#የተወጋ_ልብ
፡
፡
#ክፍል_ስድስት
፡
፡
#ድርሰት_በትክክል_ገና
.....“ግራ ገባኝ አኮ ሸዋዬ? እስቲ የተፈጠረውን ነገር በጥሞና አስረጅኝ?” እየተሽቆጠቆጠ ጠየቃት። ሸዋዬ ቱግ! ብላ ተነሳች።
“ግራ ይግባህ!! የእናት የአባቴ አምላክ ግራ ያግባህ!! ድሮውንም ግራ
ነበርክ! አሁንም ግራ ነህ!” ብልጭ! አለበት፡፡ በቆመችበት በቃሪያ ጥፊ
ሲደረግምባት እንደ ብራቅ ጮኽችና አልጋዋ ላይ በጀርባዋ ፍንችር ብላ
ወደቀች። ከዚያም የመኝታ ክፍሉ በር እንደ ቦምብ ጮሆ የኮርኒሱን ቆሻሻ እስከሚያራግፈው ድረስ አላትሞ ዘጋባትና በቀጥታ ጌትነት ወደተኛበት ክፍል መጣ፡፡
“ኢልመ ሞክራ !” ጮኽበት፡፡ “የመኩሪያ ልጅ!!” በለበጣ አጠራር፡ ጌትነት
በስማው ጩኽት ተደናግጦ ብንን.. አለ፡፡ ጭንቅላቱ ላይ ከባድ ሸክም ያረፈበት መሰለው፡፡ የት እንዳለ የት እንደወደቀ የሚያውቀው ነገር አልነበረም።ጉርሽጥ የመሰሉ ዐይኖቹ እንደተቆጣ አንበሳ ቀልተው ካፈጠጡበት የቶሎሳ ዐይኖች ላይ ተተክለው ቀሩ።
“ቶሌ ኢቦ! ሌንጮ ኬኛ ሜ ዋን ተኤ ኦዴሲ?! ጂአ ለመ ኬሳ አመለኬ
ጶከቴ ባሉ ጀልቀብዴ? 'እሺ እባክህ የኛ አንበሳ? የተፈጠረውን ነገር አውራልን እስቲ! ገና በሁለት ወርህ ሽጋ አመልህን ታወጣው ጀመር?! የተደበቀ ቆንጆ አመልህን?” ባልገባው ቋንቋ አሽሟጠጠው፡፡ ጌትነት በድንጋጤ ተርበተበተ።
“እንዴ..ምን.አደርክ ጋሼ.ቶሎ ሳ?!ከተጋደመበት በፍጥነት ተነስቶ በአክብሮት ሊጨብጠው ተንደፋደፈ። አልቻለም፡፡ ያደረደበት ቶሎ እንዳይ
ነሳ ወደ ታች ጎትቶ ያዘው።
“ሲለኔ ሀዳር ማን ጠየቆ?! አሁን ሲለፈጠረው ታሪክ ቢቻ ቶሎ በሊና
ነጊር!” እየተንጎራደደ ትዕዛዝ ሰጠው፡፡ ጌትነት ስካሩ ሙሉ ለሙሉ አልለቀቀውም ነበር። የቶሎሳን ስሜት በሚገባ ማጤን አልቻለም። እንደዚያም ሆኖ ግን ሃይለ ቃሉ ያልተለመደ ሆነበት፡፡ ደነገጠ፡፡ መጠጥ ጠጥቶ ከነልብሱ ተኝቶ በመገኘቱ፣ ባሳየው አዲስ ያልተገባ ፀባይ ተናዶ የተቆጣው መስሎት በእፍረት ተሸማቀቀና ይቅርታ ሊጠይቀው ብድግ አለ፡፡ ሸዋዬ በቶሎሳ ጭንቅላት ውስጥ ያስቀመጠችው መርዝ መኖሩን የት አውቆት? ማታ ምን እንደሰራ ምን እንዳደረገ የሚያውቀው ነገር የለም።ጠዋት ውጤቱ በግልፅ የሚታየው ስካሩን እንጂ ከስካሩ ጋር ተያይዘው ከተፈ
ጠሩት አስደናቂ ትርኢቶች መካከል አንዷን እንኳ ማስታወስ አልቻለም፡፡
ሰክሮ መገኘቱ በራሱ ትልቅ ድፍረትና ሀጢአት ነውና ጋሼ ቶሎሳ ይቅር
እንዲለው ሊለምነው ፈልጎ እንደምንም ብሎ ከአልጋው ላይ ተነሳ።
“እባክህ ጋሼ ቶሎሳ አትቀየመኝ፡፡ የቤት ጠላ ነው ብዬ ነው ከአቅሜ በላይ
የጠጣሁት። ይቅርታ አድርግልኝ?” አንገቱን አቀረቀረ፡፡
“ኢሱ የራሱ ቺጊር ኖ! ሀቂሙን ገሚቶ ጠጣው የራሱ ጉዳይ ኖ! ቶሎሳ
ጉዳይ አዶለም! ሰካራም ! ቢራ አልጠጣውም ሀላልሺም?! አሁን ሚን
ገኘሺና ጠጣሺው?!” እነዚያ ትናንሽ ዐይኖቹን እንደ ነብር አጉረጠረጠበት። ጌትነት ትናንት እና ዛሬ ተቀላቅለውበት ምንም ነገር እንዳልተፈጠረ ሁሉ ትናንት አዲስ ክስተት አዲስ ትርዒት የተፈፀመበት ቀን እንዳልነበረ ሁሉ ተረጋግቶ ነበር የተኛው፡፡ ሆዱ የቀራጭ አቅማዳ እስከሚመስል ድረስ ጠላ ሲጋት ማምሸቱን እንጂ ስለሌላው ጣጣ አሁን ቶሎሳ ስለሚያወራው ታሪክ ምንም የሚያውቀው ነገር አልነበረም፡፡ ራቱን ምን
እንደበላ እንኳ አያስታውስም፡፡ ቶሎሳ እንደዚያ ግስላ ሆኖ ሲያንባርቅ
ግራ ተጋባ፡፡ ተደነጋገረው።
“እባክህ ጋሼ ቶሎሳ ሁለተኛ አላደርገውም፡፡ አይለመደኝም። የዛሬን ብቻ ተለመነኝ፡፡ ቤቴ ነው ብዬ ተዝናንቼ ነው የጠጣሁት” በድጋሚ ተለማመነው። ቶሎሳ ብው አለ፡፡
“ኢሄ ሶዬ ጤና ኤለም ሂንዴ?!ሲለጠላ ወሬ አልፈሊጊም!! አይገባሂም
ሂንዴ?! ሲለሆነ ነገር ቢቻ ነጊር! ሲለፈጠረው ታሪክ ሀንዲም ሳታስቀሮ
ፊሪጥ ፊሪጥ አዲርጊና ነጊር!!”
ጌትነት ስለምን እንደሚያወራ ውሉን መጨበጥ ተሳነው።ድንብርብሩ
ወጣ! ዐይኖቹን ጭፍን ክድን... ጭፍን... ክድን... ጭፍን... ክድኝ...
አደረጋቸው። የቶሎሳን ያልተለመደ ቁጣና ጩኽት፣ በንዴት የተለዋወጠ ፊት ሲመለከት ክፉኛ ተደናገጠ፡፡ ዐይኖቹንም ጆሮዎቹንም ተጠራጠረ፡፡ ጆሮውን ኮረኮረ፡ እትዬ ሸዋዬ የቶሎሳን ጩኽት ስምታ ሮጣ
የምትመጣ መሰለው፡፡ እዚያ ደርሳ...“ምነው ቶሎሳ? ምን ሆናችሁ?
ምን ነካችሁ? ጉረቤት ሁሉ እስኲሚረበሽ ድረስ የምን ጩኽት ነው? ቢጠጣ ምን አለበት ታዲያ? የቤት ጠላ ነው የጠጣው። መሸታ ቤት ሄዶ
አልጠጣ? በል አሁን ይብቃህ!”ብላ ቶሎሳን ስትገስፀው በሀሳቡ ታየው።
እትዬ ሸዋዬ መጥታ እንድትገላግለው ተመኘ፡፡
“ምን እንደምትለኝ ማወቅ አልቻልኩም እኮ ጋሼ ቶሎሳ? እትዬ ሽዋዬ
ጩኽትህን ስትሰማ ትደነግጣለች። ሁለተኛ አይለመደኝም፡፡ እባክህ
የዛሬን ብቻ ይቅርታ አድርግልኝ?” እንዳይገረፍ የሚሽቆጠቆጥ ህፃን ልጅ
መሰለ፡፡ ቶሎሳ አውቆ ሊያታልለውና ሊቀልድበት የሚያደርገው የብልጣ
ብልጥነት ሙከራ መስሎት የበለጠ ተናደደ። ጨስ...“ሀቲቀባጢር!” አለና
ዘሎ አንገቱን አነቀው፡፡ መቼም የአደነጋገጡ ነገር አይነሳ። ከመውደቅ
ተረፈ እንጂ ሰማይ በላዩ ላይ የተደፋበት ነበር የመሰለው። ተርበደበደ::
“ምንድነው ነው የምትለኝ ጋሼ ቶሎሳ?!” እሱም ሰውነቱ በንዴት ማተኮስ ጀመረ። ቀስ አለና አንገቱን ጨምድዶ የያዘውን የቶሎሳን እጅ ከአንገቲ ላይ አላቀቀ። በጉልበት ቢያያዙ ቶሎሳን ጃርት የበላው ዱባ አስመስሎ እንደሚሄድ የታወቀ ነው። በፍፁም የሚመጣጠኑ አይደሉም፡፡ ጌትነት ጠፍሮ የያዘው የአክብሮትና የፍርሃት ልጓም ብቻ ነው። በሱ እምነት
ምንም የፈፀመው ወንጀል፣ ምንም የሰራው ሀጢአት የለም፡፡ የፈፀመው
ወንጀልና የስራው ሀጢአት ቢኖር ጠላ ጠጥቶ ሰክሮ መገኘቱ ነው::
ለዚህ ጥፋቱ ደግሞ እየተርበተበተ ቶሎሳን ይቅርታ እየጠየቀው ነው::
ነገሮች ቀስ በቀስ ግልፅ እየሆኑ የመጡት ቶሎሳ እንደታረደ በሬ በሚጓጉር ድምፅ ማጓራት ሲጀምር ነበር።
“ሸዋዬን ሚንዲኖ ያደረገች?!በሚን ሚኪናቲኖ ቀየመች?!ለሚንዲኖ ማቲናገሮ?!” ጮኽና በድጋሚ አንገቱን ሊያንቀው መጣበት፡፡ ጌትነት ክው አለ።
“ም..ምን….ምን?...” ከድንጋጤው የተነሳ በፍፁም የሱ የራሱ መሆኑን በሚያጠራጥር አንደበት ተንተባተበ፡፡
“ሚንዲኖ ደረካት?! ሚናባቲኖ ሆነች?!” በድጋሚ ጮኽበት።
“እ...እኔ....እኔን ...ነኝ...እኔን ምምንን ...አደረገኝ ..አለች ” አፉ
ተሳሰረ።
“አሃሃሃ!.…ሌባ ሀይና ደረቂ መሊሶ ሊብ ዲቂቂ ሀሉ! ኢንደ ታናሽ ሆንዲሙ መልኪቼው ኢንደ ታላቅ ሆንዲሙ አከቢራል መሲሎት ነበረው።አባቱ ሁለታ ከቢዶት ኢናቱና ኢቱን ኢንዲረዳው ፈለኩት።ተሪፎት አዳላም ከባሌ ጠራሁት። ካፊሎ ኢንዲበላው ሆንዲሙን አኪል ኢምነት ጣልኩት።አንታ አላ ቢሎ ሁጭ አደረው ሆንጀል ደረገና ሚስቱን
በሳጫት ሀደረው፡፡ ኢዝጋቤር ቢዲሩን ኪፈል! ስኪሮ ቲዳሩን ቢጥቢ ኡጡን ሲላወጣው መስጊናሎ!ሆ! ኢዝጋቤር!!” እሱ የሰማዩ ጌታ ብድሩን ብ
እንዲከፍለው ወደ ሰማይ ቀና ብሎ ተመለከተ። ከዚያም ተስፋ በቆረጠ
ሁኔታ ጌትነትን ትክ ብሎ አየው፡፡ ያውም ቶሎሳ ጨርቅ ከመጋፈፍ ድንበር ወዲህ ባለ ምክንያት አስቀይሟት ይሆናል በሚል ግምት እንጂ ጉዳዩ ከዚያ የዘለለ አደገኛ ሙከራ እንደነበረ ቢያውቀው ኖሮ ትርዒቱ
ከዚህ የተለየ ገጽታ በኖረው ነበር፡፡ ቶሎሳ በጌትነት ላይ የተመሰረተበት ክስ ሌላ መሆኑን የተፈጠረው ተአምር ሊገምተው የማይችለው መሆኑን ቢያውቅ ኖሮ ጉድ ይፈላ ነበር፡፡ ደግነቱ ጌትነትን እንደዚያ ሊያስጠረጥረው በሚያስችለው ሁኔታ ውስጥ አላገኘውም፡፡ ልብሱን እንኳ ሳያወልቅና ሰክሮ እንደተጋደመ ነው ያገኘው። ቶሎሳ በፍፁም
፡
፡
#ክፍል_ስድስት
፡
፡
#ድርሰት_በትክክል_ገና
.....“ግራ ገባኝ አኮ ሸዋዬ? እስቲ የተፈጠረውን ነገር በጥሞና አስረጅኝ?” እየተሽቆጠቆጠ ጠየቃት። ሸዋዬ ቱግ! ብላ ተነሳች።
“ግራ ይግባህ!! የእናት የአባቴ አምላክ ግራ ያግባህ!! ድሮውንም ግራ
ነበርክ! አሁንም ግራ ነህ!” ብልጭ! አለበት፡፡ በቆመችበት በቃሪያ ጥፊ
ሲደረግምባት እንደ ብራቅ ጮኽችና አልጋዋ ላይ በጀርባዋ ፍንችር ብላ
ወደቀች። ከዚያም የመኝታ ክፍሉ በር እንደ ቦምብ ጮሆ የኮርኒሱን ቆሻሻ እስከሚያራግፈው ድረስ አላትሞ ዘጋባትና በቀጥታ ጌትነት ወደተኛበት ክፍል መጣ፡፡
“ኢልመ ሞክራ !” ጮኽበት፡፡ “የመኩሪያ ልጅ!!” በለበጣ አጠራር፡ ጌትነት
በስማው ጩኽት ተደናግጦ ብንን.. አለ፡፡ ጭንቅላቱ ላይ ከባድ ሸክም ያረፈበት መሰለው፡፡ የት እንዳለ የት እንደወደቀ የሚያውቀው ነገር አልነበረም።ጉርሽጥ የመሰሉ ዐይኖቹ እንደተቆጣ አንበሳ ቀልተው ካፈጠጡበት የቶሎሳ ዐይኖች ላይ ተተክለው ቀሩ።
“ቶሌ ኢቦ! ሌንጮ ኬኛ ሜ ዋን ተኤ ኦዴሲ?! ጂአ ለመ ኬሳ አመለኬ
ጶከቴ ባሉ ጀልቀብዴ? 'እሺ እባክህ የኛ አንበሳ? የተፈጠረውን ነገር አውራልን እስቲ! ገና በሁለት ወርህ ሽጋ አመልህን ታወጣው ጀመር?! የተደበቀ ቆንጆ አመልህን?” ባልገባው ቋንቋ አሽሟጠጠው፡፡ ጌትነት በድንጋጤ ተርበተበተ።
“እንዴ..ምን.አደርክ ጋሼ.ቶሎ ሳ?!ከተጋደመበት በፍጥነት ተነስቶ በአክብሮት ሊጨብጠው ተንደፋደፈ። አልቻለም፡፡ ያደረደበት ቶሎ እንዳይ
ነሳ ወደ ታች ጎትቶ ያዘው።
“ሲለኔ ሀዳር ማን ጠየቆ?! አሁን ሲለፈጠረው ታሪክ ቢቻ ቶሎ በሊና
ነጊር!” እየተንጎራደደ ትዕዛዝ ሰጠው፡፡ ጌትነት ስካሩ ሙሉ ለሙሉ አልለቀቀውም ነበር። የቶሎሳን ስሜት በሚገባ ማጤን አልቻለም። እንደዚያም ሆኖ ግን ሃይለ ቃሉ ያልተለመደ ሆነበት፡፡ ደነገጠ፡፡ መጠጥ ጠጥቶ ከነልብሱ ተኝቶ በመገኘቱ፣ ባሳየው አዲስ ያልተገባ ፀባይ ተናዶ የተቆጣው መስሎት በእፍረት ተሸማቀቀና ይቅርታ ሊጠይቀው ብድግ አለ፡፡ ሸዋዬ በቶሎሳ ጭንቅላት ውስጥ ያስቀመጠችው መርዝ መኖሩን የት አውቆት? ማታ ምን እንደሰራ ምን እንዳደረገ የሚያውቀው ነገር የለም።ጠዋት ውጤቱ በግልፅ የሚታየው ስካሩን እንጂ ከስካሩ ጋር ተያይዘው ከተፈ
ጠሩት አስደናቂ ትርኢቶች መካከል አንዷን እንኳ ማስታወስ አልቻለም፡፡
ሰክሮ መገኘቱ በራሱ ትልቅ ድፍረትና ሀጢአት ነውና ጋሼ ቶሎሳ ይቅር
እንዲለው ሊለምነው ፈልጎ እንደምንም ብሎ ከአልጋው ላይ ተነሳ።
“እባክህ ጋሼ ቶሎሳ አትቀየመኝ፡፡ የቤት ጠላ ነው ብዬ ነው ከአቅሜ በላይ
የጠጣሁት። ይቅርታ አድርግልኝ?” አንገቱን አቀረቀረ፡፡
“ኢሱ የራሱ ቺጊር ኖ! ሀቂሙን ገሚቶ ጠጣው የራሱ ጉዳይ ኖ! ቶሎሳ
ጉዳይ አዶለም! ሰካራም ! ቢራ አልጠጣውም ሀላልሺም?! አሁን ሚን
ገኘሺና ጠጣሺው?!” እነዚያ ትናንሽ ዐይኖቹን እንደ ነብር አጉረጠረጠበት። ጌትነት ትናንት እና ዛሬ ተቀላቅለውበት ምንም ነገር እንዳልተፈጠረ ሁሉ ትናንት አዲስ ክስተት አዲስ ትርዒት የተፈፀመበት ቀን እንዳልነበረ ሁሉ ተረጋግቶ ነበር የተኛው፡፡ ሆዱ የቀራጭ አቅማዳ እስከሚመስል ድረስ ጠላ ሲጋት ማምሸቱን እንጂ ስለሌላው ጣጣ አሁን ቶሎሳ ስለሚያወራው ታሪክ ምንም የሚያውቀው ነገር አልነበረም፡፡ ራቱን ምን
እንደበላ እንኳ አያስታውስም፡፡ ቶሎሳ እንደዚያ ግስላ ሆኖ ሲያንባርቅ
ግራ ተጋባ፡፡ ተደነጋገረው።
“እባክህ ጋሼ ቶሎሳ ሁለተኛ አላደርገውም፡፡ አይለመደኝም። የዛሬን ብቻ ተለመነኝ፡፡ ቤቴ ነው ብዬ ተዝናንቼ ነው የጠጣሁት” በድጋሚ ተለማመነው። ቶሎሳ ብው አለ፡፡
“ኢሄ ሶዬ ጤና ኤለም ሂንዴ?!ሲለጠላ ወሬ አልፈሊጊም!! አይገባሂም
ሂንዴ?! ሲለሆነ ነገር ቢቻ ነጊር! ሲለፈጠረው ታሪክ ሀንዲም ሳታስቀሮ
ፊሪጥ ፊሪጥ አዲርጊና ነጊር!!”
ጌትነት ስለምን እንደሚያወራ ውሉን መጨበጥ ተሳነው።ድንብርብሩ
ወጣ! ዐይኖቹን ጭፍን ክድን... ጭፍን... ክድን... ጭፍን... ክድኝ...
አደረጋቸው። የቶሎሳን ያልተለመደ ቁጣና ጩኽት፣ በንዴት የተለዋወጠ ፊት ሲመለከት ክፉኛ ተደናገጠ፡፡ ዐይኖቹንም ጆሮዎቹንም ተጠራጠረ፡፡ ጆሮውን ኮረኮረ፡ እትዬ ሸዋዬ የቶሎሳን ጩኽት ስምታ ሮጣ
የምትመጣ መሰለው፡፡ እዚያ ደርሳ...“ምነው ቶሎሳ? ምን ሆናችሁ?
ምን ነካችሁ? ጉረቤት ሁሉ እስኲሚረበሽ ድረስ የምን ጩኽት ነው? ቢጠጣ ምን አለበት ታዲያ? የቤት ጠላ ነው የጠጣው። መሸታ ቤት ሄዶ
አልጠጣ? በል አሁን ይብቃህ!”ብላ ቶሎሳን ስትገስፀው በሀሳቡ ታየው።
እትዬ ሸዋዬ መጥታ እንድትገላግለው ተመኘ፡፡
“ምን እንደምትለኝ ማወቅ አልቻልኩም እኮ ጋሼ ቶሎሳ? እትዬ ሽዋዬ
ጩኽትህን ስትሰማ ትደነግጣለች። ሁለተኛ አይለመደኝም፡፡ እባክህ
የዛሬን ብቻ ይቅርታ አድርግልኝ?” እንዳይገረፍ የሚሽቆጠቆጥ ህፃን ልጅ
መሰለ፡፡ ቶሎሳ አውቆ ሊያታልለውና ሊቀልድበት የሚያደርገው የብልጣ
ብልጥነት ሙከራ መስሎት የበለጠ ተናደደ። ጨስ...“ሀቲቀባጢር!” አለና
ዘሎ አንገቱን አነቀው፡፡ መቼም የአደነጋገጡ ነገር አይነሳ። ከመውደቅ
ተረፈ እንጂ ሰማይ በላዩ ላይ የተደፋበት ነበር የመሰለው። ተርበደበደ::
“ምንድነው ነው የምትለኝ ጋሼ ቶሎሳ?!” እሱም ሰውነቱ በንዴት ማተኮስ ጀመረ። ቀስ አለና አንገቱን ጨምድዶ የያዘውን የቶሎሳን እጅ ከአንገቲ ላይ አላቀቀ። በጉልበት ቢያያዙ ቶሎሳን ጃርት የበላው ዱባ አስመስሎ እንደሚሄድ የታወቀ ነው። በፍፁም የሚመጣጠኑ አይደሉም፡፡ ጌትነት ጠፍሮ የያዘው የአክብሮትና የፍርሃት ልጓም ብቻ ነው። በሱ እምነት
ምንም የፈፀመው ወንጀል፣ ምንም የሰራው ሀጢአት የለም፡፡ የፈፀመው
ወንጀልና የስራው ሀጢአት ቢኖር ጠላ ጠጥቶ ሰክሮ መገኘቱ ነው::
ለዚህ ጥፋቱ ደግሞ እየተርበተበተ ቶሎሳን ይቅርታ እየጠየቀው ነው::
ነገሮች ቀስ በቀስ ግልፅ እየሆኑ የመጡት ቶሎሳ እንደታረደ በሬ በሚጓጉር ድምፅ ማጓራት ሲጀምር ነበር።
“ሸዋዬን ሚንዲኖ ያደረገች?!በሚን ሚኪናቲኖ ቀየመች?!ለሚንዲኖ ማቲናገሮ?!” ጮኽና በድጋሚ አንገቱን ሊያንቀው መጣበት፡፡ ጌትነት ክው አለ።
“ም..ምን….ምን?...” ከድንጋጤው የተነሳ በፍፁም የሱ የራሱ መሆኑን በሚያጠራጥር አንደበት ተንተባተበ፡፡
“ሚንዲኖ ደረካት?! ሚናባቲኖ ሆነች?!” በድጋሚ ጮኽበት።
“እ...እኔ....እኔን ...ነኝ...እኔን ምምንን ...አደረገኝ ..አለች ” አፉ
ተሳሰረ።
“አሃሃሃ!.…ሌባ ሀይና ደረቂ መሊሶ ሊብ ዲቂቂ ሀሉ! ኢንደ ታናሽ ሆንዲሙ መልኪቼው ኢንደ ታላቅ ሆንዲሙ አከቢራል መሲሎት ነበረው።አባቱ ሁለታ ከቢዶት ኢናቱና ኢቱን ኢንዲረዳው ፈለኩት።ተሪፎት አዳላም ከባሌ ጠራሁት። ካፊሎ ኢንዲበላው ሆንዲሙን አኪል ኢምነት ጣልኩት።አንታ አላ ቢሎ ሁጭ አደረው ሆንጀል ደረገና ሚስቱን
በሳጫት ሀደረው፡፡ ኢዝጋቤር ቢዲሩን ኪፈል! ስኪሮ ቲዳሩን ቢጥቢ ኡጡን ሲላወጣው መስጊናሎ!ሆ! ኢዝጋቤር!!” እሱ የሰማዩ ጌታ ብድሩን ብ
እንዲከፍለው ወደ ሰማይ ቀና ብሎ ተመለከተ። ከዚያም ተስፋ በቆረጠ
ሁኔታ ጌትነትን ትክ ብሎ አየው፡፡ ያውም ቶሎሳ ጨርቅ ከመጋፈፍ ድንበር ወዲህ ባለ ምክንያት አስቀይሟት ይሆናል በሚል ግምት እንጂ ጉዳዩ ከዚያ የዘለለ አደገኛ ሙከራ እንደነበረ ቢያውቀው ኖሮ ትርዒቱ
ከዚህ የተለየ ገጽታ በኖረው ነበር፡፡ ቶሎሳ በጌትነት ላይ የተመሰረተበት ክስ ሌላ መሆኑን የተፈጠረው ተአምር ሊገምተው የማይችለው መሆኑን ቢያውቅ ኖሮ ጉድ ይፈላ ነበር፡፡ ደግነቱ ጌትነትን እንደዚያ ሊያስጠረጥረው በሚያስችለው ሁኔታ ውስጥ አላገኘውም፡፡ ልብሱን እንኳ ሳያወልቅና ሰክሮ እንደተጋደመ ነው ያገኘው። ቶሎሳ በፍፁም
👍4
#ያልታበሱ_እንባዎች
፡
፡
#ክፍል_ስድስት
፡
፡
#ድርሰት_በአሰፋ_በቀለ_ገየሱስ
...ወይዘሮ እልፍነሽ አጭር ወፍራም ናቸው፣ ከወገባቸው ጎንበስ ያሉ ፀጉራቸወም በአጭርና ሸበቶ፤ በባህሪያቸው ወራኛ የሚባሉ ናቸው፤ አንዷን ከአስር
በላይ የሚያባዙ፤ ለውሸት ልክ የሌላቸው:: ከዚሁ ባህሪያቸው በመነጨ የጎረቤት ሰው ሁሉ እልፍነሽ ወሬ እፈሽ ይላቸዋል፡፡
ሽዋዬ ቤት ወስጥ ገብታ ራሷ ወንበር ሳብ አድርጋ ስትቀመጥ ወይዘሮ እልፍነሽ እጆቻቸውን በወገባቸው ላይ አጣምረው ከፊቷ ቆሙ፡፡ ለወሬው በጣም
የቸኮሉ ይመስላለ::
«እንደው ምን አግኝቶሽ ይሆን ልጄ?» ሲሉ ጠየቋት::
«ቁጭ በሏ!» አለቻቸው ሸዋዬ ከንፈሯን በምላሷ እያራስች፡፡ የእጆቿን መዳፎች አጋጥማ በጉልበቶቿ መሀል አጥብቃ ይዛቸዋለች፡፡
ወይዘሮ እልፍነሽ ለወሬው ሰፍ ብለዋል። ጠበብ ካለች አፋቸው ውስጥ ከአራት በላይ የማይታዩ ጥርሶቻቸውን ገለጥ አድርገው ፈገግ እያሉ ተቀመጡና፡-
«እስቲ ንገሪኝ ልጄ!» አሏት፡፡
«ጉድ የምትሰሩኝ እኮ እናንተ ጎረቤቶቼ ናችሁ!» አለቻቸው ሽዋዬ ምላሷን በከንፈሮቿ ዳር እና ዳር ግራና ቀኝ ወጣ ገባ እያረገች ወይዘሮ እልፍነሽ ደረታቸውን በእጃቸው ደሰቅ አረጉና «ውይ በሞትኩት! ምነው? ምን አደረግን?»
«የእህቴ ህይወት ሲበላሽ እያያችሁ ዝም ትሉኛላችሁ?»
«ምነው? ምን አገኛት?»
«አርግዛ ትምህርቷን ብታቋርጥስ?»
«እንዴ!» አሉ ወይዘሮ አልፍነሽ ነገሩን እንደማቃለል ዓይነት በሚያስመስል አነጋገር፡፡ «እጮኛዋ ባለሙያ አይደል እንዴ! ችግር ቢፈጥር ኣሽቀንጥሮ ይጥልላት የለ!» ካሉ በኋላ አፋቸውን የበለጠ ወደ ሸዋዬ ጠጋ በማድረግ «አአሁን ቀደምስ
ችግሩ ተፈጥሮ ገላገላት ተብሎ ብለው ሳይጨርሰ ሽዋዬ ቀደመቻቸው::
«ምን አሉ?» አለች ዓይኗን ፍጥጥ አድርጋ እያየቻቸው። እጮኛዋ ያሏት ነገር ከተቀመጠችበት አንጥሮ ሊያነሳት ሲል ደሞ የወርጃ ነገር ጨመሩባትና
በአለችበት ኩርምትምት አለች።
«ኧረ ተይኝ እቴ!» ብለው ወይዘሮ እልፍነሽ እንደ መግደርደር ዓይነት ወደ ውጭጉዳይ አየት ካደረጉ በኋላ እንደገና ወደ ሽዋዬ መለስ በማለት «በአንቺ እህት ስንት
ልጃገረዶች እየቀኑባት ደሞ እንዲህ ያለ ሥጋት ይደረብሽ እንዴ? ሆሆይ...»
ሸዋዬ በባሰ ድንጋጤ ሰውነቷ ሽምቅቅ ብሎ መንፈሷ ድክም፣ ልቧም ስንፍ አለና በተራዘመ የቃል አወጣጥ «አ ሶ ር ዳ ለ ች ነው የሚሉኝ ስትል ጠየቀቻቸው::
«ገላግሏት!»
ሸዋዬ አሁንም ድክም ባለ መንፈስ «አ መ ስ ግ ና ለ ሀ:!» አለቻቸውና
ከተቀመጠችበት በቀስታ ብድግ አለች። ወይዘሮ እልፍነሽ እወነትም አፍሰው አቃሟት፡፡
«ጠሐይ ይብረድልሽ እንጂ!» አሏት ወይዘሮ እልፍነሽ እኚያኑ
ጥርሶቻቸውን ገለጥ እያደረጉ፡፡
«ቤቴ ሄጄ ማረፍ እፈልጋለሁ። ደህና ዋሉ!» ብላቸው ወጣች፡፡
ወይዘሮ እልፍነሽ አሁንም እጃቸውን በወገባቸው ላይ አጣምረው እስር እስሯ እየሄዱ በሹክሹክታ ዓይነት «እይው ልጄ፧ እኔ እኮ ቀድሜ ጠርጥሪያለሁ፣
ብታይ አንቺ እግርሽ ወጣ ያለ ጊዜ እሱ ዘሎ ጥልቅ! ትናት ዘሎ ጥልቅ! ዛሬም ዘሎ ጥልቅ ሲል እያየሁ ሆዴ በጣም ይፈራ ነበር፡፡» አሏት፡፡
ከቤት ይዟት ወጥቶ ያውቃል?»
«ኧረ በገዛ ቤትሽ ውስጥ እቴ! ደሞ የምን ወደ ውጪ ሆይ…?» አሉና
«ማናት ይቺ እቴ ስሟን አምጪልኝ፡ ይቺ የወይዘሮ ዘነቡ ሠራተኛ?»
«ፋንታዬ?»
“እ! እሷ ቲራቲር ስታይ አይደል እንዴ የምትውለው፤ እሷን ብትጠይቂያት እኮ ጉድ ትነግርሻለች፡፡»
ሽዋዬ ነገሩ ሁሉ ገባት። ወሬው ሁሉ ከፋንትዬ እንደሚመነጭ ተረዳች፡፡
ይሁንና ብትጠይቃት ደፍራ እውነቱን ላትነግራት እንደምትችል ገመተች። ለነገሩ ወሬ በቅቷታል፡፡ ከእንግዲህ ታፈሡ ብቻ ቀረቻት፣ በእሷ ግምት አስቻለውና
ሔዋንን የምታገናኝ ታፈሡ እንደምትሆን በማመን፡፡
ሸዋዬ በዕለቱ እህል ውሃ አላሰኛትም ሔዋን ምሳ አዘጋጅታ እየጠበቀቻት ቢሆንም ቤቷ እንደ ደረሰች የሔዋንን ዓይኖች ቀና ብላ እንኳ ሳታይ በቀጥታ አልጋዋ ላይ ወጥታ ጥቅልል ብላ ተኛች፡፡ በዚያው መሽ፡፡ ቀኑም በለሊት ተተካ፡፡ ያ ሁሉ ሆና ሽዋዬ በዓይኗ ላይ እንቅልፍ አልዞረም፡፡ ይልቁንም እንኳን ራሷ ለአልጋዋም አልመቻት ብላ በየደቂቃው በመገላበጥ ስታንቋቋት አደረች፡፡
በማግስቱ ጠዋት ሔዋን ወደ ትምህርት ቤት ስትሄድ ልክ እግሯ ከቤት እንደ ወጣ ሸዋዬ ልታደርግ ስታስብ ከአደረችው እቅድ ውስጥ የመጀመሪያውን መፈፀም ጀመረች:: ሔዋንና አስቻለው የተፃፃፉት የፍቅር ደብዳቤ ካለ ብላ ደብተሮቿን መፈተሽ ያዘች ፤ ገፅ በገፅ እያገላበጠች፣ የደብተሮቹን መሸፈኛ እየገለጠችና ዘቅዝቃ እያራገፈች በረበረቻቸው። የሔዋን ቅያሪ ልብሶች
አልቀሯትም፡፡ ኪሶቿን ሁሉ ዳበሰቻቸው፡፡ ግን ምንም ነገር ሳታገኝ ቀረች፡፡
ሲደክማት አልጋዋ ላይ ቁጭ አለች:: ግን ደግሞ አንድ ነገር ትዝ አላት። የድካሟ ምክንያት ርሀብ ጭምር ነው:: ከትናንት ምሣ ጀምሮ እስከ ዛሬ ቁርስ ሰዓት ድረስ ምንም አልቀመሰችምና ወደ ምግብ አዘነበለች፡፡ በእርግጥም ከነውዝፉ አጠቃለለችው:: በንዴት ውስጥ ስለነበረች አጎራረሷ እንኳ ጤናማ አልነበረም ቶሎ
ቶሎ ጎሰጎሰችው።
ከታፈሡ ጋር የምትገናኝበት ስዓት በመከራ ደረሰ። ጠዋት ወደ ታፈሡ ቤት መሄድ አልቃጣችም፤ በአንድ በኩል ለጠብ ነው የምትፈልጋት! በሌላ በኩል ደግሞ አስቻለውም ቢሆን ከታፈሡ ቤት አይጠፋምና፡፡ በሁለተኛው ፈረቃ
የዕረፍት ሰዓት ነው ከታፈሡ ጋር የተገናኘችው፡፡ በዲላ አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ቅጥር ግቢ ውስጥ መሀል ላይ በምትገኘው ባንዲራ ሥር ሆና
ጠራቻትና አብረው እንደተቀመጡ ሸዋዬ ዓይኗን እፍጣ፣ ጥርሷን አግጣ፡-
«ስሚ አንቺ!» አለቻት፡፡
«ወይ» ታፈሡ ድንግጥ በማለት፡፡
«እህቴን ከአበ-ልጅሽ ጋር አቃጥረሽ አበላሽሻት አይደል?? »
«ኦ» ታፈሡ ሁለመናዋን ነዘር እያደረጋት።
« አላደረኩም በያ?»
«ጓደኛዬ ምን እያልሽ ነው?»
«ኧረ ጓደኛሽን ወዲያ ፈልጊ!»
«ከአንቺ የበለጠ ምን ጓደኛ እለኝ?» አለቻት ታፈሡ ነገሩ እየገባት ሂዶ ፈገግ እያለች።
«ጥሩ አቃጣሪ ኖረሻል፤ ጉድሽ ሁሉ ወጣ?»
«አቀዛሽው ሽዋዬ»
« አቃጣሪ ማለቱ? እንዲያውም ሲያንስሽ ነው»
«ጨምሪልኛ ኪም ኪም ኪም ኪም!
« አሁን ሳቂ! የምታለቅሽበት ጊዜ ይመጣል::»
«እጠብቃለኋ ኪም ኪም ኪም ኪም» ታፈው እሁንም፡፡
«እንዲህ ስትንከተከች ትንሽም አታፍሪ?» ሽዋዬ ውስጧ ብግን እያለ፡፡
«ምንም አላፍር ሽዋዬ! ምንም በማላውቀው ነገር ይህን ያህል ካልሽኝ ምናልባት ሁለቱ ተዋድደው ከአገኘኋቸው እንዲያውም እንዲያውም አጋባቸዋለሁ::»
«ኣ» ሸዋዬ ቆሽቷ እያረረ፡፡
«በእርግጥ ሁለቱ ተዋደው ከሆነ ወደ ኋላ አልልም! ታይኝ የለ!» ብላት ታፈሡ ከሸዋዬ ፊት ዘወር አለች።
ሸዋዬ ግራ ግብት እንዳላት ነበር ከዚያ በኋላ ያለውን ጊዜ ያሳለፈችው፡፡
የታፈሠ ሁኔታ ስለ ሔዋንና አስቻለው ፍቅር ብዙም ፍንጭ አልሰጣትም።
በእርግጥ ስለዚሁ ጉዳይ ባለፈው ለሊት በምታስላስልበት ጊዜ በተለይ ከወይዘሮ እልፍነሽ የሰማችው ወሬ ለጊዘው ቢያናድዳትም በእውነትነቱ ግን ተጠራጥረዋለች፡፡
፡
፡
#ክፍል_ስድስት
፡
፡
#ድርሰት_በአሰፋ_በቀለ_ገየሱስ
...ወይዘሮ እልፍነሽ አጭር ወፍራም ናቸው፣ ከወገባቸው ጎንበስ ያሉ ፀጉራቸወም በአጭርና ሸበቶ፤ በባህሪያቸው ወራኛ የሚባሉ ናቸው፤ አንዷን ከአስር
በላይ የሚያባዙ፤ ለውሸት ልክ የሌላቸው:: ከዚሁ ባህሪያቸው በመነጨ የጎረቤት ሰው ሁሉ እልፍነሽ ወሬ እፈሽ ይላቸዋል፡፡
ሽዋዬ ቤት ወስጥ ገብታ ራሷ ወንበር ሳብ አድርጋ ስትቀመጥ ወይዘሮ እልፍነሽ እጆቻቸውን በወገባቸው ላይ አጣምረው ከፊቷ ቆሙ፡፡ ለወሬው በጣም
የቸኮሉ ይመስላለ::
«እንደው ምን አግኝቶሽ ይሆን ልጄ?» ሲሉ ጠየቋት::
«ቁጭ በሏ!» አለቻቸው ሸዋዬ ከንፈሯን በምላሷ እያራስች፡፡ የእጆቿን መዳፎች አጋጥማ በጉልበቶቿ መሀል አጥብቃ ይዛቸዋለች፡፡
ወይዘሮ እልፍነሽ ለወሬው ሰፍ ብለዋል። ጠበብ ካለች አፋቸው ውስጥ ከአራት በላይ የማይታዩ ጥርሶቻቸውን ገለጥ አድርገው ፈገግ እያሉ ተቀመጡና፡-
«እስቲ ንገሪኝ ልጄ!» አሏት፡፡
«ጉድ የምትሰሩኝ እኮ እናንተ ጎረቤቶቼ ናችሁ!» አለቻቸው ሽዋዬ ምላሷን በከንፈሮቿ ዳር እና ዳር ግራና ቀኝ ወጣ ገባ እያረገች ወይዘሮ እልፍነሽ ደረታቸውን በእጃቸው ደሰቅ አረጉና «ውይ በሞትኩት! ምነው? ምን አደረግን?»
«የእህቴ ህይወት ሲበላሽ እያያችሁ ዝም ትሉኛላችሁ?»
«ምነው? ምን አገኛት?»
«አርግዛ ትምህርቷን ብታቋርጥስ?»
«እንዴ!» አሉ ወይዘሮ አልፍነሽ ነገሩን እንደማቃለል ዓይነት በሚያስመስል አነጋገር፡፡ «እጮኛዋ ባለሙያ አይደል እንዴ! ችግር ቢፈጥር ኣሽቀንጥሮ ይጥልላት የለ!» ካሉ በኋላ አፋቸውን የበለጠ ወደ ሸዋዬ ጠጋ በማድረግ «አአሁን ቀደምስ
ችግሩ ተፈጥሮ ገላገላት ተብሎ ብለው ሳይጨርሰ ሽዋዬ ቀደመቻቸው::
«ምን አሉ?» አለች ዓይኗን ፍጥጥ አድርጋ እያየቻቸው። እጮኛዋ ያሏት ነገር ከተቀመጠችበት አንጥሮ ሊያነሳት ሲል ደሞ የወርጃ ነገር ጨመሩባትና
በአለችበት ኩርምትምት አለች።
«ኧረ ተይኝ እቴ!» ብለው ወይዘሮ እልፍነሽ እንደ መግደርደር ዓይነት ወደ ውጭጉዳይ አየት ካደረጉ በኋላ እንደገና ወደ ሽዋዬ መለስ በማለት «በአንቺ እህት ስንት
ልጃገረዶች እየቀኑባት ደሞ እንዲህ ያለ ሥጋት ይደረብሽ እንዴ? ሆሆይ...»
ሸዋዬ በባሰ ድንጋጤ ሰውነቷ ሽምቅቅ ብሎ መንፈሷ ድክም፣ ልቧም ስንፍ አለና በተራዘመ የቃል አወጣጥ «አ ሶ ር ዳ ለ ች ነው የሚሉኝ ስትል ጠየቀቻቸው::
«ገላግሏት!»
ሸዋዬ አሁንም ድክም ባለ መንፈስ «አ መ ስ ግ ና ለ ሀ:!» አለቻቸውና
ከተቀመጠችበት በቀስታ ብድግ አለች። ወይዘሮ እልፍነሽ እወነትም አፍሰው አቃሟት፡፡
«ጠሐይ ይብረድልሽ እንጂ!» አሏት ወይዘሮ እልፍነሽ እኚያኑ
ጥርሶቻቸውን ገለጥ እያደረጉ፡፡
«ቤቴ ሄጄ ማረፍ እፈልጋለሁ። ደህና ዋሉ!» ብላቸው ወጣች፡፡
ወይዘሮ እልፍነሽ አሁንም እጃቸውን በወገባቸው ላይ አጣምረው እስር እስሯ እየሄዱ በሹክሹክታ ዓይነት «እይው ልጄ፧ እኔ እኮ ቀድሜ ጠርጥሪያለሁ፣
ብታይ አንቺ እግርሽ ወጣ ያለ ጊዜ እሱ ዘሎ ጥልቅ! ትናት ዘሎ ጥልቅ! ዛሬም ዘሎ ጥልቅ ሲል እያየሁ ሆዴ በጣም ይፈራ ነበር፡፡» አሏት፡፡
ከቤት ይዟት ወጥቶ ያውቃል?»
«ኧረ በገዛ ቤትሽ ውስጥ እቴ! ደሞ የምን ወደ ውጪ ሆይ…?» አሉና
«ማናት ይቺ እቴ ስሟን አምጪልኝ፡ ይቺ የወይዘሮ ዘነቡ ሠራተኛ?»
«ፋንታዬ?»
“እ! እሷ ቲራቲር ስታይ አይደል እንዴ የምትውለው፤ እሷን ብትጠይቂያት እኮ ጉድ ትነግርሻለች፡፡»
ሽዋዬ ነገሩ ሁሉ ገባት። ወሬው ሁሉ ከፋንትዬ እንደሚመነጭ ተረዳች፡፡
ይሁንና ብትጠይቃት ደፍራ እውነቱን ላትነግራት እንደምትችል ገመተች። ለነገሩ ወሬ በቅቷታል፡፡ ከእንግዲህ ታፈሡ ብቻ ቀረቻት፣ በእሷ ግምት አስቻለውና
ሔዋንን የምታገናኝ ታፈሡ እንደምትሆን በማመን፡፡
ሸዋዬ በዕለቱ እህል ውሃ አላሰኛትም ሔዋን ምሳ አዘጋጅታ እየጠበቀቻት ቢሆንም ቤቷ እንደ ደረሰች የሔዋንን ዓይኖች ቀና ብላ እንኳ ሳታይ በቀጥታ አልጋዋ ላይ ወጥታ ጥቅልል ብላ ተኛች፡፡ በዚያው መሽ፡፡ ቀኑም በለሊት ተተካ፡፡ ያ ሁሉ ሆና ሽዋዬ በዓይኗ ላይ እንቅልፍ አልዞረም፡፡ ይልቁንም እንኳን ራሷ ለአልጋዋም አልመቻት ብላ በየደቂቃው በመገላበጥ ስታንቋቋት አደረች፡፡
በማግስቱ ጠዋት ሔዋን ወደ ትምህርት ቤት ስትሄድ ልክ እግሯ ከቤት እንደ ወጣ ሸዋዬ ልታደርግ ስታስብ ከአደረችው እቅድ ውስጥ የመጀመሪያውን መፈፀም ጀመረች:: ሔዋንና አስቻለው የተፃፃፉት የፍቅር ደብዳቤ ካለ ብላ ደብተሮቿን መፈተሽ ያዘች ፤ ገፅ በገፅ እያገላበጠች፣ የደብተሮቹን መሸፈኛ እየገለጠችና ዘቅዝቃ እያራገፈች በረበረቻቸው። የሔዋን ቅያሪ ልብሶች
አልቀሯትም፡፡ ኪሶቿን ሁሉ ዳበሰቻቸው፡፡ ግን ምንም ነገር ሳታገኝ ቀረች፡፡
ሲደክማት አልጋዋ ላይ ቁጭ አለች:: ግን ደግሞ አንድ ነገር ትዝ አላት። የድካሟ ምክንያት ርሀብ ጭምር ነው:: ከትናንት ምሣ ጀምሮ እስከ ዛሬ ቁርስ ሰዓት ድረስ ምንም አልቀመሰችምና ወደ ምግብ አዘነበለች፡፡ በእርግጥም ከነውዝፉ አጠቃለለችው:: በንዴት ውስጥ ስለነበረች አጎራረሷ እንኳ ጤናማ አልነበረም ቶሎ
ቶሎ ጎሰጎሰችው።
ከታፈሡ ጋር የምትገናኝበት ስዓት በመከራ ደረሰ። ጠዋት ወደ ታፈሡ ቤት መሄድ አልቃጣችም፤ በአንድ በኩል ለጠብ ነው የምትፈልጋት! በሌላ በኩል ደግሞ አስቻለውም ቢሆን ከታፈሡ ቤት አይጠፋምና፡፡ በሁለተኛው ፈረቃ
የዕረፍት ሰዓት ነው ከታፈሡ ጋር የተገናኘችው፡፡ በዲላ አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ቅጥር ግቢ ውስጥ መሀል ላይ በምትገኘው ባንዲራ ሥር ሆና
ጠራቻትና አብረው እንደተቀመጡ ሸዋዬ ዓይኗን እፍጣ፣ ጥርሷን አግጣ፡-
«ስሚ አንቺ!» አለቻት፡፡
«ወይ» ታፈሡ ድንግጥ በማለት፡፡
«እህቴን ከአበ-ልጅሽ ጋር አቃጥረሽ አበላሽሻት አይደል?? »
«ኦ» ታፈሡ ሁለመናዋን ነዘር እያደረጋት።
« አላደረኩም በያ?»
«ጓደኛዬ ምን እያልሽ ነው?»
«ኧረ ጓደኛሽን ወዲያ ፈልጊ!»
«ከአንቺ የበለጠ ምን ጓደኛ እለኝ?» አለቻት ታፈሡ ነገሩ እየገባት ሂዶ ፈገግ እያለች።
«ጥሩ አቃጣሪ ኖረሻል፤ ጉድሽ ሁሉ ወጣ?»
«አቀዛሽው ሽዋዬ»
« አቃጣሪ ማለቱ? እንዲያውም ሲያንስሽ ነው»
«ጨምሪልኛ ኪም ኪም ኪም ኪም!
« አሁን ሳቂ! የምታለቅሽበት ጊዜ ይመጣል::»
«እጠብቃለኋ ኪም ኪም ኪም ኪም» ታፈው እሁንም፡፡
«እንዲህ ስትንከተከች ትንሽም አታፍሪ?» ሽዋዬ ውስጧ ብግን እያለ፡፡
«ምንም አላፍር ሽዋዬ! ምንም በማላውቀው ነገር ይህን ያህል ካልሽኝ ምናልባት ሁለቱ ተዋድደው ከአገኘኋቸው እንዲያውም እንዲያውም አጋባቸዋለሁ::»
«ኣ» ሸዋዬ ቆሽቷ እያረረ፡፡
«በእርግጥ ሁለቱ ተዋደው ከሆነ ወደ ኋላ አልልም! ታይኝ የለ!» ብላት ታፈሡ ከሸዋዬ ፊት ዘወር አለች።
ሸዋዬ ግራ ግብት እንዳላት ነበር ከዚያ በኋላ ያለውን ጊዜ ያሳለፈችው፡፡
የታፈሠ ሁኔታ ስለ ሔዋንና አስቻለው ፍቅር ብዙም ፍንጭ አልሰጣትም።
በእርግጥ ስለዚሁ ጉዳይ ባለፈው ለሊት በምታስላስልበት ጊዜ በተለይ ከወይዘሮ እልፍነሽ የሰማችው ወሬ ለጊዘው ቢያናድዳትም በእውነትነቱ ግን ተጠራጥረዋለች፡፡
👍3
#ምንትዋብ
፡
፡
#ክፍል_ስድስት
፡
፡
#ድርሰት_በሕይወት_ተፈራ
....“አባቱን ላስገደለ ለርጉም ተክለሃይማኖት ያደረ ርጉም ነው” እየተባሉ ሲታሙ ያዘነላቸውን ያህል፣ ያን ቀን አዘነባቸው፤
ዓመጸባቸው።የሚሉትን ሊፈጽም፣ ሊያነጋግራቸው ቀርቶ፣ በዐይኑ
ሊያያቸው ቸገረው።
ጉልምስና ዕድሜ ላይ ከደረሰበት ጊዜ ጀምሮ ሁለት ነገር ተመኝቶ
አደገ - ወለተጊዮርጊስን አግብቶ ሥዕል እየሣለ መኖር፡፡
ወለተጊዮርጊስን ብዙ ጊዜ የሚያያት እሑድ ቤተክርስቲያን ከቅዳሴ በኋላ ሲሆን፣ ከቤተክርስቲያኑ ቅጥር ግቢ ውጭ ያለው ዋርካ ስር
ጥምጥሙን አድርጎ፣ ዱላውን መሬት ላይ፣ ዐይኑን ደጀሰላሙ ላይ ተክሎ የሷን ከግቢ መውጣት ይጠባበቃል። በመልኩ ማማርና በቁመቱ ርዝመት የተማረኩ ኮረዶች እሱን እያዩ ሲሽኮረመሙ፣ እሱ ዐይኑ ደጀሰላሙ ላይ ልቡ ወለተጊዮርጊስ ጋ ነው። ነጠላ ተከናንባ ብቅ ስትል ልቡ ይደልቃል። ዐይኖቹ የሚያርፉበት ይጠፋቸዋል ። ከአያቷና
ከእናቷ ኋላ እየተራመደች ዐይኖቻቸው ሲጋጩ ፈገግታ ይመጋገባሉ። ሰላምታ ይለዋወጣሉ።
ይህ ለሳምንት ስንቅ ይሆነዋል።
በዚህ የተነሳ ዋርካውን ይወደዋል ፤ ለእሱ ብቻ የተተከለለት
ይመስለዋል። ዋርካው ሥር ቆሞ የወለተጊዮርጊስን መውጣት
ሲጠባበቅ፣ ብቅ ስትል ልቡ ሲመታ፣ ዐይኑ ማረፊያ ሲያጣ፣ ፍቅሩ ሲግል፣ ምኞቱ ሲበረታ፣ ጊዮርጊስ ዝም ብሎ አይመለከተኝም፣ ያባቴን
ልብ ያራራልኛል እያለ ዐዲስ ተስፋ ውስጡ ሲጫር ይሰማዋል።
ሌሎች ጎረምሶች አጠገቡ ሲቆሙ፣ አቅሉን ያጣል። ወለተጊዮርጊስ ከቤተስኪያኑ ከመውጣቷ በፊት ቢሄዱ ደስ ይለዋል። “እስቲ ዞር በሉ”
ለማለት ይቃጣዋል።
ወለተጊዮርጊስና እሱ ቁጭ ብለው የልባቸውን ተነጋግረው ባያውቁም፣ አባቶቻቸው ቢቀያየሙም፣ የጊዜ ጉዳይ እንጂ አብሮ መኖር ዕጣ ተርታቸው እንደሆነ ሁለቱም በልባቸው አምነዋል፤ ሳይነጋገሩ ቃል
ተገባብተዋል። አንዱ ለአንዱ ልቡንና ሕይወቱን ሰጥቷል። ምንም እንኳን እሱ ያ ንፋስ አሸዋውን አንስቶ የተሸፈነበት የእሷ ምስል ልቡ ውስጥ ተቀርጾ አልፎ አልፎ ፍርሐት ቢያሳድርበትም፣ አላገኛት ይሆን?
የሚል ጥርጣሬ ውስጥ ቢከተውም፣ ሁለቱም በአባቶቻቸው መሃል ዕርቅ
ወርዶ የሚጋቡበትን ቀን በተስፋ ተጠባብቀዋል።
ጥላዬ፣ አባቶቻቸው የገቡትን ቃል አጥፈው፣ ለዓመታት እንደ
ጠላት ለመተያየታቸው ብቻ ሳይሆን፣ ወለተጊዮርጊስን ሳያገባ
ለመቅረቱ ምክንያቱ የእሱው አባት በመሆናቸውና ሥዕል የመሣል
ፍላጎቱን ሊያመክኑበት የሚታገሉትም እኝሁ አባቱ በመሆናቸው ቁርሾ ይዞባቸዋል።
ዐይናቸውን ላለማየት፣ እናቱን በሆነ ባልሆነው ሲጨቀጭቁና ቀን ያገኙትን ሁሉ ማታ ሲራገሙ ላለመስማት፣ ማታ ዳዊታቸውን ደግመው እስኪተኙ ውጭ ጨለማ ውስጥ ተቀምጦ ራቱን በልቶ መግባትና መተኛት፣ ጠዋት ውዳሴ ማርያማቸውንና ዳዊታቸውን ሲይዙ እናቱ
የሚያስጨብጡትን ቂጣ ቋጥሮ መውጣት የዘወትር ተግባሩ ሆነ።
ለእናቱ ቢያዝንም፣ ምኞቱና ፍላጎቱ ሁሉ ከዚያ የቁጭትና የበቀል ስሜት ከተጠናወተውና “የግዞት” ቦታ መሄድ ብቻ ከሆነ ሰንብቷል።የት እንደሚሄድ ያሰላና የወለተጊዮርጊስን ቁርጥ ሳያውቅ ቋራን ጥሎ ለመሄድ አንጀቱ አልችል ይለዋል።
ዛሬ ግን ወለተጊዮርጊስ ለንጉሥ መታጨቷን ሲሰማ ማመን አቃተው፤ ለዘላለም እንዳጣትም አወቀ። ከጥቂት ዓመታት በፊት ምስሏ በአሸዋ ሲዳፈን የተመለከተው ትዝ አለውና በእርግጥም ያ ንፋስ ንግርት
እንደነበረው ተረዳ ። ሕይወቱ በዐይኑ ሥር ስታልፍ፣ ስታመልጠው ተሰማው። ምንጊዜም ቢሆን የሚፈራውና ባሰበው ቁጥር የሚባንንበት፣
አካሉ ቦታ የማይበቃው የሚመስለው ነገር ዛሬ በመድረሱ አባቱን ወነጀለ።
ወለቴን ንጉሡ አልወሰዱብኝም፡ አባቴ አሳልፈው ሰጡብኝ እንጂ
አለ። እንባውን በኩታው እየጠራረገ፣ ለመሆኑ ወለተጊዮርጊስ ለንጉሡ
መታጨቷን ስትሰማ ምን ብላ ይሆን? መቸም ልብ ለልብ ተገናኝተናልና ምንስ ቢሆን እኔን ሳታስብ ትቀራለች? አለ፣ ሲተያዩ ፊታቸው ላይ የሚዋልለውን ደስታ እያሰበ። ስለምን እስታሁን ተያይዘን አልጠፋንም ነበር? ብንጠፋ ንሮ እኼ ሁሉ አይመጣም ነበር፡፡ ነገሩን እያሰበው ሲመጣ ድንጋጤውና ቁጭቱ ወደ ንዴት ተለወጡበት። ድንገት ንዴቱ እንደ ቋያ እሳት በሠራ አከላቱ ተሰራጨ።
እጆቹ ተንቀጠቀጡ፣ ጉሮሮው ደረቀበት፤ ቁና ቁና ተነፈሰ።
እናቱ ራቱን አመጡለት። መብላት እንደማይፈልግ ነገራቸው። ቤት
ውስጥ ተመልሰው ገብተው ቆሎ በአነስተኛ ቁና፣ ውሃ ደግሞ በቅምጫና ይዘው መጥተው፣ ቅምጫናውን መሬት ላይ አስቀምጠው ቁናውንም
በእጁ እንዲቀበላቸው ጥቂት አባብለው አስይዘውት አጠገቡ ተቀመጡ።
“አይዞህ የኔ ልዥ ። ዕድሜ ኻላነሰው፣ ጊዜ አለው ሰው ይላል ያገሬ ሰው። አንድ ቀን ሰው ትሆናለህ” ብለውት ለመውረድ ያቆበቆበውን እንባቸውን በእጅጌያቸው ጠራረጉ።
“እነየ አትጨነቂ።”
“ያባትህ ነገር መላ የለው ሁኖ አንተም ተቸገርህ። እኔስ እንዳሻው::ኸዝኸ ወዲያ ምን አረጋለሁ። የሳቸው ነገር ያስቸጋሪ በሬ ነገር ሆነ እኮ።”
“ያስቸጋሪ በሬ?”
“የሴቲቱ ባል ማልዶ ተነስቶ ወደርሻ ሲኸድ በሬው ገደል ይገባበታል።ዛዲያ ዳገት ላይ ቁሞ፣ 'ኧረ እርዱኝ በሬየ ገደል ገባ! ብሎ ይጮሀል። ያን ግዝየ ምሽቱ ኸቤት ትወጣና ኸየት ያመጣኸው በሬ ነው? በራሴ
በሬ' ብላው ትገባለች..” ሲሉ ጥላዬ ከት ብሎ ሲስቅ ትን አለው።
“ውሃ ፉት በልበት” አሉና ቅምጫናውን አቀበሉት። ውሃውን ጨልጦ ሲጨርስ ጠብቀው፣ “እናልህ እንደዛ ብላው ቤት ስትገባ ባልየው፣ ኧረ በሬያችን ገደል ገባ እርዱኝ አለ። ሴትየይቱ እንደገና ወጥታ፣ ኸየት
ያመጣኸው በሬ ነውና ነው በሬያችን ምትለው? የድሮ ባሌ የሰጠኝን ብላው ቤት ገባች። በመጨረሻ ሰውየው ሚለው ቢያጣ፣ እረ ያስቸጋሪ በሬ ገደል ገባ እርዱኝ አለ ይባላል አለ” አሉት።
ጥላዬ እንደገና ከት ብሎ ሳቀ። እናቱ ለሁሉ ነገር ምሳሌ የሚሆን
ተረትና ጨዋታ አላቸው። “አይ እነየ” ብሎ መልሶ ሳቀ። “የግዞት”
ቦታ የሚለውን ቤታቸውን እናቱ በተጫዋችነታቸው፣ ነገሮችን ቀለል አድርገው በማየታቸው፣ በተረቶቻቸውና በቀልዶቻቸው ነፍስ ባይዘሩበት ኖሮ፣ ኑሮ ከባላምባራስ ሁነኝ ጋር ምን ያህል አስቸጋሪ ሊሆን ይችል
እንደነበረና እናቱ የቻሉትን፣ የታገሱትን፣ ስቀውና ቀልደው ያሳለፉትን አሰበና፣ “እነየ ስንኳንም አንቺን ሰጠኝ” አላቸው።
ወይዘሮ ጌጤነሽ ሳቅ ብለው፣ “አየ ያንተ ነገር... እንኳንም አንተን
ሰጠኝ እንጂ አለበለዚያማ...” አሉት። ትንሽም ቢሆን ሊያስቁት
በመቻላቸው ደስ ብሏቸው፣ “አሁንስ ራት አትበላም?”
ራሱን በአሉታ ነቀነቀ።
ቅር እያላቸው ወደቤት ሲገቡ እሱ ስለ ሕይወቱ ማሰላሰል ጀመረ።
አንተ የወፍታው ምነው ዝም አልኸኝ? አለ ኹለት ነገር ጠይቄህ
ስንኳ አላውቅ። እኔ ልቤ ውስጥ እሳት አለ - ወለቴና ሥዕል፡ ወለቴን
ኸነጠቅኸኝ፣ ሥዕል መስጠት አቃተህ እኔ ጠበቅሁ፤
ጠበቅሁ፤ ሰው እስተመቸ ይጠብቃል? ለመጠበቅ ብቻ መፈጠርማ የለብኝም፡፡
ኸንግዲህ ምጠብቀው ነገር ስለሌለ ቋራ ሚያስቀምጠኝ ነገር የለም። እሳቸውን ችየ የኖርሁት ወለቴን አገባለሁ ብየ እንጂ፣ እሷ ለንጉሥ ኸተዳረችማ መኸድ በቀር ሌላ ምን አለኝ? ወለቴን ንጉሥ ኸወሰዳት እኔ የሥዕል ንጉሥ ማልሆን? አለ፣ ለራሱ።
ወለተጊዮርጊስን ማጣቱና እናቱን ለአባቱ ትቶ መሄድ ማሰቡ
ቢያሳዝነውም በወጣትነት ዕድሜው ውስጥ ለመጀመሪያ ጊዜ በራሱ መወሰን መቻሉ ዐቅም ሆነው፤ አደፋፈረው፣ የነፃነት መንፈስ አለበሰው። አባቱ ከፊቱ የደነቀሩበትን ጋሬጣ፣ ዙርያውን የተበተቡበትን ገመድ
በጣጥሶ የወጣ መሰለው።
፡
፡
#ክፍል_ስድስት
፡
፡
#ድርሰት_በሕይወት_ተፈራ
....“አባቱን ላስገደለ ለርጉም ተክለሃይማኖት ያደረ ርጉም ነው” እየተባሉ ሲታሙ ያዘነላቸውን ያህል፣ ያን ቀን አዘነባቸው፤
ዓመጸባቸው።የሚሉትን ሊፈጽም፣ ሊያነጋግራቸው ቀርቶ፣ በዐይኑ
ሊያያቸው ቸገረው።
ጉልምስና ዕድሜ ላይ ከደረሰበት ጊዜ ጀምሮ ሁለት ነገር ተመኝቶ
አደገ - ወለተጊዮርጊስን አግብቶ ሥዕል እየሣለ መኖር፡፡
ወለተጊዮርጊስን ብዙ ጊዜ የሚያያት እሑድ ቤተክርስቲያን ከቅዳሴ በኋላ ሲሆን፣ ከቤተክርስቲያኑ ቅጥር ግቢ ውጭ ያለው ዋርካ ስር
ጥምጥሙን አድርጎ፣ ዱላውን መሬት ላይ፣ ዐይኑን ደጀሰላሙ ላይ ተክሎ የሷን ከግቢ መውጣት ይጠባበቃል። በመልኩ ማማርና በቁመቱ ርዝመት የተማረኩ ኮረዶች እሱን እያዩ ሲሽኮረመሙ፣ እሱ ዐይኑ ደጀሰላሙ ላይ ልቡ ወለተጊዮርጊስ ጋ ነው። ነጠላ ተከናንባ ብቅ ስትል ልቡ ይደልቃል። ዐይኖቹ የሚያርፉበት ይጠፋቸዋል ። ከአያቷና
ከእናቷ ኋላ እየተራመደች ዐይኖቻቸው ሲጋጩ ፈገግታ ይመጋገባሉ። ሰላምታ ይለዋወጣሉ።
ይህ ለሳምንት ስንቅ ይሆነዋል።
በዚህ የተነሳ ዋርካውን ይወደዋል ፤ ለእሱ ብቻ የተተከለለት
ይመስለዋል። ዋርካው ሥር ቆሞ የወለተጊዮርጊስን መውጣት
ሲጠባበቅ፣ ብቅ ስትል ልቡ ሲመታ፣ ዐይኑ ማረፊያ ሲያጣ፣ ፍቅሩ ሲግል፣ ምኞቱ ሲበረታ፣ ጊዮርጊስ ዝም ብሎ አይመለከተኝም፣ ያባቴን
ልብ ያራራልኛል እያለ ዐዲስ ተስፋ ውስጡ ሲጫር ይሰማዋል።
ሌሎች ጎረምሶች አጠገቡ ሲቆሙ፣ አቅሉን ያጣል። ወለተጊዮርጊስ ከቤተስኪያኑ ከመውጣቷ በፊት ቢሄዱ ደስ ይለዋል። “እስቲ ዞር በሉ”
ለማለት ይቃጣዋል።
ወለተጊዮርጊስና እሱ ቁጭ ብለው የልባቸውን ተነጋግረው ባያውቁም፣ አባቶቻቸው ቢቀያየሙም፣ የጊዜ ጉዳይ እንጂ አብሮ መኖር ዕጣ ተርታቸው እንደሆነ ሁለቱም በልባቸው አምነዋል፤ ሳይነጋገሩ ቃል
ተገባብተዋል። አንዱ ለአንዱ ልቡንና ሕይወቱን ሰጥቷል። ምንም እንኳን እሱ ያ ንፋስ አሸዋውን አንስቶ የተሸፈነበት የእሷ ምስል ልቡ ውስጥ ተቀርጾ አልፎ አልፎ ፍርሐት ቢያሳድርበትም፣ አላገኛት ይሆን?
የሚል ጥርጣሬ ውስጥ ቢከተውም፣ ሁለቱም በአባቶቻቸው መሃል ዕርቅ
ወርዶ የሚጋቡበትን ቀን በተስፋ ተጠባብቀዋል።
ጥላዬ፣ አባቶቻቸው የገቡትን ቃል አጥፈው፣ ለዓመታት እንደ
ጠላት ለመተያየታቸው ብቻ ሳይሆን፣ ወለተጊዮርጊስን ሳያገባ
ለመቅረቱ ምክንያቱ የእሱው አባት በመሆናቸውና ሥዕል የመሣል
ፍላጎቱን ሊያመክኑበት የሚታገሉትም እኝሁ አባቱ በመሆናቸው ቁርሾ ይዞባቸዋል።
ዐይናቸውን ላለማየት፣ እናቱን በሆነ ባልሆነው ሲጨቀጭቁና ቀን ያገኙትን ሁሉ ማታ ሲራገሙ ላለመስማት፣ ማታ ዳዊታቸውን ደግመው እስኪተኙ ውጭ ጨለማ ውስጥ ተቀምጦ ራቱን በልቶ መግባትና መተኛት፣ ጠዋት ውዳሴ ማርያማቸውንና ዳዊታቸውን ሲይዙ እናቱ
የሚያስጨብጡትን ቂጣ ቋጥሮ መውጣት የዘወትር ተግባሩ ሆነ።
ለእናቱ ቢያዝንም፣ ምኞቱና ፍላጎቱ ሁሉ ከዚያ የቁጭትና የበቀል ስሜት ከተጠናወተውና “የግዞት” ቦታ መሄድ ብቻ ከሆነ ሰንብቷል።የት እንደሚሄድ ያሰላና የወለተጊዮርጊስን ቁርጥ ሳያውቅ ቋራን ጥሎ ለመሄድ አንጀቱ አልችል ይለዋል።
ዛሬ ግን ወለተጊዮርጊስ ለንጉሥ መታጨቷን ሲሰማ ማመን አቃተው፤ ለዘላለም እንዳጣትም አወቀ። ከጥቂት ዓመታት በፊት ምስሏ በአሸዋ ሲዳፈን የተመለከተው ትዝ አለውና በእርግጥም ያ ንፋስ ንግርት
እንደነበረው ተረዳ ። ሕይወቱ በዐይኑ ሥር ስታልፍ፣ ስታመልጠው ተሰማው። ምንጊዜም ቢሆን የሚፈራውና ባሰበው ቁጥር የሚባንንበት፣
አካሉ ቦታ የማይበቃው የሚመስለው ነገር ዛሬ በመድረሱ አባቱን ወነጀለ።
ወለቴን ንጉሡ አልወሰዱብኝም፡ አባቴ አሳልፈው ሰጡብኝ እንጂ
አለ። እንባውን በኩታው እየጠራረገ፣ ለመሆኑ ወለተጊዮርጊስ ለንጉሡ
መታጨቷን ስትሰማ ምን ብላ ይሆን? መቸም ልብ ለልብ ተገናኝተናልና ምንስ ቢሆን እኔን ሳታስብ ትቀራለች? አለ፣ ሲተያዩ ፊታቸው ላይ የሚዋልለውን ደስታ እያሰበ። ስለምን እስታሁን ተያይዘን አልጠፋንም ነበር? ብንጠፋ ንሮ እኼ ሁሉ አይመጣም ነበር፡፡ ነገሩን እያሰበው ሲመጣ ድንጋጤውና ቁጭቱ ወደ ንዴት ተለወጡበት። ድንገት ንዴቱ እንደ ቋያ እሳት በሠራ አከላቱ ተሰራጨ።
እጆቹ ተንቀጠቀጡ፣ ጉሮሮው ደረቀበት፤ ቁና ቁና ተነፈሰ።
እናቱ ራቱን አመጡለት። መብላት እንደማይፈልግ ነገራቸው። ቤት
ውስጥ ተመልሰው ገብተው ቆሎ በአነስተኛ ቁና፣ ውሃ ደግሞ በቅምጫና ይዘው መጥተው፣ ቅምጫናውን መሬት ላይ አስቀምጠው ቁናውንም
በእጁ እንዲቀበላቸው ጥቂት አባብለው አስይዘውት አጠገቡ ተቀመጡ።
“አይዞህ የኔ ልዥ ። ዕድሜ ኻላነሰው፣ ጊዜ አለው ሰው ይላል ያገሬ ሰው። አንድ ቀን ሰው ትሆናለህ” ብለውት ለመውረድ ያቆበቆበውን እንባቸውን በእጅጌያቸው ጠራረጉ።
“እነየ አትጨነቂ።”
“ያባትህ ነገር መላ የለው ሁኖ አንተም ተቸገርህ። እኔስ እንዳሻው::ኸዝኸ ወዲያ ምን አረጋለሁ። የሳቸው ነገር ያስቸጋሪ በሬ ነገር ሆነ እኮ።”
“ያስቸጋሪ በሬ?”
“የሴቲቱ ባል ማልዶ ተነስቶ ወደርሻ ሲኸድ በሬው ገደል ይገባበታል።ዛዲያ ዳገት ላይ ቁሞ፣ 'ኧረ እርዱኝ በሬየ ገደል ገባ! ብሎ ይጮሀል። ያን ግዝየ ምሽቱ ኸቤት ትወጣና ኸየት ያመጣኸው በሬ ነው? በራሴ
በሬ' ብላው ትገባለች..” ሲሉ ጥላዬ ከት ብሎ ሲስቅ ትን አለው።
“ውሃ ፉት በልበት” አሉና ቅምጫናውን አቀበሉት። ውሃውን ጨልጦ ሲጨርስ ጠብቀው፣ “እናልህ እንደዛ ብላው ቤት ስትገባ ባልየው፣ ኧረ በሬያችን ገደል ገባ እርዱኝ አለ። ሴትየይቱ እንደገና ወጥታ፣ ኸየት
ያመጣኸው በሬ ነውና ነው በሬያችን ምትለው? የድሮ ባሌ የሰጠኝን ብላው ቤት ገባች። በመጨረሻ ሰውየው ሚለው ቢያጣ፣ እረ ያስቸጋሪ በሬ ገደል ገባ እርዱኝ አለ ይባላል አለ” አሉት።
ጥላዬ እንደገና ከት ብሎ ሳቀ። እናቱ ለሁሉ ነገር ምሳሌ የሚሆን
ተረትና ጨዋታ አላቸው። “አይ እነየ” ብሎ መልሶ ሳቀ። “የግዞት”
ቦታ የሚለውን ቤታቸውን እናቱ በተጫዋችነታቸው፣ ነገሮችን ቀለል አድርገው በማየታቸው፣ በተረቶቻቸውና በቀልዶቻቸው ነፍስ ባይዘሩበት ኖሮ፣ ኑሮ ከባላምባራስ ሁነኝ ጋር ምን ያህል አስቸጋሪ ሊሆን ይችል
እንደነበረና እናቱ የቻሉትን፣ የታገሱትን፣ ስቀውና ቀልደው ያሳለፉትን አሰበና፣ “እነየ ስንኳንም አንቺን ሰጠኝ” አላቸው።
ወይዘሮ ጌጤነሽ ሳቅ ብለው፣ “አየ ያንተ ነገር... እንኳንም አንተን
ሰጠኝ እንጂ አለበለዚያማ...” አሉት። ትንሽም ቢሆን ሊያስቁት
በመቻላቸው ደስ ብሏቸው፣ “አሁንስ ራት አትበላም?”
ራሱን በአሉታ ነቀነቀ።
ቅር እያላቸው ወደቤት ሲገቡ እሱ ስለ ሕይወቱ ማሰላሰል ጀመረ።
አንተ የወፍታው ምነው ዝም አልኸኝ? አለ ኹለት ነገር ጠይቄህ
ስንኳ አላውቅ። እኔ ልቤ ውስጥ እሳት አለ - ወለቴና ሥዕል፡ ወለቴን
ኸነጠቅኸኝ፣ ሥዕል መስጠት አቃተህ እኔ ጠበቅሁ፤
ጠበቅሁ፤ ሰው እስተመቸ ይጠብቃል? ለመጠበቅ ብቻ መፈጠርማ የለብኝም፡፡
ኸንግዲህ ምጠብቀው ነገር ስለሌለ ቋራ ሚያስቀምጠኝ ነገር የለም። እሳቸውን ችየ የኖርሁት ወለቴን አገባለሁ ብየ እንጂ፣ እሷ ለንጉሥ ኸተዳረችማ መኸድ በቀር ሌላ ምን አለኝ? ወለቴን ንጉሥ ኸወሰዳት እኔ የሥዕል ንጉሥ ማልሆን? አለ፣ ለራሱ።
ወለተጊዮርጊስን ማጣቱና እናቱን ለአባቱ ትቶ መሄድ ማሰቡ
ቢያሳዝነውም በወጣትነት ዕድሜው ውስጥ ለመጀመሪያ ጊዜ በራሱ መወሰን መቻሉ ዐቅም ሆነው፤ አደፋፈረው፣ የነፃነት መንፈስ አለበሰው። አባቱ ከፊቱ የደነቀሩበትን ጋሬጣ፣ ዙርያውን የተበተቡበትን ገመድ
በጣጥሶ የወጣ መሰለው።
👍12🔥1
#ትኩሳት
፡
፡
#ክፍል_ስድስት
፡
፡
#በስብሐት_ገብረ_እግዚአብሔር
ይሄ ሁሉ ሲሆን ባህራምን አልረሳሁትም ነበር ከምሳ በኋላ Le Monde የተባለውን ስመጥሩ የፈረንሳይ ጋዜጣ እገዛና፣ ካፌ ዶርቢቴል ገብቼ petit creme (ቡና በወተት በሲኒ)
አዝዤ ሀበሾቹ አጠገብ ቁጭ ብዬ ጋዜጣዬን ማንበብ እጀምራለሁ።
ጩኸት፣ ሳቅ፣ ወሬ፣ የሲጋራ ጪስ፣ የሴት ሽቶ ካፌውን
ይሞላዋል። በበጋው ሙቀት ምክንያት መስኮት ሁሉ ይከፈታል፡፡
ሰማያዊ ካኪ የስራ ልብስ የለበሱ የፋብሪካ ሰራተኞች የቡና ማፍያው መኪና የተቀመጠበትን ረዥም ባንኮኒ በክንዳቸው ተደግፈው በተርታ ቆመው ፓስቲስ (ነጭ አረቄ) እየጠጡ፣ የፋብሪካ ዘይት ምናምን ያቆሽሽውን ቀያይ ፀጉራም እጃቸውን በብዙ እያንቀሳቀሱ፣
በአስቂኝ የደቡብ ፈረንሳይኛቸው ያወራሉ። ከባንኮኒው ዳር፣ ከመስተዋት የተሰራው በር አጠገብ፣ የካፌው ባለቤት መስዬ ፖል የቂል ሳቁን እየሳቀ “Merc Bien morosiuro (እግዜር ይስጥልኝ ጌታዬ» እያለ የሚከፍሉትን ገንዘብ ይቀበላል፤ ቴምብርና ሲጋራ ይሸጣል
ከባንኮኒው ኋላ ቆንጆዋ የመስየ ፖል ሚስት ባጭሩ የተቆረጠ
ብጫ ብጤ ቀለም የተቀባ ፀጉሯ እያብለጨለጨ ለሰዎቹ ቡና ወይም ፓስቲስ እያቀበለች፣ ከወጣቶቹ ጋር ፈገግታና ቃላት ትቀባበላለች፣ ትሽኮረመማለች፣ በማርሰይ ዜማ ታወራለች። ሸርሞጥሞጥ የምትል ሴት ናት። ድምፅዋ፣ አስተያየቷ፣ አረማመዷ፣ ሁለመናዋ ወንድ ይጣራል። መስዬ ፖል በብስጭት ነው የሚኖረው ሲባል እሰማለሁ፡፡
ግን ተማሪ ውሽማ ያላትም ይላሉ። ተማሪዎቹ መስዬ ፖልን
ይወዱታል፣ ሚስቱን ሊነኩበት አይፈለጉም፡፡ እሷም ተማሪ
የምትፈልግ አትመስልም፡፡ ውሽሞቿ ጎረምሶችና የፋብሪካ ወይም የኩባ ሰራተኞች ናቸው በበጋው ሙቀት ኮታቸውን አውልቀው የሸሚዛቸውን ቁልፍ በሙሉ ፈተው፣ የደረታቸውን ፀጉርና ጡንቻ እያሳዩና እጅጌያቸውን ሰብስበው ጡንቸኛ ፀጉራም እጃቸውን እያወዛወዙ ካፌ ዶርቢቴል የሚመጡ ጎረምሶች
እጠረጴዛዎቹ መሀል ሁለቱ ሴት ቦዮች ቡና፣ መጠጥ፣ ሲጋራ እየያዙ ይዘዋወራሉ
ሀበሾቹና ባህራም ካንድ ሁለት አፍሪካውያን ወይም ፈረንሳዮች
ጋር ካርታ ሲጫወቱ፣ አጠገባቸው ቁጭ ብዬ ጋዜጣዬን አነባለሁ።
በካርታ የተሸነፉት ሁለት ልጆች፣ ሌሎች ሁለት ተሽንፈውሳቸው
ተራቸውን ለመጫወት እስኪችሉ ድረስ መጥተው ከኔ ጋር ያወራሉ
ተካ ይመጣና ጋዜጣዬን ሳነብ «የማታነበውን ገፅ ልመልከተው
ስቲ» ብሎ ጋዜጣዬን ነጥሎ ግማሹን ይወስድብኛል። የማነበውን ጨርሼ ወደሌላ ገፅ መሄዴ ሲሆን፣ ተካ «ቆይ እቺን ልጨርስና እሰጥሃለሁ» ይለኛል። «አምጣ እንጂ» ስለው «ጋዜጣው ካንተ ጋር ይውላል፣ ትንሽ ባነብ ምናለበት?» ይለኛል። ብሽቅ ብዬ አየዋለሁ፡፡
ጥፍሩን እየነከሰ ያነባል።ጋዜጣው ውስጥ ያሳቀውን ወይም
ያስገረመውን ነገር ያሳየኛል፤ በጭራሽ አያስቅም፣ አያስገርምም።አይ ተካ ብሽቁ! ግን ጥሩ ልጅ ነው፡፡ እሱ ራሱ ጋዜጣ ገዝቶ ያነብ እንደሆነ ጋዜጣውን ይሰጠኝና «የማታነበውን ገፅ ስጠኝ። ሌላውን ካንተ በኋላ ቀስ ብዪ አነበዋለሁ» ይለኛል
አንዳንዴ ሀበሾቹ ተሰብስበው ካርታ ሲጫወቱ ወዳጆቻቸው
ሴቶች አንድ ጠረጴዛ ይዘው እያወሩ ይጠብቁዋቸዋል፡፡ ሲያሰኘኝ ከነሱ ጋር ትንሽ አወራለሁ ከኒኮል ጋር ማውራት እሞክራለሁ፣ ያቅተኛል። በጣም
ታፍራለች፤ ያልለመደችውን ሰው ማናገር አይሆንላትም። ለጊዜው
በጭራሽ ላውቃት አልቻልኩም። ስለዚህ ባሀራም ምን አይቶባት
ይሆን? ለሚለው ጥያቄ የመልስ ጫፍ እንኳ አላገኘሁለትም፡፡
መልኳን አይቶ እንዳልሆነ ግን ግልፅ ነበር፡፡ ውሀ አረንጓዴ አይኖች፣ የተዘረዘሩ ጥቃቅን ጥርሶች፣ ትኩሳት እንደያዛቸው አይነት ቆዳቸው የደረቀ ከናፍር። ድምፅዋ ደስ ይላል። ባህራም ምን አይቶባት ይሆን? እውነት ለገንዘቧ ሲል ይሆን?
ከአማንዳ ጋር ግን ብዙ እናወራለን። ሀበሾቹ አማንዳ ዱቤ ነው የሚሏት፡፡ ሉልሰገድ ይዟት ሊሄድ ሲል ተካ «እንግዲህ ሂድና
ዱባህን አገላብጥ!» ይለዋል። ሉልሰገድ «አንተ ደሞ ከዱባ የተሻለች እስክታገላብጥ ድረስ ስለዱባ ባታወራ ጥሩ ነው!» ብሎት አማንዳን እቅፎ ይሄዳል፡፡ አማንዳ በእንግሊዝኛ «ምንድነው "ሚለው?»
ትለዋለች፡፡ «ተይው ዝም ብሎ ነው» ይላታል።
ጋዜጣዬን እንብቤ፣ ሰዉን አይቼ፣ ባህራምን ተመልክቼ፣ ስለራሱ ለማውራት ዝግጁ እንዳልሆነ ከተገነዘብኩ በኋላ፣ ከካፌው
ወጥቼ ወደ ኩር ሚራቦ በኩል ትንሽ እራመዳለሁ። ወደኋላ ዞሬ፣
ማንም ሀበሻ እንዳልተከተለኝ ካረጋገጥኩ በኋላ፣ እታጠፍና ወደ
ሲልቪ ቤት አመራለሁ
"አንድ ቀን ባህራምን ያዘክው?» አለችኝ
"የለም" አልኳት
"የምትይዘው ይመስልሀል?»
"እርግጠኛ ነኝ»
«የምስራቅ ሰው እንደሆንክ ያስታውቃል፡፡ ጊዜ የሚያመጣውን
ጊዜ እስኪያመጣው ትጠብቃለህ እንጂ ጊዜን ልታጣድፈው
አትሞክርም፡፡ የምእራብ ሰው ብትሆን ግን ባህራምን ሄደህ በብልሀት ታዋራው ታወጣጣው ነበር»
«እንደሱ ካረግኩማ እሱን ራሱን ላውቀው አልችልም፡፡ የማሰብና
የሰዋስው ችሎታውን ብቻ ነው ላውቅ የምችለው»
«ምን የሚል ይመስልሀል?»
«ምን እንደሚልማ ማወቅ ቀላል ነው»
«አንግዲያው ምንድነው የምትጠብቀው?»
«ያ ያልኩሽ ጊዜ ሲመጣ፣ ተጠንቅቄ ምሰማው ቃላቱን
አይደለም ኮ»
«ታድያስ?»
ድምፁን ነው:: ዜማውን፡፡ እጁ እንዴት እንደሚንቀሳቀስ። ምን
ሲል ድምፁ እንደሚለሰልስ፣ ምን ሲናገር ግምባሩ እንደሚቋጠር።
አንዳንድ ጊዜ እኛ ሳናውቅ ፊታችን ላይ ፈገግታ ወይም ህዘን በገዛ
ራሱ ይጫወት የለ? ያንን ነው ምጠብቀው:: አንድን ሰው
የምናውቀው በሚናገረው ቃላት አይደለም፣ ያን ቃላት ሲናገር
በሚያሳየው ገፅ፣ በሚያሰማው ድምፅ ነው:: እሱን እሱን ለማየት
ነው ባህራምን አድፍጬ የምጠብቀው
ከሰአት በኋላውን ከሷ ጋር አሳልፈዋለሁ፡፡ እንቅልፍ ከወሰደን ወደ አስራ አንድ ላይ እንነቃለን። ወይ እናወራለን፣ ወይ እናነባለን!
ወይ ሙዚቃ እንሰማለን። ሰኞና አርብ በአስር ሰአት ላይ ክፍል
አለባት። አንዳንዴ ተኝቼ ትታኝ ሄዳ ስትመለስ ትቀሰቅሰኛለች።
አንዳንዴ ነቅቼ እንደ ሌላ ቀን ከአርት መፃህፍት አንዱን
እየተመለከትኩ፣ ወይም እያነበብኩ፣ ወይም ሙዚቃ እየሰማሁ አቆያታለሁ
ሲመሽ ተለይቻት እሄዳለሁ። A ጠdemain cheri» («እስከ ነገ
ደህና ሁንልኝ») ምግብ ቤት ሄጄ እራቴን በልቼ፣ ከዚያ ወጥቼ
የቴሌቪዥን ዜና አይቼ ሳበቃ፣ ሆቴሌ ሄጄ ስራ እጀምራለሁ።
(አሜሪካዊቷ መምጣት ትታለች) ወይም ሲኒማ እገባለሁ። ከሲኒማ
በኋላ ለመስራት እሞክራለሁ፡፡ እምቢ ካለኝ፣ የሌሊት ፀጥታ
የዋጣቸውን የኤክስን ጠባብ መንገዶች እዘዋወርባቸዋለሁ፡፡ ንጉሳቸው ነኝ
ጧት ተነስቼ፣ ቁርሴን ሁለት croissant በልቼ፣ ቡና በወተት
ጠጥቼ፣ ወደ ቤተመፃህፍት ሄጄ እስከምሳ ሰአት እሰራለሁ። (ክፍል
መግባት ከተውኩ መቸስ ዘመን የለኝም)
ከምሳ በኋላ ካፌ ዶርቢቴልን ጎብኝቼ ወደ ሲልቪ እሄዳለሁ፡፡
በሰፊ አፏ እየሳቀች ትቀበለኛለች
አያሌ ቀናት ካለፉ በኋላ፣ ተመስገንን እየሳቅኩ
«ሲልቪ እንደወጣች ቀረች?» አልኩት
«ቀረች!» አለኝ «አሁንማ ብትመለስም አልፈልጋት»
«ምነው?»
፡
፡
#ክፍል_ስድስት
፡
፡
#በስብሐት_ገብረ_እግዚአብሔር
ይሄ ሁሉ ሲሆን ባህራምን አልረሳሁትም ነበር ከምሳ በኋላ Le Monde የተባለውን ስመጥሩ የፈረንሳይ ጋዜጣ እገዛና፣ ካፌ ዶርቢቴል ገብቼ petit creme (ቡና በወተት በሲኒ)
አዝዤ ሀበሾቹ አጠገብ ቁጭ ብዬ ጋዜጣዬን ማንበብ እጀምራለሁ።
ጩኸት፣ ሳቅ፣ ወሬ፣ የሲጋራ ጪስ፣ የሴት ሽቶ ካፌውን
ይሞላዋል። በበጋው ሙቀት ምክንያት መስኮት ሁሉ ይከፈታል፡፡
ሰማያዊ ካኪ የስራ ልብስ የለበሱ የፋብሪካ ሰራተኞች የቡና ማፍያው መኪና የተቀመጠበትን ረዥም ባንኮኒ በክንዳቸው ተደግፈው በተርታ ቆመው ፓስቲስ (ነጭ አረቄ) እየጠጡ፣ የፋብሪካ ዘይት ምናምን ያቆሽሽውን ቀያይ ፀጉራም እጃቸውን በብዙ እያንቀሳቀሱ፣
በአስቂኝ የደቡብ ፈረንሳይኛቸው ያወራሉ። ከባንኮኒው ዳር፣ ከመስተዋት የተሰራው በር አጠገብ፣ የካፌው ባለቤት መስዬ ፖል የቂል ሳቁን እየሳቀ “Merc Bien morosiuro (እግዜር ይስጥልኝ ጌታዬ» እያለ የሚከፍሉትን ገንዘብ ይቀበላል፤ ቴምብርና ሲጋራ ይሸጣል
ከባንኮኒው ኋላ ቆንጆዋ የመስየ ፖል ሚስት ባጭሩ የተቆረጠ
ብጫ ብጤ ቀለም የተቀባ ፀጉሯ እያብለጨለጨ ለሰዎቹ ቡና ወይም ፓስቲስ እያቀበለች፣ ከወጣቶቹ ጋር ፈገግታና ቃላት ትቀባበላለች፣ ትሽኮረመማለች፣ በማርሰይ ዜማ ታወራለች። ሸርሞጥሞጥ የምትል ሴት ናት። ድምፅዋ፣ አስተያየቷ፣ አረማመዷ፣ ሁለመናዋ ወንድ ይጣራል። መስዬ ፖል በብስጭት ነው የሚኖረው ሲባል እሰማለሁ፡፡
ግን ተማሪ ውሽማ ያላትም ይላሉ። ተማሪዎቹ መስዬ ፖልን
ይወዱታል፣ ሚስቱን ሊነኩበት አይፈለጉም፡፡ እሷም ተማሪ
የምትፈልግ አትመስልም፡፡ ውሽሞቿ ጎረምሶችና የፋብሪካ ወይም የኩባ ሰራተኞች ናቸው በበጋው ሙቀት ኮታቸውን አውልቀው የሸሚዛቸውን ቁልፍ በሙሉ ፈተው፣ የደረታቸውን ፀጉርና ጡንቻ እያሳዩና እጅጌያቸውን ሰብስበው ጡንቸኛ ፀጉራም እጃቸውን እያወዛወዙ ካፌ ዶርቢቴል የሚመጡ ጎረምሶች
እጠረጴዛዎቹ መሀል ሁለቱ ሴት ቦዮች ቡና፣ መጠጥ፣ ሲጋራ እየያዙ ይዘዋወራሉ
ሀበሾቹና ባህራም ካንድ ሁለት አፍሪካውያን ወይም ፈረንሳዮች
ጋር ካርታ ሲጫወቱ፣ አጠገባቸው ቁጭ ብዬ ጋዜጣዬን አነባለሁ።
በካርታ የተሸነፉት ሁለት ልጆች፣ ሌሎች ሁለት ተሽንፈውሳቸው
ተራቸውን ለመጫወት እስኪችሉ ድረስ መጥተው ከኔ ጋር ያወራሉ
ተካ ይመጣና ጋዜጣዬን ሳነብ «የማታነበውን ገፅ ልመልከተው
ስቲ» ብሎ ጋዜጣዬን ነጥሎ ግማሹን ይወስድብኛል። የማነበውን ጨርሼ ወደሌላ ገፅ መሄዴ ሲሆን፣ ተካ «ቆይ እቺን ልጨርስና እሰጥሃለሁ» ይለኛል። «አምጣ እንጂ» ስለው «ጋዜጣው ካንተ ጋር ይውላል፣ ትንሽ ባነብ ምናለበት?» ይለኛል። ብሽቅ ብዬ አየዋለሁ፡፡
ጥፍሩን እየነከሰ ያነባል።ጋዜጣው ውስጥ ያሳቀውን ወይም
ያስገረመውን ነገር ያሳየኛል፤ በጭራሽ አያስቅም፣ አያስገርምም።አይ ተካ ብሽቁ! ግን ጥሩ ልጅ ነው፡፡ እሱ ራሱ ጋዜጣ ገዝቶ ያነብ እንደሆነ ጋዜጣውን ይሰጠኝና «የማታነበውን ገፅ ስጠኝ። ሌላውን ካንተ በኋላ ቀስ ብዪ አነበዋለሁ» ይለኛል
አንዳንዴ ሀበሾቹ ተሰብስበው ካርታ ሲጫወቱ ወዳጆቻቸው
ሴቶች አንድ ጠረጴዛ ይዘው እያወሩ ይጠብቁዋቸዋል፡፡ ሲያሰኘኝ ከነሱ ጋር ትንሽ አወራለሁ ከኒኮል ጋር ማውራት እሞክራለሁ፣ ያቅተኛል። በጣም
ታፍራለች፤ ያልለመደችውን ሰው ማናገር አይሆንላትም። ለጊዜው
በጭራሽ ላውቃት አልቻልኩም። ስለዚህ ባሀራም ምን አይቶባት
ይሆን? ለሚለው ጥያቄ የመልስ ጫፍ እንኳ አላገኘሁለትም፡፡
መልኳን አይቶ እንዳልሆነ ግን ግልፅ ነበር፡፡ ውሀ አረንጓዴ አይኖች፣ የተዘረዘሩ ጥቃቅን ጥርሶች፣ ትኩሳት እንደያዛቸው አይነት ቆዳቸው የደረቀ ከናፍር። ድምፅዋ ደስ ይላል። ባህራም ምን አይቶባት ይሆን? እውነት ለገንዘቧ ሲል ይሆን?
ከአማንዳ ጋር ግን ብዙ እናወራለን። ሀበሾቹ አማንዳ ዱቤ ነው የሚሏት፡፡ ሉልሰገድ ይዟት ሊሄድ ሲል ተካ «እንግዲህ ሂድና
ዱባህን አገላብጥ!» ይለዋል። ሉልሰገድ «አንተ ደሞ ከዱባ የተሻለች እስክታገላብጥ ድረስ ስለዱባ ባታወራ ጥሩ ነው!» ብሎት አማንዳን እቅፎ ይሄዳል፡፡ አማንዳ በእንግሊዝኛ «ምንድነው "ሚለው?»
ትለዋለች፡፡ «ተይው ዝም ብሎ ነው» ይላታል።
ጋዜጣዬን እንብቤ፣ ሰዉን አይቼ፣ ባህራምን ተመልክቼ፣ ስለራሱ ለማውራት ዝግጁ እንዳልሆነ ከተገነዘብኩ በኋላ፣ ከካፌው
ወጥቼ ወደ ኩር ሚራቦ በኩል ትንሽ እራመዳለሁ። ወደኋላ ዞሬ፣
ማንም ሀበሻ እንዳልተከተለኝ ካረጋገጥኩ በኋላ፣ እታጠፍና ወደ
ሲልቪ ቤት አመራለሁ
"አንድ ቀን ባህራምን ያዘክው?» አለችኝ
"የለም" አልኳት
"የምትይዘው ይመስልሀል?»
"እርግጠኛ ነኝ»
«የምስራቅ ሰው እንደሆንክ ያስታውቃል፡፡ ጊዜ የሚያመጣውን
ጊዜ እስኪያመጣው ትጠብቃለህ እንጂ ጊዜን ልታጣድፈው
አትሞክርም፡፡ የምእራብ ሰው ብትሆን ግን ባህራምን ሄደህ በብልሀት ታዋራው ታወጣጣው ነበር»
«እንደሱ ካረግኩማ እሱን ራሱን ላውቀው አልችልም፡፡ የማሰብና
የሰዋስው ችሎታውን ብቻ ነው ላውቅ የምችለው»
«ምን የሚል ይመስልሀል?»
«ምን እንደሚልማ ማወቅ ቀላል ነው»
«አንግዲያው ምንድነው የምትጠብቀው?»
«ያ ያልኩሽ ጊዜ ሲመጣ፣ ተጠንቅቄ ምሰማው ቃላቱን
አይደለም ኮ»
«ታድያስ?»
ድምፁን ነው:: ዜማውን፡፡ እጁ እንዴት እንደሚንቀሳቀስ። ምን
ሲል ድምፁ እንደሚለሰልስ፣ ምን ሲናገር ግምባሩ እንደሚቋጠር።
አንዳንድ ጊዜ እኛ ሳናውቅ ፊታችን ላይ ፈገግታ ወይም ህዘን በገዛ
ራሱ ይጫወት የለ? ያንን ነው ምጠብቀው:: አንድን ሰው
የምናውቀው በሚናገረው ቃላት አይደለም፣ ያን ቃላት ሲናገር
በሚያሳየው ገፅ፣ በሚያሰማው ድምፅ ነው:: እሱን እሱን ለማየት
ነው ባህራምን አድፍጬ የምጠብቀው
ከሰአት በኋላውን ከሷ ጋር አሳልፈዋለሁ፡፡ እንቅልፍ ከወሰደን ወደ አስራ አንድ ላይ እንነቃለን። ወይ እናወራለን፣ ወይ እናነባለን!
ወይ ሙዚቃ እንሰማለን። ሰኞና አርብ በአስር ሰአት ላይ ክፍል
አለባት። አንዳንዴ ተኝቼ ትታኝ ሄዳ ስትመለስ ትቀሰቅሰኛለች።
አንዳንዴ ነቅቼ እንደ ሌላ ቀን ከአርት መፃህፍት አንዱን
እየተመለከትኩ፣ ወይም እያነበብኩ፣ ወይም ሙዚቃ እየሰማሁ አቆያታለሁ
ሲመሽ ተለይቻት እሄዳለሁ። A ጠdemain cheri» («እስከ ነገ
ደህና ሁንልኝ») ምግብ ቤት ሄጄ እራቴን በልቼ፣ ከዚያ ወጥቼ
የቴሌቪዥን ዜና አይቼ ሳበቃ፣ ሆቴሌ ሄጄ ስራ እጀምራለሁ።
(አሜሪካዊቷ መምጣት ትታለች) ወይም ሲኒማ እገባለሁ። ከሲኒማ
በኋላ ለመስራት እሞክራለሁ፡፡ እምቢ ካለኝ፣ የሌሊት ፀጥታ
የዋጣቸውን የኤክስን ጠባብ መንገዶች እዘዋወርባቸዋለሁ፡፡ ንጉሳቸው ነኝ
ጧት ተነስቼ፣ ቁርሴን ሁለት croissant በልቼ፣ ቡና በወተት
ጠጥቼ፣ ወደ ቤተመፃህፍት ሄጄ እስከምሳ ሰአት እሰራለሁ። (ክፍል
መግባት ከተውኩ መቸስ ዘመን የለኝም)
ከምሳ በኋላ ካፌ ዶርቢቴልን ጎብኝቼ ወደ ሲልቪ እሄዳለሁ፡፡
በሰፊ አፏ እየሳቀች ትቀበለኛለች
አያሌ ቀናት ካለፉ በኋላ፣ ተመስገንን እየሳቅኩ
«ሲልቪ እንደወጣች ቀረች?» አልኩት
«ቀረች!» አለኝ «አሁንማ ብትመለስም አልፈልጋት»
«ምነው?»
👍20❤1
#ምንዱባን
፡
፡
#ክፍል_ስድስት
፡
፡
#ትርጉም_ከዬሐንስ_ገፃዲቅ
አንዳንዴ ኃላፊነትን ከመሸከም አሳልፎ መስጠት
በ18ኛው መቶ ክፍለ ዘመን መጀመሪያ ላይ ፓሪስ አጠገብ ከሚገኘው ሞንትፌርሜ ከተባለ ሥፍራ አንድ አነስተኛ ሆቴል ቤት ነበር፡፡ ዛሬ ግን የለም:: ሆቴል ቤቱ፡ ዘቴናድዬስ የተባሉ ባልና ሚስት ንብረት ሲሆን የሚገኘው በላንገር ከተባለ ቀጭን መንገድ ላይ ነበር፡፡ ከቤቱ በራፍ ላይ ስዕል
ተንጠልጥለአል:: ስዕለ ላይ ሜዳሊያ የተሰካላትና በደም ተበክሎ የተቦጫጨቀ የጄኔራል ልብስ የለበሰ ሰው ሸክም ተሸክሞ ነው የሚታየው::በተጨማሪም ከምስሉ ባዶ ሥፍራ ላይ ጭስ በብዛት አለ:: የሚያመለክተው
የጦር ሜዳን ሳይሆን አይቀርም:: ከምስሉ ስር «የዋተርሉ ጦር ሜዳ
ጀግና የሃምሳ አለቃ» የሚል ጽሑፍ ተጽፎበታል:: ከዚህ ሆቴል ቤት በራፍ ጋሪ ቆሞ ማየት አዲስ ነገር አልነበረም:: ሆኖም «ከዋተርሉ የጦር ሜዳ ጀግናው የሃምሳ አለቃ» ሆቴል ቤት በራፍ
የተሰባበረ ጋሪ መንገድ ዘግቶ ሲቆም ዘወትር የሚታይ ትርኢት አይደለም::ጊዜው የፀደይ ወራት ሲሆን ዓመተ ምህረቱ 1818 ዓ.ም ነው፡፡ የጋሪው መንገድ ዘግቶ መቆም ፤ ያን የመሰለ ስዕል ከዚያ ቤት በራፍ መሰቀል በዚያ
ያለፈ የማንኛውም ሰዓሊ ዓይን የሚማርክ ትርዒት ነበር::
ጋሪው ትላልቅ ግንዲላዎችን ጭኖአል፡፡ ታዲያ ይህ ጋሪ ከዚህ ስፍራ ምን ይሠራ ነበር የሚል ጥያቄ ቢነሳ «ከዚያ የተገተረውማ መንገድ ለመዝጋትና የትጉህ ሠራተኞችን ተግባር ለማደናቀፍ ነው» የሚል ትርጉም
ሊያሰጥ ይችላል፡፡
ከጋሪው የእቃ መጫኛ ሥር የተንጠለጠለው ወፍራም ሰንሰለት መሬት ሊነካ ምንም አልቀረው:: አንዲት ሁለት ዓመት ተመንፈቅ የሚሆናት ልጅ ሌላ ዓመት ከስድስት ወር የሚሆናትን ሕፃን ጭንዋ ላይ አሳርፋ
ከሰንሰለቱ ላይ ተቀምጣለች:: ልጆቹ ጅዋጅዌ ላይ እንደወጡ ደስ ብሎአቸዋል፡፡ አንዲት ሴት አቀማመጣቸውን አይታ «ልጆቼ መጫወቻ አገኘ» በማለት ደስ እንደሚላት ማንኛዋም እናት በማተኮር ታያቸዋለች::አተኩሮ ለተመለከታት አንጀት የምትበላ፧ አንዴ እንኳን ለማየት የምትቀፍና
ኑሮ እጅግ ያጎሳቆላት ሌላ ሴት ከበራፉ አጠገብ ተቀምጣለች፡፡ ልጆቹ ደስ ብሏቸው ሲጫወቱ «ምናልባት ፈረሱ ደምብሮ ይጐዳቸው ይሆን» እያለች
የመጀመሪያዋ ሴት አሁንም እንደማንኛውም እናት ማሰብዋ ኣልቀረም::ሰንሰለቱ በተነቃነቀ ቁጥር ሲጥጥ እያለ ይጮሃል:: ድምፁ ሕፃናቱን አልረሸሻቸወም:: የማታ ጨረር ከልጆቹ ላይ በማረፉ ልብ ብሉ ለተመለከታቸው ዓይንን ይማርካለ::
የልጆቹ እናት በድንገት ድምፅ ትሰማለች:: «እሜቴ ደስ የሚሉ
ልጆች ነው ያሉዎት!»
ከምግብ ቤቱ በራፍ የተቀመጠችው ሌላዋ ሴትም ልጅ ታቅፋ ነበር::ከባድ የሚመስል እቃ በጀርባዋ አዝላለች:: እርስዋም የታቀፈቻት ልጅ ሁለት ወይም ሦስት ዓመት ቢሆናት ነው:: በአለባበስ ከሁለቱ ልጆች
ምንም ያህል አትለይም:: ሻሽ መሳይ ጨርቅ አስራለች:: የተቦጫጨቀ ቀሚስዋ ቀዳዳው እስከጭንዋ ሊደርስ ምንም አልቀረ:: ሆኖም ጤነኛ ነበረች:: መልክዋ ድምቡሽቡሽ ያለ ስለሆነ ንከሰኝ፣ ንከሰኝ ትላለች፡፡ዓይኖችዋ ትላልቅ ስለነበሩ እንቅልፍ ቢወስዳትም ሙሉ ለመሉ
አልተከደነም:: ለስለስ ካለው የእናትዋ ክንድ ላይ ተመችቶአት ስለተኛች እንቅልፍ ሳይጠግብ ሲቀሰቅሱት እንደማይስማው እንደማንኛውም ሕፃን
እርስዋም ቢቀሰቅሱዋት እንኳ አትሰማም::እናትየዋ ሲያዩዋት የተከፋች ምስኪንና ከተማ ስራ ፍለጋ የመጣች የገጠር ሴት ለመሆንዋ ታስታውቃለች:: በእድሜ ልጅ ናት:: ተፈጥሮ
ውበት ቢቸራትም በዚያ ሁኔታዋ ውበትዋ ጎላ ብሎ አይታይም ፀጉርዋ ዞማ እንደሆነ ቢያስታውቅም ተንጨባሮአል:: የተቀዳደደ ሻሽዋ ተፈትቶ
ሊወድቅ ብሎ ከወደኋላዋ ተንጠልጥሎአል፡፡ የደላው ሲስቅ ነጭ ጥርሱን ያሳያል እንጂ የተከፋ ስለማይስቅ ስለጥርሶችዋ ለመናገር አይቻልም:: ለረጅም
ጊዜ ለማልቀስዋ ዓይኖችዋ ይመሰክራለ:: ገርጥታለች፤ ሰውነትዋ በመዛሉ የደከማት ለመሆነ ያስታውቃል፡፡ ምናልባትም ሳትታመም አልቀረችም::ጭንዋ ላይ የተኛችዋን ልጅ አትኩራ በፍቅር ዓይን ትመለከታታለች፡፡ ልጅዋን ደግፋ የያዘችበት እጅ ሲታይ በሥራ ብዛት ለመሻከሩ ጉልህ ነው::
ጠቅላላ ሀናቴዋ ሲታይ ሩህሩህ ልብ ያላቸው ሁሉ የማያልፍዋት
ዓይነት ስለነበረች አንጀት ትበላለች:: በይበልጥ የሚያሳዝነው ግን ማን
ትሁን፤ ከየት ትምጣ ማንም አለማወቁ ነው:: እርስዋም ራስዋ ብትሆን አባትዋና እናትዋ እነማን እንደሆኑ ማለት ማን እንደወለዳት አታውቅም፡፡ስምዋ ፋንቲን ይባላል፡፡ ቤተሰብ ስላልነበራት የአባት ስም የላትም:: የክርስትና
ስምም አልወጣላትም፡፡ ምክንያቱም በዚያ አካባቢ ቤተክርስቲያን ምን እንደሆነ
አይታወቅም:: ፋንቲን ብሎ ስም ያወጣላት በዚያ ሲያልፍ ያገኛት መንገደኛ ነው ይባላል፡፡ ይህ ሰው ይህችን ሕፃን መንገድ ወድቃ ዝናብ ሲዘንብባት ነው ፋንቲን የሚል ስም ያወጣላት:: «ፋንቲን» ማለት ውሃ ወይም ምንጭ
እንደማለት ነው::
ስለዚህች ሴተ ታሪክ ከዚህ ይበልጥ የሚያውቅ ስለሌላ ስላለፈው ታሪክዋ ከዚህ ይበልጥ መናገር አይቻልም:: ሆኖም ፋንቲን ወደዚህች ዓለም ለስቃይ የመጣች በዚህ ዓይነት ነበር ብሎ ለማጠቃለል ይቻላል፡፡ ወደኋላ
እንደተደረሰበት ደግሞ አሥር ዓመት ገደማ ሲሆናት ከከተማ ወጣ ብሎ ወደሚገኝ መንደር ሥራ ፍለጋ ትሄዳለች:: አሥራ አምስት ዓመትዋ አሁንም ሥራ ፍለጋ ወደ ፓሪስ ከተማ ትመጣለች::
በመጨረሻ ጥርሶችዋ ታዩ ፧ እንደወተት የነጡ ነበሩ፡፡ ሌላ ቢጠፋ የእንጨት መፋቂያ አላጣችም ማለት ነው:: ስታገባ የተሰጣት ሳይሆን አይቀርም የሚያማምሩ ጌጣጌጦች አንገትዋ ላይ አስራለች:: ወይም ደግሞ ሥራ ብጤ አግኝታ ትንሽ ከሠራች በኋላ ፤ የገዛቻቸው ይሆናሉ፡፡ ሴት ናትና ማጌጥ አይቀርም:: እርስዋም እንደ ዓቅምዋ ለመኖር ፈልጋ ሥራ
ይዛ ነበር ማለት ነው:: ለመኖር ሆድ እንጀራ እንደሚርበው ሁሉ ልብም ፍቅር ይርበዋልና ልጅዋን እንደዚያ የምታያት የፍቅር ረሃብዋን ለማርካት ነበር፡፡
ያ ስሜት ለሕፃንዋ የእናት ፍቅር ሲሆን ለእናትዮዋ ግን የስሜት
መገንፈል ነበር፡፡ እናትና ልጅ ከተቀመጡበት አቅራቢያ የሚተላለፉ መንገደኞችና ተማሪዎች ቁጥር እጅግ ብዙ ነበር፡፡ ሕፃን ሆና ሕፃን
የታቀፈችዋን ሴት ሁሉም አይቶ አለፋት እንጂ ከመጤፍ የቆጠራት
አልነበረም::
የሕፃንዋ አባት ልጅቱ፡ እንደተወለደች ሚስቱንና ልጁን ጥሎ ከአገር ይጠፋል፡፡ አባት አንዴ ቤተሰቡን ጥሎ። ከሄደ መመለሱ ያጠራጥራል፡፡
ይህም በመሆኑ ልጅትዋ በብቸኝነት ዓለም ውስጥ እየዋዠቀች ስለነበር ተስፋ ከሚፈጥረው ደስታ ርቃለች:: በአንድ ወቅት ተሳሳተች እንጂ
በአፈጣጠርዋ ገራምና ትምክህት የተለያት ለመሆኑ ገፅታዋ ይመሰክራል በፊትዋ ገጽታ ላይ የሚነበብ ገራምነትዋ ብቻ አልነበረም፡፡ ተስፋ
መቁረጥዋን! ቀባሪና ጧሪ የሌላት መሆኑንና ከባድ ችግር ውስጥ
መዘፈቅዋንም ያሳያል፡፡ ሆኖም ፋንቲን ቆራጥና ጠንካራ ሴት ነበረች:: ወደ ትውልድ አገርዋ የመመለስ አሳብ ነበራት፡፡ ምናልባት እዚያ ከሄደን
ድንገት የሚያውቃት ሰው ይኖርና ሥራ ይሰጠኝ ይሆናል የሚል እምነት አድሮባታል፡፡ ነገር ግን የፈጸመችውን ስህተት መደበቅ ስለነበረባት ልብዋ በሀዘን ቢቆስልም ሀሳብዋን ለመፈጸም ቆረጠች፡፡ በሃያ ሁለት ዓመት
፡
፡
#ክፍል_ስድስት
፡
፡
#ትርጉም_ከዬሐንስ_ገፃዲቅ
አንዳንዴ ኃላፊነትን ከመሸከም አሳልፎ መስጠት
በ18ኛው መቶ ክፍለ ዘመን መጀመሪያ ላይ ፓሪስ አጠገብ ከሚገኘው ሞንትፌርሜ ከተባለ ሥፍራ አንድ አነስተኛ ሆቴል ቤት ነበር፡፡ ዛሬ ግን የለም:: ሆቴል ቤቱ፡ ዘቴናድዬስ የተባሉ ባልና ሚስት ንብረት ሲሆን የሚገኘው በላንገር ከተባለ ቀጭን መንገድ ላይ ነበር፡፡ ከቤቱ በራፍ ላይ ስዕል
ተንጠልጥለአል:: ስዕለ ላይ ሜዳሊያ የተሰካላትና በደም ተበክሎ የተቦጫጨቀ የጄኔራል ልብስ የለበሰ ሰው ሸክም ተሸክሞ ነው የሚታየው::በተጨማሪም ከምስሉ ባዶ ሥፍራ ላይ ጭስ በብዛት አለ:: የሚያመለክተው
የጦር ሜዳን ሳይሆን አይቀርም:: ከምስሉ ስር «የዋተርሉ ጦር ሜዳ
ጀግና የሃምሳ አለቃ» የሚል ጽሑፍ ተጽፎበታል:: ከዚህ ሆቴል ቤት በራፍ ጋሪ ቆሞ ማየት አዲስ ነገር አልነበረም:: ሆኖም «ከዋተርሉ የጦር ሜዳ ጀግናው የሃምሳ አለቃ» ሆቴል ቤት በራፍ
የተሰባበረ ጋሪ መንገድ ዘግቶ ሲቆም ዘወትር የሚታይ ትርኢት አይደለም::ጊዜው የፀደይ ወራት ሲሆን ዓመተ ምህረቱ 1818 ዓ.ም ነው፡፡ የጋሪው መንገድ ዘግቶ መቆም ፤ ያን የመሰለ ስዕል ከዚያ ቤት በራፍ መሰቀል በዚያ
ያለፈ የማንኛውም ሰዓሊ ዓይን የሚማርክ ትርዒት ነበር::
ጋሪው ትላልቅ ግንዲላዎችን ጭኖአል፡፡ ታዲያ ይህ ጋሪ ከዚህ ስፍራ ምን ይሠራ ነበር የሚል ጥያቄ ቢነሳ «ከዚያ የተገተረውማ መንገድ ለመዝጋትና የትጉህ ሠራተኞችን ተግባር ለማደናቀፍ ነው» የሚል ትርጉም
ሊያሰጥ ይችላል፡፡
ከጋሪው የእቃ መጫኛ ሥር የተንጠለጠለው ወፍራም ሰንሰለት መሬት ሊነካ ምንም አልቀረው:: አንዲት ሁለት ዓመት ተመንፈቅ የሚሆናት ልጅ ሌላ ዓመት ከስድስት ወር የሚሆናትን ሕፃን ጭንዋ ላይ አሳርፋ
ከሰንሰለቱ ላይ ተቀምጣለች:: ልጆቹ ጅዋጅዌ ላይ እንደወጡ ደስ ብሎአቸዋል፡፡ አንዲት ሴት አቀማመጣቸውን አይታ «ልጆቼ መጫወቻ አገኘ» በማለት ደስ እንደሚላት ማንኛዋም እናት በማተኮር ታያቸዋለች::አተኩሮ ለተመለከታት አንጀት የምትበላ፧ አንዴ እንኳን ለማየት የምትቀፍና
ኑሮ እጅግ ያጎሳቆላት ሌላ ሴት ከበራፉ አጠገብ ተቀምጣለች፡፡ ልጆቹ ደስ ብሏቸው ሲጫወቱ «ምናልባት ፈረሱ ደምብሮ ይጐዳቸው ይሆን» እያለች
የመጀመሪያዋ ሴት አሁንም እንደማንኛውም እናት ማሰብዋ ኣልቀረም::ሰንሰለቱ በተነቃነቀ ቁጥር ሲጥጥ እያለ ይጮሃል:: ድምፁ ሕፃናቱን አልረሸሻቸወም:: የማታ ጨረር ከልጆቹ ላይ በማረፉ ልብ ብሉ ለተመለከታቸው ዓይንን ይማርካለ::
የልጆቹ እናት በድንገት ድምፅ ትሰማለች:: «እሜቴ ደስ የሚሉ
ልጆች ነው ያሉዎት!»
ከምግብ ቤቱ በራፍ የተቀመጠችው ሌላዋ ሴትም ልጅ ታቅፋ ነበር::ከባድ የሚመስል እቃ በጀርባዋ አዝላለች:: እርስዋም የታቀፈቻት ልጅ ሁለት ወይም ሦስት ዓመት ቢሆናት ነው:: በአለባበስ ከሁለቱ ልጆች
ምንም ያህል አትለይም:: ሻሽ መሳይ ጨርቅ አስራለች:: የተቦጫጨቀ ቀሚስዋ ቀዳዳው እስከጭንዋ ሊደርስ ምንም አልቀረ:: ሆኖም ጤነኛ ነበረች:: መልክዋ ድምቡሽቡሽ ያለ ስለሆነ ንከሰኝ፣ ንከሰኝ ትላለች፡፡ዓይኖችዋ ትላልቅ ስለነበሩ እንቅልፍ ቢወስዳትም ሙሉ ለመሉ
አልተከደነም:: ለስለስ ካለው የእናትዋ ክንድ ላይ ተመችቶአት ስለተኛች እንቅልፍ ሳይጠግብ ሲቀሰቅሱት እንደማይስማው እንደማንኛውም ሕፃን
እርስዋም ቢቀሰቅሱዋት እንኳ አትሰማም::እናትየዋ ሲያዩዋት የተከፋች ምስኪንና ከተማ ስራ ፍለጋ የመጣች የገጠር ሴት ለመሆንዋ ታስታውቃለች:: በእድሜ ልጅ ናት:: ተፈጥሮ
ውበት ቢቸራትም በዚያ ሁኔታዋ ውበትዋ ጎላ ብሎ አይታይም ፀጉርዋ ዞማ እንደሆነ ቢያስታውቅም ተንጨባሮአል:: የተቀዳደደ ሻሽዋ ተፈትቶ
ሊወድቅ ብሎ ከወደኋላዋ ተንጠልጥሎአል፡፡ የደላው ሲስቅ ነጭ ጥርሱን ያሳያል እንጂ የተከፋ ስለማይስቅ ስለጥርሶችዋ ለመናገር አይቻልም:: ለረጅም
ጊዜ ለማልቀስዋ ዓይኖችዋ ይመሰክራለ:: ገርጥታለች፤ ሰውነትዋ በመዛሉ የደከማት ለመሆነ ያስታውቃል፡፡ ምናልባትም ሳትታመም አልቀረችም::ጭንዋ ላይ የተኛችዋን ልጅ አትኩራ በፍቅር ዓይን ትመለከታታለች፡፡ ልጅዋን ደግፋ የያዘችበት እጅ ሲታይ በሥራ ብዛት ለመሻከሩ ጉልህ ነው::
ጠቅላላ ሀናቴዋ ሲታይ ሩህሩህ ልብ ያላቸው ሁሉ የማያልፍዋት
ዓይነት ስለነበረች አንጀት ትበላለች:: በይበልጥ የሚያሳዝነው ግን ማን
ትሁን፤ ከየት ትምጣ ማንም አለማወቁ ነው:: እርስዋም ራስዋ ብትሆን አባትዋና እናትዋ እነማን እንደሆኑ ማለት ማን እንደወለዳት አታውቅም፡፡ስምዋ ፋንቲን ይባላል፡፡ ቤተሰብ ስላልነበራት የአባት ስም የላትም:: የክርስትና
ስምም አልወጣላትም፡፡ ምክንያቱም በዚያ አካባቢ ቤተክርስቲያን ምን እንደሆነ
አይታወቅም:: ፋንቲን ብሎ ስም ያወጣላት በዚያ ሲያልፍ ያገኛት መንገደኛ ነው ይባላል፡፡ ይህ ሰው ይህችን ሕፃን መንገድ ወድቃ ዝናብ ሲዘንብባት ነው ፋንቲን የሚል ስም ያወጣላት:: «ፋንቲን» ማለት ውሃ ወይም ምንጭ
እንደማለት ነው::
ስለዚህች ሴተ ታሪክ ከዚህ ይበልጥ የሚያውቅ ስለሌላ ስላለፈው ታሪክዋ ከዚህ ይበልጥ መናገር አይቻልም:: ሆኖም ፋንቲን ወደዚህች ዓለም ለስቃይ የመጣች በዚህ ዓይነት ነበር ብሎ ለማጠቃለል ይቻላል፡፡ ወደኋላ
እንደተደረሰበት ደግሞ አሥር ዓመት ገደማ ሲሆናት ከከተማ ወጣ ብሎ ወደሚገኝ መንደር ሥራ ፍለጋ ትሄዳለች:: አሥራ አምስት ዓመትዋ አሁንም ሥራ ፍለጋ ወደ ፓሪስ ከተማ ትመጣለች::
በመጨረሻ ጥርሶችዋ ታዩ ፧ እንደወተት የነጡ ነበሩ፡፡ ሌላ ቢጠፋ የእንጨት መፋቂያ አላጣችም ማለት ነው:: ስታገባ የተሰጣት ሳይሆን አይቀርም የሚያማምሩ ጌጣጌጦች አንገትዋ ላይ አስራለች:: ወይም ደግሞ ሥራ ብጤ አግኝታ ትንሽ ከሠራች በኋላ ፤ የገዛቻቸው ይሆናሉ፡፡ ሴት ናትና ማጌጥ አይቀርም:: እርስዋም እንደ ዓቅምዋ ለመኖር ፈልጋ ሥራ
ይዛ ነበር ማለት ነው:: ለመኖር ሆድ እንጀራ እንደሚርበው ሁሉ ልብም ፍቅር ይርበዋልና ልጅዋን እንደዚያ የምታያት የፍቅር ረሃብዋን ለማርካት ነበር፡፡
ያ ስሜት ለሕፃንዋ የእናት ፍቅር ሲሆን ለእናትዮዋ ግን የስሜት
መገንፈል ነበር፡፡ እናትና ልጅ ከተቀመጡበት አቅራቢያ የሚተላለፉ መንገደኞችና ተማሪዎች ቁጥር እጅግ ብዙ ነበር፡፡ ሕፃን ሆና ሕፃን
የታቀፈችዋን ሴት ሁሉም አይቶ አለፋት እንጂ ከመጤፍ የቆጠራት
አልነበረም::
የሕፃንዋ አባት ልጅቱ፡ እንደተወለደች ሚስቱንና ልጁን ጥሎ ከአገር ይጠፋል፡፡ አባት አንዴ ቤተሰቡን ጥሎ። ከሄደ መመለሱ ያጠራጥራል፡፡
ይህም በመሆኑ ልጅትዋ በብቸኝነት ዓለም ውስጥ እየዋዠቀች ስለነበር ተስፋ ከሚፈጥረው ደስታ ርቃለች:: በአንድ ወቅት ተሳሳተች እንጂ
በአፈጣጠርዋ ገራምና ትምክህት የተለያት ለመሆኑ ገፅታዋ ይመሰክራል በፊትዋ ገጽታ ላይ የሚነበብ ገራምነትዋ ብቻ አልነበረም፡፡ ተስፋ
መቁረጥዋን! ቀባሪና ጧሪ የሌላት መሆኑንና ከባድ ችግር ውስጥ
መዘፈቅዋንም ያሳያል፡፡ ሆኖም ፋንቲን ቆራጥና ጠንካራ ሴት ነበረች:: ወደ ትውልድ አገርዋ የመመለስ አሳብ ነበራት፡፡ ምናልባት እዚያ ከሄደን
ድንገት የሚያውቃት ሰው ይኖርና ሥራ ይሰጠኝ ይሆናል የሚል እምነት አድሮባታል፡፡ ነገር ግን የፈጸመችውን ስህተት መደበቅ ስለነበረባት ልብዋ በሀዘን ቢቆስልም ሀሳብዋን ለመፈጸም ቆረጠች፡፡ በሃያ ሁለት ዓመት
👍21❤1
#ገረገራ
፡
፡
#ክፍል_ስድስት
፡
፡
#በታደለ_አያሌው
...ወደ መኪናዬ ሽምጥ እየሮጥሁ ሳለ ነበር፣ የንስሐ አባቴን እንኳን
እንዳልተሰናበትኋቸዉ ያወቅሁት፡፡ እንደ ልማዴ በጥድፊያ ወደ ሲራክ፯ አሽከረከርኩ። መቼም ከባልቻ የተደበቀ ነገር የለም፡፡ እሱን አግኝቼ እስከማማክረዉ ድረስ ትንፋሼን እንኳን ወደ ዉስጥ መሳብ አልሆነልኝም፡፡ ቸኩያለሁ። አይደርሱት የለም ደረስሁና ቢሮዉን በርግጄ ስገባ፣ ባልቻ በወንበሩ ላይ ለጠጥ ብሎ እንቅልፍ አሸልቦት አገኘሁት።
በተለይም የሲራክ ፯ ዋና ኃላፊ ከሆነ በኋላ የግል መኖሪያ ቤቱን አይቶት የሚያዉቅ አይመስለኝም። ዉሎዉም አዳሩም እዚሁ ሆኗል። እዚሁ ምግብ ያስመጣል፣ እዚሁ ወንበሩ ላይ ትንሽ ዕረፍት ያደርጋል። ከስንት አንድ ወደ ዉጪ ቢወጣ እንኳን ምክንያቱ ለዚሁ ለሲራክ ጉዳይ ብቻ
ነዉ፡፡
“ባልቻ!” ብዬ ስጮህበት፣ ብርግግ ብሎ ብድግ አለልኝ።
“ዉብርስት?” አለ ተጨናብሶ፣ እጁን ለሰላምታ እየዘረጋልኝ፡፡
“እሰይ! ‹ዉብርስት?” አልሁት፣ ልጃለሜ የሚለዉ ቁልምጫዉ
መቅረቱ ከንክኖኝ፡፡ እኔ ደግሞ ከእሱ ብቻ ሳይሆን ከማንም ቁልምጫ የለመድሁ ሰዉ ነኝ። ቁልምጫዉን ሳይቀር እንደገና በሚያቆላምጥ ቤተሰብ መሀል ነዉ ያደግሁት። ያዉም ዉብዬዋ፣ ‹ዉቤዋ፣ የኔ ዉብ፣ ዓለሜዋ፣ ‹ልጃለሜ› እየተባልሁ። ባልቻ እንዲሁ እንደ ወረደ በስሜ ጠርቶኝ ካለማወቁ የተነሳ፣ ስሜን ሁሉ የሚያዉቀዉ አይመስለኝም
ነበር። ትዝ ሲለኝ እኔ ራሴ ባልቻ ብዬ ነዉ የጠራሁት ለካ። «አባታለም» የሚለዉ ቁልምጫዬስ? የት ተዉሁት?
“ይኸዉ መጣሽ። በስንት ጊዜሽ? ስደዉል ሳታነሺ፣ ሳስጠራሽ ሳትመጪ፣ ስፈልግሽ ሳትገኘ፤ ዛሬ ምን አመጣሽ በይ?”
“እሸቴ ጠፍቷል”
“ጠፋ? ማን እፍ ብሎት ይሆን በናትሽ? ቀድሞስ በርቶ ኖሯል እንዴi” ሲል አላገጠብኝ፡፡
“ማላገጥህ ነዉ?”
“ራስሽ ከመሀል ጀመርሽዋ! እኔና አንቺ እኮ ገና እንደገና መተዋወቅ
አለብን። ቆይ የት አዉቅሻለሁ? አንቺ ታዉቂኛለሽ?”
“በማርያም አባታለም? ፈርቻለሁ። እሽቴ በመንግሥት ደኅንነቶች እጅ
ወድቆ እንዳይሆን ልቤ ሰግቷል”
“እና ምናገባኝ እኔን?”
“ኧረ ባዛኝቱ? እንዴት ነዉ የማያገባህ፤ እሽቴ እኮ ነዉ!”
"የሆነስ እንደሆነ!”
“አዉቃለሁ አሳዝኜሃለሁ። ለዚያም እንዴ ት ይቅርታ መጠየቅ እንዳለብኝ አላዉቅም። ቢሆንም ግን በዚህ መሀል እሸቴ በጨካኞች እጅ ወድቆ
ከሆነ አያሳዝንህም?”
“ያሳዝነኛል”
“እኮ አንድ ነገር አድርጋ”
“ምን ላድርግ?”
“የማታስፈልገዉ?”
“እሺ። አስፈልጌ ሳገኘዉስ?”
“ያንተን አላዉቅም። እኔ ግን ተንበርክኬ ይቅርታ እለምነዋለሁ”
“ለምን?”
“ስለሚገባዉ”
“እሺ። መጀመሪያ ግን እንስማማ”
“ንገረኝ በምን?”
“ተንበርክከሽ የምትጠብቀዉ ከሆነና፣ ተሳክቶልኝ ካገኘሁት ደግሞ ወደ ሆስፒታል ለመሄድ ቃል ከገባሽልኝ.…”
“ይኼዉ!” ብዬ ጉልበቴ ግዉ እስከሚል ድረስ ወድቄ ተንበረከክሁ፡፡
“ብቻ አንተ እሺ በለኝ። እገባለሁ። እሄዳለሁ፤ አሁኑኑ ፈልግልኝ!”
“ዉዉዉ-ዉቤ?” የሚል ድምፅ ከኋላዬ ሰማሁ። ማን በተብታባ ድምፁ እንደ ጠራኝ ለማጣራት ዞሬ ማየት ያስፈልገኝ ኖሯል? ኧረ በጭራሽ በጠረኑ ብቻ አዉቀዋለሁ፡፡ እሸቴ ነዉ፡፡ ወይ ባልቻ! ምን ዓይነት ልብ
ነዉ የታደለዉ ግን? መቼም ጨክኖ ማኩረፉን አያውቅበት! ሆነ ብሎ ኖሯል ለካ እሸቴን ከሁላችንም እይታ እንዲጠፋ ያደረገዉ፡፡ እኔ እንደሆነ
እንዳልሞተ ሰዉ የማራክስዉ ነገር የለኝም፡፡ ጊዜ እንኳን ዉድ
የሚሆንብኝ ካለፈ በኋላ ዞሬ ሳየዉ ብቻ ነዉ። እቃም ቢሆን ከእጅ አምልጦ ካልተሰበረ ወይ ደግሞ ካልተሰረቀ በቀር ዉድነቱ አይታወቀኝም።እሸቴንም ባላጣዉ ኖሮ አልፈልገዉም ነበር። ለዚህ ይመስለኛል ባልቻም
እሸቴን ከዓይኔ እንዲጠፋ ያደረገብኝ። የእሽቴን ዉድነት እንዳምን፣ ከዓይኔ ሠወረብኝ፡፡ እንኳንም ሠወረብኝ፣ እንኳንም ናፈቅሁት፣ እንኳንም
አገኘሁት። ተሳክቶለታል።
ባልቻን በስስትም በኩራትም እያየሁት ሳለ፣ እሸቴ ከፊት ለፊቴ መጥቶ እንደኔዉ በጉልበቱ ወደቀ። ጥዉልግ ብሏል። ከንፈሩ ሳይቀር ኩችር ብሎ ደርቆ ታየኝ፡፡
“እሽቴ?”
“ጨጨጨ ጨከንሽብኝ እኮ
ዉቤ”
“ኹለተኛ አላደርገዉም”
“አአአ አአ አለሽልኝ ግን?”
“አለሁልህ። አለህልኝ?”
የባልቻን መኖር ሁሉ ረስተን፣ አንገት ለአንገት ተቆላልፈን ቆየን፡፡
እንደዚሁ እንዳለን፣ ልክ እሸቴን እንዳገኘልኝ ወደ ሆስፒታል ለመሄድ የገባሁት ቃል ትዝ አለኝ። እስከሚነጋ ቸኮልሁ።
ከአምስት ወር በላይ በሆዴ ፅንስ ይዤ፣ ያዉም እኔ ራሴ የሕክምና
ባለሙያ ሆኜ ፤ እስከ አሁን ግን የሕክምና ክትትል አለመጀመሬ ለግድ የለሽነቱ ወደር የማይገኝልኝ ሴት መሆኔን መስክሮብኛል፡፡ ይኼንን ማንም ሳይነግረኝ አዉቄዋለሁ። ሲሆን ሲሆን እርግዝና ከመፈጠሩ ከዓመት ወይ
ከወራት ቀደም ሲል ጀምሬ ዝግጅት ማድረግ ነበረብኝ፡፡ እንደኔ እንኳን እርግዝናዉ በድንገት ለተፈጠረበትም ቢሆን፣ ከመጀመሪያዉ ጀምሮ
ሙሉ ምርመራ እና ክትትል ማድረግ የግድ ነዉ። እኔ ግን ቢያንስ ቅሪት መሆኔን ያወቅሁት ቶሎ ቢሆንም፣ ይኼዉ 22ኛ ሳምንቴን ጭልጥ አድርጌ ነዉ ገና ነገርዮዉን እንኳን በበጎነቱ የተቀበልሁት።
ዛሬ ነዉ ወደ ሆስፒታል ለመምጣት የወሰንሁት። ዛሬ ገና።
ዛሬ ግን ቆርጬ መጥቻለሁ።
በእናቶች እና ሕጻናት ሕክምና ዝነኛ ወደ ሆነዉ ሐሚያሉ ሆስፒታል ገብቼ ካርድ አወጣሁና ወደ ተጠቆምሁት የዶክተር ክፍል አመራሁ። ብዙም ሳልቆይ ወረፋዬ ደረሰኝና፣ መለስ ያለዉን በር ገፍቼ ወደ ዉስጥ ገባሁ። ሆስፒታሉን በበጎ ስሙ መረጥሁት እንጂ፣ የተለየ የሐኪም ምርጫ አላደረግሁም ነበር። ሆኖም ከዉስጥ የጠበቀችኝን ሐኪም ካየሁ በኋላ፤ ሕይወት የአጋጣሚዎች ጋን መሆኗን አመንሁ።
ሐኪሟ ስንቱን አብራኝ ያሳለፈች፣ የቀድሞ ጓደኛዬ ሆና እርፍ!
“ሸዊት!” አልኋት፣ ለረዥም ደቂቃ እጄን አፌ ላይ ጭኜ ስደነቅ ከቆየሁ በኋላ።
"የፈጣሪ ያለህ! ዉብዬ ?” አለች እሷም፣ አሁንም አሁንም ዓይኖቿን
ጨፍና እየገለጠቻቸዉ። ከመልኬ እኩል በሆዴ ያለዉን አስተዉላለች፡፡ ከነጭራሹ የምንገናኝ፣ ያዉም እንዲህ ሆኜ፣ አልጠበቀችኝም ነበር። ለነገሩማ እኔስ እንዴት ብዬ እጠብቃለሁ? በጎንደር ዩኒቨርስቲ የሕክምና
ዶክትሬት ዲግሪያችንን አብረን በተማርንበት ወቅት የነበረንን ጓደኝነት አይቶ ትንሽ ትልቁ እንደዚያ ከዓይን ያዉጣችሁ እንዳላለን ሁሉ፣ እንደዚህ በአንድ ከተማ መኖራችንን እንኳን እስካለመተዋወቅ ድረስ
መራራቃችን ዋዛ ነዉ፡፡ ምን ሆነን ነዉ ግን? ምንም፡፡ ለነገሩ ዩኒቨርስቲ ካስተዋወቀኝ ወዳጆቼ ማንን አግኝቼ አዉቃለሁ? ከስንት አንድ በአጋጣሚ ካልሆነ በቀር፣ አብዛኞቹ የት እንዳሉ እንኳን አላዉቅም፡፡
“ዋዉ!” አለችኝ፣ እንደ ታቦት እየዞረችኝ፡፡
“እሩ እስኪ ሰላም በዪኝ መጀመሪያ”
“እንኳን ለዚህ አበቃሽ ዉብዬ” ብላ መጥታ አንገቴ ሥር ሰረገች፡፡
እንደገና ሆድ ሆዴን ትኩር ብላ አየችኝና፣ ጭምጭም አድርጋ ሳመችኝ፡፡የምር ደስ ብሏታል። እንባዋ ሳይቀር ጠይም ጉንጮቿን እያራሰ በብርቅዬ አንገቷ በኩል ፈሰሰ።
ሀገር ዉስጥ ነዉ የምትኖሪዉ? ጭራሽ እዚሁ አዲስ አበባ?” አልኋት፣
ደስታዋ እንዲጋባብኝ ልቤን እየደቃሁት።
“አይ፤ ቅርብ ጊዜ ነዉ የመጣሁት። ጀርመን ነበርሁ፣ ትምህርት ላይ”
“ተዪ እንጂ? ጀርመን፤ ምን ስፔሻላይዝ አደረግሽ ታዲያ?”
“ይኸዉ እያየሽኝ? ለእር ግዝና ክትትል አይደል እንዴ እኔ ጋ
የመጣሽዉ?”
“አይ አጅሪት! እንዲያ ነዉ እንጂ የኔ እህት! ደግሞ ጥሩ ምርጫ ነዉ”
“አንቺስ ምን አጠናሽ?”
፡
፡
#ክፍል_ስድስት
፡
፡
#በታደለ_አያሌው
...ወደ መኪናዬ ሽምጥ እየሮጥሁ ሳለ ነበር፣ የንስሐ አባቴን እንኳን
እንዳልተሰናበትኋቸዉ ያወቅሁት፡፡ እንደ ልማዴ በጥድፊያ ወደ ሲራክ፯ አሽከረከርኩ። መቼም ከባልቻ የተደበቀ ነገር የለም፡፡ እሱን አግኝቼ እስከማማክረዉ ድረስ ትንፋሼን እንኳን ወደ ዉስጥ መሳብ አልሆነልኝም፡፡ ቸኩያለሁ። አይደርሱት የለም ደረስሁና ቢሮዉን በርግጄ ስገባ፣ ባልቻ በወንበሩ ላይ ለጠጥ ብሎ እንቅልፍ አሸልቦት አገኘሁት።
በተለይም የሲራክ ፯ ዋና ኃላፊ ከሆነ በኋላ የግል መኖሪያ ቤቱን አይቶት የሚያዉቅ አይመስለኝም። ዉሎዉም አዳሩም እዚሁ ሆኗል። እዚሁ ምግብ ያስመጣል፣ እዚሁ ወንበሩ ላይ ትንሽ ዕረፍት ያደርጋል። ከስንት አንድ ወደ ዉጪ ቢወጣ እንኳን ምክንያቱ ለዚሁ ለሲራክ ጉዳይ ብቻ
ነዉ፡፡
“ባልቻ!” ብዬ ስጮህበት፣ ብርግግ ብሎ ብድግ አለልኝ።
“ዉብርስት?” አለ ተጨናብሶ፣ እጁን ለሰላምታ እየዘረጋልኝ፡፡
“እሰይ! ‹ዉብርስት?” አልሁት፣ ልጃለሜ የሚለዉ ቁልምጫዉ
መቅረቱ ከንክኖኝ፡፡ እኔ ደግሞ ከእሱ ብቻ ሳይሆን ከማንም ቁልምጫ የለመድሁ ሰዉ ነኝ። ቁልምጫዉን ሳይቀር እንደገና በሚያቆላምጥ ቤተሰብ መሀል ነዉ ያደግሁት። ያዉም ዉብዬዋ፣ ‹ዉቤዋ፣ የኔ ዉብ፣ ዓለሜዋ፣ ‹ልጃለሜ› እየተባልሁ። ባልቻ እንዲሁ እንደ ወረደ በስሜ ጠርቶኝ ካለማወቁ የተነሳ፣ ስሜን ሁሉ የሚያዉቀዉ አይመስለኝም
ነበር። ትዝ ሲለኝ እኔ ራሴ ባልቻ ብዬ ነዉ የጠራሁት ለካ። «አባታለም» የሚለዉ ቁልምጫዬስ? የት ተዉሁት?
“ይኸዉ መጣሽ። በስንት ጊዜሽ? ስደዉል ሳታነሺ፣ ሳስጠራሽ ሳትመጪ፣ ስፈልግሽ ሳትገኘ፤ ዛሬ ምን አመጣሽ በይ?”
“እሸቴ ጠፍቷል”
“ጠፋ? ማን እፍ ብሎት ይሆን በናትሽ? ቀድሞስ በርቶ ኖሯል እንዴi” ሲል አላገጠብኝ፡፡
“ማላገጥህ ነዉ?”
“ራስሽ ከመሀል ጀመርሽዋ! እኔና አንቺ እኮ ገና እንደገና መተዋወቅ
አለብን። ቆይ የት አዉቅሻለሁ? አንቺ ታዉቂኛለሽ?”
“በማርያም አባታለም? ፈርቻለሁ። እሽቴ በመንግሥት ደኅንነቶች እጅ
ወድቆ እንዳይሆን ልቤ ሰግቷል”
“እና ምናገባኝ እኔን?”
“ኧረ ባዛኝቱ? እንዴት ነዉ የማያገባህ፤ እሽቴ እኮ ነዉ!”
"የሆነስ እንደሆነ!”
“አዉቃለሁ አሳዝኜሃለሁ። ለዚያም እንዴ ት ይቅርታ መጠየቅ እንዳለብኝ አላዉቅም። ቢሆንም ግን በዚህ መሀል እሸቴ በጨካኞች እጅ ወድቆ
ከሆነ አያሳዝንህም?”
“ያሳዝነኛል”
“እኮ አንድ ነገር አድርጋ”
“ምን ላድርግ?”
“የማታስፈልገዉ?”
“እሺ። አስፈልጌ ሳገኘዉስ?”
“ያንተን አላዉቅም። እኔ ግን ተንበርክኬ ይቅርታ እለምነዋለሁ”
“ለምን?”
“ስለሚገባዉ”
“እሺ። መጀመሪያ ግን እንስማማ”
“ንገረኝ በምን?”
“ተንበርክከሽ የምትጠብቀዉ ከሆነና፣ ተሳክቶልኝ ካገኘሁት ደግሞ ወደ ሆስፒታል ለመሄድ ቃል ከገባሽልኝ.…”
“ይኼዉ!” ብዬ ጉልበቴ ግዉ እስከሚል ድረስ ወድቄ ተንበረከክሁ፡፡
“ብቻ አንተ እሺ በለኝ። እገባለሁ። እሄዳለሁ፤ አሁኑኑ ፈልግልኝ!”
“ዉዉዉ-ዉቤ?” የሚል ድምፅ ከኋላዬ ሰማሁ። ማን በተብታባ ድምፁ እንደ ጠራኝ ለማጣራት ዞሬ ማየት ያስፈልገኝ ኖሯል? ኧረ በጭራሽ በጠረኑ ብቻ አዉቀዋለሁ፡፡ እሸቴ ነዉ፡፡ ወይ ባልቻ! ምን ዓይነት ልብ
ነዉ የታደለዉ ግን? መቼም ጨክኖ ማኩረፉን አያውቅበት! ሆነ ብሎ ኖሯል ለካ እሸቴን ከሁላችንም እይታ እንዲጠፋ ያደረገዉ፡፡ እኔ እንደሆነ
እንዳልሞተ ሰዉ የማራክስዉ ነገር የለኝም፡፡ ጊዜ እንኳን ዉድ
የሚሆንብኝ ካለፈ በኋላ ዞሬ ሳየዉ ብቻ ነዉ። እቃም ቢሆን ከእጅ አምልጦ ካልተሰበረ ወይ ደግሞ ካልተሰረቀ በቀር ዉድነቱ አይታወቀኝም።እሸቴንም ባላጣዉ ኖሮ አልፈልገዉም ነበር። ለዚህ ይመስለኛል ባልቻም
እሸቴን ከዓይኔ እንዲጠፋ ያደረገብኝ። የእሽቴን ዉድነት እንዳምን፣ ከዓይኔ ሠወረብኝ፡፡ እንኳንም ሠወረብኝ፣ እንኳንም ናፈቅሁት፣ እንኳንም
አገኘሁት። ተሳክቶለታል።
ባልቻን በስስትም በኩራትም እያየሁት ሳለ፣ እሸቴ ከፊት ለፊቴ መጥቶ እንደኔዉ በጉልበቱ ወደቀ። ጥዉልግ ብሏል። ከንፈሩ ሳይቀር ኩችር ብሎ ደርቆ ታየኝ፡፡
“እሽቴ?”
“ጨጨጨ ጨከንሽብኝ እኮ
ዉቤ”
“ኹለተኛ አላደርገዉም”
“አአአ አአ አለሽልኝ ግን?”
“አለሁልህ። አለህልኝ?”
የባልቻን መኖር ሁሉ ረስተን፣ አንገት ለአንገት ተቆላልፈን ቆየን፡፡
እንደዚሁ እንዳለን፣ ልክ እሸቴን እንዳገኘልኝ ወደ ሆስፒታል ለመሄድ የገባሁት ቃል ትዝ አለኝ። እስከሚነጋ ቸኮልሁ።
ከአምስት ወር በላይ በሆዴ ፅንስ ይዤ፣ ያዉም እኔ ራሴ የሕክምና
ባለሙያ ሆኜ ፤ እስከ አሁን ግን የሕክምና ክትትል አለመጀመሬ ለግድ የለሽነቱ ወደር የማይገኝልኝ ሴት መሆኔን መስክሮብኛል፡፡ ይኼንን ማንም ሳይነግረኝ አዉቄዋለሁ። ሲሆን ሲሆን እርግዝና ከመፈጠሩ ከዓመት ወይ
ከወራት ቀደም ሲል ጀምሬ ዝግጅት ማድረግ ነበረብኝ፡፡ እንደኔ እንኳን እርግዝናዉ በድንገት ለተፈጠረበትም ቢሆን፣ ከመጀመሪያዉ ጀምሮ
ሙሉ ምርመራ እና ክትትል ማድረግ የግድ ነዉ። እኔ ግን ቢያንስ ቅሪት መሆኔን ያወቅሁት ቶሎ ቢሆንም፣ ይኼዉ 22ኛ ሳምንቴን ጭልጥ አድርጌ ነዉ ገና ነገርዮዉን እንኳን በበጎነቱ የተቀበልሁት።
ዛሬ ነዉ ወደ ሆስፒታል ለመምጣት የወሰንሁት። ዛሬ ገና።
ዛሬ ግን ቆርጬ መጥቻለሁ።
በእናቶች እና ሕጻናት ሕክምና ዝነኛ ወደ ሆነዉ ሐሚያሉ ሆስፒታል ገብቼ ካርድ አወጣሁና ወደ ተጠቆምሁት የዶክተር ክፍል አመራሁ። ብዙም ሳልቆይ ወረፋዬ ደረሰኝና፣ መለስ ያለዉን በር ገፍቼ ወደ ዉስጥ ገባሁ። ሆስፒታሉን በበጎ ስሙ መረጥሁት እንጂ፣ የተለየ የሐኪም ምርጫ አላደረግሁም ነበር። ሆኖም ከዉስጥ የጠበቀችኝን ሐኪም ካየሁ በኋላ፤ ሕይወት የአጋጣሚዎች ጋን መሆኗን አመንሁ።
ሐኪሟ ስንቱን አብራኝ ያሳለፈች፣ የቀድሞ ጓደኛዬ ሆና እርፍ!
“ሸዊት!” አልኋት፣ ለረዥም ደቂቃ እጄን አፌ ላይ ጭኜ ስደነቅ ከቆየሁ በኋላ።
"የፈጣሪ ያለህ! ዉብዬ ?” አለች እሷም፣ አሁንም አሁንም ዓይኖቿን
ጨፍና እየገለጠቻቸዉ። ከመልኬ እኩል በሆዴ ያለዉን አስተዉላለች፡፡ ከነጭራሹ የምንገናኝ፣ ያዉም እንዲህ ሆኜ፣ አልጠበቀችኝም ነበር። ለነገሩማ እኔስ እንዴት ብዬ እጠብቃለሁ? በጎንደር ዩኒቨርስቲ የሕክምና
ዶክትሬት ዲግሪያችንን አብረን በተማርንበት ወቅት የነበረንን ጓደኝነት አይቶ ትንሽ ትልቁ እንደዚያ ከዓይን ያዉጣችሁ እንዳላለን ሁሉ፣ እንደዚህ በአንድ ከተማ መኖራችንን እንኳን እስካለመተዋወቅ ድረስ
መራራቃችን ዋዛ ነዉ፡፡ ምን ሆነን ነዉ ግን? ምንም፡፡ ለነገሩ ዩኒቨርስቲ ካስተዋወቀኝ ወዳጆቼ ማንን አግኝቼ አዉቃለሁ? ከስንት አንድ በአጋጣሚ ካልሆነ በቀር፣ አብዛኞቹ የት እንዳሉ እንኳን አላዉቅም፡፡
“ዋዉ!” አለችኝ፣ እንደ ታቦት እየዞረችኝ፡፡
“እሩ እስኪ ሰላም በዪኝ መጀመሪያ”
“እንኳን ለዚህ አበቃሽ ዉብዬ” ብላ መጥታ አንገቴ ሥር ሰረገች፡፡
እንደገና ሆድ ሆዴን ትኩር ብላ አየችኝና፣ ጭምጭም አድርጋ ሳመችኝ፡፡የምር ደስ ብሏታል። እንባዋ ሳይቀር ጠይም ጉንጮቿን እያራሰ በብርቅዬ አንገቷ በኩል ፈሰሰ።
ሀገር ዉስጥ ነዉ የምትኖሪዉ? ጭራሽ እዚሁ አዲስ አበባ?” አልኋት፣
ደስታዋ እንዲጋባብኝ ልቤን እየደቃሁት።
“አይ፤ ቅርብ ጊዜ ነዉ የመጣሁት። ጀርመን ነበርሁ፣ ትምህርት ላይ”
“ተዪ እንጂ? ጀርመን፤ ምን ስፔሻላይዝ አደረግሽ ታዲያ?”
“ይኸዉ እያየሽኝ? ለእር ግዝና ክትትል አይደል እንዴ እኔ ጋ
የመጣሽዉ?”
“አይ አጅሪት! እንዲያ ነዉ እንጂ የኔ እህት! ደግሞ ጥሩ ምርጫ ነዉ”
“አንቺስ ምን አጠናሽ?”
👍48❤1
#ሳቤላ
፡
፡
#ክፍል_ስድስት
፡
፡
#ድርሰት_ሚሲስ_ሔንሪ_ውድ
ዌስትሊን መኻል ተጠጋግተው የተሠሩ ሁለት ቤቶች ይታያሉ " አንዱ ትልቅ ሌላው አነስ ያለ ሲሆን ትልቁ የካርላይል መኖሪያ ትንሹ ደግሞ ቤሮው ነው ካርላይል የሚለው ስም በዚያ አካባቢ በጣም የታወቀ ነው " ካርላይልና ዴቪድስን በአንደኛው ደረጃ የሚቀጠሩ ጠበቆች ነበሩ " ዱሮ ካርላይልና ዴቪድሰን በጋራ
ይዘውት የነበረ ድርጅት ዛሬ አርኪባልድ ካርላይል የብቻው አድርጐታል እነዚ የሥራ ሸሪኮች አምቻዎችም ነበሩ " የጀመሪያይቱ ሚሲዝ ካርላይል የሚስተር
ዴቪድሰን እኅት ነበረች እሷም ኮርኒሊያን ብቻ ከወለደችለት በኋላ ሞተች ኮርኒሊያ ትልቅ ልጅ ከሆነች በኋላ ሚስተር ካርላይል ሁለተኛ ሚስቱን አገባ " ሁላተኛይቱ ሚሲዝ ካርላይል ደግሞ የመጀመሪያ ልጅዋን አርኪባልድ ካርላይልን ወልዳለት ሞተችና እኀቱ ኮርነሊያ ተንከባክባ እንደ እናት ተጨንቃ እሷ በምትፈልገው ዐይነት መርታ አሳደገችው " ልጁም ሌላ እናት አያውቅም ነበርና እማማ ኮርኒ” ይላት ነበር እማማ ኮርኒ ለሱ ማድረግ የነበረባትን ሁሎ ፈጽማለታለች
ነገር ግን ዛሬም ትልቅ ከሆነ በኋላ ልክ እንደ ልጅነቱ በሷ እንዲመራ ትፈልጋለች
ከልማድ መላቀቅ በጣም ከባድ በመሆኑ አርኪባልድም ቢሆን ብዙውን ጊዜ እንዳለችው ይታዘዛታል » በአንዳንድ ነገሮች ደካማ አስተያት ይኑራት እንጂ ባጠቃላይ ግን ብርቱ ሴት ነበረች " ያለ የሌለ ሐሳቧ የአርኪባልድና የንዘብ ማስቀመጥ ፍቅር ብቻ ነበር " ሚስተር ዴቪድሰን ትዳር የሚባል ሳይሞክር ከሥራ ሸሪኩ ከሚስተር ካርላይል ቀደም ብሎ ሲሞት 'ሀብቱን ለኮርነሊያና ለአርኪባልድ እኩል አወረሳቸው " አርኪባልድን ባይዛመደውም በጥሩ ምግባሩ ይወደው ነበር ሚስተር ካርላይል ብዙ ሀብት ሊያከማች የቻለው ሁለተኛዋ ሚስቱ ባመጣችው ኻያ ሺህ ፖውንድ በመሆኑ ይሆናል ለሴት ልጁ ለኮርነሊያ ጥቂት ሰጥቶ አብዛኛውን አርኪባልድ አውርሶት የሞተው "
ሚስ ካርላይል ወይም በከተማው እንደምትጠራው ሚስ ኮርኒ ባል አላገባችም ሰዎች ለትንሽ ወንድሟ የነበራት ፍቅር ሳታገባ ብቸኛ ሆና እንድትቀር ያደረጋት ይመስላቸው ነበር ነገር ግን የባለጸጋው የሚስተር ካርላይል ልጅ ከነጭራሹ ባል የምትፈልግ አትመስልም ነበር " የፍቅር ነገር ይዘው የቀረቧትን ሁሉ አፋቸውን እያስያዘች መልሳቸዋለች የመጨረሻውን ሙከራ ያደረገው አንድ አዲስ የመጣ ቄስ ነበር " የዚያን ጊዜ ዐርባኛ ዐመቷን ይዛ ነበር አንድ ቀን ነጭ ክራባት አስሮ ወይን ጠጅ ቀለም የእጅ ሹራብ አጥልቆ አሸብርቆ ከጧቱ ቀዶም ብሎ ከቤቷ መጣ
ሚስ ኮሮኒ ከልክ ያለ የቤት አያያዝ ዐዋቂ ገረዶቿ ሊፈጽሙት ከሚፈልጉት የበለጠች ጠንቃቃ ነበረች " ለምሳ የሚዘጋጅ ሥጋ የሚጋገር ሊጥ እየመጠነች ስትሰጥና ስለ ዝግጅቱም እያስረዳች ሳለች የምግብ ቤቱ በር ተከፈተ ወዲያው ቄሱ ገባ " የዩልኝታን ነገር እርግፍ አድርጋ የተወችው ሚስ ካርላይል እንግዳ በመምጣቱ ልታጠብ ልለቃለቅ አላለችም- ሊጥ ስትከፋፍልበት የነበረ አንድ ሳህን እንድ ያዘች እንግዳው ዐረፍ ከሚልበት ምግብ ቤት ገባች "
በዐሥራ ሁለት ዓመት በዕድሜ የምትበልጠው መንፈሳዊ ሰው የሚላትን እስክትሰማ ሰሐኑን ጉኗ በነበረው ጠረጴዛ ላይ አሳረፈችው ኮርነሊያ የያዘችውን ሥራ እንዳደበላሽባት ሰውየው ሳይንተባተብባትና ሳይዘበዝብ ቶሎ እንዲወጣላት መፈለጓን
በተዘዋዋሪ መንገድ ስትጠቁመው አልገባው ሲል ቀጥውን በመንገር አጣደፈሻው » እሱ ለአንድ በጎ አድራጐት ድርጅት በረጂ አባልነት እንድትመዘገብ ሊጠይቃት መሰላት » ከሷ በሁለት ስንዝር ያህል አጠር ይል ስለነበር እሁንም ነገር አልቆርጥ በማለቱ ትግሥቷን ጨርሳ ቁልቁል ትመለከተው ጀመር" በመጨረሻ እሷን እንጂ ገንዘቧን ፈልጎ እንዳልመጣ ነገሩን ገልጾ ሲነግራት እሳት ሆነችበት " እሱን የመሰለ ውርጋጥ እሷን ለዚህ ነገር ደፍሮ ሲያስባት ኣለማፈሩን እየነገረች የቁጣ
መዓቷን አወረዶችበትና ያን ከጠረጴዛው ላይ በሰሐን አኑራው የነበረውን ሊጥ ብድግ አድርጋ በረዶ ከመሰለው ነጭ ሸሚዙ ላይ ለደፈችበት » ኃፍረትና ድንጋጤ ኩምሽሽ ያደረገው ካህን እንዴት አድርጎ ከቤት ወጥቶ በዌስት ሊን ቁልቁል ወርዶ ቤቱ እንዶ ደረሰ ለማስታወስ እንኳን አይፈልግም ነበር " ወሬው ግን ባንድ ጊዜ ዳር እስከ ዳር ተዳረሰና ከዚያ ወዲህ ሚስ ኮርኒን ለጋብቻ በመጠየቅ ረገድ ማንም ስው አስቸግሯት አያውቅም "
ሚስተር ካርላይል ከለንደን በተመለሰ ማግሥት ጧቱን ከቢሮው ገብቶ ተቀምጧል " አብዛኛውን ጊዜ ሥራውን የሚያካሒድለት ታማኝ ጸሐፊውና ሥራ አስኪያጁ የሆነው ሚስተር ዲል ከአጠገቡ ቆሟል " ሚስተር ዲል ዐይን አፋር ቢጤ አጭር ' ቀጭንና ራስ መላጣ ነበር " ድሮ በትልቁ ካርላይልና በዴቪድስን ጊዜ ቀጥሮ ገባ ጀምሮ ችሎታውና የሥራ ልምዱ ሳያንሰው ራሱን ችሎ ከመሥራት ይልቅ ሥራ አስኪያጅ እየተባለ በሰው ሥር ሆኖ ደኅና ደመወዝ እያገኘ መኖሩ ምኞቱን ያረካለት ይመስላል " ለመለየት አሳብ አልነበረውም » በዚያው አካባቢ በአንድ
ጥሩ ቤት ሲኖር እሱም እንደ ኮርነሊያ አላገባም ነበር " የሚስ ካርላይል ልባዊ ወዳጅ ስለመሆኑ ይነገር የነበረው ሐሜት በዌስት ሊን ክብደት እያገኘ መጥቶ ነበር
በሩቁ ግን የማምለክ ያህል ነበር የሚያከብራት " ግምቱ እውነት ቢሆንም ባይሆንም ሚስተስ
አርኪባልድ እያለ የሚጠራውን ያሁኑን ጌታውን ይወደው እንደነበር
ግን እርግጥ ነው አሁን ለንደን ሒዶ በሰነበተባቸው ቀኖች ውስጥ በቢሮ አካባቢ የተፈጸሙትን ነገሮች ሲያስረዳው ቆየና ወጣ"መጨረሻው ሲዶርስ «ጆንስና ራሽዎርዝ ተካረዋል " ሁለቱም በየራሳቸው እንድትቆምላቸው ፈልገውህ ትናንት መጥተው ነበር " ዛሬ የምትሰጣቸውን መልስ ለመስማት ይመጣሉ » አለው "
« ለአንዳቸውም አልቆምም " ከነሱ ጋር ምንም ግንኙነት እንዲኖረኝ አልፈልግም እነሱ መጥፎዎች ናቸው " ሀብታቸውም ሁሉ በግፍ የተለበሰበ ስለሆነ
ሰዎች አይደሉም ስለዚህ እኔ ፈቃደኛ አይደለሁምና ሌላ ሰው ይፈልጉ »
« በጣም ጥሩ እሺ» አለው ዲል
« ኰሎኔል ቤተል መጥተዋል
ጌታዬ » አለ አንዱ ጸሐፊ በሩን ከፈት አድርጎ ወዶ ሚስተር ካርላይል እያየ
«ሊያነጋግሯቸው ይችላሉ ? »
ሚስተር ዲል ወደ ተላከው ጸሐፊ ዞር ብሎ' «ኮሎኔሉን እንዲጠብቁ ንገራቸው» አለውና • ሰውየው መልሱን ሰምቶ ሲወጣ አይቶ ወደ ጌታው ምልስ ብሎ «እንግዲህ ይኸው ብቻ መሰለኝ » አለው
« ጥሩ ነው ስማ ዲል ... ሰሞኑን ስለ ኢስት ሊን የባለቤትነት ይዞታ
ስለ ወለድ አግድ ሁኔታ የሚያስረዱ ሰነዶች ከነሙሉ ማስረጃቸው ይቀርቡልሃል "
ለማንም ሳታሳይና ሳትናግር በደንብ አድርገህ እንድታያቸው እፈልጋለሁ ኢስትሊን ባለቤት ሊለወጥ ነው እንደ ሎርድ ማውንት እስቨርን ከመሰለ በችግር ከተወጠሩ ሰዎች ቦታ ሲገዙ በጣም መጠንቀቅ ያስፈልጋል ስለዚህ ማንም አንዳይሰማ ሆኖ ተጠንቅቀህ እንድትመረምረው በል አሁን ቤቴልን አስገባልኝ »
በሚስተር ካርላይልና በጸሐፊዎቹ ክፍሎች መካከል አንድ አራት ጎኑ እኩል የሆነና ወዶ ዋናው መተላለፌያ የሚያስገባ ሁለተኛ በር የነበረሙ አንድ ትንሽ መተላለፍያ ነበር » በዚያ መተላለፊ በኩል አንድ ጠባብ ክፍል ነበር » ክፍሉ ሚስተር ካርይል በማይኖርበት ወይም እንግዶችን ማያስችል ከባድ ጉዳይ ሲኖርበት ሚስተር ዲል እሱን ተክቶ የሚሸኝበት ልዩ ቢሮው ነበር " ይህ ክፍል የጸሐፊዎቹን ቢሮ የምታሳይ አንዲት ጠባብ መስኮት ነበረችው " ሚስቴር ዲል አንዳንድ ጊዜ በዚያች መስኮት አሹልኮ እየተመለከተ ስላሠቀቃቸው
፡
፡
#ክፍል_ስድስት
፡
፡
#ድርሰት_ሚሲስ_ሔንሪ_ውድ
ዌስትሊን መኻል ተጠጋግተው የተሠሩ ሁለት ቤቶች ይታያሉ " አንዱ ትልቅ ሌላው አነስ ያለ ሲሆን ትልቁ የካርላይል መኖሪያ ትንሹ ደግሞ ቤሮው ነው ካርላይል የሚለው ስም በዚያ አካባቢ በጣም የታወቀ ነው " ካርላይልና ዴቪድስን በአንደኛው ደረጃ የሚቀጠሩ ጠበቆች ነበሩ " ዱሮ ካርላይልና ዴቪድሰን በጋራ
ይዘውት የነበረ ድርጅት ዛሬ አርኪባልድ ካርላይል የብቻው አድርጐታል እነዚ የሥራ ሸሪኮች አምቻዎችም ነበሩ " የጀመሪያይቱ ሚሲዝ ካርላይል የሚስተር
ዴቪድሰን እኅት ነበረች እሷም ኮርኒሊያን ብቻ ከወለደችለት በኋላ ሞተች ኮርኒሊያ ትልቅ ልጅ ከሆነች በኋላ ሚስተር ካርላይል ሁለተኛ ሚስቱን አገባ " ሁላተኛይቱ ሚሲዝ ካርላይል ደግሞ የመጀመሪያ ልጅዋን አርኪባልድ ካርላይልን ወልዳለት ሞተችና እኀቱ ኮርነሊያ ተንከባክባ እንደ እናት ተጨንቃ እሷ በምትፈልገው ዐይነት መርታ አሳደገችው " ልጁም ሌላ እናት አያውቅም ነበርና እማማ ኮርኒ” ይላት ነበር እማማ ኮርኒ ለሱ ማድረግ የነበረባትን ሁሎ ፈጽማለታለች
ነገር ግን ዛሬም ትልቅ ከሆነ በኋላ ልክ እንደ ልጅነቱ በሷ እንዲመራ ትፈልጋለች
ከልማድ መላቀቅ በጣም ከባድ በመሆኑ አርኪባልድም ቢሆን ብዙውን ጊዜ እንዳለችው ይታዘዛታል » በአንዳንድ ነገሮች ደካማ አስተያት ይኑራት እንጂ ባጠቃላይ ግን ብርቱ ሴት ነበረች " ያለ የሌለ ሐሳቧ የአርኪባልድና የንዘብ ማስቀመጥ ፍቅር ብቻ ነበር " ሚስተር ዴቪድሰን ትዳር የሚባል ሳይሞክር ከሥራ ሸሪኩ ከሚስተር ካርላይል ቀደም ብሎ ሲሞት 'ሀብቱን ለኮርነሊያና ለአርኪባልድ እኩል አወረሳቸው " አርኪባልድን ባይዛመደውም በጥሩ ምግባሩ ይወደው ነበር ሚስተር ካርላይል ብዙ ሀብት ሊያከማች የቻለው ሁለተኛዋ ሚስቱ ባመጣችው ኻያ ሺህ ፖውንድ በመሆኑ ይሆናል ለሴት ልጁ ለኮርነሊያ ጥቂት ሰጥቶ አብዛኛውን አርኪባልድ አውርሶት የሞተው "
ሚስ ካርላይል ወይም በከተማው እንደምትጠራው ሚስ ኮርኒ ባል አላገባችም ሰዎች ለትንሽ ወንድሟ የነበራት ፍቅር ሳታገባ ብቸኛ ሆና እንድትቀር ያደረጋት ይመስላቸው ነበር ነገር ግን የባለጸጋው የሚስተር ካርላይል ልጅ ከነጭራሹ ባል የምትፈልግ አትመስልም ነበር " የፍቅር ነገር ይዘው የቀረቧትን ሁሉ አፋቸውን እያስያዘች መልሳቸዋለች የመጨረሻውን ሙከራ ያደረገው አንድ አዲስ የመጣ ቄስ ነበር " የዚያን ጊዜ ዐርባኛ ዐመቷን ይዛ ነበር አንድ ቀን ነጭ ክራባት አስሮ ወይን ጠጅ ቀለም የእጅ ሹራብ አጥልቆ አሸብርቆ ከጧቱ ቀዶም ብሎ ከቤቷ መጣ
ሚስ ኮሮኒ ከልክ ያለ የቤት አያያዝ ዐዋቂ ገረዶቿ ሊፈጽሙት ከሚፈልጉት የበለጠች ጠንቃቃ ነበረች " ለምሳ የሚዘጋጅ ሥጋ የሚጋገር ሊጥ እየመጠነች ስትሰጥና ስለ ዝግጅቱም እያስረዳች ሳለች የምግብ ቤቱ በር ተከፈተ ወዲያው ቄሱ ገባ " የዩልኝታን ነገር እርግፍ አድርጋ የተወችው ሚስ ካርላይል እንግዳ በመምጣቱ ልታጠብ ልለቃለቅ አላለችም- ሊጥ ስትከፋፍልበት የነበረ አንድ ሳህን እንድ ያዘች እንግዳው ዐረፍ ከሚልበት ምግብ ቤት ገባች "
በዐሥራ ሁለት ዓመት በዕድሜ የምትበልጠው መንፈሳዊ ሰው የሚላትን እስክትሰማ ሰሐኑን ጉኗ በነበረው ጠረጴዛ ላይ አሳረፈችው ኮርነሊያ የያዘችውን ሥራ እንዳደበላሽባት ሰውየው ሳይንተባተብባትና ሳይዘበዝብ ቶሎ እንዲወጣላት መፈለጓን
በተዘዋዋሪ መንገድ ስትጠቁመው አልገባው ሲል ቀጥውን በመንገር አጣደፈሻው » እሱ ለአንድ በጎ አድራጐት ድርጅት በረጂ አባልነት እንድትመዘገብ ሊጠይቃት መሰላት » ከሷ በሁለት ስንዝር ያህል አጠር ይል ስለነበር እሁንም ነገር አልቆርጥ በማለቱ ትግሥቷን ጨርሳ ቁልቁል ትመለከተው ጀመር" በመጨረሻ እሷን እንጂ ገንዘቧን ፈልጎ እንዳልመጣ ነገሩን ገልጾ ሲነግራት እሳት ሆነችበት " እሱን የመሰለ ውርጋጥ እሷን ለዚህ ነገር ደፍሮ ሲያስባት ኣለማፈሩን እየነገረች የቁጣ
መዓቷን አወረዶችበትና ያን ከጠረጴዛው ላይ በሰሐን አኑራው የነበረውን ሊጥ ብድግ አድርጋ በረዶ ከመሰለው ነጭ ሸሚዙ ላይ ለደፈችበት » ኃፍረትና ድንጋጤ ኩምሽሽ ያደረገው ካህን እንዴት አድርጎ ከቤት ወጥቶ በዌስት ሊን ቁልቁል ወርዶ ቤቱ እንዶ ደረሰ ለማስታወስ እንኳን አይፈልግም ነበር " ወሬው ግን ባንድ ጊዜ ዳር እስከ ዳር ተዳረሰና ከዚያ ወዲህ ሚስ ኮርኒን ለጋብቻ በመጠየቅ ረገድ ማንም ስው አስቸግሯት አያውቅም "
ሚስተር ካርላይል ከለንደን በተመለሰ ማግሥት ጧቱን ከቢሮው ገብቶ ተቀምጧል " አብዛኛውን ጊዜ ሥራውን የሚያካሒድለት ታማኝ ጸሐፊውና ሥራ አስኪያጁ የሆነው ሚስተር ዲል ከአጠገቡ ቆሟል " ሚስተር ዲል ዐይን አፋር ቢጤ አጭር ' ቀጭንና ራስ መላጣ ነበር " ድሮ በትልቁ ካርላይልና በዴቪድስን ጊዜ ቀጥሮ ገባ ጀምሮ ችሎታውና የሥራ ልምዱ ሳያንሰው ራሱን ችሎ ከመሥራት ይልቅ ሥራ አስኪያጅ እየተባለ በሰው ሥር ሆኖ ደኅና ደመወዝ እያገኘ መኖሩ ምኞቱን ያረካለት ይመስላል " ለመለየት አሳብ አልነበረውም » በዚያው አካባቢ በአንድ
ጥሩ ቤት ሲኖር እሱም እንደ ኮርነሊያ አላገባም ነበር " የሚስ ካርላይል ልባዊ ወዳጅ ስለመሆኑ ይነገር የነበረው ሐሜት በዌስት ሊን ክብደት እያገኘ መጥቶ ነበር
በሩቁ ግን የማምለክ ያህል ነበር የሚያከብራት " ግምቱ እውነት ቢሆንም ባይሆንም ሚስተስ
አርኪባልድ እያለ የሚጠራውን ያሁኑን ጌታውን ይወደው እንደነበር
ግን እርግጥ ነው አሁን ለንደን ሒዶ በሰነበተባቸው ቀኖች ውስጥ በቢሮ አካባቢ የተፈጸሙትን ነገሮች ሲያስረዳው ቆየና ወጣ"መጨረሻው ሲዶርስ «ጆንስና ራሽዎርዝ ተካረዋል " ሁለቱም በየራሳቸው እንድትቆምላቸው ፈልገውህ ትናንት መጥተው ነበር " ዛሬ የምትሰጣቸውን መልስ ለመስማት ይመጣሉ » አለው "
« ለአንዳቸውም አልቆምም " ከነሱ ጋር ምንም ግንኙነት እንዲኖረኝ አልፈልግም እነሱ መጥፎዎች ናቸው " ሀብታቸውም ሁሉ በግፍ የተለበሰበ ስለሆነ
ሰዎች አይደሉም ስለዚህ እኔ ፈቃደኛ አይደለሁምና ሌላ ሰው ይፈልጉ »
« በጣም ጥሩ እሺ» አለው ዲል
« ኰሎኔል ቤተል መጥተዋል
ጌታዬ » አለ አንዱ ጸሐፊ በሩን ከፈት አድርጎ ወዶ ሚስተር ካርላይል እያየ
«ሊያነጋግሯቸው ይችላሉ ? »
ሚስተር ዲል ወደ ተላከው ጸሐፊ ዞር ብሎ' «ኮሎኔሉን እንዲጠብቁ ንገራቸው» አለውና • ሰውየው መልሱን ሰምቶ ሲወጣ አይቶ ወደ ጌታው ምልስ ብሎ «እንግዲህ ይኸው ብቻ መሰለኝ » አለው
« ጥሩ ነው ስማ ዲል ... ሰሞኑን ስለ ኢስት ሊን የባለቤትነት ይዞታ
ስለ ወለድ አግድ ሁኔታ የሚያስረዱ ሰነዶች ከነሙሉ ማስረጃቸው ይቀርቡልሃል "
ለማንም ሳታሳይና ሳትናግር በደንብ አድርገህ እንድታያቸው እፈልጋለሁ ኢስትሊን ባለቤት ሊለወጥ ነው እንደ ሎርድ ማውንት እስቨርን ከመሰለ በችግር ከተወጠሩ ሰዎች ቦታ ሲገዙ በጣም መጠንቀቅ ያስፈልጋል ስለዚህ ማንም አንዳይሰማ ሆኖ ተጠንቅቀህ እንድትመረምረው በል አሁን ቤቴልን አስገባልኝ »
በሚስተር ካርላይልና በጸሐፊዎቹ ክፍሎች መካከል አንድ አራት ጎኑ እኩል የሆነና ወዶ ዋናው መተላለፌያ የሚያስገባ ሁለተኛ በር የነበረሙ አንድ ትንሽ መተላለፍያ ነበር » በዚያ መተላለፊ በኩል አንድ ጠባብ ክፍል ነበር » ክፍሉ ሚስተር ካርይል በማይኖርበት ወይም እንግዶችን ማያስችል ከባድ ጉዳይ ሲኖርበት ሚስተር ዲል እሱን ተክቶ የሚሸኝበት ልዩ ቢሮው ነበር " ይህ ክፍል የጸሐፊዎቹን ቢሮ የምታሳይ አንዲት ጠባብ መስኮት ነበረችው " ሚስቴር ዲል አንዳንድ ጊዜ በዚያች መስኮት አሹልኮ እየተመለከተ ስላሠቀቃቸው
👍21
#የጣሪያ_ስር_አበቦች
፡
፡
#ክፍል_ስድስት
፡
፡
#ትርጉም_ሀኒም_ኤልያስ
...የሰጠቸው አስተያየት ልባችንን ሊያሞቅ የሚገባው ቢሆንም የእኔን ልብ ግን ድምጽዋ ቀዝቃዛና ግድ የለሽ ነበር፡ በእሷ የውሸት አስተያየት በቀላሉ የምንታለልና አለመደሰቷን የሚረዳ አእምሮ የሌለን አድርጋ ቆጥራናለች ማለት ነው! ብዬ እያሰብኩ ሳለ ቀጥሎ የተናገረቻቸው ቃላት
የሀሳቤን ትክክለኛነት አረጋገጡልኝ፡....
“ጭንቅላታቸው እንደሚሰራ እርግጠኛ ነሽ? ሌላ በአይን የማይታይ የሆነ ጉድለት የለባቸውም?” እናቴ ልክ እንደ እኔ ንዴቷን ውጣ “ምንም እንከን
የለባቸውም እንደምታይው ልጆቼ በአካልም ሆነ በአእምሮ ፍፁም
ጤነኛ ናቸው” አለች ከዚያ ያችን ግራጫ የለበሰች አሮጊት አተኩራ ተመለከተቻትና ከመራመድ ብዛት እግሯ ያበጠባትን የኬሪን ልብስ ልትቀይር ዞራ ተረከዟ ላይ ቁጢጥ አለች እኔም ኮሪ ፊት ለፊት በርከክ ብዬ የጃኬቱን ቁልፍ መፍታት
ጀመርኩ። ክሪስቶፈር ደግሞ አንደኛውን ሻንጣ ከፈተና ሁለት ትናንሽ ቢጫ የሌሊት ልብሶች አወጣ።
ኬሪ የሌሊት ልብሱን እንዲቀይር እያገዝኩት አሮጊቷን አየት አደረግኳት ከሁኔታው ይህች ረጅምና ግዙፍ ሴት አያታችን እንደሆነች ገመትኩ
አሻግሬ እየተመለከትኳት ፊቷ ላይ የተጨማደደ ቆዳ ለማየት ብፈልግም መጀመሪያ የገመትኩትን ያህል አሮጊት እንዳልሆነች አወቅኩ። ፀጉሯ ደስ
በማይል አይነት ከፊቷ ወደ ኋላ በመሰብሰቡ አይኖቿን የፈጠጡና የድመት አስመስሏቸዋል። እያንዳንዱ የፀጉሯ ዘለላ እንዴት ቆዳዋን እንደጎተተው ማየት ይቻላል።
አፍንጫዋ የአሞራ መንቆር ይመስላል፤ ትከሻዋ ሰፊ ሲሆን ከንፈሯ ስስ ሆኖ አፏ በቢላ የተሰነጠቀ ጭረት መሰል ነበር። ቀሚሷ ግራጫ ሆኖ ጠበብ
ካለው አንገትጌው ላይ የአልማዝ ጌጥ አለበት፡ አንዱም ነገሯ ለስላሳና ማራኪ አይደለም፡ ጡቶቿ ሳይቀሩ መንታ ኮረብታዎች የሚመስሉ ናቸው:
ከእናታችንና ከአባታችን ጋር እንደምንጫወተው ከእሷ ጋር ቀልድ የማይታሰብ ነው።
አልወደድኳትም። ከንፈሮቼ ተንቀጠቀጡ። ቤቴ መሄድ ፈለግኩ። እንደገና አባቴ በህይወት እንዲኖር ፈለግኩ፡ እንደዚች አይነት ሴት እንዴት እንደ
እናታችን አይነት ተወዳጅና ጣፋጭ ሴት ልትወልድ ቻለች? እናቴ ቁንጅናዋንና ለዛዋን ከማን ወርሳ ነው? እየተንቀጠቀጥኩ በአይኖቼ የሞሉት እምባዎቼ እንዳይወርዱ ሞከርኩ። እናታችን ወንድ አያታችን ለሰው ፍቅር
የሌለው፣ ግድ የለሽና ተቆጪ እንደሆነ አስቀድማ በመንገር አዘጋጅታን ነበር።ነገር ግን መምጣታችንን ያመቻቸችው ሴት አያታችንም መጥፎ የመሆኗ
ነገር አስገራሚ ነበር፡
ደንግጦ የነበረው ክሪስቶፈር አይቶኝ በኋላ እንዳይቀልድብኝ አይኖቼን በማርገብገብ እምባዎቼን መለስኳቸው: እናታችን ግን ሁሉ መልካም የሚሆን
ለመሆኑ ማረጋገጫ እንዲሆነን ኮሪን ትልቁ አልጋ ላይ ስታስተኛው በደስታ ፈገግ ብላ ነበር ከዚያ ኬሪንም ከእሱ አጠገብ አስተኛች እዚያ አልጋ ላይ ሮዝ ጉንጭ ያላቸው ትልቅ አሻንጉሊቶች መስለው ተኝተው ሲታዩ እንዴት
እንደሚያምሩ። እናታችን የመንትዮቹን ጎንጮች ሳመችና በእጆቿ ግንባራቸው ላይ የተኛውን ፀጉራቸውን በእጇ ወደ ኋላ መለሰችላቸው: ከዚያ የአልጋ
ልብሱን ወደ አገጫቸው ከፍ አድርጋ ሁላችንም በምናውቀው ጣፋጭ ድምፅዋ
“ደህና እደሩ የኔ ውዶች" ስትል አንሾካሾከች መንትዮቹ አልሰሟትም፡ ገና ድሮ እንቅልፍ ወስዷቸው ነበር።
እንደተተከለ ዛፍ ቀጥ ብላ ቆማ መንትዮቹ ሲተኙ እንዲሁም እኔና ክሪስቶፈር ተጠጋግተን ስንቀመጥ እያየች የነበረችው አያታችን ደስ እንዳላት በግልፅ ያስታውቃል በጣም ስለደከመን ተደጋግፈን ተቀምጠናል። እንደ ድንጋይ
ከጠነከሩት አይኖቿ ውስጥ የሚነበበው ነገር ደስ አይልም ያልተስማማት አንድ ነገር እንዳለ ከአስተያየቷ መረዳት ይቻላል፡ ፊቷን አጨፍግጋ ዘልቆ
የሚገባ በሚመስል አስተያየት እያየችን የመሆኑ ነገር ለእናቴ የሰጣት የሆነ መልእክት ያለ ይመስላል፡ ወዲያው “ሁለቱ ያደጉት ልጆችሽ አንድ አልጋ ላይ
መተኛት አይችሉም” ስትላት እናቴ ፊቷ በንዴት ደም መሰለ።
እናታችን ባልተለመደ ኃይለኝነት “ገና ልጆች እኮ ናቸው። እማዬ ትንሽ እንኳን አልተቀየርሽም አይደል? አሁንም አስቀያሚ ተጠራጣሪ አእምሮ ነው
ያለሽ፡ ክሪስቶፈርና ካቲ ምንም አያውቁም” አለች።
“ምንም አያውቁም!?” በቁጣ መለሰች፡ የክፋት አስተያየቷ ደም የሚያፈስ ስለት ይመስል ነበር። “እኔና አባትሽም ስለአንቺና ስለ አጎትሽ ሁልጊዜም የምናስበው እንደዚያ ነበር።”
አይኖቼ በሰፊው ተከፍተው ከአንደኛቸው ወደ ሌላኛቸው ተንከራተቱ፡ ወደ ወንድሜ ሳማትር ከእድሜው ላይ አመታት የተቀነሱ ይመስል ልክ እንደ ስድስትና ሰባት አመት ህፃን ረዳት አልባ መስሏል። ከእኔ የበለጠ እንዳልገባው ያስታውቃል።
የሚፋጅ ቁጣ የእናታችንን ቀለም ለዋወጠው “እንደዚያ ካሰብሽ የተለያየ ክፍልና የተለያየ አልጋ ስጫቸዋ! እዚህ ቤት ውስጥ በቂ ክፍል እንዳለ የታወቀ ነው”
“ያ የማይቻል ነው! አጠገቡ መታጠቢያ ያለውና ወዲያ ወዲህ ሲሉ ወይም የሽንት ቤት ውሀ ሲለቁ ባለቤቴ የማይሰማበት ብቸኛ ክፍል ይሄ ብቻ ነው፡ የተለያየ ክፍል ውስጥ ከሆኑ ወዲያ ወዲህ ሲሉ ድምፃቸው ወይም ጩኸታቸውን ይሰማል ሰራተኞቹም ሊሰሙ ይችላሉ። ይህንን ክፍል ያመቻቸሁት ብዙ ካሰብኩበት በኋላ ነው ደህንነቱ የተጠበቀ ብቸኛው ክፍል
ይህ ብቻ ነው:" አለች አያታችን እንደ በረዶ በቀዘቀዘ ድምፅዋ።
“ደህንነቱ የተጠበቀ?” ሀያ፣ ሰላሳ፣ አርባ ክፍሎች ባሉበት ትልቅ ቤት ውስጥ ሁላችንም በአንድ ክፍል ውስጥ ታጭቀን እያደርን? በአንድ ክፍል ውስጥ እየኖርን? ቢሆንም ግን አሁን ሳስበው በዚህ ግዙፍ ቤት ብቻዬን አንድ ክፍል
ውስጥ መሆን አልፈልግም
“ሁለቱን ሴቶች አንዱ አልጋ ላይ፣ ሁለቱን ወንዶች ደግሞ ሌላኛው አልጋ ላይ አስተኚ” ስትል አዘዘች
እናታችን ኮሪን አንስታ ሌላኛው አልጋ ላይ አስተኛችው ከያ በኋላ ቀስ በቀስ ሁሉም ነገር አያትየው እንዲሆን እንደምትፈልገው ሆነ። ወንዶቹ ለመታጠቢያ ቤቱ ቅርብ የሆነው አልጋ ላይ፣ እኔና ኬሪ ደግሞ መስኮቱ አጠገብ ያለው አልጋ ላይ ሆንን።
አሮጊቷ እይታዋን መጀመሪያ ወደ እኔ ከዚያ ደግሞ ወደ ክሪስቶፈር አደረገች ከዚያ ልክ እንደ አዛዥ ወታደር መናገር ጀመረች። “ስሙ! ትንንሾቹን ልጆች ፀጥ እንዲሉ ማድረግን የእናንተን የትልልቆቹ ሀላፊነት ይሆናል፤ ከማወጣቸው
ህሃጎች አንዱንም እንዳትጥሱ የምለውን በጥንቃቄ በአእምሯችሁ ያዙ።
ክፍሉንና መታጠቢያ ቤቱን ልክ ሰው የማይኖርበት በሚመስል አይነት በንፅህና መያዝ ይጠበቅባችኋል። ፀጥ ማለት ግዴታ ነው! መጮህ፣ ማልቀስ ወይም መሮጥ አይቻልም ከዚህ ክፍል ወጥታችሁ መሄድ ስለማይፈቀድና በምንም
ምክንያት ወደ ቤቱ ሌላኛው አካባቢ እንድትሄዱም ስለማልፈልግ እናታችሁና
እኔ አሁን ከዚህ ስንወጣ በሩን ከውጪ እቀረቅረዋለሁ። ወንድ አያታችሁ እዚህ መኖራችሁን ካወቀ በህይወት በመኖራችሁ ብቻ በአስከፊ ሁኔታ ከቀጣችሁ በኋላ አንዲት ሳንቲም ሳይሰጣችሁ አስወጥቶ ይወረውራችኋል!
ስለዚህ እሱ እስከሚሞት ድረስ እዚህ ትቆያላችሁ: ግን እዚህ እንደሌላችሁ ትቆጠራላችሁ”
፡
፡
#ክፍል_ስድስት
፡
፡
#ትርጉም_ሀኒም_ኤልያስ
...የሰጠቸው አስተያየት ልባችንን ሊያሞቅ የሚገባው ቢሆንም የእኔን ልብ ግን ድምጽዋ ቀዝቃዛና ግድ የለሽ ነበር፡ በእሷ የውሸት አስተያየት በቀላሉ የምንታለልና አለመደሰቷን የሚረዳ አእምሮ የሌለን አድርጋ ቆጥራናለች ማለት ነው! ብዬ እያሰብኩ ሳለ ቀጥሎ የተናገረቻቸው ቃላት
የሀሳቤን ትክክለኛነት አረጋገጡልኝ፡....
“ጭንቅላታቸው እንደሚሰራ እርግጠኛ ነሽ? ሌላ በአይን የማይታይ የሆነ ጉድለት የለባቸውም?” እናቴ ልክ እንደ እኔ ንዴቷን ውጣ “ምንም እንከን
የለባቸውም እንደምታይው ልጆቼ በአካልም ሆነ በአእምሮ ፍፁም
ጤነኛ ናቸው” አለች ከዚያ ያችን ግራጫ የለበሰች አሮጊት አተኩራ ተመለከተቻትና ከመራመድ ብዛት እግሯ ያበጠባትን የኬሪን ልብስ ልትቀይር ዞራ ተረከዟ ላይ ቁጢጥ አለች እኔም ኮሪ ፊት ለፊት በርከክ ብዬ የጃኬቱን ቁልፍ መፍታት
ጀመርኩ። ክሪስቶፈር ደግሞ አንደኛውን ሻንጣ ከፈተና ሁለት ትናንሽ ቢጫ የሌሊት ልብሶች አወጣ።
ኬሪ የሌሊት ልብሱን እንዲቀይር እያገዝኩት አሮጊቷን አየት አደረግኳት ከሁኔታው ይህች ረጅምና ግዙፍ ሴት አያታችን እንደሆነች ገመትኩ
አሻግሬ እየተመለከትኳት ፊቷ ላይ የተጨማደደ ቆዳ ለማየት ብፈልግም መጀመሪያ የገመትኩትን ያህል አሮጊት እንዳልሆነች አወቅኩ። ፀጉሯ ደስ
በማይል አይነት ከፊቷ ወደ ኋላ በመሰብሰቡ አይኖቿን የፈጠጡና የድመት አስመስሏቸዋል። እያንዳንዱ የፀጉሯ ዘለላ እንዴት ቆዳዋን እንደጎተተው ማየት ይቻላል።
አፍንጫዋ የአሞራ መንቆር ይመስላል፤ ትከሻዋ ሰፊ ሲሆን ከንፈሯ ስስ ሆኖ አፏ በቢላ የተሰነጠቀ ጭረት መሰል ነበር። ቀሚሷ ግራጫ ሆኖ ጠበብ
ካለው አንገትጌው ላይ የአልማዝ ጌጥ አለበት፡ አንዱም ነገሯ ለስላሳና ማራኪ አይደለም፡ ጡቶቿ ሳይቀሩ መንታ ኮረብታዎች የሚመስሉ ናቸው:
ከእናታችንና ከአባታችን ጋር እንደምንጫወተው ከእሷ ጋር ቀልድ የማይታሰብ ነው።
አልወደድኳትም። ከንፈሮቼ ተንቀጠቀጡ። ቤቴ መሄድ ፈለግኩ። እንደገና አባቴ በህይወት እንዲኖር ፈለግኩ፡ እንደዚች አይነት ሴት እንዴት እንደ
እናታችን አይነት ተወዳጅና ጣፋጭ ሴት ልትወልድ ቻለች? እናቴ ቁንጅናዋንና ለዛዋን ከማን ወርሳ ነው? እየተንቀጠቀጥኩ በአይኖቼ የሞሉት እምባዎቼ እንዳይወርዱ ሞከርኩ። እናታችን ወንድ አያታችን ለሰው ፍቅር
የሌለው፣ ግድ የለሽና ተቆጪ እንደሆነ አስቀድማ በመንገር አዘጋጅታን ነበር።ነገር ግን መምጣታችንን ያመቻቸችው ሴት አያታችንም መጥፎ የመሆኗ
ነገር አስገራሚ ነበር፡
ደንግጦ የነበረው ክሪስቶፈር አይቶኝ በኋላ እንዳይቀልድብኝ አይኖቼን በማርገብገብ እምባዎቼን መለስኳቸው: እናታችን ግን ሁሉ መልካም የሚሆን
ለመሆኑ ማረጋገጫ እንዲሆነን ኮሪን ትልቁ አልጋ ላይ ስታስተኛው በደስታ ፈገግ ብላ ነበር ከዚያ ኬሪንም ከእሱ አጠገብ አስተኛች እዚያ አልጋ ላይ ሮዝ ጉንጭ ያላቸው ትልቅ አሻንጉሊቶች መስለው ተኝተው ሲታዩ እንዴት
እንደሚያምሩ። እናታችን የመንትዮቹን ጎንጮች ሳመችና በእጆቿ ግንባራቸው ላይ የተኛውን ፀጉራቸውን በእጇ ወደ ኋላ መለሰችላቸው: ከዚያ የአልጋ
ልብሱን ወደ አገጫቸው ከፍ አድርጋ ሁላችንም በምናውቀው ጣፋጭ ድምፅዋ
“ደህና እደሩ የኔ ውዶች" ስትል አንሾካሾከች መንትዮቹ አልሰሟትም፡ ገና ድሮ እንቅልፍ ወስዷቸው ነበር።
እንደተተከለ ዛፍ ቀጥ ብላ ቆማ መንትዮቹ ሲተኙ እንዲሁም እኔና ክሪስቶፈር ተጠጋግተን ስንቀመጥ እያየች የነበረችው አያታችን ደስ እንዳላት በግልፅ ያስታውቃል በጣም ስለደከመን ተደጋግፈን ተቀምጠናል። እንደ ድንጋይ
ከጠነከሩት አይኖቿ ውስጥ የሚነበበው ነገር ደስ አይልም ያልተስማማት አንድ ነገር እንዳለ ከአስተያየቷ መረዳት ይቻላል፡ ፊቷን አጨፍግጋ ዘልቆ
የሚገባ በሚመስል አስተያየት እያየችን የመሆኑ ነገር ለእናቴ የሰጣት የሆነ መልእክት ያለ ይመስላል፡ ወዲያው “ሁለቱ ያደጉት ልጆችሽ አንድ አልጋ ላይ
መተኛት አይችሉም” ስትላት እናቴ ፊቷ በንዴት ደም መሰለ።
እናታችን ባልተለመደ ኃይለኝነት “ገና ልጆች እኮ ናቸው። እማዬ ትንሽ እንኳን አልተቀየርሽም አይደል? አሁንም አስቀያሚ ተጠራጣሪ አእምሮ ነው
ያለሽ፡ ክሪስቶፈርና ካቲ ምንም አያውቁም” አለች።
“ምንም አያውቁም!?” በቁጣ መለሰች፡ የክፋት አስተያየቷ ደም የሚያፈስ ስለት ይመስል ነበር። “እኔና አባትሽም ስለአንቺና ስለ አጎትሽ ሁልጊዜም የምናስበው እንደዚያ ነበር።”
አይኖቼ በሰፊው ተከፍተው ከአንደኛቸው ወደ ሌላኛቸው ተንከራተቱ፡ ወደ ወንድሜ ሳማትር ከእድሜው ላይ አመታት የተቀነሱ ይመስል ልክ እንደ ስድስትና ሰባት አመት ህፃን ረዳት አልባ መስሏል። ከእኔ የበለጠ እንዳልገባው ያስታውቃል።
የሚፋጅ ቁጣ የእናታችንን ቀለም ለዋወጠው “እንደዚያ ካሰብሽ የተለያየ ክፍልና የተለያየ አልጋ ስጫቸዋ! እዚህ ቤት ውስጥ በቂ ክፍል እንዳለ የታወቀ ነው”
“ያ የማይቻል ነው! አጠገቡ መታጠቢያ ያለውና ወዲያ ወዲህ ሲሉ ወይም የሽንት ቤት ውሀ ሲለቁ ባለቤቴ የማይሰማበት ብቸኛ ክፍል ይሄ ብቻ ነው፡ የተለያየ ክፍል ውስጥ ከሆኑ ወዲያ ወዲህ ሲሉ ድምፃቸው ወይም ጩኸታቸውን ይሰማል ሰራተኞቹም ሊሰሙ ይችላሉ። ይህንን ክፍል ያመቻቸሁት ብዙ ካሰብኩበት በኋላ ነው ደህንነቱ የተጠበቀ ብቸኛው ክፍል
ይህ ብቻ ነው:" አለች አያታችን እንደ በረዶ በቀዘቀዘ ድምፅዋ።
“ደህንነቱ የተጠበቀ?” ሀያ፣ ሰላሳ፣ አርባ ክፍሎች ባሉበት ትልቅ ቤት ውስጥ ሁላችንም በአንድ ክፍል ውስጥ ታጭቀን እያደርን? በአንድ ክፍል ውስጥ እየኖርን? ቢሆንም ግን አሁን ሳስበው በዚህ ግዙፍ ቤት ብቻዬን አንድ ክፍል
ውስጥ መሆን አልፈልግም
“ሁለቱን ሴቶች አንዱ አልጋ ላይ፣ ሁለቱን ወንዶች ደግሞ ሌላኛው አልጋ ላይ አስተኚ” ስትል አዘዘች
እናታችን ኮሪን አንስታ ሌላኛው አልጋ ላይ አስተኛችው ከያ በኋላ ቀስ በቀስ ሁሉም ነገር አያትየው እንዲሆን እንደምትፈልገው ሆነ። ወንዶቹ ለመታጠቢያ ቤቱ ቅርብ የሆነው አልጋ ላይ፣ እኔና ኬሪ ደግሞ መስኮቱ አጠገብ ያለው አልጋ ላይ ሆንን።
አሮጊቷ እይታዋን መጀመሪያ ወደ እኔ ከዚያ ደግሞ ወደ ክሪስቶፈር አደረገች ከዚያ ልክ እንደ አዛዥ ወታደር መናገር ጀመረች። “ስሙ! ትንንሾቹን ልጆች ፀጥ እንዲሉ ማድረግን የእናንተን የትልልቆቹ ሀላፊነት ይሆናል፤ ከማወጣቸው
ህሃጎች አንዱንም እንዳትጥሱ የምለውን በጥንቃቄ በአእምሯችሁ ያዙ።
ክፍሉንና መታጠቢያ ቤቱን ልክ ሰው የማይኖርበት በሚመስል አይነት በንፅህና መያዝ ይጠበቅባችኋል። ፀጥ ማለት ግዴታ ነው! መጮህ፣ ማልቀስ ወይም መሮጥ አይቻልም ከዚህ ክፍል ወጥታችሁ መሄድ ስለማይፈቀድና በምንም
ምክንያት ወደ ቤቱ ሌላኛው አካባቢ እንድትሄዱም ስለማልፈልግ እናታችሁና
እኔ አሁን ከዚህ ስንወጣ በሩን ከውጪ እቀረቅረዋለሁ። ወንድ አያታችሁ እዚህ መኖራችሁን ካወቀ በህይወት በመኖራችሁ ብቻ በአስከፊ ሁኔታ ከቀጣችሁ በኋላ አንዲት ሳንቲም ሳይሰጣችሁ አስወጥቶ ይወረውራችኋል!
ስለዚህ እሱ እስከሚሞት ድረስ እዚህ ትቆያላችሁ: ግን እዚህ እንደሌላችሁ ትቆጠራላችሁ”
👍32❤4
#ጠላፊዎቹ
፡
፡
#ክፍል_ስድስት
፡
፡
#በኬንፎሌት
፡
፡
#ትርጉም_ወንዳየሁ_ንጉሴ
...‹የሚያስቸኩልሽ ነገር የለም›› አለ ኮንስታብሉ ‹‹አባትሽ ሊወስዱሽ
እየመጡ ነው፡፡››
የማርጋሬት ልብ በድንጋጤ ቀጥ አለ፡ እንዴት ሊሆን ይችላል? አሁን
ያለችበት ቦታ አባቷ የማያውቁት ስለሆነ ደህነኛ ቦታ ነው ብላ ተማምና ነበር፡፡
አባቷን ዝቅ አድርጋ ነበር የገመተቻቸው፡ በዚህ ደቂቃ ውስጥ ሊይዟት ይመጣሉ! ሃሳቡ አንቀጠቀጣት ‹‹የት እንዳለሁ እንዴት አወቀ አባባ?›› አለች፡፡
ወጣቱ ፖሊስ በኩራት ‹‹ትናንት ማታ ስለመጥፋትሽ የቴሌግራም መልዕክት ደርሶን ነበር፡፡ ስመጣ አየሁት፡፡ በጨለማ የመጣሽ ጊዜ
አላወቅኩሽም ነበር፡፡ ስምሽን ግን አስታወስኩት፡፡ ከተገኘሽ ለጌታ ኦክሰንፎርድ
እንዲነገራቸው ቴሌግራሙ ያዛል፡፡ እዚህ እንዳመጣሁሽ ለአባትሽ ደወልኩ››
ማርጋሬት ብድግ አለች፧ ልቧ በጣም ይመታል፡፡ ‹‹እሱን አልጠብቅም
አሁን ነግቷል›› አለች፡፡
ፖሊሱ ስጋት ገባው ‹‹ትንሽ ቆይ›› አለ፡፡ ዞር አለና ‹‹ሃምሳ አለቃ እመቤት ማርጋሬት መሄዴ ነው እያለች ነው›› ብሎ ነገረው፡፡
ሄሪ ማርክስ ‹‹እዚህ ይዘው ሊያቆዩሽ አይችሉም ባንቺ እድሜ ከቤት ጠፍቶ መሄድ ወንጀል ተደርጎ አይቆጠርም፡፡ መሄድ ከፈለግሽ ቀጥ ብለሽ
ሂጂ›› አላት፡፡
ሃምሳ አለቃውም ‹‹ነገር ግን ጫማ የለሽም፤ ስቶኪንግሽ ተቀዳዷል፡፡ አባትሽ ጋ ልደውልልሽ›› አላት፡፡
ማሰብ ጀመረች፡፡ ጣቢያ እንደደረሰች ነው ለአባቷ ስልክ የተደወለው፡፡
አሁን አንድ ሰዓት አልሞላውም ማለት ነው፡፡ አባቷ ደግሞ ከዚህ በኋላ
እዚህ ለመድረስ ቢያንስ ከአንድ ሰዓት በላይ ይፈጅባቸዋል፡ ‹‹ደህና›› አለች ለደጉ ፖሊስ ‹‹አመሰግናለሁ፡፡››
ሄሪ ወደ ፖሊስ ስታዘግም አየና ‹‹ጅል›› አላት፡፡
ፖሊሱ አንድ ትንሽ ክፍል ውስጥ ወስዶ አስገባት፡፡ ወንበሮቹ ተራ ናቸው፡
አንድ አግዳሚ ወንበር ይታያታል፡፡ ከላይ ማቀፊያ የሌለው አምፑል ተንጠልጥሏል፡ መስኮቱ በብረት ፍርግርግ ተዘግቷል፡ ሃምሳ አለቃው ይህ
ክፍል ከባለጉዳይ መቀበያው ክፍል የተሻለ ነው ብሎ እንዴት እንዳሰበ
አልገባሽ አላት፡፡ ልትነግረው ዞር ስትል በሩን ፊቷ ላይ ጠረቀመው፡፡ አንድ
ክፉ ነገር እንዳለ በልቧ ጠረጠረችና ፍርሃት ገባት፡፡ ተወርውራ በሩ ጋ ሄዳ
ለመክፈት ታገለች ከዚያም ፍርሃቷም እውነት መሆኑን በሩ ሲቆለፍ አረጋገጠች፡፡ የበሩን እጄታ በሃይል ነቀነቀችው፤ ነገር ግን በሩ የሚከፈት አልሆነም በተስፋ መቁረጥ በሩ ላይ ልጥፍ አለች፡፡
ከውጭ በኩል ሳቅ ይሰማታል፤ ከዚያም ሃሪ ‹‹እናንተ እርጉሞች›› ሲል
ተሰማት ‹‹አፍክን ዝጋ›› አለው ፖሊሱ፡፡
‹ምንም መብት የላችሁም ልጅቷን ለማቆየት፤ አንተም ታውቃለህ አለው።
‹‹አባቷ የተከበሩ ሰው ስለሆኑ ነው እንደዚህ ያደረኩት›› አለ፡
ማርጋሬት ያሰበችው ባለመሳካቱ በምሬት ተንገበገበች፡ የማምለጥ
እቅዷ ውሃ በልቶታል። ይረዱኛል ብላ የገመተቻቸው ሰዎች አታለዋታል ለትንሽ ጊዜ ነፃ
ነበረች አሁን ግን ነፃነቷ አብቅቷላተል ምድር ጦር
መምሪያው መሄድ አለመቻሏ አንገበገባት
ከጦርነቱ ለመሸሽ የፓን አሜሪካ ንብረት በሆነችው አይሮፕላን ተሳፍራ ኒውዮርክ ልትሄድ ነበር። ይህን ያህል ደክማም እድሏ አልሰምር አላት፡፡
ከብዙ ቆይታ በኋላ ከበሩ ወደ መስኮቱ ሄደች። በመስኮት አጮልቃ
ስታይ ምንም ነገር የማይታይበት ጓሮና የሸክላ ግድግዳ ብቻ ነው::
በሽንፈትና በአቅመቢስነት መስኮቱ ጋር ተገትራ የአባቷን መምጣት
ከመጠባበቅ በስተቀር ምንም ምርጫ አልነበራትም።
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
ኤዲ ዲኪን ለአይሮፕላኑ የመጨረሻ ፍተሻ አደረገ እያንዳንዳቸው የ1500 የፈረስ ጉልበት ያላቸው አራቱ ሞተሮች የተቀቡት ዘይት ያብለጨልጫል፡ እያንዳንዱ ሞተር የሰው ቁመት አለው። ኤዲ እያንዳንዱን የሞተር ክፍል መርምሮ ሲጨርስ ዘጋጋና ከመሰላሉ ላይ ወረደ። አይሮፕላኑ ለበረራ ሲዘጋጅ ቱታውን ያወልቅና ሰውነቱን ታጥቦ የአየር መንገዱን የበረራ ዩኒፎርም ይለብሳል።
ከአይሮፕላን ማረፊያ ወደቡ ወጥቶ ሲሄድ ፀሀይ ገና አልጠለቀችም፡ከዚያም የስራ ባልደረቦቹ ወደሚገኙበት ሆቴል አመራ: በአይሮፕላኑና
በሚሰራው ስራ ይኮራል። አትላንቲክ አቋራጭ በረራ ከሁሉም የበረራ ስራ
የበለጠ ስለሆነ አየር መንገዱ ያሰማራው አሉ የሚላቸውን የበረራ ሰዎች
ነው።
ሆኖም ይህን ስራ በቅርቡ ለመተው አቅዷል፡ አሁን እድሜው ሰላሳ ሲሆን ትዳር ከያዘ ዓመት ሆኖታል። ሚስቱ ካሮል አን ነፍሰ ጡር ናት ይህ ስራ ለወንደላጤ ምንም አይልም እሱ ግን ከቤተሰቡ ርቆ መኖር
አይፈልግም፡ የራሱን ስራ ለመጀመር በቂ ገንዘብ አጠራቅሟል፡ አሜሪካ
ውስጥ ይህን ስራ ለመስራት የሚያስችለው አየር ማረፊያ አለ፡፡" አይሮፕላን ይጠግናል፣ ነዳጅ ይሸጣል፡ በኋላም አይሮፕላን ገዝቶ ያከራያል፡
ሆቴሉ ውስጥ ሲገባ ረዳት ኢንጂነሩን ሚኪን አገኘው፡ ሚኪ ተጫዋች ሲሆን ኤዲን በችሎታው ይወደዋል። ሚኪ ስልክ እየተነጋገረ ሳለ ኤዲንን
ሲያይ ‹‹እድለኛ ነህ አሁን መጥቷል ላገናኝህ›› አለው ለደዋዩ ‹‹አንተን ነው
የሚፈልገው›› ብሎ የስልኩን መነጋገሪያ ለኤዲ ሰጠና ብቻውን መነጋገር
እንዲችል ጥሎት ሄደ።
ኤዲም ስልኩን ተቀበለና ‹‹ሄሎ?›› አለ፡
‹‹ኤድዋርድ ዲኒኪን ነህ?›› ብሎ ጠየቀ ደዋዩ፡፡
ኤዲ ግንባሩን በግርታ ቋጠረ፡ በስልክ የሚሰማው ድምጽ አዲስ ሆነበት ከዚህ በፊትም ማንም ኤድዋርድ ብሎት አያውቅም፡፡ ‹አዎ ነኝ
ማን ልበል?›› አለ፡
‹‹ቆይ ትንሽ ጠብቀኝ ባለቤትህን ላገናኝህ አጠገቤ ነው ያለችው›› የኤዲ ልብ ተንጠለጠለ ካሮል አን ለምንድነው ከአሜሪካ የደወለችልኝ ችግር አለ ማለት ነው?› ሲል ተጨነቀ፡፡
ከአፍታ በኋላ የካሮል አን ድምጿ ተሰማ ‹‹ኤዲ›› አለች እምባ እየተናነቃት፡
‹‹እንዴት ነሽ ማርዬ ምን ሆነሻል?››
ካሮል አን የባልዋን ድምጽ ስትሰማ ለቅሶዋን ለቀቀችው።
ኤዲ በዚያች ደቂቃ ውስጥ ክፉ ነገር አዕምሮው ውስጥ አቃጨለበት፡
‹ካሮሌ ላይ ምን ደርሶባት ይሆን? ውርጃ ገጠማት ይሆን? ቤቱ ተቃጠለ?
ማን ይሆን የሞተው? የሚሉ ሃሳቦች በአንድ ላይ መጡበት፡፡
«ካሮል ተረጋጊ ደህናም አይደለሽ?››
‹‹አይ ምንም አልሆንኩም›› አለች እየተነፋረቀች፡
‹‹ታዲያ ምን ሆነሽ ነው የምታለቅሺው?›› አለ ሆዱ በፍርሃት እየተንቦጫቦጨ፡
‹‹ምን ተፈጠረ ንገሪኝ የኔ ውድ?››
‹‹እነዚህ ሰዎች እቤት መጡ››
ኤዲ ይህን ሲሰማ በድንጋጤ የበረዶ ክምር ሆነ ‹‹የምን ሰዎች? ምን
አደረጉሽ?››
‹‹መኪና ውስጥ ከተው ወሰዱኝ››
‹‹ወይ አምላኬ! ማን ናቸው?›› ንዴቱ ደረቱ ላይ ውጋት ለቀቀበትና
መተንፈስ አቃተው፡
‹‹ጎድተውሻል?››
‹‹አይ ደህና ነኝ፡ ነገር ግን ኤዲ ሰዎቹ ያስፈራሉ››
ምን እንደሚል ጨነቀው፡ ብዙ ነገሮች አዕምሮው ውስጥ መጡበት፡፡"
የሆኑ ሰዎች ሚስቱን አግተዋታል፡፡ ምንድነው ነገሩ? በመጨረሻም
‹‹ለምን?›› ሲል ጠየቀ፡፡
‹‹ምክንያቱን አልነገሩኝም››
‹‹ምን አሉሽ?››
‹‹ኤዲዬ የሚሉህን በሙሉ አርግላቸው፡፡ የማውቀው ይህን ብቻ ነው››
ንዴትና ፍርሃት እየተፈራረቁበት ‹‹አንቺን ከሚያሰቃዩብኝ ያሉትን
አደርግላቸዋለሁ›› አለ፡፡
‹‹እውነት?››
‹‹አዎ የኔ ማር››
‹‹ተመስገን አምላኬ ላንተ ምን ይሳንሃል›› አለች ካሮል አን።
‹‹መቼ ነው ያገቱሽ?››
‹‹ከሁለት ሰዓት በፊት››
‹‹አሁን የት ነው ያለሽው?››
‹‹ከኛ ቤት ብዙም አይርቅም.›› ብላ ሳትጨርስ የድንጋጤ ጩኸት
አሰማች፡፡
፡
፡
#ክፍል_ስድስት
፡
፡
#በኬንፎሌት
፡
፡
#ትርጉም_ወንዳየሁ_ንጉሴ
...‹የሚያስቸኩልሽ ነገር የለም›› አለ ኮንስታብሉ ‹‹አባትሽ ሊወስዱሽ
እየመጡ ነው፡፡››
የማርጋሬት ልብ በድንጋጤ ቀጥ አለ፡ እንዴት ሊሆን ይችላል? አሁን
ያለችበት ቦታ አባቷ የማያውቁት ስለሆነ ደህነኛ ቦታ ነው ብላ ተማምና ነበር፡፡
አባቷን ዝቅ አድርጋ ነበር የገመተቻቸው፡ በዚህ ደቂቃ ውስጥ ሊይዟት ይመጣሉ! ሃሳቡ አንቀጠቀጣት ‹‹የት እንዳለሁ እንዴት አወቀ አባባ?›› አለች፡፡
ወጣቱ ፖሊስ በኩራት ‹‹ትናንት ማታ ስለመጥፋትሽ የቴሌግራም መልዕክት ደርሶን ነበር፡፡ ስመጣ አየሁት፡፡ በጨለማ የመጣሽ ጊዜ
አላወቅኩሽም ነበር፡፡ ስምሽን ግን አስታወስኩት፡፡ ከተገኘሽ ለጌታ ኦክሰንፎርድ
እንዲነገራቸው ቴሌግራሙ ያዛል፡፡ እዚህ እንዳመጣሁሽ ለአባትሽ ደወልኩ››
ማርጋሬት ብድግ አለች፧ ልቧ በጣም ይመታል፡፡ ‹‹እሱን አልጠብቅም
አሁን ነግቷል›› አለች፡፡
ፖሊሱ ስጋት ገባው ‹‹ትንሽ ቆይ›› አለ፡፡ ዞር አለና ‹‹ሃምሳ አለቃ እመቤት ማርጋሬት መሄዴ ነው እያለች ነው›› ብሎ ነገረው፡፡
ሄሪ ማርክስ ‹‹እዚህ ይዘው ሊያቆዩሽ አይችሉም ባንቺ እድሜ ከቤት ጠፍቶ መሄድ ወንጀል ተደርጎ አይቆጠርም፡፡ መሄድ ከፈለግሽ ቀጥ ብለሽ
ሂጂ›› አላት፡፡
ሃምሳ አለቃውም ‹‹ነገር ግን ጫማ የለሽም፤ ስቶኪንግሽ ተቀዳዷል፡፡ አባትሽ ጋ ልደውልልሽ›› አላት፡፡
ማሰብ ጀመረች፡፡ ጣቢያ እንደደረሰች ነው ለአባቷ ስልክ የተደወለው፡፡
አሁን አንድ ሰዓት አልሞላውም ማለት ነው፡፡ አባቷ ደግሞ ከዚህ በኋላ
እዚህ ለመድረስ ቢያንስ ከአንድ ሰዓት በላይ ይፈጅባቸዋል፡ ‹‹ደህና›› አለች ለደጉ ፖሊስ ‹‹አመሰግናለሁ፡፡››
ሄሪ ወደ ፖሊስ ስታዘግም አየና ‹‹ጅል›› አላት፡፡
ፖሊሱ አንድ ትንሽ ክፍል ውስጥ ወስዶ አስገባት፡፡ ወንበሮቹ ተራ ናቸው፡
አንድ አግዳሚ ወንበር ይታያታል፡፡ ከላይ ማቀፊያ የሌለው አምፑል ተንጠልጥሏል፡ መስኮቱ በብረት ፍርግርግ ተዘግቷል፡ ሃምሳ አለቃው ይህ
ክፍል ከባለጉዳይ መቀበያው ክፍል የተሻለ ነው ብሎ እንዴት እንዳሰበ
አልገባሽ አላት፡፡ ልትነግረው ዞር ስትል በሩን ፊቷ ላይ ጠረቀመው፡፡ አንድ
ክፉ ነገር እንዳለ በልቧ ጠረጠረችና ፍርሃት ገባት፡፡ ተወርውራ በሩ ጋ ሄዳ
ለመክፈት ታገለች ከዚያም ፍርሃቷም እውነት መሆኑን በሩ ሲቆለፍ አረጋገጠች፡፡ የበሩን እጄታ በሃይል ነቀነቀችው፤ ነገር ግን በሩ የሚከፈት አልሆነም በተስፋ መቁረጥ በሩ ላይ ልጥፍ አለች፡፡
ከውጭ በኩል ሳቅ ይሰማታል፤ ከዚያም ሃሪ ‹‹እናንተ እርጉሞች›› ሲል
ተሰማት ‹‹አፍክን ዝጋ›› አለው ፖሊሱ፡፡
‹ምንም መብት የላችሁም ልጅቷን ለማቆየት፤ አንተም ታውቃለህ አለው።
‹‹አባቷ የተከበሩ ሰው ስለሆኑ ነው እንደዚህ ያደረኩት›› አለ፡
ማርጋሬት ያሰበችው ባለመሳካቱ በምሬት ተንገበገበች፡ የማምለጥ
እቅዷ ውሃ በልቶታል። ይረዱኛል ብላ የገመተቻቸው ሰዎች አታለዋታል ለትንሽ ጊዜ ነፃ
ነበረች አሁን ግን ነፃነቷ አብቅቷላተል ምድር ጦር
መምሪያው መሄድ አለመቻሏ አንገበገባት
ከጦርነቱ ለመሸሽ የፓን አሜሪካ ንብረት በሆነችው አይሮፕላን ተሳፍራ ኒውዮርክ ልትሄድ ነበር። ይህን ያህል ደክማም እድሏ አልሰምር አላት፡፡
ከብዙ ቆይታ በኋላ ከበሩ ወደ መስኮቱ ሄደች። በመስኮት አጮልቃ
ስታይ ምንም ነገር የማይታይበት ጓሮና የሸክላ ግድግዳ ብቻ ነው::
በሽንፈትና በአቅመቢስነት መስኮቱ ጋር ተገትራ የአባቷን መምጣት
ከመጠባበቅ በስተቀር ምንም ምርጫ አልነበራትም።
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
ኤዲ ዲኪን ለአይሮፕላኑ የመጨረሻ ፍተሻ አደረገ እያንዳንዳቸው የ1500 የፈረስ ጉልበት ያላቸው አራቱ ሞተሮች የተቀቡት ዘይት ያብለጨልጫል፡ እያንዳንዱ ሞተር የሰው ቁመት አለው። ኤዲ እያንዳንዱን የሞተር ክፍል መርምሮ ሲጨርስ ዘጋጋና ከመሰላሉ ላይ ወረደ። አይሮፕላኑ ለበረራ ሲዘጋጅ ቱታውን ያወልቅና ሰውነቱን ታጥቦ የአየር መንገዱን የበረራ ዩኒፎርም ይለብሳል።
ከአይሮፕላን ማረፊያ ወደቡ ወጥቶ ሲሄድ ፀሀይ ገና አልጠለቀችም፡ከዚያም የስራ ባልደረቦቹ ወደሚገኙበት ሆቴል አመራ: በአይሮፕላኑና
በሚሰራው ስራ ይኮራል። አትላንቲክ አቋራጭ በረራ ከሁሉም የበረራ ስራ
የበለጠ ስለሆነ አየር መንገዱ ያሰማራው አሉ የሚላቸውን የበረራ ሰዎች
ነው።
ሆኖም ይህን ስራ በቅርቡ ለመተው አቅዷል፡ አሁን እድሜው ሰላሳ ሲሆን ትዳር ከያዘ ዓመት ሆኖታል። ሚስቱ ካሮል አን ነፍሰ ጡር ናት ይህ ስራ ለወንደላጤ ምንም አይልም እሱ ግን ከቤተሰቡ ርቆ መኖር
አይፈልግም፡ የራሱን ስራ ለመጀመር በቂ ገንዘብ አጠራቅሟል፡ አሜሪካ
ውስጥ ይህን ስራ ለመስራት የሚያስችለው አየር ማረፊያ አለ፡፡" አይሮፕላን ይጠግናል፣ ነዳጅ ይሸጣል፡ በኋላም አይሮፕላን ገዝቶ ያከራያል፡
ሆቴሉ ውስጥ ሲገባ ረዳት ኢንጂነሩን ሚኪን አገኘው፡ ሚኪ ተጫዋች ሲሆን ኤዲን በችሎታው ይወደዋል። ሚኪ ስልክ እየተነጋገረ ሳለ ኤዲንን
ሲያይ ‹‹እድለኛ ነህ አሁን መጥቷል ላገናኝህ›› አለው ለደዋዩ ‹‹አንተን ነው
የሚፈልገው›› ብሎ የስልኩን መነጋገሪያ ለኤዲ ሰጠና ብቻውን መነጋገር
እንዲችል ጥሎት ሄደ።
ኤዲም ስልኩን ተቀበለና ‹‹ሄሎ?›› አለ፡
‹‹ኤድዋርድ ዲኒኪን ነህ?›› ብሎ ጠየቀ ደዋዩ፡፡
ኤዲ ግንባሩን በግርታ ቋጠረ፡ በስልክ የሚሰማው ድምጽ አዲስ ሆነበት ከዚህ በፊትም ማንም ኤድዋርድ ብሎት አያውቅም፡፡ ‹አዎ ነኝ
ማን ልበል?›› አለ፡
‹‹ቆይ ትንሽ ጠብቀኝ ባለቤትህን ላገናኝህ አጠገቤ ነው ያለችው›› የኤዲ ልብ ተንጠለጠለ ካሮል አን ለምንድነው ከአሜሪካ የደወለችልኝ ችግር አለ ማለት ነው?› ሲል ተጨነቀ፡፡
ከአፍታ በኋላ የካሮል አን ድምጿ ተሰማ ‹‹ኤዲ›› አለች እምባ እየተናነቃት፡
‹‹እንዴት ነሽ ማርዬ ምን ሆነሻል?››
ካሮል አን የባልዋን ድምጽ ስትሰማ ለቅሶዋን ለቀቀችው።
ኤዲ በዚያች ደቂቃ ውስጥ ክፉ ነገር አዕምሮው ውስጥ አቃጨለበት፡
‹ካሮሌ ላይ ምን ደርሶባት ይሆን? ውርጃ ገጠማት ይሆን? ቤቱ ተቃጠለ?
ማን ይሆን የሞተው? የሚሉ ሃሳቦች በአንድ ላይ መጡበት፡፡
«ካሮል ተረጋጊ ደህናም አይደለሽ?››
‹‹አይ ምንም አልሆንኩም›› አለች እየተነፋረቀች፡
‹‹ታዲያ ምን ሆነሽ ነው የምታለቅሺው?›› አለ ሆዱ በፍርሃት እየተንቦጫቦጨ፡
‹‹ምን ተፈጠረ ንገሪኝ የኔ ውድ?››
‹‹እነዚህ ሰዎች እቤት መጡ››
ኤዲ ይህን ሲሰማ በድንጋጤ የበረዶ ክምር ሆነ ‹‹የምን ሰዎች? ምን
አደረጉሽ?››
‹‹መኪና ውስጥ ከተው ወሰዱኝ››
‹‹ወይ አምላኬ! ማን ናቸው?›› ንዴቱ ደረቱ ላይ ውጋት ለቀቀበትና
መተንፈስ አቃተው፡
‹‹ጎድተውሻል?››
‹‹አይ ደህና ነኝ፡ ነገር ግን ኤዲ ሰዎቹ ያስፈራሉ››
ምን እንደሚል ጨነቀው፡ ብዙ ነገሮች አዕምሮው ውስጥ መጡበት፡፡"
የሆኑ ሰዎች ሚስቱን አግተዋታል፡፡ ምንድነው ነገሩ? በመጨረሻም
‹‹ለምን?›› ሲል ጠየቀ፡፡
‹‹ምክንያቱን አልነገሩኝም››
‹‹ምን አሉሽ?››
‹‹ኤዲዬ የሚሉህን በሙሉ አርግላቸው፡፡ የማውቀው ይህን ብቻ ነው››
ንዴትና ፍርሃት እየተፈራረቁበት ‹‹አንቺን ከሚያሰቃዩብኝ ያሉትን
አደርግላቸዋለሁ›› አለ፡፡
‹‹እውነት?››
‹‹አዎ የኔ ማር››
‹‹ተመስገን አምላኬ ላንተ ምን ይሳንሃል›› አለች ካሮል አን።
‹‹መቼ ነው ያገቱሽ?››
‹‹ከሁለት ሰዓት በፊት››
‹‹አሁን የት ነው ያለሽው?››
‹‹ከኛ ቤት ብዙም አይርቅም.›› ብላ ሳትጨርስ የድንጋጤ ጩኸት
አሰማች፡፡
👍21❤2
#ከቡስካ_በስተጀርባ
#ድንግል_ውበት
፡
፡
#ክፍል_ስድስት
፡
፡
#በፍቅረማርቆስ_ደስታ
ዲመካና ቱርሚ ሁለቱም የሐመር አውራጃ የገጠር ከተሞች ናቸው" ለቆላማው የሐመር ክፍል ቱርሚ፣ ለደጋማው ደግሞ ዲመካ
አማካዮች ሲሆኑ፣ ሁለቱም ደረቅና ቁጥቋጦ የበዛበት መሬት ያላቸው ናቸው። ቱርሚ መንገድ ዳር ያለ ከተማ ሲሆን፣ ከዲመካ ይልቅ ሁለት ትናንሽ ምግብ ቤቶች፣ ወደ አምስት የሚደርሱ ሻይና ቂጣ
መሸጫ ቤቶች፣ ሁለት በመጠን ከፍ ያሉና ትናንሽ ሳሙና፣ ባትሪ ድንጋይ፣ ክብሪት...የሚሸጥባቸው መንገድ ላይ የሚዘረጉ ሱቆች አሉ። በተለይም በገበያ ቀን ከተማዋ ደመቅዐመቅ ብላ ትታያለች
ገበያ ውስጥ ለመጠጥ ቦርዴና የአበሻ አረቄ፣ ግልድም የሚሆን ከጥጥ
ተሠርቶ ከኮንሶ በነጋዴዎች የሚመጣ ሳዳጎራ፣ ጨሌና አንባር፣በቆሎና ማሽላ ዓይነተኛ ሸቀጦች ናቸው" ቱርሚ፣ በከብት እርባታና
በቁፋሮ ምርት ለሚተዳደረው የሐመር ሕዝብ ድል ያለች ከተማ፣
ታምሮና ተውቦ የሚታዩባት፣ ጐረምሳና ሴቱ አብሮ መሸታ ገብቶ የሚደባበስባት፣ የተጣላ የሚታረቅባት፣ ሽማግሎች ተሰባስበው
የሚመክሩባት፣ ብርቅዬ ከተማ ናት ለሐመሮች።
ዲመካ ግን፣ ከዋናው መንገድ ወጣ ብላ፣ ሰቀላ ቤቶች በአራት ማዕዘን ተሰትረው የሚታዩባት ከተማ ናት። በየሰቀላ ቤቶች ፊት ለፊትና በስተኋላ የግራር፣ የብርብራ.ዛፍ ያለ ሲሆን ከከተማው ግርጌ፣ ከወንዙ ጥግ በሚስዮናውያኑ የተተከለ በፀሐይ ብርሃን በሚንቀሳቀስ መስኖ የለማ የፍራፍሬ፣ የበቆሎና ሌሎችም ወቅታዊ
አዝርእቶች የሚታይ ሲሆን፣ ከጎን በኩልም የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን አዲስ ሕንፃና ጋራዡ፣ ዲመካን አንድ ዓይና ከመሆን አድኗታል"የገበያ ቀን፣ በየሰቀላ ቤቱ ጠጅ የሚሸጥ ሲሆን፣ ምግብ ቤት ግን ከናካቴው የለም" ደግነቱ፣ እንግዳ ብርቅ በመሆኑ ጋባዡ ብዙ ስለሆነ
እግር የጣለው ሰው ሕቅ ብሎ ሲያዝን አይሰማም" በተረፈ ገበያ ውስጥ ያለው ሸቀጥ ከቱርሚ ጋር ተመሳሳይ ነው ሁለቱንም ከተሞች ቡስካ ስር ካሉት ላላና ሻንቆ እስከ ሚኖ፣ ሚርሻ፣ ሜን፣ አንጉዳ
መንደር ድረስ የሚያገናኛቸው የማኅበረሰብ ሕይወት የሆነው የከስኪ ወንዝ ነው ከብቱ፣ ፍየሉ፣ በጉ፣ ሰው፣ አዕዋፍ...ሁሉም ጥሙን
ይቈርጥበታል።
ካርለትና ከሎ ሆራ ከዲመካ ወጣ ብላ ከምትገኘው የሻንዛ መንደር መኖር ከጀመሩ ሁለት ወራት አለፋቸው የክልሉ ኗሪዎ
ከሎ ሆራን እንዳዩ፣ «የሆራ ሻላ ልጅ» እያሉ፣ ሰላምታና ስጦታ አጐረፉለት ቆዳ ለባሽ እናቱና እኅቶቹም ደረታቸውን በመድቃት
የደስታ እንባ እያነቡ አስተናገዱት።
ካርለት፣ በቆይታዋ የተለያዩ ልምዶችን አገኘች። ከዘመናዊ ሕይወቷ እንደ ባንዲራ ወርዳለችI ይህን አጋጣሚዋን ግን በግላዊ
ትርጕሟ እንደ መጥፎ ከመውሰድ ይልቅ እንደ ጥሩ አጋጣሚ በመውሰዷ የሚሰማት ስሜት የደስታ ስሜት ነው። ይህ ደግ
ማኅበረሰቡን ለመቅረብና ለመርዳት እንድትጣጣር አድርጓታል ስለዚህ፣ ካርለት የከሎ ሆራን እናትና እኅቶች፣ የአካባቢው ሴቶችና ወንዶች ለመቅረብ የቋንቋ ትምህርቷን በማጠናከር ልትግባባ ሞክራለች ቢሆንም ግን፣ በወደፊቱ ጥናቷ ላይ ከፍተኛ እንቅፋት
እየሆነባት የመጣው በሴቶች ላይ ያለው ባህላዊ ተፅዕኖ እንደ ጋለ ብረት ምጣድ አላስጠጋሽ አላት"¸
በማኅበረሰቡ፣ ሴት ሣቂታ ወንድ ኰስታራ ነው" ሴት በልጃገረድነቷ የአባቷ፣ ባል ካአገባች ደግሞ የባሏ ጥገኛ ናት" ስለዚህ
በልባዊ ኵራት የተሞሉት የሐመር ወንዶች ካርለት ሴት ሆና እንዴት ባሏን ወይንም አባቷን ጥላ ወደ እነሱ እንደ መጣች በጣም
አስገርሟቸዋል" ሽማግሎች እንዲያውም፣ «ይእ! እሷ ምን ታድርግ? አባቷ ወይም ባሏ፣ ብቻዋን መልቀቃቸው ከቶ ምን ያሉ ነፈዞች ቢሆኑ ነው» ብለው አውግዘዋል"
ስለሆነም፣ ካርለት የጥናት ኮተቷን ይዛ ለጥያቄ ቀረብ ባለቻቸው ቍጥር የደስታ ገጽ ስለማታይባቸው ለተወሰነ ቀን ግራ ተጋብታ
ነበር" አንድ ቀን ግን ወንዶች ሊያደርጉት ባሰቡት ስብሰባ ለመካፈል ሄደች። ገላጣ ስፍራ ላይ ካለ ትልቅ ግራር ጥላ ሥር፣ የሻንቆ መንደር
ሽማግሌ፣ አባወራ፣ ጐረምሶች ተሰብስበዋል" ከወገብ በላይ ራቁት
ሆነው፣ ቆዳቸው የተሸበሸበ፣ ጸጕራቸው ገለል ብሎ ሽበት ጣል
ጣል ያደረገበት አዛውንት በሁለት ወገን ጦር የተሰካበት ብትር ይዘው፣ መሬቱን ወጋ ነቀል እያደረጉ ወዲያ ወዲህ እየተንቀሳቀሱ
ንግግር ሲያደርጉ ሁሉም ጸጥ ብሎ በተመስጦ ሲያዳምጥI ካርለት
ስብሰባውን ለመካፈል ጓጕታ ቀስ እያለች ተጠግታ ልትቀመጥ ስትል
ሁሉም ዘወር ብለው አይዋትና በስብሰባው መካፈል እንደማትችል
ነገሯት"
ካርለት፣ ወንዶችን ለመቅረብ አለመቻሏ ብቻ ሳይሆን፣ ሴቶችም
ምሥጢራቸውን ሊገልጹላት ባለመቻላቸው ግራ ተጋብታ ቅር ተሰኘች" በተለይ ደግሞ፣ ለመሳተፍ ጓጕታለት በነበረው የወንዶች
ስብሰባ ልትካፈል ባለመቻሏ ጥልቅ ኀዘን ከመስማት አልፎ ለወደፊቱ አደርገዋለሁ ብላ የደከመችለት ጥናት ሊሳካ አይችልም ብላ ሠጋች"
ስለዚህ፣ ዓይኗ ቁንዶ በርበሬ መስሎ እስኪቀላ ድረስ እያለቀሰች፣ «ከሎ! ለምን ወንዶች ጥያቄዎቼን ለመመለስ ፈቃደኛ
አይሆኑም? ለምንስ በስብሰባቸው እንዳልካፈል ይከለክሉኛል? በዚህ
ዓይነት ጥናቴንስ እንዴት ማድረግ እችላለሁ? » ብላ ጠየቀችው።
«በሐመር ማኅበረሰብ ሴት ወንድን ለመርዳትና ለማገልገል የተፈጠረች ጸጋ ናት። ለወንዶች ትንባሆ ታዘጋጃለች ልጃገረድ
ከሆነችም ታርሳለች፤ የከብቶችን በረት ታጸዳለች ሕፃናትን ትንከባከባለች ምግብ ታበስላለች.እንጂ ከወንድ ጎን ተቀምጣ ስለ
ማኅበረሰቡ ችግር በመነጋገርና በመምከር መፍትሔ መፈለግና ጦርነት
መግጠም አትችልም።
«ካርለት፣ አንቺ ወንድ ብትሆኚ ኖሮ ምንም ችግር ላያጋጥምሽ ይችል ነበር" ሆኖም ግን አንቺ ሴት ነሽ። ለሐመር ሴቶች የወጣው
ደንብ ማንኛዋንም ሴት ያጠቃልላል፣ ብለው ስለሚያምኑ በስብሰባቸው እንድትካፈይ አለመፍቀድ ብቻ ሳይሆን፣ የምትጠይ
ቂያቸውንም ሙሉ በሙሉ ለመመለስ ፈቃደኛ አይሆኑም" እኔም
ይህ ችግርሽ እጀ ሰባራ ሊያደርግሽ እንደሚችል እየተሰማኝ መጥቷል" ምናልባትም ችግሩ ግልጽ ከሆነልሽ የግልሽን መፍትሔ
ውሰጂ» አላት"
ካርለት ፈጽሞ ያልጠበቀችውን መልስ በማግኘቷ በባህላዊ
ልዩነቱ በጣም ተሸማቀቀች በአሁኑ የጥናት አያያዟ በእርግጥ ለመቀጠል አለመቻሏ ቁልጭ ብሎ ታያት በአእምሮዋ አውጥታ
አውርዳ የወሰነችው ውሳኔ፣ እስከ አሁን ያደረገችው ጥረትና ጒዞ ጥሩ የድንጋይ ምት እንዳረፈበት መስተዋት ከሽ ብሎ ሊሰበር
የተቃረበ መስሎ ታያት። ያ ችሎታዋንና ጥንካሬዋን የሚያስመሰክረው፣ ማንነቷን የሚያረጋግጠው፣ ብቃቷን ማያዋ መስተዋት
እንዲሰበር ግን ጭራሽ አትፈቅድም። በዚህም ተባለ በዚያ የጀመረችውን ከግቡ ለማድረስ ሕሊናዋ እሷን ወደፊት መግፋት
አለበት" ሰዎች ከጎሪላና ከእፉኝት፣ ከአንበሳና ከተኩላ ጋር በሐሩርና
በረዶ መኖር መቻላቸውን አስመስክረዋል" እሷም ዓላማዋን ከግቡ
ለማድረስ ተጣጣፊና ጠንካራ ለመሆን ከራሷ ጋር ተማማላች" ግን ምን መላ ትምታ? ለተወሰነ ቀን ካለ ዕረፍት በዚህ ጉዳይ ላይ ስታስብ ከቆየች በኋላ ምንም እንኳ የችግር ኮተቱን ዓይኗን ጨፍና አላይም
ብትልም፣ የሚያጋጥማት ሥቃይ ከባድ መሆኑን አውቃ ቀበቶዋን አጠበቀች
ከዚያም፣ ያሰበችውን መላ ለመጀመር ያስችላት ዘንድ ባል አለማግባቷን የሚገልጽ ወሬ ለአገኘችው ሁሉ አወራች" ወሬው ተዛምቶ በየመንደሩ መዳረሱን ስታረጋግጥ ደግሞ ጐረምሶች፣ ወጣት
ባለትዳር ወንዶች፣ ያላገቡና ባለ እጮኛ ልጃገረዶች ምሽትን ተገን አድርገው ወደሚቦርቁበት የምሽት ጭፈራ «ኢቫንጋዲ» ለመካፈል ነኢማ ከምትባለው የከሎ ሆራ እኀት ጋር ስትሄድ ምንም ተቃውሞ ሳይደርስባት ቀረ።
#ድንግል_ውበት
፡
፡
#ክፍል_ስድስት
፡
፡
#በፍቅረማርቆስ_ደስታ
ዲመካና ቱርሚ ሁለቱም የሐመር አውራጃ የገጠር ከተሞች ናቸው" ለቆላማው የሐመር ክፍል ቱርሚ፣ ለደጋማው ደግሞ ዲመካ
አማካዮች ሲሆኑ፣ ሁለቱም ደረቅና ቁጥቋጦ የበዛበት መሬት ያላቸው ናቸው። ቱርሚ መንገድ ዳር ያለ ከተማ ሲሆን፣ ከዲመካ ይልቅ ሁለት ትናንሽ ምግብ ቤቶች፣ ወደ አምስት የሚደርሱ ሻይና ቂጣ
መሸጫ ቤቶች፣ ሁለት በመጠን ከፍ ያሉና ትናንሽ ሳሙና፣ ባትሪ ድንጋይ፣ ክብሪት...የሚሸጥባቸው መንገድ ላይ የሚዘረጉ ሱቆች አሉ። በተለይም በገበያ ቀን ከተማዋ ደመቅዐመቅ ብላ ትታያለች
ገበያ ውስጥ ለመጠጥ ቦርዴና የአበሻ አረቄ፣ ግልድም የሚሆን ከጥጥ
ተሠርቶ ከኮንሶ በነጋዴዎች የሚመጣ ሳዳጎራ፣ ጨሌና አንባር፣በቆሎና ማሽላ ዓይነተኛ ሸቀጦች ናቸው" ቱርሚ፣ በከብት እርባታና
በቁፋሮ ምርት ለሚተዳደረው የሐመር ሕዝብ ድል ያለች ከተማ፣
ታምሮና ተውቦ የሚታዩባት፣ ጐረምሳና ሴቱ አብሮ መሸታ ገብቶ የሚደባበስባት፣ የተጣላ የሚታረቅባት፣ ሽማግሎች ተሰባስበው
የሚመክሩባት፣ ብርቅዬ ከተማ ናት ለሐመሮች።
ዲመካ ግን፣ ከዋናው መንገድ ወጣ ብላ፣ ሰቀላ ቤቶች በአራት ማዕዘን ተሰትረው የሚታዩባት ከተማ ናት። በየሰቀላ ቤቶች ፊት ለፊትና በስተኋላ የግራር፣ የብርብራ.ዛፍ ያለ ሲሆን ከከተማው ግርጌ፣ ከወንዙ ጥግ በሚስዮናውያኑ የተተከለ በፀሐይ ብርሃን በሚንቀሳቀስ መስኖ የለማ የፍራፍሬ፣ የበቆሎና ሌሎችም ወቅታዊ
አዝርእቶች የሚታይ ሲሆን፣ ከጎን በኩልም የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን አዲስ ሕንፃና ጋራዡ፣ ዲመካን አንድ ዓይና ከመሆን አድኗታል"የገበያ ቀን፣ በየሰቀላ ቤቱ ጠጅ የሚሸጥ ሲሆን፣ ምግብ ቤት ግን ከናካቴው የለም" ደግነቱ፣ እንግዳ ብርቅ በመሆኑ ጋባዡ ብዙ ስለሆነ
እግር የጣለው ሰው ሕቅ ብሎ ሲያዝን አይሰማም" በተረፈ ገበያ ውስጥ ያለው ሸቀጥ ከቱርሚ ጋር ተመሳሳይ ነው ሁለቱንም ከተሞች ቡስካ ስር ካሉት ላላና ሻንቆ እስከ ሚኖ፣ ሚርሻ፣ ሜን፣ አንጉዳ
መንደር ድረስ የሚያገናኛቸው የማኅበረሰብ ሕይወት የሆነው የከስኪ ወንዝ ነው ከብቱ፣ ፍየሉ፣ በጉ፣ ሰው፣ አዕዋፍ...ሁሉም ጥሙን
ይቈርጥበታል።
ካርለትና ከሎ ሆራ ከዲመካ ወጣ ብላ ከምትገኘው የሻንዛ መንደር መኖር ከጀመሩ ሁለት ወራት አለፋቸው የክልሉ ኗሪዎ
ከሎ ሆራን እንዳዩ፣ «የሆራ ሻላ ልጅ» እያሉ፣ ሰላምታና ስጦታ አጐረፉለት ቆዳ ለባሽ እናቱና እኅቶቹም ደረታቸውን በመድቃት
የደስታ እንባ እያነቡ አስተናገዱት።
ካርለት፣ በቆይታዋ የተለያዩ ልምዶችን አገኘች። ከዘመናዊ ሕይወቷ እንደ ባንዲራ ወርዳለችI ይህን አጋጣሚዋን ግን በግላዊ
ትርጕሟ እንደ መጥፎ ከመውሰድ ይልቅ እንደ ጥሩ አጋጣሚ በመውሰዷ የሚሰማት ስሜት የደስታ ስሜት ነው። ይህ ደግ
ማኅበረሰቡን ለመቅረብና ለመርዳት እንድትጣጣር አድርጓታል ስለዚህ፣ ካርለት የከሎ ሆራን እናትና እኅቶች፣ የአካባቢው ሴቶችና ወንዶች ለመቅረብ የቋንቋ ትምህርቷን በማጠናከር ልትግባባ ሞክራለች ቢሆንም ግን፣ በወደፊቱ ጥናቷ ላይ ከፍተኛ እንቅፋት
እየሆነባት የመጣው በሴቶች ላይ ያለው ባህላዊ ተፅዕኖ እንደ ጋለ ብረት ምጣድ አላስጠጋሽ አላት"¸
በማኅበረሰቡ፣ ሴት ሣቂታ ወንድ ኰስታራ ነው" ሴት በልጃገረድነቷ የአባቷ፣ ባል ካአገባች ደግሞ የባሏ ጥገኛ ናት" ስለዚህ
በልባዊ ኵራት የተሞሉት የሐመር ወንዶች ካርለት ሴት ሆና እንዴት ባሏን ወይንም አባቷን ጥላ ወደ እነሱ እንደ መጣች በጣም
አስገርሟቸዋል" ሽማግሎች እንዲያውም፣ «ይእ! እሷ ምን ታድርግ? አባቷ ወይም ባሏ፣ ብቻዋን መልቀቃቸው ከቶ ምን ያሉ ነፈዞች ቢሆኑ ነው» ብለው አውግዘዋል"
ስለሆነም፣ ካርለት የጥናት ኮተቷን ይዛ ለጥያቄ ቀረብ ባለቻቸው ቍጥር የደስታ ገጽ ስለማታይባቸው ለተወሰነ ቀን ግራ ተጋብታ
ነበር" አንድ ቀን ግን ወንዶች ሊያደርጉት ባሰቡት ስብሰባ ለመካፈል ሄደች። ገላጣ ስፍራ ላይ ካለ ትልቅ ግራር ጥላ ሥር፣ የሻንቆ መንደር
ሽማግሌ፣ አባወራ፣ ጐረምሶች ተሰብስበዋል" ከወገብ በላይ ራቁት
ሆነው፣ ቆዳቸው የተሸበሸበ፣ ጸጕራቸው ገለል ብሎ ሽበት ጣል
ጣል ያደረገበት አዛውንት በሁለት ወገን ጦር የተሰካበት ብትር ይዘው፣ መሬቱን ወጋ ነቀል እያደረጉ ወዲያ ወዲህ እየተንቀሳቀሱ
ንግግር ሲያደርጉ ሁሉም ጸጥ ብሎ በተመስጦ ሲያዳምጥI ካርለት
ስብሰባውን ለመካፈል ጓጕታ ቀስ እያለች ተጠግታ ልትቀመጥ ስትል
ሁሉም ዘወር ብለው አይዋትና በስብሰባው መካፈል እንደማትችል
ነገሯት"
ካርለት፣ ወንዶችን ለመቅረብ አለመቻሏ ብቻ ሳይሆን፣ ሴቶችም
ምሥጢራቸውን ሊገልጹላት ባለመቻላቸው ግራ ተጋብታ ቅር ተሰኘች" በተለይ ደግሞ፣ ለመሳተፍ ጓጕታለት በነበረው የወንዶች
ስብሰባ ልትካፈል ባለመቻሏ ጥልቅ ኀዘን ከመስማት አልፎ ለወደፊቱ አደርገዋለሁ ብላ የደከመችለት ጥናት ሊሳካ አይችልም ብላ ሠጋች"
ስለዚህ፣ ዓይኗ ቁንዶ በርበሬ መስሎ እስኪቀላ ድረስ እያለቀሰች፣ «ከሎ! ለምን ወንዶች ጥያቄዎቼን ለመመለስ ፈቃደኛ
አይሆኑም? ለምንስ በስብሰባቸው እንዳልካፈል ይከለክሉኛል? በዚህ
ዓይነት ጥናቴንስ እንዴት ማድረግ እችላለሁ? » ብላ ጠየቀችው።
«በሐመር ማኅበረሰብ ሴት ወንድን ለመርዳትና ለማገልገል የተፈጠረች ጸጋ ናት። ለወንዶች ትንባሆ ታዘጋጃለች ልጃገረድ
ከሆነችም ታርሳለች፤ የከብቶችን በረት ታጸዳለች ሕፃናትን ትንከባከባለች ምግብ ታበስላለች.እንጂ ከወንድ ጎን ተቀምጣ ስለ
ማኅበረሰቡ ችግር በመነጋገርና በመምከር መፍትሔ መፈለግና ጦርነት
መግጠም አትችልም።
«ካርለት፣ አንቺ ወንድ ብትሆኚ ኖሮ ምንም ችግር ላያጋጥምሽ ይችል ነበር" ሆኖም ግን አንቺ ሴት ነሽ። ለሐመር ሴቶች የወጣው
ደንብ ማንኛዋንም ሴት ያጠቃልላል፣ ብለው ስለሚያምኑ በስብሰባቸው እንድትካፈይ አለመፍቀድ ብቻ ሳይሆን፣ የምትጠይ
ቂያቸውንም ሙሉ በሙሉ ለመመለስ ፈቃደኛ አይሆኑም" እኔም
ይህ ችግርሽ እጀ ሰባራ ሊያደርግሽ እንደሚችል እየተሰማኝ መጥቷል" ምናልባትም ችግሩ ግልጽ ከሆነልሽ የግልሽን መፍትሔ
ውሰጂ» አላት"
ካርለት ፈጽሞ ያልጠበቀችውን መልስ በማግኘቷ በባህላዊ
ልዩነቱ በጣም ተሸማቀቀች በአሁኑ የጥናት አያያዟ በእርግጥ ለመቀጠል አለመቻሏ ቁልጭ ብሎ ታያት በአእምሮዋ አውጥታ
አውርዳ የወሰነችው ውሳኔ፣ እስከ አሁን ያደረገችው ጥረትና ጒዞ ጥሩ የድንጋይ ምት እንዳረፈበት መስተዋት ከሽ ብሎ ሊሰበር
የተቃረበ መስሎ ታያት። ያ ችሎታዋንና ጥንካሬዋን የሚያስመሰክረው፣ ማንነቷን የሚያረጋግጠው፣ ብቃቷን ማያዋ መስተዋት
እንዲሰበር ግን ጭራሽ አትፈቅድም። በዚህም ተባለ በዚያ የጀመረችውን ከግቡ ለማድረስ ሕሊናዋ እሷን ወደፊት መግፋት
አለበት" ሰዎች ከጎሪላና ከእፉኝት፣ ከአንበሳና ከተኩላ ጋር በሐሩርና
በረዶ መኖር መቻላቸውን አስመስክረዋል" እሷም ዓላማዋን ከግቡ
ለማድረስ ተጣጣፊና ጠንካራ ለመሆን ከራሷ ጋር ተማማላች" ግን ምን መላ ትምታ? ለተወሰነ ቀን ካለ ዕረፍት በዚህ ጉዳይ ላይ ስታስብ ከቆየች በኋላ ምንም እንኳ የችግር ኮተቱን ዓይኗን ጨፍና አላይም
ብትልም፣ የሚያጋጥማት ሥቃይ ከባድ መሆኑን አውቃ ቀበቶዋን አጠበቀች
ከዚያም፣ ያሰበችውን መላ ለመጀመር ያስችላት ዘንድ ባል አለማግባቷን የሚገልጽ ወሬ ለአገኘችው ሁሉ አወራች" ወሬው ተዛምቶ በየመንደሩ መዳረሱን ስታረጋግጥ ደግሞ ጐረምሶች፣ ወጣት
ባለትዳር ወንዶች፣ ያላገቡና ባለ እጮኛ ልጃገረዶች ምሽትን ተገን አድርገው ወደሚቦርቁበት የምሽት ጭፈራ «ኢቫንጋዲ» ለመካፈል ነኢማ ከምትባለው የከሎ ሆራ እኀት ጋር ስትሄድ ምንም ተቃውሞ ሳይደርስባት ቀረ።
👍27❤1
#ኢቫንጋዲ
፡
፡
#ክፍል_ስድስት
፡
፡
#በፍቅረማርቆስ_ደስታሰ
መጀመሪያ የደራረቀ እንጨትና ግንድ ቀጥላ ለጉልቻ የሚሆን ሦስት ድንጋይ አቅርባ እሳት አቀጣጠለችና ውሃ የያዘውን
ቶፋ ወደ አንደ በኩል ዘንበል አድርጋ ጣደችው ከዚያ በለሻ እንዲበላ ስታቀብለው “አንችስ ብይ እንጂ ተወተቱም ጠጭ…"
አላት ጭብጦውን እያላመጠ።
ይእ! ይልቅ አታስቀምጠው ጠጣው። የኔ በኋላ ይደርሳል“ ብላ በጨንዋዛ ቅጠል የተቋጠረውን ሽፈሮ ቡና ፈታ በሚቆለቆሰው
እሳት በመቅጃው የቅል ጭልፋ ዙሪያ ትጉልጉል የሚለውን እንፋሉት እንዳያቃጥላት ተጠንቅቃ የቡና ገለባውን ጨመረች:
ሰማዩ ላይ እንደ ጨሌና ዛጎል ከዋክብት ሆጨጭ ብለዋል። በስተ ሰሜን በኩል ደግሞ ብናኝ ዳመና አቅፎ የያቸው ከዋክብት
ብልጭ ድርግም... ይላሉ: የምሽት በራሪዎች የሌሊት ወፍ ጉጉት የማታ ተረኞች ሆነው ወዲህ ወዲያ ይበራሉ: ጅብ ይጮሃል
አንበሳው ያገሳል... ጦጣና ዝንጀሮ ፀጥ ብለዋል: ጉሬዛዎች ግን እንደ ዶሮ ሰዓት እየጠበቁ “ጉርር ጉርር. ጉርርርር..." እየተቀባበሉ ያውካኩና ጸጥ እረጭ ይላሉ።
ዳራና ደልቲ በሚነደው የሳት ወላፈን እሷ አንድ ጉልበቷን
አጥፋ መሬት ላይ አጋድማ፧ ሌላውን ጉልበቷን አጥፋ አቁማ አልፎ አልፎ እንጨቱን ቆስቆስ እያደረገች አይኖችዋን ጨለማው ውስጥ ተክላለች።
ደልቲ በርኮታው ላይ ቁጭ ብሎ የአባቱን ከዋክብት እንደ እሳት እየተንቦገቦጉ ቁልቁል ተወርውረው የሚጠፉትን “ሚቲዎሮች”
እያየ ያስባል።
በሁለቱ መካከል ንግግር የለም:: ፀጥታ ሆኗል: በሐመር ባህል የቡና ሥነሥርዓት እርጋታና ፀጥታ የሰፈነበት ነው:: ህፃናት
እንኳን ይህን ስለሚያውቁ ቡረቃቸውን ገተው ያደፍጣሉ። ሴቷ ወንዱ ሽማግሌው ከራሳቸው
ጋር የሚነጋገሩበት ራሳቸውን የሚመዝኑበት አደብ የሚገዙበት በጎና እኩይ ተግባራቸውን የሚፈትሹበት... ነው የቡና ሥነ ሥርዓት ለሐመሮችሽማግሌ
ትናንትን የሚያደንቅበት ዛሬን የሚያመሰግንበት ነገን በተስፋ የሚጠባበቅበት ግለሰቡ ለማህበረሰቡ ደህንነት ሰላምን፡ ጥጋብን የሚመኝበት የአባት የአያት ደንብ ወደ ልጅ የሚሸጋገርበት ጠላትና ወዳጅ ጠንቅቆ የሚታወቅበት ምላስ አጥራ ህሊና ገዝፎ መግባባት የሚመጣበት ነው የቡና ሥነ ሥርዓት። ይህ የቡና ሥነሥርዓት ለህፃን ለወጣት ለአዋቂ ለሽማግሌ ለእንግዳ ክፍት ነው። ያሻው ሁሉ ይሳተፋል እድሜና ደረጃውን ጠብቆ ይዳረሳል። የሐመር በር መዝጊያ የለውም። የሐመር ሕይወት ጓዳ የለውም፡ የሐመር ማህበረሰብ “ከሌላው ኪስ ወስደህ የኔን ኪስ ሙላ በሚል ስግብግብነት ምኞት ላይ አልተመሰረተም።
ደስታ ችግር ጦርነት... የጋራ ነው: የአንዱ ምርኩዝ ሌላው ነው: ግለሰብ ህብረተሰብን አይረሳም። ህብረተሰቡም ግለሰቡን
አይጥልም ያሳድገዋል ሃብት ያካፍለዋል ይድረዋል ለጀግንነቱም
ያሞግሰዋል...
ስሰዚህ ደልቲና ዳራ ምንም እንኳ ጫካ መሃል ብቻቸውን ቢሆኑም ህሊናቸውና አካላቸው ግን በባህላቸው ደንብና ሥርዓት
የተገነባ ነው: ፀጥታው ተጠብቆ ዝምታው ሰፍኖ እሱም ሆነ እሷ ትናንትን ቃኝተው ዛሬን አስታውሰው ነገን ሲያልሙ በሐሳብ
ተውጠው ቆዩ።
ከዚያ ዳራ ሾርቃውን ጠረግ ጠረግ አረገችና የቅል ማንኪያውን አንስታ ቶፋው ውስጥ ጨምራ ከቡናው ሁለቴ ቀድታ ሰጠችው ደልቲ ቡናውን ለማብረድ ግራና ቀኝ ጎለል አደረገና ፉት ብሎ “ፕስስ ፕስስ.." እያለ ወደ ምስራቅ ምዕራብና ወደ መሬት የሸፈሮ ቡናውን አርከፍክፎ- “የአባቴ ሰማይ ዝናብ ይጣል በሽታዎች ከሐመር ምድር ይጥፉ፤ ከብቶች ፍየሎች በጎች
አያገሱ በሰላም ይግቡ ይውጡ..." ብሎ መረቀና ወደ ዳራ ዞሮ ቡናውን ፉት ብሎ “ፕስስ..” አለና ሽፈሮ ቡናውን አርከፈከፈባት፡
ዳራ ደንገጥም አፈርም ሳትል አይኗን ከወረወረችበት
ሳትመልስ በሃሣብ እንደሰመጠች
“..ተባረኪ... ዘርሽን ያብዛው የአባትሽ የሐመር ምድር የልጆችሽ መቦረቂያ ይሁን... የባልሽ ጥገት ይብዛ" ብሎ መረቃትና ቡናውን በፀጥታ መጠጣት ጀመረ።
ሰረቅ አድርጋ አየችው: በውስጧ እንደ ህፃን የሚላወሰው እሱ ነው ከፊት ለፊቷም የተቀመጠው እሱ ነው፡ ፍቅር የሰጣት የመረቃት እሱ ነው። ስለሱ ያላትን ስሜት አሁንም በእርግጠኝነት አጤነች ስለ ጀግናው የሚባለውንም አስታወሰች።
ጥጃና ፍየል ስትጠብቅ ወንዶች የድሜ ጓደኞችዋ እነሱ ጠመንጃ እያሉ እንጨት ቆርጠው እየተሸከሙ እንደ ጥይት ዳውላ እየወረወሩ ይሄ ከብት የኔ ያ እርሻ የኔ... እየተባባሉ ሲጫወቱ። እሷም የእድሜ እኩዮችዋ ከሆኑት ልጃገረዶች ጋር ከከስኬ ወንዝ
የጭሮሽ ውሃ እየቀዱ እንጨት እየለቀሙ, ልጅ እያቀፉ... ሲጫወቱ
ይቆዩና ጫካው መሃል ሚስትና ባል ሲባባሉ ቆይተው ዘፈን ሲጀምሩ
ስለ ሐመር ተራራ ስለ ሐመር ሰማይና ምድር... ስለከብቶች ሲያዜሙ ይቆዩና የሐመር ጀግኖችን ህፃናቱ ሲያወድሱ የደልቲ ስም የደልቲ ጀግንነት... ይነሳል። ወንዶች ህፃናት “እኔ ነኝ እሱ እኔ ነኝ
ሲባባሉ እሷም ከሌሎች የእድሜ ጓደኞችዋ ጋር “ደልቲን የሆነውን ወንድ እኔ ነኝ የማገባው ! እኔ ነኝ የማገባው" ሲባባሉ አንዳንዴ ሁለት አንዳንዴ ሦስት እየሆኑ ሲያገቡት የነበረው የልጅነት ዘመኗ
ታወሳት። እንዲህ ዳሌዋ ሰፍቶ ጡቶችዋ አጎጥጉጠው ሰውነቷ
አምሮ ባለበት የቡረቃ ዘመኗ ያ ስም አብሯት አደገ:: የዚያ ጀግና መግነጢሳዊ የፍቅር ሃይል በውስጧ እየተገለባበጠ ሲያስጨንቃት ኖረ።
ገበያ ስታየው ትንፋሽዋ ቁርጥ ያለባት ሲመስላት ስሙ ሲነሳ እንደ አውሬ ስትደነብር ፍትወት ሲያስቸግራት ከልቧ
አውጥታ ጉያዋ ውስጥ በሰመመን ስታስገባው፤ በፍቅሩ ወዲያ ወዲህ
ስትንገላታ ኖረች: ነገ ነገን ሲተካ የሷ አምሮትም ከቀን ወደ ቀን ሲጨምር ከስኬ ወንዝ አሸዋ ጭራ ጭሮሽ ውሃ ስትቀዳ ያ በውስጧ
አብሯት ያደገው ጀግና ድንገት ሽቅብ ወደ ቡስካ ተራራ ሲወጣ አየችው ደነገጠች! ግራ ገባት: “አያ ደልቲ! እሱ ኮ ነው…..የኔው.." ብላ ቀባጠረች። ጓደኞችዋ ሳቁባት አላየቻቸውም።
አልሰማቻቸውም እሱም የለም: ጫካው ሰወረው። እሷ ግን ታየዋለች።አካሉ ቢሄድ እሱ ልቧ አለ፡ አወጣችው አየችው ወደደችው! አቀፈችው...
ይእ! እሰይ እሱንም ከውስጤ ያለውንም አየሁት..." ቀና ብላ ፀሐይን ሰማዩን... ቦርጆን አመሰገነች።
“እይ! እሽ ምን ልሁን! እሽ ምን ላርገው.." ጓደኞቿ እንደገና ሳቁባት። ጆሮዋ ግን አይሰማም አይኗ አያይም... ሁሉም ጀግናዋን ሊዳብሱ ሄደዋል። ውስጧ ያለው የፍቅር ሃይል ለፍንዳታ ተዘጋጀ ተቀባበለ። ሃይሉ ናጣት ወዘወዛት, አሻት... አዞራት አሽከረከራት... ዛፍ ጥላ ስር በደመ ነፍስ ሄዳ አረፈች መረጋጋት ስትጀምር ቡስካ ተራራን ቀና ብላ አየችው: ነይ" አላት። ወሰነች
ለመሄድ ጀግናዋን ጫካ መሃል ለመፈለግ ቆረጠች። ሄደች “አቅጣጫ ያላት ጀልባ ንፋሱም ይረዳታል ይባል የለ አገኘችው::
ደልቲ ዳራ የቀዳችለትን ሸፈሮ ቡና አራት ጊዜ እየተቀበለ ጠጣና ሾርቃውን ከፊት ለፊቱ አስቀመጠው: በሐመር ደንብ የጠጡበትን እቃ ማቀበል ጨምሩልኝ ሲሆን ማስቀመጥ ግን በቃኝ ማለት ነው:: ዳራ ለራሷ መጠጣት ጀመረች። በሐመር ባሀል ወንድ በሐመር ባሀል ወንድ
አንበሳ ነው ሴቷ አንበሳ መጀመሪያ ግዳይ ትጥላለች: ወንዱ ጎፈር
አንበሳ ግን ቀድሞ ይባርካል ይበላል፤ ይጠግባል፤ ተንጎማሉ ሄዶ
ለመከታነቱ ተዘጋጅቶ ይጋደማል። ሴቷ አንበሳና ደባሎችዋ የጎፈር
አንበሳው ግሣት ደህንነታቸው ህልውናቸው ነው... እሱ ሲጠግብ
እሱ ሲጠነክር ይረካሉ። ዳራም አንበሳዋ ከጠገበ በኋላ ጭብጦዋን በላች ቡናዋን ጠጣች ከዚያ እቃውን ሸካከፈች።
፡
፡
#ክፍል_ስድስት
፡
፡
#በፍቅረማርቆስ_ደስታሰ
መጀመሪያ የደራረቀ እንጨትና ግንድ ቀጥላ ለጉልቻ የሚሆን ሦስት ድንጋይ አቅርባ እሳት አቀጣጠለችና ውሃ የያዘውን
ቶፋ ወደ አንደ በኩል ዘንበል አድርጋ ጣደችው ከዚያ በለሻ እንዲበላ ስታቀብለው “አንችስ ብይ እንጂ ተወተቱም ጠጭ…"
አላት ጭብጦውን እያላመጠ።
ይእ! ይልቅ አታስቀምጠው ጠጣው። የኔ በኋላ ይደርሳል“ ብላ በጨንዋዛ ቅጠል የተቋጠረውን ሽፈሮ ቡና ፈታ በሚቆለቆሰው
እሳት በመቅጃው የቅል ጭልፋ ዙሪያ ትጉልጉል የሚለውን እንፋሉት እንዳያቃጥላት ተጠንቅቃ የቡና ገለባውን ጨመረች:
ሰማዩ ላይ እንደ ጨሌና ዛጎል ከዋክብት ሆጨጭ ብለዋል። በስተ ሰሜን በኩል ደግሞ ብናኝ ዳመና አቅፎ የያቸው ከዋክብት
ብልጭ ድርግም... ይላሉ: የምሽት በራሪዎች የሌሊት ወፍ ጉጉት የማታ ተረኞች ሆነው ወዲህ ወዲያ ይበራሉ: ጅብ ይጮሃል
አንበሳው ያገሳል... ጦጣና ዝንጀሮ ፀጥ ብለዋል: ጉሬዛዎች ግን እንደ ዶሮ ሰዓት እየጠበቁ “ጉርር ጉርር. ጉርርርር..." እየተቀባበሉ ያውካኩና ጸጥ እረጭ ይላሉ።
ዳራና ደልቲ በሚነደው የሳት ወላፈን እሷ አንድ ጉልበቷን
አጥፋ መሬት ላይ አጋድማ፧ ሌላውን ጉልበቷን አጥፋ አቁማ አልፎ አልፎ እንጨቱን ቆስቆስ እያደረገች አይኖችዋን ጨለማው ውስጥ ተክላለች።
ደልቲ በርኮታው ላይ ቁጭ ብሎ የአባቱን ከዋክብት እንደ እሳት እየተንቦገቦጉ ቁልቁል ተወርውረው የሚጠፉትን “ሚቲዎሮች”
እያየ ያስባል።
በሁለቱ መካከል ንግግር የለም:: ፀጥታ ሆኗል: በሐመር ባህል የቡና ሥነሥርዓት እርጋታና ፀጥታ የሰፈነበት ነው:: ህፃናት
እንኳን ይህን ስለሚያውቁ ቡረቃቸውን ገተው ያደፍጣሉ። ሴቷ ወንዱ ሽማግሌው ከራሳቸው
ጋር የሚነጋገሩበት ራሳቸውን የሚመዝኑበት አደብ የሚገዙበት በጎና እኩይ ተግባራቸውን የሚፈትሹበት... ነው የቡና ሥነ ሥርዓት ለሐመሮችሽማግሌ
ትናንትን የሚያደንቅበት ዛሬን የሚያመሰግንበት ነገን በተስፋ የሚጠባበቅበት ግለሰቡ ለማህበረሰቡ ደህንነት ሰላምን፡ ጥጋብን የሚመኝበት የአባት የአያት ደንብ ወደ ልጅ የሚሸጋገርበት ጠላትና ወዳጅ ጠንቅቆ የሚታወቅበት ምላስ አጥራ ህሊና ገዝፎ መግባባት የሚመጣበት ነው የቡና ሥነ ሥርዓት። ይህ የቡና ሥነሥርዓት ለህፃን ለወጣት ለአዋቂ ለሽማግሌ ለእንግዳ ክፍት ነው። ያሻው ሁሉ ይሳተፋል እድሜና ደረጃውን ጠብቆ ይዳረሳል። የሐመር በር መዝጊያ የለውም። የሐመር ሕይወት ጓዳ የለውም፡ የሐመር ማህበረሰብ “ከሌላው ኪስ ወስደህ የኔን ኪስ ሙላ በሚል ስግብግብነት ምኞት ላይ አልተመሰረተም።
ደስታ ችግር ጦርነት... የጋራ ነው: የአንዱ ምርኩዝ ሌላው ነው: ግለሰብ ህብረተሰብን አይረሳም። ህብረተሰቡም ግለሰቡን
አይጥልም ያሳድገዋል ሃብት ያካፍለዋል ይድረዋል ለጀግንነቱም
ያሞግሰዋል...
ስሰዚህ ደልቲና ዳራ ምንም እንኳ ጫካ መሃል ብቻቸውን ቢሆኑም ህሊናቸውና አካላቸው ግን በባህላቸው ደንብና ሥርዓት
የተገነባ ነው: ፀጥታው ተጠብቆ ዝምታው ሰፍኖ እሱም ሆነ እሷ ትናንትን ቃኝተው ዛሬን አስታውሰው ነገን ሲያልሙ በሐሳብ
ተውጠው ቆዩ።
ከዚያ ዳራ ሾርቃውን ጠረግ ጠረግ አረገችና የቅል ማንኪያውን አንስታ ቶፋው ውስጥ ጨምራ ከቡናው ሁለቴ ቀድታ ሰጠችው ደልቲ ቡናውን ለማብረድ ግራና ቀኝ ጎለል አደረገና ፉት ብሎ “ፕስስ ፕስስ.." እያለ ወደ ምስራቅ ምዕራብና ወደ መሬት የሸፈሮ ቡናውን አርከፍክፎ- “የአባቴ ሰማይ ዝናብ ይጣል በሽታዎች ከሐመር ምድር ይጥፉ፤ ከብቶች ፍየሎች በጎች
አያገሱ በሰላም ይግቡ ይውጡ..." ብሎ መረቀና ወደ ዳራ ዞሮ ቡናውን ፉት ብሎ “ፕስስ..” አለና ሽፈሮ ቡናውን አርከፈከፈባት፡
ዳራ ደንገጥም አፈርም ሳትል አይኗን ከወረወረችበት
ሳትመልስ በሃሣብ እንደሰመጠች
“..ተባረኪ... ዘርሽን ያብዛው የአባትሽ የሐመር ምድር የልጆችሽ መቦረቂያ ይሁን... የባልሽ ጥገት ይብዛ" ብሎ መረቃትና ቡናውን በፀጥታ መጠጣት ጀመረ።
ሰረቅ አድርጋ አየችው: በውስጧ እንደ ህፃን የሚላወሰው እሱ ነው ከፊት ለፊቷም የተቀመጠው እሱ ነው፡ ፍቅር የሰጣት የመረቃት እሱ ነው። ስለሱ ያላትን ስሜት አሁንም በእርግጠኝነት አጤነች ስለ ጀግናው የሚባለውንም አስታወሰች።
ጥጃና ፍየል ስትጠብቅ ወንዶች የድሜ ጓደኞችዋ እነሱ ጠመንጃ እያሉ እንጨት ቆርጠው እየተሸከሙ እንደ ጥይት ዳውላ እየወረወሩ ይሄ ከብት የኔ ያ እርሻ የኔ... እየተባባሉ ሲጫወቱ። እሷም የእድሜ እኩዮችዋ ከሆኑት ልጃገረዶች ጋር ከከስኬ ወንዝ
የጭሮሽ ውሃ እየቀዱ እንጨት እየለቀሙ, ልጅ እያቀፉ... ሲጫወቱ
ይቆዩና ጫካው መሃል ሚስትና ባል ሲባባሉ ቆይተው ዘፈን ሲጀምሩ
ስለ ሐመር ተራራ ስለ ሐመር ሰማይና ምድር... ስለከብቶች ሲያዜሙ ይቆዩና የሐመር ጀግኖችን ህፃናቱ ሲያወድሱ የደልቲ ስም የደልቲ ጀግንነት... ይነሳል። ወንዶች ህፃናት “እኔ ነኝ እሱ እኔ ነኝ
ሲባባሉ እሷም ከሌሎች የእድሜ ጓደኞችዋ ጋር “ደልቲን የሆነውን ወንድ እኔ ነኝ የማገባው ! እኔ ነኝ የማገባው" ሲባባሉ አንዳንዴ ሁለት አንዳንዴ ሦስት እየሆኑ ሲያገቡት የነበረው የልጅነት ዘመኗ
ታወሳት። እንዲህ ዳሌዋ ሰፍቶ ጡቶችዋ አጎጥጉጠው ሰውነቷ
አምሮ ባለበት የቡረቃ ዘመኗ ያ ስም አብሯት አደገ:: የዚያ ጀግና መግነጢሳዊ የፍቅር ሃይል በውስጧ እየተገለባበጠ ሲያስጨንቃት ኖረ።
ገበያ ስታየው ትንፋሽዋ ቁርጥ ያለባት ሲመስላት ስሙ ሲነሳ እንደ አውሬ ስትደነብር ፍትወት ሲያስቸግራት ከልቧ
አውጥታ ጉያዋ ውስጥ በሰመመን ስታስገባው፤ በፍቅሩ ወዲያ ወዲህ
ስትንገላታ ኖረች: ነገ ነገን ሲተካ የሷ አምሮትም ከቀን ወደ ቀን ሲጨምር ከስኬ ወንዝ አሸዋ ጭራ ጭሮሽ ውሃ ስትቀዳ ያ በውስጧ
አብሯት ያደገው ጀግና ድንገት ሽቅብ ወደ ቡስካ ተራራ ሲወጣ አየችው ደነገጠች! ግራ ገባት: “አያ ደልቲ! እሱ ኮ ነው…..የኔው.." ብላ ቀባጠረች። ጓደኞችዋ ሳቁባት አላየቻቸውም።
አልሰማቻቸውም እሱም የለም: ጫካው ሰወረው። እሷ ግን ታየዋለች።አካሉ ቢሄድ እሱ ልቧ አለ፡ አወጣችው አየችው ወደደችው! አቀፈችው...
ይእ! እሰይ እሱንም ከውስጤ ያለውንም አየሁት..." ቀና ብላ ፀሐይን ሰማዩን... ቦርጆን አመሰገነች።
“እይ! እሽ ምን ልሁን! እሽ ምን ላርገው.." ጓደኞቿ እንደገና ሳቁባት። ጆሮዋ ግን አይሰማም አይኗ አያይም... ሁሉም ጀግናዋን ሊዳብሱ ሄደዋል። ውስጧ ያለው የፍቅር ሃይል ለፍንዳታ ተዘጋጀ ተቀባበለ። ሃይሉ ናጣት ወዘወዛት, አሻት... አዞራት አሽከረከራት... ዛፍ ጥላ ስር በደመ ነፍስ ሄዳ አረፈች መረጋጋት ስትጀምር ቡስካ ተራራን ቀና ብላ አየችው: ነይ" አላት። ወሰነች
ለመሄድ ጀግናዋን ጫካ መሃል ለመፈለግ ቆረጠች። ሄደች “አቅጣጫ ያላት ጀልባ ንፋሱም ይረዳታል ይባል የለ አገኘችው::
ደልቲ ዳራ የቀዳችለትን ሸፈሮ ቡና አራት ጊዜ እየተቀበለ ጠጣና ሾርቃውን ከፊት ለፊቱ አስቀመጠው: በሐመር ደንብ የጠጡበትን እቃ ማቀበል ጨምሩልኝ ሲሆን ማስቀመጥ ግን በቃኝ ማለት ነው:: ዳራ ለራሷ መጠጣት ጀመረች። በሐመር ባሀል ወንድ በሐመር ባሀል ወንድ
አንበሳ ነው ሴቷ አንበሳ መጀመሪያ ግዳይ ትጥላለች: ወንዱ ጎፈር
አንበሳ ግን ቀድሞ ይባርካል ይበላል፤ ይጠግባል፤ ተንጎማሉ ሄዶ
ለመከታነቱ ተዘጋጅቶ ይጋደማል። ሴቷ አንበሳና ደባሎችዋ የጎፈር
አንበሳው ግሣት ደህንነታቸው ህልውናቸው ነው... እሱ ሲጠግብ
እሱ ሲጠነክር ይረካሉ። ዳራም አንበሳዋ ከጠገበ በኋላ ጭብጦዋን በላች ቡናዋን ጠጣች ከዚያ እቃውን ሸካከፈች።
👍37👎1
#እህቴ_ባትሆኚ_አገባሽ_ነበረ
፡
፡
#ክፍል_ስድስት
፡
፡
፡
#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ
፡
///
ከሀያ ቀን በኃላ ፤ስለእሷ ማሰብ ካቆምኩ በኃላ ...ኦልሞስት ከረሳኋት በኃላ ድንገት ተከሰተች። እለቱ ቅዳሜ ነው ፤ቅዳሜ ለአብዛኛው ሰራተኛ የደመቀች ቀን ነች። ፈገግታ የሚፈስባት ..ሙዚቃ የሚንቆረቆርባት..የዳንስ ጥበብ የሚጠበብባት ወሲብ የሚወሰብባት በስራ ሳይሆን በመዝናናት ብዛት የሚደከምባት...በወጪ ብዛት ኪስ የሚታጠብባት አዲስ ፍቅረኛ የሚጠባበስባት ክንድ ላይ ያለ ፍቅረኛ ድንገት ሾልኮ የሚሰወርበት… የታሪክ መፃፊያ ቀን ነች።
ከቅዳሜው የተትረፈረፈው ወደ እሁድ ይዘዋወራል።
ያው ከላይ በገለፅኩላችሁ ምክንያት ለእኛ ለአስተናጋጆች ዋና የስራ ቀናችን ነው።እና በዛው ልክ ወከባ አለ፡፡ ከአንዱ ወደሌላው ጠረጴዛ መስፈንጠር ..ከአንዱ ተስተናጋጅ ትዕዛዝ ወደሌላው...ብቻ ከባድ ግን ደግሞ ወሳኝ ቀን ነች።ከባድ ያልኩት የስራውን ጫና ፤ የተስተናጋጆቹ ወከባ፤ የትዕዛዝ መደበላለቅ፤ የሰከራሙ ትንኮሳ፤የሂሳብ መጉደል የመሳሰሉትን ጫና አስቤ ነው። ወሳኝ ያልኩት ሳምንቱን ሙሉ የማናገኘውን ቲፕ እና መሠል ተጨማሪ ገቢ የምናገኝበት ቀን ስለሆነ ነው።ዛሬም እስከ ምሽቱ ሶስት ሰዓት እንደወትሮ የተለመደ ስራዬን እየሠራሁ ሳለ ጋሼ አስጠረኝ።
‹‹አቤት ጋሼ፡፡››
‹‹ወንበርህን ለሌሎቹ አስረክብና ቪ.አይ.ፒ ቁጥር 4 ያሉትን እንግዶች አስተናግድ"
ፈጠን ብዬ ‹‹እሺ ጋሼ "አልኩና በደቂቃ ውስጥ ወንበሬን ለጓደኞቼ አስረክቤ ወደታዘዝኩት ቦታ ሄድኩ ፡፡ በእኛ ሆቴል ስድስት የቪ.አይ.ፒ ቦታዎች አሉ።ልክ እንደትያትር ቤት በሆቴሉ ሰፊ አዳራሽ አራቱ ኮርነሮች ላይ ከፍ ብሎ የተገነብ ሲሆን ወደ እዛ የሚወጣው ከሆቴሉ ሳይገባ በውጭ በኩል ባለ እስቴር ነው።የሁሉም መግቢያ ለየብቻ ሲሆን ቀጥታ በጓሮ በር ገብቶ መልሶ በጎሮ መውጣት ያስችላል..የቤቱ ዙሪያ በጠንካራ ኮንክሪት ግድግዳ የተገነባ ሲሆን አንድ ጎን ማለት ወደሆቴሉ ያለው ጥይት በማይበሳው መስታወት ሙሉ በሙሉ የተሸፈነ ነው ..፡፡መስታወቱ እታች ሆቴል ያለውን እንቅስቃሴ ጭፈራውንና እያንዳንድን እድምተኛ ቁልጭ አድርጎ ሲያሳይ ከሆቴል ወደላይ ግን ድፍን ጥቁር መስታወት ግድግዳ ብቻ ነው የሚታየው።ክፍሉ በጣም ዘመናዊ፤ ምቹ ሶፋዋች እና እንደ አማራጭ የባለጌ ወንበሮች ከምቹ ባልኮኒ ጋር ተገጥሞላቸዋል
መብራቶቹም በምርጫ የሚቀያየሩ ተደርገው የተሠሩ ሲሆን ሙዚቃን በተመለከተ ቀጥታ እታች የሚለቀቀው በጥራት የሚመጣበት ወይም ያንን ዘግቶ እዛው የራሳቸውን የተመረጠ ሙዚቃ የሚጠቀሙበት አማራጭ አለው። እዛ ክፍል …ተጠቃሚዎች ወይ በራፍ ላይ ቆሞ ወይ ውስጥ ተቀምጧ የሚያስተናግዳቸው የብቻቸው አስተናጋጅ ይመደብላቸዋል። የተለየ ፕራይቬሲ ከፈለጉ ደግሞ አስተናጋጅ ከክፍሉ ውጭ ይሆንና ልክ መጥሪያውን ተጭነው ከመድገማቸው በፊት ተስፈንጥሮ በመግባት ትዛዛቸውን ተቀብሎ የሚፈልጉትን ያመጣላቸዋል።
ይህን ክፍል የሚጠቀሙት ለደህንነታቸው ወይም ለስማቸው አብዝተው የሚጨነቁ ትላልቅ የቢዝነስ ሰዎች፤ዝነኞችና እና ባለስልጣኖች ናቸው። ቢሆንም ለሁሉም አገልግሎቶች ከመደበኛው ከአራት እጥፍ በላይ ያስከፋላል ።አስተናጋጅም ብዙን ጊዜ ጠቀም ያለ ጉርሻ ያገኛል።እናም ሁሉም እዚህ ቦታ ሲመደብ በደስታና በፈንጠዝያ ነው የሚቀበለው።
ደረስኩ ..በራፋን እንደመቆርቆር አደረኩና ገፋ አድርጌ ስከፍት ደነገጥኩ...፡፡እንደጠበቅኩት ቀለል ያሉ ሰዎች አይደሉም የገጠሙኝ። እርግጥ ሴቲቷ ጀርባዎን ሰጥታኝ የተቀመጠች በመሆኑ ፊቷ አይታየኝም፡፡ግን ዝንጥ ብላለች።ደማቅ ሰማያዊ ረጅም ቀሚስ፤ መካከለኛ ታኮ ካለው ሰማያዊ ጫማ ጋር አስማምታ ለብሳለች። ፀጉሯ የእውነት የእሷ ከሆነ ውብ መሆኑን በቀላሉ መናገር ይቻላል ፤ወገቧ ላይ ተበትኖ ይታያል .፡፡
.ሰውዬው ከእኔ ፊት ለፊት ናቸው ያሉት ፤ትልቅ ሰው ናቸው።ቆፍጣና ፤ኮስታራና አስፈሪ ..ፀጉራቸው ገብስማ ነው..፡፡ሙሉ ዠንጉርጉር የመከላከያ ልብስ ለብሰዋል።ትከሻቸው ላይ አራት ኮከብ ወደጎን ተደርድሯል።መቼስ በዚህ አለባበስ የሆነ ስብሰባ ላይ ወይም ወሳኝ ሀገራዊ ተልዕኮ ላይ አምሽተው ከጊዜ መጣበብ የተነሳ ወደቤታቸው ጎራ ብለው ለመቀየር ሳይችሉ ቀጥታ መተው ነው እንጂ ይሄ የክብር ልብስ ቦታው አይመስለኝም"በውስጤ አጉረመረምኩ ...
እንደምንም እራሴን አረጋግቼ ወደፊት የተወሰነ እርምጃ ጠጋ አልኩና ‹‹ጌታዬ የጎደለ ነገር አለ?››ብዬ ጠየቅኳቸው፡
"ሚበላ ምን አላችሁ?"ጎርናና እና ሻካራ ድምፅ...እኚ ጄኔራልማ እቤታቸው ልጆቻቸውና የልጅ ልጆቻቸውን አስቀምጠው ነው ከዚህች ኮረዳ ጋር የሚማግጡት› በሆዴ አማኋቸው፡፡እስቲ አሁን ምን አውቄ ነው ለሰከንድ ያየኋቸውን ሰዎዬ ወደማማትና መፈረጅ የገባሁት ብዬ እራሴን ወቀስኩ።
"ጌታዬ ሜኑ ላምጣ"
"አይ አንድ ክትፎ አምጣልን...ክትፎቸው አሪፍ ነው" አለች ሴቲቱ...አሁንም በደበዘዘው ብርሀን ከእኔ በተቃራኒ የዞረ ፊቷ እየታየኝ አይደለም ።ድምፆ ግን የሚነዝር ኃይል ነበረው። የሚያደነዝዝ...በምን ምክንያት ነዘረኝ...?ስለምንስ ውስጤ ተናጠ... ?
"በቃ ጎረምሳው እንዳለችህ አድርግ"አሉኝ ጄኔራሉ ..ንግግራቸው ብቻውን ምሽግ የሚንድ አይነት ነው፤ተስፈንጥሬ ወጣሁ።በተቻለ ፍጥነት በልዩ ሁኔታ ክትፎውን አሰርቼ ይዤ ተመለስኩ።
"የእጅ ውሀ እዚሁ ልታመጣልን ትችላለህ?"ሴቲቱ ነች ጠያቂዋ፡
"ይቻላል እመቤቴ.. አሁን አመጣለሁ"አልኩና በደቂቃ ውስጥ የእጅ ውሀ ይዤ መጣሁ። ተንደርድሬ ሄጄ በክብር ጎንበስ ብዬ ልክ እማማ ኢትዬጰያን እያስታጠብኩ እንደሆነ ኩራት እየተሠማኝ ጄኔራሉን አስታጠብኩና ወደ ሴቲቱ ዞር ስል ፊት ለፊት አይን ለአይን ግጥም ...ምን ተአምር ነው?...ልደሰት ወይስ ልዘን? ላልቅስ ወይስ ልሳቅ ?
ጎንበስ ብዬ እያስታጠብኳት ቢሆንም ግን በደመነፍስ ነው። ድምፅ አውጥቼ ላወራት አልቻልኩም ? አውቅሻለሁ... ጋብዘሺኛል.. እርቃን ገላሽን በዓይኖቼ አይቻለሁ...በጣቶቼ ዳብሼሻለሁ ልላት ፈፅሞ አልቻልኩም።
‹‹አይ የጎረምሳ ነገር....ውሀውን ደፍተህ ጨረስከው እኮ"አሉኝ ጀኔራሉ እንደመሳቅ ብለው። ለካ እሷ መታጠብን ጨርሳ እጇን ብትሰበስብም እኔ ግን አይኔን አይኖቾ ላይ እንደተከልኩ ፈዝዤ ውሀውን ማንጮርጮሬን ቀጥያለሁ...በጄኔራሉ ንግግር ባነንኩና ተስፈንጥሬ ከስራቸው ወደበሩ መራመድ ጀመርኩ።
"በራፋ አካባቢ ነኝ፤ ስትፈልጉኝ መጥሪያውን ተጫኑ ››አልኩና ክፍሉን ዘግቼላቸው ወጣሁ።የእጅ ማስታጠቢያውን አስቀምጬ በረንዳው ላይ ከወዲህ ወዲያ እየተሸከረከርኩ መብሰልሰል ጀመርኩ፡፡
"ፍፅም እንደማታውቀኝ እኮ ነው የሆነችው...ምን አይነቷ ባለጌ ነች?" ከንፈሬን በብስጭት ነከስኩ ..‹‹አንድ ለሊትም ቢሆን እኮ እንዲህ በቀላሉ የሚረሳ ነገር አልነበረንም ያሳለፍነው..? ነው ወይስ ውሽማዋን ፈርታ ነው?››
"ብትፈራ ይፈረድባታል .. ጄኔራሉ እኮ እንኳን በጎናቸው የሸጎጡት ሽጉጥ ተጨምሮበት ይቅርና እንዲሁ ያን ግንባራቸውን ቋጠር ፈታ ሲያደርጉት ያርበደብዳሉ...እኔስ ሀይ ሰላም ነሽ የሚል አጭር ሰላምታ እንኳን ለመስጠት ድፍረት ያጣሁት እሳቸውን ከመፍራት አይደል?።ግን ውሽማዎ ናቸው ነው ያልኳችሁ ..?ያንን በምን አወቅኩ ?አልነገሩኝ...ሲሳሳሙ እንኳን አላየሁም"
የመጥሪያው መንጣረር ከሀሳቤ አናጠበኝ። ፈጥኜ ወደውስጥ ገባሁና መሽቆጥቆጤን ሳልቀንስ "አቤት ጌታዬ"አልኩኝ፡፡
፡
፡
#ክፍል_ስድስት
፡
፡
፡
#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ
፡
///
ከሀያ ቀን በኃላ ፤ስለእሷ ማሰብ ካቆምኩ በኃላ ...ኦልሞስት ከረሳኋት በኃላ ድንገት ተከሰተች። እለቱ ቅዳሜ ነው ፤ቅዳሜ ለአብዛኛው ሰራተኛ የደመቀች ቀን ነች። ፈገግታ የሚፈስባት ..ሙዚቃ የሚንቆረቆርባት..የዳንስ ጥበብ የሚጠበብባት ወሲብ የሚወሰብባት በስራ ሳይሆን በመዝናናት ብዛት የሚደከምባት...በወጪ ብዛት ኪስ የሚታጠብባት አዲስ ፍቅረኛ የሚጠባበስባት ክንድ ላይ ያለ ፍቅረኛ ድንገት ሾልኮ የሚሰወርበት… የታሪክ መፃፊያ ቀን ነች።
ከቅዳሜው የተትረፈረፈው ወደ እሁድ ይዘዋወራል።
ያው ከላይ በገለፅኩላችሁ ምክንያት ለእኛ ለአስተናጋጆች ዋና የስራ ቀናችን ነው።እና በዛው ልክ ወከባ አለ፡፡ ከአንዱ ወደሌላው ጠረጴዛ መስፈንጠር ..ከአንዱ ተስተናጋጅ ትዕዛዝ ወደሌላው...ብቻ ከባድ ግን ደግሞ ወሳኝ ቀን ነች።ከባድ ያልኩት የስራውን ጫና ፤ የተስተናጋጆቹ ወከባ፤ የትዕዛዝ መደበላለቅ፤ የሰከራሙ ትንኮሳ፤የሂሳብ መጉደል የመሳሰሉትን ጫና አስቤ ነው። ወሳኝ ያልኩት ሳምንቱን ሙሉ የማናገኘውን ቲፕ እና መሠል ተጨማሪ ገቢ የምናገኝበት ቀን ስለሆነ ነው።ዛሬም እስከ ምሽቱ ሶስት ሰዓት እንደወትሮ የተለመደ ስራዬን እየሠራሁ ሳለ ጋሼ አስጠረኝ።
‹‹አቤት ጋሼ፡፡››
‹‹ወንበርህን ለሌሎቹ አስረክብና ቪ.አይ.ፒ ቁጥር 4 ያሉትን እንግዶች አስተናግድ"
ፈጠን ብዬ ‹‹እሺ ጋሼ "አልኩና በደቂቃ ውስጥ ወንበሬን ለጓደኞቼ አስረክቤ ወደታዘዝኩት ቦታ ሄድኩ ፡፡ በእኛ ሆቴል ስድስት የቪ.አይ.ፒ ቦታዎች አሉ።ልክ እንደትያትር ቤት በሆቴሉ ሰፊ አዳራሽ አራቱ ኮርነሮች ላይ ከፍ ብሎ የተገነብ ሲሆን ወደ እዛ የሚወጣው ከሆቴሉ ሳይገባ በውጭ በኩል ባለ እስቴር ነው።የሁሉም መግቢያ ለየብቻ ሲሆን ቀጥታ በጓሮ በር ገብቶ መልሶ በጎሮ መውጣት ያስችላል..የቤቱ ዙሪያ በጠንካራ ኮንክሪት ግድግዳ የተገነባ ሲሆን አንድ ጎን ማለት ወደሆቴሉ ያለው ጥይት በማይበሳው መስታወት ሙሉ በሙሉ የተሸፈነ ነው ..፡፡መስታወቱ እታች ሆቴል ያለውን እንቅስቃሴ ጭፈራውንና እያንዳንድን እድምተኛ ቁልጭ አድርጎ ሲያሳይ ከሆቴል ወደላይ ግን ድፍን ጥቁር መስታወት ግድግዳ ብቻ ነው የሚታየው።ክፍሉ በጣም ዘመናዊ፤ ምቹ ሶፋዋች እና እንደ አማራጭ የባለጌ ወንበሮች ከምቹ ባልኮኒ ጋር ተገጥሞላቸዋል
መብራቶቹም በምርጫ የሚቀያየሩ ተደርገው የተሠሩ ሲሆን ሙዚቃን በተመለከተ ቀጥታ እታች የሚለቀቀው በጥራት የሚመጣበት ወይም ያንን ዘግቶ እዛው የራሳቸውን የተመረጠ ሙዚቃ የሚጠቀሙበት አማራጭ አለው። እዛ ክፍል …ተጠቃሚዎች ወይ በራፍ ላይ ቆሞ ወይ ውስጥ ተቀምጧ የሚያስተናግዳቸው የብቻቸው አስተናጋጅ ይመደብላቸዋል። የተለየ ፕራይቬሲ ከፈለጉ ደግሞ አስተናጋጅ ከክፍሉ ውጭ ይሆንና ልክ መጥሪያውን ተጭነው ከመድገማቸው በፊት ተስፈንጥሮ በመግባት ትዛዛቸውን ተቀብሎ የሚፈልጉትን ያመጣላቸዋል።
ይህን ክፍል የሚጠቀሙት ለደህንነታቸው ወይም ለስማቸው አብዝተው የሚጨነቁ ትላልቅ የቢዝነስ ሰዎች፤ዝነኞችና እና ባለስልጣኖች ናቸው። ቢሆንም ለሁሉም አገልግሎቶች ከመደበኛው ከአራት እጥፍ በላይ ያስከፋላል ።አስተናጋጅም ብዙን ጊዜ ጠቀም ያለ ጉርሻ ያገኛል።እናም ሁሉም እዚህ ቦታ ሲመደብ በደስታና በፈንጠዝያ ነው የሚቀበለው።
ደረስኩ ..በራፋን እንደመቆርቆር አደረኩና ገፋ አድርጌ ስከፍት ደነገጥኩ...፡፡እንደጠበቅኩት ቀለል ያሉ ሰዎች አይደሉም የገጠሙኝ። እርግጥ ሴቲቷ ጀርባዎን ሰጥታኝ የተቀመጠች በመሆኑ ፊቷ አይታየኝም፡፡ግን ዝንጥ ብላለች።ደማቅ ሰማያዊ ረጅም ቀሚስ፤ መካከለኛ ታኮ ካለው ሰማያዊ ጫማ ጋር አስማምታ ለብሳለች። ፀጉሯ የእውነት የእሷ ከሆነ ውብ መሆኑን በቀላሉ መናገር ይቻላል ፤ወገቧ ላይ ተበትኖ ይታያል .፡፡
.ሰውዬው ከእኔ ፊት ለፊት ናቸው ያሉት ፤ትልቅ ሰው ናቸው።ቆፍጣና ፤ኮስታራና አስፈሪ ..ፀጉራቸው ገብስማ ነው..፡፡ሙሉ ዠንጉርጉር የመከላከያ ልብስ ለብሰዋል።ትከሻቸው ላይ አራት ኮከብ ወደጎን ተደርድሯል።መቼስ በዚህ አለባበስ የሆነ ስብሰባ ላይ ወይም ወሳኝ ሀገራዊ ተልዕኮ ላይ አምሽተው ከጊዜ መጣበብ የተነሳ ወደቤታቸው ጎራ ብለው ለመቀየር ሳይችሉ ቀጥታ መተው ነው እንጂ ይሄ የክብር ልብስ ቦታው አይመስለኝም"በውስጤ አጉረመረምኩ ...
እንደምንም እራሴን አረጋግቼ ወደፊት የተወሰነ እርምጃ ጠጋ አልኩና ‹‹ጌታዬ የጎደለ ነገር አለ?››ብዬ ጠየቅኳቸው፡
"ሚበላ ምን አላችሁ?"ጎርናና እና ሻካራ ድምፅ...እኚ ጄኔራልማ እቤታቸው ልጆቻቸውና የልጅ ልጆቻቸውን አስቀምጠው ነው ከዚህች ኮረዳ ጋር የሚማግጡት› በሆዴ አማኋቸው፡፡እስቲ አሁን ምን አውቄ ነው ለሰከንድ ያየኋቸውን ሰዎዬ ወደማማትና መፈረጅ የገባሁት ብዬ እራሴን ወቀስኩ።
"ጌታዬ ሜኑ ላምጣ"
"አይ አንድ ክትፎ አምጣልን...ክትፎቸው አሪፍ ነው" አለች ሴቲቱ...አሁንም በደበዘዘው ብርሀን ከእኔ በተቃራኒ የዞረ ፊቷ እየታየኝ አይደለም ።ድምፆ ግን የሚነዝር ኃይል ነበረው። የሚያደነዝዝ...በምን ምክንያት ነዘረኝ...?ስለምንስ ውስጤ ተናጠ... ?
"በቃ ጎረምሳው እንዳለችህ አድርግ"አሉኝ ጄኔራሉ ..ንግግራቸው ብቻውን ምሽግ የሚንድ አይነት ነው፤ተስፈንጥሬ ወጣሁ።በተቻለ ፍጥነት በልዩ ሁኔታ ክትፎውን አሰርቼ ይዤ ተመለስኩ።
"የእጅ ውሀ እዚሁ ልታመጣልን ትችላለህ?"ሴቲቱ ነች ጠያቂዋ፡
"ይቻላል እመቤቴ.. አሁን አመጣለሁ"አልኩና በደቂቃ ውስጥ የእጅ ውሀ ይዤ መጣሁ። ተንደርድሬ ሄጄ በክብር ጎንበስ ብዬ ልክ እማማ ኢትዬጰያን እያስታጠብኩ እንደሆነ ኩራት እየተሠማኝ ጄኔራሉን አስታጠብኩና ወደ ሴቲቱ ዞር ስል ፊት ለፊት አይን ለአይን ግጥም ...ምን ተአምር ነው?...ልደሰት ወይስ ልዘን? ላልቅስ ወይስ ልሳቅ ?
ጎንበስ ብዬ እያስታጠብኳት ቢሆንም ግን በደመነፍስ ነው። ድምፅ አውጥቼ ላወራት አልቻልኩም ? አውቅሻለሁ... ጋብዘሺኛል.. እርቃን ገላሽን በዓይኖቼ አይቻለሁ...በጣቶቼ ዳብሼሻለሁ ልላት ፈፅሞ አልቻልኩም።
‹‹አይ የጎረምሳ ነገር....ውሀውን ደፍተህ ጨረስከው እኮ"አሉኝ ጀኔራሉ እንደመሳቅ ብለው። ለካ እሷ መታጠብን ጨርሳ እጇን ብትሰበስብም እኔ ግን አይኔን አይኖቾ ላይ እንደተከልኩ ፈዝዤ ውሀውን ማንጮርጮሬን ቀጥያለሁ...በጄኔራሉ ንግግር ባነንኩና ተስፈንጥሬ ከስራቸው ወደበሩ መራመድ ጀመርኩ።
"በራፋ አካባቢ ነኝ፤ ስትፈልጉኝ መጥሪያውን ተጫኑ ››አልኩና ክፍሉን ዘግቼላቸው ወጣሁ።የእጅ ማስታጠቢያውን አስቀምጬ በረንዳው ላይ ከወዲህ ወዲያ እየተሸከረከርኩ መብሰልሰል ጀመርኩ፡፡
"ፍፅም እንደማታውቀኝ እኮ ነው የሆነችው...ምን አይነቷ ባለጌ ነች?" ከንፈሬን በብስጭት ነከስኩ ..‹‹አንድ ለሊትም ቢሆን እኮ እንዲህ በቀላሉ የሚረሳ ነገር አልነበረንም ያሳለፍነው..? ነው ወይስ ውሽማዋን ፈርታ ነው?››
"ብትፈራ ይፈረድባታል .. ጄኔራሉ እኮ እንኳን በጎናቸው የሸጎጡት ሽጉጥ ተጨምሮበት ይቅርና እንዲሁ ያን ግንባራቸውን ቋጠር ፈታ ሲያደርጉት ያርበደብዳሉ...እኔስ ሀይ ሰላም ነሽ የሚል አጭር ሰላምታ እንኳን ለመስጠት ድፍረት ያጣሁት እሳቸውን ከመፍራት አይደል?።ግን ውሽማዎ ናቸው ነው ያልኳችሁ ..?ያንን በምን አወቅኩ ?አልነገሩኝ...ሲሳሳሙ እንኳን አላየሁም"
የመጥሪያው መንጣረር ከሀሳቤ አናጠበኝ። ፈጥኜ ወደውስጥ ገባሁና መሽቆጥቆጤን ሳልቀንስ "አቤት ጌታዬ"አልኩኝ፡፡
👍56❤2👎2👏1
#የዘርሲዎች_ፍቅር
፡
፡
#ክፍል_ስድስት
፡
፡
#በፍቅረማርቆስ_ደስታ
ካርለት ድንኳናን ዘግታ ስትፅፍ የሰው ኮቴ የሰማች መሰላትና ጆሮዋን አቁማ አዳመጠች
"ካርለት?"
"የስ" ብላ ቶሎ በማስተካከል "ዬ! አለች - እንደ ሐመር ልጃገረዶችı ካርለት የጠራት ሰው ማን እንደሆነ አውቃዋለች
ደልቲ ነው ቀብራራው ጀግና የድንኳኗን ዚፕ ከፍታ ፈገግ ብላ አየችው" ሰውነቱ በአኖ (ከኦሞ ወንዝ ዳር በመጣ የተላቆጠ አፈር)
ተዥጎርጉሯል፥ ጴሮው (መሃል አናቱ ላይ ባለው ጌጥ) ላይ የተሰካው
የቀጭኔ ላባ በንፋስ ይርገበገባል ... እሱ ግን ፊቱን ዞሮ በርኮታው
ላይ ቁጭ ብሎ ጥርሱን በልምጭ ይፍቃል"
አንቺ ንብ አደለሽ
ምነው ቀፎሽን ዘጋግተሽ መቀመጥሽ
"ደልቲ ንፋሱ: ልጆችም
እንዳያስቸግሩኝ አለችው
ፈገግ ብላ እያየችው" እሱ ግን መልሷ አልተዋጠለትም ይህች ሰው! ነፋስና ልጅ የምትጠላ ምን ልትወድ ነው እህ! ብሎ ቆሽቱ
እያረረ ሃሣቡን ሳይናገር ከታጠቀው ዝናር አንድ ቀላህ አውጥቶ
ውታፏን ከፈተና በአውራ ጣቱ ጀርባ የትንባሆ ዱቄት ፈሰስ አድርጎ ጎንበስ ብሎ በአፍንጫው ቀዳዶች ሞዠቅ ሞዠቅ አድርጎ ሽቅብ ማገና በዐይኖቹ እንባ ፍጭጭ ብሎ ደጋግሞ ካስነጠሰው በኋላ
ትንባሆውን ለካርለት አቀበላት በሐመር ሴት ልጅ ትንባሆ መሳቧ ነውር የለውም! በፍቅረኞች መካከል ትንባሆ (ሱረት) መሰጣጣት ደግሞ አንዱ የመግባባታቸው ምልክት ነው።
"ሽማግሎች ለዛሬ ከብት ውጋ ብለውኝ ይኸው በሬዬን ይዠ መጣሁ" አላት ካርለት ትንባሆው ካስነጠሳት በኋላ ምክንያቱን የሰማች ቢሆንም ከእሱ አንደበት ለመስማት ብላ።
"ምነው ምናጠፋህ?" ስትለው መፋቂያውን አኘክ አኘክ አድርጎ ተፋና ረጋ ብሎ፣
"አንች ሰው ምነው ሥርዓት ቢኖርሽ ሴት በየት አገር ነው
የወንድን ጥፋት የምትጠይቀው?" አላት ደልቲ ካርለት እንዲህ
ስታጠፋ ጎንበስ ብላ እግሯን
እንድትይዝ አድርጎ ጡቷን
እንዳይመታ እየተጠነቀቀ ሁለት ሶስት ቀን በባራዛ አርጩሜ ደህና አድርጎ እየገረፈ ቢገራት ልክ እንደ ስልጡን አህያ ትሰግር እንደነበር አስታውሶ እህ! ሽማግሎች እንዳሉትስ በመታረሚያዋ ጊዜ
ስታጠፉ እኔ እንጂ ሌላ ማን ይታዘንበታል! ብሎ አዝኖ ጢቅ አድርጎ ምራቁን ተፋና ጥርሱን ይፍቅ ገባ።
"ጎይቲ ስታለቅስ ነው የምትውል አይተሃት ታውቃለህ?"አለችው ካርለት በጥያቄዋ ጎርጉራ አንድ አዲስ ነገር ባገኝ ብላ።
"ሰማሁ! እኔን እህቴን ምን የከፋ ችግር መጣባት! አዘነ
ደልቲ።
"ለዚህ ምን መፍትሔ አለው ታዲያ?" ስትል ካርለት ደልቲ
ሰረቅ አድርጎ አይቷት
"ምን መፍትሄ ይኖረዋል ሽማግሌ ያለውን መቀበል ነው እንጂ።
"ጎይቲ ከከሎ ጋር ከተጋቡ ወዲህ እኮ ሌላ ወንድ አታውቅም "እንደገና ለዓመል ያህል ሰረቅ አድርጎ እንደዘበት አያት የለበሰችው
ቆዳ የፊተኛው ክፍል ጉያዋ ውስጥ ተሸጉጦ: የቀኝ ጭኗ ውስጥ ክፍል እንደ ጥጥ ንጥት ብሎ ታየው"
"ተታናናሽ ወንድሞቹ ጋርስ አልቀበጠችም?"
"ከሎ ታናሽ ወንድም እኮ የለውም ሁሉም የእሱ ታላላቆች ናቸው"" ስትለው ታናሽ ወንድም እንደሌለው እያወቀ የረሳበት ምክንያት እየገረመው
"ተዘመዱ ወንዶችስ ጋር?" ካርለት የሰጎን ላባ የሰካበት ጴሮ የተተለተለውን ሳንቃ ደረቱን እንደ አቦ ሸማኔ ቀጠን ያለ ወገቡን አይታ ምራቋን ከምላሷ ስር መጣ ዋጠችና,
"ከማንም ጋር አልቀበጠችም ካለ ከሎ በቀር" አለችው
"እህ!" ሲል ካርለት ቀጥሎ የሚለውን ለመስማት ጆሮዋን መዘዘች እሱ ግን ጭራሽ ያልጠበቀችውን ጥያቄ
"የምጠጣው ውሃ ትሰጭኝ?" አለ ከኮዳዋ በኩባያ ቀድታ ውሃ
ስትሰጠው ቀና ብሎ አይቷት
"እሱን አንች ጠጭው፤ ለኔ በሾርቃ ስጭኝ" አላት ካርለት ውሃ ለማምጣት ሄደች ደልቲ አረማመዷን÷ ዳሌዋን ወገቧን ከኋላዋ የሚወናወነውን ቆዳዋን ጥርሱን እየፋቀ አየና ምራቁን ጢቅ አድርጎ ተፋና የበረቱ ከብቶች ቀለማቸው የተለያዬ ነው ቀይ፥
ዳልቻ: ነብርማ: ነጭ የካርለትም ቀለሟ ነጭ መሆኑ ሚስቶቹን
እንደ ከብቶቹ ቀለም ማሳመሩን ሲያስብ የደስታ ስሜት ተሰማው መልሶ ደግሞ የሐመር ልጃገረዶች እንዳለቁ ሁሉ ከዚች አግድም አደግ ጋር ቢቀርብኝስ ብሎ አሰበ አንዴ ግን አገባሻለሁ ብሏል1
ስለዚህ ቃሉን ማጠፍ አልፈለገም ግዴለም አገባታለሁ ድምጿ ግን
ምነው ተዛሬ ነገ ቃናው አይጣፍጥ? ብልግናዋና ድምጿ እንጂ ሴትነቷስ እያለ ሲያስብ ካርለት ውሃ በሾርቃ ይዛለት ብቅ አለች
ከርቀት እያያት ደሞ ደህና ገብሮ የነበረው ሰውነቷ እንደ ምስጥ ንጉስ ተመልሶ ለሰለሰ እያለ ሲያስብ ካርለት ሰው ጠርቷት
ዘወር ስትል የጀርባዋ ሰንበር ታየው ከሎ ከብት ሲዘል የተገረፈችው"
ደልቲ ትንሽ ፈርጠም ብሎ ሳቅ አለ ካርለት
አላየችውም ትዝ አለው ስትገረፍ ሰውነቷ የተንቀጠቀጠው ወድቃ
የተዘረረችው
ባለጌ! ብሎ ተቆጨና መልሶ ደግሞ አዘነላት ጀርባዋ ላይ
ያሉት የግርፊያ ሰንበሮች ጥቂት ናቸው ለሐመር ልጃገረድ ደግሞ
የግርፊያ ሰንበር ሌላው ውበቷ ሲሆን ዳንስ ቦታና ጫካ ውስጥ ወንዱ
እንደ አኮርዲዎን መጫወቻ ሰንበሮቹን በጣቱ እየነካካ የፍቅረኛውን የፍቅር ቅላፄ በማስተካከል የጋራ የፍቅር ስሜት የሚፈጥሩበት ነው
ሴቷና ወንዱ
በልጃገረድ ጀርባ ላይ ባለ የግርፊያ ሰንበር ላይ ሻካራ የእጅ ጣት ጫፎችን ማንቀሳቀስ ትናጋው በፍቅረኛው ምላስ የተነካ ያህል በስሜት ንዝረት መላ ሰውነቱ ያረግዳል ከዚህ በተጨማሪ ደግሞ
የግርፊያ ሰንበሯ ጀርባዋ ላይ የበዛ ዘመደ ብዙ' ካነሰ ደግሞ ዘመደ ትንሽ ናት ይባላል ብዙ ጊዜ ልጃገረዶች እርስ በርስ
ስለዚህ ሲጨዋወቱ
ይእ! ይሄ ሁሉ ማን ሲዘል የተገረፍሽው ነው? ተብላ
የተጠየቀች እንደሆነ እጅዋን አዙራ ጀርባዋን እየዳሰሰች
ይእ! ይሄ የባልዳምቤ
ይሄ የሸረምቤ ይሄ የላሎምቤ …እያለች ትዘረዝራለች ልጃገረዷ በእነዚህ ሁሉ ዘመዶችዋ ስትፎክርና ሳትፈራ ስትገረፍ ያያት ደግሞ ስንትና ስንቱ ወንድ ተመኝቷታል ከስንቱ ጋርስ ቀብጣለች ሊያገባት የፈለገውስ እንዴት እንደሚበዛ መገመቱ አይቸግርም አንድ
የሐመር ወንድ ደግሞ ሌላው የተመኛትን ያፈቀራትን የራሱ አድርጎ ከማግባት የበለጠ ትልቅ
ክብር የለም በሐመር የጋብቻ አለም።
ካርለት ግን የተገረፈችው ለአንድ ቀን ብቻ ነው፤ የዛን ቀንም ግረፉኝ ብላ አልፎከረችም ስትገረፍም ሰውነቷ እየተንቀጠቀጠ
ስታለቅስ በመጨረሻም ህሊናዋን ስታ ስትወድቅ ምድረ ጎረምሳ ተሳስቆባታል እንጂ ማንም ለፍቅር አልተመኛትም ደልቲ ይህን
አስታውሶ
ወዲህ ወዲያ ስትል እንደ ፍየል ጅራት ስትወናወን እንጂ እሷስ ብትሆን ስንትና ስንት ዘመዶችዋ ከብት ሲዘሉ ብትኖር ኖሮ
የመገረፉ እድል መች ያመልጣት ነበር! እያለ ሲትከነከን ካርለት
አጠገቡ ደርሳ ውሃ የያዘ ሾርቃውን አቀበለችው
እየተጉመጠመጠ ደጋግሞ ተፋና ስምጥጥ አድርጎ ጠጥቶ ባይሮ ኢሜ ብሎ
አመሰገናት እግዜር ይስጥልኝ ለማለት
ካርለት ሾርቃውን
ሾርቃውን ልትመልስ ሄደች ያን ጊዜ ደልቲ ደሙ ፈላ ነደደው ተቀብላ ፈንጠቅ አድርጋ ደፋችውና
ይህች አሳሳች! ብሎ እራሱን ለማረጋጋት እየሞከረ ከመቀመጫው ተነሳ
"ይእ! እህ የታል አያ ደልቲ? አለ አሁን ውሃ ብሎኝ
ሰጥቸው መጣሁ አላልሽኝ?" አለች ጎይቲ ከካርለት ጋር ወደ ድንኳኗ
እየተጠጉ
"ጎይቲ አሁን እኮ እዚህ ቁጭ ብሎ ስናወራ ቆይተን ውሃ ስጭኝ ብሎኝ ሰጥቸው ሾርቃውን መልሼ: አንችን ጠርቸሽ መጣን በዚህ ቅፅበት የት ሄደ?"
"ይእ! እኔን ትጠይቂያለሽ ደሞ ይልቅ አንች ምንሽ ውስጥ ከተትሽው? አያ ደልቲ መቼም ካለ ነገር እንዲህ ሹልክ ብሎ እንደ
ሌባ አይጠፋም ተቀያየማችሁ?"
"ኧረ በጭራሽ"
፡
፡
#ክፍል_ስድስት
፡
፡
#በፍቅረማርቆስ_ደስታ
ካርለት ድንኳናን ዘግታ ስትፅፍ የሰው ኮቴ የሰማች መሰላትና ጆሮዋን አቁማ አዳመጠች
"ካርለት?"
"የስ" ብላ ቶሎ በማስተካከል "ዬ! አለች - እንደ ሐመር ልጃገረዶችı ካርለት የጠራት ሰው ማን እንደሆነ አውቃዋለች
ደልቲ ነው ቀብራራው ጀግና የድንኳኗን ዚፕ ከፍታ ፈገግ ብላ አየችው" ሰውነቱ በአኖ (ከኦሞ ወንዝ ዳር በመጣ የተላቆጠ አፈር)
ተዥጎርጉሯል፥ ጴሮው (መሃል አናቱ ላይ ባለው ጌጥ) ላይ የተሰካው
የቀጭኔ ላባ በንፋስ ይርገበገባል ... እሱ ግን ፊቱን ዞሮ በርኮታው
ላይ ቁጭ ብሎ ጥርሱን በልምጭ ይፍቃል"
አንቺ ንብ አደለሽ
ምነው ቀፎሽን ዘጋግተሽ መቀመጥሽ
"ደልቲ ንፋሱ: ልጆችም
እንዳያስቸግሩኝ አለችው
ፈገግ ብላ እያየችው" እሱ ግን መልሷ አልተዋጠለትም ይህች ሰው! ነፋስና ልጅ የምትጠላ ምን ልትወድ ነው እህ! ብሎ ቆሽቱ
እያረረ ሃሣቡን ሳይናገር ከታጠቀው ዝናር አንድ ቀላህ አውጥቶ
ውታፏን ከፈተና በአውራ ጣቱ ጀርባ የትንባሆ ዱቄት ፈሰስ አድርጎ ጎንበስ ብሎ በአፍንጫው ቀዳዶች ሞዠቅ ሞዠቅ አድርጎ ሽቅብ ማገና በዐይኖቹ እንባ ፍጭጭ ብሎ ደጋግሞ ካስነጠሰው በኋላ
ትንባሆውን ለካርለት አቀበላት በሐመር ሴት ልጅ ትንባሆ መሳቧ ነውር የለውም! በፍቅረኞች መካከል ትንባሆ (ሱረት) መሰጣጣት ደግሞ አንዱ የመግባባታቸው ምልክት ነው።
"ሽማግሎች ለዛሬ ከብት ውጋ ብለውኝ ይኸው በሬዬን ይዠ መጣሁ" አላት ካርለት ትንባሆው ካስነጠሳት በኋላ ምክንያቱን የሰማች ቢሆንም ከእሱ አንደበት ለመስማት ብላ።
"ምነው ምናጠፋህ?" ስትለው መፋቂያውን አኘክ አኘክ አድርጎ ተፋና ረጋ ብሎ፣
"አንች ሰው ምነው ሥርዓት ቢኖርሽ ሴት በየት አገር ነው
የወንድን ጥፋት የምትጠይቀው?" አላት ደልቲ ካርለት እንዲህ
ስታጠፋ ጎንበስ ብላ እግሯን
እንድትይዝ አድርጎ ጡቷን
እንዳይመታ እየተጠነቀቀ ሁለት ሶስት ቀን በባራዛ አርጩሜ ደህና አድርጎ እየገረፈ ቢገራት ልክ እንደ ስልጡን አህያ ትሰግር እንደነበር አስታውሶ እህ! ሽማግሎች እንዳሉትስ በመታረሚያዋ ጊዜ
ስታጠፉ እኔ እንጂ ሌላ ማን ይታዘንበታል! ብሎ አዝኖ ጢቅ አድርጎ ምራቁን ተፋና ጥርሱን ይፍቅ ገባ።
"ጎይቲ ስታለቅስ ነው የምትውል አይተሃት ታውቃለህ?"አለችው ካርለት በጥያቄዋ ጎርጉራ አንድ አዲስ ነገር ባገኝ ብላ።
"ሰማሁ! እኔን እህቴን ምን የከፋ ችግር መጣባት! አዘነ
ደልቲ።
"ለዚህ ምን መፍትሔ አለው ታዲያ?" ስትል ካርለት ደልቲ
ሰረቅ አድርጎ አይቷት
"ምን መፍትሄ ይኖረዋል ሽማግሌ ያለውን መቀበል ነው እንጂ።
"ጎይቲ ከከሎ ጋር ከተጋቡ ወዲህ እኮ ሌላ ወንድ አታውቅም "እንደገና ለዓመል ያህል ሰረቅ አድርጎ እንደዘበት አያት የለበሰችው
ቆዳ የፊተኛው ክፍል ጉያዋ ውስጥ ተሸጉጦ: የቀኝ ጭኗ ውስጥ ክፍል እንደ ጥጥ ንጥት ብሎ ታየው"
"ተታናናሽ ወንድሞቹ ጋርስ አልቀበጠችም?"
"ከሎ ታናሽ ወንድም እኮ የለውም ሁሉም የእሱ ታላላቆች ናቸው"" ስትለው ታናሽ ወንድም እንደሌለው እያወቀ የረሳበት ምክንያት እየገረመው
"ተዘመዱ ወንዶችስ ጋር?" ካርለት የሰጎን ላባ የሰካበት ጴሮ የተተለተለውን ሳንቃ ደረቱን እንደ አቦ ሸማኔ ቀጠን ያለ ወገቡን አይታ ምራቋን ከምላሷ ስር መጣ ዋጠችና,
"ከማንም ጋር አልቀበጠችም ካለ ከሎ በቀር" አለችው
"እህ!" ሲል ካርለት ቀጥሎ የሚለውን ለመስማት ጆሮዋን መዘዘች እሱ ግን ጭራሽ ያልጠበቀችውን ጥያቄ
"የምጠጣው ውሃ ትሰጭኝ?" አለ ከኮዳዋ በኩባያ ቀድታ ውሃ
ስትሰጠው ቀና ብሎ አይቷት
"እሱን አንች ጠጭው፤ ለኔ በሾርቃ ስጭኝ" አላት ካርለት ውሃ ለማምጣት ሄደች ደልቲ አረማመዷን÷ ዳሌዋን ወገቧን ከኋላዋ የሚወናወነውን ቆዳዋን ጥርሱን እየፋቀ አየና ምራቁን ጢቅ አድርጎ ተፋና የበረቱ ከብቶች ቀለማቸው የተለያዬ ነው ቀይ፥
ዳልቻ: ነብርማ: ነጭ የካርለትም ቀለሟ ነጭ መሆኑ ሚስቶቹን
እንደ ከብቶቹ ቀለም ማሳመሩን ሲያስብ የደስታ ስሜት ተሰማው መልሶ ደግሞ የሐመር ልጃገረዶች እንዳለቁ ሁሉ ከዚች አግድም አደግ ጋር ቢቀርብኝስ ብሎ አሰበ አንዴ ግን አገባሻለሁ ብሏል1
ስለዚህ ቃሉን ማጠፍ አልፈለገም ግዴለም አገባታለሁ ድምጿ ግን
ምነው ተዛሬ ነገ ቃናው አይጣፍጥ? ብልግናዋና ድምጿ እንጂ ሴትነቷስ እያለ ሲያስብ ካርለት ውሃ በሾርቃ ይዛለት ብቅ አለች
ከርቀት እያያት ደሞ ደህና ገብሮ የነበረው ሰውነቷ እንደ ምስጥ ንጉስ ተመልሶ ለሰለሰ እያለ ሲያስብ ካርለት ሰው ጠርቷት
ዘወር ስትል የጀርባዋ ሰንበር ታየው ከሎ ከብት ሲዘል የተገረፈችው"
ደልቲ ትንሽ ፈርጠም ብሎ ሳቅ አለ ካርለት
አላየችውም ትዝ አለው ስትገረፍ ሰውነቷ የተንቀጠቀጠው ወድቃ
የተዘረረችው
ባለጌ! ብሎ ተቆጨና መልሶ ደግሞ አዘነላት ጀርባዋ ላይ
ያሉት የግርፊያ ሰንበሮች ጥቂት ናቸው ለሐመር ልጃገረድ ደግሞ
የግርፊያ ሰንበር ሌላው ውበቷ ሲሆን ዳንስ ቦታና ጫካ ውስጥ ወንዱ
እንደ አኮርዲዎን መጫወቻ ሰንበሮቹን በጣቱ እየነካካ የፍቅረኛውን የፍቅር ቅላፄ በማስተካከል የጋራ የፍቅር ስሜት የሚፈጥሩበት ነው
ሴቷና ወንዱ
በልጃገረድ ጀርባ ላይ ባለ የግርፊያ ሰንበር ላይ ሻካራ የእጅ ጣት ጫፎችን ማንቀሳቀስ ትናጋው በፍቅረኛው ምላስ የተነካ ያህል በስሜት ንዝረት መላ ሰውነቱ ያረግዳል ከዚህ በተጨማሪ ደግሞ
የግርፊያ ሰንበሯ ጀርባዋ ላይ የበዛ ዘመደ ብዙ' ካነሰ ደግሞ ዘመደ ትንሽ ናት ይባላል ብዙ ጊዜ ልጃገረዶች እርስ በርስ
ስለዚህ ሲጨዋወቱ
ይእ! ይሄ ሁሉ ማን ሲዘል የተገረፍሽው ነው? ተብላ
የተጠየቀች እንደሆነ እጅዋን አዙራ ጀርባዋን እየዳሰሰች
ይእ! ይሄ የባልዳምቤ
ይሄ የሸረምቤ ይሄ የላሎምቤ …እያለች ትዘረዝራለች ልጃገረዷ በእነዚህ ሁሉ ዘመዶችዋ ስትፎክርና ሳትፈራ ስትገረፍ ያያት ደግሞ ስንትና ስንቱ ወንድ ተመኝቷታል ከስንቱ ጋርስ ቀብጣለች ሊያገባት የፈለገውስ እንዴት እንደሚበዛ መገመቱ አይቸግርም አንድ
የሐመር ወንድ ደግሞ ሌላው የተመኛትን ያፈቀራትን የራሱ አድርጎ ከማግባት የበለጠ ትልቅ
ክብር የለም በሐመር የጋብቻ አለም።
ካርለት ግን የተገረፈችው ለአንድ ቀን ብቻ ነው፤ የዛን ቀንም ግረፉኝ ብላ አልፎከረችም ስትገረፍም ሰውነቷ እየተንቀጠቀጠ
ስታለቅስ በመጨረሻም ህሊናዋን ስታ ስትወድቅ ምድረ ጎረምሳ ተሳስቆባታል እንጂ ማንም ለፍቅር አልተመኛትም ደልቲ ይህን
አስታውሶ
ወዲህ ወዲያ ስትል እንደ ፍየል ጅራት ስትወናወን እንጂ እሷስ ብትሆን ስንትና ስንት ዘመዶችዋ ከብት ሲዘሉ ብትኖር ኖሮ
የመገረፉ እድል መች ያመልጣት ነበር! እያለ ሲትከነከን ካርለት
አጠገቡ ደርሳ ውሃ የያዘ ሾርቃውን አቀበለችው
እየተጉመጠመጠ ደጋግሞ ተፋና ስምጥጥ አድርጎ ጠጥቶ ባይሮ ኢሜ ብሎ
አመሰገናት እግዜር ይስጥልኝ ለማለት
ካርለት ሾርቃውን
ሾርቃውን ልትመልስ ሄደች ያን ጊዜ ደልቲ ደሙ ፈላ ነደደው ተቀብላ ፈንጠቅ አድርጋ ደፋችውና
ይህች አሳሳች! ብሎ እራሱን ለማረጋጋት እየሞከረ ከመቀመጫው ተነሳ
"ይእ! እህ የታል አያ ደልቲ? አለ አሁን ውሃ ብሎኝ
ሰጥቸው መጣሁ አላልሽኝ?" አለች ጎይቲ ከካርለት ጋር ወደ ድንኳኗ
እየተጠጉ
"ጎይቲ አሁን እኮ እዚህ ቁጭ ብሎ ስናወራ ቆይተን ውሃ ስጭኝ ብሎኝ ሰጥቸው ሾርቃውን መልሼ: አንችን ጠርቸሽ መጣን በዚህ ቅፅበት የት ሄደ?"
"ይእ! እኔን ትጠይቂያለሽ ደሞ ይልቅ አንች ምንሽ ውስጥ ከተትሽው? አያ ደልቲ መቼም ካለ ነገር እንዲህ ሹልክ ብሎ እንደ
ሌባ አይጠፋም ተቀያየማችሁ?"
"ኧረ በጭራሽ"
👍27❤2
#ባል_አስይዞ_ቁማር
፡
፡
#ክፍል_ስድስት
፡
፡
#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ
///
‹እማዬ…አንቺ እማዬ……››
እታች ምድር ቤት ሁሉም ከየክፍሉ እየወጣ እሷ ወደአለችበት የመጀመሪያ ፎቅ የሚያስወጣውን መወጣጫ ግር ብለው በመምጣት መክበብ ጀመሩ…. እናቷ ከእሷ ፊት ለፊት ካለው መኝታ ቤቷ ልብሳቸውን እንኳን በቅጡ ሳይለብስ በተለመደ ድንጋጤዋ እያለከለከች
‹‹ምን ተፈጠረ ልጄ.?ደግሞ ምን ሆነሽ ነው?››
‹‹እንዴት አድርገሽ ነው ያሳደግሺኝ?››ጮህችባቸው፡፡
‹‹አረ ተረጋጊ ልጄ …እሱ ደግሞ ምን ማለት ነው.?››
‹‹እኔ ለምንድነው እንደሌላው ሰው ጥሩ መሆን የማልችለው…? እኔ ለምንድነው ስርዓት የሌለኝ? አለሌ የሆንኩበት ምክንያት ምንድነው›?
እናቷ የምትለፈልፈውን ሌሎች ሰራተኞች እንዳይሰሙ በመጨናነቅ ይመስላል እቅፍ አረጓትና የሚወራጩ እጆቾን አንድ ላይ በዛ ግዙፍ ሰውነታቸው በመጭመቅ አንጠልጥለው ወደመኝታ ቤታቸው አስገቧትና አልጋዋ ላይ በማሳረፍ በራፍን ሄደው ዘጉት…እሷም ከንዴቷ እንደመብረድ ብላ ሹክክ ብላ ተነሳችና ሙሉ በሙሉ ወደ አልጋዋ ላይ ወጣች..፡፡ከውስጥ ገባችና ተኛች…፡፡በቃ ደከማት..እናቷም እንደእሷው አደረጉ፡፡ ቀስብላው ወደአልጋው ላይ ወጡና ከጎኗ በመተኛት ክንዳቸውን አንተርሰው ከራሳቸውጋር ልጥፍ አደረጓት፡፡
ሰው ሲከፋው እንዲህ እንደእሷ ሮጦ የሚወሸቅበት ጉያ ወይም ተንተርሶ የሚተኛበት ክንድ ወይም እቅፋ ውስጥ ገብቶ የውስጥ ቁጣውንና ለቅሷውን የሚያቀዘቅዘዝዝት ምሽግ ካላው እድለኛ ነው። ሲከፍ ወደ መጠጥ ቤት ሮጦ አልኮል ከመጎንጨት የሚያፈቅሩት ሰው እቅፍ ውስጥ ኩርምትምት ብሎ በማልቀስ የመረጋጋት አማራጭን መጠቀም ውጤታማና ብልሀት የታከለበት ውሳኔ ነው።በተለይ ያ ክንድ እንዲህ እንደልዩ የእናት ሲሆን የቀጥታም ሆነ የጎንዬሽ ጉዳቱ ለዜሮ የቀረበ ነው።
‹‹የእኔ እርግብ…. አንቺን የሚስተካከል ደግ የለም እኮ…ከአንቺም እኩል ለሰው አዛኝ እና ሰናይ ምግባር ያለው ልጅ ማግኘት ከባድ ነው….ይሄን እኔ ብቻ አይደለሁም ሀገር ምድሩ ነው የሚያወራው…እዚህ ቤት የሚርመሰመሱ ሰራተኞች አንቺ ሲያምሽ አብረው ሚታመሙት፤ ፈገግ ስትይ ሲገለፍጡ የሚውሉ ናቸው እኮ...የሰፈሩ አሮጌት ምረቃትን ካንቺ እኩል የተመረቀ ማን አለ..?ከአኔ ከእናትሽ ቦርሳ እየመዠረጥሽ ለሰፈር አሮጊትና ሽማጊሌ ብሬን ስታድይ፤ የተመመ ችግረኛ ስታሳክሚ ፤መማር ላቃተቻው ህፃናት ደብተርና ዩኒፎርም እየገዛሽ ስታድይ አይደል እንዴ የኖርሽው?
ልጄ እኔ እንደውም ይሄ ሁሉ ደግነትና ቸርነት ከየት አምጥታው ነው ?እያልኩ ዘወትር እንደተደምኩብሽና እንደኮራሁብሽ ነው..አንቺ ይሄ ክፍ አመል ባይጠናወትሽና ባይለክፍሽ እንከን አልባ መልአክ እኮ ነበርሽ..ልጄ ታዲያ ምን ላድርግሽ እንድትፈወሺልኝ ያልሞከርኩት ህክምና የላጠጣሁሽ ጠበል የለም..የእኔ ቆንጆ ሰው ሲቸገር ምንም ነገር ለመሞከር ይደፍራል፤አጣብቂኝ የትኛውንም የተነገረውን ነገር ያምናል፤ የትኛውንም መጥፎ የተባለ ስምምነት ይፈርማል፤የትኛውንም የሚወደውን ነገር አሳልፎ ይሰጣል።አዎ ችግር እንደዛ ያደርጋል።እኔም በዚሁ በአንቺ ችግር ምክንያት የሰራሁትን ዛሬ ልንገርሽ…ሚስጥር አድርጌ ይዤው ነበር.. እግዜር ይቅር ይበለኝና ይሄውልሽ ጠንቆይ ቤት ሁሉ እኮ መፍቴ ይሰጠኝ መስሎኝ ሄጄ ጠይቄያለሁ….ግን መፍትሄ አልተገኘም፡፡
‹‹እጄን አስቆርጪው…በእጄ አይደለ ምሰርቀው…በቃ አልፈልጋቸውም.. ሁለቱ እጆቼ ይቆረጡ፡፡››
‹‹በስመአብ በይ ልጄ ..በስመአብ…የሚነሳው በእጅ ቢሆንም ቀድሞ የሚሰርቀው እኮ እዕምሮ ነው..እምሮሽን አላስቆርጥ?››
›‹‹እማዬ ብቻ እኔ አንዲህ እየተዋረዱ መኖር ሰልችቶኛል…ትንሽ ጊዜ ነው የምሰጥሽ ….ካለበለዚያ..››
‹‹ካበለዚያ ምን?››
‹‹እራሴን አጠፋልሻለሁ..ከዛ ግልግል ነው፡፡››
‹‹አረ ተይ ልጄ…. ተይ እኔ እናትሽ እንኳን አላሳዝንሽም..?ሌላ ትርፍ ልጅ እንዳለው ሰው እንዲህ ትያለሽ..? አንቺ እኮ ከታችም ከላይም የሌለሽ ብቸኛ ልጄ የአይኔ ማረፊያ ነሽ…እኔ ባለኝ ሀብት በአለም በየትኛውም ጥግ ለዚህ ፈውስ ቢኖር የምሰስት ይመስልሻል ?ለምን ብዬ…ከሰባራ ሳንቲም አንስቶ ሙሉ ካማፓኒው ያንቺው ነው..እኔ ከአሁን ወዲህ የምኖረው እራሴን ለማስደሰት ሳይሆን አንቺ በሁሉ ነገር የተሳካልሽ ሆነሽ ስትስቂ ለማየት ነው…፡፡››
‹‹እና ታዲያ ምን አድርጊ እያልሺኝ ነው?››
‹‹ካልሆነ ለሁለተኛ ጊዜ እዛው አሜሪካ ሂጂና ትሞክሪ ይሆን ?››
‹‹እማዬ እኔ የትም ሀገር መሄድ አልፈልግም..ደግሞ የፈረንጆች የቅዠት ሀሳበ መሞከሪያ መሆን ሰልችቶኛል፡፡››
‹‹እሺ.በቃ ከመድህኔ ጋር ተማከሬ የሆነ ነገር አደርጋለሁ፡፡››
‹‹ከእሱ ጋር አትማከሪ በራስሽ ከቻልሽ አድርጊ ካለበለዚያ…፡፡››
‹‹በቃ በቃ. እሱን ለእኔ ተይውና ተኚ.›
እጃቸውን ፀጉሯ ውስጥ ከተው ሲዳብሷት የሆነ ፀጥ ያለ ውቅያኖስ ውስጥ እየዋኘች ያለች መሰላት…ወዲያው እንቅልፍ ይዞት ጭልጥ አለ፡፡
✨ይቀጥላል✨
፡
፡
#ክፍል_ስድስት
፡
፡
#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ
///
‹እማዬ…አንቺ እማዬ……››
እታች ምድር ቤት ሁሉም ከየክፍሉ እየወጣ እሷ ወደአለችበት የመጀመሪያ ፎቅ የሚያስወጣውን መወጣጫ ግር ብለው በመምጣት መክበብ ጀመሩ…. እናቷ ከእሷ ፊት ለፊት ካለው መኝታ ቤቷ ልብሳቸውን እንኳን በቅጡ ሳይለብስ በተለመደ ድንጋጤዋ እያለከለከች
‹‹ምን ተፈጠረ ልጄ.?ደግሞ ምን ሆነሽ ነው?››
‹‹እንዴት አድርገሽ ነው ያሳደግሺኝ?››ጮህችባቸው፡፡
‹‹አረ ተረጋጊ ልጄ …እሱ ደግሞ ምን ማለት ነው.?››
‹‹እኔ ለምንድነው እንደሌላው ሰው ጥሩ መሆን የማልችለው…? እኔ ለምንድነው ስርዓት የሌለኝ? አለሌ የሆንኩበት ምክንያት ምንድነው›?
እናቷ የምትለፈልፈውን ሌሎች ሰራተኞች እንዳይሰሙ በመጨናነቅ ይመስላል እቅፍ አረጓትና የሚወራጩ እጆቾን አንድ ላይ በዛ ግዙፍ ሰውነታቸው በመጭመቅ አንጠልጥለው ወደመኝታ ቤታቸው አስገቧትና አልጋዋ ላይ በማሳረፍ በራፍን ሄደው ዘጉት…እሷም ከንዴቷ እንደመብረድ ብላ ሹክክ ብላ ተነሳችና ሙሉ በሙሉ ወደ አልጋዋ ላይ ወጣች..፡፡ከውስጥ ገባችና ተኛች…፡፡በቃ ደከማት..እናቷም እንደእሷው አደረጉ፡፡ ቀስብላው ወደአልጋው ላይ ወጡና ከጎኗ በመተኛት ክንዳቸውን አንተርሰው ከራሳቸውጋር ልጥፍ አደረጓት፡፡
ሰው ሲከፋው እንዲህ እንደእሷ ሮጦ የሚወሸቅበት ጉያ ወይም ተንተርሶ የሚተኛበት ክንድ ወይም እቅፋ ውስጥ ገብቶ የውስጥ ቁጣውንና ለቅሷውን የሚያቀዘቅዘዝዝት ምሽግ ካላው እድለኛ ነው። ሲከፍ ወደ መጠጥ ቤት ሮጦ አልኮል ከመጎንጨት የሚያፈቅሩት ሰው እቅፍ ውስጥ ኩርምትምት ብሎ በማልቀስ የመረጋጋት አማራጭን መጠቀም ውጤታማና ብልሀት የታከለበት ውሳኔ ነው።በተለይ ያ ክንድ እንዲህ እንደልዩ የእናት ሲሆን የቀጥታም ሆነ የጎንዬሽ ጉዳቱ ለዜሮ የቀረበ ነው።
‹‹የእኔ እርግብ…. አንቺን የሚስተካከል ደግ የለም እኮ…ከአንቺም እኩል ለሰው አዛኝ እና ሰናይ ምግባር ያለው ልጅ ማግኘት ከባድ ነው….ይሄን እኔ ብቻ አይደለሁም ሀገር ምድሩ ነው የሚያወራው…እዚህ ቤት የሚርመሰመሱ ሰራተኞች አንቺ ሲያምሽ አብረው ሚታመሙት፤ ፈገግ ስትይ ሲገለፍጡ የሚውሉ ናቸው እኮ...የሰፈሩ አሮጌት ምረቃትን ካንቺ እኩል የተመረቀ ማን አለ..?ከአኔ ከእናትሽ ቦርሳ እየመዠረጥሽ ለሰፈር አሮጊትና ሽማጊሌ ብሬን ስታድይ፤ የተመመ ችግረኛ ስታሳክሚ ፤መማር ላቃተቻው ህፃናት ደብተርና ዩኒፎርም እየገዛሽ ስታድይ አይደል እንዴ የኖርሽው?
ልጄ እኔ እንደውም ይሄ ሁሉ ደግነትና ቸርነት ከየት አምጥታው ነው ?እያልኩ ዘወትር እንደተደምኩብሽና እንደኮራሁብሽ ነው..አንቺ ይሄ ክፍ አመል ባይጠናወትሽና ባይለክፍሽ እንከን አልባ መልአክ እኮ ነበርሽ..ልጄ ታዲያ ምን ላድርግሽ እንድትፈወሺልኝ ያልሞከርኩት ህክምና የላጠጣሁሽ ጠበል የለም..የእኔ ቆንጆ ሰው ሲቸገር ምንም ነገር ለመሞከር ይደፍራል፤አጣብቂኝ የትኛውንም የተነገረውን ነገር ያምናል፤ የትኛውንም መጥፎ የተባለ ስምምነት ይፈርማል፤የትኛውንም የሚወደውን ነገር አሳልፎ ይሰጣል።አዎ ችግር እንደዛ ያደርጋል።እኔም በዚሁ በአንቺ ችግር ምክንያት የሰራሁትን ዛሬ ልንገርሽ…ሚስጥር አድርጌ ይዤው ነበር.. እግዜር ይቅር ይበለኝና ይሄውልሽ ጠንቆይ ቤት ሁሉ እኮ መፍቴ ይሰጠኝ መስሎኝ ሄጄ ጠይቄያለሁ….ግን መፍትሄ አልተገኘም፡፡
‹‹እጄን አስቆርጪው…በእጄ አይደለ ምሰርቀው…በቃ አልፈልጋቸውም.. ሁለቱ እጆቼ ይቆረጡ፡፡››
‹‹በስመአብ በይ ልጄ ..በስመአብ…የሚነሳው በእጅ ቢሆንም ቀድሞ የሚሰርቀው እኮ እዕምሮ ነው..እምሮሽን አላስቆርጥ?››
›‹‹እማዬ ብቻ እኔ አንዲህ እየተዋረዱ መኖር ሰልችቶኛል…ትንሽ ጊዜ ነው የምሰጥሽ ….ካለበለዚያ..››
‹‹ካበለዚያ ምን?››
‹‹እራሴን አጠፋልሻለሁ..ከዛ ግልግል ነው፡፡››
‹‹አረ ተይ ልጄ…. ተይ እኔ እናትሽ እንኳን አላሳዝንሽም..?ሌላ ትርፍ ልጅ እንዳለው ሰው እንዲህ ትያለሽ..? አንቺ እኮ ከታችም ከላይም የሌለሽ ብቸኛ ልጄ የአይኔ ማረፊያ ነሽ…እኔ ባለኝ ሀብት በአለም በየትኛውም ጥግ ለዚህ ፈውስ ቢኖር የምሰስት ይመስልሻል ?ለምን ብዬ…ከሰባራ ሳንቲም አንስቶ ሙሉ ካማፓኒው ያንቺው ነው..እኔ ከአሁን ወዲህ የምኖረው እራሴን ለማስደሰት ሳይሆን አንቺ በሁሉ ነገር የተሳካልሽ ሆነሽ ስትስቂ ለማየት ነው…፡፡››
‹‹እና ታዲያ ምን አድርጊ እያልሺኝ ነው?››
‹‹ካልሆነ ለሁለተኛ ጊዜ እዛው አሜሪካ ሂጂና ትሞክሪ ይሆን ?››
‹‹እማዬ እኔ የትም ሀገር መሄድ አልፈልግም..ደግሞ የፈረንጆች የቅዠት ሀሳበ መሞከሪያ መሆን ሰልችቶኛል፡፡››
‹‹እሺ.በቃ ከመድህኔ ጋር ተማከሬ የሆነ ነገር አደርጋለሁ፡፡››
‹‹ከእሱ ጋር አትማከሪ በራስሽ ከቻልሽ አድርጊ ካለበለዚያ…፡፡››
‹‹በቃ በቃ. እሱን ለእኔ ተይውና ተኚ.›
እጃቸውን ፀጉሯ ውስጥ ከተው ሲዳብሷት የሆነ ፀጥ ያለ ውቅያኖስ ውስጥ እየዋኘች ያለች መሰላት…ወዲያው እንቅልፍ ይዞት ጭልጥ አለ፡፡
✨ይቀጥላል✨
👍102❤17👏3😁3
#ህያብ
፡
፡
#ክፍል_ስድስት
፡
፡
#ድርሰት_በኤርሚ
"ዮናታን እንደምናስበው አይነት ሰው አይደለም"
"ማለት" አልኩት ግራ ተጋብቼ
"ማለትማ ከየትናዬት ጋር ያላቸው ግንኙነት እኛ እንደምናስበው አይደለም...."
"እኔ ምንም እየገባኝ አይደለም ቢኒ ምንድነው እያወራህ ያለኸው"
"ተረጋጊ እነግርሻለሁ.... ዮናታን የያዝነው ክፍል ድረስ መጥቶ እንድናወራ ጠየቀኝ.... እሺ ብየው ተያይዘን ወደ ሆቴሉ ባር አመራን እናም ቁጭ ብለን ያልጠበኩትን ነገር ነገረኝ"
"ቀጥል ምን አለህ"
#ምሽት_8_ሰዓት_ላይ
የሆነውን ሁሉ እኔ ነኝ የምተርክላችሁ.... ቢኒያም
ከዮናታን ጋር ወደ ባሩ ከወረድን በኋላ መጠጥ አዘዘ እና
"የውልህ ቢኒያም ተረጋግተህ እንድትሰማኝና ከቻልክ እንድታግዘኝ እፈልጋለሁ..."
"ለማንኛውም የምትለኝን ልስማህ" እስከዚህ ድረስ እንኳን አብሬው የመጣሁት ድጋሚ ካስተማረን F እንዳያስታቅፈኝ በሚል ፍራቻ ነው
"ሁሉም ሰው የሚያውቀው እኔ ሴት አተራማሽ እንደሆንኩ ነው። በእርግጥ እውነታም አለው ጥቂት ከማይባሉ ሴቶች ጋር ግንኙነት ነበረኝ ግን ነበር ነው ከ2 አመት በፊት በመጀመሪያ እይታ አንዲት ልጅ ልቤ ውስጥ ገባች። እናም ልክ ለሌሎቹ እንደሚሰማኝ ተራ ስሜት ነው ብዬ የነበረው ህይወቴን ለመቀጠል ሞከርኩ ግን እንደድሮው መሆን አቃተኝ። ለተወሰነ ጊዜ ስወዛገብ ከረምኩና ፍቅሬን እንዴት መግለፅ እንዳለብኝና እሷን የኔ እንዴት እንደማደርግ ማሰብ ጀመርኩ።
ልጅቷ ኮስታራ እና የማያስቀርብ ፊት ነው ያላት ያለኝ አማራጭ አብራ ከምትማራቸው ሴቶች ስለሷ ሊነግረኝ የሚችል ሰው ፈልጌ መቅረብ ነበር እናም የትናዬትን ቀረብኳት...."
"ሰውዬ ስለምን እያወራህ ነው" እዚህ ጋ መምህር መሆኑን ረሳሁ
"ቢኒያም ለኔ ሁሉም ነገር የተገለፀልኝ ዛሬ ነው.... እና ከቻልክ ተረጋግተህ ስማኝ"
"ከየትናዬት ጋር ከተቀራረብን በኋላ በተደጋጋሚ ቢሮዬ እየጠራኋት ስለ ህያብ እንድትነግረኝ አደርጋት ነበር።"
"ምን እያልክ ነው እና ህያብን አንተም ታፈቅራታለህ" ማመን ከበደኝ
"አዎ ያውም በመጀመሪያ እይታ ነው ያንበረከከችኝ ለማንም ሴት እንደዚህ ሆኜ አላውቅም። የኔ ብትሆን ብዬ በምናቤ ስስላት የነበረችን ልጅ ነው በአካል ያገኘኋት"
"እሺ ከዛስ ምን ተፈጠረ"
" የትናዬት እንኳን ጠርቻት ሳልጠራትም እየመጣች ብዙ ነገር እንዳውቅ አደረገችኝ። የምትነግረኝ ነገሮች ግን ህያብን እንድቀርብ ሳይሆን እንድፈራ እና እንድሸሽ የሚያደርግ ነበር።"
"ምን ብላህ ነው"
"በመጀመሪያ ከሷ ጋር ኢለመንተሪ ጀምሮ አብረው እንደተማሩ እና እንደምትታየው ሳይሆን ውስጥ ውስጡን ወንድ አተራማሽ እንደሆነች ነገረችኝ። አላምንም ስላት በማስረጃ አረጋገጠችልኝ።"
"መቼ ነበር ያረጋገጠችልህ ማለቴ የት"
"ከአመት በፊት ካንተ ጓደኛ ጋር ቤርጎ ሲገቡ በአይኔ በብረቱ አየሁ እናም የምትለኝ እውነት እንደሆነ አረጋገጥኩ"
"የውልህ ዮናታን ያየኸው እውነት ነው ግን እንደምታስበው አይደለም። ጓደኛችን በሀይሉን ፍቅረኛው ከድታው ሌላ ሰው ጋር ሆነች እናም እሷን ማስቀናት እንደሚፈልግ ነገረን.... እኔም ለህያብ ነገርኳትና እምቢ ብትልም በግድ አሳመንኳት ከዛ ፍቅረኛው የምታይበትን ሁኔታ አመቻችተን አብረው ወደ ክፍል ሲገቡ እንድታያቸው አደረግን። ግን አንተ እዛ እንደነበርክ ማንም አላወቀም እንዴትስ ልትገኝ ቻልክ"
"የትናዬት ናት አላምንም ስላት 'ከቢኒያም ጋር ፍቅር ፍቅር እየተጫወተች የገዛ ጓደኛው ጋር ትማግጥበታለች' አለችኝ ማረጋገጥ ከፈለክ ብላ ወደዛ ቦታ ወሰደችኝ እና በአይኔ እንዳይ አደረገችን በሰዓቱ ራሴን መቆጣተር አቅቶኝ ነበር እናም እሱን ልደበድብ እሷን ልሰድብ ስራመድ የትናዬት አስቆመችኝ.... ከዛ በኋላ የምትለኝን ሁሉ አምናት ነበር እስከ ትላንትና ድረስ..... አሁን ግን ሁሉንም ከራሷ ከህያብ ነው ማረጋገጥ የምፈልገው"
ነገሩ ካሰብኩት ውጪ ሆነብኝ የትናዬት ተንኮለኛ ብትሆንም ይህን ያክል ርቃ ትሄዳለች ብዬ ግን አላሰብኩም ነበር።
"እሺ ሌላስ ምን ነገረችህ"
"አንተ ፍቅረኛዋ እንደሆንክ እና አዲስ አበባ ከሌላ የወለደቻት ልጅ እንዳለቻት"
"ምንድነው የምታወራው እኔ ከህያብ ጋር አብሬ ስለምታይ ፍቅረኛዋ ነው ብትል እሺ ግን ልጅ ከየት ፈጥራ ነው የነገረችህ...." ኪሱን በርብሮ የሆነ ፎቶ አወጣና እጄ ላይ አስቀመጠልኝ። ህያብ ልጅ አቅፋ.....
"ግን እኮ እህቷም ልትሆን ትችላለች" ካልኩ በኋላ ለእናቴም ለአባቴም አንድ ነኝ ብላ የነገረችኝ ትዝ አለኝ።
"አይደለችም ልጇ ነች ይሄን አረጋግጫለሁ ግን አንተ የምታውቅ ነበር የመሰለኝ"
"ኧረ በፍፁም ግራ እያጋባህኝ ነው" ፎቶውን ተቀብሎኝ ወደ ኪሱ ከተተና
"ቢሆንም ይሄ ጉዳዬ አይደለም.... ለሷ ያለኝን ፍቅር ያለፈ ታሪኳ ሊቀይረው አይችልም የሚያሳስበኝ የአሁኑ ነው..." ግንባሩን አሸት አሸት እያደረገ ትንሽ ከቆየ በኋላ
"ቢኒያም አንድ ጥያቄ ልጠይቅህ እናም ሳትዋሽ መልስልኝ" አለኝ
"እሺ ጠይቀኝ"
"ከህያብ ጋር ፍቅረኛሞች ናችሁ?"
"አይደለንም" ፈገግ ሲል አየሁት
"እሺ ታፈቅራታለህ" ከንግግሩ እኩል ደነገጥኩ
"አይ አላፈቅራትም" መሬት ተንበርክኮ መሳም ነው የቀረው ደግሞ ደጋግሞ ፈጣሪን አመሰገነ... ሁኔታውን ሳይ የነገረኝ ሁሉ እውነት እንደሆነ ገባኝ።
"እኔም አንድ ጥያቄ ልጠይቅህ"
"ጠይቀኝ" አለኝ በፈገግታ ተሞልቶ
"የትናዬት ፍቅረኛህ ካልሆነች ወይም የሆነ ግንኙነት ከሌላችሁ እንደዛ ተጠባብቃችሁ አንገትህን ስትስምህ...." ሳያስጨርሰኝ
"እሱ ለኔም የሚገርም አጋጣሚ ነበር። ህያብ እኛ ወደተቀመጥንበት ስትመጣ እኩል አየናት እናም የትናዬት ሳላስበው ጥምጥም ብላብኝ ሳመችኝ። ደንግጬ ስለነበር ላስቆማት አልቻልኩም ምን እያረግሽ ነው ብያት ዞር ስትልልኝ ህያብ ቆማ እያየችን ነው ወዲያው አንተ መተህ ወሰድካት"
"እንጂ ምንም አይነት ግንኙነት የላችሁም"
"ቢኖረን ለምን እዋሽሀለሁ"
ወደ ያዝነው ክፍል ከተመለስኩ በኋላ ረጅም ሰዓት ወስጄ ለማሰብ ሞከርኩ ከሁሉም አንድ ነገር ደጋግሞ አቃጨለብኝ.... "ህያብን ታፈቅራታለህ"
አዎ አፈቅራታለሁ አልኩ ጮክ ብዬ ልክ እንዳንተ መጀመሪያ ያየኋት ቀን ነው ልቤን የሰረቀችው ግን ምን ያደርጋል እሷ የምታፈቅረው አንተን.... ወዲያው በንግግሬ ደንግጬ ዝምም አልኩ ደግነቱ ከራሴ ውጪ የተናገርኩትን ማንም ሊሰማ አይችልም። ፍጥጥ እንዳልኩ ነጋ ግን ከራሴ ጋር ልስማማ አልቻልኩም እውነት ህያብ የሌላ ሰው ስትሆን ማዬት እችል ይሆን???
።።።
እኔ ነኝ ህያብ!
ፍንድቅድቅ ብያለሁ ከዚህ የበለጠ ምን ሊያስደስተኝ ይችላል በማፈቅረው ሰው መፈቅርን የመሰለ ምን ነገር አለ። ከነገረኝ ነገሮች ሁሉ ዮናታን ያፈቅርሻል የሚለው ሙሉ እኔን ተቆጣጥሮኛል።
"ህያብ ደስታሽን ላበላሽ ፈልጌ ሳይሆን እባክሽ ጥያቄዬን መልሽልኝ" ጮክ ብሎ ተናገረ
"ምን አልከኝ ቢኒ" በራሴ አለም ስዋዥቅ ምን እንዳለኝም አልሰማሁትም ነበር።
"ልጅ አለሽ" ከመደንገጤ የተነሳ ከተቀመጥኩበት ተስፈንጥሬ ተነሳሁ።
"ህያብ እንደጓደኛሽ የምታይኝ ከሆነ እውነቱን ንገሪኝ ልጅ አለሽ" ከተቀመጠበት ተነስቶ እጄን ያዘና አንድቀመጥ አደረገኝ ከዛ በተማፅኖ አይን አይኔን ያይ ጀመር "እባክሽ ህያብ ላስጨንቅሽ ፈልጌ አይደለም... ግን ዮናታን ፎቶ ሲያሳየኝ ተጠራጠርኩ" የባሰ ድንጋጤ
"ምን? ዮናታንም ያውቃል"
"አዎ እሱ ነው የነገረኝ ስነግርሽ እኮ አልሰማሽኝም መሰለኝ"
፡
፡
#ክፍል_ስድስት
፡
፡
#ድርሰት_በኤርሚ
"ዮናታን እንደምናስበው አይነት ሰው አይደለም"
"ማለት" አልኩት ግራ ተጋብቼ
"ማለትማ ከየትናዬት ጋር ያላቸው ግንኙነት እኛ እንደምናስበው አይደለም...."
"እኔ ምንም እየገባኝ አይደለም ቢኒ ምንድነው እያወራህ ያለኸው"
"ተረጋጊ እነግርሻለሁ.... ዮናታን የያዝነው ክፍል ድረስ መጥቶ እንድናወራ ጠየቀኝ.... እሺ ብየው ተያይዘን ወደ ሆቴሉ ባር አመራን እናም ቁጭ ብለን ያልጠበኩትን ነገር ነገረኝ"
"ቀጥል ምን አለህ"
#ምሽት_8_ሰዓት_ላይ
የሆነውን ሁሉ እኔ ነኝ የምተርክላችሁ.... ቢኒያም
ከዮናታን ጋር ወደ ባሩ ከወረድን በኋላ መጠጥ አዘዘ እና
"የውልህ ቢኒያም ተረጋግተህ እንድትሰማኝና ከቻልክ እንድታግዘኝ እፈልጋለሁ..."
"ለማንኛውም የምትለኝን ልስማህ" እስከዚህ ድረስ እንኳን አብሬው የመጣሁት ድጋሚ ካስተማረን F እንዳያስታቅፈኝ በሚል ፍራቻ ነው
"ሁሉም ሰው የሚያውቀው እኔ ሴት አተራማሽ እንደሆንኩ ነው። በእርግጥ እውነታም አለው ጥቂት ከማይባሉ ሴቶች ጋር ግንኙነት ነበረኝ ግን ነበር ነው ከ2 አመት በፊት በመጀመሪያ እይታ አንዲት ልጅ ልቤ ውስጥ ገባች። እናም ልክ ለሌሎቹ እንደሚሰማኝ ተራ ስሜት ነው ብዬ የነበረው ህይወቴን ለመቀጠል ሞከርኩ ግን እንደድሮው መሆን አቃተኝ። ለተወሰነ ጊዜ ስወዛገብ ከረምኩና ፍቅሬን እንዴት መግለፅ እንዳለብኝና እሷን የኔ እንዴት እንደማደርግ ማሰብ ጀመርኩ።
ልጅቷ ኮስታራ እና የማያስቀርብ ፊት ነው ያላት ያለኝ አማራጭ አብራ ከምትማራቸው ሴቶች ስለሷ ሊነግረኝ የሚችል ሰው ፈልጌ መቅረብ ነበር እናም የትናዬትን ቀረብኳት...."
"ሰውዬ ስለምን እያወራህ ነው" እዚህ ጋ መምህር መሆኑን ረሳሁ
"ቢኒያም ለኔ ሁሉም ነገር የተገለፀልኝ ዛሬ ነው.... እና ከቻልክ ተረጋግተህ ስማኝ"
"ከየትናዬት ጋር ከተቀራረብን በኋላ በተደጋጋሚ ቢሮዬ እየጠራኋት ስለ ህያብ እንድትነግረኝ አደርጋት ነበር።"
"ምን እያልክ ነው እና ህያብን አንተም ታፈቅራታለህ" ማመን ከበደኝ
"አዎ ያውም በመጀመሪያ እይታ ነው ያንበረከከችኝ ለማንም ሴት እንደዚህ ሆኜ አላውቅም። የኔ ብትሆን ብዬ በምናቤ ስስላት የነበረችን ልጅ ነው በአካል ያገኘኋት"
"እሺ ከዛስ ምን ተፈጠረ"
" የትናዬት እንኳን ጠርቻት ሳልጠራትም እየመጣች ብዙ ነገር እንዳውቅ አደረገችኝ። የምትነግረኝ ነገሮች ግን ህያብን እንድቀርብ ሳይሆን እንድፈራ እና እንድሸሽ የሚያደርግ ነበር።"
"ምን ብላህ ነው"
"በመጀመሪያ ከሷ ጋር ኢለመንተሪ ጀምሮ አብረው እንደተማሩ እና እንደምትታየው ሳይሆን ውስጥ ውስጡን ወንድ አተራማሽ እንደሆነች ነገረችኝ። አላምንም ስላት በማስረጃ አረጋገጠችልኝ።"
"መቼ ነበር ያረጋገጠችልህ ማለቴ የት"
"ከአመት በፊት ካንተ ጓደኛ ጋር ቤርጎ ሲገቡ በአይኔ በብረቱ አየሁ እናም የምትለኝ እውነት እንደሆነ አረጋገጥኩ"
"የውልህ ዮናታን ያየኸው እውነት ነው ግን እንደምታስበው አይደለም። ጓደኛችን በሀይሉን ፍቅረኛው ከድታው ሌላ ሰው ጋር ሆነች እናም እሷን ማስቀናት እንደሚፈልግ ነገረን.... እኔም ለህያብ ነገርኳትና እምቢ ብትልም በግድ አሳመንኳት ከዛ ፍቅረኛው የምታይበትን ሁኔታ አመቻችተን አብረው ወደ ክፍል ሲገቡ እንድታያቸው አደረግን። ግን አንተ እዛ እንደነበርክ ማንም አላወቀም እንዴትስ ልትገኝ ቻልክ"
"የትናዬት ናት አላምንም ስላት 'ከቢኒያም ጋር ፍቅር ፍቅር እየተጫወተች የገዛ ጓደኛው ጋር ትማግጥበታለች' አለችኝ ማረጋገጥ ከፈለክ ብላ ወደዛ ቦታ ወሰደችኝ እና በአይኔ እንዳይ አደረገችን በሰዓቱ ራሴን መቆጣተር አቅቶኝ ነበር እናም እሱን ልደበድብ እሷን ልሰድብ ስራመድ የትናዬት አስቆመችኝ.... ከዛ በኋላ የምትለኝን ሁሉ አምናት ነበር እስከ ትላንትና ድረስ..... አሁን ግን ሁሉንም ከራሷ ከህያብ ነው ማረጋገጥ የምፈልገው"
ነገሩ ካሰብኩት ውጪ ሆነብኝ የትናዬት ተንኮለኛ ብትሆንም ይህን ያክል ርቃ ትሄዳለች ብዬ ግን አላሰብኩም ነበር።
"እሺ ሌላስ ምን ነገረችህ"
"አንተ ፍቅረኛዋ እንደሆንክ እና አዲስ አበባ ከሌላ የወለደቻት ልጅ እንዳለቻት"
"ምንድነው የምታወራው እኔ ከህያብ ጋር አብሬ ስለምታይ ፍቅረኛዋ ነው ብትል እሺ ግን ልጅ ከየት ፈጥራ ነው የነገረችህ...." ኪሱን በርብሮ የሆነ ፎቶ አወጣና እጄ ላይ አስቀመጠልኝ። ህያብ ልጅ አቅፋ.....
"ግን እኮ እህቷም ልትሆን ትችላለች" ካልኩ በኋላ ለእናቴም ለአባቴም አንድ ነኝ ብላ የነገረችኝ ትዝ አለኝ።
"አይደለችም ልጇ ነች ይሄን አረጋግጫለሁ ግን አንተ የምታውቅ ነበር የመሰለኝ"
"ኧረ በፍፁም ግራ እያጋባህኝ ነው" ፎቶውን ተቀብሎኝ ወደ ኪሱ ከተተና
"ቢሆንም ይሄ ጉዳዬ አይደለም.... ለሷ ያለኝን ፍቅር ያለፈ ታሪኳ ሊቀይረው አይችልም የሚያሳስበኝ የአሁኑ ነው..." ግንባሩን አሸት አሸት እያደረገ ትንሽ ከቆየ በኋላ
"ቢኒያም አንድ ጥያቄ ልጠይቅህ እናም ሳትዋሽ መልስልኝ" አለኝ
"እሺ ጠይቀኝ"
"ከህያብ ጋር ፍቅረኛሞች ናችሁ?"
"አይደለንም" ፈገግ ሲል አየሁት
"እሺ ታፈቅራታለህ" ከንግግሩ እኩል ደነገጥኩ
"አይ አላፈቅራትም" መሬት ተንበርክኮ መሳም ነው የቀረው ደግሞ ደጋግሞ ፈጣሪን አመሰገነ... ሁኔታውን ሳይ የነገረኝ ሁሉ እውነት እንደሆነ ገባኝ።
"እኔም አንድ ጥያቄ ልጠይቅህ"
"ጠይቀኝ" አለኝ በፈገግታ ተሞልቶ
"የትናዬት ፍቅረኛህ ካልሆነች ወይም የሆነ ግንኙነት ከሌላችሁ እንደዛ ተጠባብቃችሁ አንገትህን ስትስምህ...." ሳያስጨርሰኝ
"እሱ ለኔም የሚገርም አጋጣሚ ነበር። ህያብ እኛ ወደተቀመጥንበት ስትመጣ እኩል አየናት እናም የትናዬት ሳላስበው ጥምጥም ብላብኝ ሳመችኝ። ደንግጬ ስለነበር ላስቆማት አልቻልኩም ምን እያረግሽ ነው ብያት ዞር ስትልልኝ ህያብ ቆማ እያየችን ነው ወዲያው አንተ መተህ ወሰድካት"
"እንጂ ምንም አይነት ግንኙነት የላችሁም"
"ቢኖረን ለምን እዋሽሀለሁ"
ወደ ያዝነው ክፍል ከተመለስኩ በኋላ ረጅም ሰዓት ወስጄ ለማሰብ ሞከርኩ ከሁሉም አንድ ነገር ደጋግሞ አቃጨለብኝ.... "ህያብን ታፈቅራታለህ"
አዎ አፈቅራታለሁ አልኩ ጮክ ብዬ ልክ እንዳንተ መጀመሪያ ያየኋት ቀን ነው ልቤን የሰረቀችው ግን ምን ያደርጋል እሷ የምታፈቅረው አንተን.... ወዲያው በንግግሬ ደንግጬ ዝምም አልኩ ደግነቱ ከራሴ ውጪ የተናገርኩትን ማንም ሊሰማ አይችልም። ፍጥጥ እንዳልኩ ነጋ ግን ከራሴ ጋር ልስማማ አልቻልኩም እውነት ህያብ የሌላ ሰው ስትሆን ማዬት እችል ይሆን???
።።።
እኔ ነኝ ህያብ!
ፍንድቅድቅ ብያለሁ ከዚህ የበለጠ ምን ሊያስደስተኝ ይችላል በማፈቅረው ሰው መፈቅርን የመሰለ ምን ነገር አለ። ከነገረኝ ነገሮች ሁሉ ዮናታን ያፈቅርሻል የሚለው ሙሉ እኔን ተቆጣጥሮኛል።
"ህያብ ደስታሽን ላበላሽ ፈልጌ ሳይሆን እባክሽ ጥያቄዬን መልሽልኝ" ጮክ ብሎ ተናገረ
"ምን አልከኝ ቢኒ" በራሴ አለም ስዋዥቅ ምን እንዳለኝም አልሰማሁትም ነበር።
"ልጅ አለሽ" ከመደንገጤ የተነሳ ከተቀመጥኩበት ተስፈንጥሬ ተነሳሁ።
"ህያብ እንደጓደኛሽ የምታይኝ ከሆነ እውነቱን ንገሪኝ ልጅ አለሽ" ከተቀመጠበት ተነስቶ እጄን ያዘና አንድቀመጥ አደረገኝ ከዛ በተማፅኖ አይን አይኔን ያይ ጀመር "እባክሽ ህያብ ላስጨንቅሽ ፈልጌ አይደለም... ግን ዮናታን ፎቶ ሲያሳየኝ ተጠራጠርኩ" የባሰ ድንጋጤ
"ምን? ዮናታንም ያውቃል"
"አዎ እሱ ነው የነገረኝ ስነግርሽ እኮ አልሰማሽኝም መሰለኝ"
👍48❤8🥰2👏1
#ተአምራተ_ኬድሮን
፡
፡
#ክፍል_ስድስት
፡
፡
#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ
//
‹‹ጎሽ ጥለኸኝ አልተሰወርክም…አጠገቤ አለህ ማለት ነው? ››ስትል የእፎይታ ትንፋሽ ተነፈሰችና…በከፍተኛ ፍራቻ እና ጥርጣሬ ዓይኖቾን ገለጠች…..ወንዝ የሚባል ነገር ስራቸው የለም…የሲኦል ምልክትም አይታያትም…. በሳር ፤ በትናንሽ አረንጓዴ ቁጥቆጦች እና የሚያማምሩ በቀለማት በተሸቆጠቆጡ አበቦች የተሞላ ወብ ቦታ ነው…ግን ግራ አጋቢ ቦታ…፡፡
ከስር መሬት ከላይም መሬት ነው የሚታያት ..ግዙፍ ዋሻ መሰል ነው እንዳትል ምኑም ዋሻ አይመስልም…የተለመደው አይነት ምድርና ሰማይ ነው የሚታየኝ ብላም እንዳትገምት በቆመችበት መሬት እና ወደላይ አንጋጣ በምታየው መሬት(ሰማይ) መካከል ያለው ልዩነት የሚታወቀውን ሰማይ ከመሬት የሚርቀውን ያህል እርቆ አይደለም የሚገኘው…በግምት ከመቶ ሜትር አይበልጥም፣
‹‹ተገልብጠን ከምድር ስር ይሆን እንዴ ያለነው….?ማለቴ ምድርን ከታች ወደ ላይ የምናያት..ማለቴ አሁን ላለሁበት ሚስጥራዊ ቦታ ምድር ሰማይ ትሆን እንዴ…?›ስትል በውስጧ ብትጠይቅም ለመግለጽ የፈለገችውን ሀሳቡ ለእሷው ለራሷ ተምታታባት…
ትክክለኛ መልስ ለመግኘት ወደ እሱ ዞረችና ‹‹የት ነው ያለነው…..?›› ስትል ጠየቀችው
‹‹እቤቴ››አላት
አበባ.. ትንንሽ ቁጥቋጦች.. እዚህም እዛም የሚፈልቁ ምንጮች… ለጥ ያለ ማለቂያው የማይታወቅ ሜዳ ነው የሚታያት‹‹ ….ይሄ ነው ቤትህ…..?››
‹‹አይ አይደለም….››አላት ፍርጥም ብሎ
‹‹….ቆይ ቆይ…›› እሰከአሁን በሁኔታው ተመስጣ ልብ ያላለችውን ነገር አየች…., ልብስ ለብሶም ሆነ እንደዚህ ሙሉ እርቃኑን ፊት ለፊቷ ቆሞ አይታው አታውቅም ነበር….እስከዛሬ ግምሽ አካሉ በውሀ እንደተሸፈን ከእምብርቱ በላይ ነበር የምታየው….በጣም ተገረመች…የምታየው ፍጥረት ሰው አይደለም….….?ሰው ካልሆነ ታዲያ ምንድነው ከተባለ መልሱ ለመግለፅ በጣም ይከብዳል…?፡፡ ምን ተብሎ እንደምትገለጽው እሷም ምንም አልገባትም ..እንደዚህ አይነት ፍጡር እሷ አይታ አታውቅም…፡፡እግሮቹ ጣት አልባ ናቸው… ልሙጥ እና እንደሰፌድ የተዘረጉ…ወይም የዓሳ ክንፍ የመሰሉ …..ብልቱ ደግሞ ምታህለው…ያልተገረዘች የሴት ቂንጥር በሏት… ወደ ፊት እንደባቄላ ነው አጎንቁላ የምትታየው…
ወይኔ ጉዴ››አለችና ሳቋ አመለጣት…ያሳቀት …?ስንት ቀን አሁን ቢደፍረኝስ .. ?እያለች የተጨነቀችው አጉል መጨነቅ በምናቧ መጥቶባት ነው …‹‹አሁን በዚች እንኳን መድፈር ሽንቱንስ መሽናት ይችላል…?›› የሚል ሀሳብ አሰበችና ሳቋን አረዘመችው …
ሌላው በትክክል ሰው አይደለም ብላ ያሰበችው ዋናው ምክንያት ባለጭራ መሆኑ ነው..ጭራ አለው፡፡ ጭራው ደግሞ ከኃላ ከመቀመጫው የላይኛው ክፍል በቅሎ ወደታች በመሄድ በእግሮቹ መካከል አልፎ ወደፊት ተቆልምሟል.‹‹.እንደውም ከእውነተኛው ብልቱ ይልቅ ጭራውን እንደብልትነት ቢጠቀምበት ያዋጣዋል›› ስትል በውስጧ አሰበችና ድጋሚ ፈገግ አለች፡፡
‹‹ስለእኔ ተፈጥሮ አስበሽ እና ተመራምረሽ ጨረሽ?››ብሎ አስበረገጋት
‹‹አይ ምን እመራመራለሁ….?እንዲሁ አዲስ ነገር ሆኖብኝ ነው እንጂ..››በአፍረት መለሰችለት፡፡
‹‹ግን አልፈራሺኝም…››
‹ለምን እንዳልፈራውህ እኔንም ገርሞኛል…?››የእውነትም ለምን እንዳልተንቀጠቀጠች…?ለምን ፊቷን አዙራ ወደተንጣለለው ሜዳ ፈርጥጣ እንዳልሮጠች …?ለምን ያንን ጆሮ ሰንጣቂ የዘወትር ጩኸቷን እንዳላስነካችው ?ለእሷም አልገባትም…በቃ ከመደነቅና ከመገረም ውጭ በስሜቷ ላይ ያስከተለው የጥላቻውም ሆነ የፍራቻ ስሜት አልነበረም….
‹‹ስለዚህ ወደቤት መሄድ እንችላለን?›› አለና ጎንበስ ብሎ የቆመበትን አካባቢ መሬት በእጁ ሲነካ በአስገራሚ ፍጥነት አብረቅራቂ የወርቅ ሳጥን ከተሰነጠቀው መሬት ተፈልቅቆ ወጣ…..
‹‹ፓንትሽን አውልቂ››አላት
‹‹ለምን …? ምን አስበህ ነው…?››ስትል ግራ በተጋባ ስሜት ጠየቀችው፡
‹‹በዚህች ዕቃዬ ምን አስባለሁ?›› አላት እና አሳፈራት….እሷም ልትለው የፈለገችው በዚህ ዕቃህ ምን ለማድረግ አስበህ ነው…›ነበር..ያው ልቧን በትክክል ነው ያነበበው፡
‹‹እንደዚህ ሆነሽ ወደ እኔ ቤቴ መግባት አትችይም …..ጨረር ይጎዳሻል››
መከራከሯን ትታ ፓንቷን አወለቅችና እጆቾን እፍረቷ ላይ አደራርባ ቆምች….በእጁ ካንጠለጠለው ሳጥን የሆነ ሰማያዊ መልከ ያለው የጠፈርተኞችን የሚመስል ልብስ አወጣና አለበሳት….ሙሉ በሙሉ በልብሱ ተጠቀለለች …ከዛ እጁን ወደ ፊት ሲዘረጋ እስከአሁን እይታዋ ውስጥ ያልገባ ግን ከቆመችበት በአንድ ሜትር ርቀት የነበረ ወርቅማ የብረት በር ወለል ብሎ ተበረገደ……ከዛ እቤት ሳይሆን አይታ የማታውቀው በምናቧ እንኳን ገምታው የማታውቀው በተረት አለም ብቻ የሚገኝ አይነት ምትሀታዊ የዘመነ ፤ የፀዳ እና ፀጥ ረጭ ያለ ከተማ ከፊታቸው ተነጠፈ…‹‹..እርግጠኛ ነኝ ይሄ ሁሉ እስከአሁን የሆነውና ያያሁት እውነት አይደለም….ህልም ላይ ነኝ ..ገና ከእንቅልፌም አልተነሳሁም›› በማለት እራሷን ለማፅናናትም ለማረጋጋትም ሞከረች….፡፡ግን አልተሳካላትም፡፡
…ምንም አይነት እሱን መሳይም ሆነ ሌላ ፍጡር ሳታይ ነው በወርቃማ ብርሀን ያሸበረቀውን ከተማ ሰንጥቀው እሱ ቤት የደረሱት፡፡ ይዞት የገባው አንድ ከግድግዳው ሰማያዊው ብርሀን የሚተፋ ቤት ውስጥ ነው ፡፡አራት ክፍል ቢኖሩትም ሁሉም ባዶ ነበሩ..ምንም ዕቃ የላቸውም…
‹‹እንዴ…ይሄ ነው ቤትህ..?››
‹‹አዎ ምነው… ?
አልወደድሺውም…?››
‹‹አይ ቤቱማ አሪፍ ነው..ግን ባዶ እኮ ነው….ቤትን ቤት የሚያሰኘው ደግሞ ጣሪያና ግድግዳ ብቻ ሳይሆን ውስጡም የሚገኝ መጠቀሚያ ቁሳቁስ ነው….››
‹‹ባዶ…››አለና ወደውስጥ ገብቶ ግድግዳውን ተጠጋና ማብሪያ ማጥፊያ የሚመስል ነገር ተጫነ..
ተአምር ተፈጠረ…ድፍን ግድጋዳው እየተከፋፈተ ፍሪጅ …ቴሊቭዝን የመሳሰሉት ዕቃዎች… ወለሉም እየተከፈተ ጠረጵዛ ወንበር በመውጣት እቤቱን ሞሉት…. አደመቁት…..
ምንም እንዳልተፈጠረ ሁሉን ነገር ችላ ብሎ‹‹አረፍ በይ …››አላት
‹‹ምን ጉድ ነው….!!እስኪ መኝታ ቤትህን አሳየኝ..?››ሌላ ተአምር ለማየት ከመጓጓት የመነጨ ጥያቄ ጠየቀችው፡፡
መጣና እጁን ትከሻዋ ላይ ጣል አድርጎ ይዟት ሄደ …ወደ ቀጣዩ ክፍል….በተመሳሳይ ባዶ ነበር…
-‹‹የትኛውን ልጫን …››አለችው ግድግዳ ላይ ወደተለጠፉት ማብሪያ ማጥፊያ እጇን እየሰነዘረች
‹‹አልጋ ከፈለግሽ ነጩን ተጫኚ..››
ተጫነችው፡፡
ከእምነበረድ ይሁን ከእንጨት ይሰራ ለጊዜው መለየት ያቃታትን ነጭ አንሶላ ….ነጭ አልጋልብስ የለበሰ አልጋ ከወለሉ ውስጥ ተአምራዊ በሆነ ክስተት በመውጣት ተዘረጋ…..
‹‹ወይ እዚህ ላይስ መተኛት እፈልጋለሁ..››
‹‹ታዲያ ተኚያ …ማን ከለከለሽ››
‹‹ግን ይሄንን የለበስኩትን ደባሪ ልብስ ማውለቅ እችላለሁ?››
‹‹ቆይ… ››ብሎ ወደሳሎን ሄደ…. ምን እንዳደረገ ባታውቅም ወዲያው ሰማያዊው የነበረው የቤቱ መብራት ወደ ብርማ አይነት ተለወጠ…እሱ ተመልሶ እሷ ወዳለችበት መጣ
‹‹አሁን ትችያለሽ አውልቂው››አላት፡፡
‹‹ወይ እንዴት ደባሪ መሰለህ ››አለችና ለማውለቅ ብትሞክርም የተቆላለፉትን ነገሮች እንዴት ልትፈታታቸው እንደምችል አልገባትም... ምታደርገው ግራ ገባት
‹‹አቦ ምን ቆመህ ታየኛለህ ? ናና ከእዚህ ወጥመድ ውስጥ አውጣኝ እንጂ››ቁጣ የተቀላቀለበት ልመና አሰማች፡፡
፡
፡
#ክፍል_ስድስት
፡
፡
#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ
//
‹‹ጎሽ ጥለኸኝ አልተሰወርክም…አጠገቤ አለህ ማለት ነው? ››ስትል የእፎይታ ትንፋሽ ተነፈሰችና…በከፍተኛ ፍራቻ እና ጥርጣሬ ዓይኖቾን ገለጠች…..ወንዝ የሚባል ነገር ስራቸው የለም…የሲኦል ምልክትም አይታያትም…. በሳር ፤ በትናንሽ አረንጓዴ ቁጥቆጦች እና የሚያማምሩ በቀለማት በተሸቆጠቆጡ አበቦች የተሞላ ወብ ቦታ ነው…ግን ግራ አጋቢ ቦታ…፡፡
ከስር መሬት ከላይም መሬት ነው የሚታያት ..ግዙፍ ዋሻ መሰል ነው እንዳትል ምኑም ዋሻ አይመስልም…የተለመደው አይነት ምድርና ሰማይ ነው የሚታየኝ ብላም እንዳትገምት በቆመችበት መሬት እና ወደላይ አንጋጣ በምታየው መሬት(ሰማይ) መካከል ያለው ልዩነት የሚታወቀውን ሰማይ ከመሬት የሚርቀውን ያህል እርቆ አይደለም የሚገኘው…በግምት ከመቶ ሜትር አይበልጥም፣
‹‹ተገልብጠን ከምድር ስር ይሆን እንዴ ያለነው….?ማለቴ ምድርን ከታች ወደ ላይ የምናያት..ማለቴ አሁን ላለሁበት ሚስጥራዊ ቦታ ምድር ሰማይ ትሆን እንዴ…?›ስትል በውስጧ ብትጠይቅም ለመግለጽ የፈለገችውን ሀሳቡ ለእሷው ለራሷ ተምታታባት…
ትክክለኛ መልስ ለመግኘት ወደ እሱ ዞረችና ‹‹የት ነው ያለነው…..?›› ስትል ጠየቀችው
‹‹እቤቴ››አላት
አበባ.. ትንንሽ ቁጥቋጦች.. እዚህም እዛም የሚፈልቁ ምንጮች… ለጥ ያለ ማለቂያው የማይታወቅ ሜዳ ነው የሚታያት‹‹ ….ይሄ ነው ቤትህ…..?››
‹‹አይ አይደለም….››አላት ፍርጥም ብሎ
‹‹….ቆይ ቆይ…›› እሰከአሁን በሁኔታው ተመስጣ ልብ ያላለችውን ነገር አየች…., ልብስ ለብሶም ሆነ እንደዚህ ሙሉ እርቃኑን ፊት ለፊቷ ቆሞ አይታው አታውቅም ነበር….እስከዛሬ ግምሽ አካሉ በውሀ እንደተሸፈን ከእምብርቱ በላይ ነበር የምታየው….በጣም ተገረመች…የምታየው ፍጥረት ሰው አይደለም….….?ሰው ካልሆነ ታዲያ ምንድነው ከተባለ መልሱ ለመግለፅ በጣም ይከብዳል…?፡፡ ምን ተብሎ እንደምትገለጽው እሷም ምንም አልገባትም ..እንደዚህ አይነት ፍጡር እሷ አይታ አታውቅም…፡፡እግሮቹ ጣት አልባ ናቸው… ልሙጥ እና እንደሰፌድ የተዘረጉ…ወይም የዓሳ ክንፍ የመሰሉ …..ብልቱ ደግሞ ምታህለው…ያልተገረዘች የሴት ቂንጥር በሏት… ወደ ፊት እንደባቄላ ነው አጎንቁላ የምትታየው…
ወይኔ ጉዴ››አለችና ሳቋ አመለጣት…ያሳቀት …?ስንት ቀን አሁን ቢደፍረኝስ .. ?እያለች የተጨነቀችው አጉል መጨነቅ በምናቧ መጥቶባት ነው …‹‹አሁን በዚች እንኳን መድፈር ሽንቱንስ መሽናት ይችላል…?›› የሚል ሀሳብ አሰበችና ሳቋን አረዘመችው …
ሌላው በትክክል ሰው አይደለም ብላ ያሰበችው ዋናው ምክንያት ባለጭራ መሆኑ ነው..ጭራ አለው፡፡ ጭራው ደግሞ ከኃላ ከመቀመጫው የላይኛው ክፍል በቅሎ ወደታች በመሄድ በእግሮቹ መካከል አልፎ ወደፊት ተቆልምሟል.‹‹.እንደውም ከእውነተኛው ብልቱ ይልቅ ጭራውን እንደብልትነት ቢጠቀምበት ያዋጣዋል›› ስትል በውስጧ አሰበችና ድጋሚ ፈገግ አለች፡፡
‹‹ስለእኔ ተፈጥሮ አስበሽ እና ተመራምረሽ ጨረሽ?››ብሎ አስበረገጋት
‹‹አይ ምን እመራመራለሁ….?እንዲሁ አዲስ ነገር ሆኖብኝ ነው እንጂ..››በአፍረት መለሰችለት፡፡
‹‹ግን አልፈራሺኝም…››
‹ለምን እንዳልፈራውህ እኔንም ገርሞኛል…?››የእውነትም ለምን እንዳልተንቀጠቀጠች…?ለምን ፊቷን አዙራ ወደተንጣለለው ሜዳ ፈርጥጣ እንዳልሮጠች …?ለምን ያንን ጆሮ ሰንጣቂ የዘወትር ጩኸቷን እንዳላስነካችው ?ለእሷም አልገባትም…በቃ ከመደነቅና ከመገረም ውጭ በስሜቷ ላይ ያስከተለው የጥላቻውም ሆነ የፍራቻ ስሜት አልነበረም….
‹‹ስለዚህ ወደቤት መሄድ እንችላለን?›› አለና ጎንበስ ብሎ የቆመበትን አካባቢ መሬት በእጁ ሲነካ በአስገራሚ ፍጥነት አብረቅራቂ የወርቅ ሳጥን ከተሰነጠቀው መሬት ተፈልቅቆ ወጣ…..
‹‹ፓንትሽን አውልቂ››አላት
‹‹ለምን …? ምን አስበህ ነው…?››ስትል ግራ በተጋባ ስሜት ጠየቀችው፡
‹‹በዚህች ዕቃዬ ምን አስባለሁ?›› አላት እና አሳፈራት….እሷም ልትለው የፈለገችው በዚህ ዕቃህ ምን ለማድረግ አስበህ ነው…›ነበር..ያው ልቧን በትክክል ነው ያነበበው፡
‹‹እንደዚህ ሆነሽ ወደ እኔ ቤቴ መግባት አትችይም …..ጨረር ይጎዳሻል››
መከራከሯን ትታ ፓንቷን አወለቅችና እጆቾን እፍረቷ ላይ አደራርባ ቆምች….በእጁ ካንጠለጠለው ሳጥን የሆነ ሰማያዊ መልከ ያለው የጠፈርተኞችን የሚመስል ልብስ አወጣና አለበሳት….ሙሉ በሙሉ በልብሱ ተጠቀለለች …ከዛ እጁን ወደ ፊት ሲዘረጋ እስከአሁን እይታዋ ውስጥ ያልገባ ግን ከቆመችበት በአንድ ሜትር ርቀት የነበረ ወርቅማ የብረት በር ወለል ብሎ ተበረገደ……ከዛ እቤት ሳይሆን አይታ የማታውቀው በምናቧ እንኳን ገምታው የማታውቀው በተረት አለም ብቻ የሚገኝ አይነት ምትሀታዊ የዘመነ ፤ የፀዳ እና ፀጥ ረጭ ያለ ከተማ ከፊታቸው ተነጠፈ…‹‹..እርግጠኛ ነኝ ይሄ ሁሉ እስከአሁን የሆነውና ያያሁት እውነት አይደለም….ህልም ላይ ነኝ ..ገና ከእንቅልፌም አልተነሳሁም›› በማለት እራሷን ለማፅናናትም ለማረጋጋትም ሞከረች….፡፡ግን አልተሳካላትም፡፡
…ምንም አይነት እሱን መሳይም ሆነ ሌላ ፍጡር ሳታይ ነው በወርቃማ ብርሀን ያሸበረቀውን ከተማ ሰንጥቀው እሱ ቤት የደረሱት፡፡ ይዞት የገባው አንድ ከግድግዳው ሰማያዊው ብርሀን የሚተፋ ቤት ውስጥ ነው ፡፡አራት ክፍል ቢኖሩትም ሁሉም ባዶ ነበሩ..ምንም ዕቃ የላቸውም…
‹‹እንዴ…ይሄ ነው ቤትህ..?››
‹‹አዎ ምነው… ?
አልወደድሺውም…?››
‹‹አይ ቤቱማ አሪፍ ነው..ግን ባዶ እኮ ነው….ቤትን ቤት የሚያሰኘው ደግሞ ጣሪያና ግድግዳ ብቻ ሳይሆን ውስጡም የሚገኝ መጠቀሚያ ቁሳቁስ ነው….››
‹‹ባዶ…››አለና ወደውስጥ ገብቶ ግድግዳውን ተጠጋና ማብሪያ ማጥፊያ የሚመስል ነገር ተጫነ..
ተአምር ተፈጠረ…ድፍን ግድጋዳው እየተከፋፈተ ፍሪጅ …ቴሊቭዝን የመሳሰሉት ዕቃዎች… ወለሉም እየተከፈተ ጠረጵዛ ወንበር በመውጣት እቤቱን ሞሉት…. አደመቁት…..
ምንም እንዳልተፈጠረ ሁሉን ነገር ችላ ብሎ‹‹አረፍ በይ …››አላት
‹‹ምን ጉድ ነው….!!እስኪ መኝታ ቤትህን አሳየኝ..?››ሌላ ተአምር ለማየት ከመጓጓት የመነጨ ጥያቄ ጠየቀችው፡፡
መጣና እጁን ትከሻዋ ላይ ጣል አድርጎ ይዟት ሄደ …ወደ ቀጣዩ ክፍል….በተመሳሳይ ባዶ ነበር…
-‹‹የትኛውን ልጫን …››አለችው ግድግዳ ላይ ወደተለጠፉት ማብሪያ ማጥፊያ እጇን እየሰነዘረች
‹‹አልጋ ከፈለግሽ ነጩን ተጫኚ..››
ተጫነችው፡፡
ከእምነበረድ ይሁን ከእንጨት ይሰራ ለጊዜው መለየት ያቃታትን ነጭ አንሶላ ….ነጭ አልጋልብስ የለበሰ አልጋ ከወለሉ ውስጥ ተአምራዊ በሆነ ክስተት በመውጣት ተዘረጋ…..
‹‹ወይ እዚህ ላይስ መተኛት እፈልጋለሁ..››
‹‹ታዲያ ተኚያ …ማን ከለከለሽ››
‹‹ግን ይሄንን የለበስኩትን ደባሪ ልብስ ማውለቅ እችላለሁ?››
‹‹ቆይ… ››ብሎ ወደሳሎን ሄደ…. ምን እንዳደረገ ባታውቅም ወዲያው ሰማያዊው የነበረው የቤቱ መብራት ወደ ብርማ አይነት ተለወጠ…እሱ ተመልሶ እሷ ወዳለችበት መጣ
‹‹አሁን ትችያለሽ አውልቂው››አላት፡፡
‹‹ወይ እንዴት ደባሪ መሰለህ ››አለችና ለማውለቅ ብትሞክርም የተቆላለፉትን ነገሮች እንዴት ልትፈታታቸው እንደምችል አልገባትም... ምታደርገው ግራ ገባት
‹‹አቦ ምን ቆመህ ታየኛለህ ? ናና ከእዚህ ወጥመድ ውስጥ አውጣኝ እንጂ››ቁጣ የተቀላቀለበት ልመና አሰማች፡፡
👍119❤13🤔5👎2👏2😢1