ስንክሳር
7.32K subscribers
825 photos
4 videos
37 files
237 links
በስንክሳር channal ስንክሳሩ ተገልጦ ቅዱሳን ይዘከራሉ፣ ወቅቱን የጠበቁ መረጃዎችን ያገኛሉ፡፡ ይከታተሉን!
Download Telegram
እልልልልልልልልልልል እንኳን አደረሳችሁ
ታላቅ ነቢይን ይሰጣቸው ዘንድ መልአከ ብሥራት ቅዱስ
ገብርኤልን ላከላቸው::
+ቅዱስ ዘካርያስ ሰው ነውና ከደስታ ብዛት በመከራከሩ ድዳ
ሆነ:: ቅድስቲቷ ግን መስከረም 26 ቀን ታላቁን ሰው ጸንሳ ለ6
ወራት ራሷን ሠወረች:: በ6ኛው ወር የፍጥረት ሁሉ ጌታ
በተጸነሰ ጊዜ #የአርያም_ንግሥት #ድንግል_እመቤታችን ደጋ
ደጋውን ወደ ኤልሳቤጥ መጣች:: ሁለቱ ቅዱሳት
የእህትማማች ልጆች ናቸው::
+የአምላክ እናቱ ስትደርስና "ሰላም" ስትላቸው # መንፈስ_
ቅዱስ በእናትና ልጅ ወርዶ ኤልሳቤጥ በምስጋና: ዮሐንስ
ደግሞ ገና በማሕጸን ሳለ በደስታ ዘለለ (ሰገደ):: ከዚህ
በሁዋላ በዚህች ቀን (ሰኔ 30) ተወልዶ: አባቱ ዘካርያስ
" #ዮሐንስ " ሲለው አንደበቱ ተፈትቶለታል::
+"+ # መጥምቀ_መለኮት ቅዱስ ዮሐንስ +"+
¤የቅዱሳኑ ዘካርያስና ኤልሳቤጥ ልጅ
¤በማሕጸን ሳለ መንፈስ ቅዱስ የሞላበት
¤በበርኀ ያደገና በገዳማዊ ቅድስና ያጌጠ
¤እሥራኤልን ለንስሃ ያጠመቀ
¤የጌታችንን መንገድ የጠረገ
¤ጌታውን ያጠመቀና
¤ስለ እውነት አንገቱን የተቆረጠ ታላቅ ሰው ነው::
+ስለዚሕም #ቤተ_ክርስቲያን # ነቢይ: # ሐዋርያ: #ሰማዕት :
# ጻድቅ : #ገዳማዊ : #መጥምቀ_መለኮት: # ጸያሔ_ፍኖት :
# ቃለ_ዐዋዲ ብላ ታከብረዋለች::
እንኩዋን ለካህኑ #ሰማዕት_ቅዱስ_አልዓዛር እና
ለቅዱሳን ቤተሰቡ ዓመታዊ የዕረፍት በዓል በሰላም
አደረሳችሁ
#ቅዱስ_አልዓዛር_ካህን
ይህ ቅዱስ #የብሉይ_ኪዳን_ሰማዕታት ተብለው
ከሚታወቁት ዋነኛው ነው:: የነበረበት ዘመንም ቅድመ ልደተ
ክርስቶስ ሲሆን " #ዓመተ_መቃብያን / #ዘመነ_ካህናት "
ይባላል::
በወቅቱ ሰሎሜ የምትባል ደግ ሴት አግብቶ ይኖር የነበረው
ቅዱስ አልዓዛር በኢየሩሳሌም ተወዳጅ ነበር:: ሐረገ ትውልዱ
ከአሮን ወገን ነውና በክህነቱ ተግቶ ያገለግል ነበር:: በዚያ
ላይ ሊቀ ካህንነትን በመመረጡ ሕዝቡን ይሠራ: ያስተምር:
ያስተዳድር ነበር::
ቅዱስ አልዓዛር ከተባረከች ሚስቱ ሰሎሜ 7 ወንዶች ልጆችን አፍርቷል:: እነርሱንም በሥርዓት አሳድጐ የቤተ እግዚአብሔር አገልጋዮች እንዲሆኑ አድርጐ ነበር:: በዚያው
ዘመን በኢየሩሳሌም አካባቢ የሚኖሩ 3 እኩያን (ክፉ) ካህናት
ነበሩ:: እነዚሁም ሕዝቡን ከማስቸገር: ፈጣሪን ከማሳዘን ቦዝነው
አያውቁም ነበር:: የክፋታቸው መጨረሻ ግን የገዛ ሃገራቸውን
ማጥፋት ሆነ:: ነገሩ እንዲህ ነው:- 3ቱም ተመካክረው
የአልዓዛርን የሊቀ ካህንነት ቦታ ሊቀሙ ወስነው ወደ እርሱ
ሔዱና እንዲህ አሉት::
"ሹመት በተርታ: ሥጋ በገበታ" ሲሆን ያምራልና እኛ
በተራችን በወንበሩ ላይ እንቀመጥ::" እርሱ ግን "ሕዝቡን ጠይቃችሁ ተሾሙ" አላቸው:: እነርሱም
ሕዝቡን ጠርተው "ሹመት ይገባናል" ቢሏቸው ሕዝቡ መልሶ
"አልዓዛርን የሾመው እግዚአብሔር ነውና እናንተም ከፈጣሪ ጠይቃችሁ ተሾሙ" አሏቸው:: በዚህ ጊዜ 3ቱ እኩያን ተቆጡ:: ምክንያቱም እግዚአብሔር እንደ ማይሰጣቸው ያውቃሉና:: ወዲያው ግን 3ቱም
ከአካባቢው ጠፉ:: ከኢየሩሳሌም ወጥተው ወደ ጨካኙ
የግሪክ ንጉሥ አንጥያኮስ ሔዱ::
+አንጥያኮስ ማለት "ቀኝ ዐይናችሁን ገብሩልኝ" የሚል ንጉሥ ነው:: እርሱን "#ኢየሩሳሌም ባለቤት የላትምና ሒደህ ውረራት" አሉት:: "አጥሩ ጥብቅ ነው:: በምን እገባለሁ?"
ቢላቸው "እኛ በመላ እናስገባሃለን" አሉት:: እርሱም
240,000 ሠራዊት አስከትቶ ወረደ:: እነርሱ ቀድመው ወደ ኢየሩሳሌም ገብተው ያስወሩ ጀመር::
"እናንተ ሹመት ብትነሱንም እኛ ግን አንጥያኮስን ያህል ንጉሥ
በእሥራኤል አምላክ አሳምነን መጣን" እያሉ ይሰብኩ ገቡ::
ቅዱስ አልዓዛር "አትስሟቸው:: በዚያም ላይ አሕዛብ
የተቀደሰውን ምድር መርገጥ የለባቸውም" ብሎ ነበር::
ነገር ግን አንዳንድ ችኩሎች አይጠፉምና ፈጥነው
የከተማዋን በር ከፈቱት:: ሠራዊቱን ደብቆ ትንሽ ራሱን የቆመ
የመሰለው አንጥያኮስ በምክንያት: በክፋትና በመላ ሁሉን
ሠራዊቱን አስገባ:: የሚገርመው በጊዜው የከተማዋ ሕዝብ
12 እልፍ (120,000) ሲሆን ንጉሡ ያስገባው ሠራዊት ግን
24 እልፍ (240,000) ሆኖ ተገኘ::
ወዲያው አንጥያኮስ ሕዝቡን ሰበሰበና አልዓዛርን ለብቻው
ጠርቶ ተናገረው:: "አንተ አምላክህን እንደምትወድ
ሰምቻለሁ:: አንተ የበጉን መስዋዕት በልተህ: #ለስዕለ_
ኪሩብ ሰግደህ: ሕዝቡን ግን እሪያ (አሳማ) እንዲበላና
ለጸፀሐይ እንዲሰግድ አድርግልኝ" አለው::
ቅዱስ አልዓዛር መለሰለት:- "እግዚአብሔር የሾመኝኮ በጐ
ሃይማኖትን ላስተምር እንጂ ለክፋት አይደለም:: ለሕዝቤ
የክፋት አብነት ፈጽሞ አልሆንም" አለው:: ያን ጊዜ ንጉሡ
በቅዱሱ ላይ ተቆጣ:: "የምልህን ካላደረግህ ብዙ ግፍ
ይደርስብሃል" ቢለው ቅዱሱ መልሶ "የፈለግኸውን አድርግ"
አለው:: በዚያን ጊዜ ንጉሡ የቅዱሱን ሚስትና 7 ልጆች
እንዲያመጡለት አዘዘ:: ቅዱሱ እያየ ከፊቱ ላይ 7ቱንም
ልጆቹን በሰይፍ አስመታቸውና 7ቱም ወደቁ:: ለአንድ አባት
ይህ የመጨረሻው መራራ ፈተና ነው:: #አልዓዛር ግን ምን
አንጀቱ በኀዘን ቢቃጠልም ከልጆቹ ለእግዚአብሔር አድልቷልና
ቻለው ታገሠው::
በዚህ ለውጥ እንዳልመጣ ያየው ንጉሡ ሌላ ፍርድ
ተናገረ:: ቅዱሱንና ሚስቱን ( #ሰሎሜን ) በፈትል ጠቅልለው
በሠም ነከሯቸው:: (ጧፍ እንደሚሠራበት መንገድ ማለት
ነው:: )
አሁንም ግን ከአምልኮታቸው ፈቀቅ ባለማለታቸው ትልቅ
ብረት ምጣድ ተጥዶ: 2ቱም ከነነፍሳቸው እንዲቃጠሉ
ተደረገ:: ቀጥሎም ሕዝቡን እንዲፈጁ አዋጅ ወጣ::
በከተማዋ ከነበረው ሕዝብ 40,000 ያህሉ ተገደሉ::
+40,000 ያህሉ ሲማረኩ 40,000 ያህሉን ደግሞ # ይሁዳ
የሚባል አርበኛ በር ሰብሮ ይዟቸው ሸሸ:: "እንሾማለን:
እንሸለማለን" ብለው ሕዝባቸውን ያስፈጁ እነዚያ ካህናትም
#እግዚአብሔር ፈርዶባቸው እነርሱም ተገደሉ:: ቅዱሱ
የአልዓዛር ቤተሰብ ግን የክብርን አክሊል አግኝተዋል::
#የእሥራኤል_አምላክ ቸሩ_እግዚአብሔር_እንዲህ ካለው_መከራ_በኪነ_ጥበቡ_ይሰውረን::_ከቅዱሳኑ_በረከትም_አይለየን::
✞✞✞ እንኩዋን ለካህኑ #ሰማዕት_አባ_ኦሪ ዓመታዊ
የዕረፍት በዓል በሰላም አደረሳችሁ ✞✞✞
#ቅዱስ_አባ_ኦሪ_ቀሲስ "
ይህ ቅዱስ አባት የዘመነ ሰማዕታት ፍሬ ነው:: በዘመኑ
(በ3ኛው መቶ ክ/ዘመን) #ክርስቲያን መሆን ብቻውን
ለሞት እንደሚያበቃ ወንጀል ይቆጠር ነበር:: በጊዜው
ክርስቲያን ከመሆን በባሰ መንገድ #እረኛ_ካህን ሆኖ
መገኘት በጣም ከባድ ነበር::
ከመነሻውም ያን ጊዜ ክህነት የሚሰጠው በሕዝቡና
በሊቀ ዻዻሱ ምርጫ ነበር እንጂ እንደ ዘንድሮ "እኔን ሹሙኝ" ማለት ልማድ አልነበረም:: ምዕመናንም
እረኛቸውን ሲመርጡ በጉቦ: በዝምድና አይደለም::
በርትቶ የሚያበረታቸውን: ለመንጋው ራሱን አሳልፎ
የሚሰጠውን ይመርጣሉ እንጂ::
ያልሆነ ሰው ለክህነት ቢመረጥ አንድም ክዶ ያስክዳል:
ሲቀጥልም ለሕዝቡ መሰናክል መሆኑ አይቀርም::
በጊዜው ( #በዘመነ_ሰማዕታት ) የነበሩ ካህናት የቤት
ሥራቸውም ማስተማር ብቻ አልነበረም:: በድፍረት
በምዕመናን ፊት አንገታቸውን ለሰይፍ መስጠት
ይጠበቅባቸው ነበር እንጂ::
ይህንን በገሃድ መፈጸም ከቻሉ አበው አንዱ ደግሞ አባ
ኦሪ ቀሲስ ናቸው:: ቅዱሱ ተወልደው ባደጉባት ሃገረ
#ስጥኑፍ (የግብጽ አውራጃ ናት) መጻሕፍትን የተማሩ:
ተወዳጅ እና ደግ ሰው ነበሩ::
አባ ኦሪ ገና ከወጣትነት ቀዳሚ ግብራቸው መንኖ
ጥሪት (ምናኔ) ነበር:: በንጽሕናቸው ደስ የተሰኙ
ምዕመናንም "ቅስና ተሹመህ ምራን: አስተምረን"
ቢሏቸው አበው ውዳሴ ከንቱን አይፈልጉምና "አይሆንም" አሉ::
ነገሩ ፈቃደ እግዚአብሔር ነበረና አባ ኦሪ ቅስናን ተሹመው ያገለግሉ ገቡ:: ሕዝቡን በማስተማር:
በመምከር: ደካማውን በማጽናት ብዙ ደክመዋል:: ከቅድስናቸው የተነሳ ቅዳሴ ሊቀድሱ ሲገቡ #ጌታችን በገሃድ ይገለጥላቸው ነበር:: ሠራዊተ መላእክትም
ከበው ይነጋገሯቸው ነበር::
#ሥጋውን_ደሙን በማቀበልም ተግተው ዘመናት
አለፉ:: ቆይቶ ግን ያ በዜና ይሰሙት የነበረ መከራ
( #ሰማዕትነት ) በደጃቸው ደረሰ:: በጊዜው ብዙ ሰው
በሰማዕትነት አለፈ:: አባ ኦሪም ወደ #ቤተ_እግዚአብሔር
ገብተው ስለ ራሳቸውና ሕዝቡ ጽናትን: ደኅንነትን ለመኑና
ከቤተ ክርስቲያን ወጡ::
በቀጥታ የሔዱትም ወደ #ዐውደ_ስምዕ (የምሥክርነት
አደባባይ) ነበር:: በመኮንኑ ፊት ቀርበው "#ክርስቶስ
አምላክ: ፈጣሪ: የሁሉ ጌታ ነው:: የእናንተ ጣዖት ግን
ጠፊ: ረጋፊ: ወርቅ: ብር: እንጨትና ድንጋይ ነው" ሲሉ
በድፍረት ተናገሩ:: መኮንኑም ከአነጋገራቸው የተነሳ ተቆጥቶ ሥቃይን አዘዘባቸው:: ወታደሮቹ ይሆናል ያሉትን ማሰቃያ ሁሉ
#አባ_ኦሪ ላይ ሞከሩ:: በሁዋላም ወደ ጨለማ እሥር
ቤት ወስደው ጣሏቸው:: በእሥር ቤት ውስጥም ድውያንን ፈወሱ: ተአምራትን ሠሩ:: ይሕንን ዜና የሰሙ አሕዛብ ብዙ ድውያንን ሰብስበው መጡ:: ቅዱሱም ሁሉን በጸሎታቸው ፈወሱ:: በዚህ
ምክንያትም ብዙ አሕዛብ ወደ ክርስትና መጥተዋል::
በክርስቶስ አምነውም ለክብር በቅተዋል:: ቅዱሱንም ከእሥር ቤት አውጥተው ብዙ ካሰቃዩዋቸው በሁዋላ በዚህች ቀን ገድለዋቸው ሰማዕትነትን
አግኝተዋል:: #በአክሊለ_ጽድቅ ላይ #አክሊለ_ካህናትን :
#በአክሊለ_ካህናትም ላይ #አክሊለ_ሰማዕታትን
ደርበዋል::
#አምላከ_ቅዱሳን_በአባቶቻችን_ጽናት_ያጽናን::_ጸጋ_በረከታቸውንም_ይክፈለን::
#ቅዱስ_ዮሐንስ_መጥምቅ
¤የቅዱሳኑ ዘካርያስና ኤልሳቤጥ ልጅ
¤በማሕጸን ሳለ #መንፈስ_ቅዱስ የሞላበት
¤በበርኀ ያደገና በገዳማዊ ቅድስና ያጌጠ
¤እሥራኤልን ለንስሃ ያጠመቀ
¤የጌታችንን መንገድ የጠረገ
¤ጌታውን ያጠመቀና
¤ስለ እውነት አንገቱን የተቆረጠ ታላቅ ሰው ነው::
+ስለዚሕም ቤተ ክርስቲያን # ነቢይ: #ሐዋርያ: #ሰማዕት :
#ጻድቅ : #ገዳማዊ : #መጥምቀ_መለኮት : #ጸያሔ_ፍኖት
#ቃለ_ዐዋዲ ብላ ታከብረዋለች::
ቅዱሱ በዚህች ዕለት ወደ እሥር ቤት ገብቷል:: ይሕስ
እንደ ምን ነው ቢሉ:-
¤ንጉሡ ሔሮድስ የወንድሙን የፊልዾስን ሚስት ሔሮድያዳን
በማግባቱና በመሰል ክፋቶቹ ቅዱስ ዮሐንስ ይገስጸው ነበር::
ቅዱስ ዮሐንስ "መምሕር ወመገስጽ: ዘኢያደሉ ለገጽ - ፊት
አይቶ የማያዳላ" ነውና ገሰጸው::
ሔሮድስ ቅዱሱን ይፈራው: ያከብረውም ነበር:: በሁዋላ
ግን ፈቃደ ሥጋው ስላየለበት: በተለይ ደግሞ ከ7 ቀናት
በሁዋላ ልደቱን ሲያከብር እንዳይረብሸው በመስጋት በዚህች
ቀን በወታደሮቹ አስይዞ እሥር ቤት ውስጥ ጥሎታል:: ለ7
ቀናት በጨለማ ውስጥ አሥሮ መስከረም 2 ቀን አንገቱን
እንዴት እንዳስቆረጠው ዕለቱን ጠብቀን እንመለከታለንና የዚያ
ሰው ይበለን::
እንኩዋን ለካህኑ #ሰማዕት_ቅዱስ_አልዓዛር እና
ለቅዱሳን ቤተሰቡ ዓመታዊ የዕረፍት በዓል በሰላም
አደረሳችሁ
#ቅዱስ_አልዓዛር_ካህን
ይህ ቅዱስ #የብሉይ_ኪዳን_ሰማዕታት ተብለው
ከሚታወቁት ዋነኛው ነው:: የነበረበት ዘመንም ቅድመ ልደተ
ክርስቶስ ሲሆን " #ዓመተ_መቃብያን / #ዘመነ_ካህናት "
ይባላል::
በወቅቱ ሰሎሜ የምትባል ደግ ሴት አግብቶ ይኖር የነበረው
ቅዱስ አልዓዛር በኢየሩሳሌም ተወዳጅ ነበር:: ሐረገ ትውልዱ
ከአሮን ወገን ነውና በክህነቱ ተግቶ ያገለግል ነበር:: በዚያ
ላይ ሊቀ ካህንነትን በመመረጡ ሕዝቡን ይሠራ: ያስተምር:
ያስተዳድር ነበር::
ቅዱስ አልዓዛር ከተባረከች ሚስቱ ሰሎሜ 7 ወንዶች ልጆችን አፍርቷል:: እነርሱንም በሥርዓት አሳድጐ የቤተ እግዚአብሔር አገልጋዮች እንዲሆኑ አድርጐ ነበር:: በዚያው
ዘመን በኢየሩሳሌም አካባቢ የሚኖሩ 3 እኩያን (ክፉ) ካህናት
ነበሩ:: እነዚሁም ሕዝቡን ከማስቸገር: ፈጣሪን ከማሳዘን ቦዝነው
አያውቁም ነበር:: የክፋታቸው መጨረሻ ግን የገዛ ሃገራቸውን
ማጥፋት ሆነ:: ነገሩ እንዲህ ነው:- 3ቱም ተመካክረው
የአልዓዛርን የሊቀ ካህንነት ቦታ ሊቀሙ ወስነው ወደ እርሱ
ሔዱና እንዲህ አሉት::
"ሹመት በተርታ: ሥጋ በገበታ" ሲሆን ያምራልና እኛ
በተራችን በወንበሩ ላይ እንቀመጥ::" እርሱ ግን "ሕዝቡን ጠይቃችሁ ተሾሙ" አላቸው:: እነርሱም
ሕዝቡን ጠርተው "ሹመት ይገባናል" ቢሏቸው ሕዝቡ መልሶ
"አልዓዛርን የሾመው እግዚአብሔር ነውና እናንተም ከፈጣሪ ጠይቃችሁ ተሾሙ" አሏቸው:: በዚህ ጊዜ 3ቱ እኩያን ተቆጡ:: ምክንያቱም እግዚአብሔር እንደ ማይሰጣቸው ያውቃሉና:: ወዲያው ግን 3ቱም
ከአካባቢው ጠፉ:: ከኢየሩሳሌም ወጥተው ወደ ጨካኙ
የግሪክ ንጉሥ አንጥያኮስ ሔዱ::
+አንጥያኮስ ማለት "ቀኝ ዐይናችሁን ገብሩልኝ" የሚል ንጉሥ ነው:: እርሱን "#ኢየሩሳሌም ባለቤት የላትምና ሒደህ ውረራት" አሉት:: "አጥሩ ጥብቅ ነው:: በምን እገባለሁ?"
ቢላቸው "እኛ በመላ እናስገባሃለን" አሉት:: እርሱም
240,000 ሠራዊት አስከትቶ ወረደ:: እነርሱ ቀድመው ወደ ኢየሩሳሌም ገብተው ያስወሩ ጀመር::
"እናንተ ሹመት ብትነሱንም እኛ ግን አንጥያኮስን ያህል ንጉሥ
በእሥራኤል አምላክ አሳምነን መጣን" እያሉ ይሰብኩ ገቡ::
ቅዱስ አልዓዛር "አትስሟቸው:: በዚያም ላይ አሕዛብ
የተቀደሰውን ምድር መርገጥ የለባቸውም" ብሎ ነበር::
ነገር ግን አንዳንድ ችኩሎች አይጠፉምና ፈጥነው
የከተማዋን በር ከፈቱት:: ሠራዊቱን ደብቆ ትንሽ ራሱን የቆመ
የመሰለው አንጥያኮስ በምክንያት: በክፋትና በመላ ሁሉን
ሠራዊቱን አስገባ:: የሚገርመው በጊዜው የከተማዋ ሕዝብ
12 እልፍ (120,000) ሲሆን ንጉሡ ያስገባው ሠራዊት ግን
24 እልፍ (240,000) ሆኖ ተገኘ::
ወዲያው አንጥያኮስ ሕዝቡን ሰበሰበና አልዓዛርን ለብቻው
ጠርቶ ተናገረው:: "አንተ አምላክህን እንደምትወድ
ሰምቻለሁ:: አንተ የበጉን መስዋዕት በልተህ: #ለስዕለ_
ኪሩብ ሰግደህ: ሕዝቡን ግን እሪያ (አሳማ) እንዲበላና
ለጸፀሐይ እንዲሰግድ አድርግልኝ" አለው::
ቅዱስ አልዓዛር መለሰለት:- "እግዚአብሔር የሾመኝኮ በጐ
ሃይማኖትን ላስተምር እንጂ ለክፋት አይደለም:: ለሕዝቤ
የክፋት አብነት ፈጽሞ አልሆንም" አለው:: ያን ጊዜ ንጉሡ
በቅዱሱ ላይ ተቆጣ:: "የምልህን ካላደረግህ ብዙ ግፍ
ይደርስብሃል" ቢለው ቅዱሱ መልሶ "የፈለግኸውን አድርግ"
አለው:: በዚያን ጊዜ ንጉሡ የቅዱሱን ሚስትና 7 ልጆች
እንዲያመጡለት አዘዘ:: ቅዱሱ እያየ ከፊቱ ላይ 7ቱንም
ልጆቹን በሰይፍ አስመታቸውና 7ቱም ወደቁ:: ለአንድ አባት
ይህ የመጨረሻው መራራ ፈተና ነው:: #አልዓዛር ግን ምን
አንጀቱ በኀዘን ቢቃጠልም ከልጆቹ ለእግዚአብሔር አድልቷልና
ቻለው ታገሠው::
በዚህ ለውጥ እንዳልመጣ ያየው ንጉሡ ሌላ ፍርድ
ተናገረ:: ቅዱሱንና ሚስቱን ( #ሰሎሜን ) በፈትል ጠቅልለው
በሠም ነከሯቸው:: (ጧፍ እንደሚሠራበት መንገድ ማለት
ነው:: )
አሁንም ግን ከአምልኮታቸው ፈቀቅ ባለማለታቸው ትልቅ
ብረት ምጣድ ተጥዶ: 2ቱም ከነነፍሳቸው እንዲቃጠሉ
ተደረገ:: ቀጥሎም ሕዝቡን እንዲፈጁ አዋጅ ወጣ::
በከተማዋ ከነበረው ሕዝብ 40,000 ያህሉ ተገደሉ::
+40,000 ያህሉ ሲማረኩ 40,000 ያህሉን ደግሞ # ይሁዳ
የሚባል አርበኛ በር ሰብሮ ይዟቸው ሸሸ:: "እንሾማለን:
እንሸለማለን" ብለው ሕዝባቸውን ያስፈጁ እነዚያ ካህናትም
#እግዚአብሔር ፈርዶባቸው እነርሱም ተገደሉ:: ቅዱሱ
የአልዓዛር ቤተሰብ ግን የክብርን አክሊል አግኝተዋል::
#የእሥራኤል_አምላክ ቸሩ_እግዚአብሔር_እንዲህ ካለው_መከራ_በኪነ_ጥበቡ_ይሰውረን::_ከቅዱሳኑ_በረከትም_አይለየን::
✞✞✞ እንኩዋን ለካህኑ #ሰማዕት_አባ_ኦሪ ዓመታዊ
የዕረፍት በዓል በሰላም አደረሳችሁ ✞✞✞
#ቅዱስ_አባ_ኦሪ_ቀሲስ "
ይህ ቅዱስ አባት የዘመነ ሰማዕታት ፍሬ ነው:: በዘመኑ
(በ3ኛው መቶ ክ/ዘመን) #ክርስቲያን መሆን ብቻውን
ለሞት እንደሚያበቃ ወንጀል ይቆጠር ነበር:: በጊዜው
ክርስቲያን ከመሆን በባሰ መንገድ #እረኛ_ካህን ሆኖ
መገኘት በጣም ከባድ ነበር::
ከመነሻውም ያን ጊዜ ክህነት የሚሰጠው በሕዝቡና
በሊቀ ዻዻሱ ምርጫ ነበር እንጂ እንደ ዘንድሮ "እኔን ሹሙኝ" ማለት ልማድ አልነበረም:: ምዕመናንም
እረኛቸውን ሲመርጡ በጉቦ: በዝምድና አይደለም::
በርትቶ የሚያበረታቸውን: ለመንጋው ራሱን አሳልፎ
የሚሰጠውን ይመርጣሉ እንጂ::
ያልሆነ ሰው ለክህነት ቢመረጥ አንድም ክዶ ያስክዳል:
ሲቀጥልም ለሕዝቡ መሰናክል መሆኑ አይቀርም::
በጊዜው ( #በዘመነ_ሰማዕታት ) የነበሩ ካህናት የቤት
ሥራቸውም ማስተማር ብቻ አልነበረም:: በድፍረት
በምዕመናን ፊት አንገታቸውን ለሰይፍ መስጠት
ይጠበቅባቸው ነበር እንጂ::
ይህንን በገሃድ መፈጸም ከቻሉ አበው አንዱ ደግሞ አባ
ኦሪ ቀሲስ ናቸው:: ቅዱሱ ተወልደው ባደጉባት ሃገረ
#ስጥኑፍ (የግብጽ አውራጃ ናት) መጻሕፍትን የተማሩ:
ተወዳጅ እና ደግ ሰው ነበሩ::
አባ ኦሪ ገና ከወጣትነት ቀዳሚ ግብራቸው መንኖ
ጥሪት (ምናኔ) ነበር:: በንጽሕናቸው ደስ የተሰኙ
ምዕመናንም "ቅስና ተሹመህ ምራን: አስተምረን"
ቢሏቸው አበው ውዳሴ ከንቱን አይፈልጉምና "አይሆንም" አሉ::
ነገሩ ፈቃደ እግዚአብሔር ነበረና አባ ኦሪ ቅስናን ተሹመው ያገለግሉ ገቡ:: ሕዝቡን በማስተማር:
በመምከር: ደካማውን በማጽናት ብዙ ደክመዋል:: ከቅድስናቸው የተነሳ ቅዳሴ ሊቀድሱ ሲገቡ #ጌታችን በገሃድ ይገለጥላቸው ነበር:: ሠራዊተ መላእክትም
ከበው ይነጋገሯቸው ነበር::
#ሥጋውን_ደሙን በማቀበልም ተግተው ዘመናት
አለፉ:: ቆይቶ ግን ያ በዜና ይሰሙት የነበረ መከራ
( #ሰማዕትነት ) በደጃቸው ደረሰ:: በጊዜው ብዙ ሰው
በሰማዕትነት አለፈ:: አባ ኦሪም ወደ #ቤተ_እግዚአብሔር
ገብተው ስለ ራሳቸውና ሕዝቡ ጽናትን: ደኅንነትን ለመኑና
ከቤተ ክርስቲያን ወጡ::
በቀጥታ የሔዱትም ወደ #ዐውደ_ስምዕ (የምሥክርነት
አደባባይ) ነበር:: በመኮንኑ ፊት ቀርበው "#ክርስቶስ
አምላክ: ፈጣሪ: የሁሉ ጌታ ነው:: የእናንተ ጣዖት ግን
ጠፊ: ረጋፊ: ወርቅ: ብር: እንጨትና ድንጋይ ነው" ሲሉ
በድፍረት ተናገሩ:: መኮንኑም ከአነጋገራቸው የተነሳ ተቆጥቶ ሥቃይን አዘዘባቸው:: ወታደሮቹ ይሆናል ያሉትን ማሰቃያ ሁሉ
#አባ_ኦሪ ላይ ሞከሩ:: በሁዋላም ወደ ጨለማ እሥር
ቤት ወስደው ጣሏቸው:: በእሥር ቤት ውስጥም ድውያንን ፈወሱ: ተአምራትን ሠሩ:: ይሕንን ዜና የሰሙ አሕዛብ ብዙ ድውያንን ሰብስበው መጡ:: ቅዱሱም ሁሉን በጸሎታቸው ፈወሱ:: በዚህ
ምክንያትም ብዙ አሕዛብ ወደ ክርስትና መጥተዋል::
በክርስቶስ አምነውም ለክብር በቅተዋል:: ቅዱሱንም ከእሥር ቤት አውጥተው ብዙ ካሰቃዩዋቸው በሁዋላ በዚህች ቀን ገድለዋቸው ሰማዕትነትን
አግኝተዋል:: #በአክሊለ_ጽድቅ ላይ #አክሊለ_ካህናትን :
#በአክሊለ_ካህናትም ላይ #አክሊለ_ሰማዕታትን
ደርበዋል::
#አምላከ_ቅዱሳን_በአባቶቻችን_ጽናት_ያጽናን::_ጸጋ_በረከታቸውንም_ይክፈለን::