#የጣሪያ_ስር_አበቦች
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_አራት
፡
፡
#ትርጉሜ_ሀኒም_ኤልያስ
“እንዲያውም የእህትህን ቆንጆ ፀጉር የምትሸልተው አንተ
መሆን አለብህ!” ብላ ሚስጥራዊ ፈገግታ ብልጭ አደረገችና በመልበሻው አናት ላይ መቀሱን አስቀመጠች: “ተመልሼ ስመጣ እህትህ ፀጉሯ ተቆርጦ ካገኘሁ
ብቻ አራታችሁም ምግብ የማግኘት እድል ይኖራችኋል።" ስትል ክሪስ እኔ ላይ፣ እኔም ክሪስ ላይ እንዳፈጠጥን ጥላን ሄደች:...
ክሪስ ፈገግ አለ: “አይዞሽ ካቲ መቼም ቢሆን ፀጉርሽን አልቆርጥሽም።እናታችን በየትኛውም ሰአት ተመልሳ ስለምትመጣ እንነግራታለን፡ አይዞሽ አትፍሪ መቼም ቢሆን ፀጉርሽን አልቆርጥሽም::” ሊያቅፈኝ ወደኔ መጣ፡ “በዛ
ላይ ጣሪያው ስር ያለው ክፍል አንድ ካርቶን ብስኩትና አይብ መደበቃችን መታደል አይደል? ያቺ ጠንቋይ አሮጊት ይህንን ስለማታውቅ ለዛሬ ምግብ
ይኖረናል:” አለ።
ድንገት እናታችን ካልመጣች ብለን በመስጋት ያን ዕለት ትንሽ ብቻ በላን።ግማሹን ወተትና ጥቂት ብርቱካኖች አስቀመጥን፡ ይሁንና እናታችን ሳትመጣ ቀኑ አለቀ: ምሽቱን ሙሉ አንዴ ስተኛ፣ አንዴ ስነቃ እንዲችው ስገላበጥ
ሌሊቱ ተጋመሰ፡ እንቅልፍ ሸለብ ሲያደርገኝ አሰቃቂ ቅዠት ይመጣብኛል።ኮሪና ኬሪ ጠፍተውብን ክሪስና እኔ ጥቅጥቅ ባለ ጫካ ውስጥ በጨለማ ስንፈልጋቸው አየሁ ስማቸውን እየጠራን ብንፈልጋቸውም እነሱ
ግን መልስ አይሰጡንም፡ በፍርሀት ውስጥ ሆነን በጨለማ እየሮጥን ነበር።
በጣም የሚያስጨንቅ ህልም ነበር። ስነቃ ክሪስም መንትዮቹም ተኝተዋል።እንደገና እንቅልፍ እንዳይወስደኝ ፈለግኩ፡ ልከላከለው ሞከርኩ፡ ቀስ እያልኩ
እየሰመጥኩ እየሰመጥኩ እንደገና ጥልቅ ቅዠት የተቀላቀለበት አስፈሪ ህልም ውስጥ ገባሁ፡ በጨለማ እየሮጥኩ በደም የተሞላ ኩሬ ውስጥ ወደቅኩ ደሙ ልክ እንደሬንጅ ያጣብቃል ሽታውም እንደ ሬንጅ ነው: በአልማዝ ያሸበረቀ፣ጭንቅላቱ የወርቅና አይኖቹ ቀይ የሆኑ አሳ እየሳቀ ደም በደም አደረገኝ፡
ከዚያ ደጋግሞ የሚያስተጋባ ድምፅ “እይ! እይ! ማምለጥ አትችይም!” እያለ ጮኸ፡
ማለዳው ቢጫውን የተስፋ ብርሃን ከዘጋው ከባድ መጋረጃ ጀርባ የገረጣ መስሎ ይታያል፡ ኬሪ በእንቅልፍ ልቧ ወደኔ እየተጠጋች “እማዬ፣ ይህንን ቤት አልወደውም” ስትል አጉረመረመች: ኬሪ ያለ እረፍት ስትገላበጥ ላቅፋት ፈልጌ ክንዴን ለመዘርጋት ብሞክርም ማንቀሳቀስ አልቻልኩም:: ምን ሆኛለሁ? ራሴ ልክ ድንጋይ እንደተጫነ አይነት ከበደኝ፡ ከህመሙ የተነሳ ጭንቅላቴ
ሊከፈል መሰለኝ፡ የእግሮቼና የእጆቼ ጣቶች ላይ ይወረኛል። ሰውነቴ ድርቅ ብሏል ግድግዳዎቹ ሁሉ የተጣመሙ ይመስሉኛል። ሁሉም ነገር ቀጥ ያለ መስመር የለውም።
ከአልጋው ባሻገር ባለው በሚያብረቀርቀው መስተዋት ራሴን ለማየት ሞከርኩ::
ሆኖም የከበደኝን ጭንቅላቴን ዞር ላደርገው ብሞክርም አልንቀሳቀስ አለኝ::ሁልጊዜ ከመተኛቴ በፊት ጭንቅላቴን እንደልብ ማዘዋወር እንድችል ፀጉሬን ትራሱ ላይ እበትነዋለሁ ግማሹ ጉንጬ ላይ ያርፋል: እና ደስ የሚል ሽታውና ልስላሴው በጣም ደስ ይለኛል። የፀጉሬ ጉንጬ ላይ መነስነስ ወደ
ጣፋጭ የፍቅር ህልም ይወስደኛል።
ዛሬ ግን ትራሱ ላይ ፀጉር የለም: ፀጉሬ የት ሄዶ ነው?
መቀሱ አሁንም መልበሻው አናት ላይ እንደተቀመጠ ነው: በድንግዝግዝ ይታየኛል፡ ጉሮሮዬን ለማርጠብ ምራቄን ደጋግሜ ዋጥኩና በግድ ትንሽ ድምፅ
አውጥቼ የክሪስን ስም ተጣራሁ። ወንድሜ ክሪስ እንዲሰማኝ እንዲያደርግ ወደ እግዚአብሔር ፀለይኩ። በመጨረሻ እንግዳ በሆነ ድምፅ “ክሪስ፣ የሆነ
ነገር ሆኛለሁ፡” ብዬ በሹክሹክታ መናገር ቻልኩ። ደካማዎቹ ቃላቶቼ እንዴት እንደተሰሙ ባላውቅም ክሪስን አነቁት ከእንቅልፉ በደንብ ሳይነቃ አይኖቹን እያሻሽ ካቲ ምን ፈልገሽ ነው?” አለኝ።
ከአልጋው ላይ አስፈንጥሮ ያስነሳው የሆነ ነገር አልጎመጎምኩ፡ አልጋዬ
አጠገብ ደረሰ፡ ትንፋሹን ውጦ በድንጋጤና በፍርሀት ድምፅ አወጣ፡
“ካቲ… ወይኔ አምላኬ ሆይ!”
ጩኸቱ በፍርሀት አሳቀቀኝ
'ካቲ ‥. ወይኔ ካቲ" ሲል አቃሰተ።
አይኖቹ እንዲህ በድንጋጤ እንዲፈጡ ያደረጋቸው ምን እንደሆነ ለማወቅ አልታዘዝ ያሉኝን ክንዶቼንና ያበጠ የመሰለኝን ከባድ ጭንቅላቴን ለማንቀሳቀስ
ሞከርኩ፡ እንደምንም እጄን ማንሳት ቻልኩ ከዚያ ለመሰማት የሚችል ጮክ ያለ ድምጽ አገኘሁና የእውነት ጮህኩ። ደግሜ ደጋግሜ ጮህኩ ክሪስ
በክንዶቹ አቅፎ እስኪያባብለኝ ድረስ ልክ አእምሮው እንደተነካ ሰው እየጮህኩ ነበር።
“እባክሽ አቁሚ… እባክሽ” ተንሰቀሰቀ። “ስለ መንትዮቹ ስትይ... የባሰ አታስፈራሪያቸው.
እባክሽ ካቲ አትጩሂ፡ ያሳለፉት
ይበቃቸዋል።እስከመጨረሻው ፈሪ እንዲሆኑ እንደማትፈልጊ አውቃለሁ: ካልተረጋጋሽ
ይደነግጣሉ። እመኚኝ በህይወቴ እምልልሻለሁ። ዛሬ እንደምንም ሬንጁን ከፀጉርሽ ላይ አስለቅቅልሻለሁ "
አያትየው ከእንቅልፌ እንዳልነቃ የሆነ መድኃኒት የወጋችኝን ምልክት ክንዴ ላይ አገኘሁ እና እንደተኛሁ ትኩስ ሬንጅ ፀጉሬ ላይ አፍስሳብኛለች: አንድም
ዘለላ እንዳይቀር ሬንጁን ከመጠቀሟ በፊት ፀጉሬን በደንብ ሳትሰበስበው አልቀረችም።
ክሪስ መስተዋት እንዳላይ ቢከለክለኝም ገፍትሬው መስታወቱ ላይ ተሰየምኩ።
ጭንቅላቴ አስፈሪ ጥቁር ጓል የተቀመጠበት መስሎ ሳይ አፌ በድንጋጤ ተከፈተ በመጀመሪያ የነቃው ኮሪ ነበር የተዘጋውን መጋረጃ ገለጥ አድርጎ ከእሱ
የተሸሸገችውን ፀሀይ ለማየት ከአልጋው ወጥቶ ወደ መስኮቱ እየሮጠ ሳለ ድንገት ሲያየኝ አይኖቹ ፈጠጡ፡ ከዚያ ትንንሽ እጆቹ አይኖቹን ለማሻሽት
ከፍ አሉና ባለማመን እንደገና አተኩሮ ተመልክቶኝ፡-
"ካቲ አንቺ ነሽ?” አለ፡
“አዎ”
“ፀጉርሽ ለምን ጥቁር ሆነ?"
ለዚያ ጥያቄ መልስ ከመስጠቴ በፊት ኬሪ ነቃች። “ወይኔ!” ስትል ጮኸች። ካቲ ጭንቅላትሽ ምን ሆኖ ነው?! ትልልቅ እምባዎች ከአይኖቿ ወደ ጉንጮቿ ወረዱ፡ “አሁን ጭንቅላትሽን አልወደድኩትም” ስትል ሬንጁ እሷ
ፀጉር ላይ እንደሆነ ሁሉ ስቅስቅ ብላ አለቀሰች።
“ተረጋጊ ኬሪ” አለ ክሪስ በተረጋጋ ድምጽ። ካቲ ፀጉር ላይ ያለው ሬንጅ ነው: አሁን ስትታጠብና ሻምፑ ስታደርግበት ልክ እንደ ትናንቱ ይሆናል፡ እሷ ስትታጠብ እናንተ ሁለታችሁ ደግሞ ቁርስ እስኪቀርብ ብርቱካን እየበላችሁ
ቲቪ ተመልከቱ፡ በኋላ የካቲ ፀጉር ንፁህ ሲሆን ሁላችንም ቁርሳችንን
እንበላለን፡" አለ፡ ስለ ሁኔታችን የባሰ ፍርሀት እንዳይሰማቸው በማለት የአያታችንን ስም አልጠቀሰም ስለዚህ ወለሉ ላይ ተጠጋግተው በመቀመጥ
እርስ በርስ እየተረዳዱ ብርቱካኑን እየላጡ እየበሉ ራሳቸውን በቴሌቭዥን በሚተላለፈው የቅዳሜ ጠዋት የካርቱን ፊልም ውስጥ ከተቱ..
ክሪስ ገንዳው ውስጥ የሞቀ ውሀ ሞላልኝ: በዚያ በሚፋጅ ውሀ ውስጥ ፀጉሬን ደግሜ ደጋግሜ ነከርኩት። ክሪስ ደግሞ ሬንጁ እንዲላላ ለማድረግ ሻምፑ እያደረገ ነበር። ሬንጁ ቢላላም ከፀጉሬ ውስጥ ሊወጣ አልቻለም:
ጣቶቹ በሚያጣብቀው የሬንጅ ክምር ውስጥ ገቡ። ፀጉሮቼን ሳይነቅል ሬንጁን
ለማውጣት እየሞከረ ነው: ግብግቡ ስላደከመኝ ማሰብ የቻልኩት ስለ መቀሱ ብቻ ነው: አያትየው መልበሻው አናት ላይ ስላስቀመጠችው የሚያንፀባርቅ
መቀስ።
ክሪስ ገንዳው አጠገብ ተንበርክኮ የሬንጁን ክምር ከፀጉሬ ውስጥ ሲያወጣ ሬንጁ በፀጉሮቼ የተሸፈነ ነበር፡ ሬንጁን ከፀጉሬ ውስጥ ለማውጣት ስንሞክር
ከሁለት ሰዓት በላይ ሆኖን ነበር። “መቀሱን መጠቀም አለብህ!” ብዬ ጮህኩ።
“አይሆንም መቀስ የመጨረሻ ምርጫችን ነው” አለ እናታችን ያመጣችለትን የኬሚስትሪ ዕቃዎች በመጠቀም ፀጉሬ ሳይጎዳ ሬንጁን የሚያሟሟ ኬሚካል መቀመም እንደሚችል አስቧል።
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_አራት
፡
፡
#ትርጉሜ_ሀኒም_ኤልያስ
“እንዲያውም የእህትህን ቆንጆ ፀጉር የምትሸልተው አንተ
መሆን አለብህ!” ብላ ሚስጥራዊ ፈገግታ ብልጭ አደረገችና በመልበሻው አናት ላይ መቀሱን አስቀመጠች: “ተመልሼ ስመጣ እህትህ ፀጉሯ ተቆርጦ ካገኘሁ
ብቻ አራታችሁም ምግብ የማግኘት እድል ይኖራችኋል።" ስትል ክሪስ እኔ ላይ፣ እኔም ክሪስ ላይ እንዳፈጠጥን ጥላን ሄደች:...
ክሪስ ፈገግ አለ: “አይዞሽ ካቲ መቼም ቢሆን ፀጉርሽን አልቆርጥሽም።እናታችን በየትኛውም ሰአት ተመልሳ ስለምትመጣ እንነግራታለን፡ አይዞሽ አትፍሪ መቼም ቢሆን ፀጉርሽን አልቆርጥሽም::” ሊያቅፈኝ ወደኔ መጣ፡ “በዛ
ላይ ጣሪያው ስር ያለው ክፍል አንድ ካርቶን ብስኩትና አይብ መደበቃችን መታደል አይደል? ያቺ ጠንቋይ አሮጊት ይህንን ስለማታውቅ ለዛሬ ምግብ
ይኖረናል:” አለ።
ድንገት እናታችን ካልመጣች ብለን በመስጋት ያን ዕለት ትንሽ ብቻ በላን።ግማሹን ወተትና ጥቂት ብርቱካኖች አስቀመጥን፡ ይሁንና እናታችን ሳትመጣ ቀኑ አለቀ: ምሽቱን ሙሉ አንዴ ስተኛ፣ አንዴ ስነቃ እንዲችው ስገላበጥ
ሌሊቱ ተጋመሰ፡ እንቅልፍ ሸለብ ሲያደርገኝ አሰቃቂ ቅዠት ይመጣብኛል።ኮሪና ኬሪ ጠፍተውብን ክሪስና እኔ ጥቅጥቅ ባለ ጫካ ውስጥ በጨለማ ስንፈልጋቸው አየሁ ስማቸውን እየጠራን ብንፈልጋቸውም እነሱ
ግን መልስ አይሰጡንም፡ በፍርሀት ውስጥ ሆነን በጨለማ እየሮጥን ነበር።
በጣም የሚያስጨንቅ ህልም ነበር። ስነቃ ክሪስም መንትዮቹም ተኝተዋል።እንደገና እንቅልፍ እንዳይወስደኝ ፈለግኩ፡ ልከላከለው ሞከርኩ፡ ቀስ እያልኩ
እየሰመጥኩ እየሰመጥኩ እንደገና ጥልቅ ቅዠት የተቀላቀለበት አስፈሪ ህልም ውስጥ ገባሁ፡ በጨለማ እየሮጥኩ በደም የተሞላ ኩሬ ውስጥ ወደቅኩ ደሙ ልክ እንደሬንጅ ያጣብቃል ሽታውም እንደ ሬንጅ ነው: በአልማዝ ያሸበረቀ፣ጭንቅላቱ የወርቅና አይኖቹ ቀይ የሆኑ አሳ እየሳቀ ደም በደም አደረገኝ፡
ከዚያ ደጋግሞ የሚያስተጋባ ድምፅ “እይ! እይ! ማምለጥ አትችይም!” እያለ ጮኸ፡
ማለዳው ቢጫውን የተስፋ ብርሃን ከዘጋው ከባድ መጋረጃ ጀርባ የገረጣ መስሎ ይታያል፡ ኬሪ በእንቅልፍ ልቧ ወደኔ እየተጠጋች “እማዬ፣ ይህንን ቤት አልወደውም” ስትል አጉረመረመች: ኬሪ ያለ እረፍት ስትገላበጥ ላቅፋት ፈልጌ ክንዴን ለመዘርጋት ብሞክርም ማንቀሳቀስ አልቻልኩም:: ምን ሆኛለሁ? ራሴ ልክ ድንጋይ እንደተጫነ አይነት ከበደኝ፡ ከህመሙ የተነሳ ጭንቅላቴ
ሊከፈል መሰለኝ፡ የእግሮቼና የእጆቼ ጣቶች ላይ ይወረኛል። ሰውነቴ ድርቅ ብሏል ግድግዳዎቹ ሁሉ የተጣመሙ ይመስሉኛል። ሁሉም ነገር ቀጥ ያለ መስመር የለውም።
ከአልጋው ባሻገር ባለው በሚያብረቀርቀው መስተዋት ራሴን ለማየት ሞከርኩ::
ሆኖም የከበደኝን ጭንቅላቴን ዞር ላደርገው ብሞክርም አልንቀሳቀስ አለኝ::ሁልጊዜ ከመተኛቴ በፊት ጭንቅላቴን እንደልብ ማዘዋወር እንድችል ፀጉሬን ትራሱ ላይ እበትነዋለሁ ግማሹ ጉንጬ ላይ ያርፋል: እና ደስ የሚል ሽታውና ልስላሴው በጣም ደስ ይለኛል። የፀጉሬ ጉንጬ ላይ መነስነስ ወደ
ጣፋጭ የፍቅር ህልም ይወስደኛል።
ዛሬ ግን ትራሱ ላይ ፀጉር የለም: ፀጉሬ የት ሄዶ ነው?
መቀሱ አሁንም መልበሻው አናት ላይ እንደተቀመጠ ነው: በድንግዝግዝ ይታየኛል፡ ጉሮሮዬን ለማርጠብ ምራቄን ደጋግሜ ዋጥኩና በግድ ትንሽ ድምፅ
አውጥቼ የክሪስን ስም ተጣራሁ። ወንድሜ ክሪስ እንዲሰማኝ እንዲያደርግ ወደ እግዚአብሔር ፀለይኩ። በመጨረሻ እንግዳ በሆነ ድምፅ “ክሪስ፣ የሆነ
ነገር ሆኛለሁ፡” ብዬ በሹክሹክታ መናገር ቻልኩ። ደካማዎቹ ቃላቶቼ እንዴት እንደተሰሙ ባላውቅም ክሪስን አነቁት ከእንቅልፉ በደንብ ሳይነቃ አይኖቹን እያሻሽ ካቲ ምን ፈልገሽ ነው?” አለኝ።
ከአልጋው ላይ አስፈንጥሮ ያስነሳው የሆነ ነገር አልጎመጎምኩ፡ አልጋዬ
አጠገብ ደረሰ፡ ትንፋሹን ውጦ በድንጋጤና በፍርሀት ድምፅ አወጣ፡
“ካቲ… ወይኔ አምላኬ ሆይ!”
ጩኸቱ በፍርሀት አሳቀቀኝ
'ካቲ ‥. ወይኔ ካቲ" ሲል አቃሰተ።
አይኖቹ እንዲህ በድንጋጤ እንዲፈጡ ያደረጋቸው ምን እንደሆነ ለማወቅ አልታዘዝ ያሉኝን ክንዶቼንና ያበጠ የመሰለኝን ከባድ ጭንቅላቴን ለማንቀሳቀስ
ሞከርኩ፡ እንደምንም እጄን ማንሳት ቻልኩ ከዚያ ለመሰማት የሚችል ጮክ ያለ ድምጽ አገኘሁና የእውነት ጮህኩ። ደግሜ ደጋግሜ ጮህኩ ክሪስ
በክንዶቹ አቅፎ እስኪያባብለኝ ድረስ ልክ አእምሮው እንደተነካ ሰው እየጮህኩ ነበር።
“እባክሽ አቁሚ… እባክሽ” ተንሰቀሰቀ። “ስለ መንትዮቹ ስትይ... የባሰ አታስፈራሪያቸው.
እባክሽ ካቲ አትጩሂ፡ ያሳለፉት
ይበቃቸዋል።እስከመጨረሻው ፈሪ እንዲሆኑ እንደማትፈልጊ አውቃለሁ: ካልተረጋጋሽ
ይደነግጣሉ። እመኚኝ በህይወቴ እምልልሻለሁ። ዛሬ እንደምንም ሬንጁን ከፀጉርሽ ላይ አስለቅቅልሻለሁ "
አያትየው ከእንቅልፌ እንዳልነቃ የሆነ መድኃኒት የወጋችኝን ምልክት ክንዴ ላይ አገኘሁ እና እንደተኛሁ ትኩስ ሬንጅ ፀጉሬ ላይ አፍስሳብኛለች: አንድም
ዘለላ እንዳይቀር ሬንጁን ከመጠቀሟ በፊት ፀጉሬን በደንብ ሳትሰበስበው አልቀረችም።
ክሪስ መስተዋት እንዳላይ ቢከለክለኝም ገፍትሬው መስታወቱ ላይ ተሰየምኩ።
ጭንቅላቴ አስፈሪ ጥቁር ጓል የተቀመጠበት መስሎ ሳይ አፌ በድንጋጤ ተከፈተ በመጀመሪያ የነቃው ኮሪ ነበር የተዘጋውን መጋረጃ ገለጥ አድርጎ ከእሱ
የተሸሸገችውን ፀሀይ ለማየት ከአልጋው ወጥቶ ወደ መስኮቱ እየሮጠ ሳለ ድንገት ሲያየኝ አይኖቹ ፈጠጡ፡ ከዚያ ትንንሽ እጆቹ አይኖቹን ለማሻሽት
ከፍ አሉና ባለማመን እንደገና አተኩሮ ተመልክቶኝ፡-
"ካቲ አንቺ ነሽ?” አለ፡
“አዎ”
“ፀጉርሽ ለምን ጥቁር ሆነ?"
ለዚያ ጥያቄ መልስ ከመስጠቴ በፊት ኬሪ ነቃች። “ወይኔ!” ስትል ጮኸች። ካቲ ጭንቅላትሽ ምን ሆኖ ነው?! ትልልቅ እምባዎች ከአይኖቿ ወደ ጉንጮቿ ወረዱ፡ “አሁን ጭንቅላትሽን አልወደድኩትም” ስትል ሬንጁ እሷ
ፀጉር ላይ እንደሆነ ሁሉ ስቅስቅ ብላ አለቀሰች።
“ተረጋጊ ኬሪ” አለ ክሪስ በተረጋጋ ድምጽ። ካቲ ፀጉር ላይ ያለው ሬንጅ ነው: አሁን ስትታጠብና ሻምፑ ስታደርግበት ልክ እንደ ትናንቱ ይሆናል፡ እሷ ስትታጠብ እናንተ ሁለታችሁ ደግሞ ቁርስ እስኪቀርብ ብርቱካን እየበላችሁ
ቲቪ ተመልከቱ፡ በኋላ የካቲ ፀጉር ንፁህ ሲሆን ሁላችንም ቁርሳችንን
እንበላለን፡" አለ፡ ስለ ሁኔታችን የባሰ ፍርሀት እንዳይሰማቸው በማለት የአያታችንን ስም አልጠቀሰም ስለዚህ ወለሉ ላይ ተጠጋግተው በመቀመጥ
እርስ በርስ እየተረዳዱ ብርቱካኑን እየላጡ እየበሉ ራሳቸውን በቴሌቭዥን በሚተላለፈው የቅዳሜ ጠዋት የካርቱን ፊልም ውስጥ ከተቱ..
ክሪስ ገንዳው ውስጥ የሞቀ ውሀ ሞላልኝ: በዚያ በሚፋጅ ውሀ ውስጥ ፀጉሬን ደግሜ ደጋግሜ ነከርኩት። ክሪስ ደግሞ ሬንጁ እንዲላላ ለማድረግ ሻምፑ እያደረገ ነበር። ሬንጁ ቢላላም ከፀጉሬ ውስጥ ሊወጣ አልቻለም:
ጣቶቹ በሚያጣብቀው የሬንጅ ክምር ውስጥ ገቡ። ፀጉሮቼን ሳይነቅል ሬንጁን
ለማውጣት እየሞከረ ነው: ግብግቡ ስላደከመኝ ማሰብ የቻልኩት ስለ መቀሱ ብቻ ነው: አያትየው መልበሻው አናት ላይ ስላስቀመጠችው የሚያንፀባርቅ
መቀስ።
ክሪስ ገንዳው አጠገብ ተንበርክኮ የሬንጁን ክምር ከፀጉሬ ውስጥ ሲያወጣ ሬንጁ በፀጉሮቼ የተሸፈነ ነበር፡ ሬንጁን ከፀጉሬ ውስጥ ለማውጣት ስንሞክር
ከሁለት ሰዓት በላይ ሆኖን ነበር። “መቀሱን መጠቀም አለብህ!” ብዬ ጮህኩ።
“አይሆንም መቀስ የመጨረሻ ምርጫችን ነው” አለ እናታችን ያመጣችለትን የኬሚስትሪ ዕቃዎች በመጠቀም ፀጉሬ ሳይጎዳ ሬንጁን የሚያሟሟ ኬሚካል መቀመም እንደሚችል አስቧል።
👍30❤3👏3
#የጣሪያ_ስር_አበቦች
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_አምስት
፡
፡
#ትርጉም_ሀኒም_ኤልያስ
...አሁን ጣሪያው ስር ያለው ክፍል ውስጥ ባለው ሚስጥር ላይ ቆሻሻና የሚሸቱ ጨርቆች በሻንጣዎቹ ውስጥ በመክተት ሌላ ሚስጥር ጨመርንበት.
ስለ ሁኔታው አብዝተን ባለማውራታችን ከነገሩ እጅግ አስፈሪ መሆን አመለጥን:
ጠዋት እንነሳና ፊታችን ላይ ውሀ ረጨት እናደርጋለን። ጥርሶቻችንን በባዶ ውሀ እናፀዳለን፤ ጥቂት ውሀ እንጠጣና ትንሽ ወዲያ ወዲህ እንላለን፡ ከዚያ ጋደም ብለን ቴሌቭዥን እናያለን ወይም እናነባለን፡
መንትዮቹ ምግብ ፈልገው ሲያለቅሱ መስማቴ ህይወቴን ሙሉ ልቤ ላይ የሚኖር ጠባሳ አስቀመጠልኝ፡ አያታችንን እንዴት እንደጠላኋት። ያቺ አሮጊት እና እናታችን ይህንን ስላደረጉብን ጠላኋቸው።
የመመገቢያ ሰአታችን ያለ ምግብ ሲያልፍ እንተኛለን፡ ለሰዓታት እንተኛለን::እንቅልፍ ሲወስደን የርሀብ ወይም የብቸኝነት ወይም የምሬት ስቃይ አይሰማንም በእንቅልፍ በውሸት የደስታ ስሜት ውስጥ እንሰምጣለን ከዚያ
ስንነቃ ስለምንም ነገር ግድ አይኖረንም።
እንደ ፈዘዝኩና እንደደከምኩ ጭንቅላቴን ዞር አድርጌ ክሪስንና ኮሪን እያየሁ ነበር ከዚያ ክሪስ ከኪሱ ሰንጢ አውጥቶ የእጁን አንጓ ሲቆርጥ ያለምም
ስሜት ጋደም ብዬ እየተመለከትኩ ነው። የሚደማ እጁን ወደ ኮሪ አፍ አስጠጋና ኮሪ ቢቃወምም እሱ ግን ደሙን እንዲጠጣ አደረገው: ከዚያ የኬሪ ተራ ሆነ ሁለቱ ምንም ነገር ያልበሉ በመሆናቸው፣ የትልቁ ወንድማቸውን ደም ጠጥተው፣ በደበዘዘ፣ በፈጠጠና በተቀባይነት አይን አተኩረው ተመለከቱት።
ማድረግ ባለበት ነገር የማቅለሽለሽ ስሜት ተሰምቶኝ ፊቴን አዞርኩ። ያንን በማድረጉ አድናቆት ተሰምቶኛል። ሁልጊዜ ከባባድ ችግሮችን ማቃለል
ይችልበታል።
ከዚያ ክሪስ ወደኔ አልጋ መጣና፣ አልጋው ጠርዝ ላይ ተቀምጦ ረዘም ላሉ ደቂቃዎች ሲመለከተኝ ከቆየ በኋላ አይኖቹ ወደተቆረጠው አንጓው ዝቅ
አሉ አሁን መድማቱን አቁሟል። እኔም ደሙን ጠጥቼ ረሀቤን እንዳስታግስ ሌላኛውን ደም ስሩን ለማድማት ሰንጢውን አወጣ እንዳያደርገው ነግሬ ሰንጢውን ቀምቼ ወረወርኩት። ብርታት ለማግኘት ስል የእሱን ደም
እንደማልጠጣ ምዬ ተገዝቼ ብነግረውም መሀላዬን ከቁም ነገርም ሳይቆጥር ሰንጢውን በአልኮል ማፅዳት ጀመረ።
“ተመልሳ ባትመጣ ምንድነው የምናደርገው ክሪስ?" ስል ጠየቅኩት አያታችንን ለሁለት ሳምንት አላየናትም: አይጥ ለማጥመድ ወጥመዱ
ላይ ያደረግነውን ቺዝ የሚላስ የሚቀመስ ባጣን ጊዜ በልተን ጨርሰነዋል።ምግብ የሚባል ሳንቀምስ ሶስት ቀናችን ሆኗል፡ መንትዮቹ እንዲጠጡት
የተውንላቸው ወተትም ካለቀ አስረኛ ቀን ሆኖታል።
“በረሀብ አትገድለንም” አለ ክሪስ አጠገቤ ተኝቶ በደካማ ክንዱ እያቀፈኝ። “እሷ ያንን እንድታደርግ ከፈቀድንላት ደደቦች ነን ማለት ነው ነገ ምግብ ይዛ ካልመጣች ወይ ደግሞ እናታችንም ብቅ ካላለች አንሶላ ተልትለን መሰላል
እንሰራና ወደ መሬት እንወርዳለን” አለ፡
ጭንቅላቴ በደረቱ ላይ ስለሆነ ልቡ ሲመታ ይሰማኛል። “ምን እንደምታደርግ ታውቃለህ? ስለምትጠላን እንድንሞት ትፈልጋለች። መወለድ የማይገባን
የሰይጣን ልጆች መሆናችንን ስንት ጊዜ ነው የነገረችን?
ካቲ፤ ያቺ ጠንቋይ አሮጊት ደደብ አይደለችም: እናታችን ካለችበት ከመምጣቷ በፊት ምግብ ይዛ ትመጣለች::”
የተቆረጠ እጁን ላሽግለት ተንቀሳቀስኩ ከሁለት ሳምንት በፊት እኔና ክሪስ ለማምለጥ መሞከር ይገባን ነበር። የዚያን ጊዜ ሁለታችንም ጥንካሬ ነበረን
አሁን ብንሞክር ግን በእርግጠኝነት ወድቀን እንሞታለን፡ መንትዮቹን
በጀርባችን አዝለን ከሆነ ደግሞ የበለጠ ከባድ ይሆንብናል።
በማግስቱ ጠዋት ምንም ምግብ እንዳልመጣ የተመለከተው ክሪስ ጣሪያው ስር ወዳለው ክፍል እንድንሄድ አስገደደን፡ እኔና ክሪስ ለመራመድ እጅግ ደክመው
የነበሩትን መንትዮች ተሸከምናቸው የመማሪያ ክፍሉ ጥግ ላይ ስናስቀምጣቸው አቅማቸው ስላልቻለ እንደመተኛት
እያሉ ግድግዳውን ተደግፈው ቁጭ አሉ። ክሪስ መንትዮቹን ጀርባችን ላይ የምናስርበትን ገመድ እያዘጋጀ ነው
“በሌላ መንገድ እናደርገዋለን” አለ ክሪስ እንደገና እያሰበ “በመጀመሪያ እኔ እሄዳለሁ መሬት ስደርስ ኮሪን ታስሪውና ቀስ እያልሽ ወደታች ትለቂዋለሽ
ቀጥሎ ኬሪንም እንደዚያው ታደርጊያለሽ: በመጨረሻ አንቺ ትመጫለሽ ስለ እግዚአብሔር ብለሽ የምትችይውን ጥረት ሁሉ አርጊ! አደጋ በሚደርስበት
ወቅት ከፍተኛ ንዴት ከሰው በላይ የሆነ ጥንካሬ እንደሚፈጥር ሰምቻለሁ።"
“አንተ የበለጠ ጠንካራ ስለሆንክ እኔ መጀመሪያ ልሂድ” አልኩት በድካም ስሜት “አይሆንም! ድንገት ፈጥነው ከመጡ ለመያዝ ታች መሆን አለብኝ ያንቺ ክንዶች የኔን ያሀል ጥንካሬ የላቸውም: ክብደቱ ሁሉ አንቺ ላይ
እንዳይሆን ገመዱን ጭስ መውጫው ላይ አስርልሻለሁ እና ካቲ ይvህ የአደጋ ጊዜ ነው!”
በአይጥ መያዣ ወጥመዱ ላይ አራት የሞቱ አይጦችን በድንጋጤ ተመለከትኩ።“ትንሽ ጥንካሬ እንድናገኝ እነዚህን አይጦች መብላት አለብን፡” አለ ኮስተር ብሎ፡ “ማድረግ ያለብንን ሁሉ ማድረግ አለብን::''
እነዚያን የሞቱ ትንንሽ ወፍራም ነገሮች በመጠየፍ እየተመለከትኩ “ጥሬ ስጋ? ጥሬ አይጥ? አይሆንም!" አልኩ በቀስታ:
በጣም ተናዶና አስገዳጅ በሚመስል አይነት መንትዮቹንም ሆነ ራሴን በህይወት ለማቆየት የሚያስፈልገውን የትኛውንም ነገር ማድረግ እንዳለብኝ ነገረኝ፡ “ተመልከቺ ካቲ፣ መጀመሪያ እኔ ሁለቱንም እበላለሁ ገመዶቹን
በደንብ ለመቋጠርም የልብስ መስቀያ ስለሚያስፈልገኝ ላምጣ… ታውቂያላሽ ኬቲ እጆቼ አሁን በደንብ አይሰሩም” አለ፡
ሁላችንም በጣም ከመድከማችን የተነሳ የምንንቀሳቀሰው የግዳችንን ነው::
አየት አደረገኝና “በእውነት አይጦቹ በጨውና በበርበሬ በጣም የሚጣፍጡ ይመስለኛል” አለ፡፡
ጭንቅላታቸውን ቆርጦ ቆዳቸውን ገፈፈና አንጀታቸውን አወጣው: ትንንሽ ሆዳቸውን በመሰንጠቅ ረጃጅምና ቀጫጭን አንጀቶቻቸውን እንዲሁም ትንንሽ
ልቦቻቸውንና ሌሎች የውስጥ እቃዎቻቸውን ሲያወጣ እየተመለከትኩት ነበር ሆዴ ባዶ ባይሆን ኖሮ ሊያስመልሰኝ ይችል ነበር።
ክሪስ ጨውና በርበሬ ሊያመጣ ሲሄድ አይኖቼ ቆዳቸው ተገፍፎ ለምግብነት የተዘጋጁት አይጦች ላይ ተተክለው ቀሩ። አይኖቼን ጨፍኜ የመጀመሪያውን
ጉርሻ ለመጉረስ ሞከርኩ እርቦኛል ግን ይህንን ለመብላት የሚያክል አይደለም ረሀቤ።
ወዲያው እጅ ለእጅ ተያይዘው፣ ግንባራቸውን አጋጥመውና አይናቸውን ጨፍነው ጥጉ ላይ የተኙትን መንትዮች አሰብኩ በእናታችን ማህፀን ውስጥም እንደዚህ ተቃቅፈው የነበሩ ይመስለኛል: ምስኪን ልጆች! በአንድ ወቅት በጣም የሚወዷቸው እናትና አባት ነበሯቸው።
እነሱን በደህና መሬት ለማድረስና ከጎረቤት ምግብ ለማግኘት አይጦቹ ለእኔና ለክሪስ በቂ ጥንካሬ እንደሚሰጡን ተስፋ አድርገናል።
ክሪስ ቀስ እያለ ወደኛ ሲመለስ ሰማሁ። በሩ ላይ ቆም ብሎ አመነታ።ሽራፊ ፈገግታ እያሳየ ነው ሰማያዊ አይኖቹ ወደኔ እየተመለከቱ አንፀባረቁ።
በሁለት እጆቹ በደንብ የምናውቀውን ትልቅ የሽርሽር ቅርጫት ይዟል። ቅርጫቱ መክደን እስከሚያስቸግር ድረስ በምግብ ተሞልቷል ሁለት ትልልቅ
ፔርሙዞች አወጣ አንደኛው ውስጥ የአትክልት ሾርባ፣ ሌላኛው ውስጥ ወተት ነበረበት በማየው ነገር ግራ ተጋባሁ። እናታችን አምጥታልን ነው?
ከሆነ ታዲያ ለምን ወደታች እንድንሄድ አልጠራችንም? ለምንስ ደግሞ እኛን ፍለጋ ወደዚህ አልመጣችም?
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_አምስት
፡
፡
#ትርጉም_ሀኒም_ኤልያስ
...አሁን ጣሪያው ስር ያለው ክፍል ውስጥ ባለው ሚስጥር ላይ ቆሻሻና የሚሸቱ ጨርቆች በሻንጣዎቹ ውስጥ በመክተት ሌላ ሚስጥር ጨመርንበት.
ስለ ሁኔታው አብዝተን ባለማውራታችን ከነገሩ እጅግ አስፈሪ መሆን አመለጥን:
ጠዋት እንነሳና ፊታችን ላይ ውሀ ረጨት እናደርጋለን። ጥርሶቻችንን በባዶ ውሀ እናፀዳለን፤ ጥቂት ውሀ እንጠጣና ትንሽ ወዲያ ወዲህ እንላለን፡ ከዚያ ጋደም ብለን ቴሌቭዥን እናያለን ወይም እናነባለን፡
መንትዮቹ ምግብ ፈልገው ሲያለቅሱ መስማቴ ህይወቴን ሙሉ ልቤ ላይ የሚኖር ጠባሳ አስቀመጠልኝ፡ አያታችንን እንዴት እንደጠላኋት። ያቺ አሮጊት እና እናታችን ይህንን ስላደረጉብን ጠላኋቸው።
የመመገቢያ ሰአታችን ያለ ምግብ ሲያልፍ እንተኛለን፡ ለሰዓታት እንተኛለን::እንቅልፍ ሲወስደን የርሀብ ወይም የብቸኝነት ወይም የምሬት ስቃይ አይሰማንም በእንቅልፍ በውሸት የደስታ ስሜት ውስጥ እንሰምጣለን ከዚያ
ስንነቃ ስለምንም ነገር ግድ አይኖረንም።
እንደ ፈዘዝኩና እንደደከምኩ ጭንቅላቴን ዞር አድርጌ ክሪስንና ኮሪን እያየሁ ነበር ከዚያ ክሪስ ከኪሱ ሰንጢ አውጥቶ የእጁን አንጓ ሲቆርጥ ያለምም
ስሜት ጋደም ብዬ እየተመለከትኩ ነው። የሚደማ እጁን ወደ ኮሪ አፍ አስጠጋና ኮሪ ቢቃወምም እሱ ግን ደሙን እንዲጠጣ አደረገው: ከዚያ የኬሪ ተራ ሆነ ሁለቱ ምንም ነገር ያልበሉ በመሆናቸው፣ የትልቁ ወንድማቸውን ደም ጠጥተው፣ በደበዘዘ፣ በፈጠጠና በተቀባይነት አይን አተኩረው ተመለከቱት።
ማድረግ ባለበት ነገር የማቅለሽለሽ ስሜት ተሰምቶኝ ፊቴን አዞርኩ። ያንን በማድረጉ አድናቆት ተሰምቶኛል። ሁልጊዜ ከባባድ ችግሮችን ማቃለል
ይችልበታል።
ከዚያ ክሪስ ወደኔ አልጋ መጣና፣ አልጋው ጠርዝ ላይ ተቀምጦ ረዘም ላሉ ደቂቃዎች ሲመለከተኝ ከቆየ በኋላ አይኖቹ ወደተቆረጠው አንጓው ዝቅ
አሉ አሁን መድማቱን አቁሟል። እኔም ደሙን ጠጥቼ ረሀቤን እንዳስታግስ ሌላኛውን ደም ስሩን ለማድማት ሰንጢውን አወጣ እንዳያደርገው ነግሬ ሰንጢውን ቀምቼ ወረወርኩት። ብርታት ለማግኘት ስል የእሱን ደም
እንደማልጠጣ ምዬ ተገዝቼ ብነግረውም መሀላዬን ከቁም ነገርም ሳይቆጥር ሰንጢውን በአልኮል ማፅዳት ጀመረ።
“ተመልሳ ባትመጣ ምንድነው የምናደርገው ክሪስ?" ስል ጠየቅኩት አያታችንን ለሁለት ሳምንት አላየናትም: አይጥ ለማጥመድ ወጥመዱ
ላይ ያደረግነውን ቺዝ የሚላስ የሚቀመስ ባጣን ጊዜ በልተን ጨርሰነዋል።ምግብ የሚባል ሳንቀምስ ሶስት ቀናችን ሆኗል፡ መንትዮቹ እንዲጠጡት
የተውንላቸው ወተትም ካለቀ አስረኛ ቀን ሆኖታል።
“በረሀብ አትገድለንም” አለ ክሪስ አጠገቤ ተኝቶ በደካማ ክንዱ እያቀፈኝ። “እሷ ያንን እንድታደርግ ከፈቀድንላት ደደቦች ነን ማለት ነው ነገ ምግብ ይዛ ካልመጣች ወይ ደግሞ እናታችንም ብቅ ካላለች አንሶላ ተልትለን መሰላል
እንሰራና ወደ መሬት እንወርዳለን” አለ፡
ጭንቅላቴ በደረቱ ላይ ስለሆነ ልቡ ሲመታ ይሰማኛል። “ምን እንደምታደርግ ታውቃለህ? ስለምትጠላን እንድንሞት ትፈልጋለች። መወለድ የማይገባን
የሰይጣን ልጆች መሆናችንን ስንት ጊዜ ነው የነገረችን?
ካቲ፤ ያቺ ጠንቋይ አሮጊት ደደብ አይደለችም: እናታችን ካለችበት ከመምጣቷ በፊት ምግብ ይዛ ትመጣለች::”
የተቆረጠ እጁን ላሽግለት ተንቀሳቀስኩ ከሁለት ሳምንት በፊት እኔና ክሪስ ለማምለጥ መሞከር ይገባን ነበር። የዚያን ጊዜ ሁለታችንም ጥንካሬ ነበረን
አሁን ብንሞክር ግን በእርግጠኝነት ወድቀን እንሞታለን፡ መንትዮቹን
በጀርባችን አዝለን ከሆነ ደግሞ የበለጠ ከባድ ይሆንብናል።
በማግስቱ ጠዋት ምንም ምግብ እንዳልመጣ የተመለከተው ክሪስ ጣሪያው ስር ወዳለው ክፍል እንድንሄድ አስገደደን፡ እኔና ክሪስ ለመራመድ እጅግ ደክመው
የነበሩትን መንትዮች ተሸከምናቸው የመማሪያ ክፍሉ ጥግ ላይ ስናስቀምጣቸው አቅማቸው ስላልቻለ እንደመተኛት
እያሉ ግድግዳውን ተደግፈው ቁጭ አሉ። ክሪስ መንትዮቹን ጀርባችን ላይ የምናስርበትን ገመድ እያዘጋጀ ነው
“በሌላ መንገድ እናደርገዋለን” አለ ክሪስ እንደገና እያሰበ “በመጀመሪያ እኔ እሄዳለሁ መሬት ስደርስ ኮሪን ታስሪውና ቀስ እያልሽ ወደታች ትለቂዋለሽ
ቀጥሎ ኬሪንም እንደዚያው ታደርጊያለሽ: በመጨረሻ አንቺ ትመጫለሽ ስለ እግዚአብሔር ብለሽ የምትችይውን ጥረት ሁሉ አርጊ! አደጋ በሚደርስበት
ወቅት ከፍተኛ ንዴት ከሰው በላይ የሆነ ጥንካሬ እንደሚፈጥር ሰምቻለሁ።"
“አንተ የበለጠ ጠንካራ ስለሆንክ እኔ መጀመሪያ ልሂድ” አልኩት በድካም ስሜት “አይሆንም! ድንገት ፈጥነው ከመጡ ለመያዝ ታች መሆን አለብኝ ያንቺ ክንዶች የኔን ያሀል ጥንካሬ የላቸውም: ክብደቱ ሁሉ አንቺ ላይ
እንዳይሆን ገመዱን ጭስ መውጫው ላይ አስርልሻለሁ እና ካቲ ይvህ የአደጋ ጊዜ ነው!”
በአይጥ መያዣ ወጥመዱ ላይ አራት የሞቱ አይጦችን በድንጋጤ ተመለከትኩ።“ትንሽ ጥንካሬ እንድናገኝ እነዚህን አይጦች መብላት አለብን፡” አለ ኮስተር ብሎ፡ “ማድረግ ያለብንን ሁሉ ማድረግ አለብን::''
እነዚያን የሞቱ ትንንሽ ወፍራም ነገሮች በመጠየፍ እየተመለከትኩ “ጥሬ ስጋ? ጥሬ አይጥ? አይሆንም!" አልኩ በቀስታ:
በጣም ተናዶና አስገዳጅ በሚመስል አይነት መንትዮቹንም ሆነ ራሴን በህይወት ለማቆየት የሚያስፈልገውን የትኛውንም ነገር ማድረግ እንዳለብኝ ነገረኝ፡ “ተመልከቺ ካቲ፣ መጀመሪያ እኔ ሁለቱንም እበላለሁ ገመዶቹን
በደንብ ለመቋጠርም የልብስ መስቀያ ስለሚያስፈልገኝ ላምጣ… ታውቂያላሽ ኬቲ እጆቼ አሁን በደንብ አይሰሩም” አለ፡
ሁላችንም በጣም ከመድከማችን የተነሳ የምንንቀሳቀሰው የግዳችንን ነው::
አየት አደረገኝና “በእውነት አይጦቹ በጨውና በበርበሬ በጣም የሚጣፍጡ ይመስለኛል” አለ፡፡
ጭንቅላታቸውን ቆርጦ ቆዳቸውን ገፈፈና አንጀታቸውን አወጣው: ትንንሽ ሆዳቸውን በመሰንጠቅ ረጃጅምና ቀጫጭን አንጀቶቻቸውን እንዲሁም ትንንሽ
ልቦቻቸውንና ሌሎች የውስጥ እቃዎቻቸውን ሲያወጣ እየተመለከትኩት ነበር ሆዴ ባዶ ባይሆን ኖሮ ሊያስመልሰኝ ይችል ነበር።
ክሪስ ጨውና በርበሬ ሊያመጣ ሲሄድ አይኖቼ ቆዳቸው ተገፍፎ ለምግብነት የተዘጋጁት አይጦች ላይ ተተክለው ቀሩ። አይኖቼን ጨፍኜ የመጀመሪያውን
ጉርሻ ለመጉረስ ሞከርኩ እርቦኛል ግን ይህንን ለመብላት የሚያክል አይደለም ረሀቤ።
ወዲያው እጅ ለእጅ ተያይዘው፣ ግንባራቸውን አጋጥመውና አይናቸውን ጨፍነው ጥጉ ላይ የተኙትን መንትዮች አሰብኩ በእናታችን ማህፀን ውስጥም እንደዚህ ተቃቅፈው የነበሩ ይመስለኛል: ምስኪን ልጆች! በአንድ ወቅት በጣም የሚወዷቸው እናትና አባት ነበሯቸው።
እነሱን በደህና መሬት ለማድረስና ከጎረቤት ምግብ ለማግኘት አይጦቹ ለእኔና ለክሪስ በቂ ጥንካሬ እንደሚሰጡን ተስፋ አድርገናል።
ክሪስ ቀስ እያለ ወደኛ ሲመለስ ሰማሁ። በሩ ላይ ቆም ብሎ አመነታ።ሽራፊ ፈገግታ እያሳየ ነው ሰማያዊ አይኖቹ ወደኔ እየተመለከቱ አንፀባረቁ።
በሁለት እጆቹ በደንብ የምናውቀውን ትልቅ የሽርሽር ቅርጫት ይዟል። ቅርጫቱ መክደን እስከሚያስቸግር ድረስ በምግብ ተሞልቷል ሁለት ትልልቅ
ፔርሙዞች አወጣ አንደኛው ውስጥ የአትክልት ሾርባ፣ ሌላኛው ውስጥ ወተት ነበረበት በማየው ነገር ግራ ተጋባሁ። እናታችን አምጥታልን ነው?
ከሆነ ታዲያ ለምን ወደታች እንድንሄድ አልጠራችንም? ለምንስ ደግሞ እኛን ፍለጋ ወደዚህ አልመጣችም?
👍25❤2👏2
#የጣሪያ_ስር_አበቦች
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ስድስት
፡
፡
#ትርጉም_ሀኒም_ኤልያስ
የመንግስተ ሰማያት ጣዕም
ክሪስ በቀስታና በጥንቃቄ እጁን ከእጁ ስር፣ እግሩን ከእግሩ ስር እያደረገ ወደ መሬት ወረደ እኔ ደግሞ ጣሪያው ጠርዝ ላይ በደረቴ ተኝቼ ወደታች ሲወርድ እያየሁ ነው እጁን አንስቶ ሲያውለበልብልኝ ጨረቃዋ ወጥታ ብሩህ ሆና እያበራች ነበር፡ እንድወርድ ምልክት እየሰጠኝ ነበር። ክሪስ
እንዴት እንደወረደ አይቻለሁ: ዥዋዥዌ ከመጫወት የተለየ አይደለም ብዬ
ለራሴ ነገርኩት። ቋጠሮዎቹ ትልልቅና ጠንካሮች ናቸው: በዚያ ላይ በበቂ ሁኔታ አራርቀን ነው የሰራናቸው አንድ ጊዜ ጣሪያውን ከለቀቅኩ በኋላ ወደ
ታች እንዳልመለከት አስጠንቅቆኛል መጀመሪያ አንደኛውን እግር ካሳረፍኩ
በኋላ በሌላኛው እግሬ የታችኛውን ቋጠሮ መፈለግ ላይ እንዳተኩር ነገረኝ።
እንዳለኝ እያደረግኩ ከአስር ደቂቃ ባልሞላ ጊዜ ውስጥ መሬት ላይ ከክሪስ አጠገብ ቆምኩ።
“ዋው!” አለ ወደሱ አስጠግቶ እያቀፈኝ ከእኔ በተሻለ አደረግሽው”
የፎክስወርዝ አዳራሽ የጓሮ አትክልት ቦታ ውስጥ ነን፡ ክፍሎቹ በሙሉ ጨለማ ውጧቸዋል። የሠራተኞቹ መኖሪያ መስኮቶች ሁሉ ደማቅ ቢጫ ናቸው፡ ዝቅ ባለ ድምፅ “በል መንገዱን ካወቅከው ወደ መዋኛው ምራኝ አልኩት:
በእርግጥም መንገዱን ያውቀዋል እናታችን እሷና ወንድሞቿ ከጓደኞቻቸው
ጋር እንዴት ተደብቀው ወደ ዋና እንደሚሄዱ ነግራናለች:
እጄን ይዞ በጣቶቻችን እየተራመድን ከትልቁ ቤት ወጣን በሞቃታማው
የበጋ ምሽት ውጪ መሬት ላይ መሆን ለየት ያለ ስሜት አለው መንትዮቹን ብቻቸውን የተቆለፈ ክፍል ውስጥ ትተናቸዋል፡ ትንሽዬዋን ድልድይ ስናቋርጥ አሁን ከፎክስወርዝ ግዛት ውጪ መሆናችንን ስላወቅን ደስታ ተሰማን:: ነፃ የሆንን መሰለን፡ ቢሆንም ማንም እንዳያየን ጥንቃቄ ማድረግ አለብን። ወደ ሜዳውና እናታችን ወደ ነገረችን ሀይቅ ሮጥን።
ጣሪያው ላይ ስንወጣ አራት ሰዓት ነበር: በዛፎች የተከበበውን ትንሽ የውሀ
አካል ስናገኝ አራት ሰዓት ተኩል ሆኖ ነበር። ሌሎች ሰዎች እዚያ ኖረው ምሽታችን ይበላሽብናል ብለን ፈርተን ነበር። ነገር ግን የሀይቁ ውሀ ፀጥ ያለና
በንፋስ እንኳን የማይንቀሳቀስና የሚዋኙም ሆኑ በጀልባ የሚቀዝፉ ሰዎች የሌሉበት ነበር።
በጨረቃ ብርሃን በኮከቦች በደመቀ ሰማይ ስር ሆኜ ሀይቁን እየተመለከትኩ እንደዚህ አይነት የሚያምር ውሀ አይቼ እንደማላውቅና እንደዚህ በሀሴት
የሞላኝ ምሽት ኖሮ እንደማያውቅ አሰብኩ።
“እርቃናችንን እንዋኛለን?” ሲል ክሪስ ለየት ባለ ሁኔታ እያየኝ ጠየቀኝ፡
“አይ የውስጥ ሱሪያችንን ለብሰን ነው የምንዋኘው” አልኩት።
ችግሩ አንድም የጡት መያዣ የሌለኝ መሆኑ ነበር። አሁን ግን እዚህ ደርሰናል: አጉል የሆነው የጨዋነት ጥያቄ በዚህ በጨረቃ ብርሀን በደመቀ ውሀ ከመደሰት አያስቆመኝም። ልብሴን አውልቄ የመርከብ ማቆሚያ ወደ
ሆነው ጥልቀት የሌለው ጥግ ጋ ሮጥኩ። ስደርስ ግን ውሀው እንደ በረዶ ይቀዘቅዝ ይሆናል ብዬ ስላሰብኩ በመጀመሪያ እግሬን ነከር አድርጌ አረጋገጥኩ እውነትም በጣም ቀዝቃዛ ነው! ክሪስን ሳየው ሰዓቱን ከእጁ ላይ ፈትቶ ወደጎን
በማስቀመጥ ወደ እኔ እየሮጠ መጣና ደፍሬ ወደ ውሀው ከመግባቴ በፊት ጀርባዬ ጋ ደርሶ ገፈተረኝ: ውሀው ውስጥ በደረቴ ወደቅኩና ሙሉ በሙሉ
ውሀ ውስጥ ጠለቅኩ።
ከውሀው ስወጣ እየተንቀጠቀጥኩ ነበር። ወደ ክሪስ ተመለከትኩ ከፍ ያለ ድንጋይ ላይ ቆሟል ክንዶቹን ወደ ላይ አነሳና ወደ ሀይቁ ተወርውሮ ገባ፡ በድንጋጤ አቃተትኩ። ውሀው በቂ ጥልቀት ያለው ባይሆንስ? መሬቱ
መትቶት አንገቱ ወይም ጀርባው ቢሰበርስ?
ክሪስ ወደ ላይ አልተንሳፈፈም: አምላኬ! ሞቷል ሰምጧል!
“ክሪስ!” እየጠራሁትና እያለቀስኩ ገብቶ ወደተሰወረበት ቦታ መዋኘት ጀመርኩ።
ድንገት የሆነ ነገር እግሬን ያዘኝ! ጮህኩና ወደ ውስጥ ገባሁ የጎተተኝ ክሪስ ነበር፡ በጥንካሬ እግሮቹን እያወራጨ ወደምንስቅበትና ውሀ ወደምንረጫጭበት ወጣን
“እዚያ የተረገመ የሚሞቅ ቤት ውስጥ ከመዘጋት ቅዝቃዜው አይሻልም? ሲል ጠየቀኝ፡ ልክ እንደ እብድ ዙሪያውን እየዞረ ሲጮህ ላየው ይህች ትንሽ ነፃነት እንደ ጠንካራ የወይን ጠጅ አናቱ ላይ ወጥታ ያሰከረችው ይመስል
ነበር። ዙሪያዬን እየዞረ ዋኘና እግሬን ይዞ ወደታች ሊጎትተኝ ሞከረ: አሁን
ግን አልቻለም:
ውሀ እየተረጫጨንና እየዘፈንን፣ ከዚያ ደግሞ አቅፎኝ ስንስቅና ስንጮ ነበር። ልክ እንደገና ልጆች የሆንን ይመስል ታገልን… አበድን ውሀ ውስጥ በጣም ጎበዝ ነው ልክ እንደ ዳንሰኛ: እየዋኘን እያለ በድንገት ደከመኝ::በጣም ከመድከሜ የተነሳ እንደ እርጥብ ፎጣ ሆኜ ነበር። ክሪስ በክንዱ ደግፎ ወደ ዳር እንድወጣ አገዘኝ።
ሁለታችንም ሀይቁ ዳር ላይ ያለው ሳር ላይ በጀርባችን ተጋድመን ማውራት ጀመርን።
“አንድ ጊዜ እንዋኝና ወደ መንትዮቹ እንመለስ” አለ ሁለታችንም
የሚያብረቀርቁና የሚጣቀሱ የሚመስሉት ኮከቦች ላይ አተኩረናል። ደስ የምትል ግማሽ ጨረቃ ደመናው ውስጥ ብቅ ጥልቅ እያለች ድብብቆሽ
የምትጫወት ትመስላለች፡ “ምናልባት ወደ ጣሪያው መውጣት ባንችልስ?” አልኩ
“እንችላለን፡ ምክንያቱም ማድረግ አለብን” ክሪስቶፈር ሁልጊዜ እንደሚቻል የሚያምን ልጅ ነው: ሰውነቱ በውሀ ረጥቦ፣ ፀጉሩ ግንባሩ ላይ ተጣብቆ አጠገቤ ተጋድሟል። አፍንጫው እንደ አባታችን አፍንጫ ቀጥ ያለ ነው: ከንፈሮቹ የሚያምር ቅርፅ አላቸው:: አገጩ አራት ማዕዘን ሲሆን ደረቱ መስፋት ጀምሯል። እያደገ ያለው ወንድነቱ በጠንካራ ጭኖቹ መሀል ማበጥ ጀምሯል። ስለ ወንዶች ሳስብ አንድ ነገር ይማርከኛል
ያም ጥሩ ቅርፅ ያላቸው ጭኖች ናቸው፡ ጥፋተኝነት ሳይሰማኝና ሳላፍር ቁንጅናውን በአይኖቼ ለመመገብ ባለመቻሌ አዝኜ ጭንቅላቴን አዞርኩ።
ፊቱን አዙሮ አይኖቼን ተመለከተ: እኔም አየሁት። ሌላ ቦታ መመልከት
የማንችል እስኪመስል ድረስ እይታዎቻችን ተቆላለፉ ለስላሳ የደቡብ ነፋስ ፀጉሬ ውስጥ እየተጫወተና ፊቴ ላይ ያለውን ውሀ
እያደረቀው ነው፡ ምሽቱ በጣም ጣፋጭና በጣም ደስ የሚል ቢሆንም ፍቅርን የመራብ ከፍተኛ ስሜት ውስጥ ባለ ዕድሜ ላይ ያለሁ በመሆኔ ብቻ ምንም
ምክንያት ሳይኖረኝ ማልቀስ ፈለግኩ: ከዚህ በፊት እዚህ የነበርኩ አይነት ስሜት ተሰማኝ፡ ከሀይቁ አጠገብ ሳሩ ላይ እንደተጋደምኩ እንግዳ የሆነ
ሀሳብ በመጀመሪያ እንደ ተሳዳጅ ወደዚህ ወደመጣንበትና ከማይፈልገን አለም ወደተሸሸግንበት ወደዚያ ምሽት መለሰኝ።
ክሪስ፣ አሁን አስራሰባት አመት ሊሆንህ ነው፣ አባቴ እናቴን በመጀመሪያ ሲያገኛት የነበረበት እድሜ ማለት ነው”
አንቺ ደግሞ አስራ አራት፤ ልክ በእሷ እድሜ” ድምፁ ጎርነን ብሎ ነበር።
መጀመሪያ እይታ በሚፈጠር ፍቅር ታምናለህ?”
“በዚህ ርዕስ ላይ ጠቢብ አይደለሁም ትምህርት ቤት እያለሁ፣ አመነታ አንዲት የምታምር ልጅ አይቼ ወዲያው ፍቅር ይዞኝ ነበር ስናወራ ግን የሆነች ደነዝ ነገር ሆና ሳገኛት ለሷ የነበረኝ ስሜት ጠፋ፡ ግን ውበቷ በሌሎች
ነገሮች ከተደገፈ በመጀመሪያ እይታም ፍቅር ሊይዘኝ ይችላል ብዬ አስባለሁ ነገር ግን እንደዚያ አይነት ፍቅር አካላዊ መሳሳብ ብቻ እንደሆነ አንብቤያለሁ።
“እኔስ ደነዝ እመስልሀለሁ?”
“በጭራሽ! እንደሆንሽ እንደማታስቢ ተስፋ አለኝ፡፡ ምክንያቱም አይደለሽም።ፈገግ ብሎ ፀጉሬን ሊነካ እጁን እየዘረጋ ችግሩ ካቲ፣ ብዙ ተሰጥኦዎች ስላሉሽ ሁሉንም መሆን ትፈልጊያለሽ ያ ደግሞ የማይቻል ነው:"
“ዘፋኝም ተዋናይም መሆን እንደምፈልግ እንዴት አወቅክ?”
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ስድስት
፡
፡
#ትርጉም_ሀኒም_ኤልያስ
የመንግስተ ሰማያት ጣዕም
ክሪስ በቀስታና በጥንቃቄ እጁን ከእጁ ስር፣ እግሩን ከእግሩ ስር እያደረገ ወደ መሬት ወረደ እኔ ደግሞ ጣሪያው ጠርዝ ላይ በደረቴ ተኝቼ ወደታች ሲወርድ እያየሁ ነው እጁን አንስቶ ሲያውለበልብልኝ ጨረቃዋ ወጥታ ብሩህ ሆና እያበራች ነበር፡ እንድወርድ ምልክት እየሰጠኝ ነበር። ክሪስ
እንዴት እንደወረደ አይቻለሁ: ዥዋዥዌ ከመጫወት የተለየ አይደለም ብዬ
ለራሴ ነገርኩት። ቋጠሮዎቹ ትልልቅና ጠንካሮች ናቸው: በዚያ ላይ በበቂ ሁኔታ አራርቀን ነው የሰራናቸው አንድ ጊዜ ጣሪያውን ከለቀቅኩ በኋላ ወደ
ታች እንዳልመለከት አስጠንቅቆኛል መጀመሪያ አንደኛውን እግር ካሳረፍኩ
በኋላ በሌላኛው እግሬ የታችኛውን ቋጠሮ መፈለግ ላይ እንዳተኩር ነገረኝ።
እንዳለኝ እያደረግኩ ከአስር ደቂቃ ባልሞላ ጊዜ ውስጥ መሬት ላይ ከክሪስ አጠገብ ቆምኩ።
“ዋው!” አለ ወደሱ አስጠግቶ እያቀፈኝ ከእኔ በተሻለ አደረግሽው”
የፎክስወርዝ አዳራሽ የጓሮ አትክልት ቦታ ውስጥ ነን፡ ክፍሎቹ በሙሉ ጨለማ ውጧቸዋል። የሠራተኞቹ መኖሪያ መስኮቶች ሁሉ ደማቅ ቢጫ ናቸው፡ ዝቅ ባለ ድምፅ “በል መንገዱን ካወቅከው ወደ መዋኛው ምራኝ አልኩት:
በእርግጥም መንገዱን ያውቀዋል እናታችን እሷና ወንድሞቿ ከጓደኞቻቸው
ጋር እንዴት ተደብቀው ወደ ዋና እንደሚሄዱ ነግራናለች:
እጄን ይዞ በጣቶቻችን እየተራመድን ከትልቁ ቤት ወጣን በሞቃታማው
የበጋ ምሽት ውጪ መሬት ላይ መሆን ለየት ያለ ስሜት አለው መንትዮቹን ብቻቸውን የተቆለፈ ክፍል ውስጥ ትተናቸዋል፡ ትንሽዬዋን ድልድይ ስናቋርጥ አሁን ከፎክስወርዝ ግዛት ውጪ መሆናችንን ስላወቅን ደስታ ተሰማን:: ነፃ የሆንን መሰለን፡ ቢሆንም ማንም እንዳያየን ጥንቃቄ ማድረግ አለብን። ወደ ሜዳውና እናታችን ወደ ነገረችን ሀይቅ ሮጥን።
ጣሪያው ላይ ስንወጣ አራት ሰዓት ነበር: በዛፎች የተከበበውን ትንሽ የውሀ
አካል ስናገኝ አራት ሰዓት ተኩል ሆኖ ነበር። ሌሎች ሰዎች እዚያ ኖረው ምሽታችን ይበላሽብናል ብለን ፈርተን ነበር። ነገር ግን የሀይቁ ውሀ ፀጥ ያለና
በንፋስ እንኳን የማይንቀሳቀስና የሚዋኙም ሆኑ በጀልባ የሚቀዝፉ ሰዎች የሌሉበት ነበር።
በጨረቃ ብርሃን በኮከቦች በደመቀ ሰማይ ስር ሆኜ ሀይቁን እየተመለከትኩ እንደዚህ አይነት የሚያምር ውሀ አይቼ እንደማላውቅና እንደዚህ በሀሴት
የሞላኝ ምሽት ኖሮ እንደማያውቅ አሰብኩ።
“እርቃናችንን እንዋኛለን?” ሲል ክሪስ ለየት ባለ ሁኔታ እያየኝ ጠየቀኝ፡
“አይ የውስጥ ሱሪያችንን ለብሰን ነው የምንዋኘው” አልኩት።
ችግሩ አንድም የጡት መያዣ የሌለኝ መሆኑ ነበር። አሁን ግን እዚህ ደርሰናል: አጉል የሆነው የጨዋነት ጥያቄ በዚህ በጨረቃ ብርሀን በደመቀ ውሀ ከመደሰት አያስቆመኝም። ልብሴን አውልቄ የመርከብ ማቆሚያ ወደ
ሆነው ጥልቀት የሌለው ጥግ ጋ ሮጥኩ። ስደርስ ግን ውሀው እንደ በረዶ ይቀዘቅዝ ይሆናል ብዬ ስላሰብኩ በመጀመሪያ እግሬን ነከር አድርጌ አረጋገጥኩ እውነትም በጣም ቀዝቃዛ ነው! ክሪስን ሳየው ሰዓቱን ከእጁ ላይ ፈትቶ ወደጎን
በማስቀመጥ ወደ እኔ እየሮጠ መጣና ደፍሬ ወደ ውሀው ከመግባቴ በፊት ጀርባዬ ጋ ደርሶ ገፈተረኝ: ውሀው ውስጥ በደረቴ ወደቅኩና ሙሉ በሙሉ
ውሀ ውስጥ ጠለቅኩ።
ከውሀው ስወጣ እየተንቀጠቀጥኩ ነበር። ወደ ክሪስ ተመለከትኩ ከፍ ያለ ድንጋይ ላይ ቆሟል ክንዶቹን ወደ ላይ አነሳና ወደ ሀይቁ ተወርውሮ ገባ፡ በድንጋጤ አቃተትኩ። ውሀው በቂ ጥልቀት ያለው ባይሆንስ? መሬቱ
መትቶት አንገቱ ወይም ጀርባው ቢሰበርስ?
ክሪስ ወደ ላይ አልተንሳፈፈም: አምላኬ! ሞቷል ሰምጧል!
“ክሪስ!” እየጠራሁትና እያለቀስኩ ገብቶ ወደተሰወረበት ቦታ መዋኘት ጀመርኩ።
ድንገት የሆነ ነገር እግሬን ያዘኝ! ጮህኩና ወደ ውስጥ ገባሁ የጎተተኝ ክሪስ ነበር፡ በጥንካሬ እግሮቹን እያወራጨ ወደምንስቅበትና ውሀ ወደምንረጫጭበት ወጣን
“እዚያ የተረገመ የሚሞቅ ቤት ውስጥ ከመዘጋት ቅዝቃዜው አይሻልም? ሲል ጠየቀኝ፡ ልክ እንደ እብድ ዙሪያውን እየዞረ ሲጮህ ላየው ይህች ትንሽ ነፃነት እንደ ጠንካራ የወይን ጠጅ አናቱ ላይ ወጥታ ያሰከረችው ይመስል
ነበር። ዙሪያዬን እየዞረ ዋኘና እግሬን ይዞ ወደታች ሊጎትተኝ ሞከረ: አሁን
ግን አልቻለም:
ውሀ እየተረጫጨንና እየዘፈንን፣ ከዚያ ደግሞ አቅፎኝ ስንስቅና ስንጮ ነበር። ልክ እንደገና ልጆች የሆንን ይመስል ታገልን… አበድን ውሀ ውስጥ በጣም ጎበዝ ነው ልክ እንደ ዳንሰኛ: እየዋኘን እያለ በድንገት ደከመኝ::በጣም ከመድከሜ የተነሳ እንደ እርጥብ ፎጣ ሆኜ ነበር። ክሪስ በክንዱ ደግፎ ወደ ዳር እንድወጣ አገዘኝ።
ሁለታችንም ሀይቁ ዳር ላይ ያለው ሳር ላይ በጀርባችን ተጋድመን ማውራት ጀመርን።
“አንድ ጊዜ እንዋኝና ወደ መንትዮቹ እንመለስ” አለ ሁለታችንም
የሚያብረቀርቁና የሚጣቀሱ የሚመስሉት ኮከቦች ላይ አተኩረናል። ደስ የምትል ግማሽ ጨረቃ ደመናው ውስጥ ብቅ ጥልቅ እያለች ድብብቆሽ
የምትጫወት ትመስላለች፡ “ምናልባት ወደ ጣሪያው መውጣት ባንችልስ?” አልኩ
“እንችላለን፡ ምክንያቱም ማድረግ አለብን” ክሪስቶፈር ሁልጊዜ እንደሚቻል የሚያምን ልጅ ነው: ሰውነቱ በውሀ ረጥቦ፣ ፀጉሩ ግንባሩ ላይ ተጣብቆ አጠገቤ ተጋድሟል። አፍንጫው እንደ አባታችን አፍንጫ ቀጥ ያለ ነው: ከንፈሮቹ የሚያምር ቅርፅ አላቸው:: አገጩ አራት ማዕዘን ሲሆን ደረቱ መስፋት ጀምሯል። እያደገ ያለው ወንድነቱ በጠንካራ ጭኖቹ መሀል ማበጥ ጀምሯል። ስለ ወንዶች ሳስብ አንድ ነገር ይማርከኛል
ያም ጥሩ ቅርፅ ያላቸው ጭኖች ናቸው፡ ጥፋተኝነት ሳይሰማኝና ሳላፍር ቁንጅናውን በአይኖቼ ለመመገብ ባለመቻሌ አዝኜ ጭንቅላቴን አዞርኩ።
ፊቱን አዙሮ አይኖቼን ተመለከተ: እኔም አየሁት። ሌላ ቦታ መመልከት
የማንችል እስኪመስል ድረስ እይታዎቻችን ተቆላለፉ ለስላሳ የደቡብ ነፋስ ፀጉሬ ውስጥ እየተጫወተና ፊቴ ላይ ያለውን ውሀ
እያደረቀው ነው፡ ምሽቱ በጣም ጣፋጭና በጣም ደስ የሚል ቢሆንም ፍቅርን የመራብ ከፍተኛ ስሜት ውስጥ ባለ ዕድሜ ላይ ያለሁ በመሆኔ ብቻ ምንም
ምክንያት ሳይኖረኝ ማልቀስ ፈለግኩ: ከዚህ በፊት እዚህ የነበርኩ አይነት ስሜት ተሰማኝ፡ ከሀይቁ አጠገብ ሳሩ ላይ እንደተጋደምኩ እንግዳ የሆነ
ሀሳብ በመጀመሪያ እንደ ተሳዳጅ ወደዚህ ወደመጣንበትና ከማይፈልገን አለም ወደተሸሸግንበት ወደዚያ ምሽት መለሰኝ።
ክሪስ፣ አሁን አስራሰባት አመት ሊሆንህ ነው፣ አባቴ እናቴን በመጀመሪያ ሲያገኛት የነበረበት እድሜ ማለት ነው”
አንቺ ደግሞ አስራ አራት፤ ልክ በእሷ እድሜ” ድምፁ ጎርነን ብሎ ነበር።
መጀመሪያ እይታ በሚፈጠር ፍቅር ታምናለህ?”
“በዚህ ርዕስ ላይ ጠቢብ አይደለሁም ትምህርት ቤት እያለሁ፣ አመነታ አንዲት የምታምር ልጅ አይቼ ወዲያው ፍቅር ይዞኝ ነበር ስናወራ ግን የሆነች ደነዝ ነገር ሆና ሳገኛት ለሷ የነበረኝ ስሜት ጠፋ፡ ግን ውበቷ በሌሎች
ነገሮች ከተደገፈ በመጀመሪያ እይታም ፍቅር ሊይዘኝ ይችላል ብዬ አስባለሁ ነገር ግን እንደዚያ አይነት ፍቅር አካላዊ መሳሳብ ብቻ እንደሆነ አንብቤያለሁ።
“እኔስ ደነዝ እመስልሀለሁ?”
“በጭራሽ! እንደሆንሽ እንደማታስቢ ተስፋ አለኝ፡፡ ምክንያቱም አይደለሽም።ፈገግ ብሎ ፀጉሬን ሊነካ እጁን እየዘረጋ ችግሩ ካቲ፣ ብዙ ተሰጥኦዎች ስላሉሽ ሁሉንም መሆን ትፈልጊያለሽ ያ ደግሞ የማይቻል ነው:"
“ዘፋኝም ተዋናይም መሆን እንደምፈልግ እንዴት አወቅክ?”
👍33❤2
#የጣሪያ_ስር_አበቦች
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ሰባት
፡
፡
#ትርጉም_ሀኒም_ኤልያስ
አንድ ዝናባማ ከሰዓት
ሰማዩ ከብዶ ዝናቡ በጣም እየወረደ ነው: ክፍላችን ውስጥ ያሉ መብራቶች
ሁሉ በርተዋል፡ ቲቪውም እንደተለመደው ተከፍቷል። ክሪስ የመስኮቱን ከባባድ መጋረጃዎች በሁለት እጆቹ ከፈት አድርጎ ይዞ በመቆም ከሩቅ ትንሽ የአሻንጉሊት ባቡር መስሎ ሁልጊዜ አስር ሠዓት ገደማ አሳዛኝ ፊሽካውን እያሰማ የሚያልፈውን ባቡር ለማየት እየጠበቀ ነው:
በራሱ ዓለም ውስጥ ነው፧ እኔም በራሴ አለም ውስጥ እግሮቼን አጣምሬ እኔና
ኬሪ የምንጋራው አልጋ ላይ በመቀመጥ እናታችን ለመጨረሻ የመጣች ጊዜ
ካመጣችው መፅሄት ላይ ምስሎች እየመረጥኩ በውስጡ ያሉትን ፎቶግራፎች በጥንቃቄ እየቆረጥኩ የማልመውን አይነት በደስታ የምኖርበት ቤት፣ ሺ ሴቶችን በጎኑ የሚደርግ ሳይሆን እኔን ብቻ የሚወደኝ የምምኘውን አይነት ረጅም፣ ጠንካራ፣ ጥቁር ፀጉር ያለው ባል በማድረግ የቆራረጥኳቸውን የምስል ቁራጮች ሌላ መፅሀፍ ላይ እየለጠፍኩ ህይወቴን እየሳልኩ ነው።
ዳንሰኛ መሆን ሳቆም ባልና ልጆች ይኖሩኛል የማልመው አይነት ቤት ሲኖረኝ ደግሞ ከውድ ድንጋይ የተሰራ የመታጠቢያ ገንዳ ይኖረኛል ከዚያ ለውበት የሚሆኑ ዘይቶች አደርግበትና ማንም በሩን እያንኳኳ ፈጠን በይ
ሳይለኝ ከፈለግኩ ቀኑን ሙሉ ተዘፍዝፌ እውላለሁ። ከዚያ ቆዳዬ በጣም
ለስላሳና ምንም እንከን የሌለበት ጥርት ያለ ይሆንና ደስ የሚል ሽታ ያለው
የሽቶ ጠረን ይኖረኛል። ይሄ የበሰበሰ አሮጌ ደረቅ እንጨት ሽታና ጣሪያው
ስር ያለው ክፍል አቧራ ከነችግሮቹና አሮጌ እቃዎቹ ጋር እኛን ወጣቶቹን ልክ እንደዚህ አሮጌ ቤት ያለ ጠረን እንዲኖረን አድርጎናል
ክሪስ” አልኩት ጀርባው ላይ እያፈጠጥኩ። “አሁን ጠንካሮች ነን፤ ታዲያ
ለምንድነው እናታችን ተመልሳ እስክትመጣና ሽማግሌው እስኪሞት መጠበቅ ያለብን? ለምንድነው የማምለጫ መንገድ የማንፈልገው?” ቃል አልተነፈሰም። ግን እጆቹ የመጋረጃውን ጨርቅ ጨምድደው ሲይዙ ተመለከትኩ::
“ክሪስ...”
“ስለሱ ማውራት አልፈልግም” አለ በንዴት
“ስለመሄድ እያሰብክ ካልሆነ ታዲያ ለምንድነው እዚያ ቆመህ ባቡሩ እስኪያልፍ የምትጠብቀው?”
“ባቡሩን እየጠበቅኩ አይደለም! በቃ ዝም ብዬ ወደ ውጪ እየተመለከትኩ
ነው:”
በግንባሩ የመስኮቱን መስታወት ተደግፏል። ቅርብ ያለ ጎረቤት እንዲያየው የደፈረ ይመስላል
“ክሪስ ከመስኮቱ ዞር በል የሆነ ሰው ሊያይህ ይችላል”
“ማንም ቢያየኝ ግድ የለኝም!”
የመጀመሪያ ስሜቴ ወደሱ ሮጬ በክንዶቼ አቅፌ ከእናታችን ያጣቸውን
እነዚያን መሳሞች ለማካስ ፊቱን በሙሉ በሚሊየን በሚቆጠሩ መሳሞች
ማዳረስ ነበር እሷ እንደምታደርገው ጭንቅላቱን ደረቴ ላይ አስደግፌ ፀጉሩን እያሻሸሁ በፊት ወደነበረበት አይነት ደስተኛ፣ የሚናደድበት ቀን የሌለው፣ መልካም ነገር ብቻ የሚመለከት ሰው ወደመሆኑ ልመልሰው ፈለግኩ። ነገር ግን በፊት እናታችን ታደርግለት የነበረውን ነገር ሁሉ ባደርግለትም ተመሳሳይ
እንደማይሆን አውቅ ነበር፡ እሷን ነው የሚፈልገው: ተስፋዎቹ፣ ህልሞቹና
እምነቱ በሙሉ በአንዲት ሴት ውስጥ ታሽጓል በእናታችን፡፡
አሁን ከመጣች ሁለት ወር አልፏታል! እዚህ ቤት የምናሳልፈው አንድ ቀን በትክክለኛው ህይወት ሲለካ ከወር በላይ እንደሚረዝም አልገባትም
ስለኛ አትጨነቅም? እንዴት እንደምንኖር አታስብም? ያለምንም ማብራሪያ፣
ምክንያት ወይም ሰበብ ስትተወን እያየ ክሪስ ሁልጊዜ የሷ ቀንደኛ ደጋፊ
እንደሚሆን ታምናለች? ፍቅር በጥርጣሬና በፍርሀት በአንድ ጊዜ ሊፈርስ
እንደሚችልና በፍፁም ዳግመኛ ሊገነባ እንደማይችል አታውቅም?
"ካቲ” አለ ክሪስ ድንገት “የሆነ ቦታ የመሄድ ምርጫ ቢኖርሽ የት ትሄጃለሽ?
“ደቡብ” አልኩ “የሚሞቅና ፀሀያማ የባህር ዳርቻ ወዳለው… ሞገዶች ለስላሳ
ወደሆኑበትና ሀይለኛ ነፋስ ወደማይነፍስበት መሄድ እፈልጋለሁ በነጭ አሸዋ ላይ ጋደም ብዬ የፀሀይ ብርሃኔን እየጠጣሁ ለስለስ ያለ ንፋስ ፀጉሬ ውስጥና ጉንጮቼ ላይ ሲንሸራሸር መስማት ነው የምፈልገው”
“ልክ ነው…” ተስማማ፡ “የገለፅሽበት መንገድ አሪፍ ይመስላል እኔ ግን ልክ
እንደ በረዶ ሸርተቴ ሁሉ በሀይለኛ ሞገድ ውስጥ መንሳፈፍም እወዳለሁ።”
ምስሎቹን እየቆራረጥኩ የነበርኩበትን መቀስና መፅሄቱን አስቀምጬ ሙሉ
በሙሉ ክሪስ ላይ ትኩረት አደረግኩ፡ ክሪስ የሚወዳቸውን ብዙ ስፖርቶች አጥቶ፣ በአንድ ክፍል ውስጥ ታሽጎ፣ ከእድሜው በላይ አርጅቶና አዝኖ ስመለከተው ላፅናናው ብፈልግም እንዴት እንደማፅናናው ግን አላወቅኩም።
ክሪስ እባክህ ከመስኮቱ ጋ ተመለስ?” አልኩት።
“ተይኝ! ይሄ ቦታ እጅግ ሰልችቶኛል ይህንን አታድርግ፣ ያንን አታድርግ፣
ካላናገሩህ እንዳትናገር መባል፤ በየቀኑ እነዚህን በደንብ በደንብ የማይሰሩ ጣዕም አልባ ምግቦች መብላት ታክቶኛል
በምግብም እንኳን እንዳንደሰት ሆነ ብላ ነው እንደዛ የምታደርገው: ስለዛ
ሁሉ ገንዘብ ሳስብ ደግሞ ግማሹ የእናታችንና የእኛ በመሆኑ እንደሚገባን
አስባለሁ። ያ ሽማግሌ መቼም ለዘላለም መኖር አይችልም:"
“በዓለም ላይ ያለ ገንዘብ ሁሉ ቢደመር ያጣናቸውን የመኖሪያ ቀኖች ያህል
ዋጋ የለውም!” በቁጣ መለስኩለት ወደኔ ዞር አለ፤ ፊቱ ቀልቷል። “ምናልባት
አንቺ በተሰጥኦሽ ገንዘብ ታገኚ ይሆናል እኔ ግን ከፊት ለፊቴ የብዙ አመታት
ትምህርት ይጠብቀኛል፡ አባታችን ዶክተር እንድሆን ይጠብቅ እንደነበረ ታውቂያለሽ፡ እንደምንም ብዬ ያንን ማሳካት አለብኝ፡፡ ከዚህ ከኮበለልን ግን
መቼም ዶክተር መሆን አልችልም: አንቺንና መንትዮቹን እንዲሁም ራሴን
ማኖር ይኖርብኛል። እስቲ እኛን ለማኖር ልሰራ የምችላቸውን ስራዎች
ንገሪኝ… ፍጠኚ! ሳህን አጣቢ ወይም ፍራፍሬ ለቃሚ ሌላ ምን መሆን
እችላለሁ? እነዚህ ስራዎችስ የህክምና ትምህርት ቤት ያስገቡኛል?”
የነደደ ቁጣ ሞላኝ፡ እኔ ላደርገው ስለምችለው አስተዋፅኦ ትንሽ እንኳን
ዋጋ አልሰጠውም: “እኔም መስራት እችላለሁ!” አልኩት። “ሁለታችን
ሆነን ማስተዳደር እንችላለን፡ ክሪስ የተራብን ጊዜ አራት የሞቱ አይጦች
ስታመጣልኝ፣ እግዚአብሔር በትልቅ መከራ ጊዜ ለሰዎች ተጨማሪ ጥንካሬና
ችሎታ ይሰጣል ብለኸኝ ነበር፡ እኔም እንደሚሰጥ አምናለሁ: ከዚህ ወጥተን በራሳችን መኖር ስንጀምር በአንድም በሌላም በኩል መንገዳችንን እናስተካክላለን፡ እናም ዶክተር ትሆናለህ! ያንን ዶክተር የሚለውን ማዕረግ
ከስምህ በፊት ለማየት የትኛውንም ነገር አደርጋለሁ፡”
“ምን መስራት ትችያለሽ?" በጥላቻና በመመረር አይነት ጠየቀኝ፡ መልስ መስጠት ከመቻሌ በፊት ከጀርባችን ያለው በር ተhፍቶ አያትየው በሩ ላይ ቆመችና ወደ ክፍሉ ሳትገባ ክሪስ ላይ አፈጠጠች: እሱ ደግሞ እንደበፊቱ ለመታዘዝ ፈቃደኛ ባለመሆን ግትርና እምቢተኛ ሆነና ከመስኮቱ ጋር ሳይንቀሳቀስ ፊቱን መልሶ እንደገና ዝናቡ ላይ ማፍጠጥ ቀጠለ።
“ልጅ!” ተጣራች። “ከመስኮቱ ጋር ዞር በል አሁኑኑ!
“ስሜ ልጅ አይደለም፧ ስሜ ክሪስቶፈር ነው በተሰጠኝ ስም ልትጠሪኝ ትችያለሽ ወይም ጭራሽ አለመጥራት ትችያለሽ ... ግን እንደገና ልጅ ብለሽ እንዳትጠሪኝ፡”
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ሰባት
፡
፡
#ትርጉም_ሀኒም_ኤልያስ
አንድ ዝናባማ ከሰዓት
ሰማዩ ከብዶ ዝናቡ በጣም እየወረደ ነው: ክፍላችን ውስጥ ያሉ መብራቶች
ሁሉ በርተዋል፡ ቲቪውም እንደተለመደው ተከፍቷል። ክሪስ የመስኮቱን ከባባድ መጋረጃዎች በሁለት እጆቹ ከፈት አድርጎ ይዞ በመቆም ከሩቅ ትንሽ የአሻንጉሊት ባቡር መስሎ ሁልጊዜ አስር ሠዓት ገደማ አሳዛኝ ፊሽካውን እያሰማ የሚያልፈውን ባቡር ለማየት እየጠበቀ ነው:
በራሱ ዓለም ውስጥ ነው፧ እኔም በራሴ አለም ውስጥ እግሮቼን አጣምሬ እኔና
ኬሪ የምንጋራው አልጋ ላይ በመቀመጥ እናታችን ለመጨረሻ የመጣች ጊዜ
ካመጣችው መፅሄት ላይ ምስሎች እየመረጥኩ በውስጡ ያሉትን ፎቶግራፎች በጥንቃቄ እየቆረጥኩ የማልመውን አይነት በደስታ የምኖርበት ቤት፣ ሺ ሴቶችን በጎኑ የሚደርግ ሳይሆን እኔን ብቻ የሚወደኝ የምምኘውን አይነት ረጅም፣ ጠንካራ፣ ጥቁር ፀጉር ያለው ባል በማድረግ የቆራረጥኳቸውን የምስል ቁራጮች ሌላ መፅሀፍ ላይ እየለጠፍኩ ህይወቴን እየሳልኩ ነው።
ዳንሰኛ መሆን ሳቆም ባልና ልጆች ይኖሩኛል የማልመው አይነት ቤት ሲኖረኝ ደግሞ ከውድ ድንጋይ የተሰራ የመታጠቢያ ገንዳ ይኖረኛል ከዚያ ለውበት የሚሆኑ ዘይቶች አደርግበትና ማንም በሩን እያንኳኳ ፈጠን በይ
ሳይለኝ ከፈለግኩ ቀኑን ሙሉ ተዘፍዝፌ እውላለሁ። ከዚያ ቆዳዬ በጣም
ለስላሳና ምንም እንከን የሌለበት ጥርት ያለ ይሆንና ደስ የሚል ሽታ ያለው
የሽቶ ጠረን ይኖረኛል። ይሄ የበሰበሰ አሮጌ ደረቅ እንጨት ሽታና ጣሪያው
ስር ያለው ክፍል አቧራ ከነችግሮቹና አሮጌ እቃዎቹ ጋር እኛን ወጣቶቹን ልክ እንደዚህ አሮጌ ቤት ያለ ጠረን እንዲኖረን አድርጎናል
ክሪስ” አልኩት ጀርባው ላይ እያፈጠጥኩ። “አሁን ጠንካሮች ነን፤ ታዲያ
ለምንድነው እናታችን ተመልሳ እስክትመጣና ሽማግሌው እስኪሞት መጠበቅ ያለብን? ለምንድነው የማምለጫ መንገድ የማንፈልገው?” ቃል አልተነፈሰም። ግን እጆቹ የመጋረጃውን ጨርቅ ጨምድደው ሲይዙ ተመለከትኩ::
“ክሪስ...”
“ስለሱ ማውራት አልፈልግም” አለ በንዴት
“ስለመሄድ እያሰብክ ካልሆነ ታዲያ ለምንድነው እዚያ ቆመህ ባቡሩ እስኪያልፍ የምትጠብቀው?”
“ባቡሩን እየጠበቅኩ አይደለም! በቃ ዝም ብዬ ወደ ውጪ እየተመለከትኩ
ነው:”
በግንባሩ የመስኮቱን መስታወት ተደግፏል። ቅርብ ያለ ጎረቤት እንዲያየው የደፈረ ይመስላል
“ክሪስ ከመስኮቱ ዞር በል የሆነ ሰው ሊያይህ ይችላል”
“ማንም ቢያየኝ ግድ የለኝም!”
የመጀመሪያ ስሜቴ ወደሱ ሮጬ በክንዶቼ አቅፌ ከእናታችን ያጣቸውን
እነዚያን መሳሞች ለማካስ ፊቱን በሙሉ በሚሊየን በሚቆጠሩ መሳሞች
ማዳረስ ነበር እሷ እንደምታደርገው ጭንቅላቱን ደረቴ ላይ አስደግፌ ፀጉሩን እያሻሸሁ በፊት ወደነበረበት አይነት ደስተኛ፣ የሚናደድበት ቀን የሌለው፣ መልካም ነገር ብቻ የሚመለከት ሰው ወደመሆኑ ልመልሰው ፈለግኩ። ነገር ግን በፊት እናታችን ታደርግለት የነበረውን ነገር ሁሉ ባደርግለትም ተመሳሳይ
እንደማይሆን አውቅ ነበር፡ እሷን ነው የሚፈልገው: ተስፋዎቹ፣ ህልሞቹና
እምነቱ በሙሉ በአንዲት ሴት ውስጥ ታሽጓል በእናታችን፡፡
አሁን ከመጣች ሁለት ወር አልፏታል! እዚህ ቤት የምናሳልፈው አንድ ቀን በትክክለኛው ህይወት ሲለካ ከወር በላይ እንደሚረዝም አልገባትም
ስለኛ አትጨነቅም? እንዴት እንደምንኖር አታስብም? ያለምንም ማብራሪያ፣
ምክንያት ወይም ሰበብ ስትተወን እያየ ክሪስ ሁልጊዜ የሷ ቀንደኛ ደጋፊ
እንደሚሆን ታምናለች? ፍቅር በጥርጣሬና በፍርሀት በአንድ ጊዜ ሊፈርስ
እንደሚችልና በፍፁም ዳግመኛ ሊገነባ እንደማይችል አታውቅም?
"ካቲ” አለ ክሪስ ድንገት “የሆነ ቦታ የመሄድ ምርጫ ቢኖርሽ የት ትሄጃለሽ?
“ደቡብ” አልኩ “የሚሞቅና ፀሀያማ የባህር ዳርቻ ወዳለው… ሞገዶች ለስላሳ
ወደሆኑበትና ሀይለኛ ነፋስ ወደማይነፍስበት መሄድ እፈልጋለሁ በነጭ አሸዋ ላይ ጋደም ብዬ የፀሀይ ብርሃኔን እየጠጣሁ ለስለስ ያለ ንፋስ ፀጉሬ ውስጥና ጉንጮቼ ላይ ሲንሸራሸር መስማት ነው የምፈልገው”
“ልክ ነው…” ተስማማ፡ “የገለፅሽበት መንገድ አሪፍ ይመስላል እኔ ግን ልክ
እንደ በረዶ ሸርተቴ ሁሉ በሀይለኛ ሞገድ ውስጥ መንሳፈፍም እወዳለሁ።”
ምስሎቹን እየቆራረጥኩ የነበርኩበትን መቀስና መፅሄቱን አስቀምጬ ሙሉ
በሙሉ ክሪስ ላይ ትኩረት አደረግኩ፡ ክሪስ የሚወዳቸውን ብዙ ስፖርቶች አጥቶ፣ በአንድ ክፍል ውስጥ ታሽጎ፣ ከእድሜው በላይ አርጅቶና አዝኖ ስመለከተው ላፅናናው ብፈልግም እንዴት እንደማፅናናው ግን አላወቅኩም።
ክሪስ እባክህ ከመስኮቱ ጋ ተመለስ?” አልኩት።
“ተይኝ! ይሄ ቦታ እጅግ ሰልችቶኛል ይህንን አታድርግ፣ ያንን አታድርግ፣
ካላናገሩህ እንዳትናገር መባል፤ በየቀኑ እነዚህን በደንብ በደንብ የማይሰሩ ጣዕም አልባ ምግቦች መብላት ታክቶኛል
በምግብም እንኳን እንዳንደሰት ሆነ ብላ ነው እንደዛ የምታደርገው: ስለዛ
ሁሉ ገንዘብ ሳስብ ደግሞ ግማሹ የእናታችንና የእኛ በመሆኑ እንደሚገባን
አስባለሁ። ያ ሽማግሌ መቼም ለዘላለም መኖር አይችልም:"
“በዓለም ላይ ያለ ገንዘብ ሁሉ ቢደመር ያጣናቸውን የመኖሪያ ቀኖች ያህል
ዋጋ የለውም!” በቁጣ መለስኩለት ወደኔ ዞር አለ፤ ፊቱ ቀልቷል። “ምናልባት
አንቺ በተሰጥኦሽ ገንዘብ ታገኚ ይሆናል እኔ ግን ከፊት ለፊቴ የብዙ አመታት
ትምህርት ይጠብቀኛል፡ አባታችን ዶክተር እንድሆን ይጠብቅ እንደነበረ ታውቂያለሽ፡ እንደምንም ብዬ ያንን ማሳካት አለብኝ፡፡ ከዚህ ከኮበለልን ግን
መቼም ዶክተር መሆን አልችልም: አንቺንና መንትዮቹን እንዲሁም ራሴን
ማኖር ይኖርብኛል። እስቲ እኛን ለማኖር ልሰራ የምችላቸውን ስራዎች
ንገሪኝ… ፍጠኚ! ሳህን አጣቢ ወይም ፍራፍሬ ለቃሚ ሌላ ምን መሆን
እችላለሁ? እነዚህ ስራዎችስ የህክምና ትምህርት ቤት ያስገቡኛል?”
የነደደ ቁጣ ሞላኝ፡ እኔ ላደርገው ስለምችለው አስተዋፅኦ ትንሽ እንኳን
ዋጋ አልሰጠውም: “እኔም መስራት እችላለሁ!” አልኩት። “ሁለታችን
ሆነን ማስተዳደር እንችላለን፡ ክሪስ የተራብን ጊዜ አራት የሞቱ አይጦች
ስታመጣልኝ፣ እግዚአብሔር በትልቅ መከራ ጊዜ ለሰዎች ተጨማሪ ጥንካሬና
ችሎታ ይሰጣል ብለኸኝ ነበር፡ እኔም እንደሚሰጥ አምናለሁ: ከዚህ ወጥተን በራሳችን መኖር ስንጀምር በአንድም በሌላም በኩል መንገዳችንን እናስተካክላለን፡ እናም ዶክተር ትሆናለህ! ያንን ዶክተር የሚለውን ማዕረግ
ከስምህ በፊት ለማየት የትኛውንም ነገር አደርጋለሁ፡”
“ምን መስራት ትችያለሽ?" በጥላቻና በመመረር አይነት ጠየቀኝ፡ መልስ መስጠት ከመቻሌ በፊት ከጀርባችን ያለው በር ተhፍቶ አያትየው በሩ ላይ ቆመችና ወደ ክፍሉ ሳትገባ ክሪስ ላይ አፈጠጠች: እሱ ደግሞ እንደበፊቱ ለመታዘዝ ፈቃደኛ ባለመሆን ግትርና እምቢተኛ ሆነና ከመስኮቱ ጋር ሳይንቀሳቀስ ፊቱን መልሶ እንደገና ዝናቡ ላይ ማፍጠጥ ቀጠለ።
“ልጅ!” ተጣራች። “ከመስኮቱ ጋር ዞር በል አሁኑኑ!
“ስሜ ልጅ አይደለም፧ ስሜ ክሪስቶፈር ነው በተሰጠኝ ስም ልትጠሪኝ ትችያለሽ ወይም ጭራሽ አለመጥራት ትችያለሽ ... ግን እንደገና ልጅ ብለሽ እንዳትጠሪኝ፡”
👍38😁2
#የጣሪያ_ስር_አበቦች
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ስምንት
፡
፡
#ትርጉም_ሀኒም_ኤልያስ
በመጨሻ እኖታችን
እኔና ክሪስ በግርፋቱ ቀን በመሀከላችን ስለተፈጠረው ነገር በፍፁም አላወራንም
በአብዛኛው አተኩሮ ሲመለከተኝ እይዘዋለሁ፧ ግን አይኖቼ አይኖቹን ሲመለከቱ አይኖቹን ያሸሻል እኔም ሳየው ከያዘኝ አይኖቼን ወዲያው እመልሳለሁ።
እኔም እሱም በየቀ እያደግን ነው፡ ጡቶቼ ሙሉ ሆነዋል። ዳሌዬ ሰፋ ብሎ ወገቤ ቀጠን ብሏል ግንባሬ አካባቢ የተቆረጠው ፀጉሬ አድጎ ደስ በሚል አይነት ተጠቅልሏል። ክሪስ ደግሞ ትከሻው ሰፍቷል። ደረቱና ክንዶቹ የበለጠ ወንዳወንድ ሆነዋል አንድ ጊዜ ጣሪያው ስር ያለው ክፍል ውስጥ
ሆኖ የተገረመ በሚመስል አይነት ወንድነቱን ወደታች ሲመለከትና ሲለካው
ይዤዋለሁ። ርዝመቱ ምን ጥቅም እንዳለው ለማወቅ ስለጓጓሁ “ለምን?” ብዬ
ስጠይቀው አንድ ጊዜ አባታችንን እርቃኑን ሆኖ እንዳየውና አሁን ያየው
ነገር መጠኑ በቂ እንደማይመስል ነገረኝና ፊቱን አዞረ። ልክ እኔ እናታችን የምትለብሰው የጡት መያዣ መጠን ስንት እንደሆነ ማወቅ እንደምፈልገው ማለት ነበር። “እንደገና እንደዚያ እንዳታደርግ።" አልኩት። ኮሪ ያለው የወንድ አካል ትንሽ ስለሆነ ክሪስን ተመልክቶ ልክ እንደ ክሪስ መጠኑ ትንሽ ነው
የሚል ስሜት ቢሰማውስ?
ድንገት የመማሪያ ክፍሉን ወንበሮች ማፅዳቴን አቁሜ ወደ ኬሪና ኮሪ ተመለከትኩ፡ አምላኬ! በጣም መቀራረብ እንዴት እይታን እንደሚያደበዝዝ!
ሁለት አመት ከአራት ወር የተቆለፈብን ቢሆንም መንትዮቹ እዚህ የመጣን
ጊዜ ከነበሩት አልተለወጡም ጭንቅላታቸው ተለቅ ብሎ ስለሚታይ የአይኖቻቸው መጠን ያነሰ ይመስላል፡ ሰውነታቸው ጭንቅላታቸውን መሸከም
የሚችል አይመስልም ፍዝዝ ብለው ወደ መስኮቱ ያስጠጋነው አሮጌ ፍራሽ
ላይ ተቀምጠዋል እስኪተኙ ጠበቅኩና ቀስ ብዬ ለክሪስ “ተመልከታቸው ምንም አላደጉም: ጭንቅላታቸው ብቻ ነው ትልቅ የሆነው:” አልኩት።
በከባዱ ተነፈሰ፤ ከዚያ አይኖቹን አጥብቦ ወደ መንትዮቹ ቀረበና የገረጣውን ቆዳቸውን ለመንካት ዝቅ አለ፡ “ውጪ ጣሪያው ላይ ከእኛ ጋር ወጥተው ፀሀይና ንፁህ አየር ቢነካቸው ጥሩ ይሆን ነበር ካቲ፤ ምንም ያህል ቢጮሁና ቢንፈራገጡ ወደ ውጪ እንዲወጡ ማስገደድ አለብን” አለኝ።
እንቅልፍ ላይ እንዳሉ ተሸክመን ወደ ጣሪያው ብንወስዳቸውና ፀሀይ ላይ ሆነው እኛ እንዳቀፍናቸው ቢነቁ ደህንነት ይሰማቸዋል ብለን አሰብንና ክሪ ኮሪን በጥንቃቄ ሲያነሳ፣ እኔም ኬሪን ብድግ አደረግኳት ወደ ተከፈተው የጣሪያው ስር ክፍል መስኮት ቀረብን፡ የጣሪያውን የኋላ ክፍል መጠቀም የተሻለ ነው: ቀኑ ሀሙስ ስለሆነና ሰራተኞቹ ቀኑን ሙሉ ከተማ ስለሚውሉ ጣሪያው ላይ ወጥተን የምንዝናናበት ብቸኛው ቀን ነው።
ክሪስ ቀስ ብሎ ኮሪን እንደያዘ መስኮቱን አልፎ ሲወጣ የበጋ ፀሀይ ኮሪን
ከእንቅልፉ አነቃው ዙሪያውን ሲመለከት እኔም ኬሪን ተሸክሜ ጣሪያው ላይ
ልወጣ መሆኑን ሲመለከት ጮኸ! ኬሪ ከእንቅልፏ ባነነች። ክሪስ ኮሪን ይዞ
ጣሪያው ጫፍ ላይ ሆኖ እኔ ደግሞ የት እየወሰድኳት እንደሆነ ስትመለከት
ጩኸቷን አቀለጠችው።
ክሪስ ጣሪያው ጫፍ ላይ እንዳለ “አምጫት! ለራሳቸው ነው ይህንን ማድረግ አለብን:” አለኝ፡ መጮህ ብቻ አይደለም እየተራገጡና እየመቱን ነበር።ኬሪ ክንዴ ላይ ስትነክሰኝ እኔም ጮህኩ። በጣም ትንንሾች ቢሆኑም አደጋ ላይ እንደሆኑ በማሰባቸው በጣም በጥንካሬ እየታገሉን ነበር። ፊቴን አዙሬ ወደ መማሪያ ክፍሉ መስኮት አቀናሁና እየተንቀጠቀጥኩ ኬሪን በእግሮቿ አቆምኳት እኔም አየር አጥሮኝ እያለከለክኩ ወንበሩን ተደግፌ በሰላም ወደ ውስጥ እንድመልሳት ስላደረገኝ እግዚአብሔርን አመሰገንኩ። ክሪስም ኮሪን
እህቱ አጠገብ መለሰው፡ ሙከራችን ጥቅም አልነበረውም እነሱን ጣሪያው ላይ እንዲወጡ ማስገደድ የአራታችንንም ህይወት አደጋ ላይ መጣል ነው።
በጣም ስለተናደዱብን በመጀመሪያ ቀን ወደዚህ ክፍል ስንመጣ ቁመታቸውን
ወደ ለካንበት ግድግዳ ምልክት ስንወስዳቸው ሁሉ እየታገሉን ነበር ክሪስ
ሁለቱንም ቦታው ላይ አድርጎ ሲይዝልኝ እኔ ምን ያህል እንዳደጉ ለማንበብ
ሞከርኩ፡
ሊሆን መቻሉን ባለማመን በድንጋጤ አፈጠጥኩ: በዚህ ሁሉ ጊዜ የጨመሩት
ሁለት ኢንች ብቻ ነው? ሁለት ኢንች! እኔና ክሪስ ከአምስት እስከ ሰባት
አመት እድሜያችን መሀከል ብዙ በጣም ብዙ ነበር ያደግነው ሲወለዱም
ክብደታቸው ትንሽ የነበረ ቢሆንም የተሻለ ማደግ ነበረባቸው።
የደነገጠና የፈራ ገፅታዬን ማየት እንዳይችሉ በእጆቼ ፊቴን መሸፈን ነበረብኝ፡፡
ከዚያ ሳግ ጉሮሮዬን ሲይዘኝ ጀርባዬን ሰጥቻቸው ፊቴን አዞርኩ።
“አሁን እንዲሄዱ መልቀቅ ትችላለህ” አልኩት ዞር ብዬ ሳያቸው ልክ እንደ ሁለት አይጦች በደረጃው እየተንደረደሩ ወደ ተወዳጁ ቴሌቪዥን ሮጡ።
ክሪስ hጀርባዬ ቆሞ እየጠበቀ ነው: “ምን ያህል ቁመት ጨምረዋል?” አለኝ:
ፈጠን ብዬ እምባዬን በእጄ ጠራርጌ ወደ እሱ ዞርኩ ከዚያ አይኖቹን እየተመለከትኩ ሁለት ኢንች እንደሆነ ነገርኩት᎓ አይኖቼ ውስጥ ህመም ነበር።
እሱም ያየው ያንን ነበር:
ጠደ እኔ ተጠግቶ አቀፈኝና ጭንቅላቴን ወደ ደረቱ አስጠጋኝ፡ አለቀስኩ በጣም
አለቀስኩ ይህንን በማድረጓ እናታችንን ጠላኋት የእውነት ጠላኋት! ልጆች እንደ አትክልት እንደሆኑና ለማደግ የፀሀይ ብርሃን እንደሚያስፈልጋቸው
ታውቃለች በወንድሜ እቅፍ ውስጥ እንዳለሁ ተንቀጠቀጥኩ። ነፃ ስንሆን
እንደገና ቆንጆ እንደሚሆኑ ራሴን ለማሳመን እየሞከርኩ ነበር። ቆንጆ ይሆናሉ፤ ያጡትን አመታት ያካክሳሉ፡ ልክ የፀሀይ ብርሃን ማግኘት ሲጀምሩ እንደ አትክልት ያድጋሉ። አዎ ያድጋሉ፤ ጎንጮቻቸው በጣም የጎደጎዱት፣አይኖቻቸው ወደ ውስጥ የገቡት ረጅም ጊዜ ቤት ውስጥ ስለሚቀመጡ ነው እና ያ ሁሉ ሊስተካከል ይችላል፤ አይችልም?
ከዚያ በሻካራ ድምፅ “ገንዘብ ነው አለምን የሚያሽከረክራት ወይስ ፍቅር? ለመንትዮቹ በቂ ፍቅር ሰጥተናቸዋል እናም ስድስት፣ ሰባት፣ ምናልባትም ስምንት ኢንች ቁመት መጨመር ነበረባቸው: ሁለት ብቻ አልነበረም" አልኩ፡
እኔና ክሪስ ወደዛ ወደ ደብዛዛው እስር ቤታችን ተመለስንና እንደ ሁልጊዜው
እጆቻቸውን እንዲታጠቡ ላክናቸው የምግብ ጠረጴዛችን ጋ በፀጥታ ተቀምጠን ሳንድዊቻችንን እየበላንና ወተት እየጠጣን ቲቪ ስንመለከት የክፍላችን በር ተከፈተ: መዞር አልፈለኩም ነበር። ግን ዞርኩ:
እናታችን እየሳቀች ወደ ክፍሉ ገባች የሚያምር ልብስ ለብሳለች የለበሰችው
ጃኬት አንገቱና እጆቹ ላይ ፀጉር አለው: “ውዶቼ!” አለች በመጓጓት አይነት
ሰላምታ: ከዚያ አንዳችንም ሰላም ልንላት ባለመነሳታችን እያመነታችና እርግጠኛ ባልሆነ ስሜት “መጥቻለሁ! ስታዩኝ ደስ አላላችሁም? ስላየኋችሁ እንዴት ደስ እንዳለኝ አታውቁም በጣም ስናፍቃችሁ፣ ስለናንተ ሳስብና ሳልም ነበር፡ እና በጣም በጥንቃቄ የመረጥኳቸው የሚያምሩ ስጦታዎች አምጥቼላችኋለሁ: እስክታዩዋቸው ጠብቁ፡፡ ረጅም ጊዜ የጠፋሁበትን ማካካስ እፈልጋለሁ፡ ለምን እንደምሄድ ልነግራችሁ ፈልጌ ነበር፣ እውነቴን ነው፣
ግን በጣም የተወሳሰበ ነው: ለምን ያህል ጊዜ እንደምቆይ አላወቅኩም
ነበር። ናፍቃችሁኛል! በደንብ ተይዛችኋል አይደል? አልተሰቃያችሁም
ተሰቃይታችኋል እንዴ?”
ተሰቃይታችኋል? ናፍቃችሁኛል? እሷ ማናት? አፍጥጬ እያየኋትና አራት
የተደበቁ ልጆች የሌሎችን ህይወት እንዴት አስቸጋሪ እንደሚያደርጉ እየሰማሁ
መጥፎ ሀሳቦች መጡብኝ፡ ሁለተኛ በጭራሽ እንዳትጠጋኝ ላደርጋት ፈለግኩ።ከዚያ አቅማማሁ በተስፋ ተሞልቼ እንደገና ልወዳትና ላምናትም ፈለግኩ
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ስምንት
፡
፡
#ትርጉም_ሀኒም_ኤልያስ
በመጨሻ እኖታችን
እኔና ክሪስ በግርፋቱ ቀን በመሀከላችን ስለተፈጠረው ነገር በፍፁም አላወራንም
በአብዛኛው አተኩሮ ሲመለከተኝ እይዘዋለሁ፧ ግን አይኖቼ አይኖቹን ሲመለከቱ አይኖቹን ያሸሻል እኔም ሳየው ከያዘኝ አይኖቼን ወዲያው እመልሳለሁ።
እኔም እሱም በየቀ እያደግን ነው፡ ጡቶቼ ሙሉ ሆነዋል። ዳሌዬ ሰፋ ብሎ ወገቤ ቀጠን ብሏል ግንባሬ አካባቢ የተቆረጠው ፀጉሬ አድጎ ደስ በሚል አይነት ተጠቅልሏል። ክሪስ ደግሞ ትከሻው ሰፍቷል። ደረቱና ክንዶቹ የበለጠ ወንዳወንድ ሆነዋል አንድ ጊዜ ጣሪያው ስር ያለው ክፍል ውስጥ
ሆኖ የተገረመ በሚመስል አይነት ወንድነቱን ወደታች ሲመለከትና ሲለካው
ይዤዋለሁ። ርዝመቱ ምን ጥቅም እንዳለው ለማወቅ ስለጓጓሁ “ለምን?” ብዬ
ስጠይቀው አንድ ጊዜ አባታችንን እርቃኑን ሆኖ እንዳየውና አሁን ያየው
ነገር መጠኑ በቂ እንደማይመስል ነገረኝና ፊቱን አዞረ። ልክ እኔ እናታችን የምትለብሰው የጡት መያዣ መጠን ስንት እንደሆነ ማወቅ እንደምፈልገው ማለት ነበር። “እንደገና እንደዚያ እንዳታደርግ።" አልኩት። ኮሪ ያለው የወንድ አካል ትንሽ ስለሆነ ክሪስን ተመልክቶ ልክ እንደ ክሪስ መጠኑ ትንሽ ነው
የሚል ስሜት ቢሰማውስ?
ድንገት የመማሪያ ክፍሉን ወንበሮች ማፅዳቴን አቁሜ ወደ ኬሪና ኮሪ ተመለከትኩ፡ አምላኬ! በጣም መቀራረብ እንዴት እይታን እንደሚያደበዝዝ!
ሁለት አመት ከአራት ወር የተቆለፈብን ቢሆንም መንትዮቹ እዚህ የመጣን
ጊዜ ከነበሩት አልተለወጡም ጭንቅላታቸው ተለቅ ብሎ ስለሚታይ የአይኖቻቸው መጠን ያነሰ ይመስላል፡ ሰውነታቸው ጭንቅላታቸውን መሸከም
የሚችል አይመስልም ፍዝዝ ብለው ወደ መስኮቱ ያስጠጋነው አሮጌ ፍራሽ
ላይ ተቀምጠዋል እስኪተኙ ጠበቅኩና ቀስ ብዬ ለክሪስ “ተመልከታቸው ምንም አላደጉም: ጭንቅላታቸው ብቻ ነው ትልቅ የሆነው:” አልኩት።
በከባዱ ተነፈሰ፤ ከዚያ አይኖቹን አጥብቦ ወደ መንትዮቹ ቀረበና የገረጣውን ቆዳቸውን ለመንካት ዝቅ አለ፡ “ውጪ ጣሪያው ላይ ከእኛ ጋር ወጥተው ፀሀይና ንፁህ አየር ቢነካቸው ጥሩ ይሆን ነበር ካቲ፤ ምንም ያህል ቢጮሁና ቢንፈራገጡ ወደ ውጪ እንዲወጡ ማስገደድ አለብን” አለኝ።
እንቅልፍ ላይ እንዳሉ ተሸክመን ወደ ጣሪያው ብንወስዳቸውና ፀሀይ ላይ ሆነው እኛ እንዳቀፍናቸው ቢነቁ ደህንነት ይሰማቸዋል ብለን አሰብንና ክሪ ኮሪን በጥንቃቄ ሲያነሳ፣ እኔም ኬሪን ብድግ አደረግኳት ወደ ተከፈተው የጣሪያው ስር ክፍል መስኮት ቀረብን፡ የጣሪያውን የኋላ ክፍል መጠቀም የተሻለ ነው: ቀኑ ሀሙስ ስለሆነና ሰራተኞቹ ቀኑን ሙሉ ከተማ ስለሚውሉ ጣሪያው ላይ ወጥተን የምንዝናናበት ብቸኛው ቀን ነው።
ክሪስ ቀስ ብሎ ኮሪን እንደያዘ መስኮቱን አልፎ ሲወጣ የበጋ ፀሀይ ኮሪን
ከእንቅልፉ አነቃው ዙሪያውን ሲመለከት እኔም ኬሪን ተሸክሜ ጣሪያው ላይ
ልወጣ መሆኑን ሲመለከት ጮኸ! ኬሪ ከእንቅልፏ ባነነች። ክሪስ ኮሪን ይዞ
ጣሪያው ጫፍ ላይ ሆኖ እኔ ደግሞ የት እየወሰድኳት እንደሆነ ስትመለከት
ጩኸቷን አቀለጠችው።
ክሪስ ጣሪያው ጫፍ ላይ እንዳለ “አምጫት! ለራሳቸው ነው ይህንን ማድረግ አለብን:” አለኝ፡ መጮህ ብቻ አይደለም እየተራገጡና እየመቱን ነበር።ኬሪ ክንዴ ላይ ስትነክሰኝ እኔም ጮህኩ። በጣም ትንንሾች ቢሆኑም አደጋ ላይ እንደሆኑ በማሰባቸው በጣም በጥንካሬ እየታገሉን ነበር። ፊቴን አዙሬ ወደ መማሪያ ክፍሉ መስኮት አቀናሁና እየተንቀጠቀጥኩ ኬሪን በእግሮቿ አቆምኳት እኔም አየር አጥሮኝ እያለከለክኩ ወንበሩን ተደግፌ በሰላም ወደ ውስጥ እንድመልሳት ስላደረገኝ እግዚአብሔርን አመሰገንኩ። ክሪስም ኮሪን
እህቱ አጠገብ መለሰው፡ ሙከራችን ጥቅም አልነበረውም እነሱን ጣሪያው ላይ እንዲወጡ ማስገደድ የአራታችንንም ህይወት አደጋ ላይ መጣል ነው።
በጣም ስለተናደዱብን በመጀመሪያ ቀን ወደዚህ ክፍል ስንመጣ ቁመታቸውን
ወደ ለካንበት ግድግዳ ምልክት ስንወስዳቸው ሁሉ እየታገሉን ነበር ክሪስ
ሁለቱንም ቦታው ላይ አድርጎ ሲይዝልኝ እኔ ምን ያህል እንዳደጉ ለማንበብ
ሞከርኩ፡
ሊሆን መቻሉን ባለማመን በድንጋጤ አፈጠጥኩ: በዚህ ሁሉ ጊዜ የጨመሩት
ሁለት ኢንች ብቻ ነው? ሁለት ኢንች! እኔና ክሪስ ከአምስት እስከ ሰባት
አመት እድሜያችን መሀከል ብዙ በጣም ብዙ ነበር ያደግነው ሲወለዱም
ክብደታቸው ትንሽ የነበረ ቢሆንም የተሻለ ማደግ ነበረባቸው።
የደነገጠና የፈራ ገፅታዬን ማየት እንዳይችሉ በእጆቼ ፊቴን መሸፈን ነበረብኝ፡፡
ከዚያ ሳግ ጉሮሮዬን ሲይዘኝ ጀርባዬን ሰጥቻቸው ፊቴን አዞርኩ።
“አሁን እንዲሄዱ መልቀቅ ትችላለህ” አልኩት ዞር ብዬ ሳያቸው ልክ እንደ ሁለት አይጦች በደረጃው እየተንደረደሩ ወደ ተወዳጁ ቴሌቪዥን ሮጡ።
ክሪስ hጀርባዬ ቆሞ እየጠበቀ ነው: “ምን ያህል ቁመት ጨምረዋል?” አለኝ:
ፈጠን ብዬ እምባዬን በእጄ ጠራርጌ ወደ እሱ ዞርኩ ከዚያ አይኖቹን እየተመለከትኩ ሁለት ኢንች እንደሆነ ነገርኩት᎓ አይኖቼ ውስጥ ህመም ነበር።
እሱም ያየው ያንን ነበር:
ጠደ እኔ ተጠግቶ አቀፈኝና ጭንቅላቴን ወደ ደረቱ አስጠጋኝ፡ አለቀስኩ በጣም
አለቀስኩ ይህንን በማድረጓ እናታችንን ጠላኋት የእውነት ጠላኋት! ልጆች እንደ አትክልት እንደሆኑና ለማደግ የፀሀይ ብርሃን እንደሚያስፈልጋቸው
ታውቃለች በወንድሜ እቅፍ ውስጥ እንዳለሁ ተንቀጠቀጥኩ። ነፃ ስንሆን
እንደገና ቆንጆ እንደሚሆኑ ራሴን ለማሳመን እየሞከርኩ ነበር። ቆንጆ ይሆናሉ፤ ያጡትን አመታት ያካክሳሉ፡ ልክ የፀሀይ ብርሃን ማግኘት ሲጀምሩ እንደ አትክልት ያድጋሉ። አዎ ያድጋሉ፤ ጎንጮቻቸው በጣም የጎደጎዱት፣አይኖቻቸው ወደ ውስጥ የገቡት ረጅም ጊዜ ቤት ውስጥ ስለሚቀመጡ ነው እና ያ ሁሉ ሊስተካከል ይችላል፤ አይችልም?
ከዚያ በሻካራ ድምፅ “ገንዘብ ነው አለምን የሚያሽከረክራት ወይስ ፍቅር? ለመንትዮቹ በቂ ፍቅር ሰጥተናቸዋል እናም ስድስት፣ ሰባት፣ ምናልባትም ስምንት ኢንች ቁመት መጨመር ነበረባቸው: ሁለት ብቻ አልነበረም" አልኩ፡
እኔና ክሪስ ወደዛ ወደ ደብዛዛው እስር ቤታችን ተመለስንና እንደ ሁልጊዜው
እጆቻቸውን እንዲታጠቡ ላክናቸው የምግብ ጠረጴዛችን ጋ በፀጥታ ተቀምጠን ሳንድዊቻችንን እየበላንና ወተት እየጠጣን ቲቪ ስንመለከት የክፍላችን በር ተከፈተ: መዞር አልፈለኩም ነበር። ግን ዞርኩ:
እናታችን እየሳቀች ወደ ክፍሉ ገባች የሚያምር ልብስ ለብሳለች የለበሰችው
ጃኬት አንገቱና እጆቹ ላይ ፀጉር አለው: “ውዶቼ!” አለች በመጓጓት አይነት
ሰላምታ: ከዚያ አንዳችንም ሰላም ልንላት ባለመነሳታችን እያመነታችና እርግጠኛ ባልሆነ ስሜት “መጥቻለሁ! ስታዩኝ ደስ አላላችሁም? ስላየኋችሁ እንዴት ደስ እንዳለኝ አታውቁም በጣም ስናፍቃችሁ፣ ስለናንተ ሳስብና ሳልም ነበር፡ እና በጣም በጥንቃቄ የመረጥኳቸው የሚያምሩ ስጦታዎች አምጥቼላችኋለሁ: እስክታዩዋቸው ጠብቁ፡፡ ረጅም ጊዜ የጠፋሁበትን ማካካስ እፈልጋለሁ፡ ለምን እንደምሄድ ልነግራችሁ ፈልጌ ነበር፣ እውነቴን ነው፣
ግን በጣም የተወሳሰበ ነው: ለምን ያህል ጊዜ እንደምቆይ አላወቅኩም
ነበር። ናፍቃችሁኛል! በደንብ ተይዛችኋል አይደል? አልተሰቃያችሁም
ተሰቃይታችኋል እንዴ?”
ተሰቃይታችኋል? ናፍቃችሁኛል? እሷ ማናት? አፍጥጬ እያየኋትና አራት
የተደበቁ ልጆች የሌሎችን ህይወት እንዴት አስቸጋሪ እንደሚያደርጉ እየሰማሁ
መጥፎ ሀሳቦች መጡብኝ፡ ሁለተኛ በጭራሽ እንዳትጠጋኝ ላደርጋት ፈለግኩ።ከዚያ አቅማማሁ በተስፋ ተሞልቼ እንደገና ልወዳትና ላምናትም ፈለግኩ
👍42👎2
#የጣሪያ_ስር_አበቦች
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ዘጠኝ
፡
፡
#ትርጉሜ_ሀኒም_ኤልያስ
...ልታገኝ ስለምትፈልገው ነገር ስትል ድራማ የምትሰራ አድርጌ የማስባት ለምንድነው? እኔን ችላ ብላ ክሪስን ተመለከተች።
ለሚቀጥለው ልደትህ ኢንሳይክሎፒድያ አዝዤልሀለው። ማተምያው ድረስ ራሴ ሄጄ ነው ያዘዝኩት ስምህንና ቀኑን ሰጥቺያቸዋለሁ ግን ወደዚህ በቀጥታ መላክ አይችሉም:: የሆነ ሰው ሊቀበላቸው ይገባል ልክ ሁልጊዜ ራስህን ለማስተማር ምርጡን ልሰጥህ እንደምፈልግ ሁሉ የሚያስደስትህን ስጦታ ሳስብ ሳስብ ቆይቼ ነው ያዘዝኩልህ”
ክሪስ የሚናገረውን አጣ ፊቱ ላይ የሚታየው ድብልቅልቅ ስሜት ነበር፤አይኖቹ ግራ የተጋቡና የፈዘዙ መሰሉ። አምላኬ! ካደረገችው ነገር በኋላ እንኳን ይወዳታል ማለት ነው::
ስሜቶቹ ቀጥታ ናቸው:: በቁጣ ነደድኩ እንደዚህ አይነት መፅሀፍት ከአንድ
ሺ ዶላር በላይ ይፈጃል: ምናልባትም ሁለት ወይም ሶስት ሺም ሊፈጅ ይችላል። ይህንን ገንዘብ ለምን የማምለጫ ገንዘባችን ውስጥ አትጨምረውም?
ልክ ኬሪ ስትቃወም እንደምታደርገው ልጮህ ስል ክሪስ አይኖች ላይ ያየሁት ነገር አፌን እንድዘጋ አደረገኝ፡ ሁልጊዜ እነዚያ መፃህፍት እንዲኖሩት ይፈልግ ነበር፡ በዚያ ላይ አንድ ጊዜ ታዟል: አሁን ለሷ ገንዘብ ምኗም አይደለም፧
ምናልባት እንዲያው ምናልባት አያታችን ዛሬ ወይም ነገ ሊሞት ስለሚችል አፓርታማ መከራየትም ሆነ ቤት መግዛት አያስፈልጋት ይሆናል፡
ጥርጣሬዬ ተሰምቷታል።
እናታችን ጭንቅላቷን ቀና አደረገችና ወደ በሩ ተራመደች። ስጦታዎቻችንን
ገና አልከፈትንም፤ ስንከፍት የሚኖረንን ስሜት ለመመልከትም አልቆየችም።
እየጠላኋት ለምንድነው በውስጤ የማለቅሰው? አሁን አልወዳትም አልወዳትም።
በሩጋ ደርሳ እየከፈተች “ዛሬ ስለፈጠራችሁብኝ ህመም ስታስቡና እንደገና
በፍቅርና በአክብሮት ልታስተናግዱኝ ስትችሉ ተመልሼ እመጣለሁ ከዚያ
በፊት ግን አይሆንም::” አለች።
መጣች።
ሄደች።
መጥታ ስትመለስ
ኬሪና ኮሪን አልነካቻቸውም አልሳመቻቸውም አላናገረቻቸውም ለምን እንደሆነ አውቄያለሁ፤ ሀብት ማግኘት መንትዮቹን ምን ያህል ዋጋ እንዳስከፈላቸው ማየት መቋቋም ባለመቻሏ ነበር።
ከጠረጴዛው አጠገብ ተነስተው እየሮጡ ወደ እኔ መጡና ቀሚሴን እየጎተቱ
ፊቴ ላይ አፈጠጡ ትንንሽ ፊቶቻቸው ጭንቀትና ፍርሀት አጥልቶባቸዋል።
እነሱም ደስታ እንዲሰማቸው መደሰቴን ለማየት ፊቴን እያጠኑ ነው:
ተንበርክኬ እሷ የጎዳቻቸውን በመሳምና በማቀፍ አጥለቀለቅኳቸው።
መልካችን ያስጠላል?" ጠየቀች ኬሪ በመጨነቅ፤ ትንንሽ እጆቿ እጄን
ይዘውኛል
“አይ በጭራሽ! አንቺና ኮሪ ቤት ውስጥ ብዙ በመቆየታችሁ ትንሽ የገረጣችሁ ትመስላላችሁ”
“በደንብ አድገናል?”
“አዎ፣ አዎ አድጋችኋል” እየዋሸሁ እንኳን ፈገግ ብያለሁ: በዚያ የማስመሰል
ደስታና የውሸት ፈገግታ ወለሉ ላይ ከክሪስና ከመንትዮቹ ጋር ተቀምጠን
አራታችንም ልክ እንደ ገና ቀን ስጦታዎቻችንን መክፈት ጀመርን። ሁሉም
በውድ የስጦታ ወረቀቶች በሚያምር ሁኔታ የታሸጉ ናቸው።
ወረቀቱን ቀደድን ሪቫኑን ጥለን የታሸጉበትን ካርቶኖች ገነጣጥለን ውስጡ ያለውን አወጣን... በውስጡ ለእያንዳንዳችን የሚያማምሩ ልብሶች ነበሩ:
አዳዲስ መፃህፍት፣ መጫወቻዎች፣ አንድ አይነት ቅጠል የሚስል ቅርፅ ያላቸው በትልቅ ካርቶን ውስጥ የታሸጉ የስኳር ከረሜላዎች።
እንደምታስብልን ማሳያው ይኸው! ሁላችንንም በደንብ ታውቀናለች።ከመጠኖቹ በስተቀር ፍላጎታችንን፣ ማድረግ የምንፈልገውን ሁሉ ታውቃለች።
በፈቃደኝነት ሞተን ስንቀበር ማየት ደስ በሚላት ጠንቋይ አያታችን ጥበቃ ስር የተተውንባቸውን እነዚያን ባዶና ረጃጅም ወራት በስጦታዎቹ ከፈለችን።
በዚያ ላይ እናቷ ምን አይነት እናት እንደሆነች እያወቀች... የምትሰራው ሁሉ በልቧ ትክክል እንዳልሆነ እያወቀች በመጫወቻዎቹና በአሻንጉሊቶቹ
ልትደልለንና ይቅርታ ልትጠይቀን ፈለገች
በጣፋጭ የስኳር ከረሜላ መራራውን ብቸኝነታችንን ከአፋችን፣ ከልባችንና
ከአእምሯችን ልትወስድ ተስፋ አደረገች ምንም እንኳን ክሪስ መላጨት
የሚያስፈልገው እኔም ጡት መያዣ መልበስ የሚገባን እድሜ ላይ የደረስን
ቢሆንም በእሷ አስተሳሰብ አሁንም ልጆች ነን ልክ በምታመጣው መፃህፍት
ርዕስ ትንሽ አድርጋ ለዘለዓለም ልታስቀምጠን ትፈልጋለች፡
ኬሪን አዲስ ቀይ ቀሚስ ሳለብሳትና ሀምራዊ ሪቫን ሳደርግላት ፈገግ እንዳልኩ
ነበር አሁን ሁልጊዜ እንደምትፈልገው አይነት ለብሳለች የምትወዳቸውን
ቀለማት እግሮቿ ላይ ሀምራዊ ካልሲ ከነጭ አዲስ ስኒhር ጋር አለበስኳት “በጣም ታምሪያለሽ ኬሪ” እሷም ብሩህ ቀለም ያለው ልብስ በመልበሷ ተደስታለች።
ቀጥሎ ኮሪን ቀይ አጭር ሱሪና ኪሱ ቀይ የሆነ ነጭ ካኒቴራ አለበስኩት፡
ከዚያ “አንተንም ላልብስህ ክሪስቶፈር?” ስል ቀለድኩ
“ልብሽ ከፈቀደ ቆዳዬን ገልብጠሸ ማልበስ ትችያለሽ”
“ጋጠ ወጥ አትሁን!”
ኮሪ ሌላ የሙዚቃ መሳሪያ መጣለት፡ እሱ የሙዚቃ መሳሪያውን እየነካካ ኬሪ
ትዘፍንለታለች።
ሁሉም ነገር ላይ ያለኝን ደስታ የሚወስዱብኝ እግዚአብሔር የሰጠኝ ክፉ
ሀላቦች ነበሩኝ: ማንም የማያያቸው ከሆነ ቆንጆ ልብሶች ምን ይጠቅማሉ?
እኔ የምፈልገው በሚያምሩ ወረቀቶች ያልተጠቀለሉ፣ በሪቫን ያልታሰሩ፣ ሱቆች ውስጥ በካርቶን ያልተቀመጡ ነገሮችን ነው፧ የምፈልገው ገንዘብ
ሊገዛቸው የማይችላቸውን ነገሮች ነው: ጸጉሬ ከፊቴ በአጭሩ መቆረጡን
አስተውላለች? እንዴት እንደሳሳ አይታለች?የገረጣና የሳሳው ቆዳችንን እያየች
ጤነኛ እንደሆንን ታስባለች?
ለእኔ የተባሉትን ቆንጆ ቆንጆ ልብሶች ተመለከትኩ፡ ሰማያዊ ቬልቬት ቀሚስ፣ ለግብዣ የሚለበስ ሮዝና ሰማያዊ የምሽት ጋዋን አብሮት ከሚሄድ ጫማ ጋር፧ እዚያ ተቀምጬ ከረሜላውን እየበላሁ የሆነ ነገር ትዝ አለኝ፡፡
“ኢንሳክሎፒዲያ!” ለዘለዓለም እዚህ ልንኖር ይሆን?
የስኳር ከረሜላ በጣም ከምወዳቸው ነገሮች አንዱ ነው፡፡ ይህንን የከረሜላ
ካርቶን ያመጣችው ለኔ ነበር ለኔ፡ እኔ ግን መብላት የቻልኩት አንድ ብቻ
ነበር። ያንንም በጣም በችግር።
የከረሜላው ካርቶን መሀል ላይ ተቀምጦ ክሪስ ኮሪና ኬሪ ከበውት ተቀምጠው
በጣም በመደሰት ከረሜላዎቹን እያጣጣሙ ነበር፡ “ከረሜላዎቹን ሁሉ
መጨረስ አለባችሁ ለረጅም በጣም ለረጅም ጊዜ የማታዩት የመጨረሻ
ከረሜላችሁ ነው፡” አልኳቸው በመረረ ጥላቻ
ክሪስ አየት አደረገኝ ሰማያዊ አይኖቹ ደስተኛና የሚያበሩ ሆነዋል።
እምነቶቹና መተማመኑ ሁሉ እናታችን ለአጭር ጊዜ ባደረገችው ጉብኝት
እንደተመለሱለት ለማየት ቀላል ነበር፡ ስጦታዎቹ እሷ ከዚህ በኋላ ለእኛ ግድ የሌላት የመሆኑን ሀቅ የመደበቂያ መንገድ እንደሆነ ለምን ማየት አልቻለም? ከዚህ በፊት እንደነበርነው አሁን ለእሷ እውነት እንዳልሆንን እኔ
እንዳወቅኩት እንዴት አያውቅም? እኛ ልክ ጣሪያው ስር ያለው ክፍል ውስጥ እንዳሉት አይጦች፣ ሰዎች ሊነጋገሩባቸው ከማይፈልጓቸው ደስ የማይሉ ርዕሶች ውስጥ ነን፡
“እዚያ ቁጭ ብለሽ የማይናገር ምሰይ” አለ፡ ክሪስ ደስታውን እኔ ላይ እያንፀባረቀ: “እኛ ሶስታችን አይጦቹ መጥተው ከመብላታቸው በፊት አምሮታችንን ስንወጣ አንቺ ከረሜላውን እምቢ በይ: አንቺ ቁጭ ብለሽ ስታለቅሺ፣ ለራስሽ
ስታዝኚና ራስን መስዋዕት በማድረግ ሁኔታችንን መለወጥ እንደምትችይ ስታስመስይ ኮሪ፣ ኬሪና እኔ በልተን ጨርሰን ጥርሶቻችንን እናፀዳለን፡ ቀጥይ
ካቲ አልቅሺ! ሰማዕት ሁኚ! ተሰቃይ! ጭንቅላትሽን ከግድግዳ አላትሚ! ጩኺ እኛ እንደሆነ ወንድ አያታችን እስኪሞት እዚህ መሆናችን የማይቀር ነው::በዚያ ላይ ከረሜላዎቹ ሁሉ ያልቃሉ! ያልቃሉ! ያልቃሉ”
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ዘጠኝ
፡
፡
#ትርጉሜ_ሀኒም_ኤልያስ
...ልታገኝ ስለምትፈልገው ነገር ስትል ድራማ የምትሰራ አድርጌ የማስባት ለምንድነው? እኔን ችላ ብላ ክሪስን ተመለከተች።
ለሚቀጥለው ልደትህ ኢንሳይክሎፒድያ አዝዤልሀለው። ማተምያው ድረስ ራሴ ሄጄ ነው ያዘዝኩት ስምህንና ቀኑን ሰጥቺያቸዋለሁ ግን ወደዚህ በቀጥታ መላክ አይችሉም:: የሆነ ሰው ሊቀበላቸው ይገባል ልክ ሁልጊዜ ራስህን ለማስተማር ምርጡን ልሰጥህ እንደምፈልግ ሁሉ የሚያስደስትህን ስጦታ ሳስብ ሳስብ ቆይቼ ነው ያዘዝኩልህ”
ክሪስ የሚናገረውን አጣ ፊቱ ላይ የሚታየው ድብልቅልቅ ስሜት ነበር፤አይኖቹ ግራ የተጋቡና የፈዘዙ መሰሉ። አምላኬ! ካደረገችው ነገር በኋላ እንኳን ይወዳታል ማለት ነው::
ስሜቶቹ ቀጥታ ናቸው:: በቁጣ ነደድኩ እንደዚህ አይነት መፅሀፍት ከአንድ
ሺ ዶላር በላይ ይፈጃል: ምናልባትም ሁለት ወይም ሶስት ሺም ሊፈጅ ይችላል። ይህንን ገንዘብ ለምን የማምለጫ ገንዘባችን ውስጥ አትጨምረውም?
ልክ ኬሪ ስትቃወም እንደምታደርገው ልጮህ ስል ክሪስ አይኖች ላይ ያየሁት ነገር አፌን እንድዘጋ አደረገኝ፡ ሁልጊዜ እነዚያ መፃህፍት እንዲኖሩት ይፈልግ ነበር፡ በዚያ ላይ አንድ ጊዜ ታዟል: አሁን ለሷ ገንዘብ ምኗም አይደለም፧
ምናልባት እንዲያው ምናልባት አያታችን ዛሬ ወይም ነገ ሊሞት ስለሚችል አፓርታማ መከራየትም ሆነ ቤት መግዛት አያስፈልጋት ይሆናል፡
ጥርጣሬዬ ተሰምቷታል።
እናታችን ጭንቅላቷን ቀና አደረገችና ወደ በሩ ተራመደች። ስጦታዎቻችንን
ገና አልከፈትንም፤ ስንከፍት የሚኖረንን ስሜት ለመመልከትም አልቆየችም።
እየጠላኋት ለምንድነው በውስጤ የማለቅሰው? አሁን አልወዳትም አልወዳትም።
በሩጋ ደርሳ እየከፈተች “ዛሬ ስለፈጠራችሁብኝ ህመም ስታስቡና እንደገና
በፍቅርና በአክብሮት ልታስተናግዱኝ ስትችሉ ተመልሼ እመጣለሁ ከዚያ
በፊት ግን አይሆንም::” አለች።
መጣች።
ሄደች።
መጥታ ስትመለስ
ኬሪና ኮሪን አልነካቻቸውም አልሳመቻቸውም አላናገረቻቸውም ለምን እንደሆነ አውቄያለሁ፤ ሀብት ማግኘት መንትዮቹን ምን ያህል ዋጋ እንዳስከፈላቸው ማየት መቋቋም ባለመቻሏ ነበር።
ከጠረጴዛው አጠገብ ተነስተው እየሮጡ ወደ እኔ መጡና ቀሚሴን እየጎተቱ
ፊቴ ላይ አፈጠጡ ትንንሽ ፊቶቻቸው ጭንቀትና ፍርሀት አጥልቶባቸዋል።
እነሱም ደስታ እንዲሰማቸው መደሰቴን ለማየት ፊቴን እያጠኑ ነው:
ተንበርክኬ እሷ የጎዳቻቸውን በመሳምና በማቀፍ አጥለቀለቅኳቸው።
መልካችን ያስጠላል?" ጠየቀች ኬሪ በመጨነቅ፤ ትንንሽ እጆቿ እጄን
ይዘውኛል
“አይ በጭራሽ! አንቺና ኮሪ ቤት ውስጥ ብዙ በመቆየታችሁ ትንሽ የገረጣችሁ ትመስላላችሁ”
“በደንብ አድገናል?”
“አዎ፣ አዎ አድጋችኋል” እየዋሸሁ እንኳን ፈገግ ብያለሁ: በዚያ የማስመሰል
ደስታና የውሸት ፈገግታ ወለሉ ላይ ከክሪስና ከመንትዮቹ ጋር ተቀምጠን
አራታችንም ልክ እንደ ገና ቀን ስጦታዎቻችንን መክፈት ጀመርን። ሁሉም
በውድ የስጦታ ወረቀቶች በሚያምር ሁኔታ የታሸጉ ናቸው።
ወረቀቱን ቀደድን ሪቫኑን ጥለን የታሸጉበትን ካርቶኖች ገነጣጥለን ውስጡ ያለውን አወጣን... በውስጡ ለእያንዳንዳችን የሚያማምሩ ልብሶች ነበሩ:
አዳዲስ መፃህፍት፣ መጫወቻዎች፣ አንድ አይነት ቅጠል የሚስል ቅርፅ ያላቸው በትልቅ ካርቶን ውስጥ የታሸጉ የስኳር ከረሜላዎች።
እንደምታስብልን ማሳያው ይኸው! ሁላችንንም በደንብ ታውቀናለች።ከመጠኖቹ በስተቀር ፍላጎታችንን፣ ማድረግ የምንፈልገውን ሁሉ ታውቃለች።
በፈቃደኝነት ሞተን ስንቀበር ማየት ደስ በሚላት ጠንቋይ አያታችን ጥበቃ ስር የተተውንባቸውን እነዚያን ባዶና ረጃጅም ወራት በስጦታዎቹ ከፈለችን።
በዚያ ላይ እናቷ ምን አይነት እናት እንደሆነች እያወቀች... የምትሰራው ሁሉ በልቧ ትክክል እንዳልሆነ እያወቀች በመጫወቻዎቹና በአሻንጉሊቶቹ
ልትደልለንና ይቅርታ ልትጠይቀን ፈለገች
በጣፋጭ የስኳር ከረሜላ መራራውን ብቸኝነታችንን ከአፋችን፣ ከልባችንና
ከአእምሯችን ልትወስድ ተስፋ አደረገች ምንም እንኳን ክሪስ መላጨት
የሚያስፈልገው እኔም ጡት መያዣ መልበስ የሚገባን እድሜ ላይ የደረስን
ቢሆንም በእሷ አስተሳሰብ አሁንም ልጆች ነን ልክ በምታመጣው መፃህፍት
ርዕስ ትንሽ አድርጋ ለዘለዓለም ልታስቀምጠን ትፈልጋለች፡
ኬሪን አዲስ ቀይ ቀሚስ ሳለብሳትና ሀምራዊ ሪቫን ሳደርግላት ፈገግ እንዳልኩ
ነበር አሁን ሁልጊዜ እንደምትፈልገው አይነት ለብሳለች የምትወዳቸውን
ቀለማት እግሮቿ ላይ ሀምራዊ ካልሲ ከነጭ አዲስ ስኒhር ጋር አለበስኳት “በጣም ታምሪያለሽ ኬሪ” እሷም ብሩህ ቀለም ያለው ልብስ በመልበሷ ተደስታለች።
ቀጥሎ ኮሪን ቀይ አጭር ሱሪና ኪሱ ቀይ የሆነ ነጭ ካኒቴራ አለበስኩት፡
ከዚያ “አንተንም ላልብስህ ክሪስቶፈር?” ስል ቀለድኩ
“ልብሽ ከፈቀደ ቆዳዬን ገልብጠሸ ማልበስ ትችያለሽ”
“ጋጠ ወጥ አትሁን!”
ኮሪ ሌላ የሙዚቃ መሳሪያ መጣለት፡ እሱ የሙዚቃ መሳሪያውን እየነካካ ኬሪ
ትዘፍንለታለች።
ሁሉም ነገር ላይ ያለኝን ደስታ የሚወስዱብኝ እግዚአብሔር የሰጠኝ ክፉ
ሀላቦች ነበሩኝ: ማንም የማያያቸው ከሆነ ቆንጆ ልብሶች ምን ይጠቅማሉ?
እኔ የምፈልገው በሚያምሩ ወረቀቶች ያልተጠቀለሉ፣ በሪቫን ያልታሰሩ፣ ሱቆች ውስጥ በካርቶን ያልተቀመጡ ነገሮችን ነው፧ የምፈልገው ገንዘብ
ሊገዛቸው የማይችላቸውን ነገሮች ነው: ጸጉሬ ከፊቴ በአጭሩ መቆረጡን
አስተውላለች? እንዴት እንደሳሳ አይታለች?የገረጣና የሳሳው ቆዳችንን እያየች
ጤነኛ እንደሆንን ታስባለች?
ለእኔ የተባሉትን ቆንጆ ቆንጆ ልብሶች ተመለከትኩ፡ ሰማያዊ ቬልቬት ቀሚስ፣ ለግብዣ የሚለበስ ሮዝና ሰማያዊ የምሽት ጋዋን አብሮት ከሚሄድ ጫማ ጋር፧ እዚያ ተቀምጬ ከረሜላውን እየበላሁ የሆነ ነገር ትዝ አለኝ፡፡
“ኢንሳክሎፒዲያ!” ለዘለዓለም እዚህ ልንኖር ይሆን?
የስኳር ከረሜላ በጣም ከምወዳቸው ነገሮች አንዱ ነው፡፡ ይህንን የከረሜላ
ካርቶን ያመጣችው ለኔ ነበር ለኔ፡ እኔ ግን መብላት የቻልኩት አንድ ብቻ
ነበር። ያንንም በጣም በችግር።
የከረሜላው ካርቶን መሀል ላይ ተቀምጦ ክሪስ ኮሪና ኬሪ ከበውት ተቀምጠው
በጣም በመደሰት ከረሜላዎቹን እያጣጣሙ ነበር፡ “ከረሜላዎቹን ሁሉ
መጨረስ አለባችሁ ለረጅም በጣም ለረጅም ጊዜ የማታዩት የመጨረሻ
ከረሜላችሁ ነው፡” አልኳቸው በመረረ ጥላቻ
ክሪስ አየት አደረገኝ ሰማያዊ አይኖቹ ደስተኛና የሚያበሩ ሆነዋል።
እምነቶቹና መተማመኑ ሁሉ እናታችን ለአጭር ጊዜ ባደረገችው ጉብኝት
እንደተመለሱለት ለማየት ቀላል ነበር፡ ስጦታዎቹ እሷ ከዚህ በኋላ ለእኛ ግድ የሌላት የመሆኑን ሀቅ የመደበቂያ መንገድ እንደሆነ ለምን ማየት አልቻለም? ከዚህ በፊት እንደነበርነው አሁን ለእሷ እውነት እንዳልሆንን እኔ
እንዳወቅኩት እንዴት አያውቅም? እኛ ልክ ጣሪያው ስር ያለው ክፍል ውስጥ እንዳሉት አይጦች፣ ሰዎች ሊነጋገሩባቸው ከማይፈልጓቸው ደስ የማይሉ ርዕሶች ውስጥ ነን፡
“እዚያ ቁጭ ብለሽ የማይናገር ምሰይ” አለ፡ ክሪስ ደስታውን እኔ ላይ እያንፀባረቀ: “እኛ ሶስታችን አይጦቹ መጥተው ከመብላታቸው በፊት አምሮታችንን ስንወጣ አንቺ ከረሜላውን እምቢ በይ: አንቺ ቁጭ ብለሽ ስታለቅሺ፣ ለራስሽ
ስታዝኚና ራስን መስዋዕት በማድረግ ሁኔታችንን መለወጥ እንደምትችይ ስታስመስይ ኮሪ፣ ኬሪና እኔ በልተን ጨርሰን ጥርሶቻችንን እናፀዳለን፡ ቀጥይ
ካቲ አልቅሺ! ሰማዕት ሁኚ! ተሰቃይ! ጭንቅላትሽን ከግድግዳ አላትሚ! ጩኺ እኛ እንደሆነ ወንድ አያታችን እስኪሞት እዚህ መሆናችን የማይቀር ነው::በዚያ ላይ ከረሜላዎቹ ሁሉ ያልቃሉ! ያልቃሉ! ያልቃሉ”
👍42❤3
#የጣሪያ_ስር_አበቦች
፡
፡
#ክፍል_ሰላሳ
፡
፡
#ትርጉም_ሀኒም_ኤልያስ
...“ክሪስቶፈር” አልኩ እየጮህኩ፤ ራሴን መቆጣጠር አልቻልኩም አንዳንድ ጊዜ እናቴን እጠላታለሁ! ያ ብቻ አይደለም አንዳንዴ አንተንም እጠላሀለሁ አንዳንዴ ሁሉንም ሰው በተለይ ራሴን እጠላዋለሁ! አንዳንዴ በሞትኩ ብዬ እመኛለሁ:
ምክንያቱም እዚህ ቦታ በቁም ከመቀበር መሞት ይሻላል! እኛ የበሰበሰ፣ የሚራመድ፣ የሚያወራ አትክልቶች ነን!...
ሚስጥራዊ ሀሳቦቼ በሙሉ ይፋ ወጡ፤ ልክ እንደ ቆሻሻ ተዘርግፈው ሁለቱንም
ወንድሞቼን አስደነገጣቸው፡ ትንሸዋ እህቴ ደግሞ መንቀጥቀጥ ጀምራ የበለጠ ትንሽ መሰለች እነዚያ ጨካኝ ቃላት ከአፌ እንደወጡ ወዲያውኑ እንዲመለሱ ፈለግኩ በእፍረት ሰመጥኩ፣ ይቅርታ መጠየቅና መመለስ አልቻልኩም።ዞርኩና እየሮጥኩ ወደ ልብስ ማስቀመጫው ከዚያ ወደ ደረጃዎቹ ከዚያ ጣሪያው ስር ወዳለው ክፍል ሄድኩ። ስጎዳ፣ ብዙ ጊዜም እጎዳለሁ ሙዚቃ ፈለግኩ፤ የዳንስ ልብሴን ለበስኩና ችግሮቼን ሁሉ ለመርሳት መደነስ ጀመርኩ።
እስኪደክመኝ ድረስ መደነስ ቀጠልኩ፡ ከዚያ ድንገት ሙዚቃው ሲያልቅ
ቀኝ እግሬ ታጠፈና ወለሉ ላይ ወደቅኩ። ለመነሳት ብታገልም መራመድ
አልቻልኩም: ጉልበቴን በጣም አሞኛል: ሌላ አይነት እምባ ወደ አይኖቼ
መጣ እየተጎተትኩ ወደ መማሪያው ክፍል ሄድኩኝ፡ ጉልበቴ ለዘለዓለም
ባይሰራም ግድ አልነበረኝም መስኮቱን በሰፊው ከፈትኩና ወደ ጥቁሩ ጣራ ወጣሁ። እያመመኝ መታጠፊያው ጫፍ ደረስኩና በውሀ መውረጃው አሸንዳ
ጠርዝ ላይ ስደርስ ቆምኩ። ታች ያለው መሬቱ ነው። ፊቴ ለራሱ የማዘን እምባና ህመም ምልክት አወጣ፣ እምባዬ እይታዬንም ብዥ አደረገው አይኖቼን ጨፍኜ ሚዛኔን ሳልጠብቅ መወዛወዝ ጀመርኩ፡ በደቂቃዎች ውስጥ
ሁሉም ያበቃል። እሾሀማ የፅጌረዳ ተክሎቹ ውስጥ እወድቃለሁ።
አያትየውና እናቴ አንዲት የማትታወቅ ደደብ ልጅ ጣሪያው ላይ ወጥታ
ድንገት ወደቀች ሊሉ ይችላሉ። እናቴ ሞቼና ተሰብሬ የሬሳ ሳጥን ውስጥ
ተጋድሜ ስትመለከት ታለቅስ ይሆናል። ከዚያ ያደረገችውን ታስታውስና
ክሪስንና መንትዮቹን ነፃ ለማድረግ በሩን ከፍታ እንደገና እውነተኛ ኑሮ
እንዲኖሩ ታደርግ ይሆናል።
ያ ራሴን የመግደሌ ወርቃማ ጎን ነበር።
ሌላኛውን ጎን ማየት አለብኝ: ካልሞትኩስ? ብወድቅና አወዳደቄ የሚገል ሳይሆን ቀርቶ ህይወቴን ሙሉ አካለ ጉዳተኛ ወይም ጠባሳ ቢያደርገኝስ? ከዚያ እንደገና ምናልባት ብሞትና እናታችን ባታለቅስ ወይም ባታዝን ወይም ባትፀፀትስ? እንዲያውም እንደኔ አይነቷን ተባይ በማስወገዷ ደስ
ቢላትስ? ክሪስና መንትዮቹ ያለ እኔ እንዴት ይሆናሉ? ማን ይንከባከባቸዋል?
ለመንትዮቹ ማን እናት ይሆናቸዋል?
ክሪስ ምናልባት አይፈልገኝ ይሆናል፤ የሚገዛለት ትልቁ ውዱ መፅሀፍ የኔን
ቦታ ይተካለት ይሆናል ከስሙ በፊት ዶክተር የሚለውን ማዕረግ ሲያገኝ
ህይወቱን ሙሉ ለመርካት በቂ ይሆንለት ይሆናል ግን ዶክተር ቢሆንም በቂ እንደማይሆን፣ እኔ ከሌለሁ በጭራሽ በቂ እንደማይሆን አውቃለሁ።ሁለቱንም ገፅ ለማየት ባለኝ ችሎታ ከሞት ተረፍኩ፡
ህፃንነትና ሞኝነት እየተሰማኝ ከጣሪያው ጠርዝ ስርቅ አሁንም እያለቅስኩ ነበር ጉልበቴ በጣም ስላመመኝ የጭስ መውጫው ጀርባ ጋ እስክደርስ ድረስ ጣሪያው ላይ ዳዴ እያልኩ እየሄድኩ ነበር። ሁለት ጣራዎች ተገናኝተው ምቹ ጥግ የፈጠሩበት ቦታ ነው: በጀርባዬ ተጋድሜ የማይታየውና ግድ
የሌለው ሰማይ ላይ አፈጠጥኩ። እግዚአብሔርም ሆነ መንግስተ ሰማያት
እዚያ መኖራቸውን ተጠራጠርኩ።
እግዚአብሔርና መንግስተ ሰማያት እዚሁ ምድር ላይ በአትክልት ስፍራዎቹ፣
በጫካዎቹ፣ በመናፈሻዎቹ፣ በባህር ዳርቻዎቹ፣ በሀይቆቹና በአውራ ጎዳናዎቹ ውስጥ ናቸው።
ሲኦልም እዚሁ ነው… እኔ ያለሁበት ያለማቋረጥ የከበበኝ ወደ እሱ ሊወስደኝ
የሚሞክርና አያትየው እንደምታስበው የሰይጣን ዘር ሊያደርገኝ የሚጥር
ነው።
ጨለማ እስኪሆን ድረስ እዚያ ጠንካራና ቀዝቃዛ ጣራ ላይ ተጋደምኩ።
ጨረቃ ወጣች፣ ኮከቦቹም ምን እንደሆንኩ እንደሚያውቁ ሁሉ በቁጣ እኔ ላይ አበሩ የለበስኩት የዳንስ ልብስ ብቻ ነበር ከብርዱ የተነሳ ክንዶቼ ላይ ሽፍ አለብኝ አሁንም በቀሌን እያቀድኩ ነው፡ ከመልካም ወደ ክፉ የለወጡኝንና
ከዚህ ቀን ጀምሮ የምሆነውን አይነት ሰው ያደረጉኝን እበቀላለሁ። አያቴና እናቴ በመዳፌ ስር የሚሆኑበት ቀን እንደሚመጣ ራሴን አሳመንኩት አለንጋ
እይዛለሁ፣ ሬንጁንም እይዛለሁ፣ የምግብ አሰጣጥም እቆጣጠራለሁ።
ምን እንደማደርጋቸው ለማሰብ እየሞከርኩ ነው:: ትክክለኛው ቅጣት
ምንድነው? ሁለቱንም ቆልፌባቸው ቁልፉን መወርወር? እኛ እንደተራብነው ማስራብ?
ለስላሳ ድምፅ ምሽቱንና የተጠላለፉ ሀሳቦቼን አቋረጠ። ክሪስ እያመነታ
ስሜን እየጠራ ነው: ምንም አልተናገረም ስሜን ብቻ ይጠራል: መልስ
አልሰጠሁትም አልፈልገውም፣ አሳፍሮኛል ማንንም አልፈልግም ባለ መረዳቱ አልፈልገውም።
የሆነው ሆኖ መጣና አጠገቤ ጋደም አለ። ምንም ቃል ሳይናገር ይዞት
የመጣውን ሞቃት የሱፍ ጃኬት ደረበልኝ፡ ልክ እንደ እኔ ወደ ቀዝቃዛውና
የተከለለው ሰማይ ላይ አፍጥጧል በመከላችን አስፈሪና ረጅም ፀጥታ
ነገሰ። ስለ ክሪስ የምጠላው ወይም የማልወደው ምንም ነገር የለም ወደ እሱ ዞሬ ይህንን ልነግረውና የሚሞቅ ጃኬት ስላመጣልኝ ላመሰግነው በጣም
ፈልጌያለሁ። ነገር ግን አንዲት ቃል መናገር አልቻልኩም: የሚሰማኝን
እሱና መንትዮቹ ላይ ስለተወጣሁት እንደተፀፀትኩ እንዲያውቅ ፈልጌ ነበር።ማንኛችንም ሌላ ጠላት እንደማያስፈልገን እግዚአብሔር ያውቃል በጃኬቱ ውስጥ ሆነው የሚንቀጠቀጡት ክንዶቼ አቅፈው ሊያፅናኑት ናፍቀዋል ምክንያቱም አብዛኛውን ጊዜ ከቅዠቴ ስባንን የሚያባብለኝ እሱ ነው ነገር ግን ማድረግ የቻልኩት ብቸኛው ነገር፣ እዚያው ጋደም ብዬ በብዙ ነገሮች የተያዝኩ መሆኔን እንዲረዳ ተስፋ ማድረግ ብቻ ነበር።
ሁልጊዜ አስቀድሞ ነጭ ባንዲራ የሚያውለበልበው እሱ ነው፡ ለዚህም
ለዘለአለም አመስጋኝ ነኝ። እንግዳ በሆነ ጎርናና እና ውጥረት በሚሰማበት
ከሩቅ የሚመጣ በሚመስል ድምፅ፤ እሱና መንትዮቹ ራታቸውን እንደበሉና
ለእኔ ድርሻዬን እንዳስቀመጠልኝ ነገረኝ፡ “እና ከረሜላዎቹን ሁሉ በላናቸው ያልነው እያስመሰልን ነው ካቲ ለአንቺ ብዙ ተቀምጦልሻል” አለኝ።
ከረሜላ? ስለ ከረሜላ ያወራል፤ አሁንም ከረሜላ የእምባ ማበሻ በሆነበት
የልጆች አለም ውስጥ ነው? እኔ አድጌ ለልጆች መደሰቻ ጉጉት አጥቼያለሁ።
የምፈልገው ሌሎች በእኔ እድሜ ያሉ ልጆች የሚፈልጉትን ነው፤ የምፈልገው ወደ ሙሉ ሴትነት ማደግ የምችልበትን ነፃነት ነው፤ ህይወቴን በሙሉ የምቆጣጠርበትን ነፃነት ነው፡፡ ይህንን ልነግረው ስሞክር ድምፄ ልክ እንደ እምባዬ ደረቀብኝ
ካቲ ያልሺው ነገር... ሁለተኛ አስቀያሚና እንደዚያ አይነት ተስፋ ቢስ ነገሮች አትናገሪ” አለኝ፡
“ለምን?” ተናነቀኝ “የተናገርኩት እያንዳንዱ ቃል እውነት ነው፡ የተናገርኩት በውስጤ የሚሰማኝን ነው ያወጣሁት አንተ በውስጥህ የቀበርከውን ነው
ከራስህ መደበቅህን ቀጥልበት እነዚያ እውነታዎች ወደ አሲድነት ተቀይረው ውስጥህን ሲበሉት ታገኛቸዋለህ!” “አንድ ጊዜም መሞት ተመኝቼ አላውቅም”
፡
፡
#ክፍል_ሰላሳ
፡
፡
#ትርጉም_ሀኒም_ኤልያስ
...“ክሪስቶፈር” አልኩ እየጮህኩ፤ ራሴን መቆጣጠር አልቻልኩም አንዳንድ ጊዜ እናቴን እጠላታለሁ! ያ ብቻ አይደለም አንዳንዴ አንተንም እጠላሀለሁ አንዳንዴ ሁሉንም ሰው በተለይ ራሴን እጠላዋለሁ! አንዳንዴ በሞትኩ ብዬ እመኛለሁ:
ምክንያቱም እዚህ ቦታ በቁም ከመቀበር መሞት ይሻላል! እኛ የበሰበሰ፣ የሚራመድ፣ የሚያወራ አትክልቶች ነን!...
ሚስጥራዊ ሀሳቦቼ በሙሉ ይፋ ወጡ፤ ልክ እንደ ቆሻሻ ተዘርግፈው ሁለቱንም
ወንድሞቼን አስደነገጣቸው፡ ትንሸዋ እህቴ ደግሞ መንቀጥቀጥ ጀምራ የበለጠ ትንሽ መሰለች እነዚያ ጨካኝ ቃላት ከአፌ እንደወጡ ወዲያውኑ እንዲመለሱ ፈለግኩ በእፍረት ሰመጥኩ፣ ይቅርታ መጠየቅና መመለስ አልቻልኩም።ዞርኩና እየሮጥኩ ወደ ልብስ ማስቀመጫው ከዚያ ወደ ደረጃዎቹ ከዚያ ጣሪያው ስር ወዳለው ክፍል ሄድኩ። ስጎዳ፣ ብዙ ጊዜም እጎዳለሁ ሙዚቃ ፈለግኩ፤ የዳንስ ልብሴን ለበስኩና ችግሮቼን ሁሉ ለመርሳት መደነስ ጀመርኩ።
እስኪደክመኝ ድረስ መደነስ ቀጠልኩ፡ ከዚያ ድንገት ሙዚቃው ሲያልቅ
ቀኝ እግሬ ታጠፈና ወለሉ ላይ ወደቅኩ። ለመነሳት ብታገልም መራመድ
አልቻልኩም: ጉልበቴን በጣም አሞኛል: ሌላ አይነት እምባ ወደ አይኖቼ
መጣ እየተጎተትኩ ወደ መማሪያው ክፍል ሄድኩኝ፡ ጉልበቴ ለዘለዓለም
ባይሰራም ግድ አልነበረኝም መስኮቱን በሰፊው ከፈትኩና ወደ ጥቁሩ ጣራ ወጣሁ። እያመመኝ መታጠፊያው ጫፍ ደረስኩና በውሀ መውረጃው አሸንዳ
ጠርዝ ላይ ስደርስ ቆምኩ። ታች ያለው መሬቱ ነው። ፊቴ ለራሱ የማዘን እምባና ህመም ምልክት አወጣ፣ እምባዬ እይታዬንም ብዥ አደረገው አይኖቼን ጨፍኜ ሚዛኔን ሳልጠብቅ መወዛወዝ ጀመርኩ፡ በደቂቃዎች ውስጥ
ሁሉም ያበቃል። እሾሀማ የፅጌረዳ ተክሎቹ ውስጥ እወድቃለሁ።
አያትየውና እናቴ አንዲት የማትታወቅ ደደብ ልጅ ጣሪያው ላይ ወጥታ
ድንገት ወደቀች ሊሉ ይችላሉ። እናቴ ሞቼና ተሰብሬ የሬሳ ሳጥን ውስጥ
ተጋድሜ ስትመለከት ታለቅስ ይሆናል። ከዚያ ያደረገችውን ታስታውስና
ክሪስንና መንትዮቹን ነፃ ለማድረግ በሩን ከፍታ እንደገና እውነተኛ ኑሮ
እንዲኖሩ ታደርግ ይሆናል።
ያ ራሴን የመግደሌ ወርቃማ ጎን ነበር።
ሌላኛውን ጎን ማየት አለብኝ: ካልሞትኩስ? ብወድቅና አወዳደቄ የሚገል ሳይሆን ቀርቶ ህይወቴን ሙሉ አካለ ጉዳተኛ ወይም ጠባሳ ቢያደርገኝስ? ከዚያ እንደገና ምናልባት ብሞትና እናታችን ባታለቅስ ወይም ባታዝን ወይም ባትፀፀትስ? እንዲያውም እንደኔ አይነቷን ተባይ በማስወገዷ ደስ
ቢላትስ? ክሪስና መንትዮቹ ያለ እኔ እንዴት ይሆናሉ? ማን ይንከባከባቸዋል?
ለመንትዮቹ ማን እናት ይሆናቸዋል?
ክሪስ ምናልባት አይፈልገኝ ይሆናል፤ የሚገዛለት ትልቁ ውዱ መፅሀፍ የኔን
ቦታ ይተካለት ይሆናል ከስሙ በፊት ዶክተር የሚለውን ማዕረግ ሲያገኝ
ህይወቱን ሙሉ ለመርካት በቂ ይሆንለት ይሆናል ግን ዶክተር ቢሆንም በቂ እንደማይሆን፣ እኔ ከሌለሁ በጭራሽ በቂ እንደማይሆን አውቃለሁ።ሁለቱንም ገፅ ለማየት ባለኝ ችሎታ ከሞት ተረፍኩ፡
ህፃንነትና ሞኝነት እየተሰማኝ ከጣሪያው ጠርዝ ስርቅ አሁንም እያለቅስኩ ነበር ጉልበቴ በጣም ስላመመኝ የጭስ መውጫው ጀርባ ጋ እስክደርስ ድረስ ጣሪያው ላይ ዳዴ እያልኩ እየሄድኩ ነበር። ሁለት ጣራዎች ተገናኝተው ምቹ ጥግ የፈጠሩበት ቦታ ነው: በጀርባዬ ተጋድሜ የማይታየውና ግድ
የሌለው ሰማይ ላይ አፈጠጥኩ። እግዚአብሔርም ሆነ መንግስተ ሰማያት
እዚያ መኖራቸውን ተጠራጠርኩ።
እግዚአብሔርና መንግስተ ሰማያት እዚሁ ምድር ላይ በአትክልት ስፍራዎቹ፣
በጫካዎቹ፣ በመናፈሻዎቹ፣ በባህር ዳርቻዎቹ፣ በሀይቆቹና በአውራ ጎዳናዎቹ ውስጥ ናቸው።
ሲኦልም እዚሁ ነው… እኔ ያለሁበት ያለማቋረጥ የከበበኝ ወደ እሱ ሊወስደኝ
የሚሞክርና አያትየው እንደምታስበው የሰይጣን ዘር ሊያደርገኝ የሚጥር
ነው።
ጨለማ እስኪሆን ድረስ እዚያ ጠንካራና ቀዝቃዛ ጣራ ላይ ተጋደምኩ።
ጨረቃ ወጣች፣ ኮከቦቹም ምን እንደሆንኩ እንደሚያውቁ ሁሉ በቁጣ እኔ ላይ አበሩ የለበስኩት የዳንስ ልብስ ብቻ ነበር ከብርዱ የተነሳ ክንዶቼ ላይ ሽፍ አለብኝ አሁንም በቀሌን እያቀድኩ ነው፡ ከመልካም ወደ ክፉ የለወጡኝንና
ከዚህ ቀን ጀምሮ የምሆነውን አይነት ሰው ያደረጉኝን እበቀላለሁ። አያቴና እናቴ በመዳፌ ስር የሚሆኑበት ቀን እንደሚመጣ ራሴን አሳመንኩት አለንጋ
እይዛለሁ፣ ሬንጁንም እይዛለሁ፣ የምግብ አሰጣጥም እቆጣጠራለሁ።
ምን እንደማደርጋቸው ለማሰብ እየሞከርኩ ነው:: ትክክለኛው ቅጣት
ምንድነው? ሁለቱንም ቆልፌባቸው ቁልፉን መወርወር? እኛ እንደተራብነው ማስራብ?
ለስላሳ ድምፅ ምሽቱንና የተጠላለፉ ሀሳቦቼን አቋረጠ። ክሪስ እያመነታ
ስሜን እየጠራ ነው: ምንም አልተናገረም ስሜን ብቻ ይጠራል: መልስ
አልሰጠሁትም አልፈልገውም፣ አሳፍሮኛል ማንንም አልፈልግም ባለ መረዳቱ አልፈልገውም።
የሆነው ሆኖ መጣና አጠገቤ ጋደም አለ። ምንም ቃል ሳይናገር ይዞት
የመጣውን ሞቃት የሱፍ ጃኬት ደረበልኝ፡ ልክ እንደ እኔ ወደ ቀዝቃዛውና
የተከለለው ሰማይ ላይ አፍጥጧል በመከላችን አስፈሪና ረጅም ፀጥታ
ነገሰ። ስለ ክሪስ የምጠላው ወይም የማልወደው ምንም ነገር የለም ወደ እሱ ዞሬ ይህንን ልነግረውና የሚሞቅ ጃኬት ስላመጣልኝ ላመሰግነው በጣም
ፈልጌያለሁ። ነገር ግን አንዲት ቃል መናገር አልቻልኩም: የሚሰማኝን
እሱና መንትዮቹ ላይ ስለተወጣሁት እንደተፀፀትኩ እንዲያውቅ ፈልጌ ነበር።ማንኛችንም ሌላ ጠላት እንደማያስፈልገን እግዚአብሔር ያውቃል በጃኬቱ ውስጥ ሆነው የሚንቀጠቀጡት ክንዶቼ አቅፈው ሊያፅናኑት ናፍቀዋል ምክንያቱም አብዛኛውን ጊዜ ከቅዠቴ ስባንን የሚያባብለኝ እሱ ነው ነገር ግን ማድረግ የቻልኩት ብቸኛው ነገር፣ እዚያው ጋደም ብዬ በብዙ ነገሮች የተያዝኩ መሆኔን እንዲረዳ ተስፋ ማድረግ ብቻ ነበር።
ሁልጊዜ አስቀድሞ ነጭ ባንዲራ የሚያውለበልበው እሱ ነው፡ ለዚህም
ለዘለአለም አመስጋኝ ነኝ። እንግዳ በሆነ ጎርናና እና ውጥረት በሚሰማበት
ከሩቅ የሚመጣ በሚመስል ድምፅ፤ እሱና መንትዮቹ ራታቸውን እንደበሉና
ለእኔ ድርሻዬን እንዳስቀመጠልኝ ነገረኝ፡ “እና ከረሜላዎቹን ሁሉ በላናቸው ያልነው እያስመሰልን ነው ካቲ ለአንቺ ብዙ ተቀምጦልሻል” አለኝ።
ከረሜላ? ስለ ከረሜላ ያወራል፤ አሁንም ከረሜላ የእምባ ማበሻ በሆነበት
የልጆች አለም ውስጥ ነው? እኔ አድጌ ለልጆች መደሰቻ ጉጉት አጥቼያለሁ።
የምፈልገው ሌሎች በእኔ እድሜ ያሉ ልጆች የሚፈልጉትን ነው፤ የምፈልገው ወደ ሙሉ ሴትነት ማደግ የምችልበትን ነፃነት ነው፤ ህይወቴን በሙሉ የምቆጣጠርበትን ነፃነት ነው፡፡ ይህንን ልነግረው ስሞክር ድምፄ ልክ እንደ እምባዬ ደረቀብኝ
ካቲ ያልሺው ነገር... ሁለተኛ አስቀያሚና እንደዚያ አይነት ተስፋ ቢስ ነገሮች አትናገሪ” አለኝ፡
“ለምን?” ተናነቀኝ “የተናገርኩት እያንዳንዱ ቃል እውነት ነው፡ የተናገርኩት በውስጤ የሚሰማኝን ነው ያወጣሁት አንተ በውስጥህ የቀበርከውን ነው
ከራስህ መደበቅህን ቀጥልበት እነዚያ እውነታዎች ወደ አሲድነት ተቀይረው ውስጥህን ሲበሉት ታገኛቸዋለህ!” “አንድ ጊዜም መሞት ተመኝቼ አላውቅም”
👍46🥰3❤1
#የጣሪያ_ስር_አበቦች
፡
፡
#ክፍል_ሰላሳ_አንድ
፡
፡
#ትርጉም_ሀኒም_ኤልያስ
የእናታችን ድንገተኛ ዜና
እናታችን እንደገና ልታየን ከመምጣቷ በፊት ባለፉት በእያንዳንዱ አስር ቀናት
ውስጥ፣ እኔና ክሪስ ለምን አውሮፓ ሄዳ እንደቆየችና ከሁሉም በላይ ደግሞ
ልትነግረን የነበረው ትልቅ ዜና ምን እንደሆነ ለመገመት ለሰአታት እናወራ
ነበር።
አስሩን ቀናት እንደ ሌላ ቅጣት አሰብነው ቅጣትም ነበረ: እዚህ አንድ ቤት
ውስጥ ሆነን ልክ ጣሪያው ስር ያለው ክፍል ያለን አይጦች እንደሆንን ሁሉ
ችላ ልትለንና ልትዘጋን ችላለች:
ስለዚህ ያን ያህል ቆይታ ስትመጣ እኔና ክሪስ በደንብ ስለተቀጣን የጥላቻ
ወይም የመውጣት ጥያቄያችንን ከደገምን ተመልሳ ላትመጣ ትችላለች ብለን በጣም በመፍራት ፀጥ ብለን እጣ ፈንታችንን ተቀበልን፡ ተመልሳ ካልመጣች ምን እናደርጋለን? መንትዮቹ ገና ጣሪያው ላይ ሲደርሱ ብርክ ከያዛቸው ከተተለተለ አንሶላ በሰራነው መሰላል ተጠቅመን ማምለጥ የማይታሰብ ነው።
ስለዚህ ለእናታችን ፈገግ አልንላት አንድም የማማረር ቃል አላሰማንም
ለወራት ጠፍታ ስለምታውቅ አስር ቀናት በመቆየት ለምን እንደቀጣችን
አልጠየቅናትም፡ ልትሰጠን የፈቀደችውን ተቀበልን፡ ከአባቷ ጋር ለመሆን
እንደተማረችው አይነት ታዛዥ የማይቃወሙ ቅን ልጆች ሆንን የሚገርመው እንዲህ መሆናችንን መውደዷ ነው: እንደገና የሷ ጣፋጭ አፍቃሪና ሚስጥራዊ “ውዶች” ሆንን።
አሁን በጣም ጥሩ፣ አስደሳች፣ ለእሷ አድናቆት ያለን፣ አክባሪና በእሷ
የምንተማመን መሆኑን ስታውቅ ጊዜውን ቦምቧን ለመጣል መረጠችው።
“ውዶቼ፣ ለእኔ ደስ ይበላችሁ! በጣም ደስ ብሎኛል!” እየሳቀች እጆቿን ደረቷ ላይ አድርጋ በክብ ተሽከረከረች: “ምን እንደተከሰተ ገምቱ ቀጥሉ… ገምቱ!” አለችን።
እኔና ክሪስ ተያየን “አያታችን ሞተ!” አለ። ልቤ ደስ የሚለውን ዜና ስትነግረን
ለመዝለልና ለመቦረቅ በመዘጋጀት በጣም እየደለቀ ነው።
“አይደለም!” አለች በድንገት ደስታዋ በጥቂቱ የደበዘዘ ይመስላል።
“ወደ ሆስፒታል ተወሰደ?” ብዬ ሁለተኛውን ምርጥ ግምት አቀረብኩ።
“አይደለም: አሁን አልጠላውም፧ ስለዚህ እናንተ ጋ መጥቼ በሞቱ መደሰቴን ልነግራችሁ አልችልም:”
“ታዲያ ለምን መልካም ዜናውን ራስሽ አትነግሪንም? ስለ ህይወትሽ ብዙም
ስለማናውቅም መገመት አልቻልንም” አልኳት።
ማለት የፈለግኩትን ችላ ብላ ቀጠለች፤ “ለረጅም ጊዜ የጠፋሁበትን ለመግለፅ አስቸጋሪ ሆኖብኝ የነበረው ምክንያት ባርት ዊንስሎ የተባለ ሰው ማግባቴ ነው። ጠበቃና በጣም ጥሩ ሰው ነው። ትወዱታላችሁ። እሱም ሁላችሁንም ይወዳችኋል። ጥቁር ፀጉር ያለው፣ በጣም መልከመልካም፣ ረጅምና የሚያምር ሰውነት ያለው ነው። ክሪስቶፈር፣ ልክ እንዳንተ የበረዶ ሸርታቴ ይወዳል፧ ቴኒስ ይጫወታል፤ ልክ እንዳንተ ጎበዝ ነው” ይህንን ስትናገር ወደ ክሪስ
እየተመለከተች ነበር።
በጣም ደስ የሚል ሰው ነው ሁሉም ይወዱታል። አባቴም ሳይቀር ይወደዋል
ወደ አውሮፓ የሄድኩት ለጫጉላ ሽርሽር ነበር። ያመጣሁላችሁ ስጦታዎች
ከእንግሊዝ፣ ከፈረንሳይ፣ ከስፔንና ከጣልያን የተገዙ ናቸው:” እኔና ክሪስ
በፀጥታ ተቀምጠን፡ ስለ አዲሱ ባሏ የምታወራውን እየሰማን ነበር።
እኔና ክሪስ ከገና በአል ግብዣ ምሽት ጀምሮ ብዙ ጊዜ ጥርጣሬዎቻችንን
አውርተናል: ልጆች ብንሆንም፣ እንደ እናታችን ያለች ወንዶች የምትፈልግ
ቆንጆ ወጣት ሴት ለረጅም ጊዜ ካለ ባል እንደማትቆይ እናውቅ ነበር። ሰርግ
ሳይደረግ ሁለት አመት ሲያልፍ ግን ያ ትልቅ ፂም ያለው መልከመልካም
ባለ ጥቁር ፀጉር ሰው ለእናታችን ብዙም አስፈላጊ ነው ብለን አላሰብንም
ነበር። በየዋሁ ልባችን እናታችን ለሞተው አባታችን አሁንም ታማኝ እንደሆነች ራሳችንን አሳምነን ነበር። ባለወርቃማ ፀጉር፣ ሰማያዊ አይኖች ያሉት አማልክትን የመሰለ የቅርብ ዝምድና እያላቸው እንኳን እሱን ለማግባት ከምክንያት ባሻገር ላፈቀረችው አባታችን ታማኝ ናት ብለን እናስብ ነበር::
የአባታችንን ቦታ ስለሚወስድ ሌላ ሰው ስትነግረን በጥላቻ የተሞላ ድምፅዋን ላለመስማት በመሞhር አይኖቼን ጨፍኜ ነበር: አሁን የሌላ ሰው ሚስት ናት ሙሉ በሙሉ የተለየ ሰው ሚስት ሆናለች: አሁን አልጋዋ ውስጥ
ይገባል፣ ከእሷ ጋር ይተኛል: እንግዲህ ከዚህ በኋላ ከምናገኛት ያነሰ ጊዜ
ነው የምትመጣው ማለት ነው: አምላኬ፣ እዚህ የምንቆየው ለምን ያህል ጊዜ ይሆን? ለምን ያህል?
ዜናዋና ድምፅዋ በደረቴ አጥንቶች ውስጥ የተያዘችና ልውጣ ልውጣ የምትል ትንሽ የፍርሀት ወፍ ፈጠረ።
“እባካችሁ…” ለመነችን፡ ፈገግታዋና ሳቋ ሀሴትና ደስታዋ እኛ ዜናውን
ባስተናገድንበት ቀፋፊና የተበላሽ አየር ላይ ለመቆየት እየታገሉ ነው::
“ለመረዳት ሞክሩና ለእኔ ደስ ይበላችሁ አባታችሁን እወደው እንደነበር
ታውቃላችሁ ግን እሱ ሞቷል። ከሞተ ረጅም ጊዜው ነው እና የምወደውና
የሚወደኝ ሰው ያስፈልገኛል።”
ክሪስ እንደሚወዳት፣ ሁላችንም እንደምንወዳት ለመናገር አፉን ከፈተ። ነገር
ግን ይህ ከልጆቿ የምታገኘው ፍቅር፣ እሷ የምታወራው አይነት ፍቅር
እንዳልሆነ ስለገባው ከንፈሮቹን ገጠመ እኔ ከአሁን በኋላ አልወዳትም።
ከዚህ በኋላ ትንሽ የመውደድ ስሜትም ለእሷ እንደሚኖረኝ እንኳን እርግጠኛ አይደለሁም: ግን መንትዮቹ በሁኔታዬ እንዳይደነግጡ መሳቅና ማስመሰል እንዲሁም ከአንገት በላይ መሆን እችላለሁ፡ “አዎ እማዬ፣ ለአንቺ ደስ ብሎኛል እንደገና የሚወድሽ ሰው ማግኘትሽ ጥሩ ነው።”
“ለረጅም ጊዜ ይወደኝ ነበር ካቲ፣” ተበረታታችና እንደገና በራስ በመተማመን
ፈገግ እያለች ቀጠለች “ወንደላጤ ሆኖ ለመቆየት ወስኖ ስለነበር ሚስት
እንደሚያስፈልገው ለማሳመን ቀላል አልነበረም: አያታችሁ ደግሞ በፊት
አባታችሁን በማግባት ለሰራሁት ኃጢአት ቅጣት እንዲሆን ሁለተኛ ጊዜ
እንዳገባ አልፈለገም ነበር። ግን ባርትን ይወደዋል፤ ብዙ ስለምነው ቆይቼ
በመጨረሻ እሺ አለኝ ባርትን ማግባትና ሀብቱንም መውረስ እንድችል
ፈቀደ” ንግግሯን ቆም አደረገችና የታችኛውን ከንፈሯን መብላት ጀመረች።
እንደገና ደግሞ በጭንቀት ተዋጠች ቀለበት ያጠለቀችበት ጣቷ ወደ ጉሮሮዋ ሄደና አንገቷ ላይ ያንጠለጠለችውን ጌጥ በጭንቀት ያፍተለትል ጀመር።“በእርግጥ አባታችሁን የምወደውን ያህል ባርትን አልወደውም” አለች።
የበራው ፊቷ አሁን ያላት ፍቅር በፊት ከምታውቀው እጅግ የበለጠ እንደሆነ
እያጋለጣት ነበር በረጅም ተነፈስኩ: ምስኪን አባቴ!
“ያመጣሽልን ስጦታዎች... ሁሉም ከአውሮፓ፣ ወይም ከእንግሊዝ ደሴቶች
አይደሉም: የስኳር ከረሜላው የመጣው ከቬርሞንት ነው: ቬርሞንትም ሄደሽ ነበር? እሱም ከዚያ ነው የመጣው?”
ልክ ቬርሞንት ብዙ ነገር የሰጣት ይመስል በደስታ ሳቀች። “አይ፣ እሱ የመጣው ከቬርሞንት አይደለም ካቲ፤ ግን እዚያ የምትኖር እህት አለችው ከአውሮፓ ከመጣን በኋላ በሳምንቱ መጨረሻ ልንጠይቃት ሄደን ነበር የስኳር ከረሜላ
ምን ያህል እንደምትወጂ ስለማውቅ ከዛ ነው ያመጣሁልሽ። ደቡብ የሚኖሩ ሌሎች ሁለት እህቶችም አሉት: ደቡብ ካሮላይና ውስጥ ካለች ግሪንግሌና ግሪንግሌና ወይም እንደዚያ አይነት ስም ካላት ከተማ ነው የመጣው: ግን በኒው ኢንግላንድ ብዙ ቆይቷል: የተመረቀው ከሀርቫርድ የህግ ትምህርት
፡
፡
#ክፍል_ሰላሳ_አንድ
፡
፡
#ትርጉም_ሀኒም_ኤልያስ
የእናታችን ድንገተኛ ዜና
እናታችን እንደገና ልታየን ከመምጣቷ በፊት ባለፉት በእያንዳንዱ አስር ቀናት
ውስጥ፣ እኔና ክሪስ ለምን አውሮፓ ሄዳ እንደቆየችና ከሁሉም በላይ ደግሞ
ልትነግረን የነበረው ትልቅ ዜና ምን እንደሆነ ለመገመት ለሰአታት እናወራ
ነበር።
አስሩን ቀናት እንደ ሌላ ቅጣት አሰብነው ቅጣትም ነበረ: እዚህ አንድ ቤት
ውስጥ ሆነን ልክ ጣሪያው ስር ያለው ክፍል ያለን አይጦች እንደሆንን ሁሉ
ችላ ልትለንና ልትዘጋን ችላለች:
ስለዚህ ያን ያህል ቆይታ ስትመጣ እኔና ክሪስ በደንብ ስለተቀጣን የጥላቻ
ወይም የመውጣት ጥያቄያችንን ከደገምን ተመልሳ ላትመጣ ትችላለች ብለን በጣም በመፍራት ፀጥ ብለን እጣ ፈንታችንን ተቀበልን፡ ተመልሳ ካልመጣች ምን እናደርጋለን? መንትዮቹ ገና ጣሪያው ላይ ሲደርሱ ብርክ ከያዛቸው ከተተለተለ አንሶላ በሰራነው መሰላል ተጠቅመን ማምለጥ የማይታሰብ ነው።
ስለዚህ ለእናታችን ፈገግ አልንላት አንድም የማማረር ቃል አላሰማንም
ለወራት ጠፍታ ስለምታውቅ አስር ቀናት በመቆየት ለምን እንደቀጣችን
አልጠየቅናትም፡ ልትሰጠን የፈቀደችውን ተቀበልን፡ ከአባቷ ጋር ለመሆን
እንደተማረችው አይነት ታዛዥ የማይቃወሙ ቅን ልጆች ሆንን የሚገርመው እንዲህ መሆናችንን መውደዷ ነው: እንደገና የሷ ጣፋጭ አፍቃሪና ሚስጥራዊ “ውዶች” ሆንን።
አሁን በጣም ጥሩ፣ አስደሳች፣ ለእሷ አድናቆት ያለን፣ አክባሪና በእሷ
የምንተማመን መሆኑን ስታውቅ ጊዜውን ቦምቧን ለመጣል መረጠችው።
“ውዶቼ፣ ለእኔ ደስ ይበላችሁ! በጣም ደስ ብሎኛል!” እየሳቀች እጆቿን ደረቷ ላይ አድርጋ በክብ ተሽከረከረች: “ምን እንደተከሰተ ገምቱ ቀጥሉ… ገምቱ!” አለችን።
እኔና ክሪስ ተያየን “አያታችን ሞተ!” አለ። ልቤ ደስ የሚለውን ዜና ስትነግረን
ለመዝለልና ለመቦረቅ በመዘጋጀት በጣም እየደለቀ ነው።
“አይደለም!” አለች በድንገት ደስታዋ በጥቂቱ የደበዘዘ ይመስላል።
“ወደ ሆስፒታል ተወሰደ?” ብዬ ሁለተኛውን ምርጥ ግምት አቀረብኩ።
“አይደለም: አሁን አልጠላውም፧ ስለዚህ እናንተ ጋ መጥቼ በሞቱ መደሰቴን ልነግራችሁ አልችልም:”
“ታዲያ ለምን መልካም ዜናውን ራስሽ አትነግሪንም? ስለ ህይወትሽ ብዙም
ስለማናውቅም መገመት አልቻልንም” አልኳት።
ማለት የፈለግኩትን ችላ ብላ ቀጠለች፤ “ለረጅም ጊዜ የጠፋሁበትን ለመግለፅ አስቸጋሪ ሆኖብኝ የነበረው ምክንያት ባርት ዊንስሎ የተባለ ሰው ማግባቴ ነው። ጠበቃና በጣም ጥሩ ሰው ነው። ትወዱታላችሁ። እሱም ሁላችሁንም ይወዳችኋል። ጥቁር ፀጉር ያለው፣ በጣም መልከመልካም፣ ረጅምና የሚያምር ሰውነት ያለው ነው። ክሪስቶፈር፣ ልክ እንዳንተ የበረዶ ሸርታቴ ይወዳል፧ ቴኒስ ይጫወታል፤ ልክ እንዳንተ ጎበዝ ነው” ይህንን ስትናገር ወደ ክሪስ
እየተመለከተች ነበር።
በጣም ደስ የሚል ሰው ነው ሁሉም ይወዱታል። አባቴም ሳይቀር ይወደዋል
ወደ አውሮፓ የሄድኩት ለጫጉላ ሽርሽር ነበር። ያመጣሁላችሁ ስጦታዎች
ከእንግሊዝ፣ ከፈረንሳይ፣ ከስፔንና ከጣልያን የተገዙ ናቸው:” እኔና ክሪስ
በፀጥታ ተቀምጠን፡ ስለ አዲሱ ባሏ የምታወራውን እየሰማን ነበር።
እኔና ክሪስ ከገና በአል ግብዣ ምሽት ጀምሮ ብዙ ጊዜ ጥርጣሬዎቻችንን
አውርተናል: ልጆች ብንሆንም፣ እንደ እናታችን ያለች ወንዶች የምትፈልግ
ቆንጆ ወጣት ሴት ለረጅም ጊዜ ካለ ባል እንደማትቆይ እናውቅ ነበር። ሰርግ
ሳይደረግ ሁለት አመት ሲያልፍ ግን ያ ትልቅ ፂም ያለው መልከመልካም
ባለ ጥቁር ፀጉር ሰው ለእናታችን ብዙም አስፈላጊ ነው ብለን አላሰብንም
ነበር። በየዋሁ ልባችን እናታችን ለሞተው አባታችን አሁንም ታማኝ እንደሆነች ራሳችንን አሳምነን ነበር። ባለወርቃማ ፀጉር፣ ሰማያዊ አይኖች ያሉት አማልክትን የመሰለ የቅርብ ዝምድና እያላቸው እንኳን እሱን ለማግባት ከምክንያት ባሻገር ላፈቀረችው አባታችን ታማኝ ናት ብለን እናስብ ነበር::
የአባታችንን ቦታ ስለሚወስድ ሌላ ሰው ስትነግረን በጥላቻ የተሞላ ድምፅዋን ላለመስማት በመሞhር አይኖቼን ጨፍኜ ነበር: አሁን የሌላ ሰው ሚስት ናት ሙሉ በሙሉ የተለየ ሰው ሚስት ሆናለች: አሁን አልጋዋ ውስጥ
ይገባል፣ ከእሷ ጋር ይተኛል: እንግዲህ ከዚህ በኋላ ከምናገኛት ያነሰ ጊዜ
ነው የምትመጣው ማለት ነው: አምላኬ፣ እዚህ የምንቆየው ለምን ያህል ጊዜ ይሆን? ለምን ያህል?
ዜናዋና ድምፅዋ በደረቴ አጥንቶች ውስጥ የተያዘችና ልውጣ ልውጣ የምትል ትንሽ የፍርሀት ወፍ ፈጠረ።
“እባካችሁ…” ለመነችን፡ ፈገግታዋና ሳቋ ሀሴትና ደስታዋ እኛ ዜናውን
ባስተናገድንበት ቀፋፊና የተበላሽ አየር ላይ ለመቆየት እየታገሉ ነው::
“ለመረዳት ሞክሩና ለእኔ ደስ ይበላችሁ አባታችሁን እወደው እንደነበር
ታውቃላችሁ ግን እሱ ሞቷል። ከሞተ ረጅም ጊዜው ነው እና የምወደውና
የሚወደኝ ሰው ያስፈልገኛል።”
ክሪስ እንደሚወዳት፣ ሁላችንም እንደምንወዳት ለመናገር አፉን ከፈተ። ነገር
ግን ይህ ከልጆቿ የምታገኘው ፍቅር፣ እሷ የምታወራው አይነት ፍቅር
እንዳልሆነ ስለገባው ከንፈሮቹን ገጠመ እኔ ከአሁን በኋላ አልወዳትም።
ከዚህ በኋላ ትንሽ የመውደድ ስሜትም ለእሷ እንደሚኖረኝ እንኳን እርግጠኛ አይደለሁም: ግን መንትዮቹ በሁኔታዬ እንዳይደነግጡ መሳቅና ማስመሰል እንዲሁም ከአንገት በላይ መሆን እችላለሁ፡ “አዎ እማዬ፣ ለአንቺ ደስ ብሎኛል እንደገና የሚወድሽ ሰው ማግኘትሽ ጥሩ ነው።”
“ለረጅም ጊዜ ይወደኝ ነበር ካቲ፣” ተበረታታችና እንደገና በራስ በመተማመን
ፈገግ እያለች ቀጠለች “ወንደላጤ ሆኖ ለመቆየት ወስኖ ስለነበር ሚስት
እንደሚያስፈልገው ለማሳመን ቀላል አልነበረም: አያታችሁ ደግሞ በፊት
አባታችሁን በማግባት ለሰራሁት ኃጢአት ቅጣት እንዲሆን ሁለተኛ ጊዜ
እንዳገባ አልፈለገም ነበር። ግን ባርትን ይወደዋል፤ ብዙ ስለምነው ቆይቼ
በመጨረሻ እሺ አለኝ ባርትን ማግባትና ሀብቱንም መውረስ እንድችል
ፈቀደ” ንግግሯን ቆም አደረገችና የታችኛውን ከንፈሯን መብላት ጀመረች።
እንደገና ደግሞ በጭንቀት ተዋጠች ቀለበት ያጠለቀችበት ጣቷ ወደ ጉሮሮዋ ሄደና አንገቷ ላይ ያንጠለጠለችውን ጌጥ በጭንቀት ያፍተለትል ጀመር።“በእርግጥ አባታችሁን የምወደውን ያህል ባርትን አልወደውም” አለች።
የበራው ፊቷ አሁን ያላት ፍቅር በፊት ከምታውቀው እጅግ የበለጠ እንደሆነ
እያጋለጣት ነበር በረጅም ተነፈስኩ: ምስኪን አባቴ!
“ያመጣሽልን ስጦታዎች... ሁሉም ከአውሮፓ፣ ወይም ከእንግሊዝ ደሴቶች
አይደሉም: የስኳር ከረሜላው የመጣው ከቬርሞንት ነው: ቬርሞንትም ሄደሽ ነበር? እሱም ከዚያ ነው የመጣው?”
ልክ ቬርሞንት ብዙ ነገር የሰጣት ይመስል በደስታ ሳቀች። “አይ፣ እሱ የመጣው ከቬርሞንት አይደለም ካቲ፤ ግን እዚያ የምትኖር እህት አለችው ከአውሮፓ ከመጣን በኋላ በሳምንቱ መጨረሻ ልንጠይቃት ሄደን ነበር የስኳር ከረሜላ
ምን ያህል እንደምትወጂ ስለማውቅ ከዛ ነው ያመጣሁልሽ። ደቡብ የሚኖሩ ሌሎች ሁለት እህቶችም አሉት: ደቡብ ካሮላይና ውስጥ ካለች ግሪንግሌና ግሪንግሌና ወይም እንደዚያ አይነት ስም ካላት ከተማ ነው የመጣው: ግን በኒው ኢንግላንድ ብዙ ቆይቷል: የተመረቀው ከሀርቫርድ የህግ ትምህርት
👍39❤3😁2
#የጣሪያ_ስር_አበቦች
፡
፡
#ክፍል_ሰላሳ_ሁለት
፡
፡
#ትርጉም_ሀኒም_ኤልያስ
....ክንዱን ለመንካት እጄን ዘረጋሁ። “ክሪስ” እምባ እያነቀኝ በሹክሹክታ ጠራሁት
“ወንድ መሆንህ እንዲሰማህ ምን እንደሚያስፈልግህ የማውቅ ይመስለኛል።"
አልኩት።
“ኧረ? ምን ማድረግ ትችያለሽ?”
አሁን ወደ እኔ እየተመለከተ አይደለም:: በዚያ ፋንታ ኮርኒስ ላይ እያፈጠጠ ነው ለእሱ ታመምኩ ምን እንዳስከፋው አውቄያለሁ። ሀብቱን ወረስንም አልወረስንም ህልሙን የተወው እኔን መምሰል እንዲችል ብሎ ነው: እኔን
መምሰል ደግሞ ጎምዛዛ፣ መራራ፣ ሁሉን የሚጠላና የተደበቀ ምክንያታቸውን
የሚጠራጠር መሆን ማለት ነው።
ቀስ እያልኩ ፀጉሩን ነካካሁትና “የሚያስፈልግህ አንድ ነገር ነው ፀጉር
መቆረጥ። ፀጉርህ በጣም ረጅምና የሚያምር ነው፡ ወንድነት እንዲሰማህ አጭር ፀጉር ሊኖርህ ይገባል። አሁን ግን ፀጉርህ የኔን ፀጉር ነው የሚመስለው”
እና ማነው የአንቺ ፀጉር ያምራል ያለው? ምናልባት በአንድ ወቅት ከሬንጁ
በፊት የሚያምር ፀጉር ነበረሽ” አለኝ፡
“የእውነት?” ብዙ ጊዜ አይኖቹ ፀጉሬ ከማማር በላይ እንደሆነ ነግረውኛል።
hፊት ለፊቴ ያለውን ፀጉሬን ሊቆርጥ መቀስ ሲያነሳ እየተመለከተኝ የነበረበትን
መንገድ ነግሮኛል። በጣም ሲያመነታ ላየው ህመም የማይሰማውን ፀጉር
ሳይሆን ጣቶች የሚቆርጥ ነበር የሚመስለው ከዚያ አንድ ቀን ጣሪያው
ስር ያለው ክፍል ውስጥ ፀሀይ ላይ ተቀምጦ የተቆረጠውን ጸጉሬን በእጆቹ ይዞ ሲያሸተው፣ በጉንጮቹ ሲዳስሰውና ወደ ከንፈሮቹ ሲያስጠጋቸው
አይቼዋለሁ ከዚያ ደግሞ ትራሱ ስር ለማስቀመጥ ካርቶን ውስጥ ሲደብቀው
ተመልክቻለሁ፡
ማየቴን እንዳያውቅ ሳቄን መደበቅ ቀላል አልነበረም: “ኦ ክሪስቶፈር… በጣም ውድ ሰማያዊ አይኖች አሉህ፤ ከዚህ ቦታ ነፃ ስንሆንና ወደ አለም
ስንመለስ አንተን ለሚያፈቅሩ ሴቶች ሁሉ በጣም አዝንላቸዋለሁ። በተለይ ደግሞ ከመልከመልካም ባሏ ጋር የፍቅር ግንኙነት የሚፈልጉ
በሽተኞች ያሉት ዶክተር ባል ላላት ሚስትህ አዝናለሁ። እና እኔ ሚስትህ ብሆን ከጋብቻህ ውጪ አንድ የፍቅር ግንኙነት ቢኖርህ እገድልሀለሁ! በጣም ስለማፈቅርህ እቀናለሁ ምናልባት በሰላሳ አምስት አመትህ ከህክምና
እንድትወጣ አደርግሀለሁ” ያልኩትን ሁሉ ችላ ብሎ “አንድ ጊዜም ፀጉርሽ
ያምራል ብዬ ተናግሬ አላውቅም” አለ።
በቀስታ መላጨት የሚያስፈልጋቸው ፀጉሮች ያሉበትን ጉንጩን ዳሰስ
አደረግኩት፡
ከዚያ “ባለህበት ቁጭ በል! ታውቃለህ ለረጅም ጊዜ ፀጉርህን ቆርጬህ
አላውቅም… መቀስ ላምጣ” አልኩት፡ ግን የፀጉራችን ምንም መምሰል
የህይወት ዘይቤያችን ለመለወጥ አስፈላጊ ካልሆነ የክሪስንና የኮሪን ፀጉር
ለመቁረጥ ለምን እቸገራለሁ? ከፊት ያለው ፀጉሬ ብቻ በዚያች ከብረት
የተሰራች የምትመስል ክፉ አሮጊት መሸነፋችንን ለማሳየት ከመቆረጡ
በስተቀር፤ እዚህ ከመጣን እኔና ኬሪ ፀጉራችን ጫፍ ጫፉ እንኳን ተከርክሞ
አያውቅም።
መቀሱን ላመጣ ስሄድ የእኛ ፀጉር በጣም ሲያድግ አንዳቸውም አረንጓዴ
ተክሎቻችን አለማደጋቸው እንግዳ ነገር መሆኑን አሰብኩ።
ክሪስ ወለሉ ላይ ተቀመጠ ከኋላው ተንበረከክኩ ፀጉሩ ከትከሻው በታች
የወረደ ቢሆንም ብዙ እንዲቆረጥ አልፈለገም፡ “ቀስ እያልሽ ቁረጪ" ሲል
አዘዘኝ “በአንዴ ብዙ አታሳጥሪው ድንገት በአንድ ዝናባማ ከሰአት በኋላ
ጣሪያው ስር ያለው ክፍል ውስጥ ወንድነት ቢሰማኝ አደገኛ ሊሆን ይችላል
ብሎ ቀለደና ፈገግ አለ። ከዚያ ድርድር ያሉ ነጫጭ ጥርሶቹን እያሳየ ሳቀ:
መምሰል የሚገባውን ያህል አሳምረዋለሁ።
ዙሪያውን እየዞርኩ ፀጉሩን ስቆርጥና ስከረክም እንዴት እንደምወደው እያሰብኩ ነበር፡ ያለማቋረጥ ወደኋላ ሄድ እያልኩ ፀጉሩ በትክክል መቆረጡን አረጋግጣለሁ ጭንቅላቱ የተጣመመ እንዲመስል አልፈለግኩም።
ፀጉር አስተካካዮች ሲያደርጉ እንዳየሁት፣ ፀጉሩን በማበጠሪያ ይዤ በጥንቃቄ ቆረጥኩት። ምን መምሰል እንዳለበት እንደምፈልግ አእምሮዬ ውስጥ አሉ
የሆነ የማደንቀውን ሰው
ስጨርስ ትከሻው ላይ የወደቁትን የተቆራረጡ ፀጉሮች አራገፍኩና ወደኋላ
ራቅ ብዬ በማየት ቆንጆ እንዳደረግኩት አረጋገጥኩ።
“ያው!” አልኩ በድል አድራጊነት ከባድ ጥበብ የሚመስለውን ስራ ባልተጠበቀ ጉብዝና በማጠናቀቄ ደስ ብሎኛል። “የተለየህ መልከመልካም ብቻ ሳይሆን በጣም ወንዳወንድ ሆነሀል! ሁልጊዜም ወንዳወንድ ነበርክ። አለማወቅህ
ያሳዝናል” አልኩት።
ብራማ ጀርባ ያለው የስሜ የመጀመሪያ ፊደል የተቀረፀበትን መስተዋት እጁ ላይ አስቀመጥኩለት፡ ይህ መስተዋት እናታችን ለመጨረሻ ልደቴ ከሰጠችኝ
ስጦታዎች አንዱ ነበር። ብሩሽ፣ ማበጠሪያና መስተዋት አያትየው ሶስቱ
ውድና ኩራት የሚያመጡ እቃዎች እንዳሉኝ እንዳታውቅ የሚቀመጡት
ተደብቀው ነው።
ክሪስ በመስተዋቱ ላይ ለረጅም ደቂቃዎች አፈጠጠ ለቅፅበት ደስ ያላለውና ያልወሰነ ሲመስለኝ ልቤ ደነገጠ፡ ከዚያ ቀስ በቀስ ደማቅ ፈገግታ ፊቱን አበራው።
አምላኬ! ልዑል አስመሰልሽኝ! በመጀመሪያ አልወደድኩትም ነበር። አሁን ግን ሳየው የፀጉሬን ሁኔታ ስለቀየርሽው ፊቴን አሳምሮታል። አመሰግናለሁ
ካተሪን ፀጉር መቁረጥ ላይ እንደዚህ አይነት ችሎታ እንዳለሽ አላውቅም ነበር" አለኝ።
አንተ የማታውቃቸው ብዙ ችሎታዎች አሉኝ፡”
"እኔም መጠርጠር ጀምሬያለሁ”
“እና ልዑሉ መልከመልካም፣ ወንዳወንድና ባለወርቃማ ፀጉሩን ወንድሜን በመምሰሉ እድለኛ ነው” ስል ቀለድኩ። የጥበብ ስራዬን አለማድነቅ
አልቻልኩም። ኦ አምላኬ! አንድ ቀን ልብ የሚሰብር ቆንጆ ነው የሚሆነው።
አሁንም መስተዋቱን እንደያዘ ነበር ከዚያ ቀስ ብሎ ወደጎን አስቀመጠውና
ምን ሊያደርግ እንደሆነ ከማወቄ በፊት እንደ ድመት እመር ብሎ ተነሳ ታገለኝ፤ ወደ ወለሉ እያስጎነበሰኝ መቀሱን ያዘ! ከእጄ ላይ መነጨቀኝና ፀጉሬን በእጁ ያዘ አሁን የኔ ቆንጆ እስቲ እኔም እንዳንቺ ማድረግ እችል እንደሆነ እንመልከት:"
በፍርሀት ገፈተርኩት
ስገፈትረው በጀርባው ወደቀ ከዚያ ተነሳ። ማንም የጸጉሬን ጫፉን እንኳን
አይነካም! ምናልባት አሁን በጣም ስስ ሆኖ ይሆናል። ግን ያለኝ ፀጉር ይኸው
ነው! አሁንም ከብዙ ሴቶች ፀጉር በተሻለ የሚያምር ነው እንዳይዘኝ ሮጥኩ።
ከመማሪያው ክፍል ወጥቼ ሻንጣዎቹን እየዘለልኩ በትልልቆቹ ጠረጴዛዎች
ስር እየሾለኩ ሮጥኩ። እሱም እያሯሯጠኝ ነው፡
ምንም ያህል በፍጥነት ብሮጥና በፍጥነት ብሽሎከለክም ላመልጠው
አልቻልኩም፡ በትከሻዬ በኩል ዞር ብዬ ስመለከተው ፊቱን እንኳን መለየት
አልቻልኩም ያ ደግሞ የበለጠ አስፈራኝ፡ ከጀርባዬ የተበተነውን ረጅሙን
8ጉሬን ለመያዝ ጥረት አደረገ። ፀጉሬን ቆርጦ ለመጣል የወሰነ ይመስላል
አሁን ጠልቶኛል ማለት ነው? ፀጉሬን ለማትረፍ አንድ ቀን ሙሉ በትጋት እንዳልለፋ ሁሉ… አሁን ደስ ስላለው ብቻ ሊቆርጠው ነው?
ተመልሼ ወደ መማሪያው ክፍል ሮጥኩ። ከዚያ ውስጥ ገብቼ በሩን እቆልፍና ወደ ራሱ ተመልሶ ሲረጋጋና ስህተት መሆኑ ሲገባው ተመልሼ እወጣለሁ::
ምናልባት ያሰብኩት ገብቶት ሳይሆን አይቀርም ረጃጅም ቅልጥሞቹ ላይ ፍጥነት ጨመረና ደርሶብኝ ረጅሙን ፀጉሬን ሲይዘውና ወደፊት ስወድቅ ጮህኩ!
እኔ ብቻ ሳልሆን እሱም ወደቀ ቀጥታ ላዬ ላይ! ጎኔ ላይ ድንገተኛ ህመም
ሲሰማኝ እንደገና በፍርሀት ሳይሆን በድንጋጤ ጮህኩ።
እላዬ ላይ ነው። በእጆቼ መሬቱን ተደግፎ ፊቴን አተኩሮ ይመለከታል። ፊቱ
ነጭ ሆኖ የፈራ ይመስላል። “ተጎዳሽ? ወይኔ አምላኬ! ካቲ ደህና ነሽ?” አለኝ።
፡
፡
#ክፍል_ሰላሳ_ሁለት
፡
፡
#ትርጉም_ሀኒም_ኤልያስ
....ክንዱን ለመንካት እጄን ዘረጋሁ። “ክሪስ” እምባ እያነቀኝ በሹክሹክታ ጠራሁት
“ወንድ መሆንህ እንዲሰማህ ምን እንደሚያስፈልግህ የማውቅ ይመስለኛል።"
አልኩት።
“ኧረ? ምን ማድረግ ትችያለሽ?”
አሁን ወደ እኔ እየተመለከተ አይደለም:: በዚያ ፋንታ ኮርኒስ ላይ እያፈጠጠ ነው ለእሱ ታመምኩ ምን እንዳስከፋው አውቄያለሁ። ሀብቱን ወረስንም አልወረስንም ህልሙን የተወው እኔን መምሰል እንዲችል ብሎ ነው: እኔን
መምሰል ደግሞ ጎምዛዛ፣ መራራ፣ ሁሉን የሚጠላና የተደበቀ ምክንያታቸውን
የሚጠራጠር መሆን ማለት ነው።
ቀስ እያልኩ ፀጉሩን ነካካሁትና “የሚያስፈልግህ አንድ ነገር ነው ፀጉር
መቆረጥ። ፀጉርህ በጣም ረጅምና የሚያምር ነው፡ ወንድነት እንዲሰማህ አጭር ፀጉር ሊኖርህ ይገባል። አሁን ግን ፀጉርህ የኔን ፀጉር ነው የሚመስለው”
እና ማነው የአንቺ ፀጉር ያምራል ያለው? ምናልባት በአንድ ወቅት ከሬንጁ
በፊት የሚያምር ፀጉር ነበረሽ” አለኝ፡
“የእውነት?” ብዙ ጊዜ አይኖቹ ፀጉሬ ከማማር በላይ እንደሆነ ነግረውኛል።
hፊት ለፊቴ ያለውን ፀጉሬን ሊቆርጥ መቀስ ሲያነሳ እየተመለከተኝ የነበረበትን
መንገድ ነግሮኛል። በጣም ሲያመነታ ላየው ህመም የማይሰማውን ፀጉር
ሳይሆን ጣቶች የሚቆርጥ ነበር የሚመስለው ከዚያ አንድ ቀን ጣሪያው
ስር ያለው ክፍል ውስጥ ፀሀይ ላይ ተቀምጦ የተቆረጠውን ጸጉሬን በእጆቹ ይዞ ሲያሸተው፣ በጉንጮቹ ሲዳስሰውና ወደ ከንፈሮቹ ሲያስጠጋቸው
አይቼዋለሁ ከዚያ ደግሞ ትራሱ ስር ለማስቀመጥ ካርቶን ውስጥ ሲደብቀው
ተመልክቻለሁ፡
ማየቴን እንዳያውቅ ሳቄን መደበቅ ቀላል አልነበረም: “ኦ ክሪስቶፈር… በጣም ውድ ሰማያዊ አይኖች አሉህ፤ ከዚህ ቦታ ነፃ ስንሆንና ወደ አለም
ስንመለስ አንተን ለሚያፈቅሩ ሴቶች ሁሉ በጣም አዝንላቸዋለሁ። በተለይ ደግሞ ከመልከመልካም ባሏ ጋር የፍቅር ግንኙነት የሚፈልጉ
በሽተኞች ያሉት ዶክተር ባል ላላት ሚስትህ አዝናለሁ። እና እኔ ሚስትህ ብሆን ከጋብቻህ ውጪ አንድ የፍቅር ግንኙነት ቢኖርህ እገድልሀለሁ! በጣም ስለማፈቅርህ እቀናለሁ ምናልባት በሰላሳ አምስት አመትህ ከህክምና
እንድትወጣ አደርግሀለሁ” ያልኩትን ሁሉ ችላ ብሎ “አንድ ጊዜም ፀጉርሽ
ያምራል ብዬ ተናግሬ አላውቅም” አለ።
በቀስታ መላጨት የሚያስፈልጋቸው ፀጉሮች ያሉበትን ጉንጩን ዳሰስ
አደረግኩት፡
ከዚያ “ባለህበት ቁጭ በል! ታውቃለህ ለረጅም ጊዜ ፀጉርህን ቆርጬህ
አላውቅም… መቀስ ላምጣ” አልኩት፡ ግን የፀጉራችን ምንም መምሰል
የህይወት ዘይቤያችን ለመለወጥ አስፈላጊ ካልሆነ የክሪስንና የኮሪን ፀጉር
ለመቁረጥ ለምን እቸገራለሁ? ከፊት ያለው ፀጉሬ ብቻ በዚያች ከብረት
የተሰራች የምትመስል ክፉ አሮጊት መሸነፋችንን ለማሳየት ከመቆረጡ
በስተቀር፤ እዚህ ከመጣን እኔና ኬሪ ፀጉራችን ጫፍ ጫፉ እንኳን ተከርክሞ
አያውቅም።
መቀሱን ላመጣ ስሄድ የእኛ ፀጉር በጣም ሲያድግ አንዳቸውም አረንጓዴ
ተክሎቻችን አለማደጋቸው እንግዳ ነገር መሆኑን አሰብኩ።
ክሪስ ወለሉ ላይ ተቀመጠ ከኋላው ተንበረከክኩ ፀጉሩ ከትከሻው በታች
የወረደ ቢሆንም ብዙ እንዲቆረጥ አልፈለገም፡ “ቀስ እያልሽ ቁረጪ" ሲል
አዘዘኝ “በአንዴ ብዙ አታሳጥሪው ድንገት በአንድ ዝናባማ ከሰአት በኋላ
ጣሪያው ስር ያለው ክፍል ውስጥ ወንድነት ቢሰማኝ አደገኛ ሊሆን ይችላል
ብሎ ቀለደና ፈገግ አለ። ከዚያ ድርድር ያሉ ነጫጭ ጥርሶቹን እያሳየ ሳቀ:
መምሰል የሚገባውን ያህል አሳምረዋለሁ።
ዙሪያውን እየዞርኩ ፀጉሩን ስቆርጥና ስከረክም እንዴት እንደምወደው እያሰብኩ ነበር፡ ያለማቋረጥ ወደኋላ ሄድ እያልኩ ፀጉሩ በትክክል መቆረጡን አረጋግጣለሁ ጭንቅላቱ የተጣመመ እንዲመስል አልፈለግኩም።
ፀጉር አስተካካዮች ሲያደርጉ እንዳየሁት፣ ፀጉሩን በማበጠሪያ ይዤ በጥንቃቄ ቆረጥኩት። ምን መምሰል እንዳለበት እንደምፈልግ አእምሮዬ ውስጥ አሉ
የሆነ የማደንቀውን ሰው
ስጨርስ ትከሻው ላይ የወደቁትን የተቆራረጡ ፀጉሮች አራገፍኩና ወደኋላ
ራቅ ብዬ በማየት ቆንጆ እንዳደረግኩት አረጋገጥኩ።
“ያው!” አልኩ በድል አድራጊነት ከባድ ጥበብ የሚመስለውን ስራ ባልተጠበቀ ጉብዝና በማጠናቀቄ ደስ ብሎኛል። “የተለየህ መልከመልካም ብቻ ሳይሆን በጣም ወንዳወንድ ሆነሀል! ሁልጊዜም ወንዳወንድ ነበርክ። አለማወቅህ
ያሳዝናል” አልኩት።
ብራማ ጀርባ ያለው የስሜ የመጀመሪያ ፊደል የተቀረፀበትን መስተዋት እጁ ላይ አስቀመጥኩለት፡ ይህ መስተዋት እናታችን ለመጨረሻ ልደቴ ከሰጠችኝ
ስጦታዎች አንዱ ነበር። ብሩሽ፣ ማበጠሪያና መስተዋት አያትየው ሶስቱ
ውድና ኩራት የሚያመጡ እቃዎች እንዳሉኝ እንዳታውቅ የሚቀመጡት
ተደብቀው ነው።
ክሪስ በመስተዋቱ ላይ ለረጅም ደቂቃዎች አፈጠጠ ለቅፅበት ደስ ያላለውና ያልወሰነ ሲመስለኝ ልቤ ደነገጠ፡ ከዚያ ቀስ በቀስ ደማቅ ፈገግታ ፊቱን አበራው።
አምላኬ! ልዑል አስመሰልሽኝ! በመጀመሪያ አልወደድኩትም ነበር። አሁን ግን ሳየው የፀጉሬን ሁኔታ ስለቀየርሽው ፊቴን አሳምሮታል። አመሰግናለሁ
ካተሪን ፀጉር መቁረጥ ላይ እንደዚህ አይነት ችሎታ እንዳለሽ አላውቅም ነበር" አለኝ።
አንተ የማታውቃቸው ብዙ ችሎታዎች አሉኝ፡”
"እኔም መጠርጠር ጀምሬያለሁ”
“እና ልዑሉ መልከመልካም፣ ወንዳወንድና ባለወርቃማ ፀጉሩን ወንድሜን በመምሰሉ እድለኛ ነው” ስል ቀለድኩ። የጥበብ ስራዬን አለማድነቅ
አልቻልኩም። ኦ አምላኬ! አንድ ቀን ልብ የሚሰብር ቆንጆ ነው የሚሆነው።
አሁንም መስተዋቱን እንደያዘ ነበር ከዚያ ቀስ ብሎ ወደጎን አስቀመጠውና
ምን ሊያደርግ እንደሆነ ከማወቄ በፊት እንደ ድመት እመር ብሎ ተነሳ ታገለኝ፤ ወደ ወለሉ እያስጎነበሰኝ መቀሱን ያዘ! ከእጄ ላይ መነጨቀኝና ፀጉሬን በእጁ ያዘ አሁን የኔ ቆንጆ እስቲ እኔም እንዳንቺ ማድረግ እችል እንደሆነ እንመልከት:"
በፍርሀት ገፈተርኩት
ስገፈትረው በጀርባው ወደቀ ከዚያ ተነሳ። ማንም የጸጉሬን ጫፉን እንኳን
አይነካም! ምናልባት አሁን በጣም ስስ ሆኖ ይሆናል። ግን ያለኝ ፀጉር ይኸው
ነው! አሁንም ከብዙ ሴቶች ፀጉር በተሻለ የሚያምር ነው እንዳይዘኝ ሮጥኩ።
ከመማሪያው ክፍል ወጥቼ ሻንጣዎቹን እየዘለልኩ በትልልቆቹ ጠረጴዛዎች
ስር እየሾለኩ ሮጥኩ። እሱም እያሯሯጠኝ ነው፡
ምንም ያህል በፍጥነት ብሮጥና በፍጥነት ብሽሎከለክም ላመልጠው
አልቻልኩም፡ በትከሻዬ በኩል ዞር ብዬ ስመለከተው ፊቱን እንኳን መለየት
አልቻልኩም ያ ደግሞ የበለጠ አስፈራኝ፡ ከጀርባዬ የተበተነውን ረጅሙን
8ጉሬን ለመያዝ ጥረት አደረገ። ፀጉሬን ቆርጦ ለመጣል የወሰነ ይመስላል
አሁን ጠልቶኛል ማለት ነው? ፀጉሬን ለማትረፍ አንድ ቀን ሙሉ በትጋት እንዳልለፋ ሁሉ… አሁን ደስ ስላለው ብቻ ሊቆርጠው ነው?
ተመልሼ ወደ መማሪያው ክፍል ሮጥኩ። ከዚያ ውስጥ ገብቼ በሩን እቆልፍና ወደ ራሱ ተመልሶ ሲረጋጋና ስህተት መሆኑ ሲገባው ተመልሼ እወጣለሁ::
ምናልባት ያሰብኩት ገብቶት ሳይሆን አይቀርም ረጃጅም ቅልጥሞቹ ላይ ፍጥነት ጨመረና ደርሶብኝ ረጅሙን ፀጉሬን ሲይዘውና ወደፊት ስወድቅ ጮህኩ!
እኔ ብቻ ሳልሆን እሱም ወደቀ ቀጥታ ላዬ ላይ! ጎኔ ላይ ድንገተኛ ህመም
ሲሰማኝ እንደገና በፍርሀት ሳይሆን በድንጋጤ ጮህኩ።
እላዬ ላይ ነው። በእጆቼ መሬቱን ተደግፎ ፊቴን አተኩሮ ይመለከታል። ፊቱ
ነጭ ሆኖ የፈራ ይመስላል። “ተጎዳሽ? ወይኔ አምላኬ! ካቲ ደህና ነሽ?” አለኝ።
👍40❤1
#የጣሪያ_ስር_አበቦች
፡
፡
#ክፍል_ሰላሳ_ሶስት
፡
፡
#ትርጉም_ሀኒም_ኤልያስ
...“ተነሽ ልጆቹ ቲቪ ላይ ብዙ ከማፍጠጣቸው የተነሳ አይናቸው ሳይጠፋ
ወደታች እንሂድ” አለኝ...
ስነሳ ስላመመኝ አገዘኝ በክንዶቹ ውስጥ አስጠግቶ ስለያዘኝ ጉንጬ ደረቱ
ላይ ነበር ከእሱ በፍጥነት ቢያላቅቀኝም እኔ ግን ጥብቅ አድርጌ ይዤው
ነበር። “ክሪስ አሁን ያደረግነው ኃጢአት ነው?
እንደገና ጉሮሮውን አፀዳና
“ነው ብለሽ ካሰብሽ ነው:"
ምን አይነት መልስ ነው? የኃጢአት ሀሳብ ካልገባባቸው እነዚያ ወለሉ ላይ ተኝተን በምትሀታዊ ጣቶቹና ከንፈሮቹ ሲነካካኝ የነበረባቸው ጊዜያት እዚህ
አስጠሊታ ቤት ልንኖር ከመጣንበት ጊዜ ጀምሮ አጋጥመውኝ የማያውቁ
ጣፋጭ ጊዜያት ናቸው ምን እንደሚያስብ ለማየት ቀና ብዬ ሳየው አይኖቹ ውስጥ እንግዳ የሆነ አስተያየት ተመለከትኩ፡ እርስ በእርሱ በሚጋጭ አይነት
ደስተኛ፣ ያዘነ፣ ያረጀ፣ ወጣት የሆነ፣ ብልህ፣ ሞኝ ... ይመስል ነበር። ወይም አሁን እንደ ትልቅ ወንድ እየተሰማው ይሆን? እንደዚያ ከሆነ ኃጢአት
ይሁንም አይሁንም ደስ ብሎኛል።
እጅ ለእጅ ተያይዘን ወደ መንትዮቹ ለመሄድ ደረጃውን መውረድ ጀመርን።ኮሪ የሙዚቃ መሳሪያ እየተጫወተና ኬሪ ደግሞ እየዘፈነች ነው:
ከኮሪ አጠገብ ወለሉ ላይ ተቀመጥኩና ጊታሩን ተቀብዬ ለመጫወት ሞከርኩ።
ሁላችንንም አስተምሮናል በጣም የሚወደውን ዘፈን ዘፈንኩለት፡ ስጨርስ
“የኔን ዘፈን አልወደድሽውም ካቲ?” አለኝ።
“በጣም ወድጄዋለሁ ኮሪ ግን በጣም ያሳዝናል።
ለምን ደስ የሚሉ ግጥሞች
አንጨምርበትም?” አልኩት።
“ታውቂያለሽ ካቲ… እናታችን ስለመጫወቻዬ ምንም አላለችም" አለኝ፡
“አላየችውም እኮ ኮሪ።''
“ለምን አላየችውም?”
እንወዳት የነበረች እንግዳ ሴት ከመሆኗ በስተቀር ከአሁን በኋላ እናታችን
ማንና ምን እንደሆነች ባለማወቄ በከባዱ ተነፈስኩ፡ አንዳንዴ የምንወዳቸውን ሰዎች ከእኛ ነጥሎ የሚወስዳቸው ሞት ብቻ አይደለም: አሁን ይህንን አውቄያለሁ።
“እናታችን አዲስ ባል አግኝታለች:” አለ ክሪስ “እና ሰው ፍቅር ሲይዘው ደግሞ ከራሱ ደስታ በስተቀር የሌሎችን ደስታ አያይም"
ኬሪ ሹራቤን አተኩራ እየተመለከተች፣ ካቲ፣ ሹራብሽ ላይ ያለው ምንድነው?” አለችኝ። “ቀለም” አልኩ ያለምንም ማመንታት። “ክሪስ ስዕል
መሳል ሊያስተምረኝ እየሞከረ ነበር። ከዚያ የኔ ስዕል ከእሱ ስዕል ይበልጥ
እንደሚያምር ሲመለከት ቀይ ቀለም የነበረበትን ዕቃ አንስቶ ወደ እኔ ወረወረው"
ትልቁ ወንድሜ አተኩሮ እያየኝ ነበር። “ክሪስ፣ ካቲ ከአንተ የተሻለ መሳል
ትችላለች?”
“እችላለሁ ካለች መቻል አለባት”
“ስዕሉ የታለ?”
“ጣሪያው ስር ያለው ክፍል ውስጥ።”
“ማየት እፈልጋለሁ”
“እኔ ደክሞኛል አንቺ ሂጂና አምጪው ካቲ ራት እስክታዘጋጅ ቲቪ ማየት
እፈልጋለሁ፡" ብሎ አየት አደረገኝ፡፡ “ውድ እህቴ ጨዋ ለመሆን ብለሽ
ተቀምጠን ራት ከመብላታችን በፊት ንፁህ ሹራብ ብትለብሽ ቅር ይልሻል? ስለዛ ቀይ ቀለም ጥፋተኝነት እንዲሰማኝ የሚያደርግ የሆነ ነገር አለ:”
“ደም ይመስላል” አለ ኮሪ። “አጥበሽ ካላስለቀቅሽው እንደ ደም ይሆንብሻል።"
በዚያ ምሽት የማይመች ስሜት ተሰምቶኝ እረፍት የለሽ ሆንኩ ሀሳቤ ክሪስ ጣሪያው ስር ያለው ክፍል ውስጥ ይመለከተኝ ወደነበረበት ሁኔታ
ይመላለሳል።
ለረጅም ጊዜ ስፈልገው የነበረው ሚስጠር ምን እንደሆነ አወቅኩ ያ የሚስጥር ቁልፍ ፍቅርን አካላዊና ወሲባዊ ፍላጎትን የሚገልጥ ነበር። እርቃን
ሰውነቶችን ማየት አይደለም ምክንያቱም ለረጅም ጊዜ ኮሪን ሳጥብ ነበርና።
ክሪስም እርቃኑን ሆኖ አይቼው አውቃለሁ: ነገር ግን እሱና ኮሪ ያላቸው
ነገር እኔና ኬሪ ካለን ነገር የተለየ መሆኑ ምንም አይነት የወሲብ መነሳሳት
ፈጥሮብኝ አያውቅም: እርቃን መሆን አይደለም
አይኖቹ ናቸው: የፍቅር ሚስጥር አይን ውስጥ ነው። አንድ ሰው ሌላኛውን
የሚመለከትበት መንገድ፣ ከንፈሮች ሳይነቃነቁ አይኖች የሚገናኙበትና
የሚያወሩበት መንገድ ነው: የክሪስ አይኖች ከአስር ሺህ ቃላት በላይ ተናግረዋል።
እኔን የነካበት መንገድም አይደለም… ቀስ እያለ በደግነት ማድረጉም አይደለም ሲነካኝ ወደኔ የሚመለከትበት መንገድ ነው እና ለዚያ ነው ማለት ነው አያትየው ሌላኛውን ፆታ መመልከት እንደማይገባ ህግ ያወጣችው:: ያቺ
ጠንቋይ አሮጊት የፍቅርን ሚስጥር ታውቃለች ብሎ ማሰብ ከባድ ነው መቼም ተፈቅራ ልታውቅ አትችልም አይሆንም እሷ ባለ ብረት ልብ፣ ባለ ብረት አጥንት ናት... አይኖቿም ለስላሳ ሆነው አያውቁም:
ከዚያ ርዕሱን በጥልቀት ስመረምር ከአይኖች በላይ ነው: ከአይኖች ኋላ
አእምሮ ውስጥ ነው፧ ሊያስደስትህ የሚፈልግ፣ ደስ የሚያሰኝህ፣ ሀሴት
የሚሰጥህና እንዲረዱህ በምትፈልግበት መንገድ የሚረዳህ፣ ማንም ሳይረዳህ ሲቀር ደግሞ ብቸኝነትህን የሚወስድልህ ነው። ኃጢአት በፍቅር ጉዳይ ምንም አያገባውም
ፊቴን ስመልስ ክሪስም እንደነቃ ተመለከትኩ። በጎኑ ተኝቶ ወደ እኔ
እየተመለከተ ነው። በጣም ደስ የሚል ፈገግታ ነው ያለው።እናታችን በዚያን ቀን ልታየን አልመጣችም: ከዚያ ቀን በፊትም ብቅ አላለችም
እኛ ግን የኮሪን የሙዚቃ መሳሪያ በመጫወትና በመዝፈን ራሳችንን የማስደሰቻ መንገድ አግኝተናል: እናታችን በጣም ግድ የለሽ እየሆነች የመጣች ቢሆንም
በዚያ ምሽት ሁላችንም የተኛነው በተስፋ ተሞልተን ነው፡ ለረጅም ሰዓት የደስታ ዘፈኖች መዝፈናችን፣ ጥቅጥቅ ያለ ጨለማ የወረሰው ጫካ ውስጥ የነበረን ጉዞ እያለቀ መሆኑንና ፀሀይ፣ ፍቅር፣ ሐሴትና ደስታ መታጠፊያው ላይ እየጠበቁን መሆናቸውን እንድናምን አድርጎናል።
በብሩህ ህልሜ ውስጥ የሆነ ጨለማና የሚያስፈራ ነገር ይመጣብኛል።
በየቀኑ ቅርፁ የጭራቅ አይነት ይሆንብኛል። አይኖቼን ስጨፍን አያትየው ሳትታይ መኝታ ክፍላችን ገብታ እንቅልፍ እንደወሰደኝ አስባ ፀጉሬን በሙሉ ስትላጨኝ አያለሁ። እጮሀለሁ አትሰማኝም ማንም አይሰማኝም፡ ከዚያ ትልቅ የሚያንፀባርቅ ቢላዋ ታወጣና ሁለቱንም ጡቶቼን ቆርጣ ክሪስ አፍ ውስጥ ትጨምረዋለች: እና ሌላም ሌላም… ከዚያ እወራጫለሁ። ክሪስን የሚያነቃ የጩኸት ድምፅ አሰማለሁ። መንትዮቹ ልክ ሞቶ እንደተቀበሩ ልጆች ተኝተዋል። ክሪስ እንቅልፉ ሳይለቀው አልጋው ላይ ቁጭ ብሎ እጄን
ለመያዝ እየፈለገ “ሌላ ቅዠት ነው?” ሲል ጠየቀኝ።
አይይ! ... ተራ ቅዠት አይደለም ቀድሞ ማወቅና በተፈጥሮ መረዳት መቻል ነው:: የሆነ መጥፎ ነገር እንደሚፈጠር በአጥን መቅኒ ሳይቀር ተሰምቶኛል።
ድክም ብዬና እየተንቀጠቀጥኩ አያትየው ያደረገችኝን ለክሪስ ነገርኩት። “ያ ብቻ አይደለም መጥታ ልቤን ቆርጣ ያወጣችው እናታችን ነበረች: ሁሉ ነገሯ
በአልማዝ ያብረቀርቅ ነበር” አልኩት
ካቲ ህልም እኮ ምንም ትርጉም የለውም::”
“አለው!”
ሌሎች ህልሞችና ሌሎች ቅዠቶች ለወንድሜ እነግረዋለሁ። ያዳምጠኝና ይስቃል ከዚያ ሌሊቱን ልክ ፊልም ቤት እንዳሉ አይነት ሆኖ ማሳለፍ አሪፍ እንደሆነ ያለውን እምነት ይገልፅልኛል። ግን በፍፁም እንደዛ አልነበረም::ፊልም የሆነ ሰው የፃፈው መሆኑን እያወቅህ ቁጭ ብለህ ትልቁን ስክሪን
ትመለከታለህ እኔ ግን በህልሜ ውስጥ ተሳታፊ ነኝ፡ ህልም ውስጥ
እየተሰማኝ… እየተጎዳሁ እየተሰቃየሁና ይህንን ስል እያዘንኩ ነው አልፎ አልፎም በጣም እየተደሰትኩ ነው።
ክሪስ፣ እሱ ከእኔና ከእንግዳ መንገዶቼ ውስጥ የሌለ ሆኖ ሳለ ይህ ህልም ከሌሎች ይልቅ እሱን ይጎዳው ይመስል ለምን ፀጥ ብሎ እንደ ሀውልት ተቀመጠ? እሱም ህልም አይቶ ይሆን?
፡
፡
#ክፍል_ሰላሳ_ሶስት
፡
፡
#ትርጉም_ሀኒም_ኤልያስ
...“ተነሽ ልጆቹ ቲቪ ላይ ብዙ ከማፍጠጣቸው የተነሳ አይናቸው ሳይጠፋ
ወደታች እንሂድ” አለኝ...
ስነሳ ስላመመኝ አገዘኝ በክንዶቹ ውስጥ አስጠግቶ ስለያዘኝ ጉንጬ ደረቱ
ላይ ነበር ከእሱ በፍጥነት ቢያላቅቀኝም እኔ ግን ጥብቅ አድርጌ ይዤው
ነበር። “ክሪስ አሁን ያደረግነው ኃጢአት ነው?
እንደገና ጉሮሮውን አፀዳና
“ነው ብለሽ ካሰብሽ ነው:"
ምን አይነት መልስ ነው? የኃጢአት ሀሳብ ካልገባባቸው እነዚያ ወለሉ ላይ ተኝተን በምትሀታዊ ጣቶቹና ከንፈሮቹ ሲነካካኝ የነበረባቸው ጊዜያት እዚህ
አስጠሊታ ቤት ልንኖር ከመጣንበት ጊዜ ጀምሮ አጋጥመውኝ የማያውቁ
ጣፋጭ ጊዜያት ናቸው ምን እንደሚያስብ ለማየት ቀና ብዬ ሳየው አይኖቹ ውስጥ እንግዳ የሆነ አስተያየት ተመለከትኩ፡ እርስ በእርሱ በሚጋጭ አይነት
ደስተኛ፣ ያዘነ፣ ያረጀ፣ ወጣት የሆነ፣ ብልህ፣ ሞኝ ... ይመስል ነበር። ወይም አሁን እንደ ትልቅ ወንድ እየተሰማው ይሆን? እንደዚያ ከሆነ ኃጢአት
ይሁንም አይሁንም ደስ ብሎኛል።
እጅ ለእጅ ተያይዘን ወደ መንትዮቹ ለመሄድ ደረጃውን መውረድ ጀመርን።ኮሪ የሙዚቃ መሳሪያ እየተጫወተና ኬሪ ደግሞ እየዘፈነች ነው:
ከኮሪ አጠገብ ወለሉ ላይ ተቀመጥኩና ጊታሩን ተቀብዬ ለመጫወት ሞከርኩ።
ሁላችንንም አስተምሮናል በጣም የሚወደውን ዘፈን ዘፈንኩለት፡ ስጨርስ
“የኔን ዘፈን አልወደድሽውም ካቲ?” አለኝ።
“በጣም ወድጄዋለሁ ኮሪ ግን በጣም ያሳዝናል።
ለምን ደስ የሚሉ ግጥሞች
አንጨምርበትም?” አልኩት።
“ታውቂያለሽ ካቲ… እናታችን ስለመጫወቻዬ ምንም አላለችም" አለኝ፡
“አላየችውም እኮ ኮሪ።''
“ለምን አላየችውም?”
እንወዳት የነበረች እንግዳ ሴት ከመሆኗ በስተቀር ከአሁን በኋላ እናታችን
ማንና ምን እንደሆነች ባለማወቄ በከባዱ ተነፈስኩ፡ አንዳንዴ የምንወዳቸውን ሰዎች ከእኛ ነጥሎ የሚወስዳቸው ሞት ብቻ አይደለም: አሁን ይህንን አውቄያለሁ።
“እናታችን አዲስ ባል አግኝታለች:” አለ ክሪስ “እና ሰው ፍቅር ሲይዘው ደግሞ ከራሱ ደስታ በስተቀር የሌሎችን ደስታ አያይም"
ኬሪ ሹራቤን አተኩራ እየተመለከተች፣ ካቲ፣ ሹራብሽ ላይ ያለው ምንድነው?” አለችኝ። “ቀለም” አልኩ ያለምንም ማመንታት። “ክሪስ ስዕል
መሳል ሊያስተምረኝ እየሞከረ ነበር። ከዚያ የኔ ስዕል ከእሱ ስዕል ይበልጥ
እንደሚያምር ሲመለከት ቀይ ቀለም የነበረበትን ዕቃ አንስቶ ወደ እኔ ወረወረው"
ትልቁ ወንድሜ አተኩሮ እያየኝ ነበር። “ክሪስ፣ ካቲ ከአንተ የተሻለ መሳል
ትችላለች?”
“እችላለሁ ካለች መቻል አለባት”
“ስዕሉ የታለ?”
“ጣሪያው ስር ያለው ክፍል ውስጥ።”
“ማየት እፈልጋለሁ”
“እኔ ደክሞኛል አንቺ ሂጂና አምጪው ካቲ ራት እስክታዘጋጅ ቲቪ ማየት
እፈልጋለሁ፡" ብሎ አየት አደረገኝ፡፡ “ውድ እህቴ ጨዋ ለመሆን ብለሽ
ተቀምጠን ራት ከመብላታችን በፊት ንፁህ ሹራብ ብትለብሽ ቅር ይልሻል? ስለዛ ቀይ ቀለም ጥፋተኝነት እንዲሰማኝ የሚያደርግ የሆነ ነገር አለ:”
“ደም ይመስላል” አለ ኮሪ። “አጥበሽ ካላስለቀቅሽው እንደ ደም ይሆንብሻል።"
በዚያ ምሽት የማይመች ስሜት ተሰምቶኝ እረፍት የለሽ ሆንኩ ሀሳቤ ክሪስ ጣሪያው ስር ያለው ክፍል ውስጥ ይመለከተኝ ወደነበረበት ሁኔታ
ይመላለሳል።
ለረጅም ጊዜ ስፈልገው የነበረው ሚስጠር ምን እንደሆነ አወቅኩ ያ የሚስጥር ቁልፍ ፍቅርን አካላዊና ወሲባዊ ፍላጎትን የሚገልጥ ነበር። እርቃን
ሰውነቶችን ማየት አይደለም ምክንያቱም ለረጅም ጊዜ ኮሪን ሳጥብ ነበርና።
ክሪስም እርቃኑን ሆኖ አይቼው አውቃለሁ: ነገር ግን እሱና ኮሪ ያላቸው
ነገር እኔና ኬሪ ካለን ነገር የተለየ መሆኑ ምንም አይነት የወሲብ መነሳሳት
ፈጥሮብኝ አያውቅም: እርቃን መሆን አይደለም
አይኖቹ ናቸው: የፍቅር ሚስጥር አይን ውስጥ ነው። አንድ ሰው ሌላኛውን
የሚመለከትበት መንገድ፣ ከንፈሮች ሳይነቃነቁ አይኖች የሚገናኙበትና
የሚያወሩበት መንገድ ነው: የክሪስ አይኖች ከአስር ሺህ ቃላት በላይ ተናግረዋል።
እኔን የነካበት መንገድም አይደለም… ቀስ እያለ በደግነት ማድረጉም አይደለም ሲነካኝ ወደኔ የሚመለከትበት መንገድ ነው እና ለዚያ ነው ማለት ነው አያትየው ሌላኛውን ፆታ መመልከት እንደማይገባ ህግ ያወጣችው:: ያቺ
ጠንቋይ አሮጊት የፍቅርን ሚስጥር ታውቃለች ብሎ ማሰብ ከባድ ነው መቼም ተፈቅራ ልታውቅ አትችልም አይሆንም እሷ ባለ ብረት ልብ፣ ባለ ብረት አጥንት ናት... አይኖቿም ለስላሳ ሆነው አያውቁም:
ከዚያ ርዕሱን በጥልቀት ስመረምር ከአይኖች በላይ ነው: ከአይኖች ኋላ
አእምሮ ውስጥ ነው፧ ሊያስደስትህ የሚፈልግ፣ ደስ የሚያሰኝህ፣ ሀሴት
የሚሰጥህና እንዲረዱህ በምትፈልግበት መንገድ የሚረዳህ፣ ማንም ሳይረዳህ ሲቀር ደግሞ ብቸኝነትህን የሚወስድልህ ነው። ኃጢአት በፍቅር ጉዳይ ምንም አያገባውም
ፊቴን ስመልስ ክሪስም እንደነቃ ተመለከትኩ። በጎኑ ተኝቶ ወደ እኔ
እየተመለከተ ነው። በጣም ደስ የሚል ፈገግታ ነው ያለው።እናታችን በዚያን ቀን ልታየን አልመጣችም: ከዚያ ቀን በፊትም ብቅ አላለችም
እኛ ግን የኮሪን የሙዚቃ መሳሪያ በመጫወትና በመዝፈን ራሳችንን የማስደሰቻ መንገድ አግኝተናል: እናታችን በጣም ግድ የለሽ እየሆነች የመጣች ቢሆንም
በዚያ ምሽት ሁላችንም የተኛነው በተስፋ ተሞልተን ነው፡ ለረጅም ሰዓት የደስታ ዘፈኖች መዝፈናችን፣ ጥቅጥቅ ያለ ጨለማ የወረሰው ጫካ ውስጥ የነበረን ጉዞ እያለቀ መሆኑንና ፀሀይ፣ ፍቅር፣ ሐሴትና ደስታ መታጠፊያው ላይ እየጠበቁን መሆናቸውን እንድናምን አድርጎናል።
በብሩህ ህልሜ ውስጥ የሆነ ጨለማና የሚያስፈራ ነገር ይመጣብኛል።
በየቀኑ ቅርፁ የጭራቅ አይነት ይሆንብኛል። አይኖቼን ስጨፍን አያትየው ሳትታይ መኝታ ክፍላችን ገብታ እንቅልፍ እንደወሰደኝ አስባ ፀጉሬን በሙሉ ስትላጨኝ አያለሁ። እጮሀለሁ አትሰማኝም ማንም አይሰማኝም፡ ከዚያ ትልቅ የሚያንፀባርቅ ቢላዋ ታወጣና ሁለቱንም ጡቶቼን ቆርጣ ክሪስ አፍ ውስጥ ትጨምረዋለች: እና ሌላም ሌላም… ከዚያ እወራጫለሁ። ክሪስን የሚያነቃ የጩኸት ድምፅ አሰማለሁ። መንትዮቹ ልክ ሞቶ እንደተቀበሩ ልጆች ተኝተዋል። ክሪስ እንቅልፉ ሳይለቀው አልጋው ላይ ቁጭ ብሎ እጄን
ለመያዝ እየፈለገ “ሌላ ቅዠት ነው?” ሲል ጠየቀኝ።
አይይ! ... ተራ ቅዠት አይደለም ቀድሞ ማወቅና በተፈጥሮ መረዳት መቻል ነው:: የሆነ መጥፎ ነገር እንደሚፈጠር በአጥን መቅኒ ሳይቀር ተሰምቶኛል።
ድክም ብዬና እየተንቀጠቀጥኩ አያትየው ያደረገችኝን ለክሪስ ነገርኩት። “ያ ብቻ አይደለም መጥታ ልቤን ቆርጣ ያወጣችው እናታችን ነበረች: ሁሉ ነገሯ
በአልማዝ ያብረቀርቅ ነበር” አልኩት
ካቲ ህልም እኮ ምንም ትርጉም የለውም::”
“አለው!”
ሌሎች ህልሞችና ሌሎች ቅዠቶች ለወንድሜ እነግረዋለሁ። ያዳምጠኝና ይስቃል ከዚያ ሌሊቱን ልክ ፊልም ቤት እንዳሉ አይነት ሆኖ ማሳለፍ አሪፍ እንደሆነ ያለውን እምነት ይገልፅልኛል። ግን በፍፁም እንደዛ አልነበረም::ፊልም የሆነ ሰው የፃፈው መሆኑን እያወቅህ ቁጭ ብለህ ትልቁን ስክሪን
ትመለከታለህ እኔ ግን በህልሜ ውስጥ ተሳታፊ ነኝ፡ ህልም ውስጥ
እየተሰማኝ… እየተጎዳሁ እየተሰቃየሁና ይህንን ስል እያዘንኩ ነው አልፎ አልፎም በጣም እየተደሰትኩ ነው።
ክሪስ፣ እሱ ከእኔና ከእንግዳ መንገዶቼ ውስጥ የሌለ ሆኖ ሳለ ይህ ህልም ከሌሎች ይልቅ እሱን ይጎዳው ይመስል ለምን ፀጥ ብሎ እንደ ሀውልት ተቀመጠ? እሱም ህልም አይቶ ይሆን?
👍44👏2❤1