YeneTube
119K subscribers
31.4K photos
484 videos
79 files
3.86K links
መረጃዎችን ለመላክ @Fikerassefa
Download Telegram
⬆️⬆️የኢትዮጵያ አየር መንገድ ስካይ ላይት ሆቴል ተመረቀ።

የኢትዮጵያ አየር መንገድ ያስገነባው ስካይ ላይት ሆቴል ዛሬ ጠቅላይ ሚንስትር ዶ/ር ዐቢይ አህመድ በተገኙበት በይፋ ተመርቆ ተከፍቷል፡፡
የአዲስ አበባ ቦሌ ዓለም አቀፍ አየር ማረፊያ የመንገደኞች ማስተናገጃ ተርሚናል ማስፋፊያ ፕሮጀክትም ዛሬ ይመረቃል፡፡

ምንጭ፡ ኢቢሲ
#መረጃውን_ካነበቡ_ብሀላ #ሼር_ያድርጉ
@Yenetube @Fikerassefa
የቀድሞ የሀገር መከላከያ ሰራዊት አባላት ዛሬ በደብረ ማርቆስ ከተማ የፖሊስ ኮሌጅ የመጀመሪያውን የምስረታ ጉባኤ እያካሄዱ ነው፡፡

ከ3ሺህ በላይ አባላትም እንደሚገኙ ይጠበቃል፡፡
ምንጭ:- አብመድ
#መረጃውን_ካነበቡ_ብሀላ #ሼር_ያድርጉ
@YeneTube @Fikerassefa
By this time tutorial of kids is going Mekele University MIT Campus, Auditorium Hall.

መቐለ ዩንቨርስቲ አጋዥ ትምህርት በMIT ካምፓስ ኦዲቶሪየም አዳራሽ እየተሰጠ ይገኛል።

ምንጭ:- መቐለ ዩንቨርስቲ ተማሪዎች ዲን
#መረጃውን_ካነበቡ_ብሀላ #ሼር_ያድርጉ
@YeneTube @Fikerassefa
ድሬደዋን በተመለከተ ከንቲባው ለሪፓርተር የተናገሩት ‼️

ጥር 13 ቀን 2011 ዓ.ም. የጥምቀት በዓል ማግሥት በድሬዳዋ ከተማ የተፈጠረው አለመረጋጋትና ግጭት ሃይማኖታዊ ሳይሆን የፖለቲካ አጀንዳ ባላቸው ኃይሎች አማካይነት የተቀነባበረ፣ ድሬዳዋን የብጥብጥ ማዕከል ለማድረግ የታቀደና አስቀድሞ የተሠራ መሆኑን፣ የድሬዳዋ ከተማ ከንቲባ አቶ ኢብራሂም ኡስማን ለሪፖርተር አስታወቁ፡፡

በድሬዳዋ ከተማ ችግር መፈጠር የጀመረው ጥር 12 ቀን 2011 ዓ.ም. የሚካኤል ታቦት ካደረበት ሥፍራ ሲመለስ ባልታወቁ ሰዎች ድንጋይ ከተወረወረ በኋላ መሆኑን፣ ከከተማው ነዋሪዎች ለማወቅ ተችሏል፡፡ ይህ ክስተት በነጋታው በድሬዳዋ ከተፈጠረው ችግር ጋር ቀጥታ ግንኙነት የለውም ሲሉ ግን ከንቲባው ያስረዳሉ፡፡

‹‹የችግሩ መነሻ ታቦት ሲገባ የተፈጠረው ክስተት አይደለም፡፡ አስቀድሞ ከአምስት ቀናት በፊት ይህንኑ ፀብ ለማጫርና ድሬዳዋን የብጥብጥ ማዕከል ለማድረግ የተደረገ የዝግጅት ሥራ እንደነበረ ደርሰንበታል፤›› በማለት አብራርተዋል፡፡

ችግሩን የሃይማኖትና የብሔር ግጭት ለማስመሰል መሠራቱን የገለጹት ከንቲባው፣ በዚህም ምክንያት በበርካታ የንግድ ተቋማት ላይ ዘረፋ መፈጸሙን አስታውቀዋል፡፡ ‹‹የተወሰኑ ዘራፊዎች ግርግሩን በመጠቀም ለዘረፋ እንዲያመቻቸው ችግሩን እያባባሱት ይገኛሉ፤›› ሲሉም አብራርተዋል፡፡

አመራር ይቀየርልን የሚል ጥያቄ እየተነሳ መሆኑን በመጥቀስ ሪፖርተር ላቀረበላቸው ጥያቄ፣ ‹‹የሆነ አካል አመራሩ ይውረድ እያለ ነው፡፡ ይህ ደግሞ ሕጋዊ ሒደቱን ጠብቆ አመራሩ መውረድ ካለበት ይወርዳል፣ ለሕግ መቅረብ ካለበትም ይቀርባል፡፡ ነገር ግን በጉልበትና በኃይል ይህን ማድረግ አይቻልም፤›› በማለት ምላሽ ሰጥተዋል፡፡

ከብጥብጡ ጀርባ ያሉ ኃይሎች ማን እንደሆኑ በተመለከተ ደግሞ ሁለት አካላት መለየታቸውን ገልጸዋል፡፡ ‹‹የመጀመርያው የፖለቲካ ዓላማ ኖሮት ከዚህ ቀደም የነበረው አስተዳደር አግላይ ነው የሚል አስተሳሰብ ይዞ ለረዥም ጊዜ ሲሠራ የነበረና ውጭ አገር ድረስ ትስስር የነበሩት የመሩት እንደሆነ ዓይተናል፡፡ ከዚህ በተጨማሪም በቅርቡ ወደ አገር ውስጥ የገቡ የፖለቲካ ድርጅቶችም ይኖሩበታል ብለን እናምናለን፤›› ብለዋል፡፡

‹‹አሁን በክልሉ ከተፈጠረው ችግር ጀርባ ያለው ሁለተኛ ኃይል ደግሞ ከሶማሌ ክልል የቀድሞ አመራሮች ጋር ቀጥተኛ ትስስር ያላቸው አካላት፣ ፀብ የማጫር ድርጊት ላይ ሊሳተፉ እንደሚችሉ ገምግመናል፤›› በማለት አሁን ከተፈጠረው ብጥብጥ ጀርባ አሉ ያሉዋቸውን አካላት ገልጸዋል፡፡

በድሬዳዋ ከተማ ላለፉት ቀናት በተከሰተው አለመረጋጋት የአንድ ሕፃን ልጅ ሕይወት በተባራሪ ጥይት ማለፉን፣ 15 ሰዎች ደግሞ ቀላል የሚባል ጉዳት ደርሶባቸው ሕክምና አግኝተው ወደ ቤታቸው መመለሳቸውን ከንቲባው ገልጸዋል፡፡

ከንብረት ጋር በተያያዘ ግን ከፍተኛ የሆነ ዘረፋ መፈጸሙን አስታውቀዋል፡፡ ዓርብ ጥር 17 ቀን 2011 ዓ.ም. የተወሰኑ ባንኮችንና የገበያ ማዕከላትን የመክበብ አዝማሚያ እንደነበርም አክለው ገልጸዋል፡፡ በተጨማሪም ሱቆችና የግለሰብ መኖርያ ቤቶችም የዝርፊያ ሰለባ መሆናቸውን ከንቲባው አስታውቀዋል፡፡

ሐሙስ ጥር 16 ቀን 2010 ዓ.ም. የመከላከያ ሠራዊት ድሬዳዋ ቢገባም፣ በከተማዋ ውስጥ የሚገኙ የተለያዩ መንገዶች ተዘግተው ነበር፡፡ በተፈጠረው ሁከት ምክንያት የተጠረጠሩ 84 ሰዎች በቁጥጥር ሥር መዋላቸውን ፖሊስ አስታውቋል፡፡ ችግሩን ለመፍታት የሃይማኖት አባቶችና የአገር ሽማግሌዎች ጥረት እያረጉ መሆኑን ለማወቅ ተችሏል፡፡

ምንጭ:-ሪፓርተር
#መረጃውን_ካነበቡ_ብሀላ #ሼር_ያድርጉ
@YeneTube @Fikerassefa
ደሴ ከተማ ላይ ስለ ሰላም፣አብሮነትና አንድነት እየተመከረ ነው፡፡

የኃይማኖት አባቶች እና የሃገር ሽማግሌዎች ደሴ ከተማ ላይ ስለ ሰላም፣ስለ አብሮነትና ስለ አንድነት እሴቶች እየመከሩ ነው፡፡

የኃይማኖት አባቶችና የሃገር ሽማግሌዎቹ ስለ ሀገር ሰላም አንድነትና አብሮነት መልዕክት አስተላልፈዋል፡፡

ምንጭ:- AMMA
#መረጃውን_ካነበቡ_ብሀላ #ሼር_ያድርጉ
@YeneTube @FikerAssefa
#Update ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ ደመቀ መኮንን በደቡብ ክልል በጋሞ ዞን ቆላማ አካባቢ የስንዴ ግብርና ልማት የሙከራ ፕሮጀክትን ጎብኙ።

በጉዟቸውም በሙከራ ደረጃ 200 ሄክታር የሚሸፍን በመስመር እና በመስኖ የተዘራ የስንዴ ግብርና ልማትን ነው የጎበኙት፡፡

ምንጭ:-Fana
#መረጃውን_ካነበቡ_ብሀላ #ሼር_ያድርጉ
@YeneTube @Fikerassefa
⬆️ዛሬ ኢዲስ አበባ በሚገኘው ፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፓሬሽን ዋና ቢሮ የድሬደዋ ተወላጆች ያላቸው ቅሬታ አስምተዋል።

40:40:20 ይቁም
ፍቅራችንን አትንጠቁን
ስላም ኢትዮጵያ!
ስላም ድሬደዋ!
ድሬደዋ የነዋሪዎቿ ናት!!
ስሉ ተሰምተዋል።

መረጃውን ያደረሱን የኔቲዩብ ቤተሰባች ናቸው።
#መረጃውን_ካነበቡ_ብሀላ #ሼር_ያድርጉ
@YeneTube @Fikerassefa