን ውበት ወደሚጎበኝበት ማራኪ መዓዛ ውብና እንከን የለሽ ተፈጥሮ ወደሚታይበት፣
እውነተኛ የፍቅርና የደስታ ዜማ ወደሚዜምበት ዓለም ተያይዘው ነጐዱI በሩ ተከፍቶ ተዘጋ።

።።።።።።።።።።።
ካርለት አልፈርድ በኦhስፎርድ ዩኒቨርሲቲ በሶስዮሎጂ የመጀመሪያ ዲግሪዋን ካገኘች በኋላ በዩኒቨርሲቲው የአንትሮፖሎጂ
ዲፓርትመንት አባል በመሆን በወቅቱ ታዋቂ በነበሩት አንትሮ ፖሎጂስቶች የተዘጋጁትን ጽሑፎችና ዲስኩሮች ተከታትላለች።

ከአሥራ አምስተኛው ክፍለ ዘመን በተለይም ሳይንስና ቴክኖሎጂ ከፍተኛ እመርታን ካሳየበት ከዛሬ መቶ ሃምሳ ዓመት ወዲህ እየተዋጡ
የመጡት ቅርሶች፣ የተናቁት ባህሎችና ለከፍተኛ ውጤት ሊያበቁ የሚችሉት የአርኪዮሎጂና የሌሎችም ጥናቶች የምሁራኑን አእምሮ ይበልጥ በመሳባቸው እንደ ጀርመን፣ እንግሊዝ፣ ጣሊያን፣ አሜሪካና ጃፓን የመሳሰሉት ምሁራን ትኵረት እንደ ሰጡት እንግሊዛውያንም ምሁራንም በመስኩ እጅግ ተስበው ነበር"
👍46
#ኢቫንጋዲ


#ክፍል_አንድ


#ከፍቅረ_ማርቆስ_ደስታ

...የልጃገረድ ጡት የመሰለው የሐመር ተራራ አፈዘዘው እና! ያን ማራኪ ተራራ በአይኑ ጠባው... በህሊና አኘከው... ጳ...
እኝ... ጳ... እያደረገ አጣጣመው።

hቡስካ ተራራ ላይ ሆኖ የሐመርን ምድርና ቀዬ ከአድማስ ወዲህ የአስሌንና የቡሜን ተራራ በየኮረብታው ላይ የሚታዩትን የሐመር መኖሪያ ቀዬዎች እየተጠማዘዘ ከቡስካ ተራራ ስር ጀምሮ ቁልቁል ወደ ኦሞ ወንዝ የሚጓዘውን የከስኬን ወንዝ... በአረንጓዴ
ልምላሜ የተዋበውን የሐመርን ጫካ ሲቃኝ የከብቶችን ግሣት
ሲያዳምጥ ስሜቱ ዋለለ፡፡

ደልቲ ውስጡ እንደዚያ በደስታ ቢተራመስም ውጫዊ እርጋታው ያው እንደወትሮው ነው:: ዝም!  ጅንን፡

አካባቢው በአዕዋፍ ድምፅ በሽምልማል ንፋስ ሽውሽውታ ከዛፍ እየተንጨዋለሉ በሚቦርቁት ጉሬዛና ጦጣዎች... ደምቋልዘ

ደልቲ ገልዲ ዝግባ ጥድ ግራር ካስዋበው የቡስካ ተራራ ላይ ሆኖ የአባቱን ምድር የሐመር ውብ ተፈጥሮ ሲቃኝ ቆይቶ
ከቆመበት ቦታ በስተግራ በኩል ካለችው ውብ የግራር ዛፍ ስር ሄዶ
በርኮታው ላይ ቁጭ አለ፡፡

ገሃዱ ዓለም ላይ ዋና ሥራ ጉዞ ፍቅር ጥላቻ... ይሆንና
በህሊና ቀረጢት ደግሞ ትዝታ ይከማቻል፡  ህልም ትዝታ...ማንም ከዚ ከስተት ሊያመልጥ አይችልም:: በገሃዱ የፈፀመውን
በትዝታ ምስል ያየዋል ከዚያ ይፍነከነካል ወይ ይቆዝማል! ይቅበጠበጣል ወይ ይሽማቀቃል! አልያም ይስቃል ወይ ያነባል...
ትዝታ! የተዳፈነውን እውነት እየጫረ ስሜትን ይለዋውጣል…

ደልቲም እንዲያ ከተዋበው ሥፍራ ሆኖ ዛሬን ከዛሬ ተቋድሶ ትናንትን አለማት ህልሟ  ትናንት ደግሞ የትናንት ግሣንግሷን
ይዛለት ከፊት ለፊቱ ተደቀነች፡ ጨዋታ ጭፈራ ጀግንነት ፍቅር...
አንዱ በሌላው ላይ እየተነባበረ ታየው፡፡ ገሃዱን ዓለም ከምናባዊ ትውስታው ጋር አንዳንዴ እየተጋጨ ሌላ ጊዜ እየተዋሃደ ተመለከተው የህይወት ኡደት የተፈጥሮ ባህሪ አንዱ ሌላውን እየተካ ብቅ ጥልቅ እያለ ሲያልፍ ህሊናው የትናንት ትዝታን ወደኋላ
ሲያነጠጥን ለማየት ተከተለው፡

ጦጣና ጉሬዛዎች ከዛፍ ዛፍ እየዘለሉ ሲቦርቁ አዕዋፍ ሽቅብ እየጓኑ ቁልቁል ሲወረወሩ... የደልቲ የቦዙ አይኖች የሚያዩት
ትናንትን ነው:: የትናንት ትዝታ ከሁሉም ገዝፎ በህሊናው ተንሰራፍቷል።

በዚህ የትዝታ ማጥ እንደተዘፈቀ የቦዙ አይኖቹ እንግዳ ነገር ተመለከተ
አይኑ የሚንቦገቦግ ቀንዱ የሾለ ሰውነቱ
የሚያንፀባርቅ... ግን የደነበረ አውሬ ሰውነቱ የሚንቀጠቀጥ መሸሽ
ደግሞ ያቃተው አውሬ::

ደልቲ ከትዝታ ማጡ ያለ የሌለ ሃይሉን አስተባብሮ
በመውጣት የያዘውን ክላሽንኮቭ በአውሬው ግንባር ላይ አነጣጥሮ
አመልካች ጣቱን ቃታውን ከመሳቧ በፊት ስሜቱ ሲጣራ ወስፋቱ ሲጮህ ሰማው፡፡ የተጠበሰ ስጋ ወጠሌ ጥብስ ትዝ አለው  ጎመጀ።የራበው ሰው የሚበላ ሲመጣ አይገፋም፡ ያውም ካውሬም የድኩላ
ምራቁ በአፉ ሞላ፡፡

ድኩላውን ከማሰናበቱ በፊት በመሣሪያው የማነጣጠሪያ
ለመጨረሻ ጊዜ ተመለከተው። ተሸብሯል! ፍርሃትም ያንዘፈዝፈዋል! “ለማምለጥ መሞከር ሲገባው ለምን ተገትሮ ቀረ?
አይኖቹስ ለምን ይማፀኑኛል?..” አለ በማይሰማ ድምፅ

ደልቲ ግራ ገባው፡፡ ቀጭኔ ጎሽ አንበሳ... ሲገል
እየተሯሯጠ አንዱ ለማምለጥ ሌላው ለማስቀረት እየተጣጣረ...
እየወደቀ.. እየተነሳ... ነበር: ዱኩላው ግን አልተንቀሳቀሰምI
አልሮጠም ታዲያ ደልቲ እንዴት ደንግጦ የቆመ እንስሳ ይገላል!
እንዴትስ ለሆዱ  ብሎ ተሸብሮ ከፊት ለፊቱ እንደ በግ ቆሞ የሚማፀነውን አውሬ ገድሎ የአባቱን የጀግንነት ባህልና ታሪኩን
ያበላሻል።

ዘገነነው! የራሱ የሆኑት ፍየሉች በጎችና, ከብቶች
ታሰቡት። የሥጋ አምሮት የአባት ባህል... እስሜትና እህሊና ትግል ውስጥ ከተቱት። ስሜቱ በሰውና ጥብስ ብላ አለው: ሀሊናው
“ፈርቶ ደንብሮ ጉያ ውስጥ የገባን አውሬ ተኩሶ መግደል የጀግና ሞያ አይደለም። የመልካም ስም የደግነት ሥራ ጠላቱ ከርስ ነው። ሆዳምነት! እና ተወው" አለው።

ደልቲ ይህን እያስበ ዓይኖቹን ከድኖ ሲከፍት ደነገጠ:: ተምታታበት ደኩላው ከፊት ለፊቱ የለም በሱ ቦታ የተተካውን
ማመን አቃተው አይኖቹን ጨፍኖ እንደገና ከፈታቸው: ለውጥ የለም: ድኩላው የለም: እሱን የተካው ግን ከፊት ለፊቱ ቆሟል።

ምን ጉድ ነው!" ደልቲ ተሸበረ። የሚያየውን ማመን
ተሳነው። አይኖቹን ደጋግሞ እየከደነ ከፈታቸው: አዎ! ቅዠት አይደለም እውነት ነው ከፊት ለፊቱ የቆመው ሰው ነው  ልጃገረድ... ያውም የደም ገንቦ ..

ድኵላ. ልጃገረድ… ድኩላ ልጃገረድ… ህሊናው እውነቱን ለማጣራት ሞከረ።

"ለምን መጣች? ምን ጉዳይ ይኖራት ይሆን ድኩላውስ
ለምን ቆመ? ለምን ደነገጠ? የትስ ሄደ ?  ለምን በሱ ቦታ እሷ ተተካች..." ራሱን ለማሳመን ማጠፊው አጠረበት።
ልጃገረዷን  የደም ገንቦዋን አውቋታል: የወሮ መንደር
ቆንጆ ናት ግን እሷ ስለመሆኗ ማን ማረጋገጫ ይስጠው: በህሊናው
መልስ አልባ ጥያቄዎች ተደረደሩ'

“ይእ! ከመሞት እንደሁ የሚያመልጥ የለ። ነገ ወይንም ተዚያ በኋላ በወባ ሞተች... የከስኬ ውሃ በላት… ከብት ወግቷት
ሞተች... ከምባል ደልቲ ገደላት I አፍቅራው ሄዳ ፍቅሯን ሳይረዳ
ጭንቀቷን ሳይካፈላት ራቧን ሳይራብ ሙቀቷን ሳይጋራት...ጀግናው ገደላት ቢባል ምናለ!" ልጃገረዷ ከቆመችበት ሳትንቀሳቀስ
አጉተመተመች።

እሏ ያስደነበረችው ድኩላ እሷን ፈርቶ ሮጦ ደልቲን ሲያይ ከፊት ለፊቱ ቆመ: እሷም የስንት ጎረምሳ ልብ ተነጥፎላት እየረጋገጠች አልፋ በፍቅር ልቡ ርሷል ለተባለው ጀግና ፍቅሯን
ልታበረከትለት ከደስታ ፈጣሪ ደረቱ ላይ ለመጋደም ተራራውን ወጥታ ከፊት ለፊቱ ተገተረች።

“ ደልቲ ድኩላውን ለምን ሳይገለው ቀረ? የቆመ
የተሽበረ አልገልም ብሎ እንጂ ከሰማይ ወፍ የሚያወርድ ጀግና ነው፡፡
ይእ እንዲህ ነው እንጂ ጎበዝ! ምግባሩን ለአባቱ ለባንኪሞሮ ትዕዛዝ
ያስገዛ  ለሆዱ ያላደረ... ለዚህ ጀግና ፍቅር ተራራ ቢወጡ እንደ ቅንቡርስ መሬት ለመሬት ቢልወሰወሱ እንደ ኩይሳ ከፊት ለፊቱ
ተገትረው ቢኖሩ ነፍስና ስጋን ቢሰጡት ምን ይቆረቁራል

“አይ እርጋታ! ደሞ ዛሬ እንደ አንበሳ ግርማ ሞገሱ እንዴት ያምራል? እውነት ከእሱ እቅፍ ገብታ ዓለሟን ያየች ሴት ጨረቃና
ከዋክብት በሌሉበት ድቅድቅ ጨለማ ብትጓዝ ትደናቀፍ ይሆን!"ፍቅሩ ውስጧን እያመሳት ቀባጠረች

ደልቲ ከንፈሯ ሲንቀላቀስ አይቷል። የምትለውን ግን
አልሰማም፡ ልጃገረዷ አንገቷ ላይ ከደረደረቻቸው ጨሌዎች ሦስቱን
አወጣች፡፡ ትንባሆ የያዘ ትንሽ የፍየል ቀንድ በቆዳዋ ጫፍ ቋጠረችበት ፈታች። ደልቲ በትዕግሥት ይመለከታታል፡

ልጃገረዷ አይኖችዋን ሳትሰብር በፍቅር አይን አይኑን እያየች ስትመጣ ደልቲ ትዝታው እንደአውሎ ነፋስ ወደ ኋላው ነጥቆት
ነጎደ። ወደ ትናንት ወደ ድሮ: ያኔ የትናንቱ ድሮ ጎይቲ አንተነና እሱ መጀመሪያ ከዲመካ ገበያ ተያይተው በአይን ተጠቃቅስው
በልቦናቸው ተስማምተው በፍቅር መሪነት ጫካ ገብተው ያ ያዜመችለት የወንዶች አውራ ጭን ላይ ቁጭ ብላ አእዋፍና ነፋሱ
እያጀቧት የድምጿን ቅኝት
👍663
#እህቴ_በባትሆኚ_አገባሽ_ነበረ፡፡
:
:
#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ


#ክፍል_አንድ
///

ይሄን ታሪክ እንደባዬግራፊ ውሰዱት፡፡ በነገራችን ላይ ባዬግራፊ ማንበብ ደስ ይለኛል፡፡ግለ-ታሪክ በጥልቅ ሳንሱር የተደረገ፤ የተስተካከለ እና የተሞረደ የግለሰብ ፍፅማዊ ታሪክ ነው ብዬ አምናለሁ ፡፡
ግለ-ታሪክ በተለየ መለኩ  ታዳጊዎችን ለመቅረፅና ሞዴል ኖሯቸው የወደፊቱን ህይወታቸውን  መስመር  እንዲያሲዙትና ጉዞቸውን ከመዝረክረክ፤ እራሳቸውንም ካላአስፈላጊ ውጤት አልባ መስዋዕትነት ለመታደግ  ጥረት እንዲያደርጉ ያግዛቸዋል የሚል እምነት አለኝ፡፡ግን ያው ሄዶ ሄዶ ህይወታቸው መዝረክረኩ፤ በየሂደቱም ለማይረቡ ነገሮች መሰዋዕትነት መክፈላቸው የማይቀርላቸው የህይወት ዕዳ ነው፡፡ ቢሆንም ጥረታቸው  የመዝረክረክ መጠኑ ላይ ልዩነት ያመጣል፡፡

ሌላው አዎ ግለ-ታሪክ ግለሰቦችን ብራንድና፤ ሪብራንድ የማድረጊያ ውጤታማ ዘዴ ነው፡፡ የማይሰበረው፤ሰውዬው፤የታፋኙ ማስታወሻ፤የበጋው  መብረቅ፤ የህይወቴ ጉዞና የፖለቲካ ህይወቴ  ፤የመንግስቱ ትዝታዎች ፤የመለስ ዜናዊ የህይወትና ትግል ታሪክ ፤ዳኛው ማን ነው?፤ ማማ በሰማይ ወዘተ…..
ቢሆንም ይሄን የእኔ ታሪክ ከእነዚህ ከላይ ከዘረዘርኳቸው ግለ-ታሪኮች የሚለየው ድንግል በመሆኑ ብቻ ነው፡፡ድንግል ግለ-ታሪክ ግን ምን አይነት ነው? ፡፡ለማለት የፈለኩት ስለባለታሪኩ ከዚህ በፊት በየትኛውም የመገናኛ  ዘዴ ፤በመፅሀፍ፤ በሬዲዬ ሆነ በጋዜጣ  አልሰማችሁም ፤አላነበባችሁም ማለቴ ነው፡፡

ከእኔና በዙሪያዬ ካሉ ጥቂት ሰዎች በስተቀር ማንም የማያውቀኝ ተራ ግለሰብ ነኝ፡፡ያው አናንተም እንደእኔ ተራ ከሆናችሁ ከላይ ከዘረዘርኳቸው ግለ-ታሪኮች ይልቅ የሚመጥናችሁም የሚያስተምራችሁም ይህ የእኔ የተራው ሰው ተራ ታሪክ ነው፡፡ምክንያቱም እኔ ራሴን ብራንድም፤ ሪብራንድም የማድረግ  ዓላማ የለኝም፤ምን ሊረባኝ..?እኔ መተንፈስ ብቻ ነው የምፈልገው፤ እናንተም አድማጭ እንድትሆኑኝ ብቻ ነው የምጠይቀው…በቃ ይሄው ነው፡፡

ከደብረብርሀን ወደአለማያ ዩኒቨርሲቲ ..ከአለማያ ደግሞ ወደአዲስ አበባ ከገባሁ ሁለት አመት ሆነኝ።  የተመረቅኩት በእፅዋት ሳይንስ ሲሆን ስራ ፍለጋ ከአንድ አመት በላይ የኳተንኩት ግን አዲስአበባ ነው። እርግጥ ወደ እድገት ከተማዬ ደብረብርሀን  ተመልሼ ቢሆን ኖሮ በቀላሉ በሁለት እና ሶስት ወር ውስጥ በተማርኩበት ትምህርት የሚገባኝን ወይንም ደግሞ ለጊዜውም ቢሆን የሚያኖረኝን ስራ አገኝ እንደነበረ እርግጠኛ ነኝ፤ግን እኔ ያንን ማድረግ አልቻልኩም… አልችልምም።
ለጊዜው ሰው እንደጉንዳን በሚርመሰመስባት  ፤ የህንፃ ጫካ የተጥለቀለቀባት  አዲስአበባ ምርጫዬ ሆናለች? ለምን? እራሴን ልደብቅባት፡፡ለምን ?ከሚያውቁኝ ዘመድ ወዳጅ አብሮ አደጎቼ መሠወር የምችልባት አስተማማኝ  ዋሻ አድርጌ ስለወሰድኳት።ለምን ?ባላድግባትም እትብቴ የተቀበረባት የትውልድ ከተማዬ ስለሆነች፤ ስለምወዳት፡፡የእኔ አዱ ገነት፤የእኔ ሸገር፡፡

እውነት እውነቱን እንነጋገር ከተባለ በዚህ ዘመን በኢትዬጵያ ዘመድ ወይም ወገን የምትለው ሰው በዙሪያህ ከሌለ ከዛም አለፍ ብሎ ባለጎሳና ባለ ብሄር ካልሆንክ መኖር የምትችለበት ቦታ እየጠፋ ነው…፡፡እንደእኔ ነጠላና መለመለውን ያለ ግለሰብማ ከሸገር ውጭ ለመኖር መወሰን አይደለም ማሰብ እራሱ አደጋ  ነው፡፡በዚህ ምክንያትም ይመስለኛል ሰዉ ከአራቱም አቅጣጫ በየምክንያቱ ጓዜን ማቄን ሳይል መጥቶ እየተጠቀጠቀባት ይሄው አሁን ሞልታ የሰውን ልጅ እንደ ውሻ ቡችሎች በየጎዳናው እና ስርቻው እያዝረከረከች ያለችው፡
ያው እንደነገርኳችሁ ብቸኛ ነኝ፡፡ ዋናዎቹ ቤተሠቦቼ ማለት እናትና አባቴ በህይወት የሉም።ልጅ ሆኜ ነው በድንገተኛ አደጋ ተያይዘው የሞቱት ።እህትና ወንድምም በፊቱንም የለኝም፡፡ያሳደገችኝ የእናቴ ታናሽ እህት አክስቴ ነች። አክስቴ ከእኔ ውጭ የራሷ ሶስት ልጆች አሏት ፡፡ሶስት ሴቶች  እኔ አራተኛ ልጅ ነኝ።ምን አልባት ብቸኛ ወንድ ልጅ ስለሆንኩ  ወይንም የሙት  ልጅ  ስለሆንኩ አላውቅም  ልክ እንደ ስለት ልጅ በልዩ በእንክብካቤና በሀዘኔታ ነው ያደኩት።

አሁን ግን አድጌ ዩኒቨርሲቲ ገብቼ ከተመረቅኩ በኃላ ከዘመዶቼ በመቆራረጤ አየር ላይ ቀርቼያለሁ፤ወደዛ ቤተሠብ ፊቴን ማዞር የማልችልበት ሁኔታ ውስጥ ከገባው አመታት አልፏኛል።እንዴት? ቤተሠብን አፍርሻለሁ፡፡ እከሌ ከእከሌ ሳይባል ቤተሰቦቼ ምላቸውን የሁሉንም ልብ ሰብሬያለሁ..የዚህ ሁሉ መጥፎ ስራ ውጤት ደግሞ በድምሩ ወደራሴው ተመልሶ ሙሉውን የህይወት ተስፋዬን ደረማምሶ አፍራርሶብኝል፡፡ዓላማ ቢስ …ምንም ተስፋ የሌለው ተንቀሳቃሽ ሬሳ ሆኜያለሁ፡፡ዝርዝሩን ሌላ ጊዜ ከመነሻ ታሪኩ አንስቶ ተርክላችኋለሁ፡፡
///

እንደነገርኳችሁ እንዲህ ሆናለሁ ወይም እዚህ ቦታ ደርሳለሁ የሚል እንጥፍጣፊ ምኞትና እቅድ ውስጤ የለም…ተስፋዬ ከፈረሰ ቆይቷል.. ቢሆንም ዝም ብሎ  ለመኖር ብቻ ቢሆንም እንኳን መብላት ያስፈልገኛል።ለዛውም በቀን ሁለቴ እና ሶስቴ ። እናም ያንን ለማሟላት ደግሞ በየቀኑ መስራት የግድ ይላል።አዎ ወይ መብላት ማቆም አለብኝ ወይ ደግሞ ስራ መስራትና ገንዘብ መስራት አለብኝ። ግን ምንድነው የምሰራው?ምን ችሎታ ወይም ሞያ አለኝ?ስራ ለመፈለግ ስነሳ ይሄንን ጥያቄ  ነው እራሴን የጠየቅኩት፡፡

ከአለማያ ወደአዲስ አበባ እንደገባው እጄ ላይ አጠራቅሚያት የነበረችውን ጥቂት ሳንቲም እስክታልቅ ስራ በመፈግ በመኳተን አራት ድፍን ወራቶች አሳልፌያለሁ፡፡በስተመጨረሻ ተስፋ ከቆረጥኩና ኪሴ መራቆቱ እርግጥ ከሆነ በኃላ ያገኘሁትን ማንኛውንም ስራ ለመስራት ወሰንኩ፡፡ ,…ለሁለት ወራት በኮንስትራክሽን ድርጅቶች በቀን ስራ ለመስራት ሞክሬ ነበር….ግን በእውነት በጣም ወገብ ቆራጭ ብቻ ሳይሆን ተስፋ አስቆራጭ ስራ  ነው የሆነብኝ…በፊቱኑም የሌለ ተስፋ ሲቆረጥ ይታያችሁ፡፡ዕድሜውን ሙሉ በቤቱ ምንም አይነት የጉልበት ስራ የመስራት ልምድ ለሌለው ሰው ይቅርና ልምድ ላለውም ጉልበተኛ አርማታ መግፋትን መሸከምን የመሰለ ሌላ ፈታኝ  ስራ መኖሩን እጠራጠራለሁ…ምን አልባት የምድር ውስጥ የመአድን ቁፋሮ ሊበልጠው ይችላል፡፡ ስራው እኮ በተለይ ከሰዓት በኃላ ሲሆን ምላስ ታጥፋ ጉሮሮው ውስጥ ነው የምትወተፈው፡፡
በሁለተኛ ደረጃ ለመስራት የሞከርኩት የፓርኪንግ ስራ ነው…፡፡ከቀን ስራው ቢሻልም ገቢው ግን እዚህ ግባ የሚባል አይደለም…፡፡ቢሆንም የፓርኪንግ ስራው ወደሌላ ስራ መሸጋገሪያ ድልድይ ሆነኝ….፡፡የፓርኪንግ ስራ የምሰራበት ቦታ በሁለት ቀንም ሆነ በሶስት ቀን እየመጣ ከሚጠቀም ሰው ጋር ቀስ በቀስ ተግባባን፡፡እንዲሁ ያለምክንያት ሲመጣ ደስ ይለኛል....፡፡ከሌላው የተለየ ፈገግታ እና መሽቆጥቆጥ አስተናግደዋለሁ..፡፡እሱም ቲፕ አስጨብጦኝ ይሄዳል፤ሳይመጣ አራት አምስት ቀን ካሳለፈ ቅር ይለኛል፤ለቲፑ አይደለም…እንዲሁ ለመልካምነቱ…፡፡
አንድ ቀን ታዲያ እንደወትሮ መጥቶ ፓርኪንግ ተጠቀሞ ሊሄድ ሂስብ እየተቀባበልን ሳለ ድንገት ወሬ ጀመርን፡፡
‹‹እዬብ እንዴት ነው ስራ?››
‹‹ጋሼ ሰሎሞን  ሰሪው ነው እንጂ ስራ ምን ይሆናል  ብለህ ነው?››አልኩት(ይህቺን ንግግር ከሆነ ጓደኛዬ ነው የሰማሁት)
👍914🥰3😁2👏1🤔1
#የዘርሲዎች_ፍቅር


#ክፍል_አንድ


#በፍቅረማርቆስ_ደስታ


ከእንቅልፉ ረፋዱ ላይ ነቃ ክፍሉ በብርሃን ተሞልቷል
እንደተጋደመ ማሰብ ጀመረ ተስፋ ያለው ነገር አልታየውም እዚች
አገር ከመኝታው ሲነቃ ፍንድቅድቅ የሚል የእናቱን ጡት የሚጠባ ህፃን ብቻ ነው" ሌላው ግን ህሊናውን እያከከ ምን ሰርቶ እንደሚበላ ያስባል፤ ምን ሰርቶ እንደሚኖር ያልማል ትንሹ በትልቁ ህሊና
ገብቶ መሞትን ይመኛል ሞት የሌለበትን አሸናፊነት ለማግኘት ይማስናል እና ከመኝታው ሲነሳ ጭንቀትንና ተስፋ መቁረጥን ያዛጋል

ምነው አገሬ ጭንጫ ምድር በሆነች ኖሮ ለፋን ለፋን
ምርት ግን ጠፋ ብለን እናመሃኝ ነበር ምነው ከርሰ-ምድሯ በደረቀ
ኖሮ ካለውሃ መቼስ ምን መስራት ይቻላል እንልም ነበር ካላት የከርሰ-ምድር ውሃ አስር ፐርሰንት እንኳ አለመጠቀሟን ባናውቅ
ምነው የሰው ኃይልስ ባልኖረ ምን ይደረግ
የአለንን ለመጠቀም
ሰው ያስፈልጋል እንልም ነበር የሰው ኃይል ባልኖረ ኖሮ ይህች አገር ግን ሁሉም  አላት  ልምላሜ ታሪክ ውበት እህ!.. የጭንቀታችን ምንጭ የሆነው ህምታ ከየት መጣ?" የእኛ ትውልድ የወሲብ  የጦርነት የዝርፊያ ፊልም ማየት በቃው? እኮ ምን አለፋን በፊልም የሌለንን እናያለን በፊልም የማንኖረውን እንኖራለን ..."  ብሎ ሲፈላሰፍ ቆይቶ
ከመኝታው አፈፍ ብሎ ተነሳና ወደ ተናኘ መኝታ ክፍል ሄደ  ተናኘ በጠዋቱ የለችም እሱ ግን ወደ አልጋዋ ተጠጋና ጠርዙ ላይ ቁጭ አለ ራስጌዋ ካለችው ትንሽ ኮመዲኖ ላይ የእለት ውሎዋን የምትፅፍበትን ማስታወሻ አየው" ላንሳው አላንሳው ከህሊናው ጋር
ተሟገተ እረፍ  እረፍና ተነስ! ህሊናው አዘዘው"

እንጃባህ! በልጄ …'

"ኦሆሆ! ጅል አትሁን  አንተ አባት ማስታወሻ ደግሞ
ምሥጢር ተቀባይና አስቀማጭ ነው" አንተን አያውቅም ለአንተም
አይታዘዝም ጌታው እሷ ናት ገላጯ ፀሐፊዋ  ልጅህ ናት
ለአንተ የሚሆነውን ከእሷ ጠይቅ ከእሷ ህሊና አንብብ

"ማንም ሰው ሊገልፀው የማይፈልግ የምሥጢር መቃብር ህሊናው ውስጥ አለ በሐዘን ብቻውን እንደ ጥጥ ተባዝቶ አስከፊ
መቃብሩን ተሸክሞ በፍርሃት እየራደ ከአፅም ጋር እየተፋጠጠ እጣ ፋንታው የሆነውን ዘግናኝ ህይወቱን የሚኖር አለ! ... የህሊና ውስጥ ሞት ሃዘንተኛ የማይጠይቅበት የመቃብር ሐውልት የማይታነፅበት
በየግላችን ያጣነውን መልካምም ሆነ መጥፎ የህይወት እጣ በሙሚ
ቀባብተን ሳይበሰብስ የምንቀብርበት ብቸኛው የመቃብር ሥፍራ
ህሊናችን ነው" ሁለተኛ የመቃብር ሥፍራ ደግሞ የግል ማስታወሻ
ነው" ማንም ሊያየው፥ ሊመራመርበት ሊጎበኘው ... አይችልም
ካለባለቤቱ በስተቀር ለሌላ ሰው ዝግ ነው  ስለዚህ ማስታወሻዋን
አትንካው ! በሃጢያት ደም ህሊናህን አትበክለው ...'
አያገባህም፤ ለልጄ ከኔ የበለጠ ምሥጢር ጠባቂ የላትም ይህን ሲያስብ ሰቀጠጠው፤

"እሽ ልጄ የራሷ የህይወት ምሥጢር ይኖራት ይሆናል
ማወቅም አይገባኝ ይሆናል ማስታወሻዋን ማንበቤም ትልቅ የህሊና ወቀሳ ያመጣል" ግን እሷን ደግሞ ማወቅ አለብኝ በቀጥታም ባይሆን በተዘዋዋሪ አስፈልጋታለሁ  አለሁልሽ የማልላትን ልጄን እውነተኛ
እሷነቷን በመጠየቅ አላገኘውም የማነበው ልቆጣጠራት አይደለም
ለዚያማ ህሊናዋ የት ሄዶ የምታነበው መጽሐፍ መች አንሷት እሳትና ውኃ
ለልጄ ማወቅ ያለባትን  ማሳወቅ የነበረብኝንም እሳትና ውኀ
አሳይቻታለሁ እንዴት እንደምትጠጣና እንደምታበስል ግን እያየች፥
እያነበበች እየሞከረች
ተማረች አባት ልጁን ዘለዓለም የሚያስተምር መምህር አይደለም ትምህርት አያቆምም አባትና የክፍል አስተማሪ ግን የማስተማሩ እድላቸው የሆነ ደረጃ ላይ ያቆማል ከዚያ መማማር በመጨረሻ ደግሞ ይማራሉ" እና!- ከልጄ የህይወት ፈተና ልማር ተወኝ" ብሎ ህሊናውን መንጭቆት
ማስታወሻዋን ከኮሞዲኖው ላይ አነሳው

ሰርቶ መብላት ምን ነውር አለው መሰደድስ ቢሆን
ወንድማለም! ከቸገረህ ምን ያሳፍራል? እውነቴን'ኮ ነው በሃብት ደልበዋል የተባሉትስ አሜሪካኖችና አውሮፓውያን ተሰደው ለአረብ አሽከር ሆነው ብራቸውን አፍሰው አገራቸው ይገቡ የለ ..." የሚለውን የራስ ማፅናኛ አባባል አንብቦ ሌላ ገፅ ገለጠ።

"ወንድማለም! ወገቤ እስኪቆረጥ ለሰዓታት ስማስን ቀኑ ነጉዶ
ለሊቱ ጭላጭ ሰዓት እየቀረው ነው ምስጋና የሌለበት ባዶ ህይወት!
“ለገንዘብሽ ነው ስትቆይ ያው መጥገብሽ አይቀርም ፀባይሽ ካላማረ ኮንትራትሽን ሰርዞ መተካት ነው ተሰልፎ ከሚለምነው አንዱን
እየተባልህ የዕቃ ክብር ተነፍጎህ በዘመናዊ ባርነት መኖር ወንድማለም ደከመኝ እባክህ ልተኛ! ልተኛ ማን አስተኝቶኝ ባለቤቷ እንቅልፍ ስታጣ የኔን መኝታ በር አንኳኩታ ቀስቅሳኝ
ተመልሳ መተኛት ልማዷ ነው" አንዳንዴ ሳስበው እኔ ሰራተኛዋ ብቻ ሳልሆን የእንቅልፍ ማስወሰጃ እንክብሏም ነኝ እላለሁ  በል
ለሁሉም ጎኔን ላሳርፈው ማለቱ ይሻለኛል የሚለውንም አንብቦ ሌላ
ገፅ ገለጠ።

"አይ ወንድማለም!  ይሄንስ እድሜ ልክህን ባታስበው
ይሻላል" ለአንተ እኔ ሁሌ ህፃን ነኝ አይደል?  ግንኮ ህፃን ከሆንኩ ሁለት አስርተ ዓመታት አለፉ ግን አንተ ስለጎረምሳነት ዘመንህ
ለምንድን ነው የማታወራው?  የምትወደድ ሰው ነበርህ?  ወይንስ
ጨካኝ: ዋሾ! ... ሁሉንም ሁን ለምን እንደሆንህ አላውቅምና ጭፍን
ያለ የተሳሳተ ፍርድ ሰጥቼ ልወቅስህ አልሻም ያ አይነት ፍርድ መስጠት ካቆምሁ ደግሞ ቀናት ተቆጠሩ።

"ወንድዬ! የጀመርሁትን ሳልነገርህ  ምን ዙሪያ ጥምጥም አዞረኝ? ማስታወሻዬን ነው አታነበው፤ግን ፈራሁህ ስፅፍ  እያሰብሁህ ነው" በዚህ ዓለም የምታምኝው?'
ብባል የለኝም
የምትቀርቢው? ከተባልሁ
ግን ወንድማለምን
ነው የምለው"ይከፋህ ይሆን? ይክፋህ እንጂ የምወድህ
ስለማላምንህ ስንት የደበቅሁህ ጉድ አለ መሰለህ አንተ መቼም እንደ
አባቴ ብትሆንም
ብዙ አባቶች ድፍን ፍቅርን የምትሻ ግብዝ አባት አትመስለኝም ሁሉም ልክ እንዳለው ታውቃለህ  አይደል?"

"ፍቅሬ አገረሼ ወንድዬ! አንድ ጊዜ በየሄድሁበት እያስነጠሰ የሚያሳጣ ፍቅር ይዞኝ ነበር" ያ የፍቅር ገጠመኝ አሁን ተረት ነው
የነ ጦጢትና አንበሳ ተረት የዓረብ ቤት እያፀዳሁ ግን ያ የተረት ስሜቴን ፏጨረው፤ አንዴ ይቆረጥመኛል ሌላ ጊዜ ይለበልበኛል እንደ ቁርጠት ቀስፎ አላስቆም አላስቀምጥ ይለኛል
ያንጠራራኛል እንደ ምጥ ገፍቶ ሲመጣ ደግሞ ሲቃ ነው፡ ውለጂው ነው
አንተ ወንድማለም! አሁን አሁን ሳስበው ከሱስ ነፃ ነኝ!' እያልሁ ስመፃደቅ ለካ ማፍረሻ የሌለው ሱስ ሱሰኛ ነኝ  እህህህ በሱስ መጠመድ ቢሉህ መጠመድ ነው ያውም በቅርብ ባላረከው
ወደፊትም በቅርቡ በማታገኘው ሱስ የሚፋጨው የስሜት ስለት
ህሊናህን ሲበሳሳው፤ እየወጠረ ሲያከረው ነፍስህ ረፍት አጣ ውጪ
ነፍስ ግቢ ነፍስ ብትሰቃይ ምን ይሰማህ ይሆን?" ፈገግ አለ ጥያቄዋ
አፈፍ አድርጎ ተሸክሞት ወደ ኋላው ከነፈ አልፎት ወደመጣው የወጣትነት ህይወት የልጁን ምስጢር ከዚያ በላይ አንብቦ ማወቅ
ግን አልፈለገም እሷ ግን ማስታወሻዋ ላይ ስሜቷን: ውጥረቷን ረሃቧን ጥማቷን ... ዘክዝካው ነበር"

"... ወንድማለም የአለሁት ወህኒ ቤት ነው ትናንት ሃያ
👍29