እነማንን ይዘንላችሁ እንደምንቅርብ ለማወቅ ገጾቻችንን በቴሌግራም፣ ፌስቡክ እና ኢንስታግራም ተከታተሉን።
https://www.facebook.com/gitemsitem
https://www.instagram.com/gitem_sitem
https://tttttt.me/seifetemam
ዝግጅቱን ልዩ ጥሪ የተደረገላቸው እና ቀድመው ቦታ ያስያዙ ሰዎች ብቻ በአካል ይታደሙታል። በዙም እና ፌስቡክ ደግሞ ያላችሁበት ድረስ እንመጣለን።
በገለጥነው የኛው ቀለም
ጥዑም ግጥም እናጣጥም
#ግጥምሲጥም #ግጥማዊቅዳሜ #ጥዑምግጥም
https://goo.gl/maps/EiCpLt2RCoYHLXoK7
https://www.facebook.com/gitemsitem
https://www.instagram.com/gitem_sitem
https://tttttt.me/seifetemam
ዝግጅቱን ልዩ ጥሪ የተደረገላቸው እና ቀድመው ቦታ ያስያዙ ሰዎች ብቻ በአካል ይታደሙታል። በዙም እና ፌስቡክ ደግሞ ያላችሁበት ድረስ እንመጣለን።
በገለጥነው የኛው ቀለም
ጥዑም ግጥም እናጣጥም
#ግጥምሲጥም #ግጥማዊቅዳሜ #ጥዑምግጥም
https://goo.gl/maps/EiCpLt2RCoYHLXoK7
Gitem Sitem presents you the marvelous Migbar Siraj and his works along with other outstanding poets.
Poetry, Music, Campfire, Foods and Drinks and so much more.
Please RSVP by sending your full name to gitemsitem@gmail.com or @seifdman on telegram.
ግጥም ሲጥም ልዩ ባለቅኔ የሆነውን ምግባር ሲራጅን ከሌሎች እጹብ ገጣሚያን ጋር ይዛላችሁ መጥታለች!
ስነ-ግጥም፣ ሙዚቃ፣ የእሳት ዳር ጨዋታዎች፣ ምግብና መጠጥ እንዲሁም ሌሎች መዝናኛዎች አሉን።
ዝግጅቱን ልዩ ጥሪ የተደረገላቸው እና ቀድመው ቦታ ያስያዙ ሰዎች ብቻ በአካል ይታደሙታል። (መግቢያ አናስከፍልም) ቦታ ለማስያዝ በኢሜይል ወደ gitemsitem@gmail.com ወይም በተሌግራም @seifdman ላይ ሙሉ ስማችሁን እና ስልካችሁን/ የቴሌግራም አድራሻችሁን ላኩልን።
https://goo.gl/maps/EiCpLt2RCoYHLXoK7
በገለጥነው የኛው ቀለም
ጥዑም ግጥም እናጣጥም
#ግጥምሲጥም #ግጥማዊቅዳሜ #ጥዑምግጥም #ምግባርሲራጅ
https://goo.gl/maps/EiCpLt2RCoYHLXoK7
Poetry, Music, Campfire, Foods and Drinks and so much more.
Please RSVP by sending your full name to gitemsitem@gmail.com or @seifdman on telegram.
ግጥም ሲጥም ልዩ ባለቅኔ የሆነውን ምግባር ሲራጅን ከሌሎች እጹብ ገጣሚያን ጋር ይዛላችሁ መጥታለች!
ስነ-ግጥም፣ ሙዚቃ፣ የእሳት ዳር ጨዋታዎች፣ ምግብና መጠጥ እንዲሁም ሌሎች መዝናኛዎች አሉን።
ዝግጅቱን ልዩ ጥሪ የተደረገላቸው እና ቀድመው ቦታ ያስያዙ ሰዎች ብቻ በአካል ይታደሙታል። (መግቢያ አናስከፍልም) ቦታ ለማስያዝ በኢሜይል ወደ gitemsitem@gmail.com ወይም በተሌግራም @seifdman ላይ ሙሉ ስማችሁን እና ስልካችሁን/ የቴሌግራም አድራሻችሁን ላኩልን።
https://goo.gl/maps/EiCpLt2RCoYHLXoK7
በገለጥነው የኛው ቀለም
ጥዑም ግጥም እናጣጥም
#ግጥምሲጥም #ግጥማዊቅዳሜ #ጥዑምግጥም #ምግባርሲራጅ
https://goo.gl/maps/EiCpLt2RCoYHLXoK7
[♣️እብን ይወክላል ልብን?♣️]
የመውደድ ገላ መዓዛ
ከአሪቲ ዛላ መዝዛ
ሸተተኝ የማፍቀር ለዛ።
ከአልባጥሮስ፣ ከእጣን፤ ከርቤ
የሰማሁት፤ ተደልቄ እንደ ድቤ
ተሽቀንጥሬ እንደ ፈትል
መሬት ስሜ ልክ እንደትል
ፍቅር ተማገኝ መልኩ
ታየኝ የተዘነጋ ልኩ፡፡
♣️
ኮከብ ከመሬት ተለቅማ
ሰማይ እንደ ጉንጭ ተስማ
እንደ ቃላብ ለፍቅር ተሞ
ድምጽ አውጥቶ እንዳታሞ
'ገዳም ሳይቀረው ገሞ'።
♣️
ልቡን መውደድ አሸተው
ድካሙ ዓይኑን ሸተተው
[የጠጠሮች “ቋ..ቀጭ” ዜማ
በአፍንጫው ጠረን ጽፎ
የብሌኑን ሞራ ገፎ]
ሄደ፤ ሄደ በረረ
ሽታው ግን ዕጹብ ነበረ፡፡
ለ ምግባር ሲራጅ
#ቶማሰአድማሱ #ምግባርሲራጅ #ግጥምሲጥም #ግጥማዊቅዳሜ #ጥዑምግጥም
የመውደድ ገላ መዓዛ
ከአሪቲ ዛላ መዝዛ
ሸተተኝ የማፍቀር ለዛ።
ከአልባጥሮስ፣ ከእጣን፤ ከርቤ
የሰማሁት፤ ተደልቄ እንደ ድቤ
ተሽቀንጥሬ እንደ ፈትል
መሬት ስሜ ልክ እንደትል
ፍቅር ተማገኝ መልኩ
ታየኝ የተዘነጋ ልኩ፡፡
♣️
ኮከብ ከመሬት ተለቅማ
ሰማይ እንደ ጉንጭ ተስማ
እንደ ቃላብ ለፍቅር ተሞ
ድምጽ አውጥቶ እንዳታሞ
'ገዳም ሳይቀረው ገሞ'።
♣️
ልቡን መውደድ አሸተው
ድካሙ ዓይኑን ሸተተው
[የጠጠሮች “ቋ..ቀጭ” ዜማ
በአፍንጫው ጠረን ጽፎ
የብሌኑን ሞራ ገፎ]
ሄደ፤ ሄደ በረረ
ሽታው ግን ዕጹብ ነበረ፡፡
ለ ምግባር ሲራጅ
#ቶማሰአድማሱ #ምግባርሲራጅ #ግጥምሲጥም #ግጥማዊቅዳሜ #ጥዑምግጥም
ግጥም ሲጥም አዲስ ተሰጥዖ ፍለጋ ባደረገችው ቅኝት ካገኘቻቸው ምርጥ ገጣሚዎች አንዱ የሆነውን ቃለአብ አባይነህን ተዋወቁልንማ።
#ቃለአብአባይነህ #ግጥምሲጥም #ግጥማዊቅዳሜ #ጥዑምግጥም #ምግባርሲራጅ
#ቃለአብአባይነህ #ግጥምሲጥም #ግጥማዊቅዳሜ #ጥዑምግጥም #ምግባርሲራጅ
ፍርፋሪ ታሪክ
- - - — - - -
"ከጅምሩ ማን ፍጠር አለህ እንዲህ ያለ ነገር? ይሄ ነው ፍርድህ? ዛሬስ አትወርድም፣ አትጽፍም ከግንባሩ ላይ ኃጢያቱን የሚያጽፍ ድፍን የቀዮ ጎረምሳ ተሰልፏል..."
"ተው አርዮስ! ተው! ከፈጣሪ አትጋፋ!...አዋቂ ነው...ተው"
"ድንቄም አዋቂ! ሲታወቅ እንዲህ ከሆነ እውቀት በአፍንጫዬ ይውጣ። አይገርምህም!"
"ለአንዲት ጋለሞታ ፈጣሪህን...ትክዳለህን!"
"ጋለሞታ? ጋለሞታ አልህ?...የት አየህ ስትዘሙት?...የት?...አዘሟች ከሌለ ዘማዊት ትፈጠር ይመስል።እንደወይራ፣እንደቀጋ አትበቅል ዘማዊት..."
"ይወራል።...ድፍን መቂ እሱኑ ነው የሚያወራው"
"እና አመንህ አንተ?"
"ምን አማራጭ ይኖራል? ሰው ተኩኖ።...ሁሉ አምኗል እኔ ማነኝና ሰው ያመነውን አላምን የምለው?"
"አልገባኝም?"
"አይገባህም። አንተ ብቻ ከሰው፣ ከቀየው ተነጥለህ፣ ለዘማዊት ሴት ጥብቅና የሚያስቆምህ ነገር። ብቻህን ከአድባር ትጋጫለህ?...ሴት ጠፋ? ከሸርሙጣ?"
"ዝም በል አንተ!!...ምፅዋ ሸርሙጣ አይደለችም።"
"ነች!"
"አይደለችም! ምፅዋ ሸ...ር...ሙ...ጣ... አይደለችም!! ትሰማኛለህ...አንተ ካላባለግኃት አንዲት ምስኪን ሯጭ ከመሬት ተነስታ ሸርሙጣ አትሆንም።"
"ትጠረጥረኛለህ?"
"አላምንህም"
"አህመድንስ ትጠረጥራለህ? ከእርሳቸው አፍ ነው ቀድሜ የሰማሁት።"
"እሳቸው ቅዱስ ገብርኤል ናቸው? የማልጠረጥራቸው?"
"እና እርሳቸውንም ጠርጥረህ?"
"እንክት! ምፅዋዬ እኮ ናት!"
"በል ወግድልኝ ልሂድበት መንገዴን! እውነትም አሪዎስ!...ያሳደጉህ የእናትህ ጡት ሳይሆን ስምህ እንደሆነ ገና ዛሬ ገባኝ!"
"የምን መንገድ?...የሰው መንገድ አበላሽቶ ...ወዴት?"
"የማን መንገድ ተበላሸ? አንተ ኩሩሩ ወግድልኝ!"
"የምፅዋ። የምስኪኗ...በወሬ ገፍታችሁ የጣላችኋት።...ህልሟ መንገዷ አልነበረም? እ!"
"የምን ህልም አላት ደግሞ ሸርሙጣ? ምን ትሰራበታለች ቢኖራትስ?"
"አንተም አለህ አይደል፤ አይደል እሷ? ሯጭ ነበረች ታውቃለህ።... አቦ ሸማኔ የሚያሳድድ ፍጥነት ነበራት።...የጥንቸል ሳንባ ምታስተፋ ነበረች ይህን አንተም ታውቃለህ....ምን ያረጋል!"
"ጋለሞቶች።"
"አልገለሞተችም።....አንተ ውሻ እንዳልዘነጥልህ በዚህ ከዘራ!"
"ኧረ በህግ...በህግ አምላክ!...ምን ታረግበት ነው እሱ...ኧረ ኡ!...ኡ!...ኧረ በህግ!..."
"ልጄን!...አይኔን!...በማህፀኗ...እንደያዘች...አስኮበለላችኋት...ምፅዋዬን አሸሻችኋት"
"ተው አሪዎስ!...ተው አንተ ከሐዲ!...ባለውለታህን?"
"የት ብዬ ልፈልጋት እሺ አሁን?...ንገረኝ!...እ!..."
"እንካ ቅመስ ይችን ለምፅዋዬ!!...እ!...ይህችን ደግሞ በማህፀኗ ይዛ ለተሰደደችው ልጄ...እንካ!!"
"ኡ!...ኡ!...ኡ!...ኧረ የሰው ያለህ!!!"
"የት ብዬ ነው የምፈልጋት አሁን?...እ!...ምፅዋዬ...የበኩር ልጄን እናት?"
©ምግባር ሲራጅ
ዘንባባ
ከገፅ 132 - 134
#ዘንባባ #ምግባርሲራጅ #ግጥምሲጥም #ግጥማዊቅዳሜ #ጥዑምግጥም
- - - — - - -
"ከጅምሩ ማን ፍጠር አለህ እንዲህ ያለ ነገር? ይሄ ነው ፍርድህ? ዛሬስ አትወርድም፣ አትጽፍም ከግንባሩ ላይ ኃጢያቱን የሚያጽፍ ድፍን የቀዮ ጎረምሳ ተሰልፏል..."
"ተው አርዮስ! ተው! ከፈጣሪ አትጋፋ!...አዋቂ ነው...ተው"
"ድንቄም አዋቂ! ሲታወቅ እንዲህ ከሆነ እውቀት በአፍንጫዬ ይውጣ። አይገርምህም!"
"ለአንዲት ጋለሞታ ፈጣሪህን...ትክዳለህን!"
"ጋለሞታ? ጋለሞታ አልህ?...የት አየህ ስትዘሙት?...የት?...አዘሟች ከሌለ ዘማዊት ትፈጠር ይመስል።እንደወይራ፣እንደቀጋ አትበቅል ዘማዊት..."
"ይወራል።...ድፍን መቂ እሱኑ ነው የሚያወራው"
"እና አመንህ አንተ?"
"ምን አማራጭ ይኖራል? ሰው ተኩኖ።...ሁሉ አምኗል እኔ ማነኝና ሰው ያመነውን አላምን የምለው?"
"አልገባኝም?"
"አይገባህም። አንተ ብቻ ከሰው፣ ከቀየው ተነጥለህ፣ ለዘማዊት ሴት ጥብቅና የሚያስቆምህ ነገር። ብቻህን ከአድባር ትጋጫለህ?...ሴት ጠፋ? ከሸርሙጣ?"
"ዝም በል አንተ!!...ምፅዋ ሸርሙጣ አይደለችም።"
"ነች!"
"አይደለችም! ምፅዋ ሸ...ር...ሙ...ጣ... አይደለችም!! ትሰማኛለህ...አንተ ካላባለግኃት አንዲት ምስኪን ሯጭ ከመሬት ተነስታ ሸርሙጣ አትሆንም።"
"ትጠረጥረኛለህ?"
"አላምንህም"
"አህመድንስ ትጠረጥራለህ? ከእርሳቸው አፍ ነው ቀድሜ የሰማሁት።"
"እሳቸው ቅዱስ ገብርኤል ናቸው? የማልጠረጥራቸው?"
"እና እርሳቸውንም ጠርጥረህ?"
"እንክት! ምፅዋዬ እኮ ናት!"
"በል ወግድልኝ ልሂድበት መንገዴን! እውነትም አሪዎስ!...ያሳደጉህ የእናትህ ጡት ሳይሆን ስምህ እንደሆነ ገና ዛሬ ገባኝ!"
"የምን መንገድ?...የሰው መንገድ አበላሽቶ ...ወዴት?"
"የማን መንገድ ተበላሸ? አንተ ኩሩሩ ወግድልኝ!"
"የምፅዋ። የምስኪኗ...በወሬ ገፍታችሁ የጣላችኋት።...ህልሟ መንገዷ አልነበረም? እ!"
"የምን ህልም አላት ደግሞ ሸርሙጣ? ምን ትሰራበታለች ቢኖራትስ?"
"አንተም አለህ አይደል፤ አይደል እሷ? ሯጭ ነበረች ታውቃለህ።... አቦ ሸማኔ የሚያሳድድ ፍጥነት ነበራት።...የጥንቸል ሳንባ ምታስተፋ ነበረች ይህን አንተም ታውቃለህ....ምን ያረጋል!"
"ጋለሞቶች።"
"አልገለሞተችም።....አንተ ውሻ እንዳልዘነጥልህ በዚህ ከዘራ!"
"ኧረ በህግ...በህግ አምላክ!...ምን ታረግበት ነው እሱ...ኧረ ኡ!...ኡ!...ኧረ በህግ!..."
"ልጄን!...አይኔን!...በማህፀኗ...እንደያዘች...አስኮበለላችኋት...ምፅዋዬን አሸሻችኋት"
"ተው አሪዎስ!...ተው አንተ ከሐዲ!...ባለውለታህን?"
"የት ብዬ ልፈልጋት እሺ አሁን?...ንገረኝ!...እ!..."
"እንካ ቅመስ ይችን ለምፅዋዬ!!...እ!...ይህችን ደግሞ በማህፀኗ ይዛ ለተሰደደችው ልጄ...እንካ!!"
"ኡ!...ኡ!...ኡ!...ኧረ የሰው ያለህ!!!"
"የት ብዬ ነው የምፈልጋት አሁን?...እ!...ምፅዋዬ...የበኩር ልጄን እናት?"
©ምግባር ሲራጅ
ዘንባባ
ከገፅ 132 - 134
#ዘንባባ #ምግባርሲራጅ #ግጥምሲጥም #ግጥማዊቅዳሜ #ጥዑምግጥም
Meet one of the poets we've spotted following our call to artists. This emerging poet is ready to share her perspectives and express her self through poetry.
#AdomiaFekede #gitemsitem #poeticsaturdays #migbarsiraj
#አዶሚያፈቀደ #ግጥምሲጥም #ግጣምዊቅዳሜ #ጥዑምግጥም #ምግባርሲራጅ
#AdomiaFekede #gitemsitem #poeticsaturdays #migbarsiraj
#አዶሚያፈቀደ #ግጥምሲጥም #ግጣምዊቅዳሜ #ጥዑምግጥም #ምግባርሲራጅ
Gitem Sitem presents you the marvelous Migbar Siraj and his works along with other outstanding poets.
Poetry, Music, Campfire, Foods and Drinks and so much more.
ግጥም ሲጥም የዘንባባ መጽሐፍ ደራሲ ምግባር ሲራጅን ከሌሎች እጹብ ገጣሚያን ጋር ይዛላችሁ መጥታለች!
ስነ-ግጥም፣ ሙዚቃ፣ የእሳት ዳር ጨዋታዎች፣ ምግብና መጠጥ እንዲሁም ሌሎች መዝናኛዎች አሉን።
https://tttttt.me/seifetemam
በገለጥነው የኛው ቀለም
ጥዑም ግጥም እናጣጥም
#ግጥምሲጥም #ግጥማዊቅዳሜ #ጥዑምግጥም #ምግባርሲራጅ
Poetry, Music, Campfire, Foods and Drinks and so much more.
ግጥም ሲጥም የዘንባባ መጽሐፍ ደራሲ ምግባር ሲራጅን ከሌሎች እጹብ ገጣሚያን ጋር ይዛላችሁ መጥታለች!
ስነ-ግጥም፣ ሙዚቃ፣ የእሳት ዳር ጨዋታዎች፣ ምግብና መጠጥ እንዲሁም ሌሎች መዝናኛዎች አሉን።
https://tttttt.me/seifetemam
በገለጥነው የኛው ቀለም
ጥዑም ግጥም እናጣጥም
#ግጥምሲጥም #ግጥማዊቅዳሜ #ጥዑምግጥም #ምግባርሲራጅ
Meet the poet who is also a Yoga Instructor and a Vegan Chef. Lela will be with us this Saturday!
የዮጋ አሰሪና የቬጋን ምግብ ባለሞያ የሆነችውን ገጣሚ ተዋወቁልንማ
#ሌላ #ግጥምሲጥም #ግጥማዊቅዳሜ #ጥዑምግጥም
#lela #lelamisikir #gitemsitem #poeticsaturdays
የዮጋ አሰሪና የቬጋን ምግብ ባለሞያ የሆነችውን ገጣሚ ተዋወቁልንማ
#ሌላ #ግጥምሲጥም #ግጥማዊቅዳሜ #ጥዑምግጥም
#lela #lelamisikir #gitemsitem #poeticsaturdays
አለ? ምልክት?
ላለመኖር ማስረገጫ
መኖርን በአንጻር ማስጌጫ?
ይገኛል ትርጉም?
ነፋስ ከሚወዘውዘው
ዐይኔ ከሚያየው ጀርባ
የለም እያልኩሽ ስላለው?
በማለም ሽንቁር ሾልኬ
ግልገል ሞቴን ተመርኩዤ
ከሐሳብ ቁልል መሐል
አለመኖርን መዝዤ
ስመላለስበት ባነጋ
(ሳውቅ)
ማመኔን ሳይደገፍ
መካድ ብቻውን እንዳይረጋ..
ጎሕ ቀደደ
እውኔ ብርሃን ሲያርፍበት
ሕልሜ ጥላ አረቀቀ
የካድሁትን ሆኜ ተነሳሁ
ያመንሁት ከእጄ ወደቀ
(እንዲህ እናምናለን
ስለማሰብ ሐሳብ ሆነን
ስለመፍጠር ተፈጥረን
ሕልሞቻችን እንዲያልሙ
መገፋት ደግፏቸው
ተቃርኖዎች እንደቆሙ...
እንዲህ እናምናለን
ስናምን እንክዳለን..
በማየት በማወቅ ብርታት ስልሽ
ከዚህ መለስ ህይወት የለም
የቱ ህይወት? ከየት ወዲያ?
ብለሽ ብትጠይቂ
መጥራት ህይወት አልፈጠረም?
በተቃርኖ እርቅ ጠራን
እንዲህ ክደን ማመን ዘራን!)
ግልገል ሞቴን ተንተርሼ
ነፍስ ስለመዝራት አስባለሁ
(ነጋ! ነቃሁ ብዬሽ ነበረ?)
ይሄን እየነገርኩሽ መምሸቱን ረስቻለሁ
(ስለማወቅ ስንታመም
መርሳት ደስታ አልሆነም?)
(ቃል ብርሃን ሆኖ ሕዋው ልብ ላይ ፈስሶኣል። እታች፥ ምድር እንደሕያው ዐይኖቼን በብልጭታው ተክዬ
እንዲህ ነን አይደለ?
ወደ'የሉም' ስንጠራ
ሰማይ ዜማ ልንሰራ
ግጥም ሆነን ልናበራ?
ባይ'ረዱን
የማይታይ ይቅር
የምንታይን ካዱን)
ጎሕ ቀደደ ዳግመኛ
በሄድሁበት ዞሬ መጣሁ
መኖሬ ላይ ሕይወት አጣሁ
አየሽ?
መንገድ መድረስን ሲረታው?
(ሕልሜና ዕውኔ መሐል የነበረች ስስ መጋረጃ ተገፈፈች። ነፋሱ የገፋት ቅጠል ተንሳፋ ፊቴ ላይ አረፈች... ሕይወት መገለጥ ሆነ!
ምን ነበረ የለም ያልኩሽ...?
እንዲህ እናምናለን
በማመን እንክዳለን!
በማየት በማወቅ ብርታት ስልሽ
ከዚህ መለስ ህይወት የለም
የቱ ህይወት? ከየት ወዲያ?
ብለሽ ብትጠይቂ
መጥራት ህይወት አልፈጠረም?
በተቃርኖ እርቅ ጠራን
እንዲህ ክደን ነፍስ ዘራን!)
በጀርባዬ ተንበልብዬ
ዐይኖቼን ሕዋው ልብ ላይ ተክዬ
እንደሌለሁ
እንደሌለሽ ይሄንን እውነት ስረሳ
(ብልጭ ያልነው እኛ አይደለን?)
ግጥሞች ሆነን ስንነሳ?
(እንረሳለን
እንጂ..
ካየነው ጀርባ አለን!)
ለ Migbar Siraj
#ማርቆስ_ዘመንበረ_ልዑል #ምግባርሲራጅ #ግጥምሲጥም #ግጥማዊቅዳሜ #ጥዑምግጥም
ላለመኖር ማስረገጫ
መኖርን በአንጻር ማስጌጫ?
ይገኛል ትርጉም?
ነፋስ ከሚወዘውዘው
ዐይኔ ከሚያየው ጀርባ
የለም እያልኩሽ ስላለው?
በማለም ሽንቁር ሾልኬ
ግልገል ሞቴን ተመርኩዤ
ከሐሳብ ቁልል መሐል
አለመኖርን መዝዤ
ስመላለስበት ባነጋ
(ሳውቅ)
ማመኔን ሳይደገፍ
መካድ ብቻውን እንዳይረጋ..
ጎሕ ቀደደ
እውኔ ብርሃን ሲያርፍበት
ሕልሜ ጥላ አረቀቀ
የካድሁትን ሆኜ ተነሳሁ
ያመንሁት ከእጄ ወደቀ
(እንዲህ እናምናለን
ስለማሰብ ሐሳብ ሆነን
ስለመፍጠር ተፈጥረን
ሕልሞቻችን እንዲያልሙ
መገፋት ደግፏቸው
ተቃርኖዎች እንደቆሙ...
እንዲህ እናምናለን
ስናምን እንክዳለን..
በማየት በማወቅ ብርታት ስልሽ
ከዚህ መለስ ህይወት የለም
የቱ ህይወት? ከየት ወዲያ?
ብለሽ ብትጠይቂ
መጥራት ህይወት አልፈጠረም?
በተቃርኖ እርቅ ጠራን
እንዲህ ክደን ማመን ዘራን!)
ግልገል ሞቴን ተንተርሼ
ነፍስ ስለመዝራት አስባለሁ
(ነጋ! ነቃሁ ብዬሽ ነበረ?)
ይሄን እየነገርኩሽ መምሸቱን ረስቻለሁ
(ስለማወቅ ስንታመም
መርሳት ደስታ አልሆነም?)
(ቃል ብርሃን ሆኖ ሕዋው ልብ ላይ ፈስሶኣል። እታች፥ ምድር እንደሕያው ዐይኖቼን በብልጭታው ተክዬ
እንዲህ ነን አይደለ?
ወደ'የሉም' ስንጠራ
ሰማይ ዜማ ልንሰራ
ግጥም ሆነን ልናበራ?
ባይ'ረዱን
የማይታይ ይቅር
የምንታይን ካዱን)
ጎሕ ቀደደ ዳግመኛ
በሄድሁበት ዞሬ መጣሁ
መኖሬ ላይ ሕይወት አጣሁ
አየሽ?
መንገድ መድረስን ሲረታው?
(ሕልሜና ዕውኔ መሐል የነበረች ስስ መጋረጃ ተገፈፈች። ነፋሱ የገፋት ቅጠል ተንሳፋ ፊቴ ላይ አረፈች... ሕይወት መገለጥ ሆነ!
ምን ነበረ የለም ያልኩሽ...?
እንዲህ እናምናለን
በማመን እንክዳለን!
በማየት በማወቅ ብርታት ስልሽ
ከዚህ መለስ ህይወት የለም
የቱ ህይወት? ከየት ወዲያ?
ብለሽ ብትጠይቂ
መጥራት ህይወት አልፈጠረም?
በተቃርኖ እርቅ ጠራን
እንዲህ ክደን ነፍስ ዘራን!)
በጀርባዬ ተንበልብዬ
ዐይኖቼን ሕዋው ልብ ላይ ተክዬ
እንደሌለሁ
እንደሌለሽ ይሄንን እውነት ስረሳ
(ብልጭ ያልነው እኛ አይደለን?)
ግጥሞች ሆነን ስንነሳ?
(እንረሳለን
እንጂ..
ካየነው ጀርባ አለን!)
ለ Migbar Siraj
#ማርቆስ_ዘመንበረ_ልዑል #ምግባርሲራጅ #ግጥምሲጥም #ግጥማዊቅዳሜ #ጥዑምግጥም
Meet our musician who possesses various creative sides.
Checkout her works here 👉🏾https://www.youtube.com/watch?v=gznrO3wHb4o&list=RDgznrO3wHb4o&start_radio=1&t=0
#rekik_asegidew #ረቂቅ_አሰግደው #ግጥምሲጥም #ግጥማዊቅዳሜ #ጥዑምግጥም #ምግባርሲራጅ
Checkout her works here 👉🏾https://www.youtube.com/watch?v=gznrO3wHb4o&list=RDgznrO3wHb4o&start_radio=1&t=0
#rekik_asegidew #ረቂቅ_አሰግደው #ግጥምሲጥም #ግጥማዊቅዳሜ #ጥዑምግጥም #ምግባርሲራጅ
ታዳሚዎቹም አቅራቢዎቹም ወደነዋል፣ ጥሞናል፣ ድገሙንም ብለዋል!
የታደማችሁም ያቀረባችሁም ተመስገኑልን! መምጣት ሳትችሉ ብትቀሩም ድጋፋችሁንና ሀሳባችሁን የቸራችሁንም ክበሩ!
ቦታውን ሳታገኙት ቀርታችሁ መምጣት ያልቻላችሁ ደሞ ይቅር በሉን!
ቀጣዩ እንዳያመልጣችሁ ለታህሳስ 10 ቀጠሮ ያዙ ገጾቻችንንም ተከታተሉ
https://tttttt.me/seifetemam
#ኤልያስ_ሽታሁን #ምግባር_ሲራጅ #አንዱ_ጌታቸው #ሌላ_ምስክር #ረቂቅ_አሰገደው
#ግጥምሲጥም #ግጥማዊቅዳሜ #ጥዑምግጥም
ህዳር 12 ከተካሄደው የመጀመሪያው የግጥም ሲጥም ዝግጅት ላይ የተወሰዱ ምስሎች
📷 @AnimaHela
የታደማችሁም ያቀረባችሁም ተመስገኑልን! መምጣት ሳትችሉ ብትቀሩም ድጋፋችሁንና ሀሳባችሁን የቸራችሁንም ክበሩ!
ቦታውን ሳታገኙት ቀርታችሁ መምጣት ያልቻላችሁ ደሞ ይቅር በሉን!
ቀጣዩ እንዳያመልጣችሁ ለታህሳስ 10 ቀጠሮ ያዙ ገጾቻችንንም ተከታተሉ
https://tttttt.me/seifetemam
#ኤልያስ_ሽታሁን #ምግባር_ሲራጅ #አንዱ_ጌታቸው #ሌላ_ምስክር #ረቂቅ_አሰገደው
#ግጥምሲጥም #ግጥማዊቅዳሜ #ጥዑምግጥም
ህዳር 12 ከተካሄደው የመጀመሪያው የግጥም ሲጥም ዝግጅት ላይ የተወሰዱ ምስሎች
📷 @AnimaHela
ግጥም ሲጥም በመጫን ላይ ነች . . . 20 %
ቅዳሜ፣ ታኅሣሥ 10፣ 2013
Gitem Sitem - ግጥም ሲጥም loading . . . 20%
December 19, 2020
Poetic Saturdays finalizing installation . . . 90% completed
#ጥዑምግጥም #ግጥምሲጥም #ሲጥም #ግጥማዊቅዳሜ #gitemsitem #poeticsaturdays #poetry #artinaddis #poetryinaddis
ቅዳሜ፣ ታኅሣሥ 10፣ 2013
Gitem Sitem - ግጥም ሲጥም loading . . . 20%
December 19, 2020
Poetic Saturdays finalizing installation . . . 90% completed
#ጥዑምግጥም #ግጥምሲጥም #ሲጥም #ግጥማዊቅዳሜ #gitemsitem #poeticsaturdays #poetry #artinaddis #poetryinaddis
እንሆ የህዳር ወር የግጥም መጽሔ
በቀጣይ መጽሔታችን አሁንም የእናንተኑ ስራ እንጠብቃለን።
በ shorturl.at/duyO9 ገብታችሁ እዩልን፣ አውርዳችሁም የራሳችሁ ልታደርጉት ትችላላችሁ - ለሌሎችም አጋሩልን። አይታችሁ ስታበቁ አስተያየት አቀብሉን።
ግጥማቸውንና ምስሎቻቸውን እያቀበሉ ወሩን ላደመቁልን ሁሉ ምስጋና ይድረስ!!!
#ግጥምሲጥም #ግጥማዊቅዳሜ #የግጥምመጽሔት #ጥዑምግጥም #ምግባርሲራጅ
#gietmsitem #poeticsaturdays #artinaddis #poetrybooklet
Cover Photo Credit: Hermela
በቀጣይ መጽሔታችን አሁንም የእናንተኑ ስራ እንጠብቃለን።
በ shorturl.at/duyO9 ገብታችሁ እዩልን፣ አውርዳችሁም የራሳችሁ ልታደርጉት ትችላላችሁ - ለሌሎችም አጋሩልን። አይታችሁ ስታበቁ አስተያየት አቀብሉን።
ግጥማቸውንና ምስሎቻቸውን እያቀበሉ ወሩን ላደመቁልን ሁሉ ምስጋና ይድረስ!!!
#ግጥምሲጥም #ግጥማዊቅዳሜ #የግጥምመጽሔት #ጥዑምግጥም #ምግባርሲራጅ
#gietmsitem #poeticsaturdays #artinaddis #poetrybooklet
Cover Photo Credit: Hermela