አትሮኖስ
286K subscribers
118 photos
3 videos
41 files
567 links
╔╦╦╦═╦╗╔═╦═╦══╦═╗
║║║║╩╣╚╣═╣║║║║║╩╣
╚══╩═╩═╩═╩═╩╩╩
ግጥሞች አዳዲስና ቆየት ያሉ የታዋቂ ደራሲያን መፅሐፍቶችን በ PDF እንዲሁንም
ያልተነበቡ ድርሰቶችን ግጥሞችን ታሪኮችን ያገኙበታል።


Contact. @atronosebot
please dont touch the leave button.😔😳😳
Download Telegram
#ትኩሳት


#ክፍል_አስራ_ዘጠኝ


#በስብሐት_ገብረ_እግዚአብሔር


...«ዛሬ እንዳትለየኝ አለችኝ
እቅፍ አደረግኳት። ብዙ ነገር ልነግራት ፈለግኩ። ግን የመናገር
ጊዜ አልነበረም፡፡ እንደተቃቀፍን እንቅልፍ አቀፈን .

ቀኑን በብዙ ስትስቅና «ዥማንፉ» የሚለውን ፈረንሳይኛዋን
ስትደጋግም ዋለች፡፡ እኔ አንድ የሆነ ነገር በምመለከትበት ጊዜ እሷ ያላወቅኩባት መስሏት ስትመለከተኝ ብዙ ጊዜ ተሰማኝ፡፡ እንደዚህ ስትመለከተኝ፣ አንድ ሁለት ጊዜ ድንገት ዘወር ብዬ አየኋት ያዘነና የናፈቀ ገፅታ አየሁባት፡ በአይኗ እንደምትጠጣኝ ይመስል ነበር፡፡ የማላውቀው እፍረት ተሰማኝ። ይህን ያህል የሚወደድ ምን አለኝና ነው?

ማታ ከእራት በኋላ «ለቫር ሳን ሚሼልኦ ወሰድኳትና አንድ
ሁካታ ያነሰበት ካፌ ገብተን ቢራ ካዘዝን በኋላ፣ እጄን ዘርግቼ
ጉንጫን አየዳሰስኩ
«ዛሬ ምን ሆነሻል?» አልኳት
«እኔ እንጃ፡ አዝኛለሁ። እዝን ብያለሁ» አለችና፣ እጄን በሁለት
እጇ ይዛ ሳመችው:: አሁንም እፍረት ተሰማኝ። እጄን መሳሟ
ሳይሆን አሳሳሟ
«አውራልኝ አለችኝ
«ስለምን ላውራልሽ?»
«ስላንተ። ዛሬ ውስጤ አንድ ትልቅ ቀፎ ተከፍቷል፡ ባዶውን
ነው፡፡ ባንተ ልሞላው እፈልጋለው:: ከልጅነት ጀምሮ አውራልኝ።
ምንም ሳታስቀር በሙሉ ንገረኝ፡፡»
ጧት ልነግራት ፈልጌ የነበረውን ነገርኳት። ፍርሀቴን፣ ስጋቲን፣
ጭንቀቴን ዘረዘርኩላት። ስጨርስ አንድ እጄን እያሻሽች
«ውይ የኔ ካስትሮ! ሰው ነህ ለካ!» አለችኝ፡፡ በሊላው እጄ ፀጉሯን እየደባበስኩ
«ምን መስዬሽ ኖሯል?» አልኳት
«የማትፈራ፣ የማትጨነቅ፣ የማትታመም፣ የማትሞት መስለህ
ነበር ምትታየኝ፡፡ አትሳቅብኝ! ሰው እንደመሆንህ፣ ሟች መሆንህን
አውቅ ነበር። ግን እውቀት ዋጋ የለውም፡፡ ስሜት ነው ዋናው፡፡
ስሜቴ ደሞ ስላንተ ሌላ ነገር ነበር የሚነግረኝ፡፡ ተው አትሳቅ
እየው፤ እንዲህ አስበው እስቲ።
ጊ ደ ሞፓሳን የደረሰውን
«ቤል አሚ» የተባለውን ልብወለድ ታሪክ አንብበህ የለ? ቤል አሚ
እጅግ የተዋበ፣ ሽንቅጥ የሆነ ጎረምሳ ነው። ታስታውስ የለ፣ መፅሀፉ የሚያልቀው፥ ቤተ ክርስቲያን ውስጥ ይሄ አይናማ ጎበዝ በብዙ ሰው እየተደነቀ፣ ሀብታሟን ልጅ ሲያገባ ቄሱ ወዳሉበት ሲራመድ ነው።
ታድያ ቤል አሚን ባስታወስከው ጊዜ፤ ሲያረጅ ወይ ሲታመም ወይ
ሲሞት አስበኸው ታውቃለህ? ሁልጊዜ ወጣት እንደሆነ አይደለም የሚታይህ? . . እንደሱ ነው አየህ፡፡ ሳስብህ፣ ዘለኣለም ወጣት፣ ዘለአለም ጤነኛ ዘለአለም ኩሩ ሆነህ ነበር የምትታየኝ»

«አሁን ግን ሰው ሆነህ ትታየኝ ጀመር፡፡ ጧት እንደነገርኩህ!
ማንም ሰው፣ ምንም ነገር ሊያሸንፍህ የማይችል ይመስለኝ ነበር፡፡ የብረት ሰው ትመስለኝ ነበር። አሁን ግን እንደ ቢራቢሮ ሆነህ ነው የምትታየኝ። በጣም ቆንጆ ነህ፣ ነጭ ፈገግታህ ጥቁር ፊትህ ላይ ሲያበራ፣ አልማዝ መሳይ አይኖችህ በሳቅ ብልጭ ብልጭ ሲሉ ወይም በምኞት ሲግሉ፣ በወጣትነት ፀሀይ ውስጥ የሚበር ውብ ቢራቢሮ ነህ። እንደ ቢራቢሮ በቀላሉ የምትጠፋ ነህ። ከዚህ ወጥተን መንገድ ስንሻገር መኪና ቢገጭህ ትሞታለህ፣ በባቡር ስንሄድ ከሌላ ባቡር ጋር ብንጋጭ ትሰባበራለህ፣ በኤሮፕላን ብትበር፣ እና
ኤሮፕላኑ አንድ ነገር ቢሆን፣ እንደ ወረቀት ትቦጫጨቃለህ፡፡
አንዲት ጥይት ብትመታሀ ትሞታለህ፡፡ ...»
«አይዞሽ አይዞሽ»

«ምን አይዞሽ ትለኛለህ? መሞትህ ነው ። አይታይህም?»
ሌላውም ይሞታል ኮ፡፡ አንቺም ጭምር»

ሌላውን የት አውቀዋለሁ? ምኔ ነው? አንተ ግን አንተ ነህ፡፡
ማንንም አትፈራም፡፡ እንደ ሲራኖ ደ ቤርዤራክ ነህ፡፡ ጀግና ነህ።
ወንድ ነህ። የኔ ነህ። እወድሀለሁ፡፡ የኔን የራሴን ማርጀትና መሞት
በሀሳቤ ልቀበለው እችላለሁ፡፡ አንተ ታረጃለሀ ትሞታለህ ቢሉኝ ግን አልቀበልም፡፡ ይሄ አንፀባራቂ ፈገግታህ ሲጨልም፣ እነዚህ ብሩህ አይኖችህ ሲፈዙ ለማየት አልፈልግም፡፡ አልቀበልም፡፡ እምቢዮ! ኤክስ ውስጥ ፀሀይ እየሞቁ በባዶ ብርጭቆ አይን ሞታቸውን ከሚመለከቱት ሽማግሌዎች አንዱ እንድትሆን እልፈቅድልህም፡፡
አልፈቅድልህም! ይገባሀል? አልፈቅድልህም! ወጣት መአዛህን
ወስደው የእርጅና ሽታ ሲለጥፉብህ እንዳትቀበል!»

«እሺ የኔ ቆንጆ፣ እሺ ይቅር፣ ረጋ በይ አይዞሽ። አሁን
ወጣት ነኝ፣ ካንቺ ጋር ነኝ»
«አሁን ብቻ ነዋ!»
«አሁን ብቻ አይደለም፡፡ አይዞሽ አይዞሽ»
«ከዚህ ውሰድኝ»
«እሺ»
«ውሰደኝና ልብሴን አውልቀህ እቅፍ አርገኝ። ከድሮ ይበልጥ
እቀፈኝ፡፡ ፍርሀት ይዞኛል፣ ሀዘን ተጫጭኖኛል፡፡ መወደድ መታቀፍ
እፈልጋለሁ፡፡»
«እሺ የኔ ሲልቪ»
«እንሂዱ»
«እሺ»
«በል እንሂድ»
«እሺ የኔ ፍቅር፣ ይኸው መሄዳችን ነው።»
ሆቴላችን እንደደረስን፣ ቶሎ ልብሷን አውልቄ እቅፍ አረግኳት
«እወድሻለሁ የኔ ፍቅር፣ ከልቤ እወድሻለሁ» አልኳት
«በላ አሳየኝ፣ በስጋህ አሳየኝ፣ በነብስህ አሳየኝ
«ይኸው የኔ ፍቅር፣ ይኸው»
በጭለማው፣ በሹክሹክታ
«አማልክቱ ሁሉ ሞተዋል፡፡ እኛ ብቻ ነን የቀረነው:: አንተ ለኔ
አምላኬ ነህ። እኔስ አምላክህ ነኝ?»
«አዎን አምላኬ ነሽ»
«ድገምልኝ»
«አምላኬ ነሽ፡፡ አምላኬ ነሽ፡ የኔ አምላክ ነሽ»
አፌ ውስጥ እየተነፈሰች «በላ መስዋእት አቅርብልኝ»
«እሺ። ምን መስዋእት ትፈልጊያለሽ?»
«ሁልጊዜ ከላይ ሆነህ ወደታች ታየኛለህ፡፡ ዛሬ ታች ውረድና
እኔ አዘቅዝቄ ልመልከትህ ክብርህን ሰዋልኝ»
«እሺ፡፡ ክብሬን ውሰጂው:: ላንቺ ክብሬን ብሰዋ ደስ ይለኛል።
በጭለማው በሹክሹክታ
«በላ»
«እዘዢኝ»
«እንዳታመነታ ልባርግ»
«ዝግጁ ነኝ፡፡ ንገሪኝ፡፡ ምን ላርግሽ? ምን ልሁንልሽ?»
«ወደታች ውረድና ከእግሬ ጥፍር ጀምረህ እየሳምከኝ አየላስከኝ
ወደላይ ና፡፡»
«እሺ የኔ መቤት»
ከእግሯ ጥፍር ጀምሬ እስከ አፏ ሳምኳት ላስኳት። በአፉ
ተቀበለችኝና እየሳመችኝ፣ በጭለማው በሹክሹክታ
«ጥሩ ነበር፣ ግሩም ነበር፡፡ ግን አይበቃም። በጭራሽ
አይበቃኝም» አለችኝ
«የፈለግሽውን ንገሪኝ። አደርገዋለሁ፡፡ አምላኬ ነሽ»
«እንዴት ነው ጭኖቼ መሀል ስመኘኝ የማታውቀው?»
«አድርጌው አላውቅማ»
«በጭራሽ አርገኸው አታውቅም?»
«በጭራሽ»
«በጭለማው፣ በሹክሹክታ
ውረድና ጭኖቼ
ሳመኝ። ልክ አፌን
እንደምትስመኝ አርገህ ሳመኝ፤ በከንፈርህ፣ በጥርስህ፣ በምላስህ
ሳመኝ፡፡ አምላክህ ነኝ፡፡ ካንተ ምፈልገው መስዋእት እሱ ነው::»
«እሺ»
ሳረገው አልቀፈፈኝም፡፡ በጭራሽ አልቀፈፈኝም፡፡ እንዲያውም
በጣም ነው ደስ ያለኝ። ስስማት፣ በማክበርና በማምለክ ስስማት፣
እያቃሰተች ራሴን ስታሻሽ ቆይታ ቆይታ፣ በጭንቅላቴ ስባ ወደ ላይ
ወሰደችኝና
«ትወደኛለህ፡፡ በእውነት ትወደኛለህ፡፡ እንዴት ግሩም ነው!
ትወደኛለህ፡፡ አንተ እኔን ትወደኛለህ!» አያለች ስታቃስት
«አይዞሽ አይዞሽ፣ ያንቺው ነኝ» እያልኩ አባበልኳት
«እንዴት እድለኛ ነኝ! እንደ ዛሬ ደስ ብሎኝ ኣያውቅም»
«ገዝተሽኛል»
«ገዝቼሀለሁ። እወድሀለሁ፡፡ አንተም ገዝተኸኛል። እንዴት ጥሩ
«አሁን ተኚ። ደክሞሻል፡፡»
«እሺ፣ አቅፈህ አስተኛኝ።»
ከትንሽ ዝምታ በኋላ
«እንደዚህ ጥሩ ልጅ ሆነህ ሽርሙጣ መውደድህ አያሳዝንም?»
👍21😁1
#ትኩሳት


#ክፍል_ሀያ


#በስብሐት_ገብረ_እግዚአብሔር


...ዛሬ ግን ሲልቪ አላዘነችም፡
የተለመደው ሳቋ አይኖቿን እየደጋገመ ያበራቸዋል፣ ከንፈሮቿን
ያለማቋረጥ ይከፋፍታቸዋል። እራት ላይ ሁለት ጠርሙስ ወይን
ጠጥተን ነበር፣ አሁን ሁለት ጠርሙስ ቢራ ስንቀላቅልበት ጊዜ ወሬአችን ሞቀ.
«አቤት እንዴት ነው ያማርሽኝ!» አልኳት
«ሱሪ ስለለበስኩ ነው?»
«ግማሽ»
«ግማሽስ?»
«ከስሩ ሙታንቲ ስላላረግሽ ነው። ለምን ሙታንቲ
አልለበስሽም?»
«ለምን ይመስልሀል?» አይኖቿኸ ውስጥ ያ የሚያሰክረኝ ቅንዝር
ይታያል
«እኔ እንጃ፡፡ ለምንድነው?»
«ግማሹ አንተ እንዳሁን እንድትመኘኝ ነው»
«ግማሹስ?»
«አይ! አይነገርም፡፡ በብርሀን አይነገርም፡፡» የአፏ አከፋፈት!
«ንገሪኝ። ንገሪኝ፡፡ ለምንድነው ሙታንቲ ሳትለብሺ
የመጣሽው?»
«ልንገርህ?»
«ንገሪኝ!»
«ተው ይቆጭሀል!»
«ንገሪኝ!»
«ሱሪው ጠባብ ነው:: ያለሙታንቲ ስለብሰው ቂጤ የበለጠ
አያምርም? የበለጠ አያስጐመጅም?»
«ያንገበግባል»
«እና ስራመድ ወንዶቹ እንዴት እንደሚያዩኝ አላየህም?»
ቅናቱ ጀመረኝ
«አላየሁም» አልኳት
«ያዩኝ ነበር። ይታወቀኛል'ኮ፡፡ ስራመድ ከኋላዬ ሆነው
ሲያዩኝ፣ አይናቸው ከዳሌዬ ጋር ሲንከራተት ይታወቀኛል፡፡»
«እና ምን ይሰማሻል?»
«ደስ ይለኛል፣ ዛሬ በሀይል አላምርም?»
«ታምሪያለሽ፡፡ ግን ከሌላ ጊዜ ይበልጥ እንደምታምሪ እንዴት
አወቅሽ?»
«ይታወቀኛላ»
«እንዴት ይታወቅሻል?»
«ውስጤ ይሰማኛል፡፡ አየህ፣ ዛሬ ወንድ አምሮኛል። በሀይል
አምሮኛል። ስለዚህ፣ ፊቴ፣ ገላዬ፣ አረማመዴ ሁሉ ወንድ ሊስብ
ይፈልጋል። ስለዚህ በሀይል አምራለሁ።»
የትላንቱ ሌሊት አይነት ቅናት ውስጤ መንቀሳቀስ ጀመረ
«እንዴት ነው የምታየኝ አንተ!?»
«እንዴት ነው?»
«አማርኩህ መሰለኝ»
«በጣም አምረሽኛል»
«እኔም አምረኸኛል። ግን ዛሬስ ልታጠግበኝ የምትችል
ኣይመስ ለኝም፡፡ ዛሬ የያዘኝ ምኞት እንደ እሳት ነው:: ለማጥፋት
ብዙ ብዙ ውሀ ይፈልጋል፡፡ አንተ ብቻህን ልታጠፋልኝ መቻልህን
እንጃ የትላንቱ ሌሊት ቅናት እንቅ አደረገኝ፣ ሌላ
ወንድ እንዲያምራት ተመኘሁ
«እና ምን ትፈልጊያለሽ? ንገሪኝ እስቲ»
«ትቆጣለሁ!»
«ይልቅ ንገሪኝ»
«ንገሪኝ፡፡ ምን ያምርሻል?»
«ወንድ ያምረኛል። ሶስት አራት ቆንጆ ቆንጆ ወንድ ባጎኝ
እፈቅዳለሁ፡፡
«እንድ አይበቃሽም?»
«አይበቃኝም። አልጠግብም፡፡ ዛሬስ አንተ እንኳ ብትሆን
እታጠግበኝም፡፡»
እና ምን ይሻላል?»
«አንተ ባትኖር መፍትሄ ነበረው»
«እኔ ባልኖር እንዲህ አይነት ስሜት ሲመጣብሽ ምን ታረጊያለሽ?»
ጠረጴዛ ላይ ያለውን ጥቁር ቦርሳዋን መታ እያደረገች
«ማስታወሻ ደብተሬ ውስጥ የቴሌፎን ቁጥሮች አሉኝ»

«የወንዶችሽ?»

ጭንቅላቷን በኣዎንታ ነቀነቀች
«አሁንም ልትደውይሳቸው ትችያለሽ' ኮ»– ደነገጠኩ፡፡ እንዲህ ማለት መቼ ፈለግኩና? በጭራሽ አልፈለግኩም፡፡ ምን ነካኝ? እስቲ
አሁን እንዲህ ይባላል? ምን አይነት ጉድ ውስጥ ነው የገባሁት!?
እጇን ቶሎ ሰዳ እጄን በሀይል ጨበጠች። አይኖቿ ውብ ብርሀን
ለበሱ፣ ቀያይ ከንፈሮቿን በምላሷ አረጠበች፣ ከውስጥ ወተት መሳይ
ጥርሶቿ ይብለጨለጫሉ፡፡ ማማሯ ማስጐምጀቷ ስሜት ባፈነው
ወፍራም ድምፅዋ
«ትፈቅድልኛለህ? ልደውልላቸው? አትጠላኝም? በኋላ
አታባርረኝም? ልደውልላቸው? አንተን ነው የምወደው:: ግን በሽተኛ ነኝ። መሄድ አለብኝ። ግን የምትጠላኝ ከሆነ አልሄድም፡፡ ልደውል?
ልሂድ? ትፈቅዳለህ?»
አቅበጠበጣት፡፡ አሳዘነችኝ፡፡ ደሞ በሀይል አማረችኝ፡፡ እንደዛሬ
አምራኝ አታውቅም፡፡ ግን አሁን ላገኛት ኣልፈለግኩም፡፡
ከሆነልኝና ወደ ሌሎቹ ከሄደችልኝ፣ ከሌላ ጋር መሆኗን እያሰብኩ
መሰቃየት አማረኝ፡፡ እሷ ወንዶች ያማሯትን ያህል እኔ መሰቃየት
አማረኝ፣ መቅናት፣ መቃጠል አሰኘኝ፡፡ ራሲንም ለማወቅ ተጠማሁ፡፡ማን ነኝ? ፍቅር ይዞኛል? እና ፍቅር ምንድነው? ቅናትስ? የሁለቱስ ዝምድና እንዴት ያለ ነው የሚያፈቅሩዋት ሴት ጥብቅ ያለ ሱሪ ለብሳ ሌላ ወንድ ፍለጋ ስትሄድ ማየት፣ ሄዳ ስትመለስ፣ ቢያንስ ቢያንስ ሶስት ወንድ በየተራ ሲደሰትባት፣ ሲስማት፣ ሲልሳት፣ ሲያለፋት ከቆየ በኋላ፣ ከዚያ ተቀብለው ይህን ሁሉ እያወቁ ያችን የሚወዷትን ሴት ማቀፍ፣
መሳም፣ መላስ፣ በቅናት እየነደዱ ሴትዮዋን መተኛት
ይሄ ደሞ ከሁሉ የጠለቀ፣ ከሁሉ የላቀ፣ ከሁሉ የደመቀ ከሁሉ የጨለመ፣ የሚያቃጥል፣ የሚበርድ፣ የሚያስደስት፣ የሚያበሳጭ፣ የሚገድል፣
የሚያድን፤ ከስሜት በላይ የሆነ ስሜት ይሰጥ ይሆን?

«ልሂድ ትፈቅዳለህ?» አለችኝ
«ብኋላ የት አገኝሻለሁ?» አልኳት፡፡ ድምፁ የኔው አይመስልም
ሆቴላችን»
«ከስንት ሰአት በኋላ?»
ሰአቷን አየች
«ከአምስት ሰአት በኋላ፡፡ ልክ በሰባት» አለችኝ
በጠረጴዛው ተንጠራርታ ግምባሬን ሳመችኝ
«አግባኝ፡፡ እባክህን አግባኝ! ይቅር እሺ። ይቅር፡፡ “nous nous
reverons bientôt'' (“አሁን አሁን እንገናኛለን») ብላ እጄን ስማኝ ተነስታ ከካፌው ወጣች። ስትሄድ ረዥም አንገቷን እያወዛወዘችው፣
ወደኋላዋ የተለቀቀው ፀጉሯ ዥዋዥዌ ይጫወታል። ከቀጭን ወገቧ ስር ወፍራም ዳሌዋ ይወዛወዛል፣ ስትራመድ ጠባቡ ሱሪዋ የቂጧን ውብ ቅርፅ ያሳያል ከውስጥ ሙታንቲ አልለበሰችም!!
ከጥቂት ደቂቃ በኋላ፣ ከካፌው ወጥቼ ሲኒማ ገባሁ
እንደ አጋጣሚ ኢንግግር በርግማን የተባለው ገናና የስዊድን ፊልም አዘጋጅ የፈጠረው «ሰባተኛው ማህተም» የተባለው እጅግ የተመሰገነ ፊልም ነበር አንድ የጥንት ስዊድናዊ አርበኛ፣ ከኢየሩሳሌም የመስቀል ዘመቻ ሲመለስ፣ ልክ የክርስትያን ኢውርፓን መሬት እንደረገጠ፣ ሞት የተራ ሰው መልክ ለብሶ ይመጣና
«ልወስድህ መጥቻለሁ» ይለዋል
አርበኛው
«አሁን ካንተ ጋር መምጣት አይሆንልኝም፡፡
ላደርጋቸው የሚገባኝ፣ ግን ገና ያልፈጸምኳቸው፣ አንድ ሁለት ጉዳዮች አሉ» ይለዋል
ሞት «ልወስዳቸው ስመጣ ሰዎች ሁሉ ይህንኑ ነው የሚሉኝ ይለዋል

አርበኛው «እኔ ግን እውነቴን ነው:: ላደርጋቸው የሚገባኝ
ነገሮች አሉ፡፡ . . . በቼስ ጨዋታ የሚችልህ የለም ይባላል» ይለዋል
«እውነት ነው»
አርበኛው «እኔ ግን የምችልህ ይመስለኛል። ይዋጣልን እስቲ።
ምን ቸገረህ? በመጨረሻ ማሸነፍህ አይቀር» ይለዋል
“እሺ እንጫወት»
“እስክሽነፍ ድረስ ልኑር ፍቀድልኝና፣ እኔን ለማሸነፍ ምን ያህል ጊዜ እንደሚወስድብህ እናያለን
«እሺ»
ጨዋታቸውን ይጀምራሉ
እንደሱ ያለ አስደናቂ ፊልም አይቼ አላውቅም።
እጭለማው ውስጥ ሲልቪን አንድ አምስት ጊዜ ብቻ በድንገት
እያስታወስኳት በሀይል ድንግጥ አልኩ:: ግን ያኔውኑ ፊልሙ ከሀሳቢ ያባርራታል። ግሩም ፊልም ነበር። ሲያልቅ ደገምኩት፡፡ በጭራሽ አልጠገብኩትም፡፡ ግን ሶስተኛ ላየው አልቻልኩም፡፡ ሲኒማ ቤቱ ተዘጋ፡፡ ወጥቼ ስለፊልሙ እያሰላሰልኩ ስራመድ ሰአቴን አየሁ። ሰባት ከሩብ ልቤ በሀይል መምታት ጀመረ፡፡ ባለሁበት ቆምኩ።ሲልቪ እንዴት እስካሁን የሷ ሀሳብ አላስጨነቀኝም? ይሄ
ኢንግማር በርግማን እንዴት ያለ ፍፁም አርቲስት ቢሆን ነው?!
እስካሁን ከሱ ጋር ነበርኩ። ከሱ ጋር ስለሞትና ስለህይወት ሳስብ፣
👍24
#ትኩሳት


#ክፍል_ሀያ_አንድ


#በስብሐት_ገብረ_እግዚአብሔር

...ስለነሱ ስትነግሪኝ ለምን ልቤ እንደሚጠፋ ልንገርሽ»

«ለምንድነው?»
«ከነገርሽኝ ነገሩን አወቅኩት ማለት ነው። ካወቅኩት ደሞ
አያስፈራኝም፡፡ ጭለማ ሲሆን፣ ምን ይመጣብኝ ይሆን? በማለት
እፈራለሁ እንጂ፡ በብርሀን ካየሁት ማንም ሰው ቢሆን አያስፈራኝም፡፡ ማለቴ ሳላውቀው አንድ ሰው ይተኛሽ ይሆን? ብዬ እፈራለሁ እንጂ፣ እያወቅኩ ከሆነ፣ አስር ሰው ቢተኛሽም አልፈራም፡፡
እያወቅኩት ከተደረገ ድርጊቱ የኔ ሆነ ማለት ነው፡፡ የኔ ከሆነ
ሊጎዳኝ አይችልም .. እንዴት እንደተኙሽ ስትነግሪኝ፣ እኔ እነሱን
ሆኜ ተኛሁሽ፣ ተወስዶብኝ የነበረውን ገላሽን፣ ቃላትን መለሱልኝ ማለት ነው። ... ስለዚህ ነው የተኙሽ ወንዶች ቁጥር እንደመብዛቱ መጠን የኔ ደስታ የሚበዛው፡፡»

«አልገባኝም»
«አየሽ፣ ማንም አልተኛሽም ማለት ያስፈራኛል፡፡ ጭለማ ውስጥ
ነኝ ማለት ነው። .. አንድ ሰው ተኝቶኛል ብትይ፡ ትንሽ ይሻለኛል። ግን አሁንም አንድ ሰው ደብቀሽኝ ሊሆን ይችላል። አራት ወንድ ተኛኝ ብትይ የበለጠ ይሻላል። ምክንያቱም የደበቅሽኝ ነገር
የለም ማለት ነው። ስለዚህ መፍራት አያስፈልገኝም፤ ምክንያቱም የተወሰደብኝ ሁሉ ተመልሶልኝ አቅፌዋለሁ ማለት ነው፡፡»

«ገባኝ። አንድ ጥያቄ፡፡»
«ምን?»
«እኔም እነሱም ያው ነን ካልክ፣ ምን እንዳረጉኝ ባታውቅስ ምን
ልዩነት ያመጣል?»
«ይህን አትጠይቂኝ። ላስረዳሽ አልችልም፡፡ እኔም ራሴ
አይገባኝም፡፡ ምናልባት እኔም እነሱም ያው ለመሆን የምንችለው፣ እነሱ ያረጉትን ካወቅኩ ብቻ ይሆናል፡፡»
ዝም ዝም ሆነ፡፡ ታችኛ ከንፈሯን እየነከለች ስታስብ ቆየች
«ልንገርህ?» አለች
«ምን?»
«እኔ በበኩሌ ሌላ ሆኖ ነው የሚታየኝ»
እንዴት ሆኖ ነው ሚታይሽ?»
“በጭራሽ በሽታ አልያዘህም፡፡ እንደሌላ ወንድ ነህ»
ሌሎች ወንዶች ከሌላ ጋር ተኝተሽ ነይልኝ ይሉሻል?»
« አይሉኝም
እኔም የሚሉሽ አልመሰለኝም
«ስማኝ እንግዲህ:: ክርክሩን ተውና አድምጠኝ። በግብረ ስጋ
በኩል ስለሴቶች ታውቃለህ እንጂ፣ በጥቅሉ ስለ ሴቶች ምን
ታውቃለህ? እነሱ ካልነገሩሀ ስለነሱ ለማወቅ አትችልም፡፡ እነሱ ደሞ የውስጡን አይነግሩህም። ለምሳሌ፣ አንተ እኔን ከሌሎች እየተቀበልክ እንደምትደሰትብኝ ለሰው ትነግራለህ ይመስልሀል? ለማንም አትናገርም። ሌሎችም ወንዶች ውስጣዊውን ምስጢር አይነግሩህም፡፡
ስለዚህ ሴት ካልሆንክ ወንዶችን በዚህ በኩል ልታውቃቸው
አትችልም። እኔ ልንገርህ

“ብዙ ጋብቻዎች መቀዝቀዝ ሲጀምሩ፣ ሴትዮዋ ተስፋ
ትቆርጥና ውሽማ ትይዛለች። ባልየው ሲያውቅ ምን እንደሚያደርግ ታውቃለህ? ለጊዜው ይናደዳል፣ ይደበድባታል፣ እንፋታ ይላል።
በኋላ ግን ታርቀው ይቅርታ ያደርግላትና፣ በጣም ሊወዳት
ይጀምራል። ቀዝቅዞ የነበረው ጋብቻ ይሞቃል፣ ይታደሳል። ለምን? ሴትዮዋ ሌላ ወንድ ጋ ስለሄደች ነው

መንገድ ዳር ውጣና ጎረምሶቹን ሴት ሲያድኑ እያቸው።
ሴትዮዋ በጣም ጨዋ ከመሰለቻቸው፣ ምንም ቆንጆ ብትሆን አይከተሏትም፡፡ ትንሽ በመጠኑ ስድ ብጤ ከሆነች ግን
አስተያየቷ፣ አረማመዷ፣ ወይም አለባበሷ በቂ ልቅነት ካሳየ
ጎረምሶቹ ይሻሟታል። በቀላሉ ሊያገኙዋት ስለሚችሉ ብቻ
እንዳይመስልህ፡፡ ዋናው ምክንያት ሌላ ነው። ባለጌ ከመሰለች፣
እንግዲያው ብዙ ወንድ ኣውቃለች ማለት ነው:: ለዚህ ነው
የሚሻሟት
«እየው፣ የሰው ልጅ ፍጥረቱ እንደዚህ ነው:: አንድ የለመድከው ሰው ሊለይህ የሆነ እንደሆነ ልትወደው ትጀምራለህ።
ለህይወትህ የሚያስፈራ በሽታ የያዘህ የመሰለህ እንደሆነ፣ በፊት
ከምንም የማትቆጥራትን ህይወትህን በሀይል ልትወዳት ትጀምራለህ

ሀኪም ጨው እንዳትበላ ያዘዘህ : እንደሆነ፣ ጨው ምንኛ ግሩም
ቅመም እንደሆነ ትገነዘባለህ ሴትህ ወደሌላ የሄደችብህ
እንደሆነ፣ እንዴት ቆንጆ እንደሆነች እንደ አዲስ ሊታይህ ይጀምራል
በራሲ የሚያጋጥመኝን ለምን አልነግርህም? በዚህ ሰሞን
ከማያቸው ወንዶች ሁለቱ እንዴት እንደሚሆኑ ላጫውትህ፡፡ ሁለቱም
ያው ናቸው። ስለዚህ ስለአንዱ ልንገርህ፡፡ ማርሴል ይባላል። በጣም ቆንጆ ነው። ብዙ ሴት ያወቀ ወጣት ነው። ማታ ከእራት በኋላ ካንተ እንደተለየሁ፣ በቀጥታ ወደሱ የሄድኩ እንደሆነ፣ ንፁህ ነኝ፣ የማንም ላብ አልነካኝም፣ ጠረኔ የራሴ ነው፡፡ ልብሴን አስወልቆ ያቅፈኛል! በደምብ ያስደስተኛል፡፡ አንዳንዴ ታድያ፣ ካንተ እንደትለየሁ በቀጥታ ወደሱ እልሄድም፡፡ በፊት ሌላጋ እደርሳለሁ። እና እሱጋ ስሄድ የሌላ ወንድ ላብ ነክቶኛል፣ ጠረኔ የብቻዬ ሳይሆን ከጎረምሳ ጠረን ጋር ተቀላቅሏል። አሁንም ልብሴን ያስወልቀኝና ያቅፈኛል፤ ግን እንደነብር ይሆናል፣ ይጨፈልቀኛል፣ ይነክሰኛል።
ስለሌላ ወንድ አንነጋገርም ግን ሌላጋ እንደነበርኩ በማወቁ የበለጠ እንደሚጣፍጠው ግልፅ ነው፡፡ ይታይሀል?"

«በሚገባ! እና እኔ እንዲህ የምሆንበት ምክንያቱ ምን
ይመስልሻል?» ቀላል ነው። አንደኛ፣ ሌላ ወንድ ከተኛኝ ቆንጆ ነኝ ማለት ነው። ብዙዎች ከተኙኝ እጅግ በጣም ቆንጆ ነኝ፡፡ ስለዚህ የቀለጠ ትፈልገኛለህ፡፡ ሁለተኛ፣ ሌላው ተኝቶኝ አንተ ቀጥለህ ከተኛኸኝ፣ ከሱ ቀምተህ ወሰድከኝ ማለት ነው:: እኔ በሀይል ቆንጆ ሆኜ ከሌሎቹ ሁሉ ቀምተህ ከወሰድከኝ፣ ከሌሎቹ ሁሉ የበለጠ ወንድ ነህ።በወንድነት ከሁሉ በላይ ሆንክ፣ ስለዚህ ደስ ይልሀል፡፡ በጣም ደስ ይልሀል። ወንዶች ሁላችሁም እንደሱ ናችሁ። ግን አየችኝ..

«ግን ምን?» አልኳት
አብዛኛዎቹ ወንዶች ውጪውን ጎበዝ ቢመስሉም ውስጡን ፈሪ
ናቸው፡፡ የውስጥ ስሜታቸውን አይተው መቀበል ይፈራሉ። ስለዚህ ከራሳቸው ይደብቁታል። ሁሉም ወንድ አብዛኛው ወንድ ልበል የራሱን ሴት ሌሎች ሲቀምሱበትና እሱ ነጥቋቸው መልሶ የራሱ ሲያረጋት፣ የበለጠ ወንድነት ይሰማዋል። በሀይል ደስ ይለዋል። ግን ይህን እንደ ጉድ አርጎ ስለሚቆጥረውና ስለሚያፍርበት፣ እያየውም
አውቆ አይኑን ይጨፍናል። ስለዚህ ያስመስላል፤ ያስመስላል፡
ያስመስላል። አቤት ስንት ማስመሰል አለ!

«እዚህ ላይ ነው አንተን ከልቤ የማደንቅህ፡፡ እቺን
ያህል አትፈራም። ወደነብስህ ውስጥ አትኩረህ ትመለከታለህ፡፡ እዚያ ውስጥ ምንም ቀፋፊ ነገር ብታይ አይንህን አትጨፍንም፡፡ ስለዚህ ያለማስመሰል ትኖራለህ ውስጣዊውን ኑሮ ማለቴ ነው። እንግዲህ ወደ ውስጥህ ተመለከትክ፣ ውስጥህ እኔን ሌሎች ቢተኙኝ ከነሱ
ቀምተህ ስትተኛኝ ደስ እንደሚለው ነገረህ። ስለዚህ እኔን 'ሂጂ ወንዶችሽ ጋ አልከኝ። ሄድኩ፡፡ ተመለስኩ። ተደሰትክብኝ፡፡ ወንድ
ነህ። አንተ እውነተኛ ወንድ የሆንከውን ያህል እኔ እውነተኛ ሴት ሆኜ እንደሆነ እጅግ ኩራት ይሰማኛል።»

«አንቺ እንደምትይኝ ከሆንኩ፣ አንቺም እንደኔ አይነት ነሽ።
ልክ እንደኔ አይነት! አብዛኛዎቹ ሴቶች፣ ፍቅር ከያዘኝ ወንድ ጋር
ብቻ ነው ግብረ ስጋ ደስ የሚለኝ ይላሉ። ይህም ማስመሰል፣
ማስመሰል፣ ማስመሰል ነው። አንቺ ግን ለራስሽ አትዋሺም። ቆንጆ ወጣት ሆኖ ቆንጆ ወንድ እያቀያየሩ መደሰት እንዴት ያለ ገነት ነው!' ትያለሽ። እኔኮ አልችልም፣ ቆንጆ ወንድ ሳይ አያስችለኝም፣ቁንጅናውን መንካት መዳሰስ አለብኝ፣ በወጣትነቱ መደሰት አለብኝ ትያለሽ

“አንድ ቀን አንድ ነገር አልሽኝ። አስከመቼም አልረሳውም፡፡»

«ምን አልኩህ?»
👍23👎1
#ትኩሳት


#ክፍል_ሀያ_ሁለት


#በስብሐት_ገብረ_እግዚአብሔር

በሰፊ ውብ አፏ እየሳቀችብኝ፡ እየወደደችኝ ድንገት ሳቁን እየተወች አንድ ነገር ልነግርህ እፈልግ ነበር» አለችኝ ንገሪኝ
እንዳትቆጣ፡፡ ወንድ ሆነህ አትስማኝ፡ ደራሲ ሆነህ አዳምጠኝ እንጂ
«እሺ»
"Parole d'honneur?"
"Parole d'honneur!"
«አንተን እወድሀለሁ። ከልቤ አፈቅርሀለሁ፡፡ ግን ፖልን ልረሳው
አልችልም። የመጀመሪያዬ ስለሆነ ብቻ ሳይሆን፣ ሳልጠግበው
ስለሄደብኝ ጭምር ይመስለኛል። «ይገባሀል?»
«ይገባኛል»
«እና አንድንድ ጊዜ ይናፍቀኛል፡፡ ይመስለኛል፣ በውስጤ
የልጃገረድነቴ ጊዜያት ከሱ ጋር ተዋህዷል፡፡ እና ያ ጊዜያት
ሲናፍቀኝ፣ ፖል ይናፍቀኛል። ከልቤ ላወጣው ልረሳው እሞክራለሁ።
ግን የምችል አይመስለኝም፡፡ የምልህ ይገባሀል?»
«ይመስለኛል»
«ስለዚህ ፖልን የሚመስል ሰው ሁሉ ደስ ይለኛል፤ ይስበኛል።
... እና ስለ ባህራም ልነግርህ እፈልጋለሁ፡፡»
ይናገራል ብላ ዝም አለች። መናገሩ እየከበዳት ሄዷል። ዝም
ብዬ ሳያት ቀጠለች
«አንተ ነህ ባህራምን እንድወደው ያረግከኝ፡፡ ስለሱ ብዙ ብዙ
አወራህልኝ። አራት ወር ሙሉ አወራህልኝ፡፡ ከወሬህ እንዳየሁት፣
በጣም በጣም ታከብረዋለህ። ግን እንደማውቅህ አንተ ማንንም
አታከብርም፡፡ ስለዚህ፣ ይሄ ባህራም እንዴት ያለ ሰው ቢሆን ነው? አልኩ። አንዲት ሴት እንዲህ ካለች ደሞ መመለሻ የላትም። ይህን ያባሰው ምንድነው? ከወሬህ እንደተገነዘብኩት ባህራም እንደ ፖል ያለ ሰው ነው። እንደሌላው ሰው ከተራ ጭቃ ተጠፍጥፎ አልተሰራም፡፡ ጀግናዎቹ ከሚሰሩበት ከልዩ ጭቃ ተቀርፆ፣ በልዩ ንፁህ እሳት ውስጥ ነው የተጠበሰው። ባህራምን እንደዚህ አድርገህ
ነው ያሳየኸኝ
«አንተ ያንን ያህል እያከበርከው፣ ከፖል ጋር ያንን ያህል
እየተመሳሰለ፣ እንዴት ላይለኝ ይችላል? እኔ ደሞ
እንደምታውቀኝ ነኝ:: እንዴት ላልመኘው እችላለሁ?»
«ፍቅር ይዞሻል?»
ራሷን በሀይል
እየነቀነቀች፡ ከኋላዋ ጥቁር ሀር ፀጉሯ እየተወዛወዘ፣ የደስታ ሳይሆን የመሰቃየትና የመደናገር ፈገግታ ውብ አፏን እየሸመቀቀው

እኔ እንጂ! እኔ እንጃ! እኔ እንጃ!» አለችና ራሷን ጠረጴዛው ላይ
ደፋች
ረዥም ፀጥታ
እጄን ሰድጄ ራሷ ላይ አሳረፍኩት። ቀና ብላ አየችኝ፡፡ እምባዋ
ይወርዳል
«ሶስት ፍቅር አንድ ላይ ሊይዝ ይችላል?» አለችኝ
“ሴትዮዋ ተራ ከሆነች አይችልም» አልኳት
ጠረጴዛው ላይ የነበረ እጄን ወስዳ ከጎንጯ ጋር እያተሻሸት፣
በእምባዋ እጄን እያረጠበች፡ በተጨነቀ ድምፅ
«ብዙ ጎዳሁህ፣ የኔ ቢራቢሮ?» አለችኝ
ግድ የለሽም አልኳት
«አለኝ እንጂ። ላንተ ብዙ ግድ አለኝ፡፡ ለዚህ እኮ ነው
የምነግርህ፡፡»
«አውቃለሁ»
ለኔ እንዴት ጥሩ ነህ! አሁን ምን ይሻለኛል?»
ቆንጆ ነሽ። ተወዳጅ ነሽ፡፡ ለምን አትወጂውም?»
በመሀረቤ እምባዋን እየጠረገች
«አንተስ? አትቀየምም?»
ሌሎች ጋ ትሂጂ የለ? ስለዚህ ለኔ ያው ነው»
ውይ! እንዴት ደግ ነህ!?»
«ለምን?»
ውሸትክን ነዋ» ተናፈጠች
እኔ እንድደሰት ብለህ
ትሰቃያለህ፡፡»
«የምን ስቃይ?»
መሀረቤን አጥፋ እየመለሰችልኝ
«እንግዲህ አትዋሽ። ይበቃሀል። አውቅሀለሁ'ኮ። ከምትገምተው
በላይ አውቅሀለሁ፡፡ ፊትህ ላይና አይኖችህ ውስጥ ስንትና ስንት ነገር ይታየኛል መስለህ።»
«ምን ይታይሻል?»
«ስለባህራም ስነግርህ በብዙ ነው ያዘንከው::
«ላንቺ ነዋ ያዘንኩልሽ፡፡
«እሱም ታይቶኛል። ግን ለራስህም በሀይል በመሰቃየት ላይ ነህ፡፡ እና በጣም አዝናለሁ፡፡ እንዲህ በመሆኔ በጣም አዝናለሁ፡፡»
«በማዘን የትም አይደረስም፡፡»
አውቃለሁ የኔ ቆንጆ:: ግን ማዘን አይቀርም፡፡»
ዝም ዝም ሆነ
«በኔ ብቻ ሳይሆን በባህራምም ጭምር ነው ያዘንከው። ልክ
ዝም አልኳት
«እንግዲህ ልንገርህ፡፡ እውነቱን ብታውቅ ይሻላል። ልንገርህ?»
«እሺ፡፡»
«ያን እለት ማታ ያ ሰውዬ ባህራምን ሊገድለው አልመጣም?
እና አንተ ኒኮልን ይዘህ ማርዕይ አልሄድክም? ከኒኮል ጋር
ምንም አልሰራችሁም? እውነት ተናገር፡፡»
«ምንም አልሰራንም፡፡ ይልቅ ቀጥዪ።»
«እና ሰውየውን ሲገድለው አላየሁም? እሱን ነግሬሀለሁ። እና
ከዚያ ወደ ቤት ሄድን፡፡ ባህራም ልክ ምንም እንዳልስራ በእርጋታ
ሶፋ ላይ ተቀመጠ። እኔ መጠጥ ሰጠሁትና ሶፋው ላይ አልጋ ብጤ
አነጠፍኩለት፡፡ አንጥፌ ስጨርስ 'እንግዲህ እዚህ ውስጥ ይተኛል።
ነብስ ገድሏል፤ ግን እዚህ ውስጥ ይተኛል። ከጀግና ጋር ነው'ኮ
ያለሁት። ከነብሰ ገዳይ ጋር ነው ያለሁት ብዬ አሰብኩ፡፡ ዘወር ብዬ
አየሁት። አንተ እንደ ነገርከኝ ነው። ዝም ሲል የኢራንን ሻህ
ይመስላል። ግን ማን ያውቃል? ጀግና ስለሆነ አንድ ቀን የኢራንን
ሻህ ይገድለው ይሆናል'ኮ!' ብዬ አሰብኩ
«እና በሀይል ተመኘሁት፡፡ ፍትወት ያንን ያህል አንቆ ይዞኝ
አያውቅም፡፡ ራሴን 'ተይ እንደሱ አታርጊ! - ተይ!'
እያልኩ
ከተቀመጠበት ሄድኩና እግሩ አጠገብ ተምበርክኬ ወደላይ አየሁት።
እንደ ቄስ እጁን ራሴ ላይ አሳረፈና
«ምን ሆነሻል?» አለኝ
ቀስ ብዬ ተነሳሁና አፉ ላይ ሳምኩት
አሁንም «ምን ሆነሻል?» አለኝ። ግን ገብቶታል
«ፈልጌሀለሁ» አልኩት
«እኔ አልፈልግሽም» አለ
«አውቃለሁ ትፈልገኛለህ፡፡ ትፈልገኝ የለ?»
«አዎን፡፡ ካየሁሽ ጀምሮ እንደፈለግኩሽ ነው::»
«ይኸዋ፡፡ አለሁልህ!»
«አይሆንም!»
«ለምን አይሆንም?»
«ምክንያቱን መቼ አጣሽው» አንተን ማለቱ ነው
«እሱ ንደሆነ ግድ የለውም» ኣልኩት
«እኔ ግድ አለኝ!»
«ለምን?»
«ጓደኛዬ ነው:: እፈልግሻለሁ፡፡ ግን እሺ አልልሽም። ስለዚህ
እርሺው!»
«አልረሳውም፡፡ ልረሳው አልችልም፡፡ ልረሳው አልፈልግም።
ሌሊት እመጣለሁ!» አልኩትና ሄጄ አልጋዬ ውስጥ ገባሁ፡፡ ልተወው
ቆረጥኩ። ምናልባት አንድ ሰአት ያህል ቆየሁ። ከዚያ በላይ ግን
ልቆይ አልቻልኩም፡፡ እንደዚህ አላስችል ያለኝ እሱ ስለሆነ ብቻ
ነበር፣ ወይስ ሰው ሲገድል ስላየሁት ነበር? አላውቅም፡፡ የሆነ ሆኖ፣ እሱ እዚያ ተጋድሞ እኔ እዚህ ሆኜ ልታገስ አልቻልኩም
ራቁቴን ወጣሁ፡፡ ሽቶ ተቀባሁ፡፡ ከመኝታዬ ወጣሁ፡፡ የንግዳ
ቤቱን መብራት አበራሁ። እንቅልፍ አልወሰደውም ነበር። በቀጥታ
ሄድኩና ከበላዩ ቆምኩ፡፡ ወደላይ አየኝ፡፡ ሲያየኝ ብዙ ጊዜ ቆየ፡፡
እጁን ሰደደ። ጭኔን ይዞ ወደታች ጎተተኝ
ካሸነፈኩት በኋላ ወደ አልጋዬ ሄድን፡፡»
ዝም አለች፡፡ ያችን ሌሊት እንደምታስታውስ ያስታውቃል፡፡
እንዴት ያለች ሌሊት ነበረች ይሆን? ብጠይቃት እንደማትነግረኝ
እርግጠኛ ነበርኩ፡፡ ስለሌሎቹ ወንዶች በሰፊው ትንገረኝ እንጂ፣
ስለነሱ ጥቃቅኑን ስጋዊ ተግባር ሳይቀር ትዘርዝርልኝ እንጂ፣
ስለፖልና ስለ ባሀራም አትነግረኝም፡፡ እኔም ስለነሱ መጠየቅ ልክ አልመሰለኝም፡፡ ዝም አልኩ። ቀጠለች

«ስለሌሊቱ ልንገርህ እንዴ?» አለችኝ
«ልትነግሪኝ ትፈልጊያለሽ?»
«አልፈልግም። ከፈለግክ ግን እነግርሀለሁ።»
ይህን ያለችኝ «ሳትፈልጊ ብትነግሪኝ ደስ አይለኝም»
እንደምላት አውቃ ነው እንጂ፡ ንገሪኝ ብላትም እንደማትነግረኝ
አውቃለሁ
«ሳትፈልጊ ብትነግሪኝ ደስ አይለኝም» አልኳት
👍16🤔3
#ትኩሳት


#ክፍል_ሀያ_ሶስት


#በስብሐት_ገብረ_እግዚአብሔር

የሞት ጥሪ

አማንዳ

ወደ ኤክስ ልንመለስ ሶስት ቀን ሲቀረን ሲልቪ ቤቶቿን ለመሰናበት ሄደች። ጊዜው ንፁህ ብርህንና ለስላሳ ሙቀት በዝግተኛው ነፋስ የሚንሳፈፉበት ውብ የፀደይ ቀን ነበር። የፓሪስ ሴቶች ወደ ሰፊው ስመ ጥሩ ጎዳና ወደ ሻንዜሊዜ እንደሚጎርፉ ታወቀኝ፡፡ በሜትሮ ወደዚያው ሄድኩ ሱቆቹ የፀደይ ሞድ ልብሶቻቸውን መስኮቶቻቸው ላይ ዘርግተዋል፤ ካፌዎቹ ጠረጴዛ ወምበሮቻቸውን ወደ መንገዱ
አውጥተው ከአብዛኛዎቹ ጠረጴዛዎች በላይ በልዩ ልዩ ቀለማት ያጌጡ ሰፋፊ ጃንጥላዎችን ዘርግተዋል። ሰዉ ይንጋጋል፤ ትራፊኩ ይፈሳል። አንዱ ካፈ ውጪ ሰዉ የሚተላለፍበት ቦታ አንዲት ትንሽ ጠረጴዛ አጠገብ ተቀመጥኩ

በፀደይ ቀን ሻንዚሊዜ ጎዳናው ዳር ቁጭ ብሎ ቢራ እየጠጡ
አላፊ አግዳሚዋን ፈረንሳዊት እና የስንትና ስንት ሌላ አገር ሴት
መቃኘት። ከዚህ የበለጠ ምን ደስታ ይገኛል? ሴቶቹ የፀደዩን
ብርሀንና ነፋስ ለመቀበል የፈነዱ አበባዎች ይመስላሉ፡፡ የወፍ ቋንቋ
መሳይ ፈረንሳይኛቸውን በልዝብ ድምፃቸው እንደዘፈን እየተቀባበሉ፣የተነጠፈውን ድንጋይ በረዥም ተረከዛቸው ኳ! ኳ! እያረጉ፤ ውብ ዳሌያቸውን እያወዛወዙ ወደላይና ወደታች ይተላለፋሉ፡፡ አይኔ
አብሯቸው ይመላለሳል
ቀስ እያለ አይኔ ሰከረ፡፡ ውበት በዛበት። የአንዷን ኩሩ አረማመድ ሳደንቅ ትንሽ እንደ ተራመደችልኝ፡ ህዝቡ መሀል ገብታ ትጠፋለች፡፡ የሌላዋ ግሩም ቅርፅ አይኔን ይስባል፡ ከዳሌዋና ከባት ከተረከዟ የቱን እንደምመርጥ ገና ሳልወስን ህዝቡ ይውጣታል። ደሞ
የአንዷ ፀጉርና አንገት ልቤን ይወስደዋል። የምትቀጥለዋ ወጣት ነጭ ጥብቅ ያለ ሱሪ ለብሳ ስታልፍ አይኔ በዳሌዋ እንቅስቃሴ ላይ ይተከላል። እሷንም ሚንጋጋው ህዝብ ይውጣታል። ሌላ ወበት ሌላ ሴት ላይ ተጭኖ ሲሄድ አይኔን ይስባል። እንደዚህ ሰል አይኔ ሰከረ

የቢራዩን ሂሳብ ከፍዬ ወደ ፕላስ ደ ሌትዋል በኩል ስራመድ
የአንዷ ፀጉር አይኔን ማረካው:: ሴትዮዋ ከኋላ ሲያዩዋት ምንም
አትል አረ ሻንለዚ ስላየሁዋት ነው እንጂ ሌላ ቦታ ባያት በጣም ደስ ትላለች። አጠር ያለች ወጣት ናት። ቀይ ቦርሳ አንጠልጥላለች። ገላዋን እቀፍ አርጎ የሚሸፍን፣ ነጭ ባለ ሽንሽን የፀደይ
ቀሚስ ለብሳለች። ወገቧን ሰፊ ቀይ ቀበቶ አቅፎታል። ቀይ
ባለረዥም ተረከዝ ጫማ የረገጡት እግሮቿ ወፈር ብለው፣ ቀለማቸው ወደ ቡናማ የሚያደላ ነው። ወፍራም ዳሌዋ ከነጭ ልብሷ
ስር ሲመዛዝ ያስታውቃል፣ ምኞት ይቀሰቅሳል። ግን ዋናው ውበቷ
ፀጉሯ ነው:: ይሄ ንፁህ ነጭ ፀጉሯ ወደኋላዋ ትከሻዋ ድረስ ተለቆ፣
ፀሀዩ ውስጥ ይብለጨለጫል። የረጋ የጨረቃ ብርህን የሚመስል
ንፁህ ፀጉር ከዚህ በፊት የት ነው ያየሁት? የት? መቼ? የት?
ሴትዮዋ ወደ ቀኝ በኩል ተጠምዛ ከሻንዜሊዜ ወጥታ፣ አንድ
ሌላ መንገድ ይዛ ወደሳይ በኩል መራመድ ጀመረች። ለምን
ተከተልኳት? አላውቅም
መንገዱ ዳር ብዙ መኪናዎች ቆመው ነበር፡ እሷ አንድ ጥቁር
ጃጉዋር ስፖርት መኪና ውስጥ ገባች። አልፌያት ወደ ላይ በኩል
መንገዴን ስቀጥል፣

“Hi there!” አለችኝ። ባለሁበት ቆምኩ፡፡ የአማንዳ፥ ድምፅ!
ጆሮዬን ማመን አልቻልኩም፡፡ ግን ፀጉሩ የሷ ነው። አሁንም
አስታወስኩ። ወደሷ ዞርኩ፡፡ ከመኪናዋ ወጥታ እየሮጠች መጣችና ተጠመጠመችብኝ። ሽቶዋ በጣም ደስ ይላል።
“አማንዳ ነሽ እውነት?
«እዎን»
«ታድያ ያ ሁሉ ጮማ የት ሄደ?»
«ሸጥኩት» አለችና ትንሽ ከኔ ራቅ ብላ አንድ ሁለት ጊዜ
እየተሽከረከረች ምን ይመስልሀል?» አለችኝ
«ተአምር ነው፡፡ በአይኔ ባላይሽ ኖሮ አላምንም ነበር»
"Thank you"
«እውነቴን ነው:: አሁንኮ ማን እንደሆንሽ ሳላውቅ ከኋላሽ
በኩል ሳይሽ የማናት ቆንጆ ፈረንሳይ? እያልኩ ስከተልሽ ነበር»
«አንዲት ሴት ምን መስማት እንደምትወድ ብጥር አርገህ
ታውቃለህ መቸስ፡»
«እውነቴን ነው ኧረ!»
«ደስ ካልኩህ አብረኸኝ ምሳ ብላ እስቲ»
«ጥሩ»
ወደ ቆንጆ ጥቁር መኪናዋ ገባን፡፡ አማንዳ ድሮ ቁምቡርስ
ነበረች፣ አሁን ግን ቢራቢሮ ሆናለች። ትርፍ እገጯ ጠፍቷል፣
አንገቷ ዙርያ ተጠፍጥፎ የነበረው ጯማ ረግፏል። ፊቷ ሙሉ ነው፡
ግን ደስ ይላል፡፡ ከንፈሮቿ ሮዝ ብጤ ቀለም ተቀብተው፣ ሰማያዊ
አይኖቿ በጥንቃቄ ተኩለው፣ ቀይ ጉትቻዋ ከነጭ ፀጉሯ አጠገብ
ሲታይ በረዶ አጠገብ የተንጠለጠለ እንጆሪ ይመስላል።
ከአስቀያሚዎቹ ሴቶች ማህበር ወጥታ፣ ቆንጆዎቹ ማህበር
ገብታለች፡፡ ድምፅዋ ሳይቀር ተለውጧል። ድሮ አልቃሻ ብጤ ነበር፤አሁን ግን ልስልስ ያለ ቆንጆ ድምፅ ነው
«ንገሪኝ እስቲ፡ ምን እንደዚህ ለወጠሽ?» አልኳት
«አንድ ሰካራም አለችኝ
«ምን?»
«ሉን ተሰናብቼ ወደ አገሬ ስሄድ፡ ኤሮፕላኑ ውስጥ አንድ
ሰውዬ አጠገብ ተቀመጥኩ፡፡ ሰውየው ሰክሮ ነበር። ሉ ትዝ እያለኝ ለብቻዬ ሳለቅስ
« ምን ያስለቅስሻል? የወደድሽው ሰውዬ እምቢ አለሽ? ደግ አረገ! በዚህ እድሜሽ ምን እንዲህ አወፈረሽ? አለኝና ያኔውኑ
ረሳኝ፣ እንቅልፍ ወሰደው
«እኔ ግን ቃላቱን እስከ መቼም አልረሳቸውም። ለመጀመርያ
ጊዜ አንድ እውነት ተገለፀልኝ። ይኸውም፣ ጅል ሆኜ ነው እንጂ፣
ውፍረቴን እንደ ጭነት ተሸክሜ መዞር የለብኝም፡፡ ጭነቱን አውርጄ ልጥለው እችላለሁ። ልጥለው ቆረጥኩ። ሳን ፍራንሲስኮ ሄጄ ሙያቸው ክብደት መቀነስ ከሆነ ሰዎች ጋር አራት ወር ሙሉ ሰራሁ። ውጤቱን አንተም አመሰገንክልኝ አለች። ሳቋ ውስጥ ወጣትነትና የህይወት ድል አድራጊነት ይጨፍራል!

ባለ አራት ኮከብ (ማለት ከሁሉ ይበልጥ ምቾት ያለበት) ሆቴሏ
ወሰደችኝ። ክፍሏ ሆነን በቴሌፎን ሁለት ምሳ አዘዘች። አሁንም
አስደነቀችኝ። ኤክስ ሳውቃት ፈረንሳይኛውን በአስቀያሚ የአሜሪካን ቅላፄ ነበር የምታዜመው፣ አሁን ግን የፓሪስ ፈረንሳይኛ ሊሆን ምንም አልቀረው:: እያየችኝ ስትስቅ
“እንደዚህ የሚያስደስት ለውጥ አይቼ አላውቅም።

"Thank you, you re really sweet" አለችኝ

ከምሳ በኋላ «ፓሪስ ምን ትሰራለህ?» አለችኝ፡፡ ነገርኳት፡፡
«አንቺስ?» አልኳት።
«ከኒው ዮርክ የዛሬ ሳምንት መጣሁ፡፡ ይሄ ጃጉዋር ከኢንግላንድ እስኪመጣልኝ ነበር " ምጠብቀው። ነገ ወይም ተነገ ወድያ ወደ ኤክስ መሄዴ ነው:: . . ሉን ማግኘት አለብኝ፡፡ ደህና ነው? አሁንስ የሚፈልገኝ ይመስልሀል? ለጊዜው ሴት አልያዘ እንደሆነ ጥርጥር የለውም። ይዞ እንደሆነ፣ ነጥቄ መውሰድ ይኖርብኛል።»

«ምን?»
«ነጥቄ እወስደዋለሁ። ምነው ገረመህ? የድሮዋ አማንዳ
መስዬህለሁ እንዴ? ተለውጫለሁኮ:: ተዘጋጅቼ ነው የመጣሁት፡፡ ቢያንስ አርባ የሳይኮሎጂ መፅሀፍ አንብቤያለሁ። ደሞ ሉን
አውቀዋለሁ፡፡ ግብረ ስጋ በጣም ይወዳል። ለሱም ተዘጋጅቻለሁ፡፡»

«እንዴት?»
«ለሌላ ሰው ቢሆን ይህን አልነግረውም። አንተ ግን
ትወደኛለህ። ወፍራም ሳለሁም ትወደኝ ነበር፡፡ ለኔ ግድ ነበረህ፡፡
የተሻልኩ ሰው ሆኜ ስላየኸኝ ደሞ በጣም ደስ ብሎሀል። ይሄ ለኔ
ትልቅ ስጦታ ነው። በጣም ተወዳጅ ነህ፡፡ እና ለምን እንደሆነ
ሳላውቅ በጣም አምንሀለሁ፡፡ ለምንድነው እማምንህ?»
👍14🤔2
#ትኩሳት


#ክፍል_ሀያ_አራት


#በስብሐት_ገብረ_እግዚአብሔር

....እኔ ፓሪስ ሄጀ ቅናት ውስጥ ስንፈላሰስ ኤክስ ውስጥ ምን ምን
ተደረገ? ከባህራም፣ ከተካና ከኒኮል የሰማሁትን ሳገጣጥመው እንደ እሚከተለው ሆነ፡-.

አንድ ማክሰኞ ከሰኣት በኋላ (ኒኮል ከፋሺስቶቹ ተደብቃ
ሰንብታ ከተመለሰች በኋላ) ባህራም የሚሰራበት ትምህርት ቤት ዲሬክተር ቢሮው አስገባውና ከስራዎ ላሰናብትዎ ነው» አለው።
ባህራም «ምነው?» ቢለው “በስራዎ በጣም ተደስቼ ነበር፤ ግን የጋርደን ከተማ የፖሊስ ሹም እንዳሰናብትዎ አዘዘኝ» አለው

«እዚህ ውስጥ የፖሊስ ሹም ምን አገባው?» አለ ባህራም

«አዩ፣ እርስዎ የውጭ አገር ዜጋ እንደመሆንዎ መጠን፣ እዚህ
አገር ስራ ለመያዝ ልዩ ፈቃድ ያስፈልግዎታል። እስካሁን ያለ
ፈቃድ ወረቀት ስለስሩ እርስዎም እኔም ልንቀጣ እንችል ነበር፡፡ ግን
የፖሊስ ሹሙ ጓደኛዬ ነው፡፡

የስራ ፈቃድ እንደሌለኝ እንዴት አወቀ?» አለ ባህራም

ሰው ነገረው:: ይመስለኛል፣ ኤክስ ውስጥ ጠላቶች አሉዎት።»
ባህራም ገባው። ፋሽስቶቹ መሆን አለባቸው

«እሺ ደመወዜን ይስጡኝ አለ። የሁለት ወር ከሶስት ሳምንት
ደመወዝ አለው። ዲሬክተሩ ገንዘቡን ከቢሮው ጠረጴዛ ኪስ አውጥቶ አቀበለው። ባህራም ገንዘቡን ቆጠረ። የተዋዋሉት ገንዘብ ሲሶ ነው።
«ሌላውስ?» አለ ባህራም
ዲሬክተሩ ከጠረጴዛው ኋላ እንደተቀመጠ፣ ቅዝቅዝ ባለ ክፉ
ድምፅ
«የምን ሌላ?» አለው
«ይሄ ሙሉ ደመወዜ አይደለም፡፡ አንድ ሶስተኛው ነው::
«ማን ነው ያለው? ደመወዝህን ሰጥቼሀለሁ፡፡ ከፈለግክ ውሰደው፣
ካልፈለግክ ተወው:: ድሮ አልጄርያ ሳለሁ አረቦቹን ከዚህ ባነሰ
ደመወዝ ነበር የምናሰራችሁ»
ባህራም ረጋ ባለ ድምፅ አረቦቹን ቅኝ ግዛት ስላደረጋችኋቸው
በካልቾ ብለው ካገራቸው አስወጧችሁ፡፡ የሆነ ሆኖ፣ እኔ አረብ አይደለሁም፡፡ የኢራን ሰው ነኝ፡፡ የኢራን ሰው ሰውን አይነካም። ግን ማንም ሰው የኢራንን ሰው አይበድልም፡፡ ስለዚህ አለና ድንገት
በጠረጴዛው ተንጠራርቶ ሰውዬውን አነቀው፡፡ ሰውየው ራሱን ለማስጣል አልሞከረም፡፡ ባህራም ሲያፈጥበት፣ በደነገጠ ድምፅ

«አይነቁኝ፡፡ አስም በሽታ አለብኝ» አለው ባህራም ለቀቀው፡፡ ሰውዬው ከጠረጴዛው ኪስ ሌላ ገንዘብ አውጥቶ ባህራም ፊት ቆጠረው። ባህራም ገንዘቡን አንስቶ ኪሱ ከተት። ሰውየውን አየው፡፡ ወምበሩ ላይ ተቀምጦ ወደ ላይ ይመለከተዋል። ባህራም አፉ ውስጥ ብዙ ምራቅ ሰበሰበ፡፡ ሰውዬው ፊት ላይ ተፋው፡፡ ሰውዬው መሀረብ ሊያወጣ እጁን ወደ ኪሱ ሲከት ባህራም ትቶት ወጣ

ከዚያ እየጨሰ ወደ ኤክስ የሚወስደውን አቶቡስ ተሳፈረ
ያን ቀን ተካን ባያገኘው ጥሩ ነበር
ተካ በበኩሉ ከአንድ ወር በላይ ሲበሳጭ ሰንብቷል። ጀርመንዋ
ልጅ እየባሰባት ሄደ። በፊት እንኳ ከዚያ ካገሯ ልጅ ጋር የምትወጣው አልፎ አልፎ ነበር፡፡ አሁን ግን ቢያንስ በሳምንት አራት ማታ ከሱ ጋር ነች። ተካ እንግዲህ ቢበዛ በሳምንት ሁለት ማታ ቢያገኛት ነው። ለዚያውም ሁለቱም ማታ የንትርክ ማታ ነው።
ሁልጊዜ ስለጀርመኑ ይጨቃጨቃሉ

«ከሱ ጋር ምን ትሰሪያለሽ?»
በራሴ ህይወት ምን አገባህ?»
አብራችሁ ትተኛላችሁ?»
«ምን አገባህ?»
በጥፊ እየመታት «ንገሪኝ! ይተኛል?» ይላታል
በንዴት «አዎን ይተኛኛል! በል ምን ትሆን!?» ትለዋለች
እንደገና አንድ ሁለት ጥፊ ያቀምሳትና፣ በግድ ታግሎ
ይተኛታል
አንድ ማታ ግን፣ ዝግ ባለ ድምፅ
«ልሰናበትህ ነው የመጣሁት» አለችው
ልቡ እየፈራ «ምነው? የት ልትሄጂ ነው?» አላት
«የትም አልሄድም፡፡ እስቲ
ዛሬ እንኳ ሳንጣላ እንደር፡፡
የመጨረሻችን ሌሊት ነው፡፡ ሄርማን ሊያገባኝ ቆርጧል፡፡ እኔም እሺ ብየዋለሁ።»

በሰላም አደሩ፡፡ ከዚያ በኋላ አነጋግራው አታውቅም
ጀርመንዋ ያስለመደችው ሲቀርበት ጊዜ ያንገበግበው ጀመር፡፡በቶሎ ሴት ማግኘት እንዳለበት ገባው:: ቢመለከት፣ ኒኮል አለች::መልኳ እጅግም ነው፡ ወንድ በብዙ ልትስብ አትችልም፡፡ ለዚህ አይደል ባህራምን በገንዘቧ 'ምታኖረው? ግን አሁን ባህራም
አብዛኛውን ጊዜ ከኤክስ ውጪ ነው:: ስለዚህ ሌላ ወንድ መፈለጓ
አይቀርም። እንድያውም ይህን ጊዜ እሱ (ተካ) ሴት ያስፈለገውን
ያህል እሷም ወንድ መፈለጓ አይቀርም፡፡ ሌላ ሴት እስኪያገኝ ማቆያ ትሆነዋለች። እሷም በበኩሏ ባህራም እስኪመጣላት ማቆያ ይሆናታል፡፡ የጋራ ጥቅም!
ማክሰኞ ከምሳ በኋላ ቤቷ ሄደ
ቡና አፈላችለትና «ዛሬስ ምን ሰማህና ልትጎበኘኝ መጣህ?»
አለችው
«እንድ ነገር አስቤ ነው» አላት
«ምን?»
«እኔንና አንቺን የሚጠቅም ሀሳብ ነው»
«ንገረኛ»
«ደስ ትዪኛለሽ፡፡ ስለዚህ ባህራም በሌለበት ጊዜ እዚህ ብመጣ
ጥሩ ይመስለኛል»
«መጥተህስ?»
«እናወራለን፤ እንጫወታለን» እያለ እጁን እጇ ላይ አስቀመጠ
እጇን እያሸሸች «ለኔ የሚሆን ጨዋታ ያለህ አይመስለኝም»
አለችው
«አለኝ»
«የለህም»
«ከባህራም በምን አንሳለሁ?»
በሁሉም ነገር»
«ሞኝ ነሽ። ይልቅ አንድ አቃጣሪ አረብ እየከፈልሽው
ከሚተኛሽ፣ እኔ ያለ ገንዘብ ብተኛሽ አይሻልሽም?» አላት
ፊቷ በቁጣ እሳት መሰለ፣ ግን ድምፅዋ አልተለወጠም
«ወንድ ከሆንክ ሂድና ባሀራምን አቃጣሪ አረብ ነህ በለው። እኔ
ወንድ ስላልሆንኩ የሚገባህን ቅጣት ልሰጥህ አልችልም። ግን ቆሻሻ ነህ፡፡ አንጎልህም ቆሻሻ ነው፣ ሰውነትህም ቆሻሻ ነው። እግርህ ይገማል፣ አፍህ ከሬሳ እኩል ይቆንሳል። አሁን ቤቴ ሳይገማ ተነስና ሂድልኝ አለችው
ተነሳ። ቁጭ እንዳለች ሳታስበው በጥፊ መታት። ከወምበሯ
ተከነበለች። ከወለሉ ላይ በፀጉሯ ጎትቶ እነሳትና እንገቷን ሳማት።
ስትፍጨረጨር እጁን ጠምዞ ወደ አልጋዋ ወሰዳት። አልጋው ላይ
ጣላትና አንድ ጡቷን ጭብጥ አርጎ ያዘ፡፡ መፍጨርጨሯን ተወች
በኣፏ ብቻ

ተወኝ! ብትተወኝ ይሻልሀል!» እያለች ትፎክራለች እጁን ሰደደና ሙታንቲዋን ሊያወልቅ ሲል እንደገና መፍጨርጨር ጀመረች፡፡ ጡቷን የባሰውን በሀይል ዉበጠው:: ፀጥ አለች፡፡ ሙታንቲዋን አወለቀው። እምባዎ ይወርድ ጀመር፡፡ ቁጣዋ
ወደ ልመና ተለወጠ
እባክህ ተወኝ፡፡ ምን አረግኩህ?»
ልመናዋን ከምንም አልቆጠረውም። ጡቷን ጨብጦ እንደያዘ የሱሪውን ቀበቶ ፈታ
አሁንም እምባዋ እየወረዳ «እባክህን ተወኝ፡፡ እርጉዝ ነኝ፡፡
የሁለት ወር ነብሰ ጡር ነኝ» አለችው

የሱሪውን ቁልፍ ይፈታ የነበረው እጁ ባለበት ደረቀ። ጡቷን ይዞ የነበረው እጁ ለቀቃት፡፡ ሱሪውን መልሶ ቆለፈ፡፡ ትቷት ወጣ

አልጋዋ ላይ ተደፍታ ስታለቅስ ባህራም ደረሰ፡፡ ከጋርደን
እያበሽቀ መምጣቱ ነበር። በጥፊ ተመትቶ የቀላውን ፊቷን አየ፡፡
እያለቀሰች የሆነውን ሁሉ ነገረችው
ተናዶ ተካን ፍለጋ ወጣ፡፡ ኒኮል ተከተለችው። ምናልባት
ኣደገኛ ነገር እንዳይስራ ፈርታለች። እሱ በረዥሙ ሲራመድ እሷ
አልደርስበት ብላ ከኋላው ከሩቅ ሱክ ሱክ ስትል፤ ኤክስን አቋርጠው ሲቴ አጠገብ ሲደርሱ ባህራም ተካን አየው፡፡ ጠራው፡፡ ተካ ቆመ፡፡አንድ ትልቅ ዛፍ ስር ነበር። ባህራም ደረሰና ቃል ሳይናገር በጥፊ መታው። ተካ ቡጢ ሰነዘረበት። ባህራም ጎምበስ ብሎ አመለጠና፡
በፍጥነት የተካን እጅ ይዞ ጠምዞ በሀይል ወረወረው: ከዛፉ ጋር
አጋጨው። ከዚያ በኋላ ተካ ሊካላከል አልቻለም፤ አንጎሉ ዞሮበታል፡ ባህራም እጅ ውስጥ እንደ ህፃን ሆነ። ባህራም ጭንቅላቱን ይዞ ፊቱን
ከዛፉ ጋር ደጋግሞ ደጋግሞ አጋጨው። የተካ ፊት በደም ተበከለ።ኒኮል ደርሳ ባታስጥለው ኖሮ ምናልባት ይገድለው ነበር
👍211
#ትኩሳት


#ክፍል_ሀያ_አምስት


#በስብሐት_ገብረ_እግዚአብሔር


የቀይ ኮከብ ጥሪ
ባህራም

ባህራም እየተለወጠ ሄደ፡፡ እነ ማኦ ትዜ ቱንግ የደረሱዋቸውን
መፃህፍት ማንበብ ተወ:: ስለኮሙኒዝም ማውራት ተወ፡፡ ክፍል መግባት ተወ:: እኔንም ይሽሸኝ ጀመር። እንደቀስተ ደመና ውብ የነበረውን የሬቮሉሽን ተስፋውን በብዙ የእሳት ቃላት ይነግረኝ ስለነበረ' አሁን ቀስተ ደመናው ተሰባብሮ ወድቆ ከበሰበሰ በኋላ፣ እንደገና
ሊያነጋግረኝ አልፈቀደም፡፡ ኒኮልም ፊት ነሳችኝ፡፡የባህራምን ክንፍ እንደሰበረችው ስላወቅኩ ፊት ነሳችኝ

የኤክስን ሰማይ የሉልሰገድና የጀምሺድ መቀሰፍ አላስደነገጠውም፡ የአማንዳ ጉብዝና አላስደነቀውም፡ የኒኮል ማርገዝ አላናደደውም፡ የባህራም መታሰር አላሳዘነውም፡፡ የኤክስ ሰማይ ለዚህ ሁሉ ደንታ የለውም
የኤክስ ሰማይ አብዛኛውን ጊዜ እንደ አማንዳ አይን ብሩህ
ሰማያዊ ነው፡ አንዳንድ ጊዜ እንደ ኒኮል አይን ውሀ አረንጓዴ
ይሆናል፡ ወደ ማታ ጊዜ እንደ ሲልቪ ጉንጭ ይቀላል
የኤክስ ሰማይ ደመና አይለብስም፤ ሁልጊዜ ራቁቱን ነው! ሁልጊዜ ውብ ነው፡ ሁልጊዜ ሰላማዊ ነው። ሌሊት የአልማዝ
ከዋክብትና የሰላም ፀጥታ ለብሶ ያድራል

የኤክስ የፀደይ ፀሀይ እየበረታች ሄደች። ንፁህ ብርሀኗ ቀስ
እያለ ወደ ብጫ ሀሩር ተለወጠ፡ ለስላሳውን የፀደይ ንፋስ
አደከመው፡ የሚወብቅ የአየር ባህር አደረገው፡፡ በጋ መጥቶ ኤክስ ውስጥ እንደ ሰፊ ድካም ተንሳፈፈ። አሮጊቶቹና ሽማግሌዎቹ ጥላ ውስጥ ቁጭ ብለው በዝግታ እያለከለኩ፣ የሞትን ምህረት የሚጠብቁ
ይመስሉ ጀመር

እንዳንድ ጊዚ ባህራምንና ኒኮልን ምግብ ቤቱ ሲገቡ ወይም
ሰወጡ አያቸዋለሁ። ባህራም ከስቷል፡ አይስቅም፣ በፍጥነት
አይራመድም። ሽበቱም የበዛ መሰለኝ፡፡ ኒኮል ግን ወፈር ብላ፣
እርግዝናዋ በጣም አምሮባታል፡ በዝግታ ስትራመድ ታስጎመጃለች
ቀስ በቀስ ምግብ ቤት መምጣቱን ተዉት ተካ የኒኮልን ማርገዝ ለመሸሸግ ያሉት ነው» አለኝ፡፡ ሌላ
ነገር ነገረኝ ባህራም ማታ ማታ ኒኮልን ቤቷ ትቷት ይወጣና
ሲኒማ ይገባል ከሲኒማ ወጥቶ ካፌ 'ሰንትራ' ይሄዳል፡ እዚያው
ያድራል፤ ሲነጋ ወደ ኒኮል ቤት ይኳትናል፡ ተኝቶ ይውላል

አንድ ማታ ወደ ስድስት ሰአት ላይ ከሲኒማ ወጥቼ ወደ ቤቴ
በኩል ስራመድ፡ ከኋላዬ እንደ ፈጣን እርምጃ ሲከተለኝ ተሰማኝ።
እንዳልሰሙ መንገዴን ቀጠልኩ። ደረሰብኝ፡፡ ባህራም፡፡ ወደ ካፌ
ሰንትራ ሄደን ቢራ ካዘዝን በኋላ
ቁጭ ብለን ካወራን ብዙ ጊዜ ሆነን አለኝ፡፡ አይኖቹ እንደ
መድከም ብሏቸዋል፡ ፊቱ ላይ የአምስት አመት ያህል እድሜ
ተጨምሯል
"አንተ አትገኝም አልኩት"
በገዛ ራሴ ጥፋት በታሰርኩ' አንተ ጋ መጥቼ ባለቅስብህ ተገቢ
ማስሉ አልተሰማኝም

ጥሩ እድል አጋጥሞህ ቢሆን ኖሮ ግን መጥተህ ታጫውተኝ
ነብር፡ ደስታህን ታካፍለኝ ነበር»
አዎን። ይኸውልህ፡ ልክ ከፓሪስ እንደተመለስክ እንድንጋገርበት አቅጄ ነበር፡፡ ግን ገና ሳትመለስ ጣጣ ውስጥ ገባሁ። ስትመጣ ታድያ፤ መንፈሴ ተሸንፎ ስለነበረ ያቀድኩትን ችላ አልኩት፡፡ አሁን ፈቃደኛ ከሆንክ ብንነጋገርበት ጥሩ ይመስለኛል።»
"ጥሩ"
መጀመር አስቸገረው። ሲጋራ አቀጣጠለ።
ስለሰልቪ ጉዳይ ነው። ነግርሀለች?»
«አዎን፡፡
«ምን አለችህ?»
የነገረችኝን ባጭሩ አጫወትኩት። ዝም ብሎ ሰማኝ። ስጨርስ
«ውሸቷን ነው» አለኝ
«እንዴት?
«እኔ ነኝ የለመንኳት፡፡ እሷ እምቢ ብላኝ ነበር። ለብዙ
ተለማመጥኳት። 'አሁን አሁን ከሞት ጋር ስታገል ነበር፡ ውስጤ
በፍርሀት ተሞልቷል፡ ብቻየን ነኝ፡ የሰው ሙቀት ያስፈልገኛል፣
በጣም ያስፈልገኛል አልኳት። እሺ አለችኝ። ግን እሺ ያለችኝ ብዙ
ከተለማመጥኳት በኋላ ነው»
«ማንኛችሁን ልመን?»
«እኔን
«ለምን?»
«ውሸት አልነግርህማ»
«እሷስ ለምን ውሽት ትነግረኛለች?»
«እንዳንጣላ ብላ»
ዝም አልኩ። ንዴቱ ውስጤ ሲጠራቀም ይሰማኛል
«ከፈለግክም አገጣጥመን» አለኝ፡፡ ቁጣዬን ለመግታት ስል
መዋሽት ጀመርኩ
«ግድ የለም ይቅር። አሁን ስላንተ ንገረኝ አልኩት። ድምፁ
እንደተለወጠ ተሰማኝ
«ይቅርታ አርገህልኛል ማለት ነው?» አለኝ
«እንርሳው» አልኩት
«እፍረት ይሰማኛል። አይንህ ውስጥ ንቀት ይታየኛል»
«ንቀት አይደለም» አልኩት
«ታድያ ምንድነው?»
«ስሜቴን ልግለፅልህ?»
«አዎን»
እኔ ሳላውቀው የተጨበጠ ቀኝ እጄ በፍጥነት ሄዶ አገጩን
መታው:: ከነወምበሩ ወደኋላ ተገለበጠ። እጆቼን እንደ ጨበጥኩ ከበላዩ ቆምኩ፡፡ የተገለበጠው ወምበር አጠገብ እንደተጋደመ ወደ ላይ ያየኛል። ማንኛችንም አልተንቀሳቀስንም። ወደ ላይ እያየኝ ቀስ ብሎ መሀረቡን ከኪሱ አወጣ፡፡ መሀረቡ ውስጥ ተፋ። ደም፡ ቀና
ብሉ ቀይ ፈገግታ ሰጠኝ፡፡ እጁን ዘረጋልኝ። ጨበጥኩት፣ ወደ ላይ
ሳብኩት። በየቦታችን ተመልሰን ተቀመጥን

ካፌው ውስጥ ሌሎች ሰዎች እንዳሉና እንደሚያዩን ገና አሁን
ታወቀኝ። አፈርኩ፡፡ ግምባሬን አላበኝ፡፡ መሀረቤን አውጥቼ
ጠረግኩት። ባህራም እንደገና መሀረቡ ውስጥ ተፋ፡፡ ሳቅ እያለ
«እንደሱ እንኳ ይሻላል» አለኝ
አንድ ነገር አስታወስኩ፡፡ ባህራም ቢፈልግ ነብሴ እስኪመጣ
ሊደበድበኝ ይችል ነበር! እንደገና አላበኝ። በመሀረቤ ጠረግኩት
ከዚህ በኋላ ከባህራም ጋር እንደ ድሮው ማውራት ጀመርን።
የደረሰበትን እጫወተኝ። ኒኮል ማርገዟን ስታውቅ መበሳጨት
ጀመረች፡፡ ባህራም ከስራ ሲወጣ ብስጭቷ እየባሰባት ሄደ።
ሉልሰገድና ጀምሺድ ከሞቱ በኋላ፣ ብስጭቱ ወደ እምባ ተለወጠ፡፡
ማታ ማታ ታለቅሳለች። ባህራም ያባብላት፣ በስጋ ይገናኛትና
ያስተኛታል እሷ ስትተኛ እሱ ሲጋራ አቀጣጥሎ በጨለማው ስለ ኢራን
ያስባል። ከንቱ! ያ ሁሉ ዝግጅት ከንቱ ቀረ፡፡ ያ ሁሉ አመታት
በከንቱ አለፈ፡፡ ማኑ ያ ኢራን ሳሉ የ«ፍሬ አለቃው የነበረ
ስለአምባጓሮ ያስተማረው ውድ ጓደኛው ማኑ በሱ ቦታ ቢሆን
አሁን ምን ባደረገ ነበር? ለመሆኑ፣ ማኑ የት ይሆን? እዚያው
እንግሊዝ አገር ይሆን?
«ይገርምሀል” አለ ባህራም ሲነግረኝ አንድ አስር ቀን ያህል
በተርታ፣ ማታ ማታ ስለማኑ ብዙ ብዙ አሰብኩ። እና አንድ ቀን
ከሱ ደብዳቤ መጣልኝ። አይገርምህም? አድራሻዬን እንዴት እንዳገኘ

«ደብዳቤው ምን ይላል?» አልኩት፡፡

ከኪሱ ሁለት በአረብ ፊደላት የተፃፉ ደብዳቤዎች አውጥቶ
አንዱን ተረጎመልኝ

«ብዙ ብዙ የምነግርህ አለኝ፡፡ ግን በደብዳቤ አይሆንም።ስንገናኝ ነው። እዚህ ለንደን ውስጥ ሶስት ሚልዮን ፓውንድና ኣንድ
ዘመናዊ ማተሚያ ቤት አለን፡፡ ገንዘቡ ከቻይና፣ ከሶቭየት ህብረትና ከሌሎች ወዳጆች የተሰጠን ነው፡፡ ብዙ ሌላ እርዳታም ተሰጥቶናል፡፡
አስራ አምስት ሺ ካላሽኒኮቭ ጭምር! እንግዲህ ጊዜው ደረሰ፡፡
ፎቶግራፍህን ላክልኝና ፓስፖርት ይዤልህ እመጣለሁ። እኔና አንተ
አገራችን እንገባለን፡፡ እዚያ ብዙ ብዙ ስራ ይጠብቀናል። ዝግጁ ነህ?እንዲያው ነው የምጠይቅህ እንጂ ዝግጁ እንደሆንክ እርግጠኛ ነኝ፡፡ይህን ሁለት አመት የት የት ነበርኩ መሰለህ? ፒኪንግ፣ ሞስኮ፣ፕራግ፣ ቡዳፔስት ብቻ ስንገናኝ እነግርሀለሁ። ቶሎ ፎቶህን ላክልኝ»

ባህራም ደብዳቤውን እጥፎ ኪሱ ከተተ። ረዥም ዝምታ ሰዎቹ ካፌው ውስጥ ያወራሉ። አንዷ ኮረዳ ከሽንት ቤት ወጥታ
👍181
#ትኩሳት


#ክፍል_ሀያ_ስድስት


#በስብሐት_ገብረ_እግዚአብሔር

....ካንድ አመት ተኩል በፊት፣ በክረምት፣ ቤቱ ማሞቂያ
ስላልነበረውና የክረምቱ ብርድ ስለበረታበት፣ ካፌ «ሴንትራ» ያድር
ነበር፡፡ አሁን ደሞ የኒኮል እምባ እያባረረው ካፈ «ሴንትራ»
ያድራል። ሲጋራ እያጨሰ ሲተክዝ ያድራል፡፡ ስለ ኢራን ሲያሰላስል
ያድራል። ከንቱ ሀሳብ ሲያወጣ ከንቱ ሀሳብ ሲያወርድ ከንቱ
ሌሊቶችን ያነጋል

ያን ሰሞን የሲልቪ መፅህፍ ለሶስተኛ ጊዜ እምቢ አለ።
ለሶስተኛ ጊዜ አባረረችኝ። እኔም መፃፍ አቃተኝ፡፡ እንዴትስ ላያቅተኝ ይችላል? ሲልቪ በጉልህ ሰማያዊ አይኖቿ ብርሀን ካላየችኝ፡
በውብ ሰፊ አፏ ሙቀት ካልሳመችኝ፣ ሰለስላሳ ገላዋ ካላቀፈችኝ እንዴት ልስራ እችላለሁ? መስራቱን ተውኩት
ዩኒቨርሲቲው አጠገብ ያለው መናፈሻ ውስጥ የኤክስ አዛውንት
በስጋው አቧራ ውስጥ “boule” ሲጫወቱ፡ በኮሚክ የደቡብ
ፈረንሳይኛቸው እየፎከሩ አንዷን የብረት ኳስ በሌላ እያነጣጠሩ
ወርውረው እየገጩ እየተሳደቡ ወይም እየተሳሳቁ ሲንጫጩ አያለሁ
ከዚያ ወደ ኩር ሚራቦ ሄጄ Monoprix የተባለው ትልቅ ሱቅ
ፊት ለፊት ከአንዱ ሽማግሌ ወይም ከአንዷ አሮጊት አጠገብ
አግድም ወምበር ላይ እቀመጥና፣ የኤክስ ሚስቶችና እናቶች
ከመንገዱ ወደ ሱቁ እየገቡ፣ ከውስጥ “Monoprix የሚል
የታተመባቸው የሞሉ ቡኒ የወረቀት ከረጢቶች ይዘው ወደ መንገዱ ሲጎርፉ አያለሁ፡፡ አስተያየታቸውም ሆነ አለባበሳቸው ወይም
አረማመዳቸው የጎረምሳ አይን አይስብም፡፡ ድሮ የጎረምሳ አይን
ስበው፣ ፍቅረኛ ይዘው፣ አግብተው ወልደው በቅቷቸዋል። አሁን
ወይም አርጅተዋል፣ ወይም ወፍረዋል ወይም ተዝረክርከዋል
ኮረዳዎቹ ጡታቸውን አሹለው! ዳሌያቸውን አሳብጠው፤
አይናቸውን ተኩለው፣ ፀጉራቸውን ተሰርተው ሽቶ አርከፍክፈው
እጅጌ የሌለው የበጋ ልብስ እየለበሱ፣ የብብታቸውን የተለያየ ከለር ፀጉር እያሳዩ፣ በጎረምሳ ታጅበው እየሳቁ እያወሩ በኩር ሚራቦ ይመላለሳሉ፡፡ ወይም ካፌዎቹ በር አጠገብ መንገዱ ላይ ጠረጴዛ ዙሪያ ተቀምጠው ግማሽ ጭናቸውን እያሳዩ ልዩ ልዩ ቀዝቃዛ
እየጠጡ ያወራሉ

አሮጊቶቹና ሽማግሌዎቹ አግድም ወምበር ላይ ፈዘው ቁጭ
ብለው ፀሀይ ይሞቃሉ። እኔም ቁጭ ብዬ ስለሲልቪ ስለባህራም፣ስለኒኮል፣ ስለሉልሰገድ፣ ስለአማንዳ እያሰብኩ አላፊ አግዳሚውን
እመለከታለህ
ሲልቪ መቼ መጥታ ወደ እቅፏ ትጠራኝ ይሆን? ጊዜው አላልፍልህ ይለኛል። ወደ ዘጠኝ ሰአት ላይ ሲኒማ " እገባለሁ።
ከሲኒማ ወጥቼ አንዱ ካፌ እሄድና ኣንድ ቢራ ጠጣለሁ

አንድ ቀን ወደ አስራ ሁለት ሰአት ላይ ነበር። ሰማዩ ቀልቶ፣
ፀሀይዋ እንደ ቀይ ብርቱካን ከምእራባዊው አድማስ በላይ
ተንጠልጥላለች፡ ግን ገና አትጠልቅም፡ እስከ ሁለት ሰአት ተንጠልጥላ ኤክስን ታስውባታለች
አየሩ የሚለሰልስበት ጊዜ፣ ብቸኝነት የሚፈለግበት ሰአት ነው፡
የትዝታ የትካዜ ሰአት
ካፈ ኒኮል ሄድኩና በረንዳው ላይ ፊቴን ወደ ፀሀይዋ አድርጌ ቁጭ ብዬ ቡና አይነቱን ቢራ አዘዝኩ፡፡ አሮጊቷ ቢራውን እያቀረቡልኝ
"Ça fait longtemps qu'on vous a pas vu monsieur" አሉኝ ብዙ ጊዜ ሆነን ካየኖዎት)
Oui, madame." አልኳቸው
ጓደኛዎትስ ደህና ናቸው?»
ደህና ነው። አገሩ ገብቷል
ትምህርታቸውን ጨረሱ?»
"Il était tres gentil, votre ami“ (በጣም ጥሩ ሰው ነበር ጓደኞት")
"Oui, madame"
አሮጊቷ ሄዱ፡፡ ብቻየን ቀረሁ፡፡ ከቀይዋ ፀሀይ ጋር፣ ከቡናማው
ቢራ ጋር። ከሉልሰገድ ትዝታ ጋር መንግስተ ሰማያት ማለት
ሴት በየዛፉ ስር፣ በየግድግዳው ጥግ የሚበቅልበት ማለት ነው
አየህ፣ የኒኮል ጡት እንደ ነጭ ውብ ሰማይ ነው፡፡ ሰማዩ መሀል ላይ በሮዝ ቀለም የተከበበች ወይን ጠጅ ጨረቃ አለች እኔ 'ምልህ! ከኒኮል ጋር አልጋ ላይ የወጣህ ጊዜ' በቅዱስ ብልግናዋ ትባርክሀለች
አይ አንተ ባላገር መባዳት ቁላን እምስ ውስጥ መክተት ይመስልሀል። ስንት ሳይንስና ስንት አርት እንዳለው ባወቅክ! ኒኮልን
በቀመስክ!.....
ፀሀይዋን ከለለኝ፡ ከሉልሰገድ ነጠለኝ፡፡ ቀና ብዬ አየሁት፡፡
ባህራም። አጠገቡ አንድ ቀጭን ባለመነፅር ሰውዬ ቆሟል። ቁመቱ
ከባህራም ትንሽ ይበልጣል። ያገሩ ልጅ ይመስላል ብድግ አልኩ፡፡ ሰውዬው ፈገግ አለ። ፈገግታው ደስ ይላል። የልጅ ፈገግታ ይመስላል። እጁን እየዘረጋ፣ በጣም ወፍራም በሆነ
ድምፅ በእንግሊዝኛ ከለንደን መምጣቴ ነው አለኝ
ጨበጥኩት፡፡ አጨባበጡ ልዩ ሆኖ ተሰማኝ። እጁ አይመችም።
በኋላ ሳየው መሀል ጣቱ ወደ አንድ በኩል ተጣሟል አይታጠፍም።ሌሎቹ ጣቶቼ ረዣዥም ቀጭን ቆንጆ ናቸው
እንኳን ደህና መጣህ!» አልኩት። ቁጭ አልን፡፡ባህራም ግን አልተቀመጠም። እኔን «ይሄ ማኑ ነው።የፈለግከውን ልትነግረው ትችላለህ» አለኝና ወደ ካፌው ውስጥ ገባ የማኑ ግምባር በጣም ጠባብ ነው: ወደኋላ የተበጠረው ፀጉሩ ከቅንድቦቹ ጋር ሊገናኝ ምን ያህል አይቀረው
ሳቅ አለ፡፡ የላይኛ የፊት ጥርሱ ሁለቱ የራሱ አለመሆኑን አስተዋልኩ ሰው ሰራሽ የአጥንት ጥርስ ነው። ጥያቄው አመለጠኝና

ጥርሶችህ የት ሄዱ?» አልኩት። የልጅ ሳቁን እየሳቀ ሰባራ
መሀል ጣቱን በግራ እጁ እያሻሸ
“አገሬ ትቻቸው መጣሁ:: እስር ቤት ውስጥ ኣለኝ፡፡ ወፍራም
ድምፁ ውስጥ መመረር አያሰማም፡፡ ሲስቅ ከመነፅሩ ኋላ አይኖቹ ጥፍት ይላሉ

«አህ! » አልኩት፡፡ ምን ማለቴ እንደሆነ እንጃ

«አሁን ጥርሶቼን ፍለጋ አገሬ መመለስ አለብኝ፡፡ ባህራም
ቢያፋልገኝ ቶሉ አገኛቸው ነበር። እሱ ግን ኣላግዝህም አለኝ»

«የጥርስ ኣዳኝ መሆን አልፈልግም አለ? »

“እህስ! ያውም የኔን የጓደኛውን ጥርሶች! አይገርምህም?»
በጣም እንጂ» ይሄ ምን አይነት ንግግር ነው? የሚል ሀሳብ
ጨረፈኝ

“ካንተ ጋር ብተዋወቅና በሰፊው ባወራ ደስ ይለኝ ነበር። ግን
እቸገራለሁ። ጥርሶቼ ናፍቀውኛል» አለ። ይስቃል
«ይገባኛል» አልኩት እየሳቅኩ
ባሀራም እንደሚያስፈልገኝስ ይገባሀል?»
“አዎን"
ሳቁ ከፊቱ ጠፋ፡፡ ጉንጮቹ ወደ ውስጥ የጎደጎዱ ናቸው፡፡ በብዙ
የሚመገብ አይመስልም። ቆንጆ ጣቶቹን አየሁዋቸው፤ ንፁህ ናቸው፤ የሲጋራ ልማድ አልተለጠፈባቸውም

አሮጊቷ ሲመጡ ማኑ ቀዝቃዛ ወተት አዘዘ፡፡ አንዲት ኮረዳ
ባጠገባችን ስታልፍ ሽቶዋ አንድ ጊዜ አወደን፡፡ ነጭ ሸሚዝና
ሰማያዊ ቁምጣ የለበሰው ቅርፅዋ አይን ይማርካል፡ የሚወዛወዝ ዳሌዋ ያስጎመጃል፡፡ ማኑ አይኑን ጣል አረገባት፡ ያኔውኑ ረሳት፡ ወደ
ካፌው ውስጥ እስክትገባ በአይኑ አልተከተላትም። ለምግብም፤
ለሲጋራም፣ ለመጠጥም፡ ለሴትም ጊዜ ያለው አይመስልም። ጊዜውን
በሙሉ ለሬቮሉሽኑ መድቧል? ስራውም፤ ጨዋታውም፣ እረፍቱም
ያው ሬቮሉሽን ይሆን?
እንዲህ አይነቶቹ ታጥቀው ሲነሱ፤ በሁለት አመት ውስጥ ሞስኮ፤ ፒኪንግ፣ ቡዳፔስት ወዘተርፈ እየዞሩ ሶስት ሚልዮን
ፓውንድና አስራ አምስት ሺ መትረየስ የሚያከማቹ ጎልማሶች
ታጥቀው ሲነሱ፡ እስር ቤት ውስጥ ጣታቸው ተሰብሮ ጥርሳቸው
የተሽረፈ ሰዎች ታጥቀው ሲነሱ፣ ለሴትም ለመጠጥም ጊዜ የሌላቸው ጎረምሶች ታጥቀው ሲነሱ፡ የኢራን ሻህ ለምን ያህል ጊዜ ዙፋኑ ላይ ሊቆይ ይችል ይሆን?

ማኑ እንዲህ አለኝ
👍311
#ትኩሳት


#ክፍል_ሀያ_ሰባት


#በስብሐት_ገብረ_እግዚአብሔር


....ከዚህ በፊት መፅሀፌ " እምቢ
ሲለኝ፣ አንተን አባርሬ ምን ነበር የማረገው መሰለህ?»

«ከመፅሀፍሽ ጋር የምትታገዪ ነበር የሚመስለኝ»

ተሳስተሀል። በየቀኑ ከምሳ በኋላ ማርሰይ እወርድና፡ ከሰአት
በኋላውን፣ ማታውን፣ አንድ አራት አምስት ወንድ ተኝቶኝ፣ ወደ
እኩለ ሌሊት ላይ ድክም ብሎኝ ወደ ኤክስ እመለሳለሁ:: በቀን
በቀኑ ይህን አረጋለሁ። አንድ ቀን ልሄድ ስዘጋጅ ፃፊ ፃፊ ይለኛል፡፡
መፃፍ እጀምራለሁ፡፡ ወንዶቹ በቁኝ ማለት ነው። በፊት እንዲህ ነበር
የማረገው

«አሁንስ?»

“አሁንም ላደርገው ተነሳሁ። ማርሰይ ወረድኩ። ግን ምንም
ሳላረግ ተመለስኩ።
«ወንዶችሽ እምቢ አሉሽ?»
በጉሮሮዋ ውስጥ ቅንዝረኛ ሳቋን እየሳቀች
“ትቀልዳለህ?» አለችኝ ተለውጬ ነው እንጂ። ወንድ መሄድ
ሱስ መሆኑ ቀረ»
«ሱስ መሆኑ ቀረ እንጂ መደረጉ ግን አልቀረም፣ እ?»
«መደረጉማ ለምን ይቀራል? የስሜት ደስታ አይደለም እንዴ?»
ይህን ጊዜ ቤቷ ልንደርስ አንድ መቶ ሜትር ያህል ቀርቶናል፡፡
ታሻሽው የነበረውን እጄን ለቀቀችና
ማን ይቅደም?» ብላ ትታኝ ሮጠች፡፡ እንዳልቀድማት ብዬ
ጫማዬን በሀይል እያስጮህኩ ተከተልኳት። እሷ እየጮኸች፣ እኔ
እየሳቅኩ ቤቷ ጋ ስንደርስ፣ በሩን ቀድማኝ በእጇ ነካችው
ቀደምኩህ!» አለችና በሩን ተደግፋ ቁና ቁና ስትተነፍስ፣
ጉንጮቿን በእጆቼ ይዤ ግምባሯን ሳምኳት እንደዚህ ለዋውጠኸኝ፣ በኋላ ያላንተ እንዳት ልሆን ነው?»
አለችኝ፡፡ በሀይል አሳዘነችኝ፡፡ ሆዴ ሽምቅቅ አለ፡፡ ወደኔ አስጠግቼ
ራሷን እየደባበስኩ ውይ የኔ ቆንጆ! እንድተውሽ አትፈልጊም እንዴ?» አልኳት
«አልፈልግም አልፈልግም አልፈልግም!» እያለች በጣም
ተጠጋችኝ፡ ራሷን አንገቴ ውስጥ ሸሸገች፡፡ እምባዋ አንገቴን ነካኝ
«እኔም ልተውሽ አልፈልግም፣ የኔ ቆንጆ፣ አልተውሽም፡፡
እስከመቼም አልተውሽም፡፡ ምንም ቢመጣ አልተውሽም» አልኳት
«እፈራለሁ፡፡ ካንት መለየቱን ሳስበው እፈራለሁ፡፡ አንተ አገርህ
ትሄድና፣ ከዚያ በኋላ አንገናኝም። እስከመቸም አላይህም፡፡ በቃ
ለዘለአለም?! ውይ! እቀፈኝ! እቀፈኝ!. . . መኖር እንዴት አስቸጋሪ
ነው!»
«አይዞሽ አንለያይም፣ የኔ ሲልቪ»
«አንለያይም?»
«አንለያይም። አይዞሽ አታስቢ። አሁን እንግባ»
አልጋ ውስጥ ላዬ ላይ አደረግኳትና፣ ጀርባዋንና አንገቷን
ጭንቅላቷን እየደባበስኩ ብዙ ጊዜ ከቆየን በኋላ፤
«አሁን ተለያይተን በወድያኛው ህይወት የምንገናኝ እንኳ
ቢሆን፣ ምናልባት እችለው ነበር» አለችኝ ግን መለያየቱ ለዘለአለም
ቢሆን፡ አንድ ጊዜ አይህና ከዚያ በኋላ ለዘለአለም ለዘለአለም
እስከመቸም የማንተያይ ስንሆን፣ በጣም ያስፈራኛል!» ብላ ተጠመጠመችብኝ

«አይዞሽ እንለያይም»
«አንለያይም?»
በሩ ተንኳኳ። ድንግጥ አለች
«አይዞሽ አይዞሽ»
በሩ እንደገና ተንኳኳ
«ማነው በይ» አልኳት
«ማነው?» አለች ጮክ ብላ
«ባህራም!»
ድንጋጤዋ ወደ ብሽቀት ተለወጠ። እየተነጫነጨች ተነስታ የሌሊት ካፖርቷን ራቁት ገላዋ ላይ ጣል አርጋመቀነቱን እየታጠ
ቀች ሄዳ በሩን ከፈተች
ባህራም «ይቅርታ በዚህ ሰአት ስላስቸገርኩ» እያለ ገባ። ጥቁር
ሙሉ ሱፍ ልብስ፣ ውሀ ሰማያዊ ሸሚዝ፣ ደማቅ ሰማያዊ ክራቫት::
ፂሙን ተላጭቶ፣ ፀጉሩን ወደ ኋላ አበጥሯል፡፡ ከጎንና ከጎን የበቀለው
ሽበት' የእርጅና ምልክት መሆኑ ቀርቶ ልዩ ጌጥ መስሏል፡፡ የድል
አድራጊነት ፈገግታ የሚጨፍርበት ፊቱ ወጣትነት ተላብሷል መጥቶ የተጋደምኩበት አልጋ አጠገብ ወምበር ላይ ሲቀመጥ
«እንዲህ ዘንጠህ የት ልትሄድ ነው? » አልኩት
ሲልቪ መጥታ ከጎኔ አልጋው ውስጥ ገባች
«እገሬ መግባቴ ነው» ከለ
“ልሰናበታችሁ ነው የመጣሁት»
«መሄድህ ነው በቃ?» አለችው ሲልቪ
“አዎን"
«ቆይ ዊስኪ ላምጣልህ» ብላ፣ ከአልጋው ወጥታ ወደ ወጥ ቤት
ሄደች፡፡ ቶሎ ከኪሱ አንድ ወረቀት አውጥቶ፣ ወምበር ላይ
የተሰቀለው ኮቴ ኪስ ውስጥ ከተተና፣ በሹክሹክታ
«ለብቻህ አንብበህ ቅደደው » አለኝ
"ላንተም ላምጣልህ? » አለች ከወጥ ቤቱ
«ለኔም ላንቺም አምጪ» አልኳት
ይዛ መጣች። ከልጋ ውስጥ ገባች። ዊስኪውን አነሳሁና ባሀራምን
«መልካም ጉዞ!» አልኩት
ፉት አልን
«ከመሄዴ በፊት ጥቂት ልነግርህ የሚገባኝ ነገር አለ» አለኝ።
ሲልቪ ትታን ልትሄድ ስትል «ካንቺ የሚደበቅ ያለበት አይደለም»
አላት
«እሺ» አልኩት
ብዙ ልነግርሀ በፈቀድኩ። ግን አብዛኛው የኢራን ኮሙኒስት
ፓርቲ ምስጢር ነው፡፡ አንተን አምንሀለሁ፡፡ ግን ፓርቲው
እንድነግርህ አይፈቅድልኝም»
«ይገባኛል፡፡ ምንም መናገር የለብህም»
«አውቃለሁ፡፡ ሁለት ነገር ብቻ በጠቅላላ ባጭሩ ልንገርህን
«ሁለት አመት ሙሉ በይሩት ነበርኩ፡፡ ግን ዩኒቨርሲቲው
ውስጥ የህክምና ትምህርት አልተማርኩም፡፡ ሌላ ስራ ነበረኝ። በቅርብ ምስራቅ ውስጥ ያሉትን የኢራን ኮሙኒስቶች ሳደራጅ ነበር፡፡ በሌላ በኩል ደሞ ከሻህ ሰላዮችና ከሲ.አይ.ኤ ጋር ረዥም ጦርነት ስናካሂድ ነበር። ሲ.አይ.ኤ ሊገድለኝ ሲሆን ጊዜ፣ ቱዴህ (የኢራን ኮሙኒስት ፓርቲ) እንድሸሽ አዘዘኝ። ወደ ኤክስ መጣሁ። እውነተኛ ስሜን
ልነግርህ አልችልም፡ ግን ባህራም አይደለም። ባሀራም ከፍሻር
በይሩት ዩኒቨርሲቲ ውስጥ ህክምና ይማር ነበር። በሱ ስም የውሽት ፓስፖርት አውጥቼ ነው፡፡

«ቤቶችህ ይህን ያውቃሉ?»
«ታላቅ ወንድሜ ያውቃል። ስም በቀየርኩ ቁጥር አዲስ ስሜን
በደብዳቤ ነግረዋለሁ፣ ከቤት ገንዘብ ሲመጣልኝ እሱ በአዲሱ ስሜ እየላከው ነው፡፡ እዚህ ላይ አንድ ነገር አለኝ የምነግርህ»
ምን?»
«ደጋግመህ መልክህ የኢራንን ሻህ ይመስላል ብለኸኛል።
እውነትክን ነው:: ሻህ የስጋ ዘመዴ ነው»
አጭር ዝምታ
«ላሳየኸኝ ጓደኝነትና ለዋልክልኝ ውለታ ላመሰግንህ አልችልም፡፡
ስለዚህ ሳላመሰግንህ መሄዴ ነው» አለኝና ተነሳ፡፡ በቁሙ ዊስኪውን ጨልጦ፣ ብርጭቆውን ኮሞዲኖ ላይ አኖረው:: ልሸኘው ካልጋ ልነሳ ስል
«አትነሳ። ማኑ እዚህ ውጭ ይጠብቀኛል። አብረኸኝ ብትመጣ
ያለቅስብኛል፡፡ እሱ ሁልጊዜ እንደተጠነቀቀ ነው። ወዴት በኩል
እንደምንሄድ አንተ'ንኳ እንድታውቅ አይፈልግም» ይስቃል፡፡ ማኑን
ስለሚወደው ይስቅበታል። ከማኑ ጋር ለመሆን በመቻሉ እጅግ ደስ
ብሉታል፡፡ ወጣትነቱን እንደገና አግኝቷል። እጄን ዘረጋሁ:: ጨበጠኝ። በኔ በኩል ተንጠራርቶ ሲልቪን ሳማት። ሊሄድ ወደ በሩ በኩል ከዞረ በኋላ
«ለመሆኑ አልኩት ዞረ። ፊቱ ላይ ፈገግታ የለም፡፡ የኢራንን ሻሀ ይመስላል።አፍንጫው ትልቅ ነው
«ለመጀመሪያ ጊዜ
ሳገኝህ ሶስት አሜሪካኖች
ይዘውህ ሊደበድቡህ መጀመራቸው ነበር» አልኩት
“A bas les Yankecs!” አለኝ እየሳቀ
“A bas!" አልኩት
ሰአቱን አየ፡፡ ቸኩሏል
“ሊደበድቡህ ይዘውህ ሳለ፣ ማኑ ያስተማረሀን የመከላከል ዘዴ
ለምን አልተጠቀምክበትምን» አልኩት
«ተማሪዎች ይሁኑ ወይ የሲ.አይ.ኤ ሰዎች ይሁኑ እርግጠኛ አልነበርኩም። ምናልባት እኔን ፍለጋ የመጡ የሲ.አይ.ኤ ሰዎች ቢሆኑስ? ያን አይነት ያምባጓሮ ዘዴ ማወቄን ካወቁ ባህራም አለመሆኔን ይጠረጥራሉ። ለዚህ ነው:: በሎ ደህና ሁኑ። ማኑ ይጠብቀኛል»
👍30🥰1👏1😁1
#ትኩሳት


#ክፍል_ሀያ_ስምንት


#በስብሐት_ገብረ_እግዚአብሔር

....ጧት ተነስቼ ቁርስ ከበላሁ በኋላ ከሲልቪ ቤት ወጥቼ ወደ
ሲቴ አመራሁ፡፡ ትላንት “ማታ ባህራም ኪሴ ውስጥ ያስቀመጠውን ወረቀት መንገድ ላይ አነበብኩት፡፡ ኒኮል የፃፈችለት ደብዳቤ ነው
«ውድ ባህራም
«እንዴት ልጀምር? አስቸጋሪ ነው። እወድሀለሁ፣ ከልቤ እወድሀለሁ። አሁን የምነግርህ ነገር የማልወድህ ሊያስመስለኝ
ይችላል። ግን እወድሀለሁ፤ ከልቤ አፈቅርሀለሁ
«ያለሬቮሉሽን መኖር አትችልም። ከኔ ጋር መኖር አትችልም። ስለዚህ እኔን ትተኸኝ መሄድ አለብህ
«እኔ ስለሪቮሉሽን በጭራሽ ሊገባኝ የማይችል ብዙ ብዙ ነገር
አለ። ለምሳሌ ደም ማፍሰስ። ብዙ ተከራክረንበታል፣ ታስታውሳለሁ::
ደጋግመህ አይገባሽም! ስለሪቮሉሽን በጭራሽ አይገቤሽም ብለኸኛል። እውነትክን ነው:: አይገባኝም። ግን በደምብ የገባኝ አንድ ነገር አለ። አንተ ያለ ሬቮሉሽንህ መኖር አትችልም። ስለዚህ መለያየት አለብን።

“ከዚህ ቀጥሎ የምነግርሀ ሊገባህ አይችልም። ስለዚህ እንዲገባህ ለማድረግ አትሞክር። ዝም ብለህ እመነው። ይኸው የማፈቅረው አንተን ነው። የተረገዘው ልጅ ግን ያንተ አይደለም። የሉልሰገድ ነው። ልነግርህ ሞክሬ ነበር። ብዙ ጊዜ ሞከርኩ፣ አቃተኝ፡፡ አሁንም
ቢሆን መነፅራሙ ጓደኛህ ባያግዘኝ ኖሮ አልችልም ነበር

አዝናለሁ:: ስላደረስኩብህ ሁሉ ችግር በጣም አዝናለሁ።
ብትችል በልብህ ይቅር በለኝ። ባትችል ጥላኝ፡፡ ብቻ ሂድና
ሬቮሉሽንህ ውስጥ ኑር። ደስታ ሊስጥህ የሚችል እሱ ብቻ ነው።
በሄድክበት ይቅናህ፡፡ ደህና ሁን።
ያንተ ኒኮል።
P S ልታገኘኝ አትሞክር። አታገኘኝም። ልሰናበትህ ባለመቻሌ አዝናለሁ። ግን ፊትህ ላይ ቂም ማየት እፈራለሁ። ደህና ሁን። ይህን ደብዳቢ ሶስት ጊዜ ደጋግሜ አነበብኩት፡፡ ኒኮል ለምን
ፃፈችው ይህን? ቀዳደድኩት። ቁርጥራጮቹን በተንኳቸው:: ሲቲ ሄጄ ገላዬን ታጥቤ፣ ልብሴን ቀይሬ ወደ ኒኮል ቤት ሄድኩ አልጋዋ ላይ ተጋድማ ሲጋራ እያጨሰች ሙዚቃ ትሰማለች ታቹን ነጭ ክሮሽ እንደ ሸማኔ ጥለት የከበበው ቡና አይነት ቀሚስ ለብሳለች። ስገባ ፈገግ እያለች
«እንኳን መጣህ! ጭር ብሎኝ ነበር» አለችኝ
ደህና ነሽ?
«ደህና ነኝ፡፡ በጣም ደህና ነኝ። ግን ሌላ ሰው ማየት
አልፈልግም። እባክህን በሩን ቆልፈው።
ቆልፌው ስመጣ፣ የተጋደመችበት አልጋ ላይ እንድቀሙጥ በእጇ አመለከተችኝ። ጥፍሮቿ ሀምራዊ ተቀብተው ያብለጨልጫሉ።
ተቀመጥኩ፣ አየሁዋት። በጣም የተለወጠች መሰለኝ፡፡ ከንፈሮቿ እንደ ጥፍርቿ ሀምራዊ መሳይ ቀለም ተቀብተዋል፡ ቅንድቦቿን ወደ ሰማያዊ የሚወስድ ጥቁር ቀለም አድምቋቸዋል፣ ከግምባሯ ንጣት ጋር ሲታዩ በጣም ያምራሉ። የአይኖቿ ቆዳ ልክ የአይኖቿን
የሚመስል ውሀ እረንጓዴ ኩል ተቀብቶ፣ አይኖቿ ውስጥ ተነክሮ
የወጣ ይመስላል። ከመጠን በላይ አምሮባታል። ከጥንታዊት
ግብፃዊት ጋር ያለሁ መሰለኝ። ፀጉሯ እንደ ድሮው አመዳም
አይደለም፡ ንፁህ ቡናማ ቀለም ተነክሯል
«ምን ነካሽ?» አልኳት
«ምነው?»
«እንደዚህ የምታምሪ አይመስለኝም ነበር»
"Merci
«እውነት ግን ምንድነው?» አልኳት
«እንደዚህ ነኝ፡፡ ሳዝን ሰው እንዲያውቅብኝ አልፈልግም። አሁን
ያዘንኩ እመስላለሁ?»
በጭራሽ
«ለዚህ ነው አይኔንም የተኳልኩት፣ ፀጉሬንም የተነከርኩት»
«አዝነሻል?»
«እንደ ዛሬም አዝኜ አላውቅ፡፡ ሲሄድ ደህና ዋል አለህ?»
«አዎን»
የፃፍኩለትን አሳየህ?»
«አዎን፡፡ ለምን ፃፍሽው?»
«እንዴት እንደፃፍኩት ልንገርህ?»
«ንገሪኝ»
«ከትላንት ወድያ ማታ፣ እንደዚህ ተጋድሜ ሙዚቃ ስሰማ፣
አንድ ሰው መጣ፡ መልኩ ሰው ይመስላል እንጂ እንደኔና እንዳንተ
ህዋሳቱ ውስጥ ደም እንደሚፈስ ልምልልህ አልችልም። ምናልባት
ከነሀስ የተሰራ ሰው ሊሆንም ይችላል። ረዥም ቀጭን ነው፡ መነፅር ያረጋል። ግምባር የለውም፡ ከአይኑ ቀጥሎ አናቱ ይመጣል፡፡ ድምፁ ወፍራም ከመሆኑ የተነሳ ከሆዱ እንጂ ከጉሮሮው የሚወጣ
አይመስልም»
«ጠልተሽዋል እ?»
«መጥላት አይደለም፡፡ ፈራሁት። ቀፈፈኝ፡፡ አየህ፣ ገባና
በወፍራም ድምፁ
ኮል ማለት እርስዎ ነዎት?» አለኝ
ነኝ» አልኩት
“ጥሩ። እኔ ከኢራን ኮሙኒስት ፓርቲ ተልኬ የመጣሁ ነኝ
«ታድያ እኔ ከኢራን ኮሙኒስት ፓርቲ ምን አለኝ?
«እርስዎ አይናገሩ፡፡ ጊዜ የለኝም» አለኝ፡፡ ድምፁ በጭራሽ
አይለዋወጥም፡፡ ምንም ነገር ሲናገር በዚያው በወፍራም ድምፅ ነው
“የኢራን ኮሙኒስት ፓርቲ ባህራምን ይፈልገዋል፡፡ በጣም
ይፈልገዋል። እኔን ፓርቲው ልኮኛል። ከትእዛዝ ጋር፡፡ ወያም
ባህራምን ይዘኸው ና፣ ወይም ገድለኸው ተመለስ ተብያለህ
ግደለው? ለምን?» አልኩት
ቀላል ምክንያት፡፡ የኛን ምስጢር ያውቃል፡፡ ምስጢራችንን
በሙሉ ያውቃል፡፡ ስለዚህ፣ ወይም ከኔ ጋር ይምጣል፡ ወይም
ይሞታል። ሌላ ምርጫ የለም፡፡ ግን አንድ ነገር አለ» አለኝ
ምን?»
ባህራም አልመጣም የሚለው በእርስዎ ምክንያት ነው:: እርስዎ
ባይኖሩ ይመጣል፡፡ ስለዚህ እርስዎ እንዳይኖሩ ማድረግ፡፡»
ሆዱ እየፈራ፤ «እንዴት?» አልኩት
«መግደል» አለኝና፣ ከኪሱ አንድ የታጠፈ ጩቤ አወጣ፡፡ ጫን
ሲለው ጩቤው እንደ ብልጭታ ክፍት አለ ሻህን ልግደለው!' አለኝና፤ ያንን የኢራን
ስእል አመለከተኝ፡፡ ባህራም ነው እዚያ የለጠፈው፡፡ ልተኛ ስልና ልነሳ ስል፣ ሻህ እንዲታየኝ እፈልጋለሁ ብሎ ሰቀለው::»
ግድግዳው ላይ የኢራን ሻህ የጦር ጠቅላይ አዛዥ የማእረግ
ልብሱን ለብሶ ቆሞ በከለር የተነሳው ትልቅ ፎቶ አለ
"ለምሳሌ ሻህ እርስዎ ነዎት። ጉሮሮውን ይመልከተቱ" አለና
ጩቤዋን ወረወራት። የሻህ ጉሮሮ ላይ ስክት አለች። ሰውየው ወደ
ስእሉ ሄዶ ጩቤውን ነቀለና አጥፎ ኪሱ ከተተ መንገድ ላይ እርስዎ ሲራመዱ ወይም ሲሮጡ እኔ በፈጣን መኪና እየሄድኩ ጩቤ ብወረውር፣ ጉሮሮዎትን እልስተውም፡፡ ገባዎት?» አለኝ። በድምፁ ሊያስፈራራኝ በጭራሽ አልሞከረም፡ ልክ የጂኦሜትሪ ፕሮብሌም እንደሚያስረዳኝ ያህል ነበር ገባኝ» አልኩት። እንደዚያን ጊዜ ፈርቼ አላውቅም
«ለባህራም ይንገሩት»
«ምን ብዩ?»
«ያረገዝኩት ካንተ አይደለም፣ ይበሉት
«ታድያ ከማን ነው ልበለው?»
« እንደፈለጉ። ለምሳሌ እጀምሺድ ወይም ከሉልሰገድ ነው
ሊሉት ይችላሉ፡፡ እነሱን ሊጠይቃቸው አይችልም»
«እሺ» አልኩና ደብዳቤውን ፃፈኩ። አጣጥፎ ኪሱ ሲከተው
«ባሀራም ይህንን ካነበበ በኋላም ከርስዎ ጋር መሄድ ባይፈቅድስ?»
አልኩት
«እምቢ አይልም»
«ቢልስ?»
«እገድለዋለሁ። ደህና እደሩ» አለኝና ወጣ። እንደሱ ያለ
ከሰውነት የራቀ ሰው አጋጥሞኝ አያውቅም
ኒኮል ዝም አለች፡፡ ዝም ብዬ እየኋት። በጣም ታምራለች።
ውሀ እረንጓዴ ኩሏና ሀምራዊ የከንፈር ቀለሟ የፈርኦን ዘመን
ግብፃዊት አስመስሏታል። ሳቅ አለች
«ምነው ትኩር ብለህ ታየኛለህ?»
«አማርሽኝ» አልኳት። ውስጡን ደነገጥኩ። እንደዚህ ለማለት
አላሰብኩም ነበር። ውሀ አረንጓዴ ቆዳ ሽፍን ግልጥ በሚያደርጋቸው
ውህ እረንጓዴ እይኖቿ አየችኝ፡፡ ሀምራዊ ከናፍሯ በፈገግታ
ተላቀቁ። እጄን ጉልበቷ ላይ አሳረፍኩ፣ አልከለከለችኝም
«ጫማዬን ላወልቅ ነው» አልኳት
👍285