አትሮኖስ
286K subscribers
118 photos
3 videos
41 files
567 links
╔╦╦╦═╦╗╔═╦═╦══╦═╗
║║║║╩╣╚╣═╣║║║║║╩╣
╚══╩═╩═╩═╩═╩╩╩
ግጥሞች አዳዲስና ቆየት ያሉ የታዋቂ ደራሲያን መፅሐፍቶችን በ PDF እንዲሁንም
ያልተነበቡ ድርሰቶችን ግጥሞችን ታሪኮችን ያገኙበታል።


Contact. @atronosebot
please dont touch the leave button.😔😳😳
Download Telegram
#የፍቅር_ሰመመን


#ክፍል_አስራ_ስምንት


#ድርሰት_ሲዲኒ_ሼልደን


#ትርጉም_ብርሃኑ_በላቸው

የዊሊ ባደን እና የቫለንቲና ባደን
ወደ ሎስ አንጀለስ መመለስ በሚዲያዎች ሳይታወቅ ነበር፡፡ የዊሊ የግል አውሮፕላን ማክሰኞ ዕለት አውሮፕላን ማረፍያ ላይ ካረፈ በኋላ ለፓይለቱ የተነገረው በጠዋት
አለቃውን (ዊሊን አርብ ጠዋት ላይ ወደ ካቦ እንደሚመልስው ነው። ወ/ሮ
ባደን ከተማው ውስጥ ለጥቂት ቀናት መቆየት ፈልጋለች:: ምክንያቱም ለበጎ
አድራጎት ድርጅቷ ማድረግ የሚገባት ነገር አለ። ለማንኛውም ጠበቃቸው
ግሌን የሎስ አንጀለስ ፖሊስ ዲፓርትመንት ተጭኖ እንዲያገኛቸው ቀጠሮ ስለያዛቸው ነገ ያገኟቸዋል።

“የእነርሱ በግድ ረቡዕ ዕለት ቀጠሮ ማስያዛቸው ትንሽ አላበሸቀህም?”
በማለት ጉድማን ጆንሰንን ጠየቀው፡፡ ወደ ዊሊ ዲፓርትመንት ዊሊን ለመጠየቅ በማምራት ላይ እንዳለ “ማለቴ በጣም ሀብታም ስለሆነ ይሆን እንዴ ይሄ ሁሉ ትብብር የተደረገለት?”

መርማሪዎቹ ሁለቱን ባደኖች ለየብቻ ሊጠይቋቸው ነው የተስማሙት። ጆንሰን ዊሊ ባደንን አፖርትመንቱ ድረስ
በመሄድ ሲጠይቅ ጉድማን ደግሞ
መርማሪዎቹ ሁለቱን ባደኖችን ለየብቻ ሊጠይቋቸው ነው እቅዳቸው።

“ሽማግሌው ባደን ለእኛ ዲፓርትመንት ድጋፍ ያደርጋል። በዚያ ላይ ደግሞ በራሱ ፍቃድ ነው እኛን ለማናገር በርሮ የመጣው። ስለዚህ ምንም፧
አልመሰለኝም” አለው ጆንሰን፡፡

ዊሊ ባደን በጣም ብዙ ዶላሮችን በየዓመቱ ለሎስ አንጀለስ ፖሊስ
ዲፓርትመንት የሚለግስ ሰው እንደሆነ የአደባባይ ሚስጥር ነው። በዚህም
የተነሳ ከዛሬ ሁለት ዓመት በፊት የሚስቱ በጎ አድራጎት ድርጅት የታክስ
ማጭበርበር እና ያልታወቀ ገቢ አስገብቷል በሚል ይደረግበት የነበረውን
ምርመራ ዊሊ እንዳስቀረው ይታማል። ይህንን ነገር ደግሞ ጉድማንም በወቅቱ ሰምቶት ስለነበር የቃላ መጠየቁን የቀጠሮ ቀን በዊሊ ባደን ፍላጎት መወሰኑ ጥሩ ስሜት አልሰጠውም፡፡

“ለማንኛውም ወ/ሮ ባደንን በሥርዓት አውራት” አለው እና ጆንስን
በመቀጠልም

“ይሄ ለእነርሱ ልዩ እንክብካቤ ተደረገላቸው በሚለው አመለካከትህ
ከአፍህ አፈትልኮ ይወጣ እና የዲፓርትመንታችን ዋና አዛዥ ይሆናል ቀጥሉ የሚያናግርህ” ብሎ አስጠነቀቀው፡፡

“እንዴ እኔ እኮ ሁልጊዜም መልካም ነኝ ይህንን ታውቅ አይደል” ብሎ
ጉድማን መለሰ፡፡

በቀጠሮ ቦታ ላይ ቫለንቲና ባደንን ሲያገኛት ግን ቀለል ያለ ስሜት ነበር
የተሰማው። ቫለንቲና ባደን ከቤቨርሊ ሂል መዋኛ አጠገብ ከሚገኘው ወንበር
በአንዱ ላይ ተቀምጣ ነበር። የለበሰችው ቀለል ያለ ነጭ ሙሉ ቀሚስ ነበር። የሰውነት አቋሟም ጥሩ በሚባል ደረጃ ላይ ይገኛል። ፀጉሯን በቀላሉ ሽብ አድርጋዋለች፤ ፊቷ ላይም ትንሽ ሜክአፕ ብቻ ነው የተቀባችው። ወደ እዚህ ቦታ ዘግይታ ስለመጣች ይቅርታ የጠየቀችው በትህትና ነበር።

“እንዳለመታደል ሆኖ የዊሊ ቢዝነሶች ትንሽ አስቸጋሪዎች ናቸው። ለዚህ
ነው በቀላሉ ተነስተን መምጣት ያልቻልነው” ብላ ተናገረች እና በመቀጠልም በዚያ ላይ ደግሞ የባለቤቴን ቅሌት ሚዲያዎች በሙሉ እያነፈሱ ያሉበት ጊዜ ላይ ስለነበር ለእኔም ትንሽ ችግር ነበረው። ለዚያም ነው ወደ እዚህ በቶሎ ያልመጣሁት።” አለችው፡፡

“ልክ ብለሻል” ብሎ ጉድማን ነገሩ እንደገባው ገለፀላት እና የውሃ
ግብዣዋንም ተቀብሎ “በእውነት በዚህ ችግር ውስጥ በሆንሽበት ጊዜ ላይ
እኛን ለማናገር ፈቃደኛ ስለሆንሽ ደስ ብሎኛል” አላት፡፡

“ግን እኔን ለመጠየቅ በመፈለጋችሁ በትንሹም ቢሆን ተገርሜያለሁ።
ብላ ቫለንቲና በእርጋታ ስሜት ውስጥ ሆና “ማለቴ ዊሊ ከተገደለችው ልጅ ጋር
ግኑኝነት እንዳለው ሰምቻለሁ ታዲያ ስለ እሷ እሱን ነው ማናገር የሚኖርባችሁ ብዬ አስባለሁ። ስለ ሊዛ ፍላንገን እኔ ብዙ ነገር አላውቅም ብላ የሊዛ ስም ምላሷ ላይ ምሬት እንደፈጠረባት ሁሉ ፊቷን በትንሹ
አጨፈገገች።

“ስለ ግንኙነታቸው ስትሰሚ ትንሽ የተገረምሽ ይመስለኛል?” ብሎ
ጉድማን ጠየቃት፡፡

ቫለንቲናም ወደ ፊት ትንሽ ዘንበል ብላ “ባለቤቴ ከሌሎች ሴቶች ጋር ግንኙነት እንዳለው አውቃለሁ:: ኢንስፔክተር እኔ ያን ያህል ሞኝ አይደለሁም። ግን ስለዚህች ስለተገደለችው ልጅ ከዚህ በፊት አንድም ቀን ሰምቼ አላውቅም። ስለዚህ በእናንተ ምርመራ ላይ ምን ላግዛችሁ እንደምችል
አላውቅም:” አለችው፡፡

“ከሌሎች ሴቶች ጋር ባልሽ ያለውን ግንኙነት አምነሽ ተቀብለሽ እየኖርሽ
ነበር?” ብሎ ጉድማን በግርምት እየተመለከታት ጠየቃት፡፡

ቫለንቲናም የቅሬታ ፈገግታ ለግሳው “እንደዚያ እንኳን ማለቴ አይደለም።
የትዳር ህይወት ትንሽ የተወሳሰበ ነው:: ትዳሬ ውስጥ የማያቸው ነገሮች
ስሜቴን ይጎዱታል፡፡ ግን ሌሎች ነገሮች ጥሩ እንድሆን ያደርጉኛል፡፡ የራሴን
ፍላጎቶች እና ለመስራት የምፈልጋቸውን ነገሮችንም በነፃነት እንዳደርግ
ዕድሉን ይሰጠኛል። ለምሳሌ ያህል የበጎ አድራጎት ሥራዎች ላይ እንድሳተፍ
ነፃነቱን ሰጥቶኛል” አለችው:: ጉድማን ቫለንቲና የመለሰችለት መልስ ውስጥ
ውሸቶች እንዳሉበት ተሰምቶታል።

“ብራንዶን ግሮልሽ የሚባል ወጣት ልጅን ታውቂዋለሽ?” ብሎ በቀጥታ ወደ ጉዳዩ በመግባት ጥያቄውን አቀረበ፡፡

ቫለንቲናም ወደ ኋላዋ ለጠጥ አለች እና “ብራንዶን? አዎን አውቀዋለሁ ታዲያ ብራንዶን ከአንተ ምርመራ ጋር ምን ያገናኘዋል?” ብራንዶንን
“እንዴት እንዳወቅሽው ልትነግሪኝ ትችያለሽ?” ብሎ ጠየቃት፡፡

“በአካል አላውቀውም፡፡ ግን እናቱን አውቃታለሁ። ምስኪን ፍራን” ብላ
በሀዘን ጭንቅላቷን ነቀነቀች፡፡

“ለምን ምስኪን አልሻት?” ጉድማን ጠየቃት፡፡

“አየህ ልጄ ብራንዶን ጠፍቶ ስለነበር ነው ከፍራን ጋር ለመተዋወቅ የቻልነው:: የእኛ በጎ አድራጎት ድርጅት ምን እንደሚሰራ መቼስ የምታውቅ ይመስለኛል”

ጉድማንም ራሱን በአዎንታ ነቅንቆ “አዎን ስለጠፉት ሰዎች ማንነት ለህብረተሰቡ በማሳወቅ ፍለጋችሁን እንደምታካሂዱ አውቃለሁ” አላት።

“መርማሪ ጉድማን እኛ ይሄን ብቻ አይደለም የምንሰራው” አለችው፡፡

በውስጡም ስለ ታክስ ማጭበርበር ምርመራው ልጠይቃት ይሆን? ብሎ
ጉድማን ትንሽ አሰበ። እሱን እያየች የምታወራበት መንገድ ትንሽ የመፈተን
እና የማማለል ነገር ይታይበታል።

“እስቲ ስለ ግሮልሽ ቤተሰብ ንገሪኝ”

“ያው ከአብዛኛዎቹ ከሚጠፉት ልጆች ጋር ተመሳሳይ ነው ነገሩ” ብላ ቫለንቲና በረዥሙ አየር ሳበች፤ በመቀጠልም “ብራንዶን ኣደንዛዥ ዕፁን አብዝቶ የመጠቀም ችግር ነበረበት፡፡ እናም ሱሱ ከፍተኛ ደረጃ ደርሶ ጨርስዐ መንገድ ሲስት ማንም ሃይ ያለው አልነበረም፡፡ ይሄ ደግሞ ሁሌም የሚከሰት ነገር ነው። እኛ ግን የእሱን ነገር በጣም ትኩረት ሰጥተን
ፍለጋችንን መከታተል ጀመርን” ብላ ቫለንቲና ስትናገር ከድምጿ ላይ ፍፁም
የሆነ የመቆጨት ድምፀትን ጉድማን ተመለከተ። ይህቺ ሀብታም ሴት
ድብርቷን ለማባረር እንጂ ምን ልስራ ብላ ሳይሆን የበጎ አድራጎት ድርጅቷን
ያቋቋመችው በትክክል በእናትነት ስሜት ውስጥ ሆና እና በጣም ተጨንቃ
የጠፉትን ልጆች እንደምትፈልግ በመገንዘቡ በጣም እየተገረመ ነበር
የሚያዳምጣት።

“የእኛ ድርጅት ለፍራን ልጇን ብራንዶንን በመፈለግ ተባብሯታል። ይህንን ደግሞ የእናንተ ዲፓርትመንት እንኳን አላደረገውም፡፡ ምንም እንኳን የፍለጋው ውጤት የከፋ ቢሆንም ስላደረግንላት እገዛ ከፍራን ምስጋናን አግኝተናል፡፡ በእኔ እና በአንተ መሀል ይቅር እና ባሏ ናታን ግን በጣም አስቸጋሪ ሰው ነው። በቃ ጨካኝ ነገር ነው። እንዲያውም ልጁን ብራንዶንን የሚወደው አይመስለኝም፡፡ በዚያ ላይ ደግሞ ሚስቱ በምን ያህል የሀዘን ስሜት ውስጥ እንደሆነች የሚረዳትም
👍2
#የወድያነሽ


#ክፍል_አስራ_ስምንት


#ድርሰት_ኀይለመለኮት_መዋዕል


....ከቤተሰቦቼ ጋር የነበረኝ ግንኙነት እምብዛም ሳያፈነግጥና ሳይቀርብ፣
ሳይጥምና ሳይሆመጥጥ ቀጠለ የወዲያነሽ አንድ ዓመት ከመንፈቋ እንደ አንድ የደስታ ቀን ፈጥኖ ዐለፈ፡፡ አንድ ቀን እሑድ ከሰዓት በኋላ ከአንድ ጓደኛዬ
የተዋስኩትን መቅረፀ ትርዒት (ካሜራ ወይም ፎቶ ማንሻ ይዤ ወደ ዕጓላ
ማውታ ሄድኩ

ከዚያ ቀደም ሲል ከወሰድኩለት ልብሶች መካከል ጥሩዋን ልብስ አልብሽ አነሣሁትና እንዴት እንደሚደርሳት ቀደም ብዪ ጨርሼ ስለነበር በሳምንቱ እሑድ
የልጇን ፎቶ ይዤ በጉልላት መኪና ወህኒ ቤት ሄድኩ። እንደ ተለመደው !
፣አስጠራኋት፡፡ የአጥሩን አግዳሚ ዕንጨት ተደግፋ ጥቂት አወራራን ድንገት !ሳታስበው ፎቶግራፉን ከኪሴ መዥረጥ አደረግሁና «በይ እስኪ በቃሽ እዪና ጥገቢው፡ ነጋ ጠባ፣ ልጄ! ልጄ ስትይ!...» ብዬ በወታደሪቱ ኣስተላላፊነት
አቀበልኳት፡፡ የወረቀቱን ግራ ቀኝ ጠርዝ በሁለት እጆቿ ይዛ ትኩር ብላ
ተመለከተችው:: ፊቷ ላይ ስታሸበሽብ የቆየችው ኮስማና ፈገግታ ደብዛዋ ጠፋ።

ወዲያው ብርሃኗ በጥቅጥቅ ጭጋግ እንደ ፈዘዘ ጨረቃ ፈዘዘች። እንባዋ
በዐይኖቿ ዙሪያ ግጥም አለ፡፡ አቀረቀረች። በሰንበሌጥ ላይ እየተንኳላላች እንደምትወርድ ጠፈጠፍ እንባዋ ጉንጯን ሳይነካ ከትንሿ ወረቀት ላይ ተንጠባጠበ።

ከሩኅሩኅ የእናትነቷ ባሕሪ የመነጨ የፍቅር ኩልልታ ስለነበር ለመጪው
ጊዜ የሚቀመጥ የትዝታ ጥሪት አስቀመጥኩ፡፡ ደግማ ደጋግማ ሥዕሉን ሳመች።እምብዛም ነገሬ ሳትለኝና እህ! ብላ ሳታዳምጠኝ ተሰናብቻት ተመለስኩ።

ከሌላ ስድስት ወር በኋላ የወዲ ያነሽ ሁለት ዓመት ሞላት።

እሑድ ከሰዓት በኋላ ነበር፡፡ የዕለቱን ጋዜጣ እያነበብኩ እንግዳ መቀበያ
ክፍል ውስጥ ተቀምጬ ሳለሁ የውብነሽ አጠገቤ ተቀመጠች። የያዘችውን
የአማርኛ ሰዋሰው መጽሐፍ እንደተገለጠ አጭሯ ክብ ጠረጴዛ ላይ ዘረጋችው።

ዐይኔ ተወርውራ የጊዜ ተውሳከ ግሥ የሚለውን ርዕስ አየች። ለነገርና
ለወሬ ማነሣሻ ይሆነኝ ዘንድ «ይልቅስ የአኳኋንና የሁኔታን ተውሳከ ግሥ
አታጠኚም» ብዬ መጽሐፉ ውስጥ የማነበው ያለኝ ይመስል አገላብጬ
አስቀመጥኩት። «እኔ የጊዜ ተውሳከ ግሥ አልዘለቅ ብሎኛል። አንተ ደግሞ
ሌላውን ትለኛልሀ» አለችና እጄ ላይ የነበረውን ጋዜጣ ወስዳ የመጀመሪያን ገጽ አርእስቶች በለሆሳስ አነበበች፡፡

«ሥራ አለብሽ እንዴ የውቢ? ከሌለብሽ አንድ ቦታ ደረስ ብለን እንምጣ» ብዬ ጸጉሬን አሻሸሁት፡፡ ጋዜጣውን አጣጥፋ አስቀመጠችው:: «እሺ እንሂድ፡፡ ይህን ማታም ቢሆን ልፈጽመው እችላለሁ» ብላ ከንፈሯን በምላሷ እያራሰች።
«ምንም እንኳ ለጊዜው አሳዛኝ መስሎ እንደሚታይሽ ባውቅም የኋላ ኋላ
ግን ያስደስትሽ ይሆናል» ብዩ ኩራትን ለመግለጽ በሚያስችል ወፍራም ደርባባ
ድምፅ ተናገርኩ። ካንተ ጋር ከሆንኩ ምን ያሳዝነኛል? በመጨረሻ የሚያስደስተኝ
ነገር ሁሉ ደስ ይለኛል፡፡ እንሂድ ካልክ ልብሴን ልቀያይርና እንሂድ» ብላ ተነሣች፡፡ እንዲሁ ገባ እንዳለች ዘርፈጥ ብላ የተቀመጠችበት ቀሚሷ ከበስተኋላዋ
ልሙጥነቱ ጠፍቶ ወደ ልዩ ልዩ አቅጣጫ የተሰበጣጠረ ጭምድ መስመሮች
ሠርቷል። ልብሷን ለመቀያየር ወደ መኝታ ቤት ስትገባ እኔም ጸጉሬን ለማበጠር
ወደ ክፍሌ ገባሁ፡፡

የልብሴን መስተካከል በመስተዋት ከተመለከትኩ በኋላ ጸጉሬን በደረቁ
እበጥሬው ወጣሁ፡፡ ደረጃውን ወርጀ እንደ ጨረስኩ ደረሰችብኝ።

ምንም እንኳ ወዴት እንደምንሄድ ባታውቅም «የምንሔድበት ቦታ ብዙ
ሰዎች አለበት እንዴ?» ብላ ጠየቀችኝ፡፡ «ማንም የለም። የምንሄደው አንድ እሳዛኝ
ሰው ለማየት ነው» ብዬ አለባበስና አረማመዷን እያየሁ መንገድ ገባን፡፡ ደማም ወጣትነቷና እንስታዊ ውብ ቅርጺ ማራኪነት ሰጥቷታል፡፡ ፈገግ ስትል ፍልቅቅ የሚሉት ነጫጭ ውብ ጥርሶቿ ከደም ግባቷ ጋር የአተር አበባ አስመስለዋታል፡፡

እግረ መንገዳችንን ልዩ ልዩ የሚባሉ ነገሮች ገዛሁላት። ዐሥር ደቂቃ በማይሞላ ጊዜ ውስጥ በታክሲ ዕጓለ ማውታ ደረስን፡፡ ለመጀመሪያ ጊዜ ሴት
አስከትዩ በመሄዴ ያ ዘወትር ብቻዬን ስመላለስ የሚያየኝ ዘበኛ የውብነሽን
በማየቱ የመገረም ፈገግታ ታየበት።

አብዛኛውን ጊዜ ከቤቱ ታዛ አካባቢ ከብዙ ከልጆች ጋር ተቀምጦ ሲጫወት ከሩቁ የማውቀው በልብሱ ስለነበር ሜዳው መኻል ቆም እያልኩ የቢቶቹን የፊት ዙሪያ ተመለከትኩ፡፡ ብዙ ልጆች ጨዋታቸውንና ልፊያቸውን እየተዉ አዩን፡፡ ወደ መኝታ ክፍሉ ይዣት ገባሁ። እሱኑ ከሚያካክሉ ሁለት ልጆች ጋር ወለሉ ላይ ተቀምጦ እየተኮላተፈ ይጫወታል። ሁለቱ ልጆች መለስ ብለው ካዩን በኋላ ጨዋታቸውን ቀጠሉ፡፡ የእኔ ልጅ ዐይኖች ግን እኔ ላይ
ተተከሉ፡፡ ጎንበስ ብዪ አነሣሁት፡፡

አባባና እማማ የሚባሉ ቃላት የማያውቀው፣ የወላጅ ፍቅር ያልቀመሰው
ልጄ እንደ ወፍ ዘራሽ የመስክ አበባ ያምራል። ለምን ወደ ዕጓለ ማውታ እንደ
መጣች ግራ የገባት የውብነሽ በመጠኑ ደንገጥ አለች፡፡ ወደ እርስዋ ዞሬ ትከሻዋን
ቸብ ካደረግሁዋት በኋላ እስኪ ይህን ልጅ ተመልከችው የውብነሽ ቆንጆ ልጅ
አይደለም እንዴ? ብዬ ጠየቅኋት። እ..ብላ ዝም አለች።

ሰውነቷ በጥርጣሬና በሐሳብ የተጠመደ መሰለ፡ ድንገት ከእንቅልፏ ነቅታ ባጋጣሚ ያየችው ይመስል ሁለት እጆቿን ዘርግታ «እውይ እማምዬ ማማሩ! ደስ ማለቱ?» ብላ ከእጁ ላይ ወስዳ ታቀፈችው፡፡

በፊቱ ላይ አንዳችም ሌላ ለውጥ ሳይታይና ፈገግታው ሳይቀንስ ዝርግፍ
ብሉ ወደ እርሷ በመሄዱ በጣም ደስ አለኝ፡፡ እንዲያውም እዚያች ጠባብ ደረቷ
ላይ ልጥቅ አለ፡፡ ነገር ግን ልጄን ለመጀመሪያ ጊዜ ያቺ የማፈቅራትና
የምንሰፈሰፍላት የወዲያዬ ሳትሆን እኅቴ አቅፋው በማየቴ በፋይዳ የለሽ ጥላቻ
ተናደድኩ፡፡ ጉንጮቹን ሳም ሳም ካደረገች በኋላ ፊቷን ወደ እኔ መለስ አድርጋ
<<የማን ልጅ ነው ?» ብላ በጓጓ ስሜት ጠየቀችኝ። የምናገረው እውነተኛና ርግጠኛ እንዲመስል ለመመለስ የማሰላሰያ ጊዜ አልወሰድኩም፡፡ «አንቺ የማታውቂው አንድ ጓደኛ ነበረኝ፡፡ የዚህ ልጅ አባት ማለቴ ነው። ትዝ እይልሽም ይሆናል እንጂ እኛም ቤት አንድ ሁለት ቀን ያህል መጥቶ ነበር» ካልኩ በኋላ የነገሩን
ድምጥማጥ ይበልጥ ለማጥፋት «ነገር ግን ከአንድ ዓመት ከመንፈቅ በፊት
በድንገተኛ የመኪና አደጋ ሞቷል፡፡ ልጁ ግን ለጊዜው አሳዳጊ ዘመድ በማጣቱ
ይኸው እዚህ በምታይው ሁኔታ በማደግ ላይ ይገኛል፡፡ የዚህ ልጅ አባት በጣም
ግሩም ሰው ስለ ነበር እሱን በማሰብና ለልጁ በማዘን ብቻ አልፎ አልፎ ብቅ
እያልኩ እጠይቀዋለሁ፡፡ ጉልላትም አንዳንድ ቀን እየመጣ ያየዋል» ብዬ ዋሸኋት፡፡ግንባሩን ሁለት ጊዜ ያህል ስማ ውብ ዐይኖቹን ባንጸባራቂ ሸጋ ዐይኖቿ ትኩር ብላ ተመለከተቻቸው::

«ምነው አንተም እንዲህ የሚያምርና የሚያስጐመዥ ልጅ በነበረህ» ብላ
እንደ ወይን እሽት የሚያስጐመዡትን ጉንጮቹን ሳመቻቸው:: ንግግሯ ለጊዜው
ረግቶና በርዶ የቆየውን የሕሊናዬን ባሕር በብስጭት ማዕበል አረሰው፡፡

“ምናልባት ሚስት ባገባ ማስቴን በርግዝናዋ ወራት ከቤት አታባርሯት
እንደሆነ ነዋ እንዲህ ያለ ልጅ ማግኘት የሚቻለው» ብዩ በሽሙጥ መለስኩላት።
ድንገተኛው የንግግሬ ይዘት ፊቷን አስቀጨመው:: ልጁን ከሰጠችኝ በኋላ
አንገቷን ስብራ አቀረቀረች። ከጥቂት ዝምታ በኋላ ከወለሉ ላይ ቃላት
እየለቃቀመች ትናገር ይመስል ወለሉን እያየች «ያ ያለፈው ሁሉ ሌላ ጉዳይ
ነው፡፡ የማይገናኙ ነገሮች አታገናኝ እኔን ምን አድርጊ ትለኛለህ? አንተ ከእኔ
የበለጠ ብልህ መሆንህን ዐውቃለሁ አባታችን ቢሰማ ኖሮ በአንተና በእርሱ
መካከል ትልቅ ጠብና ማለቂያ የሌለው
👍4
#የተወጋ_ልብ


#ክፍል_አስራ_ስምንት


#ድርሰት_በትክክል_ገና


...ስድስት ወራት አለፉ። ጌትነት የስድስት ወር ደሞዙን በላ፡፡ በዚች አጭር ጊዜ ውስጥ ራሱን በብዙ ነገር ቀየረ። አዲስ ልብስም ገዛ፣ ዩኒቨርሲቲ በሶሻል ሳይንስ "አካውንቲንግ ዲፓርትመንት" ትምህርቱን
ጀመረ። በወር ከሚያገኘው ሁለት መቶ ብር ደመወዝ ላይ ለእናቱ ተቆራጭ አድርጎላት ለአባቱ የገባውን የአደራ ቃል ለማክበርና ትምህርቱን በሚገባ በመከታተል በመጀመሪያው ሰሚስተር ጥሩ ውጤት ለማስመዝገብ ቻለ። በዩኒቨርሲቲው ከፍተኛ ውጤት ያመጡ ተማሪዎች ስም ዝርዝር በሚለጠፍበት ሠሌዳ ላይ የጌትነትን ማንነት ለማያውቁት ሁሉ አስተዋወቀ። "እንኳ” ደስ አላችሁ!!" በሚለው ማስታወቂያ ስር ስማቸው ከተዘረዘረው ጥቂት ተማሪዎች መካከል ጌትነት መኩሪያ ግንባር ቀደሙ
ሆነ፡፡ በሁሉም የትምህርት ዓይነቶች "ኤ" በማገኘቱ ስሙ በግሬት ዲስቲንክሽን ሊስት ውስጥ ተካተተ፡፡ የክፍሉ ተማሪዎች “እሱ ማን ነው?" ብለው ውስጥ ለውስጥ ሲነጋገሩበት ከረሙ:: በኋላም እሱ አንገቱን የደፋው፣ እሱ ትህትና ያልጎደለው፣ እሱ ብቻውን ገብቶ ብቻውን የሚወጣው በመጨረሻ ወንበር ላይ የሚቀመጠው ያልጠበቁት ሰው ሆኖ
አገኙት፡፡ በአብዛኛዎቹ ዘንድ በአድናቆት መታየት ጀመረ። ከሁሉ የበለጠ ስለሱ ማንነት ለማወቅ የተጨነቀችው ግን አማረች ነበረች፡፡ አማረች በአንድ የግል ድርጅት ውስጥ በሂሳብ ሠራተኛነት ተቀጥራ የምትሰራ በትምህርቱ ጎበዝ የሆነ ስው የምትወድ ቆንጆ ልጅ ናት። ያንን ከፍተኛ ፉክክር ያለበትን የዩኒቨርሲቲ ህይወት ለመምራት ተማሪ እርስ በርሱ
ይፈላለጋል፡፡ በተለይ ጎበዝ ተማሪ አድኖ ለመያዝ ሩጫው ብዙ ነው። ለዚህ ነበር ያንን አመርቂ ውጤት አምጥቶ ለአካውንቲንግ የመጀመሪያ አመት የዲግሪ ተማሪዎች ቁንጮ የሆነውን “እንኳ” ደስ አለህ” የተባለውን የክፍሏን ተማሪ ማንነት ለማወቅ የተጣደፈችው። ብዙ ጊዜ አልወሰደባትም። አወቀችው፡፡አማረች የቀይ ዳማ ናት። ሰውነቷ ሞላ ቁመትዋ ዘለግ ያለ ፀጉርዋ እንደ ስንዴ ነዶ ጀርባዋ ላይ ዘፍ ያለ እንደ ስሟ
መልኳ የሚያምር፡፡ የመጀመሪያው ትምህርት ክፍለ ጊዜ ደርሷል። የዛ
ሬውን 'ሌክቸር የሚስጠው መምህር ዘግይቶ ነበር፡፡ አማረች ሆን ብላ ያንን ጎበዝ ተማሪ፣ ያንን ቁመቱ ዘንከት ያለ የሚስብ ልጅ ልትተዋወቀው ፈለገች፡፡ በቀጥታ ሄደችና ከአጠገቡ ባለው ባዶ ወንበር ላይ ዐይኖቿ” ተከለች።ሌሎቹ ተማሪዎች ደብተሮቻቸውን ገልጠው መምህራቸውን በመጠባበቅ ላይ ነበሩ፡፡
"ሰው አለው?" በጣቷ ባዶውን ቦታ እየጠቆመች በፈገግታ ተጥለቅልቃ
ጠየቀችው፡፡ ቀና ብሎ አያት። ደነገጠ፡፡

"የለው...እ? አለው!" ከሩቁ የሚጠላት ልጅ. በአብዛኛው መልኳ ሸዋዬን

የምትመስለው ልጅ.. ቀድሞውኑ ሲያያት ያልወደዳት ልጅ የምትቀመጥበትን የፊት ወንበር ትታ እሱ አጠገብ ከኋላ ለመቀመጥ መፈለጓ ድንገተኛ ሆኖበት መልሱን ለመስጠት ተደነጋገረው፡፡ የልጁ ሁኔታ አማረችን ገረማት። ሰው የሌለበትን ወንበር አለበት በማለት አሳፈራት። ማንም
እንደዚህ አሳፍሯት አያውቅም፡፡ እየሳቀችና እየተገላመጠች ወደ ቀድሞ
ቦታዋ ሹክክ ብላ ተመለሰች። "እሽ" ብላ አፍራ ምልስ ስትል አሳዘነችውና ተፀፅቶ ራሱን ወቀሰ፡፡ ለምን ያንን ቦታ እንደፈለገችው ገርሞት በዐይኖቹ ተከተላት።

የትምህርቱ ክፍለ ጊዜ አብቅቶ መውጣት ሲጀምሩ አማረች ቀስ ብላ ጭለማውን ተገን አድርጋ የጌትነትን እንቅስቃሴ ትከታተል ነበር። የዩኒቨርሲቲውን ምድረ ግቢ እንደለቀቀ ግራ ቀኝ ሳይል ታክሲውን ይዞ በረረ፡፡ በሚቀጥለውም በወዲያኛው ቀንም ተከታተለችው። ብቻውን እየወጣ ታክሲውን ተሳፍሮ ይከንፋል። ባደረገችው ተደጋጋሚ ጥናት የሴትም ሆነ የወንድ ጓደኛ እንደሌለው አረጋገጠች። አማረች በምቾት ያደገች የሚያምር ተክለ ቁመና ያላት የጠበቃው የአቶ በልሁ ወዳጄነህ
የመጀመሪያ ልጅ ናት። ከሁሉ የበለጠ የሚስበው ውብ ተክለ ቁመናዋ ነው። አነስ አነስ ያሉት ሳቂታ ዐይኖቿ ጉርድ ያለው አፍንጫዋ ከትንሿ ክብ ፊቷ ጋር በህብረት ሲታዩ በትልቅ ሰውነት ላይ የተቀመጠ የህፃን ልጅ ፊት ያስመስላታል፡፡ አማረች ከቁንጅናዋ ይልቅ የደስ ደሷ ከሩቁ ይጣራል። ጉንጮቿ እንጆሪ ይመስላሉ፡፡ ጌትነት እንደዚያ ይጥላት እንጂ ብዙዎቹ ወንዶች ሲያይዋት ጉሮሯቸው እስከሚጮህ ድረስ ምራቃቸውን ይውጣሉ፡፡ አቤት በተለይ ሱሪ ለብሳ የመጣች ዕለት! በዐይኖቻቸው
ሱሪዋን አውልቀው ያንን የሚገላበጥ ዳሌዋን በምናብ እየቃኙ በስሜት
ከወንድነታቸው ጋር ሲታገሉ ይውላሉ። ያያት ወንድ ሁሉ ቢመኛትም አማረች ግን ቁጥብ ነበረች፡፡ በቀላሉ የምትገኝ
አወጣ የተባለ ወንድ ሎተሪ እንደወጣለት ተደርጎ የሚጋነንበት ሁኔታ ነበር፡፡ ሲበዛ ፈታኝ ሰው ነች። ይሄ ሁሉነትዋ ግን በጌትነት ዘንድ ዋጋ አጥቷል። ሰው መስላ አልታየችውም። በሸዋዬነት ውስጥ የበቀለች የአንድ ሳንቲም ሁለት ገፅታዎች ሲል ደምድሟል።ይቺ በመማሯ ሽዋዬ ደግሞ በማይምነቷ መካከል ያለ ልዩነት እንጂ በሴትነት ባህሪያቸው አንድ ናቸው ብሎ የራሱን ድምዳሜ ሰጥቷል። በመልክ በጣም ይቀራረባሉ። በሌላ ፀባያቸውም ያው ናቸው የሚል እምነት ነው ያደረበት፡፡ አማረች አብዛኛው የሀሳብ ክፍሏን ለጌትነት አሳልፋ ሰጠች። ወደ ክፍል ሲገባና ከክፍል ሲወጣ ደጋግማ በስውር ተከታተለችው። ብቸኛ መሆኑን ካረጋገጠች በኋላ "ምን ችግር ቢኖርበት ይሆን?" ስትል ራሷን ጠየቀች፡፡ ቀርባ ልታነጋግረውና ስለማንነቱ በሰፊው ለማወቅ ተንስፈሰፈች። ናቅ ስላደረጋት ነው መስል ምን ሲደረግ? የሚል እልህ ተናነቃት። ሌሎች ለሷ ያላቸውን ግምት በሚገባ ታውቃለች። ታዲያ ጌትነት
የምን ትዕቢት ነው? በትምህርቱ ጎበዝ ስለሆነ? መልከ መልካም ስለሆነ?
እኛ ስላለችው? ወይስ ሰው መስዬ ስላልታየሁት? ራሷን በብዙ ጥያቄዎች ዙሪያ በጭንቀት እንድታሽከረክር አደረጋት። ልቧ ዋተተ። እሱ እሷን በሚሸሽበት፣ በሚጠላበት ልክ እሷ ደግሞ እሱን ለመተዋወቅ ልቧ
ሽፈተ።

ይቀጥላል
👍1
#ያልታበሱ_እንባዎች


#ክፍል_አስራ_ስምንት


#ድርሰት_በአሰፋ_በቀለ_ገየሱስ


....በማግስቱ ጠዋት ዘመድ ወዳጁን ሞት የነጠቀው፣ የቆሰለበትና ገና የሆነውን ነገር በውል ያላወቀ የዲላ ነዋሪ ሁሉ ማልዶ ተነሳ፡፡ ማልዶ ወደ
መናኸሪያ ተመመ። ማልዶ ጉዞ ጀመረ፡፡ የተሽከርካሪ ችግር አልገጠመውም። በዲላ ዙሪያ ባሉ መዳረሻዎች ይሰሩ የነበሩ በርካታ ተሸከርካሪዎች ሁሉ ለዕለቱ አስቸኳይ ጉዞ ተመድበዋል። መሄድ የፈለገ ሁሉ ተሳፍሯል፡፡ ሽኝቱ በለቅሶ የተደበላለቀ ነበር፡፡
በልሁም አንዱ ተጓዥ ነበርና በታፈሡ በሔዋንና በርዕድ እየየ እና ጩኸት ተሽኘ፡፡

ገዞው ከወትሮው ፍፁም የተለየ ነበር። ሁሉም ሀዘንተኛ በመሆኑ የተኳረፈ ይመስላል ፀጥ ረጭ ባለ ሁኔታ ይጓዛል፡፡ አብዛኛው ሰው ጋቢና ነጠላ እንዲሁም
ጥቋቁር ልብስ ለብሷል፡፡ የፍተሻ ኬላዎችም ረግበዋል። በየመኪናው ውስጥ ገባ
ብለው ወጣ ከማለት ውጪ ተጓዡን ከመኪና ላይ አስወርደው ሁሉን ነገር በመበርበር ያጠፉት ጊዜ አልነበረም፡፡ ሾፌሮችም የጫኑትን ሕዝብ የውስጥ ስሜት
ያውቁ ነበርና ለከሰል ግዢ የትም ቦታ አልቆመም፡፡ እየተከታተሉ እንዳንዴም እየተሽቀዳደሙ በመብረር እረፋዱ አራት ሠዓት ተኩል ላይ ከዚያ አደጋ የደረሰበት
ቦታ ደረሱ፤ ከዝዋይ ከተማ በስተደቡብ በአሥራ አምስት ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ፡፡
ያ ቦታ ለአየው ሁሉ ይሰቀጥጣል። ወጭ ወራጅ ሁሉ ከሚጓዝበት መኪና ላይ እየ'ወረደ ያለቅስበታል። የተጋጩት መኪኖች ራሳቸው እንደ ሰው ያሳዝናሉ፡፡
ከሞጆ ወደ ሻሸመኔ ስትበር የነበረችው ሊዮንቺን ለዓመታት ስትረገጥ የኖረች ጣሳ መስላ ተጨራምታለኝ፡፡ ሁሉም ወንበሮቿ ሜዳ ላይ እንደ ቆሉ ተበትነዋል። ከዲላ ወደ አዲስ አበባ ይሄድ የነበረው አውቶብስ ደግሞ ፊት ለፊቱ ተቦድሶ ከግራ በኩል ያለው ጎኑ እስከ ኋላ ድረስ ከውጭ ወደ ውስጥ ተጠርምሷል
ከሎንቺኗ በአጠቃላይ፣ እንዲሁም በአውቶቡሰ ግራ በአል ከተቀመጠ ተሳፋሪ መሀል ሰው
ይተርፋል ብሎ ለመገመት እጅግ ያስቸግራል።
መኪኖቹን ተወት አድርጎ የተጋጩበትን አካባቢ መሬት ሲያዩት ደግሞ የባሰ አንጀት ያላውሳል። የአደጋ ሰለባዎች ደም ቦይ ሰርቶ ተንኳሉበታል። ከፈረሱ
ጭንቅላቶች የተበተነ አንጎልን በያለበት ተረጭቶ ዝንቦች ሰፍረውበታል፡፡ የተለያየ
ቅርጽ' ቀለምና መጠን ያላቸው የወንዶችም የሴቶችም ጫማዎች ሚዳው ላይ ተበታትነዋል፡፡ ደም
የተጠረገባቸው ጨርቆችና ስስ ወረቀቶች በየቦታው ተበታትነዋል፡፡
በዚያ ላይ ያ የዲላ ተሳፋሪ ሁሉ ከቦታው ደርሶ ከየመኪናው
እየወረደ፤ እንባ ሲራጭበት ያ ቦታ የባሰውነ መዓት ወረደበት።

በልሁ ትናንት ጠዋት አስቻለውን ሲሸኝ የተቀመጠበትን ቦታ አይቷልና ከመኪና እንደ ወረደ በቀጥታ በፊት በር በኩል ወደ አውቶቡሱ ሮጠ፡፡ በዚያ ቦታ
ላይ ያየው ሁኔታ መሬት ላይ ካለው የባሰ ነው፤ ደም ተጋግርበታል። የሞተሩ ክዳን
ወደ ኋላ ተጨራምቶ ወደ ወንበሩ መደገፊያ በመጠጋቱ ከዚያ ውስጥ ሰው ከነነፍሱ ሊወጣ ይችላል ብሎ መገመት ያስቸግራል። በልሁ በሁለት እጆቹ ራሱን ይዞ በለቅሶ
ሲንሰቀሰቅ ከቆየ በኋላ ድንገት የአስቻለውን የአካል ቁራጭ የሚያገኝ መስሎት ጎንበስ ብሎ በተጨራመተው የሞተር ክዳን ሥር ሲመለከት የአስቻለውን የቀኝ
እግር ቢጫ ጫማ አያት።

ድምጹን ከፍ እድርጎ «ወየው ወየው ወየው ወየው..» ካለ በኋላ
በመኪናው በር በኩል አንገቱን መጣ አድርጎ ጎበዝ ጎበዝ ጎበዝ ድረሱልኝ ጎበዝ ድረሱልኝ!» ሲል ዕርዳታ ጩኸት አሰማ፡፡ በአካባባው የነበሩ ሰዎች ሰምተውት ኖሮ ጠጋ ጠጋ ብለው ምነው? ምነው?» ሲሉት በልሁ እያለቀሰ «የወንድሜ እግር
እዚህ ቀርቷል! ኑ አውጡልኝ! ቶሎ በሉልኝ!» አላቸው።
ሰዎቹ ወደመኪናው ውስጥ ገብተው በልሁ ወደ ጠቆማቸው ቦታ ጎንበስ እያሉ ሲያዩ፡ እውነትም ቢጫ ነገር ታያቸው። ያን የሞተር ክዳን እንደ ምንም ተረዳድተው ወደ ፊት ከመለሱ በኋላ ከመኪና ስፖንዳ ጋር ተጣብቃ የነበረችውን
ጫማ ፈልቀቁኝው በማውጣት ለበልሁ ሰጡት::
በልሁ ያቺን ቢጫ ጫማ ይዞ ከመኪናው ላይ ወረደና ጫማዋን ወደ ላይ ከፍ፡ አድርጎ ለሕዝብ እያሳየ «እዩት ወገኖቼ! እዩዋት የወንድሜን ጫማ! የሆነውን
ነገር በዚህ ገምቱ! ወንድሜ ሞቷል! ወንድሜ ሞቷል! ...» እያለ ይጮህ ጀመር።
አስቸለህኑን የማያውቅ ሁሉ የሆነውን ነገር እየገመተ እንባውን አፈሰስ፡፡

ወዲያው ደግሞ ጥቂት ሰዎች በስቲሽን ዋገን ቶዮታ መኪና አስከሬን ጭነው ከቦታው ደረሱ፤ የጠይሟ ልጃገረድ አስከሬን ኗሯል፡፡ ህዝቡ ሁሉ ግርር
ብሎ፤ ኸደ መኪናዋ ሲሮጥ
በልሁም አብሮ ተጠጋ። ሌላው ሰው ከኋላ ከተሳፈሩት ሰዎች ጋር ሲነጋገር በልሁ ግን የልጅቷን አባት ጋቢና ውስጥ ሆኖ ሲያለቅስ
አየውና ጠጋ ብሎ፡
“አቶ ዘመድኩን!» ሲል ጠራው እንባውን በጉንጩ ላይ እያፈሰስ፡፡
“እንዲህ ሆንኩልህ በልሁ! የድሃ ልጄን ጉድ ተሰራሁ! ስንት ሆኔ ያሳደኳትን የበኩር ልጁን ወይኔ ወይኔ በማለት እያለቀሰ ሀዘኑን ለበልሁ ገለፀ።
«አስክሪን የት አገኘህ?» ሲል ጠየቀው በልሁ አሁንም እያለቀሰ፡፡
ከናዝሪት ውስቢታል ነው የሰጡኝ በልሁ::
«ምናልባት የልጅህን አስከሬን ስታወጣ ልብ ያልከው ነገር ይኖር ይሆን?» ሲል በልሁ ጠየቀው። ዘመድኩን የበልሁ ፍላጎት ገብቶታል።
«ምኑ ይለያል ብለሀ በልሁ? የሬሳ መዓት ተከምሯል፡፡ በያ ላይ እንዳንዱ ምነም ምነም አያስታውቅ፣ ስውነቱ ሁሉ ፈራርሷል። ብታይ እኮ ጉድ ነው
የሚታየው::» አለው ፊቱን በመሀረብ ሞዥቅ አድርጎ እየጠረንገ።
በልሁ አንጀቱ ብጥስ ያለ መስለው፡፡ መቆም አቃተውና ከመኪናዋ ራቅ ብሎ ሜዳው ላይ ቁጭ አለ፡፡ ያቺን የእስቻለውን ጫማ ከፊቱ አስቀምጦ በእግሮች
መሀል እጎንብሶ እያየ ያለቅስ ጀመር፡፡
የጠይሟን ልጃገረድ እስከሬን የጫነችው መኪና ወደ ዲላ ጉዞ ስትጀምር ወደ ናዝሬት የሚሄዱ አዘንተኞችን የጫኑ መኪኖች ሾፌሮችም ወደየመኪናው እንዲገባና ጉዞው እንዲቀጥል ይለምኑ ጀመር። በዚያ ሰዓት ስለ
አደጋው ያጠኑ የነበሩ የትራፊክ ፖሊሶችም መንገድ በማስለቀቅ ሰበብ ሕዝቡ እንዲሳፈር ወደ መኪናው መግፋት ጀመሩ። በልሁንም ደጋግፈው በማንሳት ወደ መቀመጫው ወስደው አስቀመጡት፡፡

ጉዞው ተጀመረ። ማታ እራት በወጉ፣ ጠዋትም ቁርስ ያልበላ ሀዘንተኛ ሁሉ ዝዋይ ሲደርስ እህል ልቅመስ አላለም፡፡ ሾፌሮቹ እንኳ አልከጀሉም፡፡ ዝም ብለው አለፉ፡፡ መቂና አለም ጤና እንዲሁም ቆቃ ከተሞች ታለፉ፡፡ ህዝቡ ደግሞ
አደጋው በደረሰበት ቦታ ላይ አልቅሶ አልቅሶ ደክሞት ስለነበር ጉዞውም ፀጥ ረጭ ያለ ሆነ፡፡ በአብዛኛው የተሳፋሪ እምነት የናዝሬት ሃይለ ማርያም ማሞ ሆስፒታል የአስክሬን መልቀምያ ወይም የቁስለኛ መገኛ ነውና ሁኔታዎች መቀየር የጀመሩት
ሞጆ ከተማ ታልፋ ወደ ናዝሬት ማቆልቆል ሲጀምር ነው፡፡ በተለይ ከናዝሬት መዳረሻ የመጨረሻዋ ዳገት ላይ ሲደርስ ለጥ ባለ ሜዳ ላይ የተቆረቆረችውን የናዝሬት ከተማ ሲያይ ሁሉም ተሳፋሪ ያለቅስ ጀመር፡፡ ከተማ ውስጥ ሲገባ ደግሞ ጫጫታና ኡአታ። ሆስፒታሉ በር ላይ ሲደርስ ደግሞ አገር ቀለጠ፡፡
ሕዝቡ ከየመኪኖቹ ላይ እየተሽቀዳደመ በመውረድ እያለቀሰና እየጮኸ ከሆስፒታሉ ቅጥር ግቢ ውስጥ ሲገባ ወዴት አቅጣጫ መሄድ እንደነበረበት
👍5
#ምንትዋብ


#ክፍል_አስራ_ስምንት


#ድርሰት_በሕይወት_ተፈራ

“ሺሕ ዓመት ንገሥ።"

ምንትዋብ፣ አፄ በካፋ ወደ መሠሪ እንድትመጣ ሲልኩባት፣ ሕይወቷ
ዳግም ተለወጠ። ለጥቂት ቀናት መሠሪ ሱባዔ ገብተው ስለነበር
ጨርሰው ነው ብላ አስባለች። ከእናቷና ከአያቷ ጋር መሠሪ ስትደርስ፣የበካፋ ታማኝ እልፍኝ አስከልካዮች ቴዎድሮስ፣ ገላስዮስና ድንጉዜ ዐይኖቻቸው ደም መስለዋል። እጅ ነስተዋት ስትገባ መሠሪ ከብዶታል፤
ጨላልሟል። ከወትሮው ጠባብ ሆኖባታል።

አፄ በካፋ ከተኙበት ኣልጋ ራስጌ የነፍስ አባታቸው አባ ዐደራ
መስቀላቸውን ይዘው ቆመዋል። ኒቆላዎስ ከንጉሠ ነገሥቱ ግርጌ
አቀርቅሮ ቆሟል። ምንትዋብ ርምጃዋን ገታ አድርጋ ክፍሉንም
ሰዎቹንም ቃኘች።

ነገሩ አላምር አላት። መንፈሷ ተረበሸ። ሱባዔ ላይ የነበሩት ባሏ ምን እንደደረሰባቸው መገመት አቃታት። ወደ አልጋቸው መራመድ ፈልጋ እግሮቿ አልታዘዝ አሏት፤ ትንፋሽ አጠራት። ልቧ ደረቷን ሲደልቅ እንደ ማጥወልወል አላት። ሐውልት ይመስል ደርቃ ቀረች። ዐይኗ ኒቆላዎስን ኣልፎ ንጉሠ ነገሥቱ ላይ ሲያርፍ፣ ፊታቸው ተሸፍኗል።

ዕለቱ ማክሰኞ፣ ቀኑ መስከረም አስራ ስድስት ዓመተ ምህረቱ 1723 ነው። እኒያ ቅኔ የሚቀኙት፣ መንፈሳዊ መጻሕፍትን የሚፈትሹት፣ አደን የሚወዱት፣ ለሃገራቸው ፊደላት ጥብቅና ቆመው፣ “ፊደል አሳስቶ የጻፈ
እጁ ይቆረጣል” ብለው አዋጅ የጣሉት፣ ሥነ-ጥበብ እንዲዳብር፣ ቃላት እንዲበለፅጉ የጣሩት፣ በወባ ንዳድ ርደው እንደተራ ሰው ባላባት ቤት መደብ ላይ የተኙት፣ ላይ ታች እያሉ ያመጸውን ያስገበሩት፣ ያጠፋውን አይቀጡ ቅጣት የቀጡት፣ እንደ ቀደምት ነገሥታት የሃይማኖት ክርክር
ያከራከሩትና አሻራቸውን ለመተው የራሳቸውን ግንብ የገነቡት አፄ
በካፋ በነገሠ በዘጠኝ ዓመት ከዐራት ወራቸው፣ ምንትዋብን ባገቡ በሰባት ዓመታቸውና በተወለዱ በሰላሳ ሰባት ዓመታቸው ሕይወታቸው
አልፏል።

“ምንድርነው? ጃንሆይ ምን ሁነዋል?” አለች፣ ምንትዋብ፣ ድምጾ ይርበተበታል ።
ተጠጋቻቸውና ቡሉኮውን ከፊታቸው ላይ ገለጥ አደረገችው።አፍንጫቸው ጫፍ ላይ ደም አየች፤ መላ ሰውነቷ ራደ። ኒቆላዎስ ላይ አፈጠጠች።

“ድንገት ነው የሆነው። ባፍ ባፍንጫቸው ደም ፈሰሰ... ምንም ያህል አልቆዩ ዐረፉ” አላት።

ራሷን በሁለት እጆቿ ይዛ “ኡኡኡኡ...” አለች። እናቷና አያቷ
ፈጠን ብለው ግራና ቀኝ ደገፏት።

“ምነው ሳትነግሩኝ? ስለምንስ ከፋችሁብኝ?” እያለች ጮኸች።
መሬት ላይ ተንከባለለች።

ያን ጊዜ እናቷና አያቷ አብረዋት ጮሁ። እንደ እሷ መሬት
ላይ ተንከባለሉ። መሠሪ ጩኸት በጩኸት ሆነ። ዋይታ በረከተ።
ምንትዋብ ለያዥ አስቸገረች። እነግራዝማች ኒቆላዎስ ተጨነቁ፡
ለቅሶው እንዳይሰማ። የቤተመንግሥት ባለሟሎች እንኳን እንዲሰሙ አልተፈለገም።

ምንትዋብ የምትሆነው ጠፋት። ከቶውንም የደረሰውን ማመን
አቃታት። አጎንብሳ፣ “ወዮ እኔ! ይብላኝ ለኔ” እያለች እንባዋን አዘራች።ኒቆላዎስና አባ ዐደራ ግራና ቀኝ እጆቿን ይዘው እንድትቀመጥ ግድግዳ ተጠግቶ ወደ ተቀመጠ ወንበር ሊወስዷት ሞከሩ።

“ተዉኝ... ተዉኝ! ለባሌ ላልቅስ።
ተዉኝ!” እያለች እሪ አለች።

“እቴጌ ባክዎ ለቅሶዎ እንዳይሰማ” አሏት፣ አባ ዐደራ።

“ይሰማ ይሰማ! አገር ይስማ! እኔ አለባል ልዤ አላባት መቅረታችንን...አገር ይስማ... ወዮ እኔ...ወዮ ልዢ ።”

እነኒቆላዎስ እንደ ምንም አባብለው አስቀመጧት። አንዴ ንጉሠ ነገሥቱ የተኙበትን አልጋ፣ ሌላ ጊዜ ደግሞ ጣራውን ደግሞም ወለሉን እያየች እንባዋ ረገፈ። ሐዘኗ መሪር ሆነ። የደረሰባትን ድንገተኛ ሐዘን
ጫንቃዋ መቋቋም የሚችል አልመስል አላት። ዓለም አስፈሪ ቦታ ሆነችባት። ሕይወቷ ላይ የሐዘን ጥላ አጠላችበት። የመኖር ተስፋዋን ሸረሽረችው። ትናንት ማሾ እያበራች ፈለጓን የተከተለችው መሬትም
ድንገት ጨለመችባት።

አልጋ ባልጋ የመጣው የሕይወቷ መንገድ ፍጻሜው የተቃረበ
መሰላት።

እንደገና ጩኸት ጀመረች። እነኒቆላዎስ ተደናገጡ። የእሷም
ሆነ የእናቷና የአያቷ ጩኸት እንዳይሰማ ፈሩ፤ ለማባበል ሞከሩ፤ አልሆነላቸውም። ምንትዋብን ብዙ ኃላፊነት እንደሚጠብቃት ኒቆላዎስ
ለማስረዳት ቢሞክር አልሰማ አለችው።

“ባሌ ኸሞቱ ገዳም ገብቸ መመንኮስ አለብኝ” አለችው።
እንባዋ ደረቷ ላይ ይወርዳል። ያቺ ፀዳል የመሰለች ሴት ፊቷ ድንገት
ጨለማ ለብሷል። ከመቅጽበት ዕድሜዋ ላይ ዓመታት የተጨመሩ
መስለዋል። ከዐይኗም ከአፍንጫዋም የሚወርደው ፈሳሽ አልቃሻ ሕፃን ልጅ አስመስሏታል።

ኒቆላዎስና አባ ዐደራ ተረበሹ። እናቷና አያቷ ለቅሷቸውን አቋርጠው በድንጋጤ ተመለከቷት።

“አዎ... ኸዝኸ በኋላ ምን ዓለም አለኝ? እኔም እንደ ባለቤቴ መሬት
እስትገባ ዓለሜ ምናኔ ነው። እሳቸው ሙተው እኔ እንዴት ባለም
ኖራለሁ? ልዤን ይዤ ኸዳለሁ” እያለች ጮኸች።

ኒቆላዎስ፣ “የለም የለም፤ እኼማ አይሆንም” አላት፣ ተጠግቷት።
“ደሞስ ምናኔ ማን ያደርስሻል? የጃንሆይ ጠላቶች ወይም ወህኒ
አምባ ያሉ ደጋፊዎች ምንገድ ላይ ጠብቀው አንቺንም ልዥሽንም
ይገድሏችኋል። ባይገድሏችሁ ስንኳ መውጫና መውረጃ የሌለው ወህኒ አምባ ወስደው ያስሯችኋል። ገዳም ብትገቢም ጃንሆይ ቅባት ሃይማኖት
ተከታይ ነበሩ ተብለው ስለሚጠረጠሩ እዚያ ብዙ የተዋሕዶ መነኩሴ ጠላቶች አሏቸው፤ ይጣሉሻል” አላት።

እሷ ግን፣ “በቁስቋሟ ተዉኝ! ተዉኝ” እያለች እጆቿን እያርገበገበች ተማጸነቻቸው።

ያን ጊዜ አባ ዐደራ፣ “እቴጌ መቸም መቀበል እንጂ ምን ማረግ ይቻላል? ኸሞት ሚቀር የለ። አሁን እርስዎ እንደዝኸ ሲሆኑ ሳንዘጋጅ የጃንሆይ መሞት የተሰማ እንደሁ ሁከት ይነሳል። ወህኒ ያሉትም እግረ ሙቃቸውን ፈተው ይመጣሉ። ንጉሥ ሞተ ሲባል ሚሆነውን እናውቃለን። ባክዎ ይጠንክሩልን” እያሉ ተለማመኗት።

ዮልያናም፣ “የኔ ልዥ! ባክሽ ጠንክሪ። እንደዝህ መሆን ደግ ማዶል” እያሉ እንባዋን በነጠላቸው ጠራረጉላት፣ የራሳቸውን ለመግታት
እየታገሉ።

“ልጄ በጡቴ ይዤሻለሁ! በኢያሱ ይዠሻለሁ! በምትወጃት በቁስቋም ማርያም ይዠሻለሁ! በምትወጃቸው ባባትሽ አጥንት ይሻለሁ በርቺልኝ” እያሉ እንኰዬም ሙሾ እንደሚያወርዱ ሁሉ እጃቸውን ወደ ኋላ አድርገው እንባቸውን እያዘሩ ለመኗት።

እሷ ግን እንባዋን መግታት አቃታት፤ አልጽናና አለች።

ኒቆላዎስ አንዴ እንድታዳምጠው ለምኗት የንጉሠ ነገሥቱን ኑዛዜ
ቃል በቃል ነገራት።

“ምን እንደተሰማቸው አላወቅሁም ብቻ እኔን አስጠሩኝ። ኒቆላዎስ...
ዐደራ ምልህ ልዤን... አሉኝ፣ ድምጣቸው እየተቆራረጠ። ልዤን
ኢያሱን እንድታነግሥልኝ። ለነገሥታት ሚደረገውን ሥርዐት ሁሉ... ቅባዓ ንጉሡንም ዘውዱንም... አርገህ እንዲነግሥልኝ። እናቱ ምንትዋብ
ብልህ ናት ትርዳው፤ ኸጎኑ ትሁን። እሷ አገር መምራትና... ማስተዳደር
ትችላለች። አርቆ አስተዋይና እዝጊሃር የባረካት ሰው ናት። አገሬን... አገሬን ኸልዣችን ጋር ሁና፣ ተባህር እስተ ባህር ታስተዳድር። አገሬ.. ምንም ዓይነት በደል እንዳይፈጠምባት። እኔ የዠመርሁትን ሁሉ. አጠናክረሽ ቀጥይ፤ በዐጸደ ነፍስ ኹኜም አልለይሽም በልልኝ። ሁላችሁም ቃሌን ንገሩልኝ…. ዐደራ” ብለው አንቺን እንድንጠራላቸው
ሲጠይቁ፤ ደም ባፍ ባፍንጫቸው ያለማቋረጥ ወረደ። ግዝየም አላገኙ ነፍሳቸው ከሥጋቸው ተለየች።”

ምንትዋብ፣ ተናግሮ ሲጨርስ ሳግ እየተናነቃት ጣሪያውን፣
ግድግዳውን፣ ወለሉን፣ ሁሉንም በየተራ ተመለከተች። እነሱ ምን
እያሰበች እንደሆነ መገመት አቃታቸው። አንዴ እርስ በእርስ እየተያዩ ሌላ ጊዜ እሷን እያዩ ከአፉ የሚወጣውን ለመስማት ተጠባበቁ።
👍111
#ትኩሳት


#ክፍል_አስራ_ስምንት


#በስብሐት_ገብረ_እግዚአብሔር

ጥሪ
የሳጥናኤል ኮከብ

የሴሰኝነት ጥሪ
ሲልቪ

እኔና ሲልቪ ለሁለተኛ ጊዜ ወደ ፓሪስ ተጓዝን። በሷ መሪነት
ከፓሪስ ጋር ይበልጥ ተዋወቅኩ። በሲልቪ አስተማሪነት ከቅናት ጋር
ይበልጥ ተዋወቅኩ፡፡ ራሴንም ይበልጥ አወቅኩ ፓሪስ በገባን በሁለት ቀናችን፣ እንደ ልማዷ አንድ ደስ የሚላት ጎረምሳ አየችና አጣድፋ ወደ ሆቴላችን ወሰደችኝ፡፡ መብራቱን አጠፋች፡፡ እንደ “ልማዷ በኔ ገላ ጎረምሳውን ተደሰተችበት፣
አቃሰተች፣ ነገሩ ሊያልቅ ሲል ጮኸች። ተኛን፡፡ ያን ጊዜ እኔም
እሷም አላወቅነውም እንጂ፣ ከኔ ጋር እንዲህ ስትሆንና ስታደርግ
የመጨረሻ ጊዜዋ ነበር ነቃሁ። ጭለማ ውስጥ ነኝ። ምን እንደቀሰቀሰኝ እንጃ:: ከጎኔ
ተንቀሳቀሰች፡፡ በእንቅልፍ ልቧ «“Non! Non! Non!" እያለች
እየተጨነቀች ተፈራገጠች። በጣም የሚያስፈራ ህልም መሆን
አለበት። እየቀሰቀስኳት
«አይዞሽ አይዞሽ፣ ከኔ ጋር ነሽ» አልኳት ራሷን እየደባበስኩ።
በሀይል እየተነፈሰች ተጠጋችኝና
«አንድ ነገር አስደነገጠኝ፡፡ መብራቱን አብራልኝ አለችኝ
አበራሁት። አይኔ ብርሀኑን ከለመደው በኋላ ታየችኝ፡፡ ጥቁር
ረዣዥም ፀጉሯ ጉንጭና አንገቷ ላይ ተጠምጥሟል፣ተለጣጥፏል። ግምባሯ ላይ ላቡ ያብለጨልጫል፡ ጠረግኩላት፣
ፀጉሯን ወደ ኋላዋ ሰበሰብኩሳት
ውሀ» አለችኝ፡፡ ራስጌ ካለው ጠርሙስ አጠጣሁዋት
«ደህና ነሽ?» ስላት፣ ሳቅ ብላ
«አጥፋው» አለችኝ። አጠፋሁት፣ አቀፍኳት
«ቅዠት ነበር፡፡ ኮሙኒስቶች የኢራንን ሻህ መንገድ ላይ
አግኝተውት በጩቤ ሲገድሉት አየሁ፡፡ በኋላ ግን ባህራም ሆነ።
«አይዞሽ ነቅተሻል፡ አይዞሽ» እያልኩ እጄን ጀርባዋ ላይ
ሳንሸራትት ትንሽ ከቆየሁ በኋላ
Tu es plutôt une mére Française qu' un sauvage Africain"
አለችኝ («ፈረንሳዊት እናት ነህ እንጂ አፍሪካዊ አረመኔ
አይደለህም ኮ») ሁለታችንም በሳቅ መንፈርፈር ጀመርን። ታድያ'ኮ ያን ያህል የሚያስቅ አልነበረም፤ ያን ጊዜ መሳቅ ስላስፈለገን ነው
እንጂ፡፡ እየተጠመጠመችብኝ፣ ደስታ ባፈነው ድምፅ
«መኖር እንዴት ጥሩ ነው!» አለችኝ
ካንቺ ጋር ሲሆኑማ!»
የኔ ካስትሮ፣ ይልቅ ካንተ ጋር ሲሆኑ ነው እንጂ፡፡»
እቅፍ አድርጌ ጉንጯን ሳምኳት። በጭለማው ላዬ ላይ ወጣች፡
እንደምትወደው ጀርባዋንና አንገቷን እያሻሸሁ
«ምን ይሰማሻል?» አልኳት
እንደምትወደኝ ይሰማኛል»
«አውቀሻል»
«የተለየ ስጦታህ ምን እንደሆነ ልንገርህ?»
«ምንድነው?»
«የሰላም
ተሰጥዎ ነው ያለህ፡፡ ካንተ ጋር ስሆን ሰላም ይሰማኛል። ካንተ ጋር ስሆን ፀፀትና ንስሀ አያስፈልገኝም፡፡»
«ፀፀትና ንስሀ?»
በተለወጠ ድምፅ
«ቅድም ስለበደልኩህ ገላህን ለጋራ ጥቅማችን ሳይሆን ለግል
ደስታዬ ስላዋልኩት»
ፀፀት ሊጀምራት እንደሆነ ገባኝ፡ አሳዘነችኝ
«የኔ ቆንጆ፡ ቂል አትሁኚ። አንቺ ገላሽን እንድደሰትበት
ትሰጪኝ የለ?» አልኳት
«አዎን»
«ታድያ እኔ ገላዬን እንድትደሰቺበት ብሰጥሽ ምናለበት?»
«ከዚያ ይለያላ»
«አስር ጊዜ ልዩ ይሁን። በናንተ አገር ፍቅር ማለት ምንድነው?
መስጠትና መቀበል አይደለም?»
«ነው»
«ታድያ ገላዬን ብሰጥሽና ተቀብለሽ ብትደሰቺበት ምን ፀፀት
ያስፈልገዋል? እኛ አገር መስጠት ማለት መስጠት ነው። ገላዬን
ከሰጠሁሽ የራስሽ ሆነ ማለት ነው፡፡ የራስሽ ከሆነ ደሞ የፈለግሽውን ልታረጊበት ትችያለሽ ማለት ነው።
«እንደሱ ሆኖ ነው እሚታይህ?»
«ነው እንጂ»
«እንዴት ጥሩ ነህ! እኔ ግን እንዴት መጥፎ ነኝ!»
እንዴት?
«ውሸታም ነኛ!»
«ውሸታም?»
«አዎን፡፡ ለምሳሌ፣ ያን ጊዜ ስትጠይቀኝ የሌላ ሰው ገላ
እያቀፍሽ በሰውየው ገላ ከኔ ጋር ተኝተሽ ታውቂያለሽ ወይ?”
አላልከኝም? እኔ ምን አልኩህ? »
«በጭራሽ አድርጌው አላውቅም አልሽኝ»
«አዎን። ግን ውሽቴን ነበር። ላንተ
መዋሸቴ በጣም ይቆጨኛል፡፡ ስለዚህ አሁን አንድ ውል እንግባ። አንተ ላለፈው ውሸቴ ይቅርታ አድርግልኝ። እኔ ደሞ ለወደፊቱ ሁልጊዜ እውነቱን እነግርሀለሁ፡፡»
«ስሚኝ የኔ ቆንጆ:: ለኔ ምንም ነገር መንገር የለብሽም፡፡»
“አውቃለሁ። ለዚህ ነው ልነግርህ የምፈልገው:: ከዚያም በላይ፣
አንተ ልትረዳኝ ትችል ይሆናል፡፡ እውነቱን ልንገርህ?»
«እሺ»
«አትጠላኝም?»
«በጭራሽ አልጠላሽም»
እሺ፡፡ ያኔ ታስታውሳለህ?»
የኔ ሻህራዝድ የኔ ቆንጆ፣ እንዴት ልረሳው እችላለሁ?»
“ተመስገንን ፍለጋ የምመጣ ይመስልህ ነበር፡፡ እኔ ግን አንተን
ለማግኘት ነበር የምመጣው፡፡ ሳይህ በጣም ደስ ትለኝ ነበር።
ካስትሮን ትመስለኝ ነበር። ስንቀልድ ስንስቅ ጥርስህን አፍህን ሳየው
አንቀህ እንድትስመኝ እመኝ ነበር፡፡ ታድያ አንተ እምቢ አልክ።
ስለዚህ ካንተ ስለይ፡ ተመስገን ጋ እሄድና አይኔን ጨፍኜ አንተን
እያሰብኩ አቅፈው ነበር፡፡»
«ያውቅ ነበር?»
«ምስኪን ተመስገን! እንዴት አርጎ ይወቅ?»
እንጃ፣ ነግረሽው ሊያውቅ ይችላል ምናልባት?»
«እንዲህ አይነት ነገር እንዴት ሊገባው ይችላል?»
»እሺ ቀጥዪ»
«ትጠላኛለህ»
«እንግዲህ ቂል አትሁኚ፡፡ በኔ የመጣ ስለምንም አለመግባባት
አትስጊ። ንገሪኝ፡፡»
«እንዴት አርጌ ልንገርህ?»
«እንደመጣልሽ»
ከነገርኩህ በኋላ ምን እንደሚመስልህ ትነግረኝ እንደሆን»
“Parole d'honneur?'' (የከበሬታ ቃልህን ሰጥተሃል?»)
“Parole d'honneur” («የከበሬታ ቃሌን ሰጥቻለሁ»)
«እሺ። እንዲህ ነው:: አየህ፣ ካንተ ጋር ግብረ ስጋ በጣም
ደስ ይለኛል። ደጋግሜ ነግሬሀለሁ፡፡ ያንተን ግማሽ እንኳ ያህል እኔን ማስደሰት የቻለበት የለም፡፡ ብቻ ምን ልበልህ፣ ታጠግበኛለህ፡፡ ግን
በሽታዬ ይመጣል። ሲመጣ ደሞ መከላከያ የለኝም። ገባህ?»
«ገና አልገባኝም
«እንዳልኩህ፤ ታጠግበኛለህ፡፡ ግን በሽታዬ ይመጣል፡፡ በጣም
ታምረኛለህ፣ በሀይል እመኝሀለሁ
«ታድያ አለሁልሽ አይደለም?»
“እንደሱ አይደለማ የምታምረኝ»
ልቤ መምታት እየጀመረ
“ታድያ እንዴት ነው?» አልኳት፣ ጐሮሮዬም መድረቅ ጀምሯል
በሀይል ታምረኛለህ፣ ምኞቱ ያንገበግበኛል። ግን ስትተኛኝ
በገዛ ገላህ እንዳይሆን ያስፈልጋል። የሌላ ወንድ ገላ ተውሰህ፣ በሱ ገላ አንተ እንድትተኛኝ ፈልጋለሁ። እንደዚህ ያማርከኝ ጊዜ፣ ካንተ
ተለይቼ መሄድ ይኖርብኛል።»
«ወዴት?» ጉሮሮዬ ጨርሶ ደርቋል
“አንተን ፍለጋ፣ ሌላ ወንድ ፍለጋ»
«ታገኚዋለሽ?»
«ምን ይመስልሀል?» ጉሮሮዋ ውስጥ ወፍራም ተንኮለኛ ሳቅ
ተሰማኝ ቅናት ማለት ይሄ ይሆን እንዴ? ታድያ ንዴቱና ብስጭቱ
የታለ? እኔን የሚሰማኝ ጥልቅ የሆነ እሳት የሆነ የሚያቃጥል
ቅንዝር! እንደ ዛሬም አንገብግቦኝ አያውቅ! ተለይታኝ ስትሄድ፣
ወፍራም ዳሌዋን እያወዛወዘች፣ ውብ ኣይኖቿን ክፍት ክድን
እያረገች፣ በፍትወተ ስጋ እስኪፈነዱ ብልታቸውን በሚያሳብጠው ፈገግታዋ የመረጠችውን እድለኛ ወንድ ስትጣራ ታየችኝ። ስጋዬ
አላስታግስ አላስችል አለኝ፣ እላዬ ላይ እንደተጋደመች በጥድፊያ
ገለበጥኳትና ጭኖቿን ፈልቅቄ ስገባ፣ በሙዚቃዊ ፈረንሳይኛዋ፣
በቅንዝር ድምፅዋ
“Ah. cheri, comme tu es sauvage! C'est delicieux"
👍20
#ምንዱባን


#ክፍል_አስራ_ስምንት


#ትርጉም_ከዬሐንስ_ገፃዲቅ

ኮዜት

ኦርዮን የተባለ መርከብ


ከአሁን በኋላ በጣም ዝርዝር ውስጥ ባንገባ ይሻላል፡፡ ግን በሚቀጥለው ቀን ጋዜጣ ላይ የወጣውን ባጭሩ መጥቀስ ደህና ሳይሆን አይቀርም፡፡

«ዣን ቫልዣ የተባለ ወንጀለኛ ካመለጠበት ተይዞ ለፍርድ ቀርቦአል፡፡ይህ ወንጀለኛ ከእስር ቤት ካመለጠ በኋላ ስሙን በመቀየሩ በቀላሉ በፖሊሶች
ሳይያዝ ቆይቶ ነበር፡፡ እንዲያውም ከነአካቴው ከጮሌነቱ ብዛት ከሀገራችን በስተሰሜን ለምትገኝ አነስተኛ ከተማ ከንቲባ እስከ መሆን ደረሰ፡፡ በዚህች ከተማ ውስጥ ብዙ ጥቅም የሚያስገኝለት ሥራም ሠርቷል፡፡ በመጨረሻ ግን በባለሥልጣኖች ታላቅ ጥረትና ድካም ማንነቱ ታውቆ ለመያዝ በቅቷል፡፡
በተያዘበት ወቅት በእቁባትነት ያስቀመጣት ሴት አዳሪ በድንጋጤ ሞታለች፡፡
ይህ እንደ ጎልያድ በጣም ጉልበተኛ የሆነ ሌባና ቀማኛ በድንገት ቢያመልጥም
በፖሊሶች ጥረት ከሦስት ቀን በኋላ ከፓሪስ ወደ ነበረበት ከተማ በሚጓዝ መኪና ውስጥ ሊገባ ሲል ተይዟል፡፡ ከተያዘ በኋላም ለሦስት ቀን የተሰወረው ከባንክ የነበረውን ከፍተኛ ገንዘብ ለማውጣት እንደሆነ ተደርሶበታል::
የነበረውም ገንዘብ ከስድስት እስከ ሰባት መቶ ሺህ ፍራንክ እንደሆነ ተገልጿል፡፡
ከባንክ ያወጣውን ገንዘብ ግን የት እንዳስቀመጠው ከራሱ በቀር ማንም ስላላወቀ ገንዘቡን ለመውረስ አልተቻለም:: ይህ ዣን ቫልዣ የተባለ ቀማኛ የአንድ ሕፃን ልጅ ገንዘብ በመዝረፉ ክስ ተመስርቶበት ፍርድ ቤት ቀርቦአል፡፡ይህ ሽፍታ የተከሰሰበትን ጉዳይ ለመካድ አልፈለገም፡፡ ገንዘቡን የዘረፈው
ዣን ቫልዣ ብቻውን ሳይሆን የዘራፊዎችን ቡድን በመምራት እንደሆነ በሥራቸው የተመሰገነና አንደበተ-ርቱዕ የሆኑ የመንግሥት ባለሥልጣኖች አረጋግጠዋል:: ይህም በመሆነ የዣን ቫልዣ ወንጀለኛነት ስለተረጋገጠ
በሞት እንዲቀጣ ተፈርዶበታል፡፡ ወንጀለኛው ወደ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ወይም ወደ ንጉሡ ይግባኝ ብሎ ወደ እድሜ ልክ እስራት እንዲለወጥለት ቢጥርም አልሆነለትም:: ዣን ቫልዣ ቱሉን ወደሚገኘው ወህኒ ቤት
ወዲያውኑ ተወስዶአል፡፡ ዣን ቫልዣ ቀደም ሲል የተሰጠው የእስር ቤት ቁጥር ተለውጦ አዲስ ቁጥር ተሰጥቶታል፡፡ አዲሰ ቁጥር 9430 ነው::

ወንጀለኛው ዣን ቫልዣ ለጥቂት ቀናት በተሰወረበት ሰሞን
ባለሥልጣኖች ሞንትፌርሜ ካተባለ መንደር ሲንሸራሽር መታየቱን ተናግረዋል:: ሞንትፐርሜ ከተባለ መንደር ውስጥ አንድ ወደ ዱር አዘውትሮ
መሄድ የሚወድ ሽማግሌ ነበር:: ሽማግሌ በአንድ ወቅት እስር ቤት
እንደነበር ሕዝቡ ይናገራል:: ፖሊሶችም በዓይነ ቁራኛ ይጠብቁታል:: ይህም ሽማግሌ ሥራ በማጣቱ በጣም ዝቅተኛ በሆነ ክፍያ የአውራ ጉዳና ጠጋኝ
ሆኖ እንዲሠራ መንግሥት ይቀጥረዋል፡፡

አንድ ቀን የተበላሽ መንገድ ለመጠገን በጠዋት ወደ ሥራው ቦታ ሲሄድ ከጫካ ውስጥ ከአንድ ዛፍ አጠገብ አካፋና ዶማ ተቀምጦ ያያል:: ከዚያም በመቆፈሪያውና በአካፋው አንድ ጊዜ እቃ እንደጠፋበት ሰው
አካባቢውን ያስሳል፤ ቆይቶ ደግሞ ትንንሽ ጉድባዎችን በጥድፊያ ይቆፍራል::

ይህን ተግባር ሲፈጽም የአንድ ትምህርት ቤት ዳይሬክተርና የአንድ ሆቴል ቤት ባለቤት የሆነው ሚስተር ቴናድዬ የተባለው የኮዜት አሳዳሪ በማየታቸው በጣም ይገረማሉ፡፡ «ታስሮ እኮ ነበር» ይላል ሚስተር ቴናድዬ ፤ «ጫካ ውስጥ እኮ ምን እንዳለ አይታወቅም፧ ምን ይሠራ ይሆን!»

ሁለቱ ሰዎች ጓደኛሞች ሲሆኑ ሽማግሌው ጋርም ቅርበት ነበራቸው:: በሌላ ቀን ሚስተር ቴናድዬ ተንኮል አስቦ ሰውዩው በመጠጥ ኃይል ወገቡ እስኪጐብጥ ድረስ በማጠጣት ያሰክሩታል፡፡ ይህ ቡላትሩስ የተባለው ግለሰብ በጣም ብዙ ስለጠጣ ብዙ ይለፈልፋል፡: በስካር መንፈስ የተናገረውን
በማቀናጀት የትምህርት ቤት ዳይሬክተሩና ሚስተር ቴናድዬ ከሚቀጥለው መደምደሚያ ላይ ይደርሳሉ::

«አንድ ቀን ጠዋት ሊነጋጋ ሲል ቡላትሩስ ወደ ሥራው ቦታ
ሲሄድ አካፋና ዶማ ከቁጥቋጦ ስር ተወሽቀው በማየቱ በጣም ይገረማል፡፡ ሆኖም መሣሪያዎቹ ምናልባት ከሠፈርተኞች መሃል አንዱ ረስቷቸው የሄደ ይሆናሉ ብሎ ከመገመቱ በስተቀር ምንም ነገር ሳያደርግ ያልፋቸዋል፡፡ ነገር
ግን በዚያው ቀን ወደማታ ለዓይን ያዝ ሲያደርግ ቡላትሩስ የሚያውቀው ሰው በትልቅ ዛፍ ተከልሎ ይመለከታል፡፡ ቡላትሩስን ግን አላየውም፡፡ ሰውዬው ለአገሩ ባዳ ለሰው እንግዳ ሲሆን በእነቴናድዬ አተረጓጉም ቡላትሩስ
ግለሰቡን የሚያውቀው እስር ቤት ነው:: ይህ ሰው ከዛፉ ከለላ ወጥቶ ጥቅጥቅ ወዳለው ጫካ አመራ፡፡ ሽማግሌው ምንም እንኳን ቢሰክርም
የሰውዬውን ስም ለመናገር አልፈቀደም:: ግለስቡ አንድ በጋ የተጠቀለለ አነስተኛ ሻንጣ መሳይ ነገር ይዟል፡፡ ከሁለትና ከሦስት ሰዓት በኋላ ሰውዬው
ጥቅጥቅ ካለው ጫካ ተመልሶ ወደ ውጭ ሊወጣ ቡላትሩስ አይቶታል፡፡
ሲመለስ ግን የያዘው ሻንጣ ሳይሆን ዶማና አካፋ ብቻ ነበር፡፡ በሚቀጥለው ቀን በጠዋት ሰውዬው በሄደበት አቅጣጫ ቡላትሩስ ይሄዳል፡፡ ግን ያ
ግለሰብ ከዚያ ሥፍራ አልነበረም:: በላትሩስ ምን ብሎ ያስባል? «ማታ ሰውዬው ይዞት በነበረው ዶማ ጉድጓድ ቆፍሮ ያንን ሻንጣ መሳይ ነገር ከቀበረ በኋላ በያዘው አካፋ አፈሩን በመመለስ ደፍኖታል:: መቼስ የቀበረው
ነገር ሰው አይሆንም፣ ምክንያቱም ሳጥንዋ ትንሽ ናት:: ስለዚህ የቀበረው ገንዘብ ነዋ» በማለት ደመደመ::
ስለዚህ ገንዘቡን ለማግኘት ቡላትሩስ ፍለጋውን ቀጠለ፡፡ ወጣ፣ ወረደ ፣ አዲስ የተነካካ አፈር ባገኘ ቁጥር ቆፈረ፤ መሬቱን ጠራረገ፣ የወደቀ ቅጠል
አገላበጠ፡፡ ግን ልፋቱ ሁሉ ከንቱ፡ ሆኖ ምንም ነገር አላገኘም::

ቡላትሩስ በሰከረ ቁጥር ይህን ታሪክ በመዘላበድና በመቀባጠር
ያወራል፡፡ ሆኖም ማንም ሰው ምንም ነገር ስላላገኘ ወሬው ከጊዜ በኋላ እየተረሳ ሄደ፡፡
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።

በ1923 ዓ.ም. ወደ ጥቅምት ወር መገባደጃ ላይ የቱሉን ከተማ
ነዋሪዎች ኦርዮን የተባለ የጦር መርከብ ሲመጣ በሩቁ ያያሉ፡፡ ሰው ተሰባስቦ መርከቡን ይጠብቃል፡፡ መርከቡ ጉዳት ደርሶበት ለጥገና ነበር
የመጣው:: አንድ ቀን ጠዋት የመርከቡ ሠራተኞች የጥገና ሥራ ሲሰሩ ያልታሰበ አደጋ ይደርሳል፡፡

የመርከቡ ሠራተኛ ከመርከቡ ጫፍ ላይ ቆሞ ገመድ እየጠቀለለ ሳለ መቆሚያውን ስቶ ሊወድቅ ይንገዳገዳል፡፡ ቀጥ ብሎ ለመቆም ጥቂት ከታገላ
በኋላ ለመመለስ ስላልቻለ ጥልቀት ካለው ባህር ውስጥ ሊወድቅ ሲል ባንድ እጁ ገመድ ይዞ ይንጠላጠላል፡፡ ከዚያም በሁለት እጁ ገመዱን ጥፍር
አድርጎ ላለመውደቅ ትግሉን ይቀጥላል:: ገመዱን ከለቀቀ በርቀት ተወርውሮ ጥልቀት ካለው ባህር ውስጥ ሊወድቅ ሆነ፡፡ ከዚያ ርቀት ከወደቀ እንደሚሞት
ያውቃል፡፡ ሰውዬውን ለመርዳት መሞከር ማለት ደግሞ ከትልቅ አደጋ ውስጥ መውደቅ ማለት ነበር፡፡ ግለሰቡን ለማዳን የሚሞክር ሰው ከባህሩ
ውስጥ መውደቅ ማለት ነበር፡፡ ግለሰቡን ለማዳን የሚሞክር ሰው ከባህሩ ውስጥ ሊገባ እንደሚችል ከዚያ የነበረ ሁሉ የሚያውቀው ነበር። ስለዚህ ግለሰቡን ለመርዳት ማንም አልደፈረም:: ሰውዬው ግን እየደከመ ሄደ::
👍171🥰1
#ገረገራ


#ክፍል_አስራ_ስምንት


#በታደለ_አያሌው


...."“እስኪ…” አለች ዶክተር ከብዙ ዝምታ በኋላ፣ ወደ በሩ እያመለከተቻቸዉ። “እስኪ አድ አፍታ ላስቸግራችሁ፣ ዉጪ ጠብቁ ያለ ምንም ጥያቄ ሁሉም ምሰስ እያሉ ሲወጡ፣ በክፍሉ እኔና እሷ ብቻ ቀረንበት.

“ልጄን…” ስል ተቀበልኋት፣ ባልቻን የሸኙ ዓይኖቿ ወደኔ ሲመለሱልኝ፡
“ልጄ አታሳዪኝም?”

“ናፈቀችሽ አይደል?”

“ኧረ አልቻልሁም ሽዊት”

“ይገባኛል። አዉቃለሁ”

“ታዲያ አምጭልኛ”

“እያወቅሽዉ? እንደሱማ አይሆንም”

“እንዴት ናት ግን? እንደ ፈራነዉ ሆነ ወይስ እግዜር ተአምሩን አሳየሽ?” አልኋት፣ ፈራ ተባ እያልሁ።

“ኹለቱም”

የምትለዉን እንድትል ጠበቅኋት፡
“እንደ ፈራሁትም ነዉ፤ እግዚአብሔርም ተአምሩን አሳይቶኛል። ኹለቱንም”

አሁንም ጭጭ ብዬ አዳመጥኋት፡ ጠበቅኋት እያየኋት የግንባሯ ሰማይ ዳመነ፡ የዳመኑ ዓይኖቿም እንባ አዘሉ፡ ምንም ሳይቆይ ያዘለዘለ እንባዋ ቡልቅ እያለ ሲወርድ እኔም አልቻልሁም: የኔም ጉንጮች ቀዝቃዛ እንባ አለፈባቸዉ: ከመሬት ተነስቶ ብርድ አንሰፈሰፈኝ

“ቁርጤን ልስማዉ?” አልኋት፣ መጥፎ ነገር ብትነግረኝ ፍጥርቅ ብዬ ለመሞት እየተሰናዳሁ: ከመሞት በቀር ምን ምርጫ አለኝ? ምንም:: እሞታለሁ

“ግልጹል ንገርሽ: ወደ ኦፕራሲዮን ክፍሉ ስገባ፣ አንቺን ለማትረፍ
እንጂ ልጅሽ በሕይወት ትመጣለች ብዬ አልጠበቅሁም ነበር። በሆድ
ሳለች የልብ ምቷ ስናዳምጠዉ በጣም አስፈሪ ነበር። አንቺም ትናትና እንዳልሽኝ በሆድሽ ዉስጥ እየተንቀሳቀሰች አልነበረም: በዚያ ላይ ከመደበኛዉ የመወለጃ ጊዜ እጅግ ቀድማ ስለመጣች፣ ላንቺ ፈርቼልሽ ነበር: በግልጽ ልንግርሽ አይደል ዉብዬ? የልጅሽ በሕይወት መትረፍ፣ ያንቺም በጤና መገላገል የእግዚአብሔርን ሥራ በዓይኔ በብረቱ ያየሁበት
ተአምር ነዉ”
“እንግዲያዉ ምድነዉ የሚያስለቀሰሽ?”
ለመናገር ዳዳችና ተወችዉ፡፡

በጥያቄ የተጥለቀለቀ ፊቴን ስታይ ቆይታ፣ የነርሶቹን መጥሪያ ደወል ተጫነችዉ፡ ደወሉን ሳትለቀዉ ገና፣ ከቅድም ጀምራ በተለየ ሁኔታ ጠብ እርግፍ ስትልልኝ የነበረችዋ ነርስ ያለንበትን ክፍል ከፈት አድርጋ ገባች
“አቤት ዶክተር''
“እስኪ ባክሽ አንድ ነገር ላስቸግርሽ”
“ምን ልታዘዝ ዶክተር?''
“እስኪ ባክሽ ዉብርስት ወደ lCሀ ክፍል እንዉሰድና አንዳፍታ ልጇን
በዓይኗ እናሳያት”
“ኧረ?” አለች፣ ድንግጥ እያለች:
“አይዞሽ፤ አብሬሽ አለሁ: ኃላፊነቱን ራሴ እወስዳለሁ” ስትል
አደፋፈረቻት፣ ነፍሴን የያዘልኝ ግሉኮስ የተንጠለጠለበትን ዘንግ ራሷ ከፍ አድርጋ እያነሳችና መንገድ እየጀመረች:

ነርሷም ትንሽ እንደ ማቅማማት ስትል ከቆየች በኋላ መታዘዟን
አስበልጣ የተንጋለልኩበትን አልጋ
ማሽከርከር ጀመረች መኪና ማቆም ከሚያያስችለዉ የሕንጻዉ ሰፊ አሳንሰር ከነአልጋዬ ከጫኑኝ በኋላ ኹለት ፎቆች ወደ ላይ ወሰዱኝ፡ ከአሳንሠሩ ወርደን ትንሽ እንደ ሄድን፣ ጥልቀት ያለው እንክብካቤ ወደሚደረግበት (ICU) ክፍል ደረስን፡ እጅግ ሰፋ
ወዳለዉ አዳራሽ ከመግባቴ፣ የተለያየ ስምና መጠን ያላቸዉ ማሽኖች ተደርድረዉ አየሁ፡ በአብዛኛዎቹ ማሽኖች፣ በተለይም ያለ ዕድሜያቸው የተወለዱ ሕጻናት ተኝተዉባቸዋል፡ ያዉም በሆድ፣ አፍና አፍንጫቸ
ላይ በልዩ ልዩ ማስተላለፊያዎች ተተብትበዉ፡ በነዚህ ትብታቦች
አማካኝነት በዋናነት ምግብ እና አየር የሚያገኙ ሲሆን፣ ማሽኖች
የየራሳቸዉ ማሞቂያም ሆነ ማቀዝቀዣ የተሟላላቸዉ መሆናቸዉን በስማቸዉ አዉቃቸዋለሁ መሀል ለመሀል እየወሰዱኝ ሳለ፣ በግራም
በቀኝም በኩል ዓይኔ ዉስጥ የገቡትን ሕጻናት ሥራዬ ብዬ ተመለከትሁ ሁሉም እንደየአቅማቸዉ እግርና እጃቸዉን ያወራጫሉ።

ቱናትን ላያት ነዉ፡

ብዙ የተገመተላትን፣ የልጄን ዓይን በዓይኔ ላየዉ ነዉ፡፡ ልጄ ቱናት
ያለችበት ክፍል ዉስጥ መሆኔን ሳዉቅ፣ ይኼ ነዉ ብዬ መግለጽ
የማልችለዉ ሽብር ወረረኝ፡፡ ፍርሃቴም ናፍቆቴም ተደራርበዉ ልቤን ጫፍ ላይ አደረሱብኝ፡፡ ልትወጣ ምንም አልቀራትም፡፡

ፍርሃቴ ጫፉ ላይ ደርሷል፡

“ይቅርታ” አለች ዶክተር፣ ወደ ነርሷ ዘወር ብላ፡ ሲመስለኝ ቱናት
ያለችበት አጠገብ ደርሰናል በዓይኔ ባጣብራት ግን ላገኛት አልቻልሁም ጭንቅላቷ ከፍ ያለ ልጅ ፍለጋ ዓይኔን ባንከራትትም አላገኘኋትም፡ የዶክተሯ ጥቅሻ ገብቷት ነርሷ የያዘችዉን የአልጋዬን ብረት ለቀቀችና
ተመልሳ ወጣች:: ኹለት የክፍሉ ባለሙያዎች በክፍሉ ያሉ ቢሆንም፣በማሽኖች አጠገብ ግን አይደለም የቆሙት ዝም ብለዉ ብቻ እንደ ንቁ ወታደር፣ ወዲያ ወዲህ ይንጎራደዳሉ።

እኔም እሷም ወደ'ዚህ ክፍል ለመግባት፣ ቢያንስ የእነሱ ፈቃድ
እንደሚያስፈልግ እኔም ገምቻለሁ
በመሆኑም በየስማቸዉ ጠርታ ሰላም እያለቻቸዉ ወደ እነሱ ቀረበች: ምን እንደ ተባባሉ ባይሰማኝም፣ ብቻ የሆነ ነገር ብላ አሳምናቸዉ መጣች: በአንድ እጇ ግሉኮስ የተንጠለጠበትን የብረት ዘንግ፣ በሌላ እጇ ደግሞ አልጋዬን በትራስጌ በኩል እየገፋች ዉስጥ ለዉስጥ ተሂዶ ወደሚገኝ ሌላ ክፍል አደረሰችኝ፡: ጠጋ ብላ
ካነጋገረቻቸዉ ባለሙያዎች አንደኛዉ ቀደም ብሎ በመዳፉ አሻራ በሩን ከፈተልንና ገባን፡፡ እሱን በደረቅ ፈገግታም ጭምር እጅ ነስታ ከሸኘችዉ በኋላ፣ እስከ አሁን በጭራሽ አይቼባት የማላውቀዉን ፊቷን አሳየችኝ፡፡

ከተለዩትም የተለየ እክብካቤ ስለሚያስፈልጋት፣ ልጅሽ ያለችዉ
በዚህኛዉ ለይቶ ማቆያ ክፍል ነዉ: ልጅሽን የማየት መብት ቢኖርሽም፣ መንገዱ ግን አሁን የመጣንበት አይደለም: እንግዲህ ያለ ግርግር መምጣት የፈለግሁበት ምክንያት አንቺም የምታጭዉ አይመስለኝም”
ለጥያቄ አፌን እያሞጠሞጥሁ ሳለ፣ ቀልጠፍ ብላ ከአጠገባችን ያለዉን ማሽን ቁልፎች መነካካት ጀመረች ማሽኑ እጅግ ግዙፍ ሲሆን፣ ከላይ የተገለበጠ ሙኸዶ የሚመስል ክዳን አለዉ፡ ልክ መነካካት ስትጀምር፣
ቀድሞ ወደ ላይ ተስቦ የተከረፈደዉ ይኼዉ ክዳን ነዉ፡ በእርግጥ ክዳኑ ብርሃን አስተላላፊ ስለሆነ፣ ለቆመ ሰዉ እንደ ተከደነም ቢሆን ወደ ዉስጥ
ከማየት አይከለክልም፡ እኔ ግን እንደ ተንጋለልሁ ስለሆነ ተከፍቶልኝ እንኳን ልጄን ማየት አልቻልሁም እስከመጨረሻዉ ድረስ አልጋዬን ከወገብ በላይ አቃንታልኝ፣ ራሷ የመሸከም ያህል ደግፋ ቀና አደረገችኝ
እና ወደ ዉስጥ እንድመለከት አመቻቸልኝ፡

በሙሉ ዓይን ባይሆንም፣ አንገቴን ቀና አድርጋ አሳየችኝ አየኋት
ቱናትን አገኘኋት።እንደ ተፈራዉ ናት።

“ስንት ኪሎ ሆነች?” አልኋት፣ የጭንቅላቷን ግዝፈት እያስተዋልሁ፡አትሆንም እንጂ ኹለት ኪሎ እንኳን ብትሞላ ከግማሽ በላዩን የሚመዝነዉ ጭንቅላቷ እንደሚሆን ያስታዉቃል፡ ዓይኖቿ ወደ ዉስጥ
መቀበራቸዉ ሳያንስ ከተመለከቱም የሚመለከቱት ቁልቁል ብቻ ነዉ፡ እንቅስቃሴ የሚባል የላትም፡ የተኛ ሰዉ እንኳን ሲተነፍስ ሆዱ ላይ ብቅ ጥልቅ ይታይበታል፡ ልጄ ግን ጸጥ ብላለች፡ እኔን ልጄ!

“መቼስ እግዚአብሔር ምን ይሉታል?” አልሁ፣ ተአምሩን ለእኔም ያልገለጠልኝን አምላክ በመቀየም እና በማመስገን መካከል ሆኜ:

“ኧረ እንጃ። ከፊት ለፊትሽ ግን እንዲህ ነዉ የማይሉት ፈተና እንዳለ ልዋሽሽ አልፈልግም: ትእዛዝ ተቀባይ ነርቮች ብዙዎቹ በትክክል አይሠሩም: ስፓይናቢፊዳ እና ሀይድሮሴፋለስ ከጠበቅናቸዉም በላይ ሆነዉ
👍30
#ሳቤላ


#ክፍል_አስራ_ስምንት


#ድርሰት_ሚሲስ_ሔንሪ_ውድ


ሚስተር ካርይል ከካስል ማርሊንግ ወደ ዌስትሊን እንደ ተመለስ ጥፋቱ እንዳይሰማበት ለመደበቅ የተገደደ ተማሪ ይመስል ተጨነቀ ምንም እንኳን ሰውየው ነገሩ ሁል ጊዜ ግልጽ ቢሆንም • በአሁኑ ጊዜ የተፈጸውን ነገር ከመግለጽ መቆጠቡ የተሻለ መስሎ ታየው ምክንያቱም እኅቱ የሱን ጋብቻ እንድትሰማ የማትፈልግ ከመሆኗም በላይ ለመልከ ቀና ሴቶች ደግሞ አዘኔታም ፍቅርም ስላልነበራትና ወይዘሮ ሳቤላንም እንደማትወዳት ያውቅ ስለነበር ነው ስለዚህ ነገሩ
ከሚስ ካርላይል ጆሮ የደረሰ እንደሆነ የምትቃወመውና ምናልባትም ጋብቻቸውን ለማፍረ
መሞከሯ እንደማይቀር አሰበና ተነጋግሮ መምጣቱን ደበቃት እንዲያውም ኢስትሊን ለመከራየት መጥተው የነበሩትን ሰዎች ከልክሎ እንደ መለሳቸው እንኳን አልነገራትም "

ሚስተር ካርላይል ከካሰል ማርሊንግ ከተመለሰ ከሶስት ሳምንት በኋላ ባርባራ ሔር አንድ ቀን ማታ ሚስ ካርላይልን ለማየት መጥታ ከተለመደው ሰዓት ቀደም
ብለው ሻይ ሊጠጡ ሲሉ አገኘቻቸው "

ቀደም ብለን ራት በላንና አርኪባልድ ሻይ ሳይጠጣ እንዳይቀር ብዬ ገበታ ሲነሳ ወድያው ቶሎ ሻይ እንዲቀርብ አዘዝኩ ” አለቻት ሚስ ካርላይል ።
ባልጠጣም ምንም አይለኝ” አለ ሚስተር ካርይል ገና የማከናውነው ብዙ ሥራ አለብኝ።

“ ለምን ተብሎ? እኔም ካልጠጣህ ደስ አይለኝም " ቆብሽን አውልቂው ባርባራ ሥራው ሁሉ ከሰው የተለየ ነው ይውልሽ ነገ ወደ ካስል ማርሊንግ ልሔድ ነው ይላል እስከ ዛሬ ዝም ብሎ ገና አሁን ነው የነገረኝ ”

ታመመ የተባለው ሰውዬ እስከ ዛሬ እዚያ ነው እንዴ ያለው ?

“ እስከ ዛሬ እዚያ ነው " አለ ሚስተር ካርላይል "

ባርባራ ስለምትቸኩል አይሆንም ብትልም በግድ ሻይ ለመጠጣት እንድትቀመጥ ሆነ » ሚስ ካርላይል ደግሞ ባርባራ ንግግሯን ሳትጨርስ አቋረጠቻትና
ወንድሟን ዞር ብላ ዕቃውን ልታዘጋጅለት እንደምሔድ ነገረችው "

“ አይ የለም ” አላት ፈጠን ብሎ " ዕቃውን እኔ ራሴ አሰናዳዋለሁ ፒተር ሻንጣውን ወደ ክፍሌ አስገባልኝ » ትልቁን ነው ... ገባህ ? ”

“ ትልቁን ” ብላ ጮኸች ያለ እሷ ጣልቃ ገብነት ምንም ነገር የማያልፈው ኮርነሊያ“ ደሞ ቤት የሚያህል ሻንጣ እየጎተትክ የምትሔደው ለምንህ ነው?

“ከልብሴ ሌላ ጨምሬ የምይዛቸው ሰነዶችና ሌሎችም ነገሮች አሎኝ "

“ እኔ እንተ የምትላቸውን ነገሮች ሁሉ በትንሹ ሻንጣ ማስገባት እችላለሁ ብላ ድርቅ አለች ኮርነሊያ « “ እሞክረዋለሁ አንተ ብቻ የምትፈልገውን ዕቃ ንገረኝ ፒተር ... ትንሹን ሻንጣ ከጌታህ ክፍል አስገባ " አለችው "

ሚስተር ካርሳይል ፒተርን ሲያየው መልሶ አየውና ራሱን በእሽታ ነቀነቀ“ ዕቃዩን ራሴ ሳሰናዳው ነው ደስ የሚለኝ ኮርነሊያ እጅሽን ደግሞ ምን አደረግሽው? ” አላት "

“ዕብደት አታውቅም አለችው ሚስ ኮርነሊያ አለልቧ ከቢላዋ ጋር ስትጫወት ጣቷን ቆረጠችና ' ' ልጥፍ የሚል ፕላስተር አለህ ? " አለችው "

“ የኪስ ማስታወሻ ደብተሩን ከጠረጴዛው ላይ አድርጎ ገለጠውና ከውስጡ አንድ ጥቁር ፕላስተር ሲያወጣ የማያርፉት የኮርነሊያ ዐይኖች አንድ ደብዳቤ ከደብተሩ ውስጥ አዩ " ምንም ሳትጠይቅ እጅዋን ሰዳ ብድግ አድርጋ ገለጠችው።

“ ከማን የመጣ ነው የሴት ጽሕፈት ነው "

ለማንበብ ከመሞከሯ በፊት ሚስተር ካርላይል እጁን ዘርግቶ ሸፈነባትና ፡ “ይቅርታ ኮርነሊያ. . . . የግል ደብዳቤ ነው " አላት "

“ ኧረ ወዲያ ምስጢር ብሎ ነገር ' ከኔ የሚደበቁ የምስጢር ደብዳቤዎች እንደ ማይዶርሱ እርግጠኛ ነኝ የፖስታ ቤቱ ማኅተም የትናንት ነው ።

“ ይሀን ደብዳቤ ልቀቂልኝ” አላት ሚስ ካርላይል በዚያ ረጋ ያለ ሥልጣን አዘል ድምፁ ሲነግራት ከበዳትና ለቀቀችለት "

"ምን ነካህ... አርኪባልድ?”

ምንም ” አላት ፕላስተሩን ከአወጣላት በኋላ ደብዳቤውን ወደ ኪስ ደብተሩ እየመለሰ “ የወንድ ልጅ ደብዳቤዎችን ማየት ደግ አይደለም " ነው እንዴ ! ባርባራ ? '' አለና ወደሷ እየተመለከተ ሣቀ " በዚህ ጊዜ ፊቱ ሲለዋመጥ አየችው "

በቀላሉ የማትለቀው ኮርነሊያ ደግሞ ፡ “ ደብዳቤው የቬን ቤተሰብ ዐርማ ታትሞበታል ” አለችው "

“ የቬን ዐርማ ከደብዳቤው ላይ ኖረውም አልኖረውም ጽሑፉ ለኔ ዐይኖች ብቻ የተላከ ነው ” ሲል ቁርጥ ያለው አነጋገሩን ሰምታ ዝም አለች

ሁሉም ዝም ሲባባሉ ጊዜ 'ባርባራ ዝምታውን ጥሳ ንግግር ጀመረች "

“ ባሁኑ ጊዜ ማውንት እስቨርኖችን ትጠይቃቸዋለህ እንዴ ? ”

“ አዎን ”

“ስለ ወይዘሮ ሳቤላ ጋብቻ ምን ይወራል... ልጄ የሰማኸዉ ነገር አለን ? ”

“እኔ የሰማሁትንና ያልሰማሁትን ማስታወስ ይቸግረኛል ባርባራ ሻይሽ ሱካር ሳያንሰው አልቀረም " አይደለም እንዴ ! ”

“ አዎን ጥቂት ” ስትለው ' የሱኳሩን ማቅሬቢያ ጠጋ አደረገና ተው ከመባሉ በፊት አምስት አንኳር አንሥቶ ጨመረበት።

“ለምንድነው ይህን ያህል?” ስትለው ከት ብሎ ሣቀና የምሠራውንም ረሳሁ "
ባርባራ ይቅርታ አድርጊልኝ ኮርኒሊያ ሌላ ስኒ ትሰጥሻለች ” አላት "

“ ባንድ ስኒ ሻይ የባከነው ይኸ ሁሉ ሱኳርስ ቀላል ነገር መሆኑ ነው ? ” አለችው ኮርኒሊያ ቆጣ ብላ "

ሻይ ተጠጥቶ እንደ አበቃ ባርባራ ለመሔድ ተነሣች “ አቤት ጨለመብኝ በዚህ ጨለማ ብቻዬን በመውጣቴ እማማ ትቆጣኛለች ” አለች "

“እርኪባልድ ያደርስሻል " አለቻት ኮርኒሊያ "
ባርባራ ሚስ ኮርነሊያን ተሰናብታ ከሚስተር ካርላይል ጋር ወጣች ጃንጥላዋን ተቀበላትና በእርሻዎቹ መካከል አቋርጠው እየተጫወቱ ሔዱ።

ባርባራ ሳቤላ ቬንን ልትረሳት አልቻለችም ሚስተር ካርይል ወደ ኢስትሊን ሲመላለስ በነበረበት ጊዜ ከልቧ አድሮባት የነበረው ቅናት አልጠፋም " አሁንም
በጫወታቸው ወደዚሁ ርዕስ ተመለሰችበት "

ወይዘሮ ሳቤላ ቬን ስለ ማግባቷ ጉዳይ የሰማኸው እንዳለ ጠይቄህ እኮ መልስ አልሰጠኸኝም .. አርኪባልድ ” አላችው "

አኔ የምሰማውን ሁሉ ማስታወሱ አልችልም ብዬ አልነገርኩሽም? ”

“ብልኸኝ ነበር ? ”

“አስጨንቀሽ ያዝሺኝ አይደለም እንዴ ! " ብሎ ሣቅ አለና አዎን ነምቴገባ ይመስለኛል ” አላት "

" ማንን ? ” አለችው ያስጨነቃት ሐሳብ እንደ መልቀቅ እያደረጋት "
አሁንም ፈገግታው ከከንፈሩ ሳይለቅ “ ሁሉን ነገር ባንድ ጊዜ ማወቅ እችል ይመስልሻል ?
ምናልባት ከካስል ማርሊንግ ስመለስ ልነግርሽ እችል ይሆናል "

“ በል አረጋግጠህ እንድትመጣ ምናልባት ሎርድ ቬንን ይሆን የምታገባው !ማን እንደሆነ እንጃ እንጂ ብዙ ጋብቻዎች የሚጠነሰሱት ብዙ ጊዜ ከመቀራሪብ ነው ብሏል ” ስትለው ትክ ብሎ አያትና ሣቀባት "

“እንዴት ያለሽ ግምት ዐዋቂ ነሽ ? ሎርድ ሔል እኮ ያምስት ወይም የስድስት ዓመት ልጅ ነው " ይልቁንስ ካነሣሺው እንዴት ያለ ጥሩ ልጅ መሰለሽ " እኔ ልጆች
ቢኖሩኝ እንደሱ ቢሆኑልኝ ነው የምመኘው "

ድፍን ዌስት ሊንን ሳታገባ መቅረትህን ካሳመንከው በኋላ እንዲህ መናገርህም
ትልቅ የምሥራች ነው "

“ እኔ ከዌስትሊን ሰው አላገባም ብዬ ቃል መግባቴን አላስታውስም

ባርባራ ሣቀች” “ ዌስትሊን በመልክ ግምት ይሔዳል መሰለኝ አንድ ሰው ሠላሳ ዓመት ከሞላው ...ኀ
“ እና ታዲያ ሠላሳ አልሞላኝ ደግሞ ሠላላ ሳይሞላኝ አባ ወራ እሆናለሁ” አላት ሚስተር ካርላይል ከመንገዱ ዳር የነበረውን የድንበር ቅጠል በያዘው ጃንጥላ ያለ ልቡ እየጨፈጨፈ ሲጓዝ "

ሚስትህን መርጠህ አኑረሃል ማለት ነው ? ”
👍13
#የጣሪያ_ስር_አበቦች


#ክፍል_አስራ_ስምንት


#ትርጉም_ሀኒም_ኤልያስ


...የምስጋና ቀንና ገና እንደቀረበ ሊያስታውሰን ህያው የቀን መቁጠሪያችን የሆነው የረጅሙ አትክልት አገዳ ትንሽ እምቡጥ ያዘ፡ ያልደረቀው ብቸኛ አትክልታችን እሱ ብቻ ስለነበር በጣም የምንወደው ንብረታችን ነበር᎓ ጣሪያው ስር ካለው ክፍል አንስተን አንድ ሞቃት ምሽት ከእኛ ጋር እንዲያሳልፍ ወደ መኝታ ክፍላችን ወሰድነው: በየማለዳው ገና ሲነጋ ኮሪ ያቺ እምቡጥ ምሽቱን በደህና ማሳለፏን ለማረጋገጥ ሮጦ ሄዶ ይመለከታታል ኬሪም ተከትላው ሄዳ አጠገቡ ትቆምና ሌሎች ሲደርቁ ብቻዋን በመቆየቷ ያቺን ድል አድራጊ ጠንካራ ተክል ታደንቃለች አፈሩ ውሀ የሚፈልግ መሆኑ መንትዮቹ ቢሰማቸውም፣
ግድግዳው ላይ የተሰቀለውን ቀን መቁጠሪያ እየተመለከቱ ቀኑ አረንጓዴ ተሰምሮበት፣ አትክልቱ ውሀ የሚፈልግበትን ቀን እንዲያመለክት ይጠብቃሉ።
ያ ስለማይሆንና በራሳቸው ለማድረግም እርግጠኛ ስለማይሆኑ ወደ እኔ ይመጡና “አትክልቱን ውሀ እናጠጣው? ውሀ የጠማው፦ ይመስልሻል?” ሲሉ ይጠይቁኛል።

ስም የምንሰጠውና የኛ የምንለው ግዑዝም ሆነ ህያው ነገር የለንም
አትክልታችን ብቻ ከኛ ጋር ለመኖር ቆርጧል ኬሪም ሆነች ኮሪ ከባዱን ማሰሮ ይዘው በቅርብ የፀሀይ ብርሃን ወደሚኖርበት ጣሪያው ስር ወዳለው ክፍል ለመውሰድ ጥንካሬ አልነበራቸውም፡ ስለዚህ እኔ አትክልቱን እንድይዘው ተፈቀደልኝ ሲመሽ ደግሞ ክሪስ ወደታች ይመልሰዋል በእያንዳንዱ ምሽት ተራ በተራ ቀኖቹን በቀይ ቀለም ምልክት እናደርጋለን፡ እስካሁን መቶ ቀኖች
ላይ ምልክት አድርገናል።

ክረምቱ በመግባቱ ዝናብ መጣ፡፡ ሀይለኛ ንፋስ እየነፈሰ ነው፤ አንዳንድ ጊዜ ከባድ ጭጋግ የጠዋቷን የፀሀይ ብርሀን ይከልላታል ምሽት ላይ ደግሞ
ነፋሱ የደረቁትን የዛፍ ቅርንጫፎችን ከቤቱ ጋር ሲያስታክካቸው ከእንቅልፌ
ያባንነኝና የሆነ አስፈሪ ነገር መጥቶ የሚበላኝ እየመሰለኝ ትንፋሽ ያጥረኛል በኋላ ላይ ወደ በረዶ ሊለወጥ የሚችል ዝናብ እየወረደ ባለበት ቀን እናታችን
ትንፋሽዋ ቁርጥ ቁርጥ እያለ የምስጋና ቀን በዓል እንዲመስልልን ጠረጴዛችንን
የምናስጌጥባቸው የሚያማምሩ የግብዣ ጌጣጌጦች ይዛ ወደ መኝታ ክፍላችን ገባች በተጨማሪም ብሩህ ቢጫ ቀለም ያለው የጠረጴዛ ልብስና ጥልፍ
ያለበት ብርቱካናማ የአፍ መጥረጊያ መሀረቦች ይዛ ነበር።

የያዘችውን ዕቃ በሩ አጠገብ ያለው አልጋ ላይ እያስቀመጠችና ለመውጣት ፊቷን እያዞረች: “ነገ እራት ላይ እንግዶች አሉብን” ስትል አብራራች: “እና አንደኛው ለእኛ ሌላኛው ደግሞ ለሰራተኞቹ የሚሆን ሁለት ዶሮዎች
ይጠበሳሉ፡ ነገር ግን አያታችሁ የሽርሽር ቅርጫት ይዛ በምትመጣበት ወቅት አይደለም ግን አትጨነቁ፣ ልጆቼ በምስጋና ቀን ለቀኑ የሚመጥን ምግብ
ሳይኖራቸው በዓልን አያሳልፉም እንደምንም ብዬ እኛ ከምንበላው ምግብዐለእናንተ የማመጣበትን መንገድ እፈልጋለሁ ለአባቴ ራሴ እንዳቀርብለት እፈልጋለሁ ብዬ ብዙ አዘጋጅና ለእሱ የማቀርበውን ሳሰናዳ በሌላ ትሪ ደግሞ
ለእናንተ ላስቀምጥላችሁ እችላለሁ ነገ ሰባት ሰዓት አካባቢ ጠብቁኝ” አለች።

በትልቅ ሳህን የሚቀርብ ትኩስ የምስጋና ቀን ምግብ ለመብላት በመጠበቅ ደስታ ውስጥ ጥላን ልክ በበሩ በኩል እንደሚገባው ነፋስ ገብታ ወጣች።

“የምስጋና ቀን ምንድነው? አለች ኬሪ።

“ከምግብ በፊት ከማመስገን ጋር አንድ ነው” ሲል ኮሪ መለሰላት በአንድ በኩል ልክ ነው ብዬ አስባለሁ።

ሰባት ሰዓት መጣ፣ ሄደ። ኬሪ ጮክ ብላ አጉረመረመች “አሁን ምሳችንን እንብላ፣ ካቲ!”

“ታገሺ እናታችን ልዩ ትኩስ ምግብ፣ ዶሮና ማባያዎቹ ሁሉ ያሉበት ትሪ ይዛ ትመጣለች ይኼኛው ለእራታችን ነው ምሳ አይደለም” አልኳት: የእኔ የቤት እመቤትነት ስራ ለጊዜው አለቀና በደስታ አልጋው ላይ ጥቅልል ብዬ
ማንበብ ጀመርኩ።

ካቲ ሆዴ ትዕግስት የለውም” አለ ኮሪ፤ ክሪስ በሸርሎክ ሆልምስ ታሪክ ተመስጧል፡ መንትዮቹ ሆዳቸውን ፀጥ እንዲል አድርገው እንደ እኔና እንደ ክሪስ ቢያነቡ ጥሩ አልነበር?

“የተወሰኑ ዘቢቦች ብላ ኮሪ”

“ምንም የተረፈ የለም”

“ለውዝ ብላ”

“ለውዙም ሁሉም አልቋል”

“እሺ ብስኩት ብላ”

“የመጨረሻውን ብስኩት ኬሪ በልታዋለች”

“ኬሪ ብስኩቶቹን ለምን ለወንድምሽ አላካፈልሽውም?”

“የዚያን ጊዜ አልፈልግም ብሎኝ ነው”

ስምንት ሰዓት ሆነ አሁን ሁላችንም እርቦናል። ሁልጊዜም ልክ ስድስት
ሰዓት ላይ ነው የምንበላው፡ እናታችንን ምን አዘገያት? በመጀመሪያ ራሷ ልትበላና ከዚያ ልታመጣልን ነው? ግን'ኮ እንደዚያ አላለችንም ነበር።

ዘጠኝ ሰዓት አለፍ እንዳለ እናታችን በችኮላ ገባች ከላይ በሳህኖች የተሸፈነ ትልቅ ብራማ ቀለም ያለው ትሪ ይዛለች። ሰማያዊ የሱፍ ቀሚስ ለብሳለች። ፀጉሯ ደግሞ ከፊቷ ላይ ተሰብስቦ ኮሌታዋ አካባቢ ዝቅ ብሎ በፀጉር መያዣ
ተይዟል፡ እንዴት ታምራለች! “እንደራባችሁ አውቄያለሁ።" ወዲያውኑ ይቅርታ መጠየቅ ጀመረች: “በመጨረሻዋ ደቂቃ ላይ አባቴ ሀሳቡን ቀይሮ
ተሽከርካሪ ወንበሩን በመጠቀም ከእኛ ጋር ለመብላት ወሰነ።” በመጠኑ ፈገግ አለችልን። “ካቲ ጠረጴዛውን ቆንጆ አድርገሽ አዘጋጅተሽዋል። ሁሉንም ነገር
በትክክል ነው ያደረግሽው: እኔ ግን አበቦቹን ስለረሳሁ ይቅርታ: መርሳት አልነበረብኝም: ዘጠኝ እንግዶች ነበሩብኝ ሁሉም እያዋሩኝና ለብዙ ጊዜ የት
እንደነበርኩ ሺ ጥያቄዎችን እየጠየቁኝ ነበር እና ጆኒ ሳያየኝ የአስተናጋጆቹ ጓዳ ውስጥ መግባት እንዴት ችግር እንደሆነ አታውቁም ያ ሰው ከኋላው
ሳይቀር አይን ያለው ነው የሚመስለው ማንም ሰው እንደኔ ከምግብ ላይ አስር ጊዜ ቁጭ ብድግ ሲል አይታችሁ አታውቁም

“እንግዶቹ ጨዋ እንዳልሆንኩ፣ ወይም ሞኝ እንደሆንኩ ሳያስቡ አይቀርም ግን ያም ሆኖ ሳህኖቻችሁን መሙላትና መደበቅ ችዬ ነበር ከዚያ ወደ መመገቢያው ጠረጴዛ መመለስ፣ ፈገግ ማለትና ሌላ ክፍል ገብቼ አፍንጫዬን
ከማፅዳቴ በፊት ደግሞ አንዴ መጉረስ ነበረብኝ፡፡ መኝታ ክፍሌ ውስጥ ባለው የግል መስመር የተደወሉልኝን ስልኮች መመለስና ማንም እንዳይገምት ድምፄን
መቀነስ ሁሉ ነበረብኝ የዱባ ኬክ ላመጣላችሁ ፈልጌ፣ ጆን ቆራርጦ ሳህኖች ላይ አድርጓቸው ነበር። ምን ማድረግ እችላለሁ? አራት ኬኮች ቢጠፉበት ማወቁ አይቀርም:"በአየር ላይ ሳመችን ደስ የሚል ግን የችኮላ ፈገግታ ሰጠችንና ከበሩ ወጥታ ተሰወረች: አምላኬ ሆይ! እውነትም ህይወቷን አወሳስበንባታል! ለመብላት ወደ ጠረጴዛው ተጣደፍን፡ ክሪስ አንገቱን ዝቅ አድርጎ ጆሮዎች ልብ የሚነካ ምስጋና በሚሰሙበት በዚህ ቀን እግዚአብሔርን ብዙም የማያስደስት የችኮላ ምስጋና አቀረበ፡ “ጌታ ሆይ፣ ስለዚህ ስለዘገየ የምስጋና ቀን ምግብ
እናመሰግንሀለን፡፡ አሜን!”

በክሪስ ቀጥታ ወደ ጉዳዩ የመግባት ባህርይ እየሳቅኩ፣ አስተናጋጃችን እርሱ በመሆኑ ሳህን አቀበልኩትና አንድ በአንድ ምግባችንን ሳህኖቻችን ላይ አደረገልን ምግቦቹ እየቀዘቀዙ ነበር: “ቀዝቃዛ ምግብ አንወድም!” አለች ኬሪ ሳህኗ ላይ የተደረጉላትን ምግብ እየተመለከተች።

የእውነቴን ለእናቴ አዘንኩላት ለእኛ ትኩስ ምግብ ለማምጣት ስትሞክር የራሷን ምግብ በስርዓት ሳትበላ በእንግዶቹ ፊት እንደሞኝ ተቆጥራ፣ አሁን ደግሞ እነዚህ ሁለቱ ሶስት ሰዓት ሙሉ ራበን እያሉ ሲነጫነጩ እንዳልቆዩ
ስለቀዘቀዘ አንበላም ይላሉ… አይ ልጆች!

ክሪስ በየጠዋቱ በሽርሽር ቅርጫት መጥቶ ከሚወረወርልን የችኮላ ምግብ በተለየ በሚጥም ሁኔታ የተሰራውን ምግብ በመብላት በደስታ አይኖቹን ጨፈነ። እውነት ለመናገር አያታችን አንድም ቀን ረስታን አታውቅም።
👍316🥰1