#የወድያነሽ
፡
፡
#ክፍል_አስራ_አንድ
፡
፡
#ድርሰት_ኀይለመለኮት_መዋዕል
...«አዎ ይኸው ነው! ጨርሻለሁ! አንዲት ሕይወት አንጋድጃለሁ! ቅንና ገር ሕይወት ቀርድጄ ጥያለሁ» ብዪ አጠገቤ ያለውን ጠረጴዛ በቡጢ መታሁት፡፡
ጉልላትም «እኔም እኮ መጀመሪያውኑ ያውም ገና ከቡቃያነቱ ከፍ ሳይል
ነግሬህ ነበር» ብሎ ሲያነብ የቆየውን መፍሐፍ በሌባ ጣቱ አለበና «እንደ ጨው
ካሟሟሃት በኋላ ወደየትም ቦታ ትረጫታለህ፡ ወይም እንደ እንኮይ ከበላሃትና እንደ አጥንት ከጋጥሃት በኋላ እንትፍ ብለህ ትጥላታለህ ብዬህ ነበር፡፡ ክልልህና ክልሏ አንድ ካለመሆኑ የተነሣ እንዴ አጋጣሚ እንኳን ሆኖ ብትንጠለጠልባት እንደ ተልባ ሥፍር ትንሽራተታለህ፥ በአንተና በእርሷ መካከል: የኮርማና የአምቦሳ ያህል ልዩነት አለ» ብሎ ቁልቁል ወለል ወለሉን አየ። በየወጂያነሽ ላይ የደረሰውን ማንኛውንም ነገርና ሁኔታ ሁሉ ተርኬ ጨርሼለት ስለ ነበር አሁን ከእርሱ የምጠብቀው ምክሩን እንጂ በሰነበተው ሐሳቡ ውስጥ የነበረውን አፍራሽ ነቀፌታ አልነበረም፡፡
«ስማ» አለኝ የመጽሐፉን ገጾች እየገለባበጠና ዐይኑን በሐሳብ እያቦዘ፣
«ከእንግዲህ ምስጢርህ ሁሉ ያንተ እስረኛና ምርኮኛ መሆን አለበት፡፡ ከበተንከውና ከረጨኸው ግን አንተው የምስጢርህ ምርኮኛና ግዳይ ትሆናለህ፡፡ ምስጢርህን በውስጥህ ለማዳፈን የምትችል ከሆንክና እሷንም እንደማትከዳት ከራስህ ጋር
እውነተኛ ቃል ኪዳን ከገባ ዓላማህን ለመፈጸምና የትግልህን ምርት ለማፈስ
ነገሩ የካባድ ቀላል ይሆናል፡፡ አሁንም እንደገና ልንገርህ፤ ያለ ጥርጥር ድል
ማድረግ ትችላለህ !» ብሎ አንገቱን ወደ ኋላ ቀልሶ ጣራ ጣራውን ማየት ጀመረ።
ሳይታወቀው እግሩን ዘረጋ።
«ያጠፋሁትን የሕይወቷን ቀንዲል እንደገና ለመለኮስና በተደላደለ የኑሮ
መሠረት ላይ እንድትገኝ ለማድረግ ታጥቄ ተነሥቻለሁ! ዛሬ ባላገኛት ነገ፣ ነገ
ባይሳካልኝ ከነገ ወዲያ ከዚያም ከዚያም በኋላ ቢሆን አገኛት ይሆናል። ሆነም
ቀረም ያስጨበጥኳትን መራራ የኑሮ ጽዋ ከንብዬ ሌላ ጣፋጭ የሕይወት ጽዋ
እስጨብጣታላሁ! ሕይወቴም እፎይታና ልባዊ እርካታ ማግኘት የምትችለው
የተጉደፈደፈችበትን የጸጸት ዕድፍ አጥባ ስታጠራ ብቻ ነውና እስከ ዘለቄታው
እታገላለሁ:: ከጥንትን፣ ሥጋንና ደምን፣ ክብርንና ርካሽ አዋራጅ ቃላትንም
በቆራጥነት እቋቋማቸዋለሁ» ብዩ ተራ ለቀቅሁ።
ጣራ ጣራውን ሲመለከተ የቆዩትን ዐይኖቹን ወደ እኔ መለስ አደረገና
አንገቱን አስተካከሎ
«ሌላ ነገር ባደርግልሀና ብመክርህ ይሻለኛል፡፡ እኔም የሐሳብ እንጂ ሙሉ
የተግባር ሰው አይደለሁም፡፡ የወላጆችህን እምነትና አስተሳሰብ በቀላሉ መለወጥ እችላለሁ ብዬ አልናገርም፡፡ አስተሳሰብን መለወጥ እንደሚቻል ባውቅም አፈፃፀሙ ግን ብዙ ውጣ ወረድ አለበት፡፡ ለዘመናት የኖረን የሕዝብን እምነት መለወጥ ቀላል ጉዳይ አይደለም፡፡ አንተም ውስጥ እኮ ያ እምነት አለ፡፡ እኔም ዘንድ አለ:: ኋላ ቀር አመለካከትን ከሕሊና ላይ አጥቦ ለማፅዳት አያሌ ዓመታት ይፈጃል። በዚያ ላይ ርዝራዥ እስኪወገድ ብዙ ፈተና አለ። ይህ ጉዳይ ከተራው ዜጋ እስከ ከፍተኛው ባለሥልጣን ድረስ ይዘልቃል፡፡ ያም ሆነ ይህ አንተ ግን ከዛሬ ጀምረህ በዓለም ላይ ያለውን አንድ ተራ አድካሚ ሥራ ለማከናወን ሞክር፡፡«በመጠኑ እንኳ ከተሳካልህ ጥሩ ታጋይ ነህ ማለት ነው። አዎ ሌላ አይደለም፡ እስኪ በመጀመሪያ ራስህን ለማወቅና ለማሽነፍ ሞክር፡፡ ብልህ መሆን ማለት ስለ አንድ ስለ አጣኸው ወይም ስለማታገኘው ነገር ተጎልተህ መተከዝ አይደለም፡፡ ይልቅስ እሷ በአካልና በሕሊና የምትካስበትንና መልሰህም ማግኘት የምትችልበትን መንገድ መፈለግ ነው» ብሎ ጸጉሩን ማሻሸት ጀመረ።
ምንም እንኳ ሐሳቡ ረቅቆ የሚያመራምር ባይሆንም ለጊዜው ብቻዬን ሆኜ በአእምሮዬ ሰለቅሁት። በየበኩላችን ሐሳብ በማንሣትና በመጣል ላይ እንዳለን
እኅቱ ሻይ ይዛልን ከተፍ አለች፡፡
«ግን» አለ ያንን ሁለትና ሦስት ጊዜ ያህል እ-ፍ-እ-ፍ ብሎ ፉት ያለውን ሻይ ኣፉ ውስጥ አቀዝቅዞ ከዋጠው በኋላ፡፡
«ይኸው ለእኔ እንኳ ከምስጢርህ ውስጥ ጥቂቱን ነግረኸኛል፤ ቀሪውን ቀብረህ ለመጠበቅ የሚኖርህ ኃይል ግን አነስተኛ መሆን የለበትም። አደራህን! አንተ ልታምቀው ያልተቻለህን የገዛ ራስህን ምስጢር ሌላ ሰው ሊጠብቅልህ
አይችልምና ማንም የማይከፍተው የልብ ሳጥን ይኑርህ! ዓላማህን ለመፈጸምና
ከግብህ ለመድረስ ለራስህ ከራስህ የሚቀርብህና በፍጹም ተግባራዊ መሰልህ ሌላ ማንም እንደማይገኝ አትዘንጋ» ብሎ ወደ ሻዩ ዞረ።
ጓደኝነቱን በቃል ሳይሆን በተግባር ያከናወነልኝ ስለመሰለኝ ጉልላትን
ከቀድሞው በበለጠ ከራሴ ጋር አዋሐድኩት፡፡
ሐሳቡን ለአንድ አፍታ ቆም አድርጎ ደረጃ በደረጃ ፈገግ ካለ በኋላ ለዛ የሌለው ሣቅ ሣቀ። «ለመሆኑ አሁን ብታገኛት ምን ትላታልሀ? ” ምንስ ታደርግላታለህ?» ብሎ ደረቅ ፈገግታውን አሳየኝ፡፡
ድንገተኛ ጥያቄው ድንገተኛ መልስ እንድሰጥ ያስገደደኝ ይመስል
የንግግሬን አካሔድ ሳልመለከት የመጣው ይምጣ እንጂ ቤት ተከራይቼ
አብሬያት እኖራለሁ፡፡ ከዚያ ወዲያ ማንም ያሻውን ቢልና በእኔና በእርሷ የተነሣ
ቤተሰቦቼ እንኳ ብትንትናቸው ቢወጣ ግድ የለኝም» ብዬ መለስኩለት፡፡ አሁንም
ሐሳብ ሊሽከሽክ ሰምቶ ዝም አለ፡፡
ጉልላትን ከማደንቅበት አንደኛዉ ዋና ምክንያት የግል ሐሳቡን ስፋት ብቻ ሳይሆን ከሌሎች ሰዎች ያገኘውን ዕውቀትና አነጋገር ሳይረሳ ለሌላ
የማስተላፍ ችሎታዉን ነው::
«መቼም በራስ መተማመንና ሕሊናን መግዛት የጀግንነት ምሰሶ ነው ብሏል አንድ ሊቅ» ብሎ ንግግሩን በመጀመር «የሚያዋጣትን ትክክለኛ መንገድ
ለማግኘት ስትል የምትፈራና የምትጨነቅ አእምሮ ፍጻሜዋ ያማረና የሠመረ
ይሆናል” ብሏል አንዱ ሌላ ሊቅ ደግሞ» በማለት የማዳምጥ መሆኔን ለመገንዘብ
ትኩር ብሎ አየኝ::
«እኔም ለፅኑ ጓደኝነታችንና ለፍቅራችን ዘላቂ ሕይወት ስል የችግሮችህ
ሁሉ ሙሉ ተካፋይ እሆናለሁ፡፡ በምታደርገው የውጣ ውረድ ትግልም ይሁን በሌላ ማናቸውም ነገር እኔ አንዱ ግማሽህ ነኝ፡፡ የብርሃናዊም ይሁን የጽልመታዊ ፍጻሜህ ማኅበርተኛ እሆናለሁ» ብሎ የማያወላውል ልበዊ ጓደኝነቱን አረጋገጠልኝ፡፡ የዕለቱ ምከራችንና ሐሳባችን ሰምና ወርቅ ሆኖ አለቀ።
የወዲያነሽ አድራሻና መገኛ ትላንትም ከትላንት ወዲያም እንደሆነው
ሁሉ፣ ወደፊት ግን የሕልም ሩጫ ሆኖ እንደማይቀር ሙሉ ተስፋ ነበረኝ።
የወዲያነሽን ፍለጋ ጉልላትም አብሮኝ ባዘነ፡፡ ዳሩ ምን ያደርጋል! የሁለታችንም
ልፋት የማይገኝ የቅዠት ወርቅ ሆኖ ቀረ።
እናቴን በጥላቻ ጥቁር ዐይኖች ተመለከትኳት። በቤተሰቤ መኻል እያለሁ
የከለልኩት የብቸኝነት ክልል ግን እኔኑ እንጂ ማንንም አልጎዳ፡፡ እኔ የእኔዉ
ረመጥ ነኝና የሕሊናዬ ረመጥ እኔኑ መልሶ ፈጀኝ፡፡
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
ጥቅምት ኸያ አራት ቀን አንድ ያልተጠበቀና ያልታሰበ ምንም ዝግጅት
ያልተደረገለት ትልቅ የደስታ ቀን ሆኖ ዋለ፡ ቤታችን በእንግዶች እና በልዩ ልዩ
ስዎች ተጣበበ፡፡ ላለው ምን ይሳነው፡ ሆንና ለተገኘው ደስታ የተፋጠነ ድግስና
መጠነኛ ግብዣ ተደረገ፡፡ አባቴ የከፍተኛው ፍርድ ቤት ዳኛ እንዲሆን ተሾመ ትልቁ ክፍል ውስጥ መላወሻ ጠፍቶ ዋለ። አንዳንዶቹ ያልፈጸመውን እየጨመሩና እያሞጋገሱ የሆነና ያልሆነውን ዝና እየሰጡ አወሩ።
አንዳንዶቹ ደግሞ ግራ ቀኛቸውን መልከትከት ብለው ቤተኛ ሰው ያለመኖሩን ካረጋገጡ በኋላ ከሐሜታው
ወርወር አደጉ። አባቴ የመጣውን ሰው ሁሉ በደስታና በፈገግታ እየተቀበለ ሸኘ።
ሹመት ያዳብር ጌታዩ” እያለ የሚመላለሰውና እጅ የሚነሳው
፡
፡
#ክፍል_አስራ_አንድ
፡
፡
#ድርሰት_ኀይለመለኮት_መዋዕል
...«አዎ ይኸው ነው! ጨርሻለሁ! አንዲት ሕይወት አንጋድጃለሁ! ቅንና ገር ሕይወት ቀርድጄ ጥያለሁ» ብዪ አጠገቤ ያለውን ጠረጴዛ በቡጢ መታሁት፡፡
ጉልላትም «እኔም እኮ መጀመሪያውኑ ያውም ገና ከቡቃያነቱ ከፍ ሳይል
ነግሬህ ነበር» ብሎ ሲያነብ የቆየውን መፍሐፍ በሌባ ጣቱ አለበና «እንደ ጨው
ካሟሟሃት በኋላ ወደየትም ቦታ ትረጫታለህ፡ ወይም እንደ እንኮይ ከበላሃትና እንደ አጥንት ከጋጥሃት በኋላ እንትፍ ብለህ ትጥላታለህ ብዬህ ነበር፡፡ ክልልህና ክልሏ አንድ ካለመሆኑ የተነሣ እንዴ አጋጣሚ እንኳን ሆኖ ብትንጠለጠልባት እንደ ተልባ ሥፍር ትንሽራተታለህ፥ በአንተና በእርሷ መካከል: የኮርማና የአምቦሳ ያህል ልዩነት አለ» ብሎ ቁልቁል ወለል ወለሉን አየ። በየወጂያነሽ ላይ የደረሰውን ማንኛውንም ነገርና ሁኔታ ሁሉ ተርኬ ጨርሼለት ስለ ነበር አሁን ከእርሱ የምጠብቀው ምክሩን እንጂ በሰነበተው ሐሳቡ ውስጥ የነበረውን አፍራሽ ነቀፌታ አልነበረም፡፡
«ስማ» አለኝ የመጽሐፉን ገጾች እየገለባበጠና ዐይኑን በሐሳብ እያቦዘ፣
«ከእንግዲህ ምስጢርህ ሁሉ ያንተ እስረኛና ምርኮኛ መሆን አለበት፡፡ ከበተንከውና ከረጨኸው ግን አንተው የምስጢርህ ምርኮኛና ግዳይ ትሆናለህ፡፡ ምስጢርህን በውስጥህ ለማዳፈን የምትችል ከሆንክና እሷንም እንደማትከዳት ከራስህ ጋር
እውነተኛ ቃል ኪዳን ከገባ ዓላማህን ለመፈጸምና የትግልህን ምርት ለማፈስ
ነገሩ የካባድ ቀላል ይሆናል፡፡ አሁንም እንደገና ልንገርህ፤ ያለ ጥርጥር ድል
ማድረግ ትችላለህ !» ብሎ አንገቱን ወደ ኋላ ቀልሶ ጣራ ጣራውን ማየት ጀመረ።
ሳይታወቀው እግሩን ዘረጋ።
«ያጠፋሁትን የሕይወቷን ቀንዲል እንደገና ለመለኮስና በተደላደለ የኑሮ
መሠረት ላይ እንድትገኝ ለማድረግ ታጥቄ ተነሥቻለሁ! ዛሬ ባላገኛት ነገ፣ ነገ
ባይሳካልኝ ከነገ ወዲያ ከዚያም ከዚያም በኋላ ቢሆን አገኛት ይሆናል። ሆነም
ቀረም ያስጨበጥኳትን መራራ የኑሮ ጽዋ ከንብዬ ሌላ ጣፋጭ የሕይወት ጽዋ
እስጨብጣታላሁ! ሕይወቴም እፎይታና ልባዊ እርካታ ማግኘት የምትችለው
የተጉደፈደፈችበትን የጸጸት ዕድፍ አጥባ ስታጠራ ብቻ ነውና እስከ ዘለቄታው
እታገላለሁ:: ከጥንትን፣ ሥጋንና ደምን፣ ክብርንና ርካሽ አዋራጅ ቃላትንም
በቆራጥነት እቋቋማቸዋለሁ» ብዩ ተራ ለቀቅሁ።
ጣራ ጣራውን ሲመለከተ የቆዩትን ዐይኖቹን ወደ እኔ መለስ አደረገና
አንገቱን አስተካከሎ
«ሌላ ነገር ባደርግልሀና ብመክርህ ይሻለኛል፡፡ እኔም የሐሳብ እንጂ ሙሉ
የተግባር ሰው አይደለሁም፡፡ የወላጆችህን እምነትና አስተሳሰብ በቀላሉ መለወጥ እችላለሁ ብዬ አልናገርም፡፡ አስተሳሰብን መለወጥ እንደሚቻል ባውቅም አፈፃፀሙ ግን ብዙ ውጣ ወረድ አለበት፡፡ ለዘመናት የኖረን የሕዝብን እምነት መለወጥ ቀላል ጉዳይ አይደለም፡፡ አንተም ውስጥ እኮ ያ እምነት አለ፡፡ እኔም ዘንድ አለ:: ኋላ ቀር አመለካከትን ከሕሊና ላይ አጥቦ ለማፅዳት አያሌ ዓመታት ይፈጃል። በዚያ ላይ ርዝራዥ እስኪወገድ ብዙ ፈተና አለ። ይህ ጉዳይ ከተራው ዜጋ እስከ ከፍተኛው ባለሥልጣን ድረስ ይዘልቃል፡፡ ያም ሆነ ይህ አንተ ግን ከዛሬ ጀምረህ በዓለም ላይ ያለውን አንድ ተራ አድካሚ ሥራ ለማከናወን ሞክር፡፡«በመጠኑ እንኳ ከተሳካልህ ጥሩ ታጋይ ነህ ማለት ነው። አዎ ሌላ አይደለም፡ እስኪ በመጀመሪያ ራስህን ለማወቅና ለማሽነፍ ሞክር፡፡ ብልህ መሆን ማለት ስለ አንድ ስለ አጣኸው ወይም ስለማታገኘው ነገር ተጎልተህ መተከዝ አይደለም፡፡ ይልቅስ እሷ በአካልና በሕሊና የምትካስበትንና መልሰህም ማግኘት የምትችልበትን መንገድ መፈለግ ነው» ብሎ ጸጉሩን ማሻሸት ጀመረ።
ምንም እንኳ ሐሳቡ ረቅቆ የሚያመራምር ባይሆንም ለጊዜው ብቻዬን ሆኜ በአእምሮዬ ሰለቅሁት። በየበኩላችን ሐሳብ በማንሣትና በመጣል ላይ እንዳለን
እኅቱ ሻይ ይዛልን ከተፍ አለች፡፡
«ግን» አለ ያንን ሁለትና ሦስት ጊዜ ያህል እ-ፍ-እ-ፍ ብሎ ፉት ያለውን ሻይ ኣፉ ውስጥ አቀዝቅዞ ከዋጠው በኋላ፡፡
«ይኸው ለእኔ እንኳ ከምስጢርህ ውስጥ ጥቂቱን ነግረኸኛል፤ ቀሪውን ቀብረህ ለመጠበቅ የሚኖርህ ኃይል ግን አነስተኛ መሆን የለበትም። አደራህን! አንተ ልታምቀው ያልተቻለህን የገዛ ራስህን ምስጢር ሌላ ሰው ሊጠብቅልህ
አይችልምና ማንም የማይከፍተው የልብ ሳጥን ይኑርህ! ዓላማህን ለመፈጸምና
ከግብህ ለመድረስ ለራስህ ከራስህ የሚቀርብህና በፍጹም ተግባራዊ መሰልህ ሌላ ማንም እንደማይገኝ አትዘንጋ» ብሎ ወደ ሻዩ ዞረ።
ጓደኝነቱን በቃል ሳይሆን በተግባር ያከናወነልኝ ስለመሰለኝ ጉልላትን
ከቀድሞው በበለጠ ከራሴ ጋር አዋሐድኩት፡፡
ሐሳቡን ለአንድ አፍታ ቆም አድርጎ ደረጃ በደረጃ ፈገግ ካለ በኋላ ለዛ የሌለው ሣቅ ሣቀ። «ለመሆኑ አሁን ብታገኛት ምን ትላታልሀ? ” ምንስ ታደርግላታለህ?» ብሎ ደረቅ ፈገግታውን አሳየኝ፡፡
ድንገተኛ ጥያቄው ድንገተኛ መልስ እንድሰጥ ያስገደደኝ ይመስል
የንግግሬን አካሔድ ሳልመለከት የመጣው ይምጣ እንጂ ቤት ተከራይቼ
አብሬያት እኖራለሁ፡፡ ከዚያ ወዲያ ማንም ያሻውን ቢልና በእኔና በእርሷ የተነሣ
ቤተሰቦቼ እንኳ ብትንትናቸው ቢወጣ ግድ የለኝም» ብዬ መለስኩለት፡፡ አሁንም
ሐሳብ ሊሽከሽክ ሰምቶ ዝም አለ፡፡
ጉልላትን ከማደንቅበት አንደኛዉ ዋና ምክንያት የግል ሐሳቡን ስፋት ብቻ ሳይሆን ከሌሎች ሰዎች ያገኘውን ዕውቀትና አነጋገር ሳይረሳ ለሌላ
የማስተላፍ ችሎታዉን ነው::
«መቼም በራስ መተማመንና ሕሊናን መግዛት የጀግንነት ምሰሶ ነው ብሏል አንድ ሊቅ» ብሎ ንግግሩን በመጀመር «የሚያዋጣትን ትክክለኛ መንገድ
ለማግኘት ስትል የምትፈራና የምትጨነቅ አእምሮ ፍጻሜዋ ያማረና የሠመረ
ይሆናል” ብሏል አንዱ ሌላ ሊቅ ደግሞ» በማለት የማዳምጥ መሆኔን ለመገንዘብ
ትኩር ብሎ አየኝ::
«እኔም ለፅኑ ጓደኝነታችንና ለፍቅራችን ዘላቂ ሕይወት ስል የችግሮችህ
ሁሉ ሙሉ ተካፋይ እሆናለሁ፡፡ በምታደርገው የውጣ ውረድ ትግልም ይሁን በሌላ ማናቸውም ነገር እኔ አንዱ ግማሽህ ነኝ፡፡ የብርሃናዊም ይሁን የጽልመታዊ ፍጻሜህ ማኅበርተኛ እሆናለሁ» ብሎ የማያወላውል ልበዊ ጓደኝነቱን አረጋገጠልኝ፡፡ የዕለቱ ምከራችንና ሐሳባችን ሰምና ወርቅ ሆኖ አለቀ።
የወዲያነሽ አድራሻና መገኛ ትላንትም ከትላንት ወዲያም እንደሆነው
ሁሉ፣ ወደፊት ግን የሕልም ሩጫ ሆኖ እንደማይቀር ሙሉ ተስፋ ነበረኝ።
የወዲያነሽን ፍለጋ ጉልላትም አብሮኝ ባዘነ፡፡ ዳሩ ምን ያደርጋል! የሁለታችንም
ልፋት የማይገኝ የቅዠት ወርቅ ሆኖ ቀረ።
እናቴን በጥላቻ ጥቁር ዐይኖች ተመለከትኳት። በቤተሰቤ መኻል እያለሁ
የከለልኩት የብቸኝነት ክልል ግን እኔኑ እንጂ ማንንም አልጎዳ፡፡ እኔ የእኔዉ
ረመጥ ነኝና የሕሊናዬ ረመጥ እኔኑ መልሶ ፈጀኝ፡፡
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
ጥቅምት ኸያ አራት ቀን አንድ ያልተጠበቀና ያልታሰበ ምንም ዝግጅት
ያልተደረገለት ትልቅ የደስታ ቀን ሆኖ ዋለ፡ ቤታችን በእንግዶች እና በልዩ ልዩ
ስዎች ተጣበበ፡፡ ላለው ምን ይሳነው፡ ሆንና ለተገኘው ደስታ የተፋጠነ ድግስና
መጠነኛ ግብዣ ተደረገ፡፡ አባቴ የከፍተኛው ፍርድ ቤት ዳኛ እንዲሆን ተሾመ ትልቁ ክፍል ውስጥ መላወሻ ጠፍቶ ዋለ። አንዳንዶቹ ያልፈጸመውን እየጨመሩና እያሞጋገሱ የሆነና ያልሆነውን ዝና እየሰጡ አወሩ።
አንዳንዶቹ ደግሞ ግራ ቀኛቸውን መልከትከት ብለው ቤተኛ ሰው ያለመኖሩን ካረጋገጡ በኋላ ከሐሜታው
ወርወር አደጉ። አባቴ የመጣውን ሰው ሁሉ በደስታና በፈገግታ እየተቀበለ ሸኘ።
ሹመት ያዳብር ጌታዩ” እያለ የሚመላለሰውና እጅ የሚነሳው
👍4❤1
#የወድያነሽ
፡
፡
#ክፍል_አስራ_ሁለት
፡
፡
#ድርሰት_ኀይለመለኮት_መዋዕል
....እሑድ ማለዳ ነበር፡፡ ሰማዩ በመፀው ደመና ተሸፍኗል። ብን ብን የምትለዋ ካፊያ ኻያና ሠላሳዎ በአንድ ላይ ተጠራቅማ አንድ ሙሉ ኩልልታ ሆና
ትንጠፈጠፋለች። ፀሐይ በወፍራም ጉምና ደመና በመሸፈኗ ጨረሯ ከደመናዉ ጣራ በላይ ውሏል። ዕለቱ ተስፋ የቆረጠ ሰው ፊት መስለ ፈገግታ እርቆቷል።
አንዳንድ ጊዜ እስከ ቤት ድረስ እየመጡ ከሚጠይቁኝ ተራ ጓደኞቼ መካክል ታምራት ደረሰ መጣ፡፡ ከመጠን በላይ ተለማማጭነትንና ጉብቂጥ ማለትን ስለሚያዘወትር በተለይ ከጉልላት ጋር በሐሳብና በአመለካከታቸው
አይጣጣሙም፡፡
እኔም ከተራ ጉዳይ በስተቀር ምስጢሬን አላካፍለውም፡፡ በቤት ውስጥ ከእኔና ወዲያ ወዲህ ከሚሉት ሠራተኞች በስተቀር ማንም አልነበረም፡፡ ቁም ነገር
የሌላቸው ልዩ ልዩ ወሬዎችን አወራን፡፡ ድንገት በወሬያችን መኻል ስለ ሰው
ልጅ ጠባይ ምርምር የወጠነ ይመስል “አይ የሰው ልጅ! » ብሎ ራሱን ነቀነቀ፡፡
በምርምር እንዳልበሰለ ፈላስፋ ብዙ ሐሳብ መቧጠጥ ልማዱ ነበር፡፡ ፊቱ
ላይ የነበረችው ፈገግታ ቀስ በቀስ ተዳቀቀች። ምክንያቱን ሳላጣራና ሳልሰማ
ብናገር ፈጥኜ መሳሳት ስለ መሰለኝ “ምነው?» እንኳ ሳልለው ቀረሁ፡፡
«መጀመሪያስ ፍላጐትና ስሜት አስገድዷቸው ፈጽመውታል እንበል! ከተወለደ በኋላ ግን እንደ ውሻ ቡችላ የትም አውጥተው መጣላቸው በጣም ያሠቅቃል፡፡የዘመናችን ሰዎች አረመኔና ከሃዲዎች ሆነዋል፡፡ በእንዲህ ዐይነቱ ሰዎች ላይ ፍርድ ስጥ ቢለኝ ምን ፍርድ እንደምሰጥ እኔ ዐውቅ ነበር፡፡ በጣም የገረመኝ ግን የእናትዮዋ ነው:: ለምና እንኳ ብታሳድገው ምን ነበረበት?» ብሎ ከንፈሩን በቁጭት ነካከሰው::
«ምን ሆነሃል? ምን ነካህ ዛሬ?» ብዬ ከመጠየቄ እንደ ገና ራሱን ነቅንቆ
«እስኪ እግዚኣብሐር ያሳይህ! ሰው ክቡር ነው; ሰው ከሁሉም ፍጥረታት በላይ
ነው። እግዚአብሐር እንኳ የፈጠረው በገዛ ራሱ የመልክ አምሳል ነው ይባላል፡፡
ዛሬ ምን ያየሁ መሰለህ! እንዷ እናት፣ ኧረ ይችስ እናትም ልትባል አይገባት፡
በተቦጫጨቀ እሮጌ ቀሚስ ጠቅልላ በእንድ በማይረባ ዝንጥልጥል ዝንቢል እንደ ቃሪያና ሽንኩርት ሽምልላ፣ ሰው ሳይነሣና ሳያያት ልጅዋን ያላንዳች ርኅራኄ
ለውርጭና ለፀሐይ ጥላው ሄዳ እየሁ» ብሉ ተሟግቶ እንደ ተረታ ሰው አቀረቀረ፡፡ የእኔን አንጎል ከፍተኛ ድንጋጤ የተጠናወተው፣ መብረቅ አጠገቡ
እንዳረፈበት ሰዉ ነው ያልኩት እሱ ገና ወሬውን እንዳጋመሰ ነበር፡፡ የሞቱ
ዘመዶቹን የመርዶ ስም ዝርዝር እየሰማ አሁን ደግሞ የሞተው ማን ይሆን እያለ
እንደሚጨነቅ ሰው ልቤ በሥጋት ተሸበረ፡፡
ውስጥ ውስጡን የጥርጣሬ ቃጠሎ አጋየኝ፡፡ አንጎሌ በፍርሃት ማዕበል
በመጠንጋቱ ራሴን መቆጣጠር የምችል አልመስል አለኝ፡፡ ወዲያው ተወልዶ
ወዲያው ያደገው ጥርጣሬዬ ጎለመሰ።
«ለመሆኑ ልጁ የተገኘው የት ነው?” ብዬ ጠየቅሁት። ከወንበሩ ላይ ተነሥቶ ሱሪውን ሽቅብ ወደ እንብርቱ ከፍ ከፍ ካደረገ በኋላ «ልጁ የተገኘውማ
ከእኛ ቤት አጠገብ ከግቢ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ዝቅ ብሉ ባለው መንደር
ውስጥ ከመንገድ ዳር ነው» ብሎ ተቀመጠ፡፡ «መቼ መሰለህ ዛሬ እኮ ነው
በማለት ንግግሩን ቀጠለ። ባሮጌ ብጭቅጫቂ ጨርቅ አቅፈው ልጅ እኮ ተጥሉ አገኘሁ እያሉ አንዲት ሴትዮ ለዐላፊ አግዳሚው ሲያሳዩ እኔም ጠጋ ብዬ አየሁ፡፡ያውም እኮ ይገርምሃል! ስንዝር የምትሞላ ብጫቂ ጨርቅ አላለበሰችውም፡፡ መክሳቱና መጎዳቱ ነው እንጂ እንዴት ያለ ደስ የሚል ልጅ መስለህ?» አለና ከክቧ ጠረጴዛ ላይ መጽሔት እንሥቶ ማገላበጥ ጀመረ። በጥርጣሬና በሐሳብ ተቃጥሉ እንኩቶ ሆነው ሰውነቴ ውስጥ እሳት የሚንቦለቦል መሰለኝ።
«በመጨረሻስ፣ ልጁን ወዴት አደረሱት?» ብዬ እኔም ተከራክሮ እንደ ተረታ ሰው ጸጥ አልኩ፡፡ መፅሔቱን እያገላበጠ «ከዚያ በኋላማ እዚያው አካባቢ
የነበሩ ልጆች ፖሊስ ጠርተው ካመጡ በኋላ ካገኙት ሴትዮ ጋር ይዘዋቸው
ካዛንቺስ ወደ ስድስተኛ ፖሊስ ጣቢያ ሔዱ» ብለ በተራ ጸጸት እንደተለመዱ
ተራ ወሬ ነገረኝ፡፡
ጥርጣሬዬ ከመጠን በላይ እደገ፡፡ አፌን ደም ደም አለኝ። ወዲያው ደግሞ ከመጅ እንዳመለጠች ጥሬ ሌላ ሐሳብ ከጭንቅላቴ ውስጥ ተፈናጥራ ወጣች። እእምሮዬ ነገሩን አገላብጦ ለማየት ፋታና ትዕግሥት አጣ፡፡
የየወጂያነሽን ቀሚሶች አንድ ባንድ ዐውቃቸው ስለ ነበር «ለመሆኑ ሕፃኑ
የተጠቀለለበት ጨርቅ ምን እንደሚመስል ልብ ብለህ አይተኸዋል?» ብዬ እንደ ዘበት ጠየቅሁት፡፡ ከት ብሎ ከሳቀ በኋላ «አይ ያንተ ነገር! የልብሱ ዐይነት ምን ያደርግልሃል?» አለኝ፡፡
የምክንያቱ አመጣጥ እንዴት እንደ ቀናኝ እንጃ! «የአንዳንድ ስዎችን ጠባይ በልብሳቸው የቀለም ዐይነት ማወቅ ይቻላል ይባላል። ለዚህ ነው
የተጠቀለለበትን ጨርቅ የጠየቅሁህ» ብዩ ሐሳቤን ከሐሳቡ አራቅኋት። ዓይኑን
ከደን አድርጎ አስበና፡ ሐሳቡ ልጁ ወደ ተጣለበት አካባቢ ደርሶ ተመለሰ፡፡
በጨርቁ ላይ የደበዘዙ ሰፋፊና ሰማያዊ የአበባ ሥዕሎች አለበት። አንተ
የጨርቁን ትጠይቀኛለሀ፡ እኔ ስሜቴን በጣም የነካው ልጁ ነው» ብሎ አንደ
ቁምነገረኛ መለሰልኝ፡፡ አናቴን የተመታሁ ያህል እንዘፈዘፈኝ።
አፌ ውስጥ ከመንጋጋዬ ግራና ቀኝ የሚገኘውን ለስላሳዉን የውስጥ
ጉንጨን ነከስኩት። ከመጽሔቷ ላይ ቀና ብሎ እኔን እየተመለከተ የዘንቢሉ
ማንጠልጠያ ጆሮ በወፍራም ቀይ ሽቦ ተጠምጥሞ የተጠገነ ነው በማለት
ያልተጠየቀውን ጨምሮ አወጋኝ፡፡ ልቤ ክፉኛ ተርበተበተች፡፡ አንድ አዲስ
የጥርጣሬ ግምት አእምሮዩን ጠቅ አደረጋት፡፡ መንፈሴ ተበጠበጠ፡፡ አንዳንድ
አጋጣሚዎች ያልተጠበቀ መልካም ወይም መጥፎ ነገር ሊያስከትሉ ይችላሉ፡፡ የአእምሮዬን ጓዳ አገላብጬ ፈተሽኩት፡፡ ማንጠልጠያው በቀይ የመዳብ ሽቦ የተጠገነ ዘንቢል ትውስ አለኝ፡፡ “ጠብቀኝ አልኩትና ወደ ዕቃ ቤት ገሰገስኩ።አንዷ ሠራተኛችን ዕቃ ስታንጉዳጉድ ደረስኩ። “ቀይ የሽቦ ማንጠልጠያ የነበረው ዘንቢል አልነበረንም እንዴ?» አልኳት በድፍረት:: ቀና ብላ አየችኝና «ያቺ እዚህ የነበረችው “ማን ነበር ስሟ ወንድሜ፣ ልብሷን ይዛበት ሄዳለች መሠለኝ» አለችኝ፡፡ «ከዚህ በላይ ምን ማረጋገጫ አለ» ብዬ ተመለስኩ፡፡ በነገሩ ላይ ሙሉ በሙሉ እርግጠኛ ባልሆንም ያን ዘንቢል የተጠገነበትን የመዳብ ሽቦ በዘንቢሉ ላይ
የጠመጠምኩት እኔ ነበርኩ፡፡
ጉዳዩ ሲገጣጠም ታየኝና፡ ኡ ኡ ብዪ ወደ ማላመልጥበት የመከራ አዘቅት በሐሳብ እየዳህኩ ወረድኩ፡፡ የወዲያናሽንም መልካም ሕይወት እፍ ብዬ በማጥፋት አሳዛኝና አሠቃቂ የእናትነት ታሪክ እንዳሳቀፍኳት ግዙፍ ጥፋቴ ወለል
ብሎ ታየኝ::
እጅግ በጣም የጠቆረው የበደልና የግፍ፡ ሥራዬ ሰው ከመባል ደረጃ አሽቀንጥሮ እንደሚወረውረኝ ታወቀኝ፡፡ እንደገና ሰው ለመሰኘት ብዙ ትግልና ውጣ ውረድ ማለፍና ፈተናውን ሁሉ ድል ማድረግ እንደሚኖርብኝ ከራሴ ሕይወት ውስጥ ወዲያውኑ ለመረዳት ቻልኩ:: ታምራትም ለእርሱ አንደ ተራ ወሬ ለእኔ ግን ምናልባትም አንድ ትልቅ ስውር መርዶ የሆነውን ጉዳይ ከዘረገፈልኝ በኋላ እንደ
ልማዱ መጻሕፍት ተውሶ ሲሄድ፡ ያመጣውን ያልተረጋገጠ መርዶ ግን ይዞት አልተመለሰም::
“በርግጥ የወዲያነሽ ትሆን ይሆን? ወይስ ሌላ?” በማለት አያሌ የሥቃይንና የጭንቀት ደቂቃዎች አሳለፍኩ። ራሴን እንደ ሞኝና እንደ ወፈፌ ቆጥሬ ስብእናዬን ተጸየፍኩት።
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
አባቴ የት እንደ ቀረ ባላውቅም እናቴና እኅቴ ከቤተክርስቲያን ተመለሱ እናቴ ያለፈውን ነገር ሁሉ ረስቶታል ወይም ንቆ ትቶታል ብላ ከእኔ ጋር እንደ ዱሮዋ
፡
፡
#ክፍል_አስራ_ሁለት
፡
፡
#ድርሰት_ኀይለመለኮት_መዋዕል
....እሑድ ማለዳ ነበር፡፡ ሰማዩ በመፀው ደመና ተሸፍኗል። ብን ብን የምትለዋ ካፊያ ኻያና ሠላሳዎ በአንድ ላይ ተጠራቅማ አንድ ሙሉ ኩልልታ ሆና
ትንጠፈጠፋለች። ፀሐይ በወፍራም ጉምና ደመና በመሸፈኗ ጨረሯ ከደመናዉ ጣራ በላይ ውሏል። ዕለቱ ተስፋ የቆረጠ ሰው ፊት መስለ ፈገግታ እርቆቷል።
አንዳንድ ጊዜ እስከ ቤት ድረስ እየመጡ ከሚጠይቁኝ ተራ ጓደኞቼ መካክል ታምራት ደረሰ መጣ፡፡ ከመጠን በላይ ተለማማጭነትንና ጉብቂጥ ማለትን ስለሚያዘወትር በተለይ ከጉልላት ጋር በሐሳብና በአመለካከታቸው
አይጣጣሙም፡፡
እኔም ከተራ ጉዳይ በስተቀር ምስጢሬን አላካፍለውም፡፡ በቤት ውስጥ ከእኔና ወዲያ ወዲህ ከሚሉት ሠራተኞች በስተቀር ማንም አልነበረም፡፡ ቁም ነገር
የሌላቸው ልዩ ልዩ ወሬዎችን አወራን፡፡ ድንገት በወሬያችን መኻል ስለ ሰው
ልጅ ጠባይ ምርምር የወጠነ ይመስል “አይ የሰው ልጅ! » ብሎ ራሱን ነቀነቀ፡፡
በምርምር እንዳልበሰለ ፈላስፋ ብዙ ሐሳብ መቧጠጥ ልማዱ ነበር፡፡ ፊቱ
ላይ የነበረችው ፈገግታ ቀስ በቀስ ተዳቀቀች። ምክንያቱን ሳላጣራና ሳልሰማ
ብናገር ፈጥኜ መሳሳት ስለ መሰለኝ “ምነው?» እንኳ ሳልለው ቀረሁ፡፡
«መጀመሪያስ ፍላጐትና ስሜት አስገድዷቸው ፈጽመውታል እንበል! ከተወለደ በኋላ ግን እንደ ውሻ ቡችላ የትም አውጥተው መጣላቸው በጣም ያሠቅቃል፡፡የዘመናችን ሰዎች አረመኔና ከሃዲዎች ሆነዋል፡፡ በእንዲህ ዐይነቱ ሰዎች ላይ ፍርድ ስጥ ቢለኝ ምን ፍርድ እንደምሰጥ እኔ ዐውቅ ነበር፡፡ በጣም የገረመኝ ግን የእናትዮዋ ነው:: ለምና እንኳ ብታሳድገው ምን ነበረበት?» ብሎ ከንፈሩን በቁጭት ነካከሰው::
«ምን ሆነሃል? ምን ነካህ ዛሬ?» ብዬ ከመጠየቄ እንደ ገና ራሱን ነቅንቆ
«እስኪ እግዚኣብሐር ያሳይህ! ሰው ክቡር ነው; ሰው ከሁሉም ፍጥረታት በላይ
ነው። እግዚአብሐር እንኳ የፈጠረው በገዛ ራሱ የመልክ አምሳል ነው ይባላል፡፡
ዛሬ ምን ያየሁ መሰለህ! እንዷ እናት፣ ኧረ ይችስ እናትም ልትባል አይገባት፡
በተቦጫጨቀ እሮጌ ቀሚስ ጠቅልላ በእንድ በማይረባ ዝንጥልጥል ዝንቢል እንደ ቃሪያና ሽንኩርት ሽምልላ፣ ሰው ሳይነሣና ሳያያት ልጅዋን ያላንዳች ርኅራኄ
ለውርጭና ለፀሐይ ጥላው ሄዳ እየሁ» ብሉ ተሟግቶ እንደ ተረታ ሰው አቀረቀረ፡፡ የእኔን አንጎል ከፍተኛ ድንጋጤ የተጠናወተው፣ መብረቅ አጠገቡ
እንዳረፈበት ሰዉ ነው ያልኩት እሱ ገና ወሬውን እንዳጋመሰ ነበር፡፡ የሞቱ
ዘመዶቹን የመርዶ ስም ዝርዝር እየሰማ አሁን ደግሞ የሞተው ማን ይሆን እያለ
እንደሚጨነቅ ሰው ልቤ በሥጋት ተሸበረ፡፡
ውስጥ ውስጡን የጥርጣሬ ቃጠሎ አጋየኝ፡፡ አንጎሌ በፍርሃት ማዕበል
በመጠንጋቱ ራሴን መቆጣጠር የምችል አልመስል አለኝ፡፡ ወዲያው ተወልዶ
ወዲያው ያደገው ጥርጣሬዬ ጎለመሰ።
«ለመሆኑ ልጁ የተገኘው የት ነው?” ብዬ ጠየቅሁት። ከወንበሩ ላይ ተነሥቶ ሱሪውን ሽቅብ ወደ እንብርቱ ከፍ ከፍ ካደረገ በኋላ «ልጁ የተገኘውማ
ከእኛ ቤት አጠገብ ከግቢ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ዝቅ ብሉ ባለው መንደር
ውስጥ ከመንገድ ዳር ነው» ብሎ ተቀመጠ፡፡ «መቼ መሰለህ ዛሬ እኮ ነው
በማለት ንግግሩን ቀጠለ። ባሮጌ ብጭቅጫቂ ጨርቅ አቅፈው ልጅ እኮ ተጥሉ አገኘሁ እያሉ አንዲት ሴትዮ ለዐላፊ አግዳሚው ሲያሳዩ እኔም ጠጋ ብዬ አየሁ፡፡ያውም እኮ ይገርምሃል! ስንዝር የምትሞላ ብጫቂ ጨርቅ አላለበሰችውም፡፡ መክሳቱና መጎዳቱ ነው እንጂ እንዴት ያለ ደስ የሚል ልጅ መስለህ?» አለና ከክቧ ጠረጴዛ ላይ መጽሔት እንሥቶ ማገላበጥ ጀመረ። በጥርጣሬና በሐሳብ ተቃጥሉ እንኩቶ ሆነው ሰውነቴ ውስጥ እሳት የሚንቦለቦል መሰለኝ።
«በመጨረሻስ፣ ልጁን ወዴት አደረሱት?» ብዬ እኔም ተከራክሮ እንደ ተረታ ሰው ጸጥ አልኩ፡፡ መፅሔቱን እያገላበጠ «ከዚያ በኋላማ እዚያው አካባቢ
የነበሩ ልጆች ፖሊስ ጠርተው ካመጡ በኋላ ካገኙት ሴትዮ ጋር ይዘዋቸው
ካዛንቺስ ወደ ስድስተኛ ፖሊስ ጣቢያ ሔዱ» ብለ በተራ ጸጸት እንደተለመዱ
ተራ ወሬ ነገረኝ፡፡
ጥርጣሬዬ ከመጠን በላይ እደገ፡፡ አፌን ደም ደም አለኝ። ወዲያው ደግሞ ከመጅ እንዳመለጠች ጥሬ ሌላ ሐሳብ ከጭንቅላቴ ውስጥ ተፈናጥራ ወጣች። እእምሮዬ ነገሩን አገላብጦ ለማየት ፋታና ትዕግሥት አጣ፡፡
የየወጂያነሽን ቀሚሶች አንድ ባንድ ዐውቃቸው ስለ ነበር «ለመሆኑ ሕፃኑ
የተጠቀለለበት ጨርቅ ምን እንደሚመስል ልብ ብለህ አይተኸዋል?» ብዬ እንደ ዘበት ጠየቅሁት፡፡ ከት ብሎ ከሳቀ በኋላ «አይ ያንተ ነገር! የልብሱ ዐይነት ምን ያደርግልሃል?» አለኝ፡፡
የምክንያቱ አመጣጥ እንዴት እንደ ቀናኝ እንጃ! «የአንዳንድ ስዎችን ጠባይ በልብሳቸው የቀለም ዐይነት ማወቅ ይቻላል ይባላል። ለዚህ ነው
የተጠቀለለበትን ጨርቅ የጠየቅሁህ» ብዩ ሐሳቤን ከሐሳቡ አራቅኋት። ዓይኑን
ከደን አድርጎ አስበና፡ ሐሳቡ ልጁ ወደ ተጣለበት አካባቢ ደርሶ ተመለሰ፡፡
በጨርቁ ላይ የደበዘዙ ሰፋፊና ሰማያዊ የአበባ ሥዕሎች አለበት። አንተ
የጨርቁን ትጠይቀኛለሀ፡ እኔ ስሜቴን በጣም የነካው ልጁ ነው» ብሎ አንደ
ቁምነገረኛ መለሰልኝ፡፡ አናቴን የተመታሁ ያህል እንዘፈዘፈኝ።
አፌ ውስጥ ከመንጋጋዬ ግራና ቀኝ የሚገኘውን ለስላሳዉን የውስጥ
ጉንጨን ነከስኩት። ከመጽሔቷ ላይ ቀና ብሎ እኔን እየተመለከተ የዘንቢሉ
ማንጠልጠያ ጆሮ በወፍራም ቀይ ሽቦ ተጠምጥሞ የተጠገነ ነው በማለት
ያልተጠየቀውን ጨምሮ አወጋኝ፡፡ ልቤ ክፉኛ ተርበተበተች፡፡ አንድ አዲስ
የጥርጣሬ ግምት አእምሮዩን ጠቅ አደረጋት፡፡ መንፈሴ ተበጠበጠ፡፡ አንዳንድ
አጋጣሚዎች ያልተጠበቀ መልካም ወይም መጥፎ ነገር ሊያስከትሉ ይችላሉ፡፡ የአእምሮዬን ጓዳ አገላብጬ ፈተሽኩት፡፡ ማንጠልጠያው በቀይ የመዳብ ሽቦ የተጠገነ ዘንቢል ትውስ አለኝ፡፡ “ጠብቀኝ አልኩትና ወደ ዕቃ ቤት ገሰገስኩ።አንዷ ሠራተኛችን ዕቃ ስታንጉዳጉድ ደረስኩ። “ቀይ የሽቦ ማንጠልጠያ የነበረው ዘንቢል አልነበረንም እንዴ?» አልኳት በድፍረት:: ቀና ብላ አየችኝና «ያቺ እዚህ የነበረችው “ማን ነበር ስሟ ወንድሜ፣ ልብሷን ይዛበት ሄዳለች መሠለኝ» አለችኝ፡፡ «ከዚህ በላይ ምን ማረጋገጫ አለ» ብዬ ተመለስኩ፡፡ በነገሩ ላይ ሙሉ በሙሉ እርግጠኛ ባልሆንም ያን ዘንቢል የተጠገነበትን የመዳብ ሽቦ በዘንቢሉ ላይ
የጠመጠምኩት እኔ ነበርኩ፡፡
ጉዳዩ ሲገጣጠም ታየኝና፡ ኡ ኡ ብዪ ወደ ማላመልጥበት የመከራ አዘቅት በሐሳብ እየዳህኩ ወረድኩ፡፡ የወዲያናሽንም መልካም ሕይወት እፍ ብዬ በማጥፋት አሳዛኝና አሠቃቂ የእናትነት ታሪክ እንዳሳቀፍኳት ግዙፍ ጥፋቴ ወለል
ብሎ ታየኝ::
እጅግ በጣም የጠቆረው የበደልና የግፍ፡ ሥራዬ ሰው ከመባል ደረጃ አሽቀንጥሮ እንደሚወረውረኝ ታወቀኝ፡፡ እንደገና ሰው ለመሰኘት ብዙ ትግልና ውጣ ውረድ ማለፍና ፈተናውን ሁሉ ድል ማድረግ እንደሚኖርብኝ ከራሴ ሕይወት ውስጥ ወዲያውኑ ለመረዳት ቻልኩ:: ታምራትም ለእርሱ አንደ ተራ ወሬ ለእኔ ግን ምናልባትም አንድ ትልቅ ስውር መርዶ የሆነውን ጉዳይ ከዘረገፈልኝ በኋላ እንደ
ልማዱ መጻሕፍት ተውሶ ሲሄድ፡ ያመጣውን ያልተረጋገጠ መርዶ ግን ይዞት አልተመለሰም::
“በርግጥ የወዲያነሽ ትሆን ይሆን? ወይስ ሌላ?” በማለት አያሌ የሥቃይንና የጭንቀት ደቂቃዎች አሳለፍኩ። ራሴን እንደ ሞኝና እንደ ወፈፌ ቆጥሬ ስብእናዬን ተጸየፍኩት።
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
አባቴ የት እንደ ቀረ ባላውቅም እናቴና እኅቴ ከቤተክርስቲያን ተመለሱ እናቴ ያለፈውን ነገር ሁሉ ረስቶታል ወይም ንቆ ትቶታል ብላ ከእኔ ጋር እንደ ዱሮዋ
👍3
#የወድያነሽ
፡
፡
#ክፍል_አስራ_ሦስት
፡
፡
#ድርሰት_ኀይለመለኮት_መዋዕል
...ስሜቴ በመጠኑ በመለወጡ ደስታ መሰል ሁኔታ ተሰማኝ። ደስታዬ እርሷ በመታስሯ ሳይሆን እርሷ ትሆን በማለት ሲዋልል የሰነበተው ጥርጣሬዬ ወደ
አንድ መጠነኛ ውጤት በመቃረቡ ነበር፡፡ ወደ ውጪ ወጣ ብዬ ወደ ግራ ተጠመዘዝኩ። ጥቂት ርምጃዎች እንደ ተራመድኩ ፊቴን ወደ ሰሜን መለስኩ፡፡
እስር ቤቱ ከፖሊስ ጣቢያው በስተጀርባ ነው፡፡ አረማመዴ ፈጠን ያለ ስለነበር
ጠበንጃ ይዞ የቆመው ዘብ «ቁም ወዴት ትሄዳለህ?» አለኝ። ሥርዓት እንደጣስኩ
ገባኝ፡፡
ቃሉ ቃለ ሕግ በመሆኗ ቀጥ አልኩ፡፡ ቀጠን ሳለች አስደንጋጭ የቁጣ
ድምፅ «ማንን ነው የምትፈልገው?» አለኝ።
«አንዲት ሴት እስረኛ ለመጠየቅ ነው?» ብዬ ከቆምኩበት ሳልንቀሳቀስ
መለስኩለት። ለአካባቢው ፍፁም እንግዳ መሆኔ ገባው:: ውስጡ ትሁት እንደሆነ
ተሰማኝ፡፡ ፈገግ አለልኝ። ፈገግታው እለመቆጣቱን ስላስረዳኝ አራት እርምጃዎች ወደፊት ቀጠልኩ፡፡ እሷ መሆኗን ባላረጋግጥም የወዲያነሽን እስረኛ በማለቴ የልቤ ግርማ ሞገስ ተገፈፈ፡፡ በወታደሩና በእኔ መካከል ከስድስት ደኅና ደኅና ርምጃ
የማይበልጥ ርቀት ነበር፡፡
«ምን ይዘሃል? ባዶ እጅህን ነው እንዴ እስረኛ ጥሩልኝ የምትለው? እስረኛ እኮ በማንኛውም ሰዓት አይጠየቅም፡፡ የተወሰነ ጊዜ አለው» አለ አሁንም
በመጠነኛ ፈገግታ። አነጋገሩ የሰውየውን የፈቃደኝነት ስሜት ስላስረዳኝ ሁለት
እርምጃዎች ጨመርኩ፡፡
«ገና እርሷ መሆኗንም አላረጋገጥኩ፡ መጀመሪያ ላረጋግጥ ብዬ» ሳልጨርስ አይኖቼ ዕንባ አቀረሩ፡፡ ጊዜም አልሰጡኝ፡ ተንጠባጠቡ። እምብዛም ጥልቅ ኀዘን በማይታይበት ፊቴ ላይ ዕንባ ሲወርድ በማየቱ፣
«ምነው ምን ነካህ? ወንድ ልጅ ያውም አንተን የሚያህል ያለቅሳል እንዴ?» አለኝ፡፡
«ምንም አልሆንኩ፡ እንዲያው ብቻ...»
«ለመሆኑ ማን ትባላለች?»
«የወዲያነሽ ትባላለች?»።
«እረግ! ኧረ! ያቺን ዕብድ አይሏት ጤነኛ ነው እንዴ? እሷማ ያቻትልህ! ያቺው ተጨብጣ ተቀምጣልሃለች! በል ሂድ! ፈጠን በል! ታዲያ ሥርዓቱን ባለማወቅህና እደጅ በመሆኗ ነው እንጂ እቤት ውስጥ ብትሆን ኖሮ
አይፈቀድም ነበር። እዚህ ድረስም አይመጣም ሰዓቱም ገና ነው» ብሎ አደራ አዘል ፈቃድ ሰጠኝ። አጠገቧ ከመድረሴ በፊት ትንሽ ራቅ ብዬ ቆምኩ::
ሲሽመደመድ የሰነበተው ጥርጣሬዩ ቀና አለ፡፡
ቀሚሷ ተዘነጣጥሎ ተቀዷል፡፡ እግሯ በእሳት የተለበለበ የክትክታ ዕንጨት መስሎ ዐልፎ አልፎ ልብሷ ላይ ጭቃ ተለጥፏል። የተራቆተው ግራ ቀኝ ክንዷ ዐመድ የተነሰነሰበት መስሎ ጽጉሯ እዚህና እዚያ የተነቀለ የጓያ ማሳ
መስሏል። መናገርም መራመድም አቃተኝ፡፡ የወዲያነሽ ጉስቁልና ለሁለተኛ ጊዜ አናቴ ላይ ተከመረ፡፡
ጥርጣሬዬ ጥርጣሬ መሆኑ ቀረ። ለየለት። የወጺያነሽ ተገኘች! ያም ሆነ ይህ የፍቅር ዐይኖቼ አላምጠው ዋጧት እንጂ አልተጸየፏትም። አእምሮዬ ውስጥ
የፍቅር ደማቅ ነበልባል በራ እንጂ የጥላቻና የንቀት ጥቁር ማቅ አልተሸመነም።አንድ ቀጠን ያለ ድምፅ ከበስተጀርባዬ ቶሉ በል እንጂ ሰውዩ!» ሲለኝ ሰማሁ:: በሐሳብ ከማንቀላፋበት አጭር ሰመመን ባነንኩ፡፡ ወደፊት ራመድ ብዪ ከወዲያነሽ አጠገብ ቆምኩ፡፡ ጉልበቷ ላይ ተደፍታ ስለነበር ድንገት ስናገር እንዳትደነግጥ የቆምኩበትን ሸካራ ንጥፍ ድንጋይ በቀኝ እግሬ ረመረምኩት።የፈራሁት አልቀረም፣ በድንጋጤ ባንና ተነሣች። በጣም ከስታለች። ፊቷ ጢስ የጠገበ ቋንጣ መስሏል፡፡ ልብ ብሎ ባላየ ዓይን ቀና ብላ አየችኝ። ማን መሆኔን አላወቀችም፡፡
አገጯን በእግሮቿ መሃል አስገብታ እግር እግሬን እየተመከለተች
«ምነው? ምን አጠፋሁ? ወድጀ እኮ አይደለም! ምን አባቴ ላድርግ! የሚላስና
የሚቀመስ በማጣቴ በረሃብና በችግር ከሚሞት ለነፍሴ ያለ ወስዶ እንዲያሳድገው ብዬ መንገድ ዳር አስቀመጥኩት፡፡ ምነው ሞቴን ባቀረበው?» ብላ ንግግሯን እንደ
ጨረሰች ቀና ስትል የሻገተ እንቀልባ በመሰለው ጉንጫ ላይ ዕንባዋ ተዝረበረበ።
በቁጣ ስሜት ዐይኗን አፍጥጣ «ከዚህ ወዲያ ምን እሆናለሁ ግደሉኝ!
ስቀሉኝ! አንጠልጥለኝ?» አለችና ጉልበቷ ላይ ደፋ አለች።
ጐንበስ ብዬ የቀኝ እጅ ክንፏን ያዝኩና «እኔ ነኝ እኮ የወዲያነሽ፣ እኔ ጌታነህ እኮ ነኝ» አልኳት፡፡ ቀስ ብላ ቀና ካለች በኋላ አፏን በፍርሃትና በድንጋጤ ከፈተችው፡፡ በሰውነቷ ውስጥ ይገኛል ተብሎ በማይገመት እንቅስቃሴ ተነስታ
አንገቴ ላይ ተጠመጠመች፡፡ እንዲህ ዓይነቱ ሁኔታ አይፈቀድም ያለኝ ፖሊስ
ምን ይል ይሆን በማለት ፈራሁ፡፡ መንማና ክንዶቿ ሥጋው ተፈቅፍቆ የወደቀ አጥንት እንጂ ሥጋ የለበሱ አይመስሉም፡፡ አንገቴ ላይ ተጠምጥማ እዬዬዋን ለቀቀችው፡፡ ተንሰቀሰቀች። የሟሸሹ ጉንጮችዋን ሳምኳቸው:: ደርቆና ተሰነጣጥቆ
ያረረ ደረቆት የሚመስለው ከንፈሯ ሻካራ ድንጋይ መስሏል። ያ ዝንፍልፍልና
የውበቷ ደረባ የነበረው ጸጉሯ ተሸላልቷል። አምክ እምክ የሚሽተው ጠረኗ የሥቃይዋን፡ ብዛት ያስረዳል፡፡ አይቼ ሳልጠግባትና አንዳች ነገር እንኳ ጠይቄ ሳልረዳ ፖሊሱ “በቃህ!» ብሎኝ ተመለስኩ:: እንባዋን እየረጨችና እያለቀሰች ተለያየን።
"እኔና የወዲያነሽ ተለያይተን የምንቆየው እስከ መቼ ይሆን ብዬ ራሴን ጠየቅሁ። እጅ እግር ላልነበረው ለዚህ ድፍን ጥያቄ አሁን በአሁን መልስ አላገኘሁም፡፡ አዲስ የፈተናና የስራ ገፅ ተከፈተ። ወደ ቤቴ ከመመለሴና የወዲያነሽንም መታሰር ለጉልላት ከመንገሬ ቀደም ብዬ አንድ ነገር ለማከናወን ወሰንኩ። በኪሴ ውስጥ የነበረችኝን የገንዘብ ልክ ዐወቅሁ፡፡ ከዚያም አራዳ ልብስ ተራ ገባሁ፡፡ በግምት አንድ ጥሩ ቀሚስ እና የውስጥ ልብስ፡ በቀድሞ ቁጥሯ አንድ ተራ ጫማ፣ ዋጋው ቀነስ ያለ የብርድ ልብስ ወዲያ ወዲህ ተሯሩጬ ገዛሁ፡፡
ኀዘንና ደስታዬ በመስተካከሉ መፈንጠዣና መተከዣ የሚሆን ምክንያት አገኘሁ፡፡ የገዛሁትን ልብስ በፖሊስ አስመርምሬ ለየወዲያነሽ ሰጥቻት ተመለስኩ፡፡
ከዚያች ዕለት ጀምሮ በየሣልስቱና ባመቸኝ ቁጥር እየተመላለስኩ
መጠየቄን ቀጠልኩ። አብዳለች፣ ወፍፏታል የተባለው ሁሉ ጠንባራ ስሕተት
መሆኑን ከቀን ወደ ቀን ከሁኔታዎቿ አረጋገጥኩ፡፡
ከግራና ቀኝ የቆሰለ ሰው ሁለቱንም ቁስሎቹን ተራ በተራ እንደሚያይና እንደሚያክም ሰው፡ እኔም ልክ ከዐሥር ቀን በኋላ እንደገና ወደ ጋንዲ ሆስፒታል ሄድኩ፡፡ የተስፋ ቅራሪ ሳይሆን የርግጠኛነት ድፍድፍ ይዣለሁ፡፡
ልክ ሁለትና ሁለት ኣራት እንደሆነ ሁሉ ጋንዲ ሆስፒታል ውስጥ የተኛው ሕፃን
የየወዲያነሽ ልጅ መሆኑን ከዚህም ከዚያም እጅግ በሚገባ አረጋግጫለሁ፡፡
ለመጀመሪያ ጊዜ የአጥንቴን ክፋይና የሥጋዬን ቁራጭ በአንዲት አነስተኛ ጠባብ ኣልጋ ላይ ደስ በሚያሰኝ ጥንቃቄና አኳኋን ተኝቶ አየሁት።
የወዲያነሽ መታሰር ልጁም ልጅዋ መሆኑን ማመኗ አብስለሰለኝ፡፡ ይህ
ሁሉ ከመሆኑ በፊት ባገኘኋት ኖሮ!!... እያልኩ በማሰብ፣ እከሌ እኮ እንዲህ
ቢደረግለት ኖሮ አይሞትም ነበር እያሉ ስለ ሞተ ሰው እንደሚጸጸቱ ሰዎች
በጸጸት ተቃጠልኩ፡፡ ዐመድ እንደገና ዕንጨት አይሆንምና ሐሳቤ በነነ፡፡ ያም ሆነ ይህ ሕይወት እጆቿን ዘርግታ ክቡር ስጦታ ሰጠችኝ! የእኔና የየወዲያነሽ ፍቅር
ጊዚያዊ መሪር ፍሬ አፈራ።
አስታማሚዋ አጠገቤ እንደ ቆመች ጎንበስ ብዬ ደጋግሜ ግንባሩን ሳምኩ፡፡ ከወዲያነሽ ማሕፀን የተገኘውን ክቡር ፍሬ እሷን በሳምኩበት ከንፈሬ
በመሳሜ ልቤ በደስታ ቦረቀች። በሕይወት መቃብር ውስጥ የሚፍለከለከው የወዲያነሽ ኑሮ ግን መንጠቆውን ይዞ አንጠለጠለኝ፡፡ በጸጥታ የሚያንቀላፋውን ሕፃን እየተመለከትኩ 'ጌታነህ! አንተ ጌታነህ! ዛሬ ደግሞ ሌላ
፡
፡
#ክፍል_አስራ_ሦስት
፡
፡
#ድርሰት_ኀይለመለኮት_መዋዕል
...ስሜቴ በመጠኑ በመለወጡ ደስታ መሰል ሁኔታ ተሰማኝ። ደስታዬ እርሷ በመታስሯ ሳይሆን እርሷ ትሆን በማለት ሲዋልል የሰነበተው ጥርጣሬዬ ወደ
አንድ መጠነኛ ውጤት በመቃረቡ ነበር፡፡ ወደ ውጪ ወጣ ብዬ ወደ ግራ ተጠመዘዝኩ። ጥቂት ርምጃዎች እንደ ተራመድኩ ፊቴን ወደ ሰሜን መለስኩ፡፡
እስር ቤቱ ከፖሊስ ጣቢያው በስተጀርባ ነው፡፡ አረማመዴ ፈጠን ያለ ስለነበር
ጠበንጃ ይዞ የቆመው ዘብ «ቁም ወዴት ትሄዳለህ?» አለኝ። ሥርዓት እንደጣስኩ
ገባኝ፡፡
ቃሉ ቃለ ሕግ በመሆኗ ቀጥ አልኩ፡፡ ቀጠን ሳለች አስደንጋጭ የቁጣ
ድምፅ «ማንን ነው የምትፈልገው?» አለኝ።
«አንዲት ሴት እስረኛ ለመጠየቅ ነው?» ብዬ ከቆምኩበት ሳልንቀሳቀስ
መለስኩለት። ለአካባቢው ፍፁም እንግዳ መሆኔ ገባው:: ውስጡ ትሁት እንደሆነ
ተሰማኝ፡፡ ፈገግ አለልኝ። ፈገግታው እለመቆጣቱን ስላስረዳኝ አራት እርምጃዎች ወደፊት ቀጠልኩ፡፡ እሷ መሆኗን ባላረጋግጥም የወዲያነሽን እስረኛ በማለቴ የልቤ ግርማ ሞገስ ተገፈፈ፡፡ በወታደሩና በእኔ መካከል ከስድስት ደኅና ደኅና ርምጃ
የማይበልጥ ርቀት ነበር፡፡
«ምን ይዘሃል? ባዶ እጅህን ነው እንዴ እስረኛ ጥሩልኝ የምትለው? እስረኛ እኮ በማንኛውም ሰዓት አይጠየቅም፡፡ የተወሰነ ጊዜ አለው» አለ አሁንም
በመጠነኛ ፈገግታ። አነጋገሩ የሰውየውን የፈቃደኝነት ስሜት ስላስረዳኝ ሁለት
እርምጃዎች ጨመርኩ፡፡
«ገና እርሷ መሆኗንም አላረጋገጥኩ፡ መጀመሪያ ላረጋግጥ ብዬ» ሳልጨርስ አይኖቼ ዕንባ አቀረሩ፡፡ ጊዜም አልሰጡኝ፡ ተንጠባጠቡ። እምብዛም ጥልቅ ኀዘን በማይታይበት ፊቴ ላይ ዕንባ ሲወርድ በማየቱ፣
«ምነው ምን ነካህ? ወንድ ልጅ ያውም አንተን የሚያህል ያለቅሳል እንዴ?» አለኝ፡፡
«ምንም አልሆንኩ፡ እንዲያው ብቻ...»
«ለመሆኑ ማን ትባላለች?»
«የወዲያነሽ ትባላለች?»።
«እረግ! ኧረ! ያቺን ዕብድ አይሏት ጤነኛ ነው እንዴ? እሷማ ያቻትልህ! ያቺው ተጨብጣ ተቀምጣልሃለች! በል ሂድ! ፈጠን በል! ታዲያ ሥርዓቱን ባለማወቅህና እደጅ በመሆኗ ነው እንጂ እቤት ውስጥ ብትሆን ኖሮ
አይፈቀድም ነበር። እዚህ ድረስም አይመጣም ሰዓቱም ገና ነው» ብሎ አደራ አዘል ፈቃድ ሰጠኝ። አጠገቧ ከመድረሴ በፊት ትንሽ ራቅ ብዬ ቆምኩ::
ሲሽመደመድ የሰነበተው ጥርጣሬዩ ቀና አለ፡፡
ቀሚሷ ተዘነጣጥሎ ተቀዷል፡፡ እግሯ በእሳት የተለበለበ የክትክታ ዕንጨት መስሎ ዐልፎ አልፎ ልብሷ ላይ ጭቃ ተለጥፏል። የተራቆተው ግራ ቀኝ ክንዷ ዐመድ የተነሰነሰበት መስሎ ጽጉሯ እዚህና እዚያ የተነቀለ የጓያ ማሳ
መስሏል። መናገርም መራመድም አቃተኝ፡፡ የወዲያነሽ ጉስቁልና ለሁለተኛ ጊዜ አናቴ ላይ ተከመረ፡፡
ጥርጣሬዬ ጥርጣሬ መሆኑ ቀረ። ለየለት። የወጺያነሽ ተገኘች! ያም ሆነ ይህ የፍቅር ዐይኖቼ አላምጠው ዋጧት እንጂ አልተጸየፏትም። አእምሮዬ ውስጥ
የፍቅር ደማቅ ነበልባል በራ እንጂ የጥላቻና የንቀት ጥቁር ማቅ አልተሸመነም።አንድ ቀጠን ያለ ድምፅ ከበስተጀርባዬ ቶሉ በል እንጂ ሰውዩ!» ሲለኝ ሰማሁ:: በሐሳብ ከማንቀላፋበት አጭር ሰመመን ባነንኩ፡፡ ወደፊት ራመድ ብዪ ከወዲያነሽ አጠገብ ቆምኩ፡፡ ጉልበቷ ላይ ተደፍታ ስለነበር ድንገት ስናገር እንዳትደነግጥ የቆምኩበትን ሸካራ ንጥፍ ድንጋይ በቀኝ እግሬ ረመረምኩት።የፈራሁት አልቀረም፣ በድንጋጤ ባንና ተነሣች። በጣም ከስታለች። ፊቷ ጢስ የጠገበ ቋንጣ መስሏል፡፡ ልብ ብሎ ባላየ ዓይን ቀና ብላ አየችኝ። ማን መሆኔን አላወቀችም፡፡
አገጯን በእግሮቿ መሃል አስገብታ እግር እግሬን እየተመከለተች
«ምነው? ምን አጠፋሁ? ወድጀ እኮ አይደለም! ምን አባቴ ላድርግ! የሚላስና
የሚቀመስ በማጣቴ በረሃብና በችግር ከሚሞት ለነፍሴ ያለ ወስዶ እንዲያሳድገው ብዬ መንገድ ዳር አስቀመጥኩት፡፡ ምነው ሞቴን ባቀረበው?» ብላ ንግግሯን እንደ
ጨረሰች ቀና ስትል የሻገተ እንቀልባ በመሰለው ጉንጫ ላይ ዕንባዋ ተዝረበረበ።
በቁጣ ስሜት ዐይኗን አፍጥጣ «ከዚህ ወዲያ ምን እሆናለሁ ግደሉኝ!
ስቀሉኝ! አንጠልጥለኝ?» አለችና ጉልበቷ ላይ ደፋ አለች።
ጐንበስ ብዬ የቀኝ እጅ ክንፏን ያዝኩና «እኔ ነኝ እኮ የወዲያነሽ፣ እኔ ጌታነህ እኮ ነኝ» አልኳት፡፡ ቀስ ብላ ቀና ካለች በኋላ አፏን በፍርሃትና በድንጋጤ ከፈተችው፡፡ በሰውነቷ ውስጥ ይገኛል ተብሎ በማይገመት እንቅስቃሴ ተነስታ
አንገቴ ላይ ተጠመጠመች፡፡ እንዲህ ዓይነቱ ሁኔታ አይፈቀድም ያለኝ ፖሊስ
ምን ይል ይሆን በማለት ፈራሁ፡፡ መንማና ክንዶቿ ሥጋው ተፈቅፍቆ የወደቀ አጥንት እንጂ ሥጋ የለበሱ አይመስሉም፡፡ አንገቴ ላይ ተጠምጥማ እዬዬዋን ለቀቀችው፡፡ ተንሰቀሰቀች። የሟሸሹ ጉንጮችዋን ሳምኳቸው:: ደርቆና ተሰነጣጥቆ
ያረረ ደረቆት የሚመስለው ከንፈሯ ሻካራ ድንጋይ መስሏል። ያ ዝንፍልፍልና
የውበቷ ደረባ የነበረው ጸጉሯ ተሸላልቷል። አምክ እምክ የሚሽተው ጠረኗ የሥቃይዋን፡ ብዛት ያስረዳል፡፡ አይቼ ሳልጠግባትና አንዳች ነገር እንኳ ጠይቄ ሳልረዳ ፖሊሱ “በቃህ!» ብሎኝ ተመለስኩ:: እንባዋን እየረጨችና እያለቀሰች ተለያየን።
"እኔና የወዲያነሽ ተለያይተን የምንቆየው እስከ መቼ ይሆን ብዬ ራሴን ጠየቅሁ። እጅ እግር ላልነበረው ለዚህ ድፍን ጥያቄ አሁን በአሁን መልስ አላገኘሁም፡፡ አዲስ የፈተናና የስራ ገፅ ተከፈተ። ወደ ቤቴ ከመመለሴና የወዲያነሽንም መታሰር ለጉልላት ከመንገሬ ቀደም ብዬ አንድ ነገር ለማከናወን ወሰንኩ። በኪሴ ውስጥ የነበረችኝን የገንዘብ ልክ ዐወቅሁ፡፡ ከዚያም አራዳ ልብስ ተራ ገባሁ፡፡ በግምት አንድ ጥሩ ቀሚስ እና የውስጥ ልብስ፡ በቀድሞ ቁጥሯ አንድ ተራ ጫማ፣ ዋጋው ቀነስ ያለ የብርድ ልብስ ወዲያ ወዲህ ተሯሩጬ ገዛሁ፡፡
ኀዘንና ደስታዬ በመስተካከሉ መፈንጠዣና መተከዣ የሚሆን ምክንያት አገኘሁ፡፡ የገዛሁትን ልብስ በፖሊስ አስመርምሬ ለየወዲያነሽ ሰጥቻት ተመለስኩ፡፡
ከዚያች ዕለት ጀምሮ በየሣልስቱና ባመቸኝ ቁጥር እየተመላለስኩ
መጠየቄን ቀጠልኩ። አብዳለች፣ ወፍፏታል የተባለው ሁሉ ጠንባራ ስሕተት
መሆኑን ከቀን ወደ ቀን ከሁኔታዎቿ አረጋገጥኩ፡፡
ከግራና ቀኝ የቆሰለ ሰው ሁለቱንም ቁስሎቹን ተራ በተራ እንደሚያይና እንደሚያክም ሰው፡ እኔም ልክ ከዐሥር ቀን በኋላ እንደገና ወደ ጋንዲ ሆስፒታል ሄድኩ፡፡ የተስፋ ቅራሪ ሳይሆን የርግጠኛነት ድፍድፍ ይዣለሁ፡፡
ልክ ሁለትና ሁለት ኣራት እንደሆነ ሁሉ ጋንዲ ሆስፒታል ውስጥ የተኛው ሕፃን
የየወዲያነሽ ልጅ መሆኑን ከዚህም ከዚያም እጅግ በሚገባ አረጋግጫለሁ፡፡
ለመጀመሪያ ጊዜ የአጥንቴን ክፋይና የሥጋዬን ቁራጭ በአንዲት አነስተኛ ጠባብ ኣልጋ ላይ ደስ በሚያሰኝ ጥንቃቄና አኳኋን ተኝቶ አየሁት።
የወዲያነሽ መታሰር ልጁም ልጅዋ መሆኑን ማመኗ አብስለሰለኝ፡፡ ይህ
ሁሉ ከመሆኑ በፊት ባገኘኋት ኖሮ!!... እያልኩ በማሰብ፣ እከሌ እኮ እንዲህ
ቢደረግለት ኖሮ አይሞትም ነበር እያሉ ስለ ሞተ ሰው እንደሚጸጸቱ ሰዎች
በጸጸት ተቃጠልኩ፡፡ ዐመድ እንደገና ዕንጨት አይሆንምና ሐሳቤ በነነ፡፡ ያም ሆነ ይህ ሕይወት እጆቿን ዘርግታ ክቡር ስጦታ ሰጠችኝ! የእኔና የየወዲያነሽ ፍቅር
ጊዚያዊ መሪር ፍሬ አፈራ።
አስታማሚዋ አጠገቤ እንደ ቆመች ጎንበስ ብዬ ደጋግሜ ግንባሩን ሳምኩ፡፡ ከወዲያነሽ ማሕፀን የተገኘውን ክቡር ፍሬ እሷን በሳምኩበት ከንፈሬ
በመሳሜ ልቤ በደስታ ቦረቀች። በሕይወት መቃብር ውስጥ የሚፍለከለከው የወዲያነሽ ኑሮ ግን መንጠቆውን ይዞ አንጠለጠለኝ፡፡ በጸጥታ የሚያንቀላፋውን ሕፃን እየተመለከትኩ 'ጌታነህ! አንተ ጌታነህ! ዛሬ ደግሞ ሌላ
👍3
#የወድያነሽ
፡
፡
#ክፍል_አስራ_አራት
፡
፡
#ድርሰት_ኀይለመለኮት_መዋዕል
....«እኔ በበኩሌ ብዙ ጊዜ ነግሬሃለሁ። እናትህም ብትሆን ዘወትር እንደ ለመነችህ ነው:: የተማረ ሰው ጥቅምና ጉዳቱን ለይቶ ማወት ያቅተዋል ብዬ አላስብም፡፡ ርግጥ ነው፡ ዐዋቂም ቢሆን መካሪና ነጋሪ ያስፈልገዋል። ግን ሁልጊዜ የሚመከርና የሚነገር ጤነኛ ሰው አይደለም፡፡ በከንቱ ከምታማስነን ይልቅ ዐይንህን የጣልክባትና የወደድካት የጨዋ ልጅ ካለች ንገረኝ። አለበለዚያም እኔ
የምመርጥልህንና ደኅና ሰው ቤት ገብቼ የማመጣልህን ተቀበል፡፡ እኔማ ካነገርኩህ
ይኸው ሁለት ዓመት ዐለፈ፡፡ ምነው የወንድሞችህንና የእኀቶችህን ልብ ቢሰጥ ብሎ መልሴን ለመስማት ትክ ብሎ አየኝ፡፡
«አየህ አባዬ በማለት በተለመደች አጠሪሬ ንግግሬን ጀመርኩ።
“ማንኛውም ሰው የሚያገባው ራሱን ለማስደሰትና ኑሮውን ለመመሥረት እንጂ
ሌላውን ደስ ለማሰኘት አይደለም፡፡ አንተ የምትመርጥልኝን አልቀበልም ለማለት
ሳይሆን ላንተ የምትስማማህና ደስ የምትልህ ለእኔ ደስ አትለኝም ይሆናል።
"ማንኛውም ሰው እለማወት ወይ ድንቁርና ከተገቢዉ በላይ ብዙ እንዲያደንቅና በጠባብ አስተሳሰብ እንዲሠራ በስውርና በግልጽ ሊያስገድዱት ይችላሉ፡፡ እኔ በመጠኑም ቢሆን ከጠባብ አስተሳሰብ ተላቅቄአለሁ። በአጭሩ እንድታውቅልኝና እንድትገነዘብልኝ የምፈልገው ግን ለመግባባት የሚችል ሕሊና እንጂ ከቀን ወደ ቀን የሚለወጥ ሰብአዊ ውበት ብቻውን ጋብቻን ጽኑና ተፈላጊ መሠረት ሊሰጠው አይችልም» ብዬ ረዘም ባለው አነጋገሬ የምን ይለኝ ጅራፍ እየለመጠጠኝ
በመናገር አይኖቼን ወደ ወለሉ ተክዩ ዝም እልኩ፡፡
«ኤድያ! ኤድያ! ደርሶ መንዘባነን ደስ አይለኝ! የዘንድሮ ወጣቶች ሐሳብና መልስ በየቤቱ ይኸው ሆኗል፡፡ ቁም ነገር የሚሠራ ሰው ብዘ አያወራም፡፡ ጋብቻ የጎበዝና የደፋር ሙያ እንጂ ለሰነፍና ለፈሪ የሚታደግ የጠበል ፃዲቅ
ድርሻ አይደለም፡፡ አስተዋይ ልቦና ያለው እንዳቅሙ ይዘላል፡፡ ያለ መቸኮልህስ
ይሁን በጄ! የአቦ ዕለት ሲሉህ የመድኃኔ ዓለም ዕለት ማለት ግን በዛ፡፡ ዛሬን
እንደ ዛሬ ኑረህ ነገን እንደ ነገ መኖርና ነገን መስለህ መገኘት ቁርጥ ዓላማህና
ፍላጎትህ መሆን አለበት፡፡ ዝምታህ እምቢታ መሆኑን ዐውቃለሁ» ብሎ ከጉዳዩ ጋር የተያያዘውንና ያልተያያዘውን ሁሉ ተናግሮ ቆጣ አለ፡፡ ከጊዜያዊ ቁጣው
በኋላ ዝምታ እንዳይጀምር በማሰብ “ምናልባት በሰው ልጅ እኩልነት የምታምን ከሆነ ለምን የትልቅ ሰው ልጅ፡ አጥንተ ጥሩ፣ ባለክብር፣ ባለ ዝና እያልክ
ታማርጣለህ? » ብዬ ለመጀመሪያ ጊዜ ቅንጣት ድፍረት የተቀላቀለባትን ጥያቄ
ሆዴ በፍርሃት እየተናጠ አቀረብኩኝ።
«አድሮ ጥጃ አለ ያገሬ ሰው ብዙ ጊዜ ነግሬሃለሁ፡ ለምን ነጋ ጠባ
ትጠይቀኛለህ? በማለት ንግግሩን ሲጀምር በቁጣ ትክ ብሎ
የማይሆነውንና የማይገባውን ሁሉ አትመኝ"ሐለሙ ሕልመ ወአልቦ ዘረከቡ"
ተብሏል፡፡ ማንም ሰው ቢሆን የኑሮ ደረጃውን መጠበቅና መመልከት አለበት።
እኔ እባትህ ከትልልቅና ካዋቂ ሰዎች ጋር የምውል ነኝ። አንተም እንደ እኔ
መሆን ይገባሃል።
ዝናና ክብር ቀላል ነገር አይምሰልህ፡፡ ከሜዳ ላይ አይታፈስም። የዘመኑ
ሰዎች ለጤና ያድርግላችሁ እንጂ “አለ "አብልሑ ልሳኖሙ ከመ አርዌ ምድር»
እንዳለው ሆናችኋል። የምታመጣት ልጅ ከጨዋ ቤተሰብ የተወለደች፣ ዘርና
ትውልዷ የታወቀና የጠራ መሆን አለበት። ወይራ ከወይራ ነው፡ ስንዴ ከጓያ
አይቀየጥም፡፡ «ከመልኮስኮስ መመንኮስ» ሲባል አልሰማህም እንዴ? «የማንንም ስድ አደግና ቅሬ ከየትም ለቅመህ ዝናና ክብሬን ብታጠፋት አደባባይ አውጥተሀ የገደልከኝ ያህል እቆጥረዋለሁ፡፡ የደሃ ቀርቀቦ ቢንከባለል ከደሃ ደጅ” ምኞትህ ሁሉ ልክስክስ አይሁን» ብሎ ቁጭቱን ለመግለጽ ያህል ራሱን ነቀነቀ።
ያቺ በስንትና ስንት ጊዜ ውስጥ የምታጋጥመኝ ጭቅጭቅ አይሏት
ውይይት አብዛኛውን ጊዜ ፍፃሜዋ አያምርም። የእኔና የእርሱ ሐሳብ በተቃራኒ አቅጣጫ ስለሚጓዝ ከመከራከርና ከመጨነቅ ይልቅ ሰምቼ መለየትን እመርጣለሁ።
«ማንንና እንዴት ለማግባት እንደምፈልግ ለመግለጽ እስከምችል ድረስ
የመዘጋጃ ጊዜ ቢሰጠኝና ከራሴ ጋር ብመክር ጥሩ ነው:: እኔ ግን ከአንዳንድ
ሁኔታዎች በስተቀር ማንኛውም ሰው በተፈጥሮ ዐይን ሲታይና ሲመዘን እኩል
ነው” በሚለው አምናለሁ» ብዬ እምነቴን ገለጽኩ፡፡ ለመነሣት ሲመቻች ጋብቻን
እንደ አንድ ትልቅ ጦርነት የምትፈራው መስለህ ታይተኸኛል። ጋብቻ ማለት
ሌላ ነገር አይምሰልህ፡ ከአንዲት ከምትወዳት ሴት ጋር ለመኖር የምታደርገው የኑሮ ውል ነው፡፡ ከሆነችህ አብረሃት መኖር፡ እንዲያ ሆነም ምን ውጣ ወረድ አለው፡ ደህና ዋይ ብሉ ማሰናበት ነው:: ከዛሬ ጀምሮ ግን አግባ አታግባ እያልኩ አልነታረክም፡፡ አስቦና የሚሻውን ወስኖ ለማደር ከቻለ አቅመ አዳም ከደረሰ ሰው ጋር ስለ ራሱ ጉዳይ መከራከር ከንቱ ድካም ነው::
«አንተማ በልብህ ግን እንደኔ ማለትህ አይቀርም፣ ንገሩኝ ባይ!»
“ከትንሽ ጅረት ውስጥ የምትንሳፈፍ ቅጠል ከትልቁ ኩሬ ውስጥ ስትገባ
ቁጫጭ አህላ ትታያለች፡፡ ዐወቅሁ ብለህ ሙተሃል፡፡ የሰው ልጅ ክፉ ጠላቱ ደግሞ
በውስጡ የታጎረው ሽካራ ሐሳቡ ነው:: ካንጀቴ ነው:: ራስን ለማረምና ለማሻሻልም እኮ ከሌሎች ሰዎች ስሕተት መማርና መረዳት ካስተዋይነታቸውም መልካም መልካሙን መቅሰም ማለፊያ ዘዴ ነው» ብሎ ፈንጠር ብላ በጸጥታ ነጠላ ወደምትቋጨው እናቴ አሻግሮ አየ። ምንም እንኳ ላቀረበው ሐሳብ ተነጻጻሪና የተሻለ መልስ ቢኖረኝም
እያደር የሚንር ቁጣውን በመፍራት ደጓን ዝምታ ቀጠልኩ።
የተጨማደደውን ግንባሩን እየጠራረገ ከተነሣ በኋላ ሐሳቤን በጠቅላላ
የሚቃወም መሆኑን ለማስረዳት ወለሉን በቀኝ እግሩ ጠፍ ጠፍ እደረገው፡፡
«የሚታየው እኮ እንዴትና የት ማደግህ ብቻ አይደለም፡ ከማን መወለድህም ጭምር እንጂ። መልካም አዝመራ የሚገኘው እንደ ገበሬውና እንደ
መሬቱ ብቻ ሳይሆን እንደ ዘሩም ነው» ብሎ በቀጥታ ወደ መኝታ ቤቱ ሔደ::
ወደ ውስጥ ሰምጣ የነበረችው ለስላሳ መቀመጫ ትንሽ በትንሽ በመሙላት ቅርጿ ተስተካከለ።
«እስኪ አሁን በኪዳነ ምሕረትና በእሑድ ምድር ባትጨቃጨቁ ምን ቸገረሀ ልጄ? ነጋ ጠባ ይነግርሃል፤ እርሱ አይደክመው፣ አንተ አይሰለችህ! መጥኔ እቴ! ወዴት አባቴ ልግባላችሁ ይሆን? በዚያ ላይ ደግሞ ስንተዜ ልንገርህ? ሲሆን
ሲሆን አንተና እኔ ምንና ምን? አንተ በትምርትህም ቢሆን አታጣውም፡ አሁን
በዚህ በአንተ ምልልስ የተነሣ ያ ሰበበኛ የደም ብዛቱ ቢነሣ አበሳው ለኛው ነው፡፡
እሞት አገር አድርሶ እንደሚመልሰው ታውቃለህ፡፡ ከሐኪሙ ቤት የሚያመጣውን አንድ ቁና ኪነን ታያለህ፡፡ እሱ በጦም በጸሉት እያለ ባይዘው ኖሮ ይኸነዩ ጥሪኝ አፈር ሆኖ ነበር። እሱ እንደሁ እሱ ነው: አንተ ግን ሲያመር ሲያመር ከፊቱ ገለል በልለት» በማለት ራቅ ብላ የተቀመጠችው እናቴ ምሬቷን ገለጸች፡፡
አሁንም እንደገና ከእናቴ ጋር የነገር ገበና ለመጫወት ባለመፈለጌ ሰምቼ
ዝም አልኩ። ዐልፎ በልፎ ከሚሰማው ከእናቴ የጉሮሮ ማስሊያ እህህታ በስተቀር
ቤቱ በዝምታ ታመቀ። በሐሳብ ዐውሎ ነፋስ ከወዲያ ወዲህ በመንገዋለል ላይ
እንዳለሁ ጉልላት ከቸች አለ።
እጆቹን ወደ ኋሳ አጥፍቶ እርስ እርሳቸው ካያያዘ በኋላ አንድ እግሩን ትንሽ ቀደም በማድረግ ጎንበስ ብሎ ለእናቴ ሰላምታ አቀረበ፡፡ እናቴ ስለ ጉልላት ስትናገር «እኔ ከሌላው ከሌላዉ ሁሉ የሚያስደስተኝ ትትናውን እጅ አነሳሡ ነው» ትላለች። ከጎኔ ተቀመጠ። ከእናቴ ጋር ልብ ለልብ ተገናኝቼ እንደማላወራ ስለሚያውቅ የጋሪ ወሬ ለመክፈት አልፈለገም፡፡
፡
፡
#ክፍል_አስራ_አራት
፡
፡
#ድርሰት_ኀይለመለኮት_መዋዕል
....«እኔ በበኩሌ ብዙ ጊዜ ነግሬሃለሁ። እናትህም ብትሆን ዘወትር እንደ ለመነችህ ነው:: የተማረ ሰው ጥቅምና ጉዳቱን ለይቶ ማወት ያቅተዋል ብዬ አላስብም፡፡ ርግጥ ነው፡ ዐዋቂም ቢሆን መካሪና ነጋሪ ያስፈልገዋል። ግን ሁልጊዜ የሚመከርና የሚነገር ጤነኛ ሰው አይደለም፡፡ በከንቱ ከምታማስነን ይልቅ ዐይንህን የጣልክባትና የወደድካት የጨዋ ልጅ ካለች ንገረኝ። አለበለዚያም እኔ
የምመርጥልህንና ደኅና ሰው ቤት ገብቼ የማመጣልህን ተቀበል፡፡ እኔማ ካነገርኩህ
ይኸው ሁለት ዓመት ዐለፈ፡፡ ምነው የወንድሞችህንና የእኀቶችህን ልብ ቢሰጥ ብሎ መልሴን ለመስማት ትክ ብሎ አየኝ፡፡
«አየህ አባዬ በማለት በተለመደች አጠሪሬ ንግግሬን ጀመርኩ።
“ማንኛውም ሰው የሚያገባው ራሱን ለማስደሰትና ኑሮውን ለመመሥረት እንጂ
ሌላውን ደስ ለማሰኘት አይደለም፡፡ አንተ የምትመርጥልኝን አልቀበልም ለማለት
ሳይሆን ላንተ የምትስማማህና ደስ የምትልህ ለእኔ ደስ አትለኝም ይሆናል።
"ማንኛውም ሰው እለማወት ወይ ድንቁርና ከተገቢዉ በላይ ብዙ እንዲያደንቅና በጠባብ አስተሳሰብ እንዲሠራ በስውርና በግልጽ ሊያስገድዱት ይችላሉ፡፡ እኔ በመጠኑም ቢሆን ከጠባብ አስተሳሰብ ተላቅቄአለሁ። በአጭሩ እንድታውቅልኝና እንድትገነዘብልኝ የምፈልገው ግን ለመግባባት የሚችል ሕሊና እንጂ ከቀን ወደ ቀን የሚለወጥ ሰብአዊ ውበት ብቻውን ጋብቻን ጽኑና ተፈላጊ መሠረት ሊሰጠው አይችልም» ብዬ ረዘም ባለው አነጋገሬ የምን ይለኝ ጅራፍ እየለመጠጠኝ
በመናገር አይኖቼን ወደ ወለሉ ተክዩ ዝም እልኩ፡፡
«ኤድያ! ኤድያ! ደርሶ መንዘባነን ደስ አይለኝ! የዘንድሮ ወጣቶች ሐሳብና መልስ በየቤቱ ይኸው ሆኗል፡፡ ቁም ነገር የሚሠራ ሰው ብዘ አያወራም፡፡ ጋብቻ የጎበዝና የደፋር ሙያ እንጂ ለሰነፍና ለፈሪ የሚታደግ የጠበል ፃዲቅ
ድርሻ አይደለም፡፡ አስተዋይ ልቦና ያለው እንዳቅሙ ይዘላል፡፡ ያለ መቸኮልህስ
ይሁን በጄ! የአቦ ዕለት ሲሉህ የመድኃኔ ዓለም ዕለት ማለት ግን በዛ፡፡ ዛሬን
እንደ ዛሬ ኑረህ ነገን እንደ ነገ መኖርና ነገን መስለህ መገኘት ቁርጥ ዓላማህና
ፍላጎትህ መሆን አለበት፡፡ ዝምታህ እምቢታ መሆኑን ዐውቃለሁ» ብሎ ከጉዳዩ ጋር የተያያዘውንና ያልተያያዘውን ሁሉ ተናግሮ ቆጣ አለ፡፡ ከጊዜያዊ ቁጣው
በኋላ ዝምታ እንዳይጀምር በማሰብ “ምናልባት በሰው ልጅ እኩልነት የምታምን ከሆነ ለምን የትልቅ ሰው ልጅ፡ አጥንተ ጥሩ፣ ባለክብር፣ ባለ ዝና እያልክ
ታማርጣለህ? » ብዬ ለመጀመሪያ ጊዜ ቅንጣት ድፍረት የተቀላቀለባትን ጥያቄ
ሆዴ በፍርሃት እየተናጠ አቀረብኩኝ።
«አድሮ ጥጃ አለ ያገሬ ሰው ብዙ ጊዜ ነግሬሃለሁ፡ ለምን ነጋ ጠባ
ትጠይቀኛለህ? በማለት ንግግሩን ሲጀምር በቁጣ ትክ ብሎ
የማይሆነውንና የማይገባውን ሁሉ አትመኝ"ሐለሙ ሕልመ ወአልቦ ዘረከቡ"
ተብሏል፡፡ ማንም ሰው ቢሆን የኑሮ ደረጃውን መጠበቅና መመልከት አለበት።
እኔ እባትህ ከትልልቅና ካዋቂ ሰዎች ጋር የምውል ነኝ። አንተም እንደ እኔ
መሆን ይገባሃል።
ዝናና ክብር ቀላል ነገር አይምሰልህ፡፡ ከሜዳ ላይ አይታፈስም። የዘመኑ
ሰዎች ለጤና ያድርግላችሁ እንጂ “አለ "አብልሑ ልሳኖሙ ከመ አርዌ ምድር»
እንዳለው ሆናችኋል። የምታመጣት ልጅ ከጨዋ ቤተሰብ የተወለደች፣ ዘርና
ትውልዷ የታወቀና የጠራ መሆን አለበት። ወይራ ከወይራ ነው፡ ስንዴ ከጓያ
አይቀየጥም፡፡ «ከመልኮስኮስ መመንኮስ» ሲባል አልሰማህም እንዴ? «የማንንም ስድ አደግና ቅሬ ከየትም ለቅመህ ዝናና ክብሬን ብታጠፋት አደባባይ አውጥተሀ የገደልከኝ ያህል እቆጥረዋለሁ፡፡ የደሃ ቀርቀቦ ቢንከባለል ከደሃ ደጅ” ምኞትህ ሁሉ ልክስክስ አይሁን» ብሎ ቁጭቱን ለመግለጽ ያህል ራሱን ነቀነቀ።
ያቺ በስንትና ስንት ጊዜ ውስጥ የምታጋጥመኝ ጭቅጭቅ አይሏት
ውይይት አብዛኛውን ጊዜ ፍፃሜዋ አያምርም። የእኔና የእርሱ ሐሳብ በተቃራኒ አቅጣጫ ስለሚጓዝ ከመከራከርና ከመጨነቅ ይልቅ ሰምቼ መለየትን እመርጣለሁ።
«ማንንና እንዴት ለማግባት እንደምፈልግ ለመግለጽ እስከምችል ድረስ
የመዘጋጃ ጊዜ ቢሰጠኝና ከራሴ ጋር ብመክር ጥሩ ነው:: እኔ ግን ከአንዳንድ
ሁኔታዎች በስተቀር ማንኛውም ሰው በተፈጥሮ ዐይን ሲታይና ሲመዘን እኩል
ነው” በሚለው አምናለሁ» ብዬ እምነቴን ገለጽኩ፡፡ ለመነሣት ሲመቻች ጋብቻን
እንደ አንድ ትልቅ ጦርነት የምትፈራው መስለህ ታይተኸኛል። ጋብቻ ማለት
ሌላ ነገር አይምሰልህ፡ ከአንዲት ከምትወዳት ሴት ጋር ለመኖር የምታደርገው የኑሮ ውል ነው፡፡ ከሆነችህ አብረሃት መኖር፡ እንዲያ ሆነም ምን ውጣ ወረድ አለው፡ ደህና ዋይ ብሉ ማሰናበት ነው:: ከዛሬ ጀምሮ ግን አግባ አታግባ እያልኩ አልነታረክም፡፡ አስቦና የሚሻውን ወስኖ ለማደር ከቻለ አቅመ አዳም ከደረሰ ሰው ጋር ስለ ራሱ ጉዳይ መከራከር ከንቱ ድካም ነው::
«አንተማ በልብህ ግን እንደኔ ማለትህ አይቀርም፣ ንገሩኝ ባይ!»
“ከትንሽ ጅረት ውስጥ የምትንሳፈፍ ቅጠል ከትልቁ ኩሬ ውስጥ ስትገባ
ቁጫጭ አህላ ትታያለች፡፡ ዐወቅሁ ብለህ ሙተሃል፡፡ የሰው ልጅ ክፉ ጠላቱ ደግሞ
በውስጡ የታጎረው ሽካራ ሐሳቡ ነው:: ካንጀቴ ነው:: ራስን ለማረምና ለማሻሻልም እኮ ከሌሎች ሰዎች ስሕተት መማርና መረዳት ካስተዋይነታቸውም መልካም መልካሙን መቅሰም ማለፊያ ዘዴ ነው» ብሎ ፈንጠር ብላ በጸጥታ ነጠላ ወደምትቋጨው እናቴ አሻግሮ አየ። ምንም እንኳ ላቀረበው ሐሳብ ተነጻጻሪና የተሻለ መልስ ቢኖረኝም
እያደር የሚንር ቁጣውን በመፍራት ደጓን ዝምታ ቀጠልኩ።
የተጨማደደውን ግንባሩን እየጠራረገ ከተነሣ በኋላ ሐሳቤን በጠቅላላ
የሚቃወም መሆኑን ለማስረዳት ወለሉን በቀኝ እግሩ ጠፍ ጠፍ እደረገው፡፡
«የሚታየው እኮ እንዴትና የት ማደግህ ብቻ አይደለም፡ ከማን መወለድህም ጭምር እንጂ። መልካም አዝመራ የሚገኘው እንደ ገበሬውና እንደ
መሬቱ ብቻ ሳይሆን እንደ ዘሩም ነው» ብሎ በቀጥታ ወደ መኝታ ቤቱ ሔደ::
ወደ ውስጥ ሰምጣ የነበረችው ለስላሳ መቀመጫ ትንሽ በትንሽ በመሙላት ቅርጿ ተስተካከለ።
«እስኪ አሁን በኪዳነ ምሕረትና በእሑድ ምድር ባትጨቃጨቁ ምን ቸገረሀ ልጄ? ነጋ ጠባ ይነግርሃል፤ እርሱ አይደክመው፣ አንተ አይሰለችህ! መጥኔ እቴ! ወዴት አባቴ ልግባላችሁ ይሆን? በዚያ ላይ ደግሞ ስንተዜ ልንገርህ? ሲሆን
ሲሆን አንተና እኔ ምንና ምን? አንተ በትምርትህም ቢሆን አታጣውም፡ አሁን
በዚህ በአንተ ምልልስ የተነሣ ያ ሰበበኛ የደም ብዛቱ ቢነሣ አበሳው ለኛው ነው፡፡
እሞት አገር አድርሶ እንደሚመልሰው ታውቃለህ፡፡ ከሐኪሙ ቤት የሚያመጣውን አንድ ቁና ኪነን ታያለህ፡፡ እሱ በጦም በጸሉት እያለ ባይዘው ኖሮ ይኸነዩ ጥሪኝ አፈር ሆኖ ነበር። እሱ እንደሁ እሱ ነው: አንተ ግን ሲያመር ሲያመር ከፊቱ ገለል በልለት» በማለት ራቅ ብላ የተቀመጠችው እናቴ ምሬቷን ገለጸች፡፡
አሁንም እንደገና ከእናቴ ጋር የነገር ገበና ለመጫወት ባለመፈለጌ ሰምቼ
ዝም አልኩ። ዐልፎ በልፎ ከሚሰማው ከእናቴ የጉሮሮ ማስሊያ እህህታ በስተቀር
ቤቱ በዝምታ ታመቀ። በሐሳብ ዐውሎ ነፋስ ከወዲያ ወዲህ በመንገዋለል ላይ
እንዳለሁ ጉልላት ከቸች አለ።
እጆቹን ወደ ኋሳ አጥፍቶ እርስ እርሳቸው ካያያዘ በኋላ አንድ እግሩን ትንሽ ቀደም በማድረግ ጎንበስ ብሎ ለእናቴ ሰላምታ አቀረበ፡፡ እናቴ ስለ ጉልላት ስትናገር «እኔ ከሌላው ከሌላዉ ሁሉ የሚያስደስተኝ ትትናውን እጅ አነሳሡ ነው» ትላለች። ከጎኔ ተቀመጠ። ከእናቴ ጋር ልብ ለልብ ተገናኝቼ እንደማላወራ ስለሚያውቅ የጋሪ ወሬ ለመክፈት አልፈለገም፡፡
👍1
#የወድያነሽ
፡
፡
#ክፍል_አስራ_አምስት
፡
፡
#ድርሰት_ኀይለመለኮት_መዋዕል
....በመካከላችን ባሉት አጥሮች መኻል የነበረው አንድ ረጂም ርምጃ የሚሆን ርቀት በእኔና በየወዲያነሽ መካከል የሚገኝ ጥልቅ የሥቃይ አዘቅት ሆነ።
ፊቴን ከእርሷ መለስ አድርጌ በዐይኖቼ ዙሪያ የሚንቀዋለለውን እንባ
በመሐረቤ አበስኩና “አይዞሽ ተስፋ አትቁረጪ! ሰው በሕይወቱ ከዚህ የባሰና
የከፋ መከራ ያጋጥመዋል። በተቻለሽ ዐቅም ሁሉንም ነገር ለመቋቋም ሞክሪ።
ላለፈው ነገር ሁሉ ያላግባብ ከተጸጸትሽ ግን እንደገና ደግሞ በራስሽ ብስጭት
ወህኒ ቤት ውስጥ ገባሽ ማለት ነው» ስላት ከበፊቱ የበለጠ ሆድ ባሳትና
ስቅስቅታዋ ትከሻዋን ሽቅብ እስኪያዘልለው ድረስ ልቅሶዋነ ቀጠለች፡፡
የወዲያነሽ በቀጠሮ ወህኒ ቤት ከገባች ጀምሮ ሕሊናዋ ቀዘቀዘ፡፡ ፊቷ የትካዜ ጭጋግ ለበሰ። እረማመዷ በኃዘን ጓግ ተቀየደ፡፡ ዐይኖቿ ሠረጉ፡፡ ነጣ ብሎ ወፈር ያለውን የመከለያ ፍርግርግ የእግር ዕንጨት በእጅዋ እያሸች እንገቷን
ሰበር አድርጋ ዕንባዋን ታንዶለዱለው ጀመር፡፡ በአፍንጫዋ የቀኝ ቀዳዳ በኩል ብቅ ያለችውን ራሰ ድቡልቡል ቀጭን ንፍጥ በግራ እጁዋ ቁርጥ አድርጋ
አሽቀነጠረቻት፡፡
ጎንበስ ብላ በውስጥ ልብሷ ዐይንና አፍንጫዋን እባብሳ ቀና አለች፡፡ዐይኖቿ ድልህ መሰሉ። ክንፈሮቿ መላቀቅ እየተሳናቸው «እኔ መቼም ዕድሌ
ነው፡ በጎደሎ ቀን ነው የተፈጠርኩት፡እግዚአብሔርም ከላደለኝ። አንተ ግን
ለእኔ ብለህ አትንገላታ፡፡ የልጄን ነገር አደራ አደራ በምድር አደራ በሰማይ!
የእኔ ሥራ እኔኑ ያንገበግበኛል፡፡ መቼም የሚሉኝን እስከሚሉኝ ታንቄ አልሞት።
ዐልፎ ዐልፎ ከጠየቅኸኝ ይበቃኛል። ያዩህና የሰሙብህ እንደሆነ ይጣሉሃል» ብላ ንግግሯን ሳትጨርስ ትንፋሿ እጥር ቅትት አለ። ከነዚያ በቀላሉ እንባ
ከሚያፈልቁት ዐይኖቿ ያለማቋረጥ እንባ ወረደ። የተጠቂነቷ መግለጫ ነው::
የወሰድኩላትን ልዩ ልዩ ዕቃና ምግብ በሴቷ ወታደር አቀባይነት ከሰጠኋት በኋላ በዝምታ ቆምኩ፡፡ ዓይኖቿ ምስጋና አቀረቡ፡፡ «በይ እንግዲህ በደኅና ሰንብች ! እየመጣሁ እጠይቅሻለሁ፡፡ የሚፈቀደውንና የሚያስፈልግሽን ሁሉ
ጠይቂኝ፡ አመጣልሻለሁ፡፡ ስለ ልጁም በፍጹም አትሥጊ፡ አታስቢ፡ እኔ አለሁለት»
ብያት ትዝታዬን ጥዬላት መንገድ ገባሁ::
አላስችል ስላለኝ መለስ ብዬ ሳያት፡
እሷም ቆማ ትመለከተኝ ነበር። እግሮቼ ተግመድምደው መራመድ አቃተኝ
ዐይኖቼ በናፍቆት አዩዋት። የሰጠኋትን ኮተት አንሥታ በዝግታ ሔደች።
የውስጤን ብስጭትና ጥጥር ትካዜ ዘልቃ ለማወቅ የቻለች ይመስል
ቅስሟ ተሰብሮ በወጣትነቷ ስለጠወለገችው የየወዲያነሽ ሕይወት
እያሰላሰልኩ ሜክሲኮ አደባባይ ደረስኩ፡፡ ከዚያም እስከ አራዳ ጊዮርጊስ በታክሲ
ተጓዝኩ። ሰባት ሰዓት ሊሞላ ጥቂት ደቂቃዎች ቀርተው ነበር። በጠራው ሰማይ ላይ የምትንተገተገው ፀሐይ የዕለቱን ከፍተኛ የሰማይ ጣራ ነክታለች፡፡ ለምሳ ወደ ቤት ከመግባቴ በፊት ትንሽ ዘወርወር ማለት ስለፈለግሁ ወደ አቡነ ጴጥሮስ ሐውልት ሳሽቆለቁል የዕለቷን ከባድ የፀሐይ ሐሩር ለመከላከል ከራሱ በላይ የታጠፈ ጋዜጣ ዘርግቶ ከወደ ታች ሲያሻቅብ ከጉልላት ጋር ተገጣጠምን።
በየሳምንቱ እሑድ ወደ ወህኒ ቤት እንደምሔድ ስለሚያውቅ ገና ሰላምታ ሳይሰጠኝ «አልሔድኩም ብቻ እንዳትለኝ? ደርሰህ መጣህ እንዴ?» ብሎ
ጠየቀኝ፡፡
መልስ ሳልሰጠው ተጨባበጥን፡፡ «ደርሼ
መመለሴ ነው» ብዬ እርግጠኛነቴን ለማስረዳት ትኩር ብዬ አየሁት። ከግንባሩ በላይ ፀጉሩጥጋ ጥግ እንዲሁም ባፍንጫው አካባቢ የሚታየውን ያቸፈቸፈ ወዙን እየተመለከትኩ ዛሬም ተሠርታ አልወጣች እንዴ ያቺ መኪናህ?» ብዬ ፈገግሁ፡፡
የመኪናው ነገር ያስመረረው መሆኑን ፊቱን አቀጭሞ «እባክህ የሷን ነገር ተወኝ! ትላንት አንዱ ተጠግኖ እንደሁ ዛሬ ደግሞ ሌላው ይነክታል።
ችግር ነው ጌትነት” አሉ። ከናካቴው እኮ ውልቅልቋ ቢወጣ እኔም እፎይ እል
ነበር:: የዘወትር በሽተኛ እስቸገረ መድኃኒተኛ” ሆነብኝ ብሎ እንዳበቃ እኔም
ተመልሼ አሻቀብኩ፡፡
አሁንም የዚያቹ የመኪና ነገር ውስጥ ውስጡን ስለ ከነካነው «ከየትም
ከየትም ብዬ እለቃቃምና ባንድ ፊቱ አሳምሬ አሳድሳታለሁ፡፡ እንኩትኩቷ ወጥቶ እስክትወድቅ ድረስ ሌላ አልገዛም በደንብ አሳድሳታለሁ፡፡ አንተም እሑድ እሑድ ወደ የወዲያነሽ ትሔድባታለህ» ብሎ ድንገት ቀጥ ብሎ ቆመ፡፡
ከተማ ገብቶ መንገድ እንደ ጠፋው ገጠሬ በዙሪያችን ያሉትን መንገዶች
ተራ በተራ ተመለከታቸው:: ወዲያው ባጠገባችን ሁለት ደም ግባታቸው
የሚማርክ ወጣት ሴቶች ዐለፉ። የጉልላትን ትከሻ በትከሻዬ ገጨት አድርጌ «ያቺ ልጅ፣ ያቺ በስተግራ በኩል ያለችው እታለማሁን አትመስልም?» አልኩት።
አታለማሁ ጉልላት በጣም የወደዳትና የእርሷ ፍቅር ምን ጊዜም ቢሆን
ከልቤ ውስጥ አይፋቅም» እያለ የሚያነሣት ፍቅረኛው ነበረች። ሆኖም
ፍቅራቸው በነበር መቃብር ውስጥ ተቀብሯል።
“የማን ናት እታለማሁ? እታለማሁን እኔ ብቻ ላሰላስላት፣ እኔ ብቻ በትዝታ ላመንዥካት። አታስታውሰኝ እያልኩ ብዙ ጊዜ ለምኜህ አልነበረም።”ብሎ ዐይን ዐይኔን በቅሬታ እያየ ቆም አለ፡፡
«በሕይወቴ የምጠላውና እንደ ውርደት የምቆጥረው ነገር ሌሎች ክብራቸውንና ዝናቸውን ለመጠበቅና ከፍ ለማድረግ ብለው አንድን እንደ ጥፋት የማይቆጠር ነገር በማጋነን ይቅርታ ጠይቅ ሲሉና ሲንጠራሩብኝ ብቻ ነው፡፡ለእነርሱ የሚመራቸውን ነገር ለምን ቅመስልኝ ይሉኛል? የእርሷ ነገር እንደዚያ
ነበር። ታውቀዋለህ፡፡ ስለዚህ ለወደፊቱ እታንሣት ...» ካለ በኋላ በቁጣ ወደ ፊት
ቸር እለ። ወደ ሀር ፍቅር የምታዘቀዝቀዋ መንገድ በቁልቁለታማነቷ እንዘፍ
እንዘፍ አደረገችው::
«ታዲያ ምን አጠፋሁ? ትመስላለች ማለት ነች ማለት አይደለም» ብዬ መለስኩለት፡፡ «ስማ ልንገርህ» ብሎ ከነማይዘልቅ ቁጣው ቆመ፡፡ “የምትጠላውንም
ሆነ የምትወደውን ሰው ስም “ማስታወስ ድርጊቱን ሁሉ እንድታስታውስ ያደርግሃል፡ከእርሷ በፊት ማንንም እንደ እርሷ እንዳላፈቀርኩ የማውቀው እኔው
ብቻ ነኝ፡፡ በምድር ላይም ሆነ በማላውቀው ጠፈር ውስጥ የሚገኙትን ጥሩና ውብ ነገሮች የምመኘው ለእኔ ሳይሆን ለእርሷ ነበር፡፡ ሕይወት በፈገግታ እንድትቀበላት የምጓጓው ለእርሷ ነበር ብዬ ስናገር ሰምተሃል። አሁንም ቢሆን የከበረ ፍቅሯን ሳላጎድፍ እና ሳላጠፋ በልቤ ውስጥ ይዤው እኖራለሁ፡፡ እሷ ግን የትም ትኑር የትም፣ ትዝ ባለችኝ ቁጥር ያን ያለፈ ጊዜ መለስ ብዪ የማይባት የትዝታ መነፅሬ ናት፡፡ ስሟን አእላፋት ጊዜ ብታነሳልኝና ስለ እርሷም ብትተርክልኝ የሕሊናዩ ከርስ አይጠግብም። ግን አታንሣብኝ በውስጤ አዳፍና የተወችው የፍቅር ረመጥ በትዝታዋ በተጫረ ቁጥር የሚያንገበግበኝ በቂዩ ነው» ብሎ
እባክህን በምትል አኳኋን እንገቱን ዘንበል አደረገ፡፡
ከዚያ በኋላ እኔም ስለ እርሷ አላነሣውም፡፡ ጉልላት አንድ ነገር ካፈቀረና
ካመነበት ትክክለኛ ነገርም መስሎ ከታየው እስከ መጨረሻው መጽናት እንጂ
መወላወል አይወድም።
የወዲያነሽ ጋር የጀመርኩትን ፍቅራዊ ግንኙነት እንድገፋበትና ትክክለኛ ፍጻሜውንም ለማየት ቆርጬ እንድነሣ ያለ ማቋረጥ አበረታታኝ። እስከ
ኮከበ ጽባሕ ትምህርት ቤት ድረስ በታክሲ ሔድን፡፡
ወደ ቤት ስንገባ እናቴና ወይዘሮ የውብዳር ፊት ለፊት ተቀምጠው
ወሬያቸውን ሲሰልቁ ደረስን፡፡ ወይዘሮ የውብዳር ብርጭቆአቸውን እንደ ጨበጡ
መለስ አሉና ኖር የእኔ ልጅ» ብለው ለወጉ ያህል ከመቀመጫቸው ቆነጥነጥ
አሉና ወሬያቸውን ቀጠሉ። በደፈናው ለሁለም እጅ ነሥተን ተቀመጥን፡፡
“የዚያችኛዋስ ምንም አይደል፡ እኔ ያናደደኝ የዚችኛዋ የዚች የከይሲ
፡
፡
#ክፍል_አስራ_አምስት
፡
፡
#ድርሰት_ኀይለመለኮት_መዋዕል
....በመካከላችን ባሉት አጥሮች መኻል የነበረው አንድ ረጂም ርምጃ የሚሆን ርቀት በእኔና በየወዲያነሽ መካከል የሚገኝ ጥልቅ የሥቃይ አዘቅት ሆነ።
ፊቴን ከእርሷ መለስ አድርጌ በዐይኖቼ ዙሪያ የሚንቀዋለለውን እንባ
በመሐረቤ አበስኩና “አይዞሽ ተስፋ አትቁረጪ! ሰው በሕይወቱ ከዚህ የባሰና
የከፋ መከራ ያጋጥመዋል። በተቻለሽ ዐቅም ሁሉንም ነገር ለመቋቋም ሞክሪ።
ላለፈው ነገር ሁሉ ያላግባብ ከተጸጸትሽ ግን እንደገና ደግሞ በራስሽ ብስጭት
ወህኒ ቤት ውስጥ ገባሽ ማለት ነው» ስላት ከበፊቱ የበለጠ ሆድ ባሳትና
ስቅስቅታዋ ትከሻዋን ሽቅብ እስኪያዘልለው ድረስ ልቅሶዋነ ቀጠለች፡፡
የወዲያነሽ በቀጠሮ ወህኒ ቤት ከገባች ጀምሮ ሕሊናዋ ቀዘቀዘ፡፡ ፊቷ የትካዜ ጭጋግ ለበሰ። እረማመዷ በኃዘን ጓግ ተቀየደ፡፡ ዐይኖቿ ሠረጉ፡፡ ነጣ ብሎ ወፈር ያለውን የመከለያ ፍርግርግ የእግር ዕንጨት በእጅዋ እያሸች እንገቷን
ሰበር አድርጋ ዕንባዋን ታንዶለዱለው ጀመር፡፡ በአፍንጫዋ የቀኝ ቀዳዳ በኩል ብቅ ያለችውን ራሰ ድቡልቡል ቀጭን ንፍጥ በግራ እጁዋ ቁርጥ አድርጋ
አሽቀነጠረቻት፡፡
ጎንበስ ብላ በውስጥ ልብሷ ዐይንና አፍንጫዋን እባብሳ ቀና አለች፡፡ዐይኖቿ ድልህ መሰሉ። ክንፈሮቿ መላቀቅ እየተሳናቸው «እኔ መቼም ዕድሌ
ነው፡ በጎደሎ ቀን ነው የተፈጠርኩት፡እግዚአብሔርም ከላደለኝ። አንተ ግን
ለእኔ ብለህ አትንገላታ፡፡ የልጄን ነገር አደራ አደራ በምድር አደራ በሰማይ!
የእኔ ሥራ እኔኑ ያንገበግበኛል፡፡ መቼም የሚሉኝን እስከሚሉኝ ታንቄ አልሞት።
ዐልፎ ዐልፎ ከጠየቅኸኝ ይበቃኛል። ያዩህና የሰሙብህ እንደሆነ ይጣሉሃል» ብላ ንግግሯን ሳትጨርስ ትንፋሿ እጥር ቅትት አለ። ከነዚያ በቀላሉ እንባ
ከሚያፈልቁት ዐይኖቿ ያለማቋረጥ እንባ ወረደ። የተጠቂነቷ መግለጫ ነው::
የወሰድኩላትን ልዩ ልዩ ዕቃና ምግብ በሴቷ ወታደር አቀባይነት ከሰጠኋት በኋላ በዝምታ ቆምኩ፡፡ ዓይኖቿ ምስጋና አቀረቡ፡፡ «በይ እንግዲህ በደኅና ሰንብች ! እየመጣሁ እጠይቅሻለሁ፡፡ የሚፈቀደውንና የሚያስፈልግሽን ሁሉ
ጠይቂኝ፡ አመጣልሻለሁ፡፡ ስለ ልጁም በፍጹም አትሥጊ፡ አታስቢ፡ እኔ አለሁለት»
ብያት ትዝታዬን ጥዬላት መንገድ ገባሁ::
አላስችል ስላለኝ መለስ ብዬ ሳያት፡
እሷም ቆማ ትመለከተኝ ነበር። እግሮቼ ተግመድምደው መራመድ አቃተኝ
ዐይኖቼ በናፍቆት አዩዋት። የሰጠኋትን ኮተት አንሥታ በዝግታ ሔደች።
የውስጤን ብስጭትና ጥጥር ትካዜ ዘልቃ ለማወቅ የቻለች ይመስል
ቅስሟ ተሰብሮ በወጣትነቷ ስለጠወለገችው የየወዲያነሽ ሕይወት
እያሰላሰልኩ ሜክሲኮ አደባባይ ደረስኩ፡፡ ከዚያም እስከ አራዳ ጊዮርጊስ በታክሲ
ተጓዝኩ። ሰባት ሰዓት ሊሞላ ጥቂት ደቂቃዎች ቀርተው ነበር። በጠራው ሰማይ ላይ የምትንተገተገው ፀሐይ የዕለቱን ከፍተኛ የሰማይ ጣራ ነክታለች፡፡ ለምሳ ወደ ቤት ከመግባቴ በፊት ትንሽ ዘወርወር ማለት ስለፈለግሁ ወደ አቡነ ጴጥሮስ ሐውልት ሳሽቆለቁል የዕለቷን ከባድ የፀሐይ ሐሩር ለመከላከል ከራሱ በላይ የታጠፈ ጋዜጣ ዘርግቶ ከወደ ታች ሲያሻቅብ ከጉልላት ጋር ተገጣጠምን።
በየሳምንቱ እሑድ ወደ ወህኒ ቤት እንደምሔድ ስለሚያውቅ ገና ሰላምታ ሳይሰጠኝ «አልሔድኩም ብቻ እንዳትለኝ? ደርሰህ መጣህ እንዴ?» ብሎ
ጠየቀኝ፡፡
መልስ ሳልሰጠው ተጨባበጥን፡፡ «ደርሼ
መመለሴ ነው» ብዬ እርግጠኛነቴን ለማስረዳት ትኩር ብዬ አየሁት። ከግንባሩ በላይ ፀጉሩጥጋ ጥግ እንዲሁም ባፍንጫው አካባቢ የሚታየውን ያቸፈቸፈ ወዙን እየተመለከትኩ ዛሬም ተሠርታ አልወጣች እንዴ ያቺ መኪናህ?» ብዬ ፈገግሁ፡፡
የመኪናው ነገር ያስመረረው መሆኑን ፊቱን አቀጭሞ «እባክህ የሷን ነገር ተወኝ! ትላንት አንዱ ተጠግኖ እንደሁ ዛሬ ደግሞ ሌላው ይነክታል።
ችግር ነው ጌትነት” አሉ። ከናካቴው እኮ ውልቅልቋ ቢወጣ እኔም እፎይ እል
ነበር:: የዘወትር በሽተኛ እስቸገረ መድኃኒተኛ” ሆነብኝ ብሎ እንዳበቃ እኔም
ተመልሼ አሻቀብኩ፡፡
አሁንም የዚያቹ የመኪና ነገር ውስጥ ውስጡን ስለ ከነካነው «ከየትም
ከየትም ብዬ እለቃቃምና ባንድ ፊቱ አሳምሬ አሳድሳታለሁ፡፡ እንኩትኩቷ ወጥቶ እስክትወድቅ ድረስ ሌላ አልገዛም በደንብ አሳድሳታለሁ፡፡ አንተም እሑድ እሑድ ወደ የወዲያነሽ ትሔድባታለህ» ብሎ ድንገት ቀጥ ብሎ ቆመ፡፡
ከተማ ገብቶ መንገድ እንደ ጠፋው ገጠሬ በዙሪያችን ያሉትን መንገዶች
ተራ በተራ ተመለከታቸው:: ወዲያው ባጠገባችን ሁለት ደም ግባታቸው
የሚማርክ ወጣት ሴቶች ዐለፉ። የጉልላትን ትከሻ በትከሻዬ ገጨት አድርጌ «ያቺ ልጅ፣ ያቺ በስተግራ በኩል ያለችው እታለማሁን አትመስልም?» አልኩት።
አታለማሁ ጉልላት በጣም የወደዳትና የእርሷ ፍቅር ምን ጊዜም ቢሆን
ከልቤ ውስጥ አይፋቅም» እያለ የሚያነሣት ፍቅረኛው ነበረች። ሆኖም
ፍቅራቸው በነበር መቃብር ውስጥ ተቀብሯል።
“የማን ናት እታለማሁ? እታለማሁን እኔ ብቻ ላሰላስላት፣ እኔ ብቻ በትዝታ ላመንዥካት። አታስታውሰኝ እያልኩ ብዙ ጊዜ ለምኜህ አልነበረም።”ብሎ ዐይን ዐይኔን በቅሬታ እያየ ቆም አለ፡፡
«በሕይወቴ የምጠላውና እንደ ውርደት የምቆጥረው ነገር ሌሎች ክብራቸውንና ዝናቸውን ለመጠበቅና ከፍ ለማድረግ ብለው አንድን እንደ ጥፋት የማይቆጠር ነገር በማጋነን ይቅርታ ጠይቅ ሲሉና ሲንጠራሩብኝ ብቻ ነው፡፡ለእነርሱ የሚመራቸውን ነገር ለምን ቅመስልኝ ይሉኛል? የእርሷ ነገር እንደዚያ
ነበር። ታውቀዋለህ፡፡ ስለዚህ ለወደፊቱ እታንሣት ...» ካለ በኋላ በቁጣ ወደ ፊት
ቸር እለ። ወደ ሀር ፍቅር የምታዘቀዝቀዋ መንገድ በቁልቁለታማነቷ እንዘፍ
እንዘፍ አደረገችው::
«ታዲያ ምን አጠፋሁ? ትመስላለች ማለት ነች ማለት አይደለም» ብዬ መለስኩለት፡፡ «ስማ ልንገርህ» ብሎ ከነማይዘልቅ ቁጣው ቆመ፡፡ “የምትጠላውንም
ሆነ የምትወደውን ሰው ስም “ማስታወስ ድርጊቱን ሁሉ እንድታስታውስ ያደርግሃል፡ከእርሷ በፊት ማንንም እንደ እርሷ እንዳላፈቀርኩ የማውቀው እኔው
ብቻ ነኝ፡፡ በምድር ላይም ሆነ በማላውቀው ጠፈር ውስጥ የሚገኙትን ጥሩና ውብ ነገሮች የምመኘው ለእኔ ሳይሆን ለእርሷ ነበር፡፡ ሕይወት በፈገግታ እንድትቀበላት የምጓጓው ለእርሷ ነበር ብዬ ስናገር ሰምተሃል። አሁንም ቢሆን የከበረ ፍቅሯን ሳላጎድፍ እና ሳላጠፋ በልቤ ውስጥ ይዤው እኖራለሁ፡፡ እሷ ግን የትም ትኑር የትም፣ ትዝ ባለችኝ ቁጥር ያን ያለፈ ጊዜ መለስ ብዪ የማይባት የትዝታ መነፅሬ ናት፡፡ ስሟን አእላፋት ጊዜ ብታነሳልኝና ስለ እርሷም ብትተርክልኝ የሕሊናዩ ከርስ አይጠግብም። ግን አታንሣብኝ በውስጤ አዳፍና የተወችው የፍቅር ረመጥ በትዝታዋ በተጫረ ቁጥር የሚያንገበግበኝ በቂዩ ነው» ብሎ
እባክህን በምትል አኳኋን እንገቱን ዘንበል አደረገ፡፡
ከዚያ በኋላ እኔም ስለ እርሷ አላነሣውም፡፡ ጉልላት አንድ ነገር ካፈቀረና
ካመነበት ትክክለኛ ነገርም መስሎ ከታየው እስከ መጨረሻው መጽናት እንጂ
መወላወል አይወድም።
የወዲያነሽ ጋር የጀመርኩትን ፍቅራዊ ግንኙነት እንድገፋበትና ትክክለኛ ፍጻሜውንም ለማየት ቆርጬ እንድነሣ ያለ ማቋረጥ አበረታታኝ። እስከ
ኮከበ ጽባሕ ትምህርት ቤት ድረስ በታክሲ ሔድን፡፡
ወደ ቤት ስንገባ እናቴና ወይዘሮ የውብዳር ፊት ለፊት ተቀምጠው
ወሬያቸውን ሲሰልቁ ደረስን፡፡ ወይዘሮ የውብዳር ብርጭቆአቸውን እንደ ጨበጡ
መለስ አሉና ኖር የእኔ ልጅ» ብለው ለወጉ ያህል ከመቀመጫቸው ቆነጥነጥ
አሉና ወሬያቸውን ቀጠሉ። በደፈናው ለሁለም እጅ ነሥተን ተቀመጥን፡፡
“የዚያችኛዋስ ምንም አይደል፡ እኔ ያናደደኝ የዚችኛዋ የዚች የከይሲ
👍3
#የወድያነሽ
፡
፡
#ክፍል_አስራ_ስድስት
፡
፡
#ድርሰት_ኀይለመለኮት_መዋዕል
....የማለዳዋ የጥር ወር ፀሐይ በመሬት ወለል አካባቢ ከየሚዳው! ከየተራራው፣ ከየዛፉ፣ ከየቤቱ፣ ከየጉራንጉሩ ቀዝቃዛ አየር ጋር ትንቅንቅ ገጥማለች። ተፈጥሮ ራሷን በራሷ የምታስተካክልበትና የምትለዋውጥበት ተፈራራቂ ኃይል ስላላት ቀዝቃዛው አየሩ ቀስ በቀስ ተረታ። ለውጥ የተፃራሪ ኃይሎች የግብግብ ውጤት ነው::
በእኔ ሕይወት ውስጥ ግን ጎልቶ የሚጠቀስ ለውጥ ባለመገኘቱ ሕሊናዩ
እየቀዘቀዘ ከመሔድ በቀር የብርታት ለውጥ አልታየብኝም፡፡ ከመኝታዬ ተነሥቼ
ልብሴን ስለባብስ ሰውነቴ ቀነቀነኝ፡፡ እውነተኛዎቹ የሐሳቤ ቅንቅኖች ግን አንጎሌ ውስጥ ይርመሰመሳሉ። የሥራ ቀን ነበር፡፡
መንገዱ የሚያልቅልኝ ስላልመስለኝ ቀደም ብዬ ተነሣሁ፡፡ ወደ ሕጋዊ ፍርድ ቤት ሳይሆን ወደ ግፈኞች የመከራ ሽንጎ የምገሠግሥ መሰለኝ፡፡ ከአራት ኪሎ እስከ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ያለውን ርቀት በሁለት ታክሲ አጠቃለልኩት፡፡
ጠበቆች፣ ዳኞች፣ ጸሐፊዎች፣ ነገረ ፈጆችና ወኪሎች፣ ተሟጋቾችና አማላጆች፣ “ጫማ ጠራጊዎችና ሥራ ፈቶች፣ እንደየ ኑሮ ደረጃቸው ለብሰው ተራ በተራ ሁለትና ሦስት እየሆኑ በመምጣት የፍርድ ቤቱን አካባቢ የበጋ ወራት ገብያ
አስመሰሉት፡፡ አንዳንዶቹ ሰዎች የለበሱት ነጠላና ጋቢ በጣም ከመቆሸሹ የተነሣ
ዳግመኛ ታጥቦ የሚነጣ አይመስልም፡፡ ጥለቱ የተንዘለዘለ፣ ዐልፎ ዐልፎ አይጥ
የበላው ይመስል የተቀዳደደ፣ እንደ አረጀ ሻሽ አለቅጥ የሳሳ ልብስ፣ በተለያየ
የጨርቅ ዐይነት የተጣጣፈ ኮትና ሱሪ፣ ከታጠበ ብዙ ዓመታት ዐልፈውት እድፉ
እንደ ማሰሻ የተላከከበት ሱፍ ኮት፣ ከተወለወለ ወራት ያለፉትና የቆዳው ቀለም የተገጣጠባ ከወደ አፍንጫው በእንቅፋት አልቆ ቀዳዳው የደረቀ የዓሣ አፍ የመሰለ፡ ከወደ ተረከዙ ወይም ከወደ ጎኑ ባንድ ወገን ተበልቶ የተንጋደደ ጫማ፣
በፀሐይ ሐሩርና በውርጭ፣ በአቧራና በእንክርት ቀለሙ ጠፍቶ የነተበ ባርኔጣ፣
የለበሱ ያደረጉና የደፉ ሰዎች በተስፋ መቁረጥ ስሜት እዚህም እዚያም
ቆመዋል፡፡ ለአያሌ ወራትና ዓመታት የተንገላቱና የተጎሳቆሉ ባለጉዳዮች ናቸው::በረሃብና በጥማት በርዛትና በንዴት በመጎዳታቸው አብዛኛዎቹ ውርጭ ላይ ያደረ አንጋሬ ይመስላሉ፡፡ ሕይወታቸው በትካዜ በመሞላቱ የገጽታቸው ፈገግታ ደርቋል፡፡
ወዛቸው እንደ ቅቤ ቅል የሚቅለጠለጥ ፊታቸው በዶሮ ጮማ እንደተወለወለ የወይራ በትር የሚያበራ፣ ቦርጫቸው የመንፈቅ ርጉዝ መስሎ ሱሪያቸው መታጠቂያው ላይ የሪቅ አፍ የሚያህል፣ አለባበሳቸው ሁሉ በጣም ያማረና የተዋበ ደንደሳሞች፣ በየደቂቃው በሚረባና በማይረባው ሁሉ የሚሥቁ በጣም መሠሪ ሰዎች ከየቢጤዎቻቸው ጋር ሰብሰብ ከምችት ብለው አፍ ለአፍ
ገጥመው ያወራሉ። የያዙት የሰነዶች መያዣ ኮሮጆ እንደ ባለቤቶቹ የፀዳ ሲሆን
የልፋት እንክርት አልነካውም፡፡ የተሰበሰበውን ሰው በዝርዝር ሲያዩት እያንዳንዱ ብቻውን ቆሞ እጁን እያወራጨ ከራሱ ጋር ይሟገታል።
አብዛኛው ጨርቅ ለባሽ በሌላ ሰው ወረቀት እያስነበበ ይኽ ልክ ነው
የለም ይኽ ሐሰት ነው! ለዚህ በቂ ነቃሽ አለኝ! ያያት የቅድመ አያቴ ነው ይግባኝ እላለሁ፡ ከዳኛው ጋር ተዋውለው ነው። ወላዲተ አምላክን!” እያለ እሰጥ
አገባ ይላል። ሁሉም ከሕይወት ወዲያ ማዶ በውሸት ዓለም ውስጥ የሚንቀሳቀሱ እንጂ በርግጠኛ ሕይወት በእውነተኛ ዓለም የሚኖሩ አልመሰሉኝም
የመጥፎ ነገር ጥቀርሻ በጥብጠው የጋቱኝ ይመስል አእምሮዩ ተጨነቀ፡፡
የማያቋርጠው የጊዜ ጎርፍ እየጋፈረ መጓዙን ቀጠለ። ደቂቃ የደቂቃ ርካብ ረግጣ እየተፈናጠጠች ላትመለስ ትጋልባለች።
ጎነ ረጂሙ የከፍተኛው ፍርድ ቤት ግዙፍ ሕንፃ ታላቅ የመከራ ተራራ መስሎ ፊት ለፊት ተገትሯል። የማደርገውን ጥንቃቄ አሟልቼ አካባቢዬን ገልመጥ እያልኩ እያየሁ መለስ ቀለስ አልኩ፡፡ ጭንቀቴና ጥበቴ እንደ ሐምሌ ጥቁር ደመና ከብዶ አንጎሌ ውስጥ አንዣሰሰ። በውስጤ የነበረው ሥጋት በድኃ ገበሬዎች አዋሳኝ እንዳለ የከበርቴ እርሻ መስፋቱን ቀጠለ። ረፈደ።
በወታደሮች ታጅበው በእግራቸውና በመኪና የመጡ አያሌ እስረኞች
በተለየ ቦታ ሰብሰብ አጀብ ብለው ቆሙ። ገር ገጭ ገጭ ገጭ፣ ሲጢጢጢጢጢ !
ካካካካካኪ! የሚል ድምፅ የምታሰማ ቮልስዋገን መጥታ አጠገቤ ቆመች፡፡ ጉልላት ነው። የየወዲያነሽ ቀነ ቀጠሮ በመሆኑ እኔና እርሱ ከፍተኛው ፍርድ ቤት
ለመገናኘት ተነጋግረን ነበር። ድክምክም ባለ እንቅስቃሴ የመኪናይቱን ቋቋቲያም
“በር ከፍቶ ወጣና ጨበጠኝ፡፡
ለአራት ሰዓት ሩብ ጉዳይ እኮ ሆኗል እስካሁን አላመጧትም እንዴ?»
አለኝ፡፡ ከንፈሬ ተጣብቆና ምላሴ አልላወስ ብሎ ቢያስቸግረኝም የለም እስካሁን አላመጧትም» ብዬ ዝም አልኩ። ውካታ በበዛበት አካባቢ ጥቂት ዝም ብለን ቆምን። ትላንት ማምሻዬን ሦስት ባለሙያ ጠበቆች አነጋግሬ ነበር። ሁሉም የሰጡኝ መልስ በጣም ተቀራራቢ ነበር፡፡ ቢበዛ አምስት ዓመት” አሉኝ። እንተስ ምን ይመስልሃል?» ብሎ ዐይኔን ማየት ጀመረ።
«እኔ ምን ዐውቃለሁ፡፡ ማንም ቢሆን ከራሱ ላይ ይልቅ በሌላው ላይ
መፍረድ ይቀልለዋል። የፍርድ ሰጪዎቹን ማንነት ስታየው ግን አምስት ዓመት
የሚበዛ አይመስልም፡፡ ቢሆንም ለእኔና ለእርሷ እያንዳንዱ ደቂቃ የሕይወታችን
ማሻከሪያ ክፍለ ጊዜ መሆኗ ነው» ብዬ ዝም አልኩ፡፡
«መቼም ቢሆን» አለ ጉልላት ወደድክም ጠላህም ምን ጊዜም ቢሆን ሕግ አለ። በሕጉም የሚጠቀሙና ጥቅማቸውን የሚያስጠብቁ አሉ። አህያና ጅብ
ባንድ ላይ ሕግ አያረፉም፡፡ ለጨቋኝና ለተጨቋት በአንድ ጊዜ በእኩልነት
የሚያገለግል ሕግ የለም፣ አልነበረምም፡፡ ሕግ ስለተፃፈ ብቻ ሕጋዊ አሠራር አለ
ማለት አይቻልም። እኔና አንተ ባለንበት ሥርዓተ ማኅበር ውስጥ እጀግ በጣም
አያሌ ባለሥልጣኖችና አጫፋሪዎቻቸው በልዩ ልዩ የእሠራር ስልትና ሥልጣን
ፈጠር ከለላ ከሕግ በላይ የሆኑበትና የሚሆኑበት ሁኔታ እንዳለ መዘንጋት
የለበትም፡፡ ስለሆነም ሕግ በትክክለኛው መንገድ በሥራ ላይ እስካልዋለ ድረስ
የሌለ ያህል ነው፡፡ ይህ ጉዳይ በስፋት የሚያነጋግግር ስለሆነ አሁን ከመጣንበት
ጉዳይ ጋር በቀጥታ ተያያዥነት የለውም። ወደ መጣንበት ጉዳይ እንመለስ፡፡
ስለዚህ በሚሰጠው ፍርድ እንዳትገረም፡፡ የበዛ ወይም ያነሰ ሊሆን ይሆናል» ብሎ
ወደፊት ተራመደ፡፡ ርምጃዬን ከርምጃው ጋር አስተካክዩ ተከተልኩት።
ከእኛ ትንሽ ራቅ ብሎ አንድ ብረት ሽፍን ባለ ጥቁር ሰሌዳ አረንጓዴ መኪና ቆሟል፡፡ ጉልላት መኪናውን አሻግሮ እየተመለከተ «ለምንድን ነው አልመጣችም ያልከኝ? ያ እኮ ነው የወህኒ ቤቱ መኪና» ብሎ ጥሎኝ ሔደ፡፡
አልተከተልኩትም፡፡
መኪናው ውስጥ ከተቀመጠው ሰው ጋር ምን እንደተባባሉ ባይሰማም ጉልላት ትንሽ ራቅ ብሎ ተነጋገሩ። ወዲያው ወደ እኔ ዞር ብሉ ና ቶሉ በሚል አኳኋን ጠቀሰኝ እና ሄድኩ፡፡ እስረኞቹ ወደሚገኙበት አካባቢ እንደ ደረስን ዐይኔ
ያካባቢው የብርሃን መጠን ያነሣት ይመስል የውበት ሃያ መስኮቶቿ ተሸጎሩ።
አጠርጠር ያሉና በሰፊ የካኪ ጨርቅ ስልቻ ውስጥ የቆሙ የሚመስሉ
የወህኒ ቤት ሴት ወታደሮች እያንዳንዳቸው አጠር ያለ ዱላ ይዘው ቆመዋል። በአቅራቢያቸው አምስት ሴቶች ሰብሰብ ብለው ተቀምጠዋል። የትካዜ እሳት ያነኮታቸው ይመስላሉ። ንዳድ እንደ ተነሣበት ሰው መላ ሰውነቴ ጋየ፡፡
የሕይወቴ ክፋይ የሆነችውና የማፈቅራት የወዲያነሽ አንገቷን ሰበር አድርጋና ጀርባዋን ለረፋዷ ፀሐይ ሰጥታ መሬት ትቆረቁራለች። ጉልላት ከሴቷ ወታደር ትንሽ ራቅ ብሎ በትሕትና እጅ ነሣ ራመድ ብዬ ከጎኑ ቆመኩ
በተከዘ ፊቱ ላይ ለማስደሰት የሚፍጨረጨር ፈገግታ እያሳየ «ከነዚህ
፡
፡
#ክፍል_አስራ_ስድስት
፡
፡
#ድርሰት_ኀይለመለኮት_መዋዕል
....የማለዳዋ የጥር ወር ፀሐይ በመሬት ወለል አካባቢ ከየሚዳው! ከየተራራው፣ ከየዛፉ፣ ከየቤቱ፣ ከየጉራንጉሩ ቀዝቃዛ አየር ጋር ትንቅንቅ ገጥማለች። ተፈጥሮ ራሷን በራሷ የምታስተካክልበትና የምትለዋውጥበት ተፈራራቂ ኃይል ስላላት ቀዝቃዛው አየሩ ቀስ በቀስ ተረታ። ለውጥ የተፃራሪ ኃይሎች የግብግብ ውጤት ነው::
በእኔ ሕይወት ውስጥ ግን ጎልቶ የሚጠቀስ ለውጥ ባለመገኘቱ ሕሊናዩ
እየቀዘቀዘ ከመሔድ በቀር የብርታት ለውጥ አልታየብኝም፡፡ ከመኝታዬ ተነሥቼ
ልብሴን ስለባብስ ሰውነቴ ቀነቀነኝ፡፡ እውነተኛዎቹ የሐሳቤ ቅንቅኖች ግን አንጎሌ ውስጥ ይርመሰመሳሉ። የሥራ ቀን ነበር፡፡
መንገዱ የሚያልቅልኝ ስላልመስለኝ ቀደም ብዬ ተነሣሁ፡፡ ወደ ሕጋዊ ፍርድ ቤት ሳይሆን ወደ ግፈኞች የመከራ ሽንጎ የምገሠግሥ መሰለኝ፡፡ ከአራት ኪሎ እስከ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ያለውን ርቀት በሁለት ታክሲ አጠቃለልኩት፡፡
ጠበቆች፣ ዳኞች፣ ጸሐፊዎች፣ ነገረ ፈጆችና ወኪሎች፣ ተሟጋቾችና አማላጆች፣ “ጫማ ጠራጊዎችና ሥራ ፈቶች፣ እንደየ ኑሮ ደረጃቸው ለብሰው ተራ በተራ ሁለትና ሦስት እየሆኑ በመምጣት የፍርድ ቤቱን አካባቢ የበጋ ወራት ገብያ
አስመሰሉት፡፡ አንዳንዶቹ ሰዎች የለበሱት ነጠላና ጋቢ በጣም ከመቆሸሹ የተነሣ
ዳግመኛ ታጥቦ የሚነጣ አይመስልም፡፡ ጥለቱ የተንዘለዘለ፣ ዐልፎ ዐልፎ አይጥ
የበላው ይመስል የተቀዳደደ፣ እንደ አረጀ ሻሽ አለቅጥ የሳሳ ልብስ፣ በተለያየ
የጨርቅ ዐይነት የተጣጣፈ ኮትና ሱሪ፣ ከታጠበ ብዙ ዓመታት ዐልፈውት እድፉ
እንደ ማሰሻ የተላከከበት ሱፍ ኮት፣ ከተወለወለ ወራት ያለፉትና የቆዳው ቀለም የተገጣጠባ ከወደ አፍንጫው በእንቅፋት አልቆ ቀዳዳው የደረቀ የዓሣ አፍ የመሰለ፡ ከወደ ተረከዙ ወይም ከወደ ጎኑ ባንድ ወገን ተበልቶ የተንጋደደ ጫማ፣
በፀሐይ ሐሩርና በውርጭ፣ በአቧራና በእንክርት ቀለሙ ጠፍቶ የነተበ ባርኔጣ፣
የለበሱ ያደረጉና የደፉ ሰዎች በተስፋ መቁረጥ ስሜት እዚህም እዚያም
ቆመዋል፡፡ ለአያሌ ወራትና ዓመታት የተንገላቱና የተጎሳቆሉ ባለጉዳዮች ናቸው::በረሃብና በጥማት በርዛትና በንዴት በመጎዳታቸው አብዛኛዎቹ ውርጭ ላይ ያደረ አንጋሬ ይመስላሉ፡፡ ሕይወታቸው በትካዜ በመሞላቱ የገጽታቸው ፈገግታ ደርቋል፡፡
ወዛቸው እንደ ቅቤ ቅል የሚቅለጠለጥ ፊታቸው በዶሮ ጮማ እንደተወለወለ የወይራ በትር የሚያበራ፣ ቦርጫቸው የመንፈቅ ርጉዝ መስሎ ሱሪያቸው መታጠቂያው ላይ የሪቅ አፍ የሚያህል፣ አለባበሳቸው ሁሉ በጣም ያማረና የተዋበ ደንደሳሞች፣ በየደቂቃው በሚረባና በማይረባው ሁሉ የሚሥቁ በጣም መሠሪ ሰዎች ከየቢጤዎቻቸው ጋር ሰብሰብ ከምችት ብለው አፍ ለአፍ
ገጥመው ያወራሉ። የያዙት የሰነዶች መያዣ ኮሮጆ እንደ ባለቤቶቹ የፀዳ ሲሆን
የልፋት እንክርት አልነካውም፡፡ የተሰበሰበውን ሰው በዝርዝር ሲያዩት እያንዳንዱ ብቻውን ቆሞ እጁን እያወራጨ ከራሱ ጋር ይሟገታል።
አብዛኛው ጨርቅ ለባሽ በሌላ ሰው ወረቀት እያስነበበ ይኽ ልክ ነው
የለም ይኽ ሐሰት ነው! ለዚህ በቂ ነቃሽ አለኝ! ያያት የቅድመ አያቴ ነው ይግባኝ እላለሁ፡ ከዳኛው ጋር ተዋውለው ነው። ወላዲተ አምላክን!” እያለ እሰጥ
አገባ ይላል። ሁሉም ከሕይወት ወዲያ ማዶ በውሸት ዓለም ውስጥ የሚንቀሳቀሱ እንጂ በርግጠኛ ሕይወት በእውነተኛ ዓለም የሚኖሩ አልመሰሉኝም
የመጥፎ ነገር ጥቀርሻ በጥብጠው የጋቱኝ ይመስል አእምሮዩ ተጨነቀ፡፡
የማያቋርጠው የጊዜ ጎርፍ እየጋፈረ መጓዙን ቀጠለ። ደቂቃ የደቂቃ ርካብ ረግጣ እየተፈናጠጠች ላትመለስ ትጋልባለች።
ጎነ ረጂሙ የከፍተኛው ፍርድ ቤት ግዙፍ ሕንፃ ታላቅ የመከራ ተራራ መስሎ ፊት ለፊት ተገትሯል። የማደርገውን ጥንቃቄ አሟልቼ አካባቢዬን ገልመጥ እያልኩ እያየሁ መለስ ቀለስ አልኩ፡፡ ጭንቀቴና ጥበቴ እንደ ሐምሌ ጥቁር ደመና ከብዶ አንጎሌ ውስጥ አንዣሰሰ። በውስጤ የነበረው ሥጋት በድኃ ገበሬዎች አዋሳኝ እንዳለ የከበርቴ እርሻ መስፋቱን ቀጠለ። ረፈደ።
በወታደሮች ታጅበው በእግራቸውና በመኪና የመጡ አያሌ እስረኞች
በተለየ ቦታ ሰብሰብ አጀብ ብለው ቆሙ። ገር ገጭ ገጭ ገጭ፣ ሲጢጢጢጢጢ !
ካካካካካኪ! የሚል ድምፅ የምታሰማ ቮልስዋገን መጥታ አጠገቤ ቆመች፡፡ ጉልላት ነው። የየወዲያነሽ ቀነ ቀጠሮ በመሆኑ እኔና እርሱ ከፍተኛው ፍርድ ቤት
ለመገናኘት ተነጋግረን ነበር። ድክምክም ባለ እንቅስቃሴ የመኪናይቱን ቋቋቲያም
“በር ከፍቶ ወጣና ጨበጠኝ፡፡
ለአራት ሰዓት ሩብ ጉዳይ እኮ ሆኗል እስካሁን አላመጧትም እንዴ?»
አለኝ፡፡ ከንፈሬ ተጣብቆና ምላሴ አልላወስ ብሎ ቢያስቸግረኝም የለም እስካሁን አላመጧትም» ብዬ ዝም አልኩ። ውካታ በበዛበት አካባቢ ጥቂት ዝም ብለን ቆምን። ትላንት ማምሻዬን ሦስት ባለሙያ ጠበቆች አነጋግሬ ነበር። ሁሉም የሰጡኝ መልስ በጣም ተቀራራቢ ነበር፡፡ ቢበዛ አምስት ዓመት” አሉኝ። እንተስ ምን ይመስልሃል?» ብሎ ዐይኔን ማየት ጀመረ።
«እኔ ምን ዐውቃለሁ፡፡ ማንም ቢሆን ከራሱ ላይ ይልቅ በሌላው ላይ
መፍረድ ይቀልለዋል። የፍርድ ሰጪዎቹን ማንነት ስታየው ግን አምስት ዓመት
የሚበዛ አይመስልም፡፡ ቢሆንም ለእኔና ለእርሷ እያንዳንዱ ደቂቃ የሕይወታችን
ማሻከሪያ ክፍለ ጊዜ መሆኗ ነው» ብዬ ዝም አልኩ፡፡
«መቼም ቢሆን» አለ ጉልላት ወደድክም ጠላህም ምን ጊዜም ቢሆን ሕግ አለ። በሕጉም የሚጠቀሙና ጥቅማቸውን የሚያስጠብቁ አሉ። አህያና ጅብ
ባንድ ላይ ሕግ አያረፉም፡፡ ለጨቋኝና ለተጨቋት በአንድ ጊዜ በእኩልነት
የሚያገለግል ሕግ የለም፣ አልነበረምም፡፡ ሕግ ስለተፃፈ ብቻ ሕጋዊ አሠራር አለ
ማለት አይቻልም። እኔና አንተ ባለንበት ሥርዓተ ማኅበር ውስጥ እጀግ በጣም
አያሌ ባለሥልጣኖችና አጫፋሪዎቻቸው በልዩ ልዩ የእሠራር ስልትና ሥልጣን
ፈጠር ከለላ ከሕግ በላይ የሆኑበትና የሚሆኑበት ሁኔታ እንዳለ መዘንጋት
የለበትም፡፡ ስለሆነም ሕግ በትክክለኛው መንገድ በሥራ ላይ እስካልዋለ ድረስ
የሌለ ያህል ነው፡፡ ይህ ጉዳይ በስፋት የሚያነጋግግር ስለሆነ አሁን ከመጣንበት
ጉዳይ ጋር በቀጥታ ተያያዥነት የለውም። ወደ መጣንበት ጉዳይ እንመለስ፡፡
ስለዚህ በሚሰጠው ፍርድ እንዳትገረም፡፡ የበዛ ወይም ያነሰ ሊሆን ይሆናል» ብሎ
ወደፊት ተራመደ፡፡ ርምጃዬን ከርምጃው ጋር አስተካክዩ ተከተልኩት።
ከእኛ ትንሽ ራቅ ብሎ አንድ ብረት ሽፍን ባለ ጥቁር ሰሌዳ አረንጓዴ መኪና ቆሟል፡፡ ጉልላት መኪናውን አሻግሮ እየተመለከተ «ለምንድን ነው አልመጣችም ያልከኝ? ያ እኮ ነው የወህኒ ቤቱ መኪና» ብሎ ጥሎኝ ሔደ፡፡
አልተከተልኩትም፡፡
መኪናው ውስጥ ከተቀመጠው ሰው ጋር ምን እንደተባባሉ ባይሰማም ጉልላት ትንሽ ራቅ ብሎ ተነጋገሩ። ወዲያው ወደ እኔ ዞር ብሉ ና ቶሉ በሚል አኳኋን ጠቀሰኝ እና ሄድኩ፡፡ እስረኞቹ ወደሚገኙበት አካባቢ እንደ ደረስን ዐይኔ
ያካባቢው የብርሃን መጠን ያነሣት ይመስል የውበት ሃያ መስኮቶቿ ተሸጎሩ።
አጠርጠር ያሉና በሰፊ የካኪ ጨርቅ ስልቻ ውስጥ የቆሙ የሚመስሉ
የወህኒ ቤት ሴት ወታደሮች እያንዳንዳቸው አጠር ያለ ዱላ ይዘው ቆመዋል። በአቅራቢያቸው አምስት ሴቶች ሰብሰብ ብለው ተቀምጠዋል። የትካዜ እሳት ያነኮታቸው ይመስላሉ። ንዳድ እንደ ተነሣበት ሰው መላ ሰውነቴ ጋየ፡፡
የሕይወቴ ክፋይ የሆነችውና የማፈቅራት የወዲያነሽ አንገቷን ሰበር አድርጋና ጀርባዋን ለረፋዷ ፀሐይ ሰጥታ መሬት ትቆረቁራለች። ጉልላት ከሴቷ ወታደር ትንሽ ራቅ ብሎ በትሕትና እጅ ነሣ ራመድ ብዬ ከጎኑ ቆመኩ
በተከዘ ፊቱ ላይ ለማስደሰት የሚፍጨረጨር ፈገግታ እያሳየ «ከነዚህ
👍3❤1
#የወድያነሽ
፡
፡
#ክፍል_አስራ_ሰባት
፡
፡
#ድርሰት_ኀይለመለኮት_መዋዕል
....«ስለ ልጅሽ አታስቢ አንቺንም በሚገባ እረዳሻለሁ። አየሽ አእምሮዩ ባንዲት ተስፋ ብቻ ትደሰታለች። ይኸውም ካንቺ ጋር እንደገና እንገናኛለን የሚለው ተስፋ ነው» ብያት ሳልወድ በግድ ዝም አልኩ።
ምላሴ ተቆልፋ እምቢ ባትለኝ ኖሮ በውስጤ የማግበሰበሰው ሐሳብስ ስፍር
ቁጥር አልነበረውም። በብስጭት ከመለብለብ ብዬ ጥያቸው ገለል አልኩ።
ጉልላትም ካሦስት ደቂቃ በኋላ ተለይቷት መጣ፡፡ የእሱን መኪና እንደ ተደገፈን
ብዙ ደቂቃዎች ዐለፉ። እንሒድ ተባብለን ወደ ፍርድ ቤቱ በር አካባቢ ተጠጋን፡፡
አንድ ወፈር ያለ ድምፅ «የወዲያአሉሽ አሸናፊ!» ብሎ ተጣራ፡፡ ለፈተና
እንዳልተዘጋጀ ሰነፍ ተማሪ ተርበተበትኩ፡፡ ሮጥ ሮጥ ብለን ሴቷን ወታደር
ደረስንባትና ስንተኛ ችሎት ነው የምትቀርበው?» ብለን ጠየቅናት።
«አንደኛ ወንጀል ችሎት» ብላ የወደያነሽን ለዕርድ እንደሚነዳ ሠንጋ ነዳቻት። በረዶ የመታኝ ያህል ተንዘፈዘፍኩ፡፡ ወደ ፍርድ ቤቱ ለመግባት ከባለጉዳዮችና ከአቸፍቻፊዎች ጋር ተደባልቄ ዘለቅሁ፡፡
የፍርድ ቤቱን ደፍ ራመድ እንዳልኩ፣ ልክ ከፊት ለፊቴ ድንገተኛ መብረቅ የወደቀ ይመስል አካላቴ በታላቅ ድንጋጤ ተተረተረ። ወዲያም ወዲህ ሳላይ ቀንዷን እንደ ተመታች ላም ወደ ኋላ ተመለስኩ፡፡ ተከታትለው የሚይዙኝ ይመስል ሽሽቴን ቀጠልኩ፡፡ የምገባበት ጨነቀኝ፣ ተቅበዘበዝኩ፡፡ መሬት ተሰንጥቃ
ብትውጠኝ ባልጠላሁ ነበር። መለስ ብዬ ብመለከት የጉልላትም ፊት ቡን ብሏል፡፡
ጭንቅላቴን ይዤ አፈሩ ላይ ተጎለትኩ፡፡ መላ ሰውነቴን አሳከከኝ። ዐይኔ ውስጥ
አሽዋ የገባበት ይመስል ቆረቆረኝ፡፡ ዙሪያው ጨለመብኝ። አተነፋፈሴ ፈጠነ፡፡
የእጮኛውን ሞት እንዳረዱነት ወጣት መላ አካላቴ በውስጣዊ የኃዘን ማረሻ
ታርሶ ተበረቃቀሰ፡፡
«የወዲያነሽ ስንት ዓመት ይፈረድባት ይሆን?» እያልኩ ከእግር እስከ ራሴ በፍርሃትና በሥጋት ማጥ ውስጥ ተዘፈቅሁ፡፡
የፍርድ ቤቱን ደፍ ገና ረገጥ ስናደርግ እኔንና ጉልላትን ያስበረገገን ግን
ከሦስቱ ዳኞች አንዱ ያውም የመኻል ዳኛው የእኔው አባት ባሻ ያየህይራድ
መሆኑ ነበር፡፡ ከዚያ ቀደም እንደዚያ ያለ ድንጋጤ አጋጥሞኝ አያውቅም፡፡
አቀርቅሮ የክስ ፋይል ይመለከት ስለነበር አላየኝም፡፡ እነዚያ በሕይወቴ ውስጥ
ዕድሜ እየሆኑ የተቆጠሩት አስደንጋጭ ደቂቃዎች እንደ ማንኛውም ደቂቃ
ዐለፉ፡፡ በዚያ ቅፅበት በእእምሮዬ ውስጥ የጎረፈውን የስጋት ሽብር በተግባር
ለቀመሰው እንጂ በወሬ ለሚሰማው ክብደት የለውም፡፡
አቃቤ ሕጉ በየወዲያነሽ ላይ የሚያቀርበውን ክስና አባቴ ከሁለቱ ዳኞች ጋር ሆኖ የሚሰጠውን የቅጣት ፍርድ ፊት ለፊት ለማየትና ለመስማት ባለመቻሌ ምን ጊዜም የማልበቀለው ጉዳት አጨቀየኝ።
የየወዲያነሽ ሰውነት በጣም በመኮስመኑና ስሟም በመጠኑ ተለውጦ
የወዲያ አሉሽ በመባሏ አባቴ ሊያውቃት አይችልም፡፡ አለባበሷና አንገተ
ሰባራነቷ እንደሚያዛልቅ ወለል ብሎ ታየኝ፡፡ ጭንቅላቴን ይዤ እንዳቀረቀርኩና
ከተቀመጥኩበት ሳልነሳ ጉልላትም እንደ ማማ ተገትሮ እንደ ቆመ ግማሽ ሰዓት
ያህል ነጎደ። ወዴት እንደሚሔድ ባላውቅም የእግሩ ኮቴ ድምፅ ከወደ ኋላዬ እየራቀ ሄደ። አሁንም ጥቂት ደቂቃዎች ዐለፉ፡፡ እፎይታ ሳይሆን የመከራ ነዲድ በውስጤ ተግፈጠፈጠ።
የአባቴን ጠቅላላ የሕሊናና የአካል አቋም ከልጅነት እስከ ዕውቀት የማውቀውን ያህል እያሰላሰልኩ ከፊት ለፊቴ አቆምኩት፡፡ እርሱ በሚያነብበው
የሃይማኖት ታሪክ መጽሐፍ ውስጥ የሚነገርለት ሰው በላው ሰው ሰባ ስምንት
ሰዎች በልቷል እየተባለ ይነገራል። አባቴም በላዔ ሰብ እየተባለ የሚነገርለትን የክፉ ሰው አምሳል መስሎ ታየኝ።
እሱም እንደ ሰው በላው ሰው የሰው አካል አወራርዶና ግጦ የሰው ሥጋ ባይበላም ሰው በላ ነው:: የሰውን ሕይወት በማጥፋትና የሰውን ሕሊና በመግደል
መካከል ምንም ልዩነት የለም፡፡ ስለ እውነተኛ ርትእና ፍትሕ እየተናገረ
ከሓሰተኞች ጎን ቆሞ ፍርድ ያዛባል፡፡ ከሐቅ ጋር ለቆመ ድሃ ሳይሆን ከሐሰትና
ከክህደት ጋር ጡት ለተጣቡ ባለጊዜና ባለ ገንዘብ ይፈርዳል። ስለዚህም «ሰው
በላ» ነው፡፡
ስለ ድሀ መጨቆንና መበደል ሲያወራ ማንም የሚስተካከለው አይመስልም፡፡ የየአካላችን ደም ስለየሕሊናችን ቅንነትና መሠሪነት መስካሪ ቢሆን ኖሮ ከአባቴ ኣካል የሚንጠፈጠፍ ደም ምንኛ ባጋለጠው!
ከጥቅምና ከኑሮው ላይ ቅንጣት ታህል የሚነካ ሰው ከመጣ፡ አንዷ ሰው
በላው ሰው የሰው አካል ዘነጣጥሎ ባይበላም ነገር ሽርቦና ጉንጉኖ ዓመት ሳይተኩስ ጥርኝ ዐፈር ያደርገዋል።
«ጨርቅ ለባሽ፣ አጥንተርካሽ በማለት የሚጸየፋቸውን ሰዎች ስለ ስምና
ክብሩ ብሉ ያንገላታቸውን ድሆች ሳስታውስ አባቴ እንደዚያ እንደ ታሪኩ ሰው
በቀጥታ የሰው ሥጋ ሳይሆን የሰው ሕይወት በልቷል። ስለ ሰው ችግርና ሥቃይ ፍጹም ደንታ የለሹ አባቴ፣ ማንም ቢንገላታና በጊሳቆል የቁጫጭ ሞት ያህል አያሳዝነውም፡፡ በአባቴና በመሰሎቹ አካባቢ ግዙፍ በደል በድሉ፣ በእጅ አዙር ሰው አስገድሉ፣ ከድሆችና ከከልታሞች ዲቃላ ደቅሎ ምስጢርን መቅ መጨመር የመሠሪነት ሳይሆን «የትልቅ ሰውነት» መለዮ ነው:: ለዚህ ዐይነቱ ደባ የሹም ምልመላ ቢካሔድ አባቴ ያላንዳች ቀዳሚ በትራሹመቱን ይጨብጣል።
«እሳቸው የሞቱ ዕለት ስንቱ ዲቃላ ከየሥርቻ ስርኩቻው ይጎለጎል ይሆን?» በማለት ውስጥ ውስጡንና የሚያማው ብዙ ነው:: እንደ ሰው ሐሜትማ ከሆነ ከልዩ ልዩ ሴቶች ተወልደው በአባቴ የተካዱትን እኀት ወንድሞቼን በግምት ሳሰላስል፣ አባቴ ከሰው በላው ብሶ ታየኝ። በተለይም ጠለቅ ብሎ ሥር ከፍ ብሎ ግንድ የለሽ» እያለ ሌሎችን በማኮሰስ የራሱን የዘር ሐረግ ሲያሳምር ታየኝና አስተሳሰቡን ሁሉ ተፀየፍኩት፡፡
ጉልላት ተመልሶ ከፊት ለፊቴ ቆመ፡፡ በእጆቹ ጎትቶ አስነሣኝ፡፡ በፊቱ ላይ አደናጋሪ ፈገግታ እየታየ «የምሥራች ጌታነህ!» አለኝ፡፡
በዚያች አስጨናቂ ጊዜ ውስጥ አንዳችም የምሥራች ይገኛል ብዬ ስላልጠረጠርኩ ነገሩን ችላ አልኩት፡፡ ቀጠል አደረገና «ምነው ዝም አልክ? የወዲያነሽ እኮ ተፈረደባት። የምሥራች ያልኩህ ግን እጅዋ ከተያዘበት ቀን አንሥቶ አምስት ዓመት እንድትታሠር ስለተፈረደባት ነው:: 'የፈረዱብኝ የጌታነህ አባትና አብረዋቸው ያሉት ናቸው” አለችኝ፡፡ የቅጣቱን ውሳኔ ግን በንባብ ያሰሙት ያንተ አባት ናቸው አለች፡ በስሜ መለወጥና በመጎሳቆሌ
አላወቁኝም በማለቷ በጣም ተደስቻለሁ፡፡ አለቀ። በፍርሃት የሚጠብቁት ሥቃይ
ካለፈ እፎይታ ነው» ብሎ ከሚተናነቀው ምስቅልቅል ሲቃ ጋር ዝምታውን ቀጠለ።
ከፍርዱ በኋላ የወዲያነሽ ወደ ነበረችበት አካባቢ አብረን ሄድን፡፡ ያ የዐይኗ ቋንቋ የሆነው እንባዋ ገነፈለ። ሴቷ ወታደር ትካዜያችንን አይታ አዘነች፡፡ እኔና ጉልላት እንደገና ጠጋ ብለን ለማነጋገር አዲስ ፈቃድ አልጠየቅንም፡፡
«አይዞሽ! ብዙ ጊዜ አይደለም፡፡ በወህኒ ቤት ውስጥም ሆነ እስራትሽን ጨርሰሽ ስትወጪ የእኔ ነሽ። እኔም ያንቺ እንጂ የማንም የሌላ እይደለሁም፡፡ የልብሽ አዳራሽ በዚህ እውነተኛ በሆነ የቃል ኪዳን ተስፋ ይሞላ። ይህን በላይሽ ላይ የጫንኩትን የመከራ ቀንበር አብሬሽ እሸከመዋለሁ፡፡ በመጨረሻም አብረን
እንሰባብረዋለን፡፡ ያጠቆርኩትን ሕይወትሽን በአዲስ የኑሮ ብርሃን እንዲደሞቅ እስከ መጨረሻው እታገላለሁ» ብዬ የልቤን ፅላት ሰጠኋት። አፏ ባይናገርም ልቧ ተቀብሉኛል፡፡ ያደረግሁት ንግግር ተፅፎ የተጠና እንጂ እዚያው ተቀናብሮ የተነገረ ስለማይመስል እኔኑ መልሶ ገረመኝ፡፡
መለስ ብዩ ለሴቷ ወታደር ምናምን ጨበጥ እደረኩላት፡፡ የማይፈቀድ
ነገር
፡
፡
#ክፍል_አስራ_ሰባት
፡
፡
#ድርሰት_ኀይለመለኮት_መዋዕል
....«ስለ ልጅሽ አታስቢ አንቺንም በሚገባ እረዳሻለሁ። አየሽ አእምሮዩ ባንዲት ተስፋ ብቻ ትደሰታለች። ይኸውም ካንቺ ጋር እንደገና እንገናኛለን የሚለው ተስፋ ነው» ብያት ሳልወድ በግድ ዝም አልኩ።
ምላሴ ተቆልፋ እምቢ ባትለኝ ኖሮ በውስጤ የማግበሰበሰው ሐሳብስ ስፍር
ቁጥር አልነበረውም። በብስጭት ከመለብለብ ብዬ ጥያቸው ገለል አልኩ።
ጉልላትም ካሦስት ደቂቃ በኋላ ተለይቷት መጣ፡፡ የእሱን መኪና እንደ ተደገፈን
ብዙ ደቂቃዎች ዐለፉ። እንሒድ ተባብለን ወደ ፍርድ ቤቱ በር አካባቢ ተጠጋን፡፡
አንድ ወፈር ያለ ድምፅ «የወዲያአሉሽ አሸናፊ!» ብሎ ተጣራ፡፡ ለፈተና
እንዳልተዘጋጀ ሰነፍ ተማሪ ተርበተበትኩ፡፡ ሮጥ ሮጥ ብለን ሴቷን ወታደር
ደረስንባትና ስንተኛ ችሎት ነው የምትቀርበው?» ብለን ጠየቅናት።
«አንደኛ ወንጀል ችሎት» ብላ የወደያነሽን ለዕርድ እንደሚነዳ ሠንጋ ነዳቻት። በረዶ የመታኝ ያህል ተንዘፈዘፍኩ፡፡ ወደ ፍርድ ቤቱ ለመግባት ከባለጉዳዮችና ከአቸፍቻፊዎች ጋር ተደባልቄ ዘለቅሁ፡፡
የፍርድ ቤቱን ደፍ ራመድ እንዳልኩ፣ ልክ ከፊት ለፊቴ ድንገተኛ መብረቅ የወደቀ ይመስል አካላቴ በታላቅ ድንጋጤ ተተረተረ። ወዲያም ወዲህ ሳላይ ቀንዷን እንደ ተመታች ላም ወደ ኋላ ተመለስኩ፡፡ ተከታትለው የሚይዙኝ ይመስል ሽሽቴን ቀጠልኩ፡፡ የምገባበት ጨነቀኝ፣ ተቅበዘበዝኩ፡፡ መሬት ተሰንጥቃ
ብትውጠኝ ባልጠላሁ ነበር። መለስ ብዬ ብመለከት የጉልላትም ፊት ቡን ብሏል፡፡
ጭንቅላቴን ይዤ አፈሩ ላይ ተጎለትኩ፡፡ መላ ሰውነቴን አሳከከኝ። ዐይኔ ውስጥ
አሽዋ የገባበት ይመስል ቆረቆረኝ፡፡ ዙሪያው ጨለመብኝ። አተነፋፈሴ ፈጠነ፡፡
የእጮኛውን ሞት እንዳረዱነት ወጣት መላ አካላቴ በውስጣዊ የኃዘን ማረሻ
ታርሶ ተበረቃቀሰ፡፡
«የወዲያነሽ ስንት ዓመት ይፈረድባት ይሆን?» እያልኩ ከእግር እስከ ራሴ በፍርሃትና በሥጋት ማጥ ውስጥ ተዘፈቅሁ፡፡
የፍርድ ቤቱን ደፍ ገና ረገጥ ስናደርግ እኔንና ጉልላትን ያስበረገገን ግን
ከሦስቱ ዳኞች አንዱ ያውም የመኻል ዳኛው የእኔው አባት ባሻ ያየህይራድ
መሆኑ ነበር፡፡ ከዚያ ቀደም እንደዚያ ያለ ድንጋጤ አጋጥሞኝ አያውቅም፡፡
አቀርቅሮ የክስ ፋይል ይመለከት ስለነበር አላየኝም፡፡ እነዚያ በሕይወቴ ውስጥ
ዕድሜ እየሆኑ የተቆጠሩት አስደንጋጭ ደቂቃዎች እንደ ማንኛውም ደቂቃ
ዐለፉ፡፡ በዚያ ቅፅበት በእእምሮዬ ውስጥ የጎረፈውን የስጋት ሽብር በተግባር
ለቀመሰው እንጂ በወሬ ለሚሰማው ክብደት የለውም፡፡
አቃቤ ሕጉ በየወዲያነሽ ላይ የሚያቀርበውን ክስና አባቴ ከሁለቱ ዳኞች ጋር ሆኖ የሚሰጠውን የቅጣት ፍርድ ፊት ለፊት ለማየትና ለመስማት ባለመቻሌ ምን ጊዜም የማልበቀለው ጉዳት አጨቀየኝ።
የየወዲያነሽ ሰውነት በጣም በመኮስመኑና ስሟም በመጠኑ ተለውጦ
የወዲያ አሉሽ በመባሏ አባቴ ሊያውቃት አይችልም፡፡ አለባበሷና አንገተ
ሰባራነቷ እንደሚያዛልቅ ወለል ብሎ ታየኝ፡፡ ጭንቅላቴን ይዤ እንዳቀረቀርኩና
ከተቀመጥኩበት ሳልነሳ ጉልላትም እንደ ማማ ተገትሮ እንደ ቆመ ግማሽ ሰዓት
ያህል ነጎደ። ወዴት እንደሚሔድ ባላውቅም የእግሩ ኮቴ ድምፅ ከወደ ኋላዬ እየራቀ ሄደ። አሁንም ጥቂት ደቂቃዎች ዐለፉ፡፡ እፎይታ ሳይሆን የመከራ ነዲድ በውስጤ ተግፈጠፈጠ።
የአባቴን ጠቅላላ የሕሊናና የአካል አቋም ከልጅነት እስከ ዕውቀት የማውቀውን ያህል እያሰላሰልኩ ከፊት ለፊቴ አቆምኩት፡፡ እርሱ በሚያነብበው
የሃይማኖት ታሪክ መጽሐፍ ውስጥ የሚነገርለት ሰው በላው ሰው ሰባ ስምንት
ሰዎች በልቷል እየተባለ ይነገራል። አባቴም በላዔ ሰብ እየተባለ የሚነገርለትን የክፉ ሰው አምሳል መስሎ ታየኝ።
እሱም እንደ ሰው በላው ሰው የሰው አካል አወራርዶና ግጦ የሰው ሥጋ ባይበላም ሰው በላ ነው:: የሰውን ሕይወት በማጥፋትና የሰውን ሕሊና በመግደል
መካከል ምንም ልዩነት የለም፡፡ ስለ እውነተኛ ርትእና ፍትሕ እየተናገረ
ከሓሰተኞች ጎን ቆሞ ፍርድ ያዛባል፡፡ ከሐቅ ጋር ለቆመ ድሃ ሳይሆን ከሐሰትና
ከክህደት ጋር ጡት ለተጣቡ ባለጊዜና ባለ ገንዘብ ይፈርዳል። ስለዚህም «ሰው
በላ» ነው፡፡
ስለ ድሀ መጨቆንና መበደል ሲያወራ ማንም የሚስተካከለው አይመስልም፡፡ የየአካላችን ደም ስለየሕሊናችን ቅንነትና መሠሪነት መስካሪ ቢሆን ኖሮ ከአባቴ ኣካል የሚንጠፈጠፍ ደም ምንኛ ባጋለጠው!
ከጥቅምና ከኑሮው ላይ ቅንጣት ታህል የሚነካ ሰው ከመጣ፡ አንዷ ሰው
በላው ሰው የሰው አካል ዘነጣጥሎ ባይበላም ነገር ሽርቦና ጉንጉኖ ዓመት ሳይተኩስ ጥርኝ ዐፈር ያደርገዋል።
«ጨርቅ ለባሽ፣ አጥንተርካሽ በማለት የሚጸየፋቸውን ሰዎች ስለ ስምና
ክብሩ ብሉ ያንገላታቸውን ድሆች ሳስታውስ አባቴ እንደዚያ እንደ ታሪኩ ሰው
በቀጥታ የሰው ሥጋ ሳይሆን የሰው ሕይወት በልቷል። ስለ ሰው ችግርና ሥቃይ ፍጹም ደንታ የለሹ አባቴ፣ ማንም ቢንገላታና በጊሳቆል የቁጫጭ ሞት ያህል አያሳዝነውም፡፡ በአባቴና በመሰሎቹ አካባቢ ግዙፍ በደል በድሉ፣ በእጅ አዙር ሰው አስገድሉ፣ ከድሆችና ከከልታሞች ዲቃላ ደቅሎ ምስጢርን መቅ መጨመር የመሠሪነት ሳይሆን «የትልቅ ሰውነት» መለዮ ነው:: ለዚህ ዐይነቱ ደባ የሹም ምልመላ ቢካሔድ አባቴ ያላንዳች ቀዳሚ በትራሹመቱን ይጨብጣል።
«እሳቸው የሞቱ ዕለት ስንቱ ዲቃላ ከየሥርቻ ስርኩቻው ይጎለጎል ይሆን?» በማለት ውስጥ ውስጡንና የሚያማው ብዙ ነው:: እንደ ሰው ሐሜትማ ከሆነ ከልዩ ልዩ ሴቶች ተወልደው በአባቴ የተካዱትን እኀት ወንድሞቼን በግምት ሳሰላስል፣ አባቴ ከሰው በላው ብሶ ታየኝ። በተለይም ጠለቅ ብሎ ሥር ከፍ ብሎ ግንድ የለሽ» እያለ ሌሎችን በማኮሰስ የራሱን የዘር ሐረግ ሲያሳምር ታየኝና አስተሳሰቡን ሁሉ ተፀየፍኩት፡፡
ጉልላት ተመልሶ ከፊት ለፊቴ ቆመ፡፡ በእጆቹ ጎትቶ አስነሣኝ፡፡ በፊቱ ላይ አደናጋሪ ፈገግታ እየታየ «የምሥራች ጌታነህ!» አለኝ፡፡
በዚያች አስጨናቂ ጊዜ ውስጥ አንዳችም የምሥራች ይገኛል ብዬ ስላልጠረጠርኩ ነገሩን ችላ አልኩት፡፡ ቀጠል አደረገና «ምነው ዝም አልክ? የወዲያነሽ እኮ ተፈረደባት። የምሥራች ያልኩህ ግን እጅዋ ከተያዘበት ቀን አንሥቶ አምስት ዓመት እንድትታሠር ስለተፈረደባት ነው:: 'የፈረዱብኝ የጌታነህ አባትና አብረዋቸው ያሉት ናቸው” አለችኝ፡፡ የቅጣቱን ውሳኔ ግን በንባብ ያሰሙት ያንተ አባት ናቸው አለች፡ በስሜ መለወጥና በመጎሳቆሌ
አላወቁኝም በማለቷ በጣም ተደስቻለሁ፡፡ አለቀ። በፍርሃት የሚጠብቁት ሥቃይ
ካለፈ እፎይታ ነው» ብሎ ከሚተናነቀው ምስቅልቅል ሲቃ ጋር ዝምታውን ቀጠለ።
ከፍርዱ በኋላ የወዲያነሽ ወደ ነበረችበት አካባቢ አብረን ሄድን፡፡ ያ የዐይኗ ቋንቋ የሆነው እንባዋ ገነፈለ። ሴቷ ወታደር ትካዜያችንን አይታ አዘነች፡፡ እኔና ጉልላት እንደገና ጠጋ ብለን ለማነጋገር አዲስ ፈቃድ አልጠየቅንም፡፡
«አይዞሽ! ብዙ ጊዜ አይደለም፡፡ በወህኒ ቤት ውስጥም ሆነ እስራትሽን ጨርሰሽ ስትወጪ የእኔ ነሽ። እኔም ያንቺ እንጂ የማንም የሌላ እይደለሁም፡፡ የልብሽ አዳራሽ በዚህ እውነተኛ በሆነ የቃል ኪዳን ተስፋ ይሞላ። ይህን በላይሽ ላይ የጫንኩትን የመከራ ቀንበር አብሬሽ እሸከመዋለሁ፡፡ በመጨረሻም አብረን
እንሰባብረዋለን፡፡ ያጠቆርኩትን ሕይወትሽን በአዲስ የኑሮ ብርሃን እንዲደሞቅ እስከ መጨረሻው እታገላለሁ» ብዬ የልቤን ፅላት ሰጠኋት። አፏ ባይናገርም ልቧ ተቀብሉኛል፡፡ ያደረግሁት ንግግር ተፅፎ የተጠና እንጂ እዚያው ተቀናብሮ የተነገረ ስለማይመስል እኔኑ መልሶ ገረመኝ፡፡
መለስ ብዩ ለሴቷ ወታደር ምናምን ጨበጥ እደረኩላት፡፡ የማይፈቀድ
ነገር
#የወድያነሽ
፡
፡
#ክፍል_አስራ_ስምንት
፡
፡
#ድርሰት_ኀይለመለኮት_መዋዕል
....ከቤተሰቦቼ ጋር የነበረኝ ግንኙነት እምብዛም ሳያፈነግጥና ሳይቀርብ፣
ሳይጥምና ሳይሆመጥጥ ቀጠለ የወዲያነሽ አንድ ዓመት ከመንፈቋ እንደ አንድ የደስታ ቀን ፈጥኖ ዐለፈ፡፡ አንድ ቀን እሑድ ከሰዓት በኋላ ከአንድ ጓደኛዬ
የተዋስኩትን መቅረፀ ትርዒት (ካሜራ ወይም ፎቶ ማንሻ ይዤ ወደ ዕጓላ
ማውታ ሄድኩ
ከዚያ ቀደም ሲል ከወሰድኩለት ልብሶች መካከል ጥሩዋን ልብስ አልብሽ አነሣሁትና እንዴት እንደሚደርሳት ቀደም ብዪ ጨርሼ ስለነበር በሳምንቱ እሑድ
የልጇን ፎቶ ይዤ በጉልላት መኪና ወህኒ ቤት ሄድኩ። እንደ ተለመደው !
፣አስጠራኋት፡፡ የአጥሩን አግዳሚ ዕንጨት ተደግፋ ጥቂት አወራራን ድንገት !ሳታስበው ፎቶግራፉን ከኪሴ መዥረጥ አደረግሁና «በይ እስኪ በቃሽ እዪና ጥገቢው፡ ነጋ ጠባ፣ ልጄ! ልጄ ስትይ!...» ብዬ በወታደሪቱ ኣስተላላፊነት
አቀበልኳት፡፡ የወረቀቱን ግራ ቀኝ ጠርዝ በሁለት እጆቿ ይዛ ትኩር ብላ
ተመለከተችው:: ፊቷ ላይ ስታሸበሽብ የቆየችው ኮስማና ፈገግታ ደብዛዋ ጠፋ።
ወዲያው ብርሃኗ በጥቅጥቅ ጭጋግ እንደ ፈዘዘ ጨረቃ ፈዘዘች። እንባዋ
በዐይኖቿ ዙሪያ ግጥም አለ፡፡ አቀረቀረች። በሰንበሌጥ ላይ እየተንኳላላች እንደምትወርድ ጠፈጠፍ እንባዋ ጉንጯን ሳይነካ ከትንሿ ወረቀት ላይ ተንጠባጠበ።
ከሩኅሩኅ የእናትነቷ ባሕሪ የመነጨ የፍቅር ኩልልታ ስለነበር ለመጪው
ጊዜ የሚቀመጥ የትዝታ ጥሪት አስቀመጥኩ፡፡ ደግማ ደጋግማ ሥዕሉን ሳመች።እምብዛም ነገሬ ሳትለኝና እህ! ብላ ሳታዳምጠኝ ተሰናብቻት ተመለስኩ።
ከሌላ ስድስት ወር በኋላ የወዲ ያነሽ ሁለት ዓመት ሞላት።
እሑድ ከሰዓት በኋላ ነበር፡፡ የዕለቱን ጋዜጣ እያነበብኩ እንግዳ መቀበያ
ክፍል ውስጥ ተቀምጬ ሳለሁ የውብነሽ አጠገቤ ተቀመጠች። የያዘችውን
የአማርኛ ሰዋሰው መጽሐፍ እንደተገለጠ አጭሯ ክብ ጠረጴዛ ላይ ዘረጋችው።
ዐይኔ ተወርውራ የጊዜ ተውሳከ ግሥ የሚለውን ርዕስ አየች። ለነገርና
ለወሬ ማነሣሻ ይሆነኝ ዘንድ «ይልቅስ የአኳኋንና የሁኔታን ተውሳከ ግሥ
አታጠኚም» ብዬ መጽሐፉ ውስጥ የማነበው ያለኝ ይመስል አገላብጬ
አስቀመጥኩት። «እኔ የጊዜ ተውሳከ ግሥ አልዘለቅ ብሎኛል። አንተ ደግሞ
ሌላውን ትለኛልሀ» አለችና እጄ ላይ የነበረውን ጋዜጣ ወስዳ የመጀመሪያን ገጽ አርእስቶች በለሆሳስ አነበበች፡፡
«ሥራ አለብሽ እንዴ የውቢ? ከሌለብሽ አንድ ቦታ ደረስ ብለን እንምጣ» ብዬ ጸጉሬን አሻሸሁት፡፡ ጋዜጣውን አጣጥፋ አስቀመጠችው:: «እሺ እንሂድ፡፡ ይህን ማታም ቢሆን ልፈጽመው እችላለሁ» ብላ ከንፈሯን በምላሷ እያራሰች።
«ምንም እንኳ ለጊዜው አሳዛኝ መስሎ እንደሚታይሽ ባውቅም የኋላ ኋላ
ግን ያስደስትሽ ይሆናል» ብዩ ኩራትን ለመግለጽ በሚያስችል ወፍራም ደርባባ
ድምፅ ተናገርኩ። ካንተ ጋር ከሆንኩ ምን ያሳዝነኛል? በመጨረሻ የሚያስደስተኝ
ነገር ሁሉ ደስ ይለኛል፡፡ እንሂድ ካልክ ልብሴን ልቀያይርና እንሂድ» ብላ ተነሣች፡፡ እንዲሁ ገባ እንዳለች ዘርፈጥ ብላ የተቀመጠችበት ቀሚሷ ከበስተኋላዋ
ልሙጥነቱ ጠፍቶ ወደ ልዩ ልዩ አቅጣጫ የተሰበጣጠረ ጭምድ መስመሮች
ሠርቷል። ልብሷን ለመቀያየር ወደ መኝታ ቤት ስትገባ እኔም ጸጉሬን ለማበጠር
ወደ ክፍሌ ገባሁ፡፡
የልብሴን መስተካከል በመስተዋት ከተመለከትኩ በኋላ ጸጉሬን በደረቁ
እበጥሬው ወጣሁ፡፡ ደረጃውን ወርጀ እንደ ጨረስኩ ደረሰችብኝ።
ምንም እንኳ ወዴት እንደምንሄድ ባታውቅም «የምንሔድበት ቦታ ብዙ
ሰዎች አለበት እንዴ?» ብላ ጠየቀችኝ፡፡ «ማንም የለም። የምንሄደው አንድ እሳዛኝ
ሰው ለማየት ነው» ብዬ አለባበስና አረማመዷን እያየሁ መንገድ ገባን፡፡ ደማም ወጣትነቷና እንስታዊ ውብ ቅርጺ ማራኪነት ሰጥቷታል፡፡ ፈገግ ስትል ፍልቅቅ የሚሉት ነጫጭ ውብ ጥርሶቿ ከደም ግባቷ ጋር የአተር አበባ አስመስለዋታል፡፡
እግረ መንገዳችንን ልዩ ልዩ የሚባሉ ነገሮች ገዛሁላት። ዐሥር ደቂቃ በማይሞላ ጊዜ ውስጥ በታክሲ ዕጓለ ማውታ ደረስን፡፡ ለመጀመሪያ ጊዜ ሴት
አስከትዩ በመሄዴ ያ ዘወትር ብቻዬን ስመላለስ የሚያየኝ ዘበኛ የውብነሽን
በማየቱ የመገረም ፈገግታ ታየበት።
አብዛኛውን ጊዜ ከቤቱ ታዛ አካባቢ ከብዙ ከልጆች ጋር ተቀምጦ ሲጫወት ከሩቁ የማውቀው በልብሱ ስለነበር ሜዳው መኻል ቆም እያልኩ የቢቶቹን የፊት ዙሪያ ተመለከትኩ፡፡ ብዙ ልጆች ጨዋታቸውንና ልፊያቸውን እየተዉ አዩን፡፡ ወደ መኝታ ክፍሉ ይዣት ገባሁ። እሱኑ ከሚያካክሉ ሁለት ልጆች ጋር ወለሉ ላይ ተቀምጦ እየተኮላተፈ ይጫወታል። ሁለቱ ልጆች መለስ ብለው ካዩን በኋላ ጨዋታቸውን ቀጠሉ፡፡ የእኔ ልጅ ዐይኖች ግን እኔ ላይ
ተተከሉ፡፡ ጎንበስ ብዪ አነሣሁት፡፡
አባባና እማማ የሚባሉ ቃላት የማያውቀው፣ የወላጅ ፍቅር ያልቀመሰው
ልጄ እንደ ወፍ ዘራሽ የመስክ አበባ ያምራል። ለምን ወደ ዕጓለ ማውታ እንደ
መጣች ግራ የገባት የውብነሽ በመጠኑ ደንገጥ አለች፡፡ ወደ እርስዋ ዞሬ ትከሻዋን
ቸብ ካደረግሁዋት በኋላ እስኪ ይህን ልጅ ተመልከችው የውብነሽ ቆንጆ ልጅ
አይደለም እንዴ? ብዬ ጠየቅኋት። እ..ብላ ዝም አለች።
ሰውነቷ በጥርጣሬና በሐሳብ የተጠመደ መሰለ፡ ድንገት ከእንቅልፏ ነቅታ ባጋጣሚ ያየችው ይመስል ሁለት እጆቿን ዘርግታ «እውይ እማምዬ ማማሩ! ደስ ማለቱ?» ብላ ከእጁ ላይ ወስዳ ታቀፈችው፡፡
በፊቱ ላይ አንዳችም ሌላ ለውጥ ሳይታይና ፈገግታው ሳይቀንስ ዝርግፍ
ብሉ ወደ እርሷ በመሄዱ በጣም ደስ አለኝ፡፡ እንዲያውም እዚያች ጠባብ ደረቷ
ላይ ልጥቅ አለ፡፡ ነገር ግን ልጄን ለመጀመሪያ ጊዜ ያቺ የማፈቅራትና
የምንሰፈሰፍላት የወዲያዬ ሳትሆን እኅቴ አቅፋው በማየቴ በፋይዳ የለሽ ጥላቻ
ተናደድኩ፡፡ ጉንጮቹን ሳም ሳም ካደረገች በኋላ ፊቷን ወደ እኔ መለስ አድርጋ
<<የማን ልጅ ነው ?» ብላ በጓጓ ስሜት ጠየቀችኝ። የምናገረው እውነተኛና ርግጠኛ እንዲመስል ለመመለስ የማሰላሰያ ጊዜ አልወሰድኩም፡፡ «አንቺ የማታውቂው አንድ ጓደኛ ነበረኝ፡፡ የዚህ ልጅ አባት ማለቴ ነው። ትዝ እይልሽም ይሆናል እንጂ እኛም ቤት አንድ ሁለት ቀን ያህል መጥቶ ነበር» ካልኩ በኋላ የነገሩን
ድምጥማጥ ይበልጥ ለማጥፋት «ነገር ግን ከአንድ ዓመት ከመንፈቅ በፊት
በድንገተኛ የመኪና አደጋ ሞቷል፡፡ ልጁ ግን ለጊዜው አሳዳጊ ዘመድ በማጣቱ
ይኸው እዚህ በምታይው ሁኔታ በማደግ ላይ ይገኛል፡፡ የዚህ ልጅ አባት በጣም
ግሩም ሰው ስለ ነበር እሱን በማሰብና ለልጁ በማዘን ብቻ አልፎ አልፎ ብቅ
እያልኩ እጠይቀዋለሁ፡፡ ጉልላትም አንዳንድ ቀን እየመጣ ያየዋል» ብዬ ዋሸኋት፡፡ግንባሩን ሁለት ጊዜ ያህል ስማ ውብ ዐይኖቹን ባንጸባራቂ ሸጋ ዐይኖቿ ትኩር ብላ ተመለከተቻቸው::
«ምነው አንተም እንዲህ የሚያምርና የሚያስጐመዥ ልጅ በነበረህ» ብላ
እንደ ወይን እሽት የሚያስጐመዡትን ጉንጮቹን ሳመቻቸው:: ንግግሯ ለጊዜው
ረግቶና በርዶ የቆየውን የሕሊናዬን ባሕር በብስጭት ማዕበል አረሰው፡፡
“ምናልባት ሚስት ባገባ ማስቴን በርግዝናዋ ወራት ከቤት አታባርሯት
እንደሆነ ነዋ እንዲህ ያለ ልጅ ማግኘት የሚቻለው» ብዩ በሽሙጥ መለስኩላት።
ድንገተኛው የንግግሬ ይዘት ፊቷን አስቀጨመው:: ልጁን ከሰጠችኝ በኋላ
አንገቷን ስብራ አቀረቀረች። ከጥቂት ዝምታ በኋላ ከወለሉ ላይ ቃላት
እየለቃቀመች ትናገር ይመስል ወለሉን እያየች «ያ ያለፈው ሁሉ ሌላ ጉዳይ
ነው፡፡ የማይገናኙ ነገሮች አታገናኝ እኔን ምን አድርጊ ትለኛለህ? አንተ ከእኔ
የበለጠ ብልህ መሆንህን ዐውቃለሁ አባታችን ቢሰማ ኖሮ በአንተና በእርሱ
መካከል ትልቅ ጠብና ማለቂያ የሌለው
፡
፡
#ክፍል_አስራ_ስምንት
፡
፡
#ድርሰት_ኀይለመለኮት_መዋዕል
....ከቤተሰቦቼ ጋር የነበረኝ ግንኙነት እምብዛም ሳያፈነግጥና ሳይቀርብ፣
ሳይጥምና ሳይሆመጥጥ ቀጠለ የወዲያነሽ አንድ ዓመት ከመንፈቋ እንደ አንድ የደስታ ቀን ፈጥኖ ዐለፈ፡፡ አንድ ቀን እሑድ ከሰዓት በኋላ ከአንድ ጓደኛዬ
የተዋስኩትን መቅረፀ ትርዒት (ካሜራ ወይም ፎቶ ማንሻ ይዤ ወደ ዕጓላ
ማውታ ሄድኩ
ከዚያ ቀደም ሲል ከወሰድኩለት ልብሶች መካከል ጥሩዋን ልብስ አልብሽ አነሣሁትና እንዴት እንደሚደርሳት ቀደም ብዪ ጨርሼ ስለነበር በሳምንቱ እሑድ
የልጇን ፎቶ ይዤ በጉልላት መኪና ወህኒ ቤት ሄድኩ። እንደ ተለመደው !
፣አስጠራኋት፡፡ የአጥሩን አግዳሚ ዕንጨት ተደግፋ ጥቂት አወራራን ድንገት !ሳታስበው ፎቶግራፉን ከኪሴ መዥረጥ አደረግሁና «በይ እስኪ በቃሽ እዪና ጥገቢው፡ ነጋ ጠባ፣ ልጄ! ልጄ ስትይ!...» ብዬ በወታደሪቱ ኣስተላላፊነት
አቀበልኳት፡፡ የወረቀቱን ግራ ቀኝ ጠርዝ በሁለት እጆቿ ይዛ ትኩር ብላ
ተመለከተችው:: ፊቷ ላይ ስታሸበሽብ የቆየችው ኮስማና ፈገግታ ደብዛዋ ጠፋ።
ወዲያው ብርሃኗ በጥቅጥቅ ጭጋግ እንደ ፈዘዘ ጨረቃ ፈዘዘች። እንባዋ
በዐይኖቿ ዙሪያ ግጥም አለ፡፡ አቀረቀረች። በሰንበሌጥ ላይ እየተንኳላላች እንደምትወርድ ጠፈጠፍ እንባዋ ጉንጯን ሳይነካ ከትንሿ ወረቀት ላይ ተንጠባጠበ።
ከሩኅሩኅ የእናትነቷ ባሕሪ የመነጨ የፍቅር ኩልልታ ስለነበር ለመጪው
ጊዜ የሚቀመጥ የትዝታ ጥሪት አስቀመጥኩ፡፡ ደግማ ደጋግማ ሥዕሉን ሳመች።እምብዛም ነገሬ ሳትለኝና እህ! ብላ ሳታዳምጠኝ ተሰናብቻት ተመለስኩ።
ከሌላ ስድስት ወር በኋላ የወዲ ያነሽ ሁለት ዓመት ሞላት።
እሑድ ከሰዓት በኋላ ነበር፡፡ የዕለቱን ጋዜጣ እያነበብኩ እንግዳ መቀበያ
ክፍል ውስጥ ተቀምጬ ሳለሁ የውብነሽ አጠገቤ ተቀመጠች። የያዘችውን
የአማርኛ ሰዋሰው መጽሐፍ እንደተገለጠ አጭሯ ክብ ጠረጴዛ ላይ ዘረጋችው።
ዐይኔ ተወርውራ የጊዜ ተውሳከ ግሥ የሚለውን ርዕስ አየች። ለነገርና
ለወሬ ማነሣሻ ይሆነኝ ዘንድ «ይልቅስ የአኳኋንና የሁኔታን ተውሳከ ግሥ
አታጠኚም» ብዬ መጽሐፉ ውስጥ የማነበው ያለኝ ይመስል አገላብጬ
አስቀመጥኩት። «እኔ የጊዜ ተውሳከ ግሥ አልዘለቅ ብሎኛል። አንተ ደግሞ
ሌላውን ትለኛልሀ» አለችና እጄ ላይ የነበረውን ጋዜጣ ወስዳ የመጀመሪያን ገጽ አርእስቶች በለሆሳስ አነበበች፡፡
«ሥራ አለብሽ እንዴ የውቢ? ከሌለብሽ አንድ ቦታ ደረስ ብለን እንምጣ» ብዬ ጸጉሬን አሻሸሁት፡፡ ጋዜጣውን አጣጥፋ አስቀመጠችው:: «እሺ እንሂድ፡፡ ይህን ማታም ቢሆን ልፈጽመው እችላለሁ» ብላ ከንፈሯን በምላሷ እያራሰች።
«ምንም እንኳ ለጊዜው አሳዛኝ መስሎ እንደሚታይሽ ባውቅም የኋላ ኋላ
ግን ያስደስትሽ ይሆናል» ብዩ ኩራትን ለመግለጽ በሚያስችል ወፍራም ደርባባ
ድምፅ ተናገርኩ። ካንተ ጋር ከሆንኩ ምን ያሳዝነኛል? በመጨረሻ የሚያስደስተኝ
ነገር ሁሉ ደስ ይለኛል፡፡ እንሂድ ካልክ ልብሴን ልቀያይርና እንሂድ» ብላ ተነሣች፡፡ እንዲሁ ገባ እንዳለች ዘርፈጥ ብላ የተቀመጠችበት ቀሚሷ ከበስተኋላዋ
ልሙጥነቱ ጠፍቶ ወደ ልዩ ልዩ አቅጣጫ የተሰበጣጠረ ጭምድ መስመሮች
ሠርቷል። ልብሷን ለመቀያየር ወደ መኝታ ቤት ስትገባ እኔም ጸጉሬን ለማበጠር
ወደ ክፍሌ ገባሁ፡፡
የልብሴን መስተካከል በመስተዋት ከተመለከትኩ በኋላ ጸጉሬን በደረቁ
እበጥሬው ወጣሁ፡፡ ደረጃውን ወርጀ እንደ ጨረስኩ ደረሰችብኝ።
ምንም እንኳ ወዴት እንደምንሄድ ባታውቅም «የምንሔድበት ቦታ ብዙ
ሰዎች አለበት እንዴ?» ብላ ጠየቀችኝ፡፡ «ማንም የለም። የምንሄደው አንድ እሳዛኝ
ሰው ለማየት ነው» ብዬ አለባበስና አረማመዷን እያየሁ መንገድ ገባን፡፡ ደማም ወጣትነቷና እንስታዊ ውብ ቅርጺ ማራኪነት ሰጥቷታል፡፡ ፈገግ ስትል ፍልቅቅ የሚሉት ነጫጭ ውብ ጥርሶቿ ከደም ግባቷ ጋር የአተር አበባ አስመስለዋታል፡፡
እግረ መንገዳችንን ልዩ ልዩ የሚባሉ ነገሮች ገዛሁላት። ዐሥር ደቂቃ በማይሞላ ጊዜ ውስጥ በታክሲ ዕጓለ ማውታ ደረስን፡፡ ለመጀመሪያ ጊዜ ሴት
አስከትዩ በመሄዴ ያ ዘወትር ብቻዬን ስመላለስ የሚያየኝ ዘበኛ የውብነሽን
በማየቱ የመገረም ፈገግታ ታየበት።
አብዛኛውን ጊዜ ከቤቱ ታዛ አካባቢ ከብዙ ከልጆች ጋር ተቀምጦ ሲጫወት ከሩቁ የማውቀው በልብሱ ስለነበር ሜዳው መኻል ቆም እያልኩ የቢቶቹን የፊት ዙሪያ ተመለከትኩ፡፡ ብዙ ልጆች ጨዋታቸውንና ልፊያቸውን እየተዉ አዩን፡፡ ወደ መኝታ ክፍሉ ይዣት ገባሁ። እሱኑ ከሚያካክሉ ሁለት ልጆች ጋር ወለሉ ላይ ተቀምጦ እየተኮላተፈ ይጫወታል። ሁለቱ ልጆች መለስ ብለው ካዩን በኋላ ጨዋታቸውን ቀጠሉ፡፡ የእኔ ልጅ ዐይኖች ግን እኔ ላይ
ተተከሉ፡፡ ጎንበስ ብዪ አነሣሁት፡፡
አባባና እማማ የሚባሉ ቃላት የማያውቀው፣ የወላጅ ፍቅር ያልቀመሰው
ልጄ እንደ ወፍ ዘራሽ የመስክ አበባ ያምራል። ለምን ወደ ዕጓለ ማውታ እንደ
መጣች ግራ የገባት የውብነሽ በመጠኑ ደንገጥ አለች፡፡ ወደ እርስዋ ዞሬ ትከሻዋን
ቸብ ካደረግሁዋት በኋላ እስኪ ይህን ልጅ ተመልከችው የውብነሽ ቆንጆ ልጅ
አይደለም እንዴ? ብዬ ጠየቅኋት። እ..ብላ ዝም አለች።
ሰውነቷ በጥርጣሬና በሐሳብ የተጠመደ መሰለ፡ ድንገት ከእንቅልፏ ነቅታ ባጋጣሚ ያየችው ይመስል ሁለት እጆቿን ዘርግታ «እውይ እማምዬ ማማሩ! ደስ ማለቱ?» ብላ ከእጁ ላይ ወስዳ ታቀፈችው፡፡
በፊቱ ላይ አንዳችም ሌላ ለውጥ ሳይታይና ፈገግታው ሳይቀንስ ዝርግፍ
ብሉ ወደ እርሷ በመሄዱ በጣም ደስ አለኝ፡፡ እንዲያውም እዚያች ጠባብ ደረቷ
ላይ ልጥቅ አለ፡፡ ነገር ግን ልጄን ለመጀመሪያ ጊዜ ያቺ የማፈቅራትና
የምንሰፈሰፍላት የወዲያዬ ሳትሆን እኅቴ አቅፋው በማየቴ በፋይዳ የለሽ ጥላቻ
ተናደድኩ፡፡ ጉንጮቹን ሳም ሳም ካደረገች በኋላ ፊቷን ወደ እኔ መለስ አድርጋ
<<የማን ልጅ ነው ?» ብላ በጓጓ ስሜት ጠየቀችኝ። የምናገረው እውነተኛና ርግጠኛ እንዲመስል ለመመለስ የማሰላሰያ ጊዜ አልወሰድኩም፡፡ «አንቺ የማታውቂው አንድ ጓደኛ ነበረኝ፡፡ የዚህ ልጅ አባት ማለቴ ነው። ትዝ እይልሽም ይሆናል እንጂ እኛም ቤት አንድ ሁለት ቀን ያህል መጥቶ ነበር» ካልኩ በኋላ የነገሩን
ድምጥማጥ ይበልጥ ለማጥፋት «ነገር ግን ከአንድ ዓመት ከመንፈቅ በፊት
በድንገተኛ የመኪና አደጋ ሞቷል፡፡ ልጁ ግን ለጊዜው አሳዳጊ ዘመድ በማጣቱ
ይኸው እዚህ በምታይው ሁኔታ በማደግ ላይ ይገኛል፡፡ የዚህ ልጅ አባት በጣም
ግሩም ሰው ስለ ነበር እሱን በማሰብና ለልጁ በማዘን ብቻ አልፎ አልፎ ብቅ
እያልኩ እጠይቀዋለሁ፡፡ ጉልላትም አንዳንድ ቀን እየመጣ ያየዋል» ብዬ ዋሸኋት፡፡ግንባሩን ሁለት ጊዜ ያህል ስማ ውብ ዐይኖቹን ባንጸባራቂ ሸጋ ዐይኖቿ ትኩር ብላ ተመለከተቻቸው::
«ምነው አንተም እንዲህ የሚያምርና የሚያስጐመዥ ልጅ በነበረህ» ብላ
እንደ ወይን እሽት የሚያስጐመዡትን ጉንጮቹን ሳመቻቸው:: ንግግሯ ለጊዜው
ረግቶና በርዶ የቆየውን የሕሊናዬን ባሕር በብስጭት ማዕበል አረሰው፡፡
“ምናልባት ሚስት ባገባ ማስቴን በርግዝናዋ ወራት ከቤት አታባርሯት
እንደሆነ ነዋ እንዲህ ያለ ልጅ ማግኘት የሚቻለው» ብዩ በሽሙጥ መለስኩላት።
ድንገተኛው የንግግሬ ይዘት ፊቷን አስቀጨመው:: ልጁን ከሰጠችኝ በኋላ
አንገቷን ስብራ አቀረቀረች። ከጥቂት ዝምታ በኋላ ከወለሉ ላይ ቃላት
እየለቃቀመች ትናገር ይመስል ወለሉን እያየች «ያ ያለፈው ሁሉ ሌላ ጉዳይ
ነው፡፡ የማይገናኙ ነገሮች አታገናኝ እኔን ምን አድርጊ ትለኛለህ? አንተ ከእኔ
የበለጠ ብልህ መሆንህን ዐውቃለሁ አባታችን ቢሰማ ኖሮ በአንተና በእርሱ
መካከል ትልቅ ጠብና ማለቂያ የሌለው
👍4
#የወድያነሽ
፡
፡
#ክፍል_አስራ_ዘጠኝ
፡
፡
#ድርሰት_ኀይለመለኮት_መዋዕል
...የካቲት ነበር፣ የመጀመሪያዉ እሑድ። ከዚያ ቀደም እንደማደርገው ልዩ ልዩ ነገሮች ይዤላት ወህኒ ቤት ሄድኩ። የወዲያነሽን ለማስጠራት ዐይኔ
እየዋተተ ጠሪ ስፈልግ ከስድስት ዓመታት በፊት በነበራት የፈገግታ ዐይነት ፊቷ
ፈክቶ ሣቅ ሣቅ እያለች «አንተ ጌታነህ! » ብላ ጠራችኝ፡፡ የአሁኑ ፈገግታዋ
ከቀድሞው የሚለየው ፊቷ ከሲታ ሆኖ በመገርጣቱ ብቻ ነው፡፡ ለምን ከአንጀቷ
ፈገግ እንዳለች የምከንያቱ መነሾ ጠፋኝ፡፡ ለወትሮው የወዲያነሽን የማገኛት
እያስጠራሁ ነበር፡፡ የዚያን ዕለት ግን ቀደም ብላ መጥታ ስትጠብቀኝ በመድረሴ ለውጡ ግራ ገባኝ፡፡
ምንም እንኳን ፈገግታዋና ሣቋ ደስ ቢያሰኘኝም ለጊዜው ደስታዬን አምቄ «ደኅና ነሽ ወይ? ደኅና ሰነበትሽ ወይ?» አልኳት። የደስታ ሲቃ እየተናነቃት አይታ የማትጠግበኝ ይመስል ዓይኖቿ ቃበዙ፡፡ አጥሩን ዘላ የምትወጣ መሰለች፡፡
አጥሩ ግን የሥቃይ ሕግ ግድግዳ እንጂ ተራ እንጨት አልነበረም፡፡አፏን ሁለትና ሦስት ጊዜ ከፍታ መልሳ ገጠመችው:: የወሰድኩላትን ጥቂት ዕቃና ምግብ በወታደሯ አማካይነት እንዲደርሳት አደረግሁ፡፡ በማስቀመጥ ፈንታ
ዐቅፋው ቆመች፡፡ የደነገጥን ይመስል
ዝም ተባባልን፡፡ የታቀፈችው ዕቃ
አምልጧት እግሯ ሥር ዱብ አለ፡፡ ተሰባሪ ነገር ስላልነበረበት አልደነገጥኩም፡፡
እዚያው እንዳለ ጎንበስ ብላ እግሮቿ መኻል አስገብታ እጣብቃ ይዛው ቆመች።
ባላት አካላዊ ሁኔታ ላይ ፈገግታዋ የመጨረሻውን ደረጃ ያዘ፡፡
«ጌታነህ» ብላ በዚያች ውብ የሴታ ሴት ድምጺ ከጠራችኝ በኋላ «ነገ ሮብ እኮ» ብላ ዝም እለች፡፡ ከበፊቱ በበለጠ ጥንቃቄ አቆብቁቤና አፍጥጬ
ተመለከትኳት። ዝግ ብላ ምራቋን ዋጠችና «ሮብ እኮሮብ እኮ ትለቀቂያለሽ'
ትፈቺያለሽ ተባልኩ» ብላ በዐይኖቿ ዙሪያ እንባ ከተረ፡፡ የሰማሁት ነገር እውነት
ስላልመሰለኝ ድንገተኛ የደስታ እና የድንጋጤ ሲቃ ያዘኝ፡፡ «ምን?! ምን
አልሽ?!» አልኩና ነፋስ እንዳስጎነበሳት ለጋ ቅርንጫፍ አንገቴን ወደፊት
አሰገግሁ።
«ሮብ ትለቀቂያለሽ ብለውኛል ነው የምልህ» ብላ ጥርሶቿን እንደ ፈለቀቀች ከነፈገግታዋ ዝም አለች፡፡ ዘልዬ በአንገቷ ዙሪያ እንዳልጠመጠምባትና ጮቤ እየዘለልሁ ደስታዬን እንዳልገልጽ በመካከላችን የተጋረጠው ዐፅሙ የገጠጠ አጥር የመከራ ገረገራ ሆኖ አገደኝ፡፡ የምይዝ የምጨብጠው ጠፋኝ። የደስታ ዕብደት አበድኩ፡፡ አዲስ የሕይወት ብርሃን ፏ አለ፡፡ የሰማይን ሰማያዊ ውብ ጣራ አንጋጥጬ ተመለከትኩ፡፡ በውብ የመስክ አበቦች መካከል እየተዘዋወረች ያሻትን አበባ እንደምትቀስም ንብ ሕሊናዬ ባስፈለጋት የደስታ ዐይነት መካከል
እያማረጠች ቦረቀች።
አምስቱ የሥቃይ ዓመታት እንደ አንድ ረዘም ያለ አስፈሪና አስደንጋጭ ሕልም አለፉ። የደስታ ዘለላዎች እየተሸመጠጡ የሚታደለ ተጨባጭ ነገሮች ቢሆኑ ኖሮ በዚያች ሰዓት ውስጥ ለአያሌ ሰዎች እተርፍ ነበር። በደስታ የሚንከባለሉትንና ብዙ ነገር ለማየት የጓጉትን ዐይኖቿን እየተመለከትኩ በይ እንግዲህ መሔዴ ነው፣ ለጉልላትም ልንገረው:: ሮብ ጧት ከሁለት ሰዓት ጀምሮ ካጥር ውጪ እጠብቅሻለሁ» አልኳት፡፡
«ሮብ ዕለት መጥተህ ወዴት ትወስደኛለህ? ከእንግዲህ ወዲያ ደግሞ
አንተን ላስቸግር ነው?» ብላ ተከዘች፡፡
የማያወላውል ዓላማና ግቤን ስለማውቅ በጊዜያዊ ትካዜዋ አልተበሳጨሁም፡፡
ለ ሮብ ዕለተ ጉዳይ የማውቅው እኔ ነኝ፡፡ ጉዳዩን ሁሉ ለእኔ ተይው:: አሁን ግን
ደኅና ዋይ! እንደ ልቤ ልፈንድቅበት!» ብያት ለመጀመሪያ ጊዜ በርግጠኛ ተስፋ
ተሰናብቻት መንገድ ገባሁ፡፡
ከዕለቱ የደስታ ማሕበል የተወለዱ አስደሳች ትርዒቶች በአንጎሌ ውስጥ
እያሸበሸቡ በመደዳ ከነፉ::
ወዲያ ወዲህ ሳልል በቀጥታ ወደ ጉልላት ቤት አመራሁ። የተሣፈርኩባት መኪና በጣም ያዘገመች ስለ መሰለኝ «ቶሎ ቶሎ በል ጃል» እያልኩ በተደጋጋሚ ወተወትኩ፡፡
ጉልላት «መቼ አነሱኝና · ይበቁኛል፣ ከብዙ ደረቅ ጥቂት ርጥብ ይበልጣል» የሚላቸውን የግቢውን አባቦችና አትክልቶች ዐልፌ ወደ ቤት ገባሁ።
እንግዳ መቀበያ ክፍላቸው ውስጥ ጉልላትና እናቱ ወይዘሮ አማከለች ጐን
ለጐን ተቀምጠው ሲያወሩ ደረስኩ፡፡ እንዴት ሰላምታ ሰጥቻቸው እንደ
ተቀመጥኩ አላስታውስም፡፡ ከእናትዬው ጋር ያደረግሁት «የእንደምን ሰነበቱ?
ሰላምታ በምን አኳኋን እንደ ተፈጸመች ሃች አምና የታየ ሕልምን ያህል እንኳ
አትታወሰኝም፡፡
«ጌታነህ» አሉ ከተቀመጡበት እየተነሡ «እስኪ አሁን ደግሞ ያንተ ተራ ይሁን ተጫወቱ » ብለው ወደ ውጪ ወጡ። እንዴት ብዬ እንደምጀምር ስለጰ ጠፋኝ ሁለት ጊዜ ሀይኔን ጨፈንኩ፡፡ አልከሠትልህ ስላለኝ ድንገት ተነሣሁ።
ጸጉሬን ካወዲያ ወዲህ አሽቼ መነጨርኩት፡፡ የፍርሃቴ ሸክም ከጭንቅላቴ ላይ ዘጭ ብሎ የወደቀልኝ ይመስል የምሥራች ጉልላት!» አልኩት።
አንጋጦ ዐይን ዐይኔን እያዬ «ምሥር ብላ! ምን አገኘህ?» ብሎ ለመስማት ተጣደፈ። በሕይወቴ ውስጥ ትልቁ ደስታ ሊጀመር፣ ነባሩ የትግላችን ምዕራፍ የፊታችን ሮብ ሲዘጋ ሌላው ደግሞ ወዲያው ይከፈታል!» ብዬ እንደገና አዲስ ብርታት በመጨመር የፊታችን ሮብ የወዲያነሽ ትፈታለች!» አልኩት ጮክ ብዩ።
«እስኪ ሙት በለኝ!» ብሎ አንገቴ ላይ ተጠመጠመ። ለብዙ ዓመታት
እንደ ተለያዩ ጓደኛሞች ተሳሳምን፡፡ ጉልላት በደስታ ባሕር ውስጥ ተዘፍቆ
ውስጣዊ ስሜቱን በይፋ ገለጠ፡፡ ትከሻዩን ያዝ እንዳደረገ ግራና ቀኝ ተቀመጥን።
ፈገግታ በፊቱ ላይ እስክስ አለች። «አየህ እኔና አንተ ባለፈው ቅዳሜ የተሳሳትነው አንድ ነገር ነበር። እጅዋ ከተያዘበት ዕለት ጀምሮ የሚለውን የፍርድ ውሳኔ ዘንግተነዋል። የሰባት ወር ጊዜ ሲጠቃለል ሙሉ አምስት ዓመት
ይሆናል ማለት ነው» ካልኩ በኋላ ጣራ ግድግዳውን በጠቅላላ የቤቱን ዙሪያ
ተመለከትኩት፡፡ «እንግዲህ እኔ እንኳን ደስ ያለህ ነው ወይስ እንኳን ደስ ያለሽ
የምለው?» አለና በደስታ የፈዘዘ አእምሮዬን ለማንቃት ትከሻዬን ይዞ ነቀነቀኝ፡፡
«እኔን አይደለም እርሷን መሆን አለበት፡፡ የእኔማ ጉዳይ ገና ምኑ ተነካና! ገና ብዙ ፈተናና ተከታታይ ችግር ይጠብቀኛል። እሷንና ቤተሰቦቼን ለማገናኘት ወይም ዘላቂ መብትና የእኩልነት ሕልውናዋን ለማረጋገጥ ከመጪው ሮብ ጀምሮ አንድ ትልቅ ተጋድሎና ጦርነት እጀምራለሁ፡፡ የወዲያነሽ ሙሉ የሕሊና ነጻነት እስከምትጎናጸፍ ድረስ እታገላለሁ፡፡ በተመሳሳይ የሕሊና ባርነት ውስጥ የሚገኙ እልፍ አዕላፍ ሰዎች ስላሉ ብቻችንን አይደለንም፡፡ ያም ሆነ ይህ
ከወላጆቼ ጋር ያለኝ ግንኙነት ግን ከሮብ ጀምሮ ከዋናው ግንድ ላይ ተሰብራ
በልጧ ብቻ የተንጠለጠለች ቅርንጫፍ እምሳያ መሆኑ ነው» ብዬ መለስኩለት፡፡
በንግግሬ ውስጥ ያለውን የሐሳብ ይዘት እያሰላሰለ ጥቂት ዝም ስላለ «ብዙ ጊዜ
ቢፈጅም አንድ ቀን ድል እንደማደርግ አውቃለሁ፡፡ ይህን አስፈሪ መሳይ ያረጀ
አፍራሽ የልማድ ድልድይ እንዴት ኣድርጌ እንደማልፈውና እንደምሻገረው ካሁኑ
ጭንቅ ጥብብ ብሎኛል። የምፈራውና የሚያርበተብተኝ ምን እንደሆነ አሣምረህ
ታውቀዋለህ፡፡ ፍርሃቴ በዚህ ሁኔታ ከቀጠለ ግን የወዲያነሽን ለመከራ አሳልፈ መስጠቴ ነው» ብዪ እንደ ጨረስኩ ወደ ጉዳዩ ዝርዝር ክርክርና ፍሬ ነገር ገባን።
ያን ዕለት ከሰዓት በኋላ ወደ ዕጓለ ማውታ ሳልሄድ ቀረሁ። ከቤቱ ውስጥ ወበቅ ደጁ ይሻል ይሆናል በማለት ከቤት ከወጣን በኋላ ግራና ቀኝ ቆም እንዳልን
«እንግዲህ የወዲያነሽ ነገ ሮብ መፈታቷ ነው:: ከወህኒ ቤት እንደ ወጣች ከእኔ
ሌላ ምንም መግቢያና መጠጊያ የላትም፡፡ ስለዚህ ነገም ይሁን ከነገ ወዲያ ባፋጣኝ
፡
፡
#ክፍል_አስራ_ዘጠኝ
፡
፡
#ድርሰት_ኀይለመለኮት_መዋዕል
...የካቲት ነበር፣ የመጀመሪያዉ እሑድ። ከዚያ ቀደም እንደማደርገው ልዩ ልዩ ነገሮች ይዤላት ወህኒ ቤት ሄድኩ። የወዲያነሽን ለማስጠራት ዐይኔ
እየዋተተ ጠሪ ስፈልግ ከስድስት ዓመታት በፊት በነበራት የፈገግታ ዐይነት ፊቷ
ፈክቶ ሣቅ ሣቅ እያለች «አንተ ጌታነህ! » ብላ ጠራችኝ፡፡ የአሁኑ ፈገግታዋ
ከቀድሞው የሚለየው ፊቷ ከሲታ ሆኖ በመገርጣቱ ብቻ ነው፡፡ ለምን ከአንጀቷ
ፈገግ እንዳለች የምከንያቱ መነሾ ጠፋኝ፡፡ ለወትሮው የወዲያነሽን የማገኛት
እያስጠራሁ ነበር፡፡ የዚያን ዕለት ግን ቀደም ብላ መጥታ ስትጠብቀኝ በመድረሴ ለውጡ ግራ ገባኝ፡፡
ምንም እንኳን ፈገግታዋና ሣቋ ደስ ቢያሰኘኝም ለጊዜው ደስታዬን አምቄ «ደኅና ነሽ ወይ? ደኅና ሰነበትሽ ወይ?» አልኳት። የደስታ ሲቃ እየተናነቃት አይታ የማትጠግበኝ ይመስል ዓይኖቿ ቃበዙ፡፡ አጥሩን ዘላ የምትወጣ መሰለች፡፡
አጥሩ ግን የሥቃይ ሕግ ግድግዳ እንጂ ተራ እንጨት አልነበረም፡፡አፏን ሁለትና ሦስት ጊዜ ከፍታ መልሳ ገጠመችው:: የወሰድኩላትን ጥቂት ዕቃና ምግብ በወታደሯ አማካይነት እንዲደርሳት አደረግሁ፡፡ በማስቀመጥ ፈንታ
ዐቅፋው ቆመች፡፡ የደነገጥን ይመስል
ዝም ተባባልን፡፡ የታቀፈችው ዕቃ
አምልጧት እግሯ ሥር ዱብ አለ፡፡ ተሰባሪ ነገር ስላልነበረበት አልደነገጥኩም፡፡
እዚያው እንዳለ ጎንበስ ብላ እግሮቿ መኻል አስገብታ እጣብቃ ይዛው ቆመች።
ባላት አካላዊ ሁኔታ ላይ ፈገግታዋ የመጨረሻውን ደረጃ ያዘ፡፡
«ጌታነህ» ብላ በዚያች ውብ የሴታ ሴት ድምጺ ከጠራችኝ በኋላ «ነገ ሮብ እኮ» ብላ ዝም እለች፡፡ ከበፊቱ በበለጠ ጥንቃቄ አቆብቁቤና አፍጥጬ
ተመለከትኳት። ዝግ ብላ ምራቋን ዋጠችና «ሮብ እኮሮብ እኮ ትለቀቂያለሽ'
ትፈቺያለሽ ተባልኩ» ብላ በዐይኖቿ ዙሪያ እንባ ከተረ፡፡ የሰማሁት ነገር እውነት
ስላልመሰለኝ ድንገተኛ የደስታ እና የድንጋጤ ሲቃ ያዘኝ፡፡ «ምን?! ምን
አልሽ?!» አልኩና ነፋስ እንዳስጎነበሳት ለጋ ቅርንጫፍ አንገቴን ወደፊት
አሰገግሁ።
«ሮብ ትለቀቂያለሽ ብለውኛል ነው የምልህ» ብላ ጥርሶቿን እንደ ፈለቀቀች ከነፈገግታዋ ዝም አለች፡፡ ዘልዬ በአንገቷ ዙሪያ እንዳልጠመጠምባትና ጮቤ እየዘለልሁ ደስታዬን እንዳልገልጽ በመካከላችን የተጋረጠው ዐፅሙ የገጠጠ አጥር የመከራ ገረገራ ሆኖ አገደኝ፡፡ የምይዝ የምጨብጠው ጠፋኝ። የደስታ ዕብደት አበድኩ፡፡ አዲስ የሕይወት ብርሃን ፏ አለ፡፡ የሰማይን ሰማያዊ ውብ ጣራ አንጋጥጬ ተመለከትኩ፡፡ በውብ የመስክ አበቦች መካከል እየተዘዋወረች ያሻትን አበባ እንደምትቀስም ንብ ሕሊናዬ ባስፈለጋት የደስታ ዐይነት መካከል
እያማረጠች ቦረቀች።
አምስቱ የሥቃይ ዓመታት እንደ አንድ ረዘም ያለ አስፈሪና አስደንጋጭ ሕልም አለፉ። የደስታ ዘለላዎች እየተሸመጠጡ የሚታደለ ተጨባጭ ነገሮች ቢሆኑ ኖሮ በዚያች ሰዓት ውስጥ ለአያሌ ሰዎች እተርፍ ነበር። በደስታ የሚንከባለሉትንና ብዙ ነገር ለማየት የጓጉትን ዐይኖቿን እየተመለከትኩ በይ እንግዲህ መሔዴ ነው፣ ለጉልላትም ልንገረው:: ሮብ ጧት ከሁለት ሰዓት ጀምሮ ካጥር ውጪ እጠብቅሻለሁ» አልኳት፡፡
«ሮብ ዕለት መጥተህ ወዴት ትወስደኛለህ? ከእንግዲህ ወዲያ ደግሞ
አንተን ላስቸግር ነው?» ብላ ተከዘች፡፡
የማያወላውል ዓላማና ግቤን ስለማውቅ በጊዜያዊ ትካዜዋ አልተበሳጨሁም፡፡
ለ ሮብ ዕለተ ጉዳይ የማውቅው እኔ ነኝ፡፡ ጉዳዩን ሁሉ ለእኔ ተይው:: አሁን ግን
ደኅና ዋይ! እንደ ልቤ ልፈንድቅበት!» ብያት ለመጀመሪያ ጊዜ በርግጠኛ ተስፋ
ተሰናብቻት መንገድ ገባሁ፡፡
ከዕለቱ የደስታ ማሕበል የተወለዱ አስደሳች ትርዒቶች በአንጎሌ ውስጥ
እያሸበሸቡ በመደዳ ከነፉ::
ወዲያ ወዲህ ሳልል በቀጥታ ወደ ጉልላት ቤት አመራሁ። የተሣፈርኩባት መኪና በጣም ያዘገመች ስለ መሰለኝ «ቶሎ ቶሎ በል ጃል» እያልኩ በተደጋጋሚ ወተወትኩ፡፡
ጉልላት «መቼ አነሱኝና · ይበቁኛል፣ ከብዙ ደረቅ ጥቂት ርጥብ ይበልጣል» የሚላቸውን የግቢውን አባቦችና አትክልቶች ዐልፌ ወደ ቤት ገባሁ።
እንግዳ መቀበያ ክፍላቸው ውስጥ ጉልላትና እናቱ ወይዘሮ አማከለች ጐን
ለጐን ተቀምጠው ሲያወሩ ደረስኩ፡፡ እንዴት ሰላምታ ሰጥቻቸው እንደ
ተቀመጥኩ አላስታውስም፡፡ ከእናትዬው ጋር ያደረግሁት «የእንደምን ሰነበቱ?
ሰላምታ በምን አኳኋን እንደ ተፈጸመች ሃች አምና የታየ ሕልምን ያህል እንኳ
አትታወሰኝም፡፡
«ጌታነህ» አሉ ከተቀመጡበት እየተነሡ «እስኪ አሁን ደግሞ ያንተ ተራ ይሁን ተጫወቱ » ብለው ወደ ውጪ ወጡ። እንዴት ብዬ እንደምጀምር ስለጰ ጠፋኝ ሁለት ጊዜ ሀይኔን ጨፈንኩ፡፡ አልከሠትልህ ስላለኝ ድንገት ተነሣሁ።
ጸጉሬን ካወዲያ ወዲህ አሽቼ መነጨርኩት፡፡ የፍርሃቴ ሸክም ከጭንቅላቴ ላይ ዘጭ ብሎ የወደቀልኝ ይመስል የምሥራች ጉልላት!» አልኩት።
አንጋጦ ዐይን ዐይኔን እያዬ «ምሥር ብላ! ምን አገኘህ?» ብሎ ለመስማት ተጣደፈ። በሕይወቴ ውስጥ ትልቁ ደስታ ሊጀመር፣ ነባሩ የትግላችን ምዕራፍ የፊታችን ሮብ ሲዘጋ ሌላው ደግሞ ወዲያው ይከፈታል!» ብዬ እንደገና አዲስ ብርታት በመጨመር የፊታችን ሮብ የወዲያነሽ ትፈታለች!» አልኩት ጮክ ብዩ።
«እስኪ ሙት በለኝ!» ብሎ አንገቴ ላይ ተጠመጠመ። ለብዙ ዓመታት
እንደ ተለያዩ ጓደኛሞች ተሳሳምን፡፡ ጉልላት በደስታ ባሕር ውስጥ ተዘፍቆ
ውስጣዊ ስሜቱን በይፋ ገለጠ፡፡ ትከሻዩን ያዝ እንዳደረገ ግራና ቀኝ ተቀመጥን።
ፈገግታ በፊቱ ላይ እስክስ አለች። «አየህ እኔና አንተ ባለፈው ቅዳሜ የተሳሳትነው አንድ ነገር ነበር። እጅዋ ከተያዘበት ዕለት ጀምሮ የሚለውን የፍርድ ውሳኔ ዘንግተነዋል። የሰባት ወር ጊዜ ሲጠቃለል ሙሉ አምስት ዓመት
ይሆናል ማለት ነው» ካልኩ በኋላ ጣራ ግድግዳውን በጠቅላላ የቤቱን ዙሪያ
ተመለከትኩት፡፡ «እንግዲህ እኔ እንኳን ደስ ያለህ ነው ወይስ እንኳን ደስ ያለሽ
የምለው?» አለና በደስታ የፈዘዘ አእምሮዬን ለማንቃት ትከሻዬን ይዞ ነቀነቀኝ፡፡
«እኔን አይደለም እርሷን መሆን አለበት፡፡ የእኔማ ጉዳይ ገና ምኑ ተነካና! ገና ብዙ ፈተናና ተከታታይ ችግር ይጠብቀኛል። እሷንና ቤተሰቦቼን ለማገናኘት ወይም ዘላቂ መብትና የእኩልነት ሕልውናዋን ለማረጋገጥ ከመጪው ሮብ ጀምሮ አንድ ትልቅ ተጋድሎና ጦርነት እጀምራለሁ፡፡ የወዲያነሽ ሙሉ የሕሊና ነጻነት እስከምትጎናጸፍ ድረስ እታገላለሁ፡፡ በተመሳሳይ የሕሊና ባርነት ውስጥ የሚገኙ እልፍ አዕላፍ ሰዎች ስላሉ ብቻችንን አይደለንም፡፡ ያም ሆነ ይህ
ከወላጆቼ ጋር ያለኝ ግንኙነት ግን ከሮብ ጀምሮ ከዋናው ግንድ ላይ ተሰብራ
በልጧ ብቻ የተንጠለጠለች ቅርንጫፍ እምሳያ መሆኑ ነው» ብዬ መለስኩለት፡፡
በንግግሬ ውስጥ ያለውን የሐሳብ ይዘት እያሰላሰለ ጥቂት ዝም ስላለ «ብዙ ጊዜ
ቢፈጅም አንድ ቀን ድል እንደማደርግ አውቃለሁ፡፡ ይህን አስፈሪ መሳይ ያረጀ
አፍራሽ የልማድ ድልድይ እንዴት ኣድርጌ እንደማልፈውና እንደምሻገረው ካሁኑ
ጭንቅ ጥብብ ብሎኛል። የምፈራውና የሚያርበተብተኝ ምን እንደሆነ አሣምረህ
ታውቀዋለህ፡፡ ፍርሃቴ በዚህ ሁኔታ ከቀጠለ ግን የወዲያነሽን ለመከራ አሳልፈ መስጠቴ ነው» ብዪ እንደ ጨረስኩ ወደ ጉዳዩ ዝርዝር ክርክርና ፍሬ ነገር ገባን።
ያን ዕለት ከሰዓት በኋላ ወደ ዕጓለ ማውታ ሳልሄድ ቀረሁ። ከቤቱ ውስጥ ወበቅ ደጁ ይሻል ይሆናል በማለት ከቤት ከወጣን በኋላ ግራና ቀኝ ቆም እንዳልን
«እንግዲህ የወዲያነሽ ነገ ሮብ መፈታቷ ነው:: ከወህኒ ቤት እንደ ወጣች ከእኔ
ሌላ ምንም መግቢያና መጠጊያ የላትም፡፡ ስለዚህ ነገም ይሁን ከነገ ወዲያ ባፋጣኝ
👍2
#የተወጋ_ልብ
፡
፡
#ክፍል_አስር
፡
፡
#ድርሰት_ኀይለመለኮት_መዋዕል
.....ሸዋዬ ከመኝታ ክፍሏ ውስጥ ሆና አንጀቷ በእልህና በቁጭት ሲቃጠልና በእምባ ብዛት ያበጡት ዐይኖቿን ስታሻሽ አረፈደች።
ባሏ ቶሎሳ ደግሞ የምሳ ሰዓት ሲደርስ ወደ ቤቱ ለመሄድ ከጀለና የሸዋዬን የጠዋቱን ሁኔታዋን ሲያስታውሰው ፍርሃት አደረበት። ልቡ በመሄድና በመቅረት መካከል ሲዋልል ከቆየ በኋላ “ግዴለም እዚያው ባልና ሚስትን በሚያስታርቀው አልጋ ላይ ብንገናኝ ይሻላል” በማለት ራሱን አሳመነና ሲመሽ ወደ ቤቱ መሄድን መረጠ፡፡
አምሽቶ ገብቶ ጌትነትንና ሸዋዬን ሊያስታርቃቸው፣የበደለን ይቅርታ እንዲጠይቅ የተበደለ ደግሞ ይቅር ለእግዚአብሄር እንዲል የማድረግ ዕቅዱን
ይዞ ምሳውን ከሆቴል ቤት ቀማመስና ስራው ላይ አመሸ፡፡ ሸዋዬ በወደ
ቀችበት አልጋ ላይ ቆይታ ከቀኑ ወደ ስድስት ሰዓት ተኩል ገደማ ብድግ
አለች። የተመሰቃቀሉ ልብሷንና የተበታተነ ፀጉሯን በወግ በወጉ ካደረገች
በኋላ ወደ ፊት አመራችና ግድግዳው ላይ የተንጠለጠለውን መስታወት አንስታ ፊቷን ጣደችበት። ዐይኖቿ ንብ የነደፋቸው መስለዋል። ብርቱካን የሚመስለው ቀይ ጉንጫ በቶሎሳ ጥፊ ምክንያት ደም መስሏል።አራት የጣት አሻራዎች ተጋድመውበታል። በአጠቃላይ ከለቅሶውና ከጥፊው ጋር ፊቷ ተጉረብርቦ ስታየው የሷ መሆኑን ተጠራጠረች።
ያንን አዲስ መልኳን ከመስታወቱ ውስጥ ትክ ብላ ስትመለከተው ሌላዋ
ሸዋዬን እንጂ ራሷን የምትመለከት አልመስልሽ አላት፡፡ ያቺ በመስታወቱ
ውስጥ የምታያት ሽዋዬ መልኳ የተበላሸበትን ምክንያት ወደ ኋላ መለስ
ብላ ስታስበው ደግሞ ለዚህ ሁሉ መንስኤው ራሷ የፈጠረችው ችግር
መሆኑን ከመስታወቱ ውስጥ ነጥሮ የሚመለስው የራሷ ምስል የሚመ
ሰክርባት ሌላ ስው ሆኖ ታያት፡፡ ምስሉ ውስጠ ገመናዋን ፈትሾ ሴሰኛነቷን ያሳበቀባት መሰላት፡ ጌትነትን ሆን ብላ በማሳሳት የፈፀመችውን እያንዳንዷን ድርጊት፣ እያንዳንዷ እንቅስቃሴ በመስታወቱ ውስጥ በምትመለከታት ሸዋዬ ውስጥ ቁልጭ ብሎ ታያት፡፡ በትናንትናው ምሽት ከጌትነት ጋር የፈፀመችው ድርጊት ሁሉ ወለል ብሎ የታያት አሁን ገና ያቺን ፊቷ የነፈረቀው ሸዋዬን ስትመለከታት ነበር፡፡ ቶሎሳ ለቅሶ ቤት አድሮ በጠዋቱ ቤቱ ሲገባ ያዙኝ ልቀቁኝ እያለች ተበዳይነቷን ለማስረዳት የለፈለፈችው፣ከፍላጎቷ ውጭ ጌትነት ለወሲብ የፈለጋት መሆኑን ለመግለጽ የሞከረችው ፣ የባሏ ታማኝ ሚስት መሆኗን ለማሳወቅ እንደ አለብላቢት የሚያቃጥል ምላሷን ያሾለችው፣ እነዚያ ሁሉ ባዶ ቃላቶቿ ደጋግመው በጭንቅላቷ ውስጥ አስተጋቡባት። ግን አልተቆጨችም፡፡ አልተፀፀተችም፡፡ ራሷንም አልወቀሰችም፡፡ራሷን ያልወቀሰችው ደግሞ በጌትነት የማይረባ ድርጊት ምክንያት ነው፡፡ እሷ ልትሰርቀው ስትመኝ፣ቀምሳ ልታጣጥመው ስትቋምጥ ባልጠበቀችውና ባልገመተችው ሁኔታ ራቁቷን ገፍትሮ መሬት ላይ ጥሎ አዋረዳት፡፡ በድንጋጤ አሽማቆ ሰድቦ አባረራት፡፡ አቤት ስድቡ! ቆጠቆጣት፡፡ ባለጌ! የአእምሮ ጠባሳ ነው፡፡ ከሱ አጥንት የሚሰብር ስድብስ የቶሎሳ ጥፊ ይሻላል አለች። የቶሎሳ ጥፊ ከጥቂት ጊዜ በኋላ ይጠፋል። የጌትነት ስድብ ግን ሁል ጊዜም እንዳንገ
በገባት ይኖራል።
“እስኪ መሰራረቅ ምን ነውር አለበት? የሚጣፍጠው ሰርቀው የበሉት
አይዴል? ቶሎሳስ ቢሆን ምኑ ነው? ደርሶ ታማኝነት... ወገኛ! እርጥብ ባላገር! ቆዳ !የሰው ቆዳ! እስኪ ምን ነበረበት በዚያ ባለቀለት ሰዓት በወሲብ እሳት ነደን፣ እንደ ቅቤ ቀልጠን፣ ወይ አርፎ አልተቀመጠ
ጭኖቼን ደባብሶ፣ ስሜቴን ቆስቁሶ፣ በመወስወሻው ወስውሶ፣ ከንፈሮቼን በከንፈሮቹ ዋግምት እየመጠጠ መቃጠል ስንጀምር ኣሽቀንጥሮ፣
ወርውሮ በረዶውን የለቀቀብኝ? ምቀኛ! መልኩ እንጂ ምኑም አየለን የማ
ይመስል ነሆለል! እኔው ነኝ ወራዳዋ ጥንት ሞቶ አፈር የለበሰውን ጀግና
በዚህ በቁርበት ባላገር ውስጥ አገኘዋለሁ ብዬ መመኘቴ!" ቅጥል አለች።
ከእንግዲህ በኋላ ሆድና ጀርባ ሆነዋል፡፡ አይጥና ድመት….ከአሁን በኋላ እትዬ አትበለኝ ሸዋዬ እያልክ ጥራኝ ትለው የነበረው ለምን እንደሆነ ታውቋል። ከአሁን በኋላ እንደዚያ እሱ ጋ ስትደርስ የምታሳያቸው ለየት ያሉ ባህሪያት ስስ የውስጥ ልብስ እየለበሱ በመኝታ ቤቱ ውስጥ ብቅ ጥልቅ ማለት፣ዳሌን እያውረገረጉ አንጀት ለመብላት መሞከር፣
ጡትን ደጅ እያሳደሩ ብርድ ማስመታት፣ አስር ጊዜ ጎንበስ ቀና እያሉ
ጭንን ለማስቃኘት የሚደረጉ ጥረቶች ሁሉ ምክንያታቸው ታውቋል።ቶሎሳን ለሁለት ነው እንዴ ያገባችሁኝ?! ስትል አንባርቃበታለች። ከእንግዲህ በኋላ ጌትነትን ለማግኘት የነበራት ተስፋ ሙጥጥ ብሎ አልቋል።
ከእንግዲህ በኋላ አብሮ የመኖሩ ጉዳይ የማይታሰብ ነው። ደግሞ ማን ያውቃል ከቶሎሳ ጋር ተያይዘው ነው ከቤት የወጡት። በዚህ አጋጣሚ የትናንትናው ድርጊቷን ያጋልጥ ይሆናል። ለትናንትናው ጥፋት መንስኤው እሷ መሆኗን አስቀድሞ ነግሮት አሳምኖት ከሆነ ደግሞ ጉድ ሊፈላ ነው። ጩኽቷ ሁሉ የውሸት፣ ለቅሶዋ ሁሉ የአዞ እንባ እንደነበረ ከተነቃባት ከቶሎሳ ጋር የመጨረሻቸው መሆኑ ታያት። ስለዚህ ያ በሷ ንፁህነት፣ በሷ ተበዳይነት የተጀመረው ድራማ ተጠናክሮ እንዲቀጥልና በሷ አሸናፊነት በድል እንዲደመደም ከተፈለገ ጌትነት በፍጥነት ከዚያች ቤት እንዲባረር ማድረግ ያስፈልጋል፡፡ ይህንን ሃሳቧን ለማሳካት ደግሞ ባሏን እንደ ጠዋቱ እየጮኽች እያጓራችበት ሳይሆን ጣፋጭነቷን እየመገበችው፣ ፍቅሯን እያስኮመኮመችው፣ እያባበለችው ልቡን በመስለብ የትናንትናውን የጌትነት ድፍረት ፍርጥ አድርጋ ልትነግረው ተዘጋጀች...
ለአንድ ቀን ቶሎሳ ውጭ ቢያድር ያቺን ቀዳዳ ተጠቅሞ ለወሲብ ያባበላት
መሆኑን እሷ ግን ለትዳሯ ታማኝ በመሆን ያሳፈረችው መሆኑን ልትነግረውና በፍጥነት ከዚያች ቤት እንዲያባርረው ለማድረግ ዕቅዷን አጠናቅቀች። እንዳይመሽ የለም መሽ፡፡ የቶሎሳ መግቢያ ሰዓቱ ደረሰ። እሷ ተጨነቀች፣ ተጠበበች እንጂ ጌትነት ቀድሟት ነበር። “የት አባቱ ይሄዳል? መግቢያ ቀዳዳው ያቺው የቶሎሳ ጎጆ ነች ተመልሶ መምጣቱ አይቀርም” ነበር ግምቷ። እሷ እንደገመተችው ሳይሆን ዳግም ላይመለስ ለአንዴና ለመጨረሻ ግዜ ተሰናብቶ የሄደ መሆኑን ብታውቅ ኖሮ ቶሎሳን እንደዚያ ተሽቆጥቁጣ መሬት ሆና አትጠብቀውም ነበር። በጥፊ ሲያላጋት ሰማይ ምድሩ ነበር የተደበላለቀባት፡፡ እንደዚያ በጥፊ ሲደረግምባት ዘመዱን አግዞ ለዘመዱ አድልቶ የደበደባት መስሏት ስትበሳጭ ስትብከነከን ነበር የዋለችው። ጌትነት እንደወጣ የሚቀር መሆኑን አስቀድማ አውቃው ቢሆን ኖሮ አራስ ነብር እንደሆነች ትጠብቀው ነበር እንጂ እንደዚያ ላስላሳ ድመት ሆና አትለማመጠውም ነበር። ያንን የጌትነትን ውሳኔ አላወቀችምና ዱላውን ረስታ ብስጭቷን እርግፍ አድርጋ ትታ በፈገግታ
እጆቿን ዘርግታ በፍቅር ስለፍቅር ተቀበለችው።
“ለምንድነው ደግሞ ለምሳ ያልመጣኸው?” አንገቱን እቅፍ አድርጋ ከፊል ሳቅ ከፊል ንዴት ያለበት በሚመስል ሰው ሰራሽ የማስመሰል ችሎታዋ
ፊቷን ልውጥውጥ አድርጋ ጠየቀችው።
“ምን አባቴ ላድርግ ሸዋዬ? በጠዋቱ የቁርሴን ፋንታ አራስ ነብር ሆነሽ
በነገር አጣድፈሽ ከቤት ስታስወጪኝ የተረፈውን ደግሞ በምሳዬ ላይ ጨምረሽ እንዳታባርሪኝ ፈርቼ ነዋ!” አላት በመገረም የሚስቱን ዐይን ዐይኖቿን እያየ :
“ርቦሃል አይደል? ጠዋት ጦምህን እንደወጣህ ነህ አይደል? ! በል አረፍ በልና መክሰስህን ብላ”እጁን እየጎተተች ወደ ጓዳ አስገባችው። ዛሬ ለቶሎሳ አልጋው የመመገቢያ ጠረጴዛ ሆነለት።
“ተመስጌን አምላኬ ላንተ ምን ይሳንሃል? ጠዋት እንደዚያ አራስ ነብር ሆና ከቤት ያባረረችኝ ሴትዮ ማታ ላይ ደግሞ እንደ
፡
፡
#ክፍል_አስር
፡
፡
#ድርሰት_ኀይለመለኮት_መዋዕል
.....ሸዋዬ ከመኝታ ክፍሏ ውስጥ ሆና አንጀቷ በእልህና በቁጭት ሲቃጠልና በእምባ ብዛት ያበጡት ዐይኖቿን ስታሻሽ አረፈደች።
ባሏ ቶሎሳ ደግሞ የምሳ ሰዓት ሲደርስ ወደ ቤቱ ለመሄድ ከጀለና የሸዋዬን የጠዋቱን ሁኔታዋን ሲያስታውሰው ፍርሃት አደረበት። ልቡ በመሄድና በመቅረት መካከል ሲዋልል ከቆየ በኋላ “ግዴለም እዚያው ባልና ሚስትን በሚያስታርቀው አልጋ ላይ ብንገናኝ ይሻላል” በማለት ራሱን አሳመነና ሲመሽ ወደ ቤቱ መሄድን መረጠ፡፡
አምሽቶ ገብቶ ጌትነትንና ሸዋዬን ሊያስታርቃቸው፣የበደለን ይቅርታ እንዲጠይቅ የተበደለ ደግሞ ይቅር ለእግዚአብሄር እንዲል የማድረግ ዕቅዱን
ይዞ ምሳውን ከሆቴል ቤት ቀማመስና ስራው ላይ አመሸ፡፡ ሸዋዬ በወደ
ቀችበት አልጋ ላይ ቆይታ ከቀኑ ወደ ስድስት ሰዓት ተኩል ገደማ ብድግ
አለች። የተመሰቃቀሉ ልብሷንና የተበታተነ ፀጉሯን በወግ በወጉ ካደረገች
በኋላ ወደ ፊት አመራችና ግድግዳው ላይ የተንጠለጠለውን መስታወት አንስታ ፊቷን ጣደችበት። ዐይኖቿ ንብ የነደፋቸው መስለዋል። ብርቱካን የሚመስለው ቀይ ጉንጫ በቶሎሳ ጥፊ ምክንያት ደም መስሏል።አራት የጣት አሻራዎች ተጋድመውበታል። በአጠቃላይ ከለቅሶውና ከጥፊው ጋር ፊቷ ተጉረብርቦ ስታየው የሷ መሆኑን ተጠራጠረች።
ያንን አዲስ መልኳን ከመስታወቱ ውስጥ ትክ ብላ ስትመለከተው ሌላዋ
ሸዋዬን እንጂ ራሷን የምትመለከት አልመስልሽ አላት፡፡ ያቺ በመስታወቱ
ውስጥ የምታያት ሽዋዬ መልኳ የተበላሸበትን ምክንያት ወደ ኋላ መለስ
ብላ ስታስበው ደግሞ ለዚህ ሁሉ መንስኤው ራሷ የፈጠረችው ችግር
መሆኑን ከመስታወቱ ውስጥ ነጥሮ የሚመለስው የራሷ ምስል የሚመ
ሰክርባት ሌላ ስው ሆኖ ታያት፡፡ ምስሉ ውስጠ ገመናዋን ፈትሾ ሴሰኛነቷን ያሳበቀባት መሰላት፡ ጌትነትን ሆን ብላ በማሳሳት የፈፀመችውን እያንዳንዷን ድርጊት፣ እያንዳንዷ እንቅስቃሴ በመስታወቱ ውስጥ በምትመለከታት ሸዋዬ ውስጥ ቁልጭ ብሎ ታያት፡፡ በትናንትናው ምሽት ከጌትነት ጋር የፈፀመችው ድርጊት ሁሉ ወለል ብሎ የታያት አሁን ገና ያቺን ፊቷ የነፈረቀው ሸዋዬን ስትመለከታት ነበር፡፡ ቶሎሳ ለቅሶ ቤት አድሮ በጠዋቱ ቤቱ ሲገባ ያዙኝ ልቀቁኝ እያለች ተበዳይነቷን ለማስረዳት የለፈለፈችው፣ከፍላጎቷ ውጭ ጌትነት ለወሲብ የፈለጋት መሆኑን ለመግለጽ የሞከረችው ፣ የባሏ ታማኝ ሚስት መሆኗን ለማሳወቅ እንደ አለብላቢት የሚያቃጥል ምላሷን ያሾለችው፣ እነዚያ ሁሉ ባዶ ቃላቶቿ ደጋግመው በጭንቅላቷ ውስጥ አስተጋቡባት። ግን አልተቆጨችም፡፡ አልተፀፀተችም፡፡ ራሷንም አልወቀሰችም፡፡ራሷን ያልወቀሰችው ደግሞ በጌትነት የማይረባ ድርጊት ምክንያት ነው፡፡ እሷ ልትሰርቀው ስትመኝ፣ቀምሳ ልታጣጥመው ስትቋምጥ ባልጠበቀችውና ባልገመተችው ሁኔታ ራቁቷን ገፍትሮ መሬት ላይ ጥሎ አዋረዳት፡፡ በድንጋጤ አሽማቆ ሰድቦ አባረራት፡፡ አቤት ስድቡ! ቆጠቆጣት፡፡ ባለጌ! የአእምሮ ጠባሳ ነው፡፡ ከሱ አጥንት የሚሰብር ስድብስ የቶሎሳ ጥፊ ይሻላል አለች። የቶሎሳ ጥፊ ከጥቂት ጊዜ በኋላ ይጠፋል። የጌትነት ስድብ ግን ሁል ጊዜም እንዳንገ
በገባት ይኖራል።
“እስኪ መሰራረቅ ምን ነውር አለበት? የሚጣፍጠው ሰርቀው የበሉት
አይዴል? ቶሎሳስ ቢሆን ምኑ ነው? ደርሶ ታማኝነት... ወገኛ! እርጥብ ባላገር! ቆዳ !የሰው ቆዳ! እስኪ ምን ነበረበት በዚያ ባለቀለት ሰዓት በወሲብ እሳት ነደን፣ እንደ ቅቤ ቀልጠን፣ ወይ አርፎ አልተቀመጠ
ጭኖቼን ደባብሶ፣ ስሜቴን ቆስቁሶ፣ በመወስወሻው ወስውሶ፣ ከንፈሮቼን በከንፈሮቹ ዋግምት እየመጠጠ መቃጠል ስንጀምር ኣሽቀንጥሮ፣
ወርውሮ በረዶውን የለቀቀብኝ? ምቀኛ! መልኩ እንጂ ምኑም አየለን የማ
ይመስል ነሆለል! እኔው ነኝ ወራዳዋ ጥንት ሞቶ አፈር የለበሰውን ጀግና
በዚህ በቁርበት ባላገር ውስጥ አገኘዋለሁ ብዬ መመኘቴ!" ቅጥል አለች።
ከእንግዲህ በኋላ ሆድና ጀርባ ሆነዋል፡፡ አይጥና ድመት….ከአሁን በኋላ እትዬ አትበለኝ ሸዋዬ እያልክ ጥራኝ ትለው የነበረው ለምን እንደሆነ ታውቋል። ከአሁን በኋላ እንደዚያ እሱ ጋ ስትደርስ የምታሳያቸው ለየት ያሉ ባህሪያት ስስ የውስጥ ልብስ እየለበሱ በመኝታ ቤቱ ውስጥ ብቅ ጥልቅ ማለት፣ዳሌን እያውረገረጉ አንጀት ለመብላት መሞከር፣
ጡትን ደጅ እያሳደሩ ብርድ ማስመታት፣ አስር ጊዜ ጎንበስ ቀና እያሉ
ጭንን ለማስቃኘት የሚደረጉ ጥረቶች ሁሉ ምክንያታቸው ታውቋል።ቶሎሳን ለሁለት ነው እንዴ ያገባችሁኝ?! ስትል አንባርቃበታለች። ከእንግዲህ በኋላ ጌትነትን ለማግኘት የነበራት ተስፋ ሙጥጥ ብሎ አልቋል።
ከእንግዲህ በኋላ አብሮ የመኖሩ ጉዳይ የማይታሰብ ነው። ደግሞ ማን ያውቃል ከቶሎሳ ጋር ተያይዘው ነው ከቤት የወጡት። በዚህ አጋጣሚ የትናንትናው ድርጊቷን ያጋልጥ ይሆናል። ለትናንትናው ጥፋት መንስኤው እሷ መሆኗን አስቀድሞ ነግሮት አሳምኖት ከሆነ ደግሞ ጉድ ሊፈላ ነው። ጩኽቷ ሁሉ የውሸት፣ ለቅሶዋ ሁሉ የአዞ እንባ እንደነበረ ከተነቃባት ከቶሎሳ ጋር የመጨረሻቸው መሆኑ ታያት። ስለዚህ ያ በሷ ንፁህነት፣ በሷ ተበዳይነት የተጀመረው ድራማ ተጠናክሮ እንዲቀጥልና በሷ አሸናፊነት በድል እንዲደመደም ከተፈለገ ጌትነት በፍጥነት ከዚያች ቤት እንዲባረር ማድረግ ያስፈልጋል፡፡ ይህንን ሃሳቧን ለማሳካት ደግሞ ባሏን እንደ ጠዋቱ እየጮኽች እያጓራችበት ሳይሆን ጣፋጭነቷን እየመገበችው፣ ፍቅሯን እያስኮመኮመችው፣ እያባበለችው ልቡን በመስለብ የትናንትናውን የጌትነት ድፍረት ፍርጥ አድርጋ ልትነግረው ተዘጋጀች...
ለአንድ ቀን ቶሎሳ ውጭ ቢያድር ያቺን ቀዳዳ ተጠቅሞ ለወሲብ ያባበላት
መሆኑን እሷ ግን ለትዳሯ ታማኝ በመሆን ያሳፈረችው መሆኑን ልትነግረውና በፍጥነት ከዚያች ቤት እንዲያባርረው ለማድረግ ዕቅዷን አጠናቅቀች። እንዳይመሽ የለም መሽ፡፡ የቶሎሳ መግቢያ ሰዓቱ ደረሰ። እሷ ተጨነቀች፣ ተጠበበች እንጂ ጌትነት ቀድሟት ነበር። “የት አባቱ ይሄዳል? መግቢያ ቀዳዳው ያቺው የቶሎሳ ጎጆ ነች ተመልሶ መምጣቱ አይቀርም” ነበር ግምቷ። እሷ እንደገመተችው ሳይሆን ዳግም ላይመለስ ለአንዴና ለመጨረሻ ግዜ ተሰናብቶ የሄደ መሆኑን ብታውቅ ኖሮ ቶሎሳን እንደዚያ ተሽቆጥቁጣ መሬት ሆና አትጠብቀውም ነበር። በጥፊ ሲያላጋት ሰማይ ምድሩ ነበር የተደበላለቀባት፡፡ እንደዚያ በጥፊ ሲደረግምባት ዘመዱን አግዞ ለዘመዱ አድልቶ የደበደባት መስሏት ስትበሳጭ ስትብከነከን ነበር የዋለችው። ጌትነት እንደወጣ የሚቀር መሆኑን አስቀድማ አውቃው ቢሆን ኖሮ አራስ ነብር እንደሆነች ትጠብቀው ነበር እንጂ እንደዚያ ላስላሳ ድመት ሆና አትለማመጠውም ነበር። ያንን የጌትነትን ውሳኔ አላወቀችምና ዱላውን ረስታ ብስጭቷን እርግፍ አድርጋ ትታ በፈገግታ
እጆቿን ዘርግታ በፍቅር ስለፍቅር ተቀበለችው።
“ለምንድነው ደግሞ ለምሳ ያልመጣኸው?” አንገቱን እቅፍ አድርጋ ከፊል ሳቅ ከፊል ንዴት ያለበት በሚመስል ሰው ሰራሽ የማስመሰል ችሎታዋ
ፊቷን ልውጥውጥ አድርጋ ጠየቀችው።
“ምን አባቴ ላድርግ ሸዋዬ? በጠዋቱ የቁርሴን ፋንታ አራስ ነብር ሆነሽ
በነገር አጣድፈሽ ከቤት ስታስወጪኝ የተረፈውን ደግሞ በምሳዬ ላይ ጨምረሽ እንዳታባርሪኝ ፈርቼ ነዋ!” አላት በመገረም የሚስቱን ዐይን ዐይኖቿን እያየ :
“ርቦሃል አይደል? ጠዋት ጦምህን እንደወጣህ ነህ አይደል? ! በል አረፍ በልና መክሰስህን ብላ”እጁን እየጎተተች ወደ ጓዳ አስገባችው። ዛሬ ለቶሎሳ አልጋው የመመገቢያ ጠረጴዛ ሆነለት።
“ተመስጌን አምላኬ ላንተ ምን ይሳንሃል? ጠዋት እንደዚያ አራስ ነብር ሆና ከቤት ያባረረችኝ ሴትዮ ማታ ላይ ደግሞ እንደ
👍3