♥እልልልልልልልልልልል እንኳን አደረሳችሁ ♥
ታላቅ ነቢይን ይሰጣቸው ዘንድ መልአከ ብሥራት ቅዱስ
ገብርኤልን ላከላቸው::
+ቅዱስ ዘካርያስ ሰው ነውና ከደስታ ብዛት በመከራከሩ ድዳ
ሆነ:: ቅድስቲቷ ግን መስከረም 26 ቀን ታላቁን ሰው ጸንሳ ለ6
ወራት ራሷን ሠወረች:: በ6ኛው ወር የፍጥረት ሁሉ ጌታ
በተጸነሰ ጊዜ #የአርያም_ንግሥት #ድንግል_እመቤታችን ደጋ
ደጋውን ወደ ኤልሳቤጥ መጣች:: ሁለቱ ቅዱሳት
የእህትማማች ልጆች ናቸው::
+የአምላክ እናቱ ስትደርስና "ሰላም" ስትላቸው # መንፈስ_
ቅዱስ በእናትና ልጅ ወርዶ ኤልሳቤጥ በምስጋና: ዮሐንስ
ደግሞ ገና በማሕጸን ሳለ በደስታ ዘለለ (ሰገደ):: ከዚህ
በሁዋላ በዚህች ቀን (ሰኔ 30) ተወልዶ: አባቱ ዘካርያስ
" #ዮሐንስ " ሲለው አንደበቱ ተፈትቶለታል::
+"+ # መጥምቀ_መለኮት ቅዱስ ዮሐንስ +"+
¤የቅዱሳኑ ዘካርያስና ኤልሳቤጥ ልጅ
¤በማሕጸን ሳለ መንፈስ ቅዱስ የሞላበት
¤በበርኀ ያደገና በገዳማዊ ቅድስና ያጌጠ
¤እሥራኤልን ለንስሃ ያጠመቀ
¤የጌታችንን መንገድ የጠረገ
¤ጌታውን ያጠመቀና
¤ስለ እውነት አንገቱን የተቆረጠ ታላቅ ሰው ነው::
+ስለዚሕም #ቤተ_ክርስቲያን # ነቢይ: # ሐዋርያ: #ሰማዕት :
# ጻድቅ : #ገዳማዊ : #መጥምቀ_መለኮት: # ጸያሔ_ፍኖት :
# ቃለ_ዐዋዲ ብላ ታከብረዋለች::
ታላቅ ነቢይን ይሰጣቸው ዘንድ መልአከ ብሥራት ቅዱስ
ገብርኤልን ላከላቸው::
+ቅዱስ ዘካርያስ ሰው ነውና ከደስታ ብዛት በመከራከሩ ድዳ
ሆነ:: ቅድስቲቷ ግን መስከረም 26 ቀን ታላቁን ሰው ጸንሳ ለ6
ወራት ራሷን ሠወረች:: በ6ኛው ወር የፍጥረት ሁሉ ጌታ
በተጸነሰ ጊዜ #የአርያም_ንግሥት #ድንግል_እመቤታችን ደጋ
ደጋውን ወደ ኤልሳቤጥ መጣች:: ሁለቱ ቅዱሳት
የእህትማማች ልጆች ናቸው::
+የአምላክ እናቱ ስትደርስና "ሰላም" ስትላቸው # መንፈስ_
ቅዱስ በእናትና ልጅ ወርዶ ኤልሳቤጥ በምስጋና: ዮሐንስ
ደግሞ ገና በማሕጸን ሳለ በደስታ ዘለለ (ሰገደ):: ከዚህ
በሁዋላ በዚህች ቀን (ሰኔ 30) ተወልዶ: አባቱ ዘካርያስ
" #ዮሐንስ " ሲለው አንደበቱ ተፈትቶለታል::
+"+ # መጥምቀ_መለኮት ቅዱስ ዮሐንስ +"+
¤የቅዱሳኑ ዘካርያስና ኤልሳቤጥ ልጅ
¤በማሕጸን ሳለ መንፈስ ቅዱስ የሞላበት
¤በበርኀ ያደገና በገዳማዊ ቅድስና ያጌጠ
¤እሥራኤልን ለንስሃ ያጠመቀ
¤የጌታችንን መንገድ የጠረገ
¤ጌታውን ያጠመቀና
¤ስለ እውነት አንገቱን የተቆረጠ ታላቅ ሰው ነው::
+ስለዚሕም #ቤተ_ክርስቲያን # ነቢይ: # ሐዋርያ: #ሰማዕት :
# ጻድቅ : #ገዳማዊ : #መጥምቀ_መለኮት: # ጸያሔ_ፍኖት :
# ቃለ_ዐዋዲ ብላ ታከብረዋለች::
♥ቅድስት ኤልሳቤጥ ♥
በወንጌላዊው የተመሰገነች እናታችን ቅድስት
ኤልሳቤጥ ትውልዷ ከነገደ #ሌዊ ነው:: ሐረገ ሙላዷም
ከቅዱስ #አሮን_ካህን ወገን ይመዘዛል:: ከአሮን በቴክታና
በጥሪቃ ወርዶ #ሔርሜላ ላይ ይደርሳል::
✝ይህቺ ሔርሜላ የምትባል ደግ ሴት #ማጣት ("ጣ"
ጠብቆ ይነበብ) የሚባል የተባረከ ሰው አግብታ 3
ቡሩካት ልጆችን ወለደች:: የመጀመሪያዋን 'ማርያም'
አሏት:: እርሷ ቅድስት ሰሎሜን ወለደች:: ሁለተኛዋን
'ሶፍያ' አሏት:: እርሷ ደግሞ ቅድስት ኤልሳቤጥን
ወለደች::
✝ሦስተኛዋ ግን የተለየች ናት:: 'ሐና' ብለው ሰየሟት::
እርሷም የሰማይና የምድር ንግሥት የሆነችውን ድንግል
ማርያምን ወለደች:: በዚህም መሠረት ድንግል ማርያም:
ቅድስት ኤልሳቤጥና ቅድስት ሰሎሜ የእህትማማች
ልጆች ናቸው::
✝ቅድስት ኤልሳቤጥ እድሜዋ በደረሰ ጊዜ ስም አጠራሩ
የከበረ: ደግ ካህን ለሆነ: ቅዱስ #ዘካርያስ አጋቧት::
እርሷ የሊቀ ካህናቱ ሚስት ናትና ክብሯ ከፍ ያለ ነበር::
ምንም ልጅ ባይኖራትም ዘወትር በጸሎትና በጾም:
ምጽዋትንም በማዘውተር: ነዳያንንም በማሰብ የምትኖር
እናትም ነበረች::
ቅዱስ ወንጌል ላይ ከእመቤታችን ቀጥሎ የነዘካርያስን
ቤተሰብ ያህል ክብሩ የተገለጠለት ፍጡር ይኖራል ብሎ
መናገሩ ይከብዳል:: ቅዱስ ሉቃስ ወንጌሉን የጀመረው
በዚህ ቅዱስ ቤተሰብ ነውና መንፈስ ቅዱስ እንዲህ ሲል
አጽፎታል::
"ዘካርያስ ካህኑና ቅድስት ኤልሳቤጥ በሰውና
በእግዚአብሔር ፊት ያለ ነቀፋ የሚኖሩ ጻድቃን ነበሩ"
ይላቸዋል:: (ሉቃ. 1:6)
✝የሰውን እንተወውና በእግዚአብሔር ፊት ያለ ነቀፋ
መኖር ምን ይረቅ?
ለዚህ አንክሮ (አድናቆት) ይገባል! እሊህ ቅዱሳን ባልና
ሚስት ግን መካኖች በመሆናቸው ልጅ ሳይወልዱ
ዘመናቸው አልፎ ነበር:: እንደ ቤተ ክርስቲያን ትውፊት
ዕድሜአቸው የኤልሳቤጥ 90 የዘካርያስ 100 ደግሞ
ደርሶ ነበር::
✝ፍጹም መታገሳቸውን የተመለከተ ጌታ ግን በስተ
እርጅናቸው ከሰው ሁሉ በላይ የሆነ ታላቅ ነቢይን
ይሰጣቸው ዘንድ መልአከ ብሥራት ቅዱስ ገብርኤልን
ላከላቸው:: ቅድስቲቷ መስከረም 26 ቀን ታላቁን ሰው
ጸንሳ ለ6 ወራት ራሷን ሠወረች::
✝ #ድንግል_እመቤታችን ወደ እርሷ መጥታ 'ሰላም'
ባለቻት ጊዜ ምንም ያሳደገቻት ልጇ ማለት ብትሆን:
መንፈስ ቅዱስ ስለ ሞላባት እመ ብርሃንን
አመስግናታለች:: ቡርክት: ብጽእት: ከፍጥረተ ዓለሙ
የከበረች መሆኗንም መስክራለች:: በማሕጸኗ ያለ የ6 ወር ጽንስም የእመ አምላክን ድምጽ ቢሰማ በደስታ ዘሏል:: ለፈጣሪውም ስግደተ-ስባሔ
አቅርቧል:: ቅድስት ኤልሳቤጥ አክላም "ወምንትኑ አነ
ከመ ትምጽኢ ኀቤየ እሙ ለእግዚእየ-የጌታየ እናቱ ወደ
እኔ ትመጪ ዘንድ እንዴት ይገባኛል?" ስትል በትኅትና
ተናግራለች:: ከጌታ እናት ጋር ለ3 ወራት በአንድ ቤት ቆይታለች::
✝ ቅዱስ ዮሐንስ ከተወለደ 2 ዓመት ከ6 ወር በሆነው
ጊዜ ሰብአ ሰገል በመምጣታቸው በእሥራኤል ምድር
የሚገኙ ሕጻናትን ሔሮድስ ቁዝ አስፈጀ:: ትንሽ ቆይቶም
አይሁድ ለሔሮድስ ስለ ቅዱሱ ሕጻን ነገሩት:: "ሲጸነስ
የአባቱን አንደበት የዘጋ: ሲወለድ ደግሞ የከፈተ
'ዮሐንስ' የሚባል ሕጻን አለና እሱንም ግደል" አሉ::
✝እናቱ ቅድስት ኤልሳቤጥ ይዛው ስትሸሽ ካህኑን
ዘካርያስን ግን በቤተ መቅደስ መካከል ገድለውታል::
አረጋይት ኤልሳቤጥም ሕጻኑን እያሳደገች በገዳመ ዚፋታ
ለ3 (5) ዓመታት ቆይታለች:: ቅዱስ ዮሐንስ 5 (7)
ዓመት ሲሞላው ግን እዚያው በበርሃ እናቱ ዐረፈች:: ከሰማይ
ዘካርያስና ስምዖን ወርደው
ቀበሯት:: #ኤልሳቤጥ ማለት 'እግዚአብሔር መሐላየ
ነው': አንድም 'የጌታ አገልጋይ' ማለት ነው::
በወንጌላዊው የተመሰገነች እናታችን ቅድስት
ኤልሳቤጥ ትውልዷ ከነገደ #ሌዊ ነው:: ሐረገ ሙላዷም
ከቅዱስ #አሮን_ካህን ወገን ይመዘዛል:: ከአሮን በቴክታና
በጥሪቃ ወርዶ #ሔርሜላ ላይ ይደርሳል::
✝ይህቺ ሔርሜላ የምትባል ደግ ሴት #ማጣት ("ጣ"
ጠብቆ ይነበብ) የሚባል የተባረከ ሰው አግብታ 3
ቡሩካት ልጆችን ወለደች:: የመጀመሪያዋን 'ማርያም'
አሏት:: እርሷ ቅድስት ሰሎሜን ወለደች:: ሁለተኛዋን
'ሶፍያ' አሏት:: እርሷ ደግሞ ቅድስት ኤልሳቤጥን
ወለደች::
✝ሦስተኛዋ ግን የተለየች ናት:: 'ሐና' ብለው ሰየሟት::
እርሷም የሰማይና የምድር ንግሥት የሆነችውን ድንግል
ማርያምን ወለደች:: በዚህም መሠረት ድንግል ማርያም:
ቅድስት ኤልሳቤጥና ቅድስት ሰሎሜ የእህትማማች
ልጆች ናቸው::
✝ቅድስት ኤልሳቤጥ እድሜዋ በደረሰ ጊዜ ስም አጠራሩ
የከበረ: ደግ ካህን ለሆነ: ቅዱስ #ዘካርያስ አጋቧት::
እርሷ የሊቀ ካህናቱ ሚስት ናትና ክብሯ ከፍ ያለ ነበር::
ምንም ልጅ ባይኖራትም ዘወትር በጸሎትና በጾም:
ምጽዋትንም በማዘውተር: ነዳያንንም በማሰብ የምትኖር
እናትም ነበረች::
ቅዱስ ወንጌል ላይ ከእመቤታችን ቀጥሎ የነዘካርያስን
ቤተሰብ ያህል ክብሩ የተገለጠለት ፍጡር ይኖራል ብሎ
መናገሩ ይከብዳል:: ቅዱስ ሉቃስ ወንጌሉን የጀመረው
በዚህ ቅዱስ ቤተሰብ ነውና መንፈስ ቅዱስ እንዲህ ሲል
አጽፎታል::
"ዘካርያስ ካህኑና ቅድስት ኤልሳቤጥ በሰውና
በእግዚአብሔር ፊት ያለ ነቀፋ የሚኖሩ ጻድቃን ነበሩ"
ይላቸዋል:: (ሉቃ. 1:6)
✝የሰውን እንተወውና በእግዚአብሔር ፊት ያለ ነቀፋ
መኖር ምን ይረቅ?
ለዚህ አንክሮ (አድናቆት) ይገባል! እሊህ ቅዱሳን ባልና
ሚስት ግን መካኖች በመሆናቸው ልጅ ሳይወልዱ
ዘመናቸው አልፎ ነበር:: እንደ ቤተ ክርስቲያን ትውፊት
ዕድሜአቸው የኤልሳቤጥ 90 የዘካርያስ 100 ደግሞ
ደርሶ ነበር::
✝ፍጹም መታገሳቸውን የተመለከተ ጌታ ግን በስተ
እርጅናቸው ከሰው ሁሉ በላይ የሆነ ታላቅ ነቢይን
ይሰጣቸው ዘንድ መልአከ ብሥራት ቅዱስ ገብርኤልን
ላከላቸው:: ቅድስቲቷ መስከረም 26 ቀን ታላቁን ሰው
ጸንሳ ለ6 ወራት ራሷን ሠወረች::
✝ #ድንግል_እመቤታችን ወደ እርሷ መጥታ 'ሰላም'
ባለቻት ጊዜ ምንም ያሳደገቻት ልጇ ማለት ብትሆን:
መንፈስ ቅዱስ ስለ ሞላባት እመ ብርሃንን
አመስግናታለች:: ቡርክት: ብጽእት: ከፍጥረተ ዓለሙ
የከበረች መሆኗንም መስክራለች:: በማሕጸኗ ያለ የ6 ወር ጽንስም የእመ አምላክን ድምጽ ቢሰማ በደስታ ዘሏል:: ለፈጣሪውም ስግደተ-ስባሔ
አቅርቧል:: ቅድስት ኤልሳቤጥ አክላም "ወምንትኑ አነ
ከመ ትምጽኢ ኀቤየ እሙ ለእግዚእየ-የጌታየ እናቱ ወደ
እኔ ትመጪ ዘንድ እንዴት ይገባኛል?" ስትል በትኅትና
ተናግራለች:: ከጌታ እናት ጋር ለ3 ወራት በአንድ ቤት ቆይታለች::
✝ ቅዱስ ዮሐንስ ከተወለደ 2 ዓመት ከ6 ወር በሆነው
ጊዜ ሰብአ ሰገል በመምጣታቸው በእሥራኤል ምድር
የሚገኙ ሕጻናትን ሔሮድስ ቁዝ አስፈጀ:: ትንሽ ቆይቶም
አይሁድ ለሔሮድስ ስለ ቅዱሱ ሕጻን ነገሩት:: "ሲጸነስ
የአባቱን አንደበት የዘጋ: ሲወለድ ደግሞ የከፈተ
'ዮሐንስ' የሚባል ሕጻን አለና እሱንም ግደል" አሉ::
✝እናቱ ቅድስት ኤልሳቤጥ ይዛው ስትሸሽ ካህኑን
ዘካርያስን ግን በቤተ መቅደስ መካከል ገድለውታል::
አረጋይት ኤልሳቤጥም ሕጻኑን እያሳደገች በገዳመ ዚፋታ
ለ3 (5) ዓመታት ቆይታለች:: ቅዱስ ዮሐንስ 5 (7)
ዓመት ሲሞላው ግን እዚያው በበርሃ እናቱ ዐረፈች:: ከሰማይ
ዘካርያስና ስምዖን ወርደው
ቀበሯት:: #ኤልሳቤጥ ማለት 'እግዚአብሔር መሐላየ
ነው': አንድም 'የጌታ አገልጋይ' ማለት ነው::