Forwarded from Hamrin A
🗝️ እጅግ አመቺ በሆነ አከፋፈል የቤት ባለቤት ይሁኑ
60% የባንክ ብድር የተመቻቸላቸውን ቤቶች በልዮ ቅናሽ
❇️ በጉጉት ሲጠበቅ የነበረው DMC Real Estate የመጨረሻው መንደር ወቅቱን ባገናዘበ ቅናሽ ዋጋ በተለያዩ ካሬ አማራጮች አቅርቦሎታል : :
⭐️ከሀያ አምስት ዓመታት በላይ ግንባታ ላይ ከቆየ አንጋፋ ድርጅት
📍አድራሻ - በመሀል ከተማ ለቡ መብራት-ሀይል
💸ቅድመ ክፍያ
💎ባለ 1 መኝታ በ 431 ሺ ብር
💎ባለ 2 መኝታ በ 619 ሺ ብር
💎ባለ 3 መኝታ በ 751 ሺ ብር
💎ባለ 4 መኝታ በ 1,051,626 ብር
🛍️🛒ሱቆች ከ 43 ካሬ ጀምሮ
🏦60% የባንክ ብድር የተመቻቸላቸው (እየኖሩበት ወይም አከራይተውት እስከ 20 አመት ቀስ ብለው የሚከፍሉት)
➡️በ 8% ቅድመ ክፍያ
➡️እስከ 30% በሚደርስ ቅናሽ ዋጋ (ለ20 ቤቶች) በመጠቀም የዘመናዊ መንደራችን አካል ይሁኑ
➡️☎️ 09 31 14 82 42
➡️@Novi_03 (telegram)
➡️Whatsapp Link-
https://wa.me/251931148242
60% የባንክ ብድር የተመቻቸላቸውን ቤቶች በልዮ ቅናሽ
❇️ በጉጉት ሲጠበቅ የነበረው DMC Real Estate የመጨረሻው መንደር ወቅቱን ባገናዘበ ቅናሽ ዋጋ በተለያዩ ካሬ አማራጮች አቅርቦሎታል : :
⭐️ከሀያ አምስት ዓመታት በላይ ግንባታ ላይ ከቆየ አንጋፋ ድርጅት
📍አድራሻ - በመሀል ከተማ ለቡ መብራት-ሀይል
💸ቅድመ ክፍያ
💎ባለ 1 መኝታ በ 431 ሺ ብር
💎ባለ 2 መኝታ በ 619 ሺ ብር
💎ባለ 3 መኝታ በ 751 ሺ ብር
💎ባለ 4 መኝታ በ 1,051,626 ብር
🛍️🛒ሱቆች ከ 43 ካሬ ጀምሮ
🏦60% የባንክ ብድር የተመቻቸላቸው (እየኖሩበት ወይም አከራይተውት እስከ 20 አመት ቀስ ብለው የሚከፍሉት)
➡️በ 8% ቅድመ ክፍያ
➡️እስከ 30% በሚደርስ ቅናሽ ዋጋ (ለ20 ቤቶች) በመጠቀም የዘመናዊ መንደራችን አካል ይሁኑ
➡️☎️ 09 31 14 82 42
➡️@Novi_03 (telegram)
➡️Whatsapp Link-
https://wa.me/251931148242
❤5👍1
ለ7ኛው ሀገራዊ ምርጫ ዕጩዎችና መራጮች በኦንላይን መመዝገብ የሚችሉበት ሶፍትዌር ተዘጋጀ
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በ7ኛው ሀገራዊ ምርጫ ላይ መራጮችና ዕጩዎች ካሉበት ሆነው በኦንላይን መመዝገብ የሚችሉበት ሶፍትዌር ማበልፀጉን አስታወቀ፡፡
የቦርዱ ሰብሳቢ ሜላትወርቅ ኃይሉ፤ ያለፉት ሥድስት የኢትዮጵያ የምርጫ ሂደቶች ማንዋል እንደነበሩ ጠቅሰው፤ በ7ኛው ሀገራዊ ምርጫ መራጮችም ሆኑ ዕጩዎች ካሉበት ሆነው በኦንላይን መመዝገብ የሚችሉበትን ሶፍትዌር ማበልፀግ መቻሉን አስታውቀዋል፡፡
ሰብሳቢዋ ይህን ያሉት፤ በዛሬው ዕለት በቴክኖሎጂው አሥተዳደር ሥርዓት ላይ ቦርዱ ከፖለቲካ ፓርቲዎች ጋር ባደረገው ውይይት ነው።
ወ/ሮ ሜላትወርቅ ሂደቱ ኢትዮጵያ በምርጫ ሥርዓቷ “አንድ እርምጃ ወደፊት መራመድ የሚያስችላት” ከመሆኑ ባለፈ፤ በምርጫው ሂደት ላይ “ግልፅነትና ተጠያቂነትን” ለማስፈን ያስችላል ብለዋል።
የውይይቱ ተሳታፊ የፖለቲካ ፓርቲዎች በበኩላቸው ሶፍትዌሩ ጊዜ ቆጣቢና እንግልት የሚቀንስ መሆኑን ጠቅሰው፤ ለግልፅነትና ለተጠያቂነት ምቹ መደላድል እንደሚፈጥር ተናግረዋል ሲል ኤፍ ኤም ሲ ዘግቧል፡፡
ባሳለፍነው ወር ቦርዱ ለ7ኛው ዙር ሀገራዊ ምርጫ፤ ሁለተኛ ዙር የምርጫ ጣቢያዎችን በዲጂታል ሲስተም የመመዝገብ ሥራ ማከናወኑን ማስታወቁ ይታወሳል።
ቦርዱ ለ7ኛው ዙር ሀገራዊ ምርጫ የተለያዩ የቅድመ ዝግጅት ሥራዎችን በማከናወን ላይ መሆኑን ገልጾ ከዚህ በፊት ከተካሄዱት ምርጫዎች በአፈጻጸም ቀልጣፋና ጊዜው የሚጠይቀውን ዘመናዊነት የተከተለ ለማድረግ እየተሰራ መሆኑን ጠቁሟል።
@Yenetube @Fikerassefa
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በ7ኛው ሀገራዊ ምርጫ ላይ መራጮችና ዕጩዎች ካሉበት ሆነው በኦንላይን መመዝገብ የሚችሉበት ሶፍትዌር ማበልፀጉን አስታወቀ፡፡
የቦርዱ ሰብሳቢ ሜላትወርቅ ኃይሉ፤ ያለፉት ሥድስት የኢትዮጵያ የምርጫ ሂደቶች ማንዋል እንደነበሩ ጠቅሰው፤ በ7ኛው ሀገራዊ ምርጫ መራጮችም ሆኑ ዕጩዎች ካሉበት ሆነው በኦንላይን መመዝገብ የሚችሉበትን ሶፍትዌር ማበልፀግ መቻሉን አስታውቀዋል፡፡
ሰብሳቢዋ ይህን ያሉት፤ በዛሬው ዕለት በቴክኖሎጂው አሥተዳደር ሥርዓት ላይ ቦርዱ ከፖለቲካ ፓርቲዎች ጋር ባደረገው ውይይት ነው።
ወ/ሮ ሜላትወርቅ ሂደቱ ኢትዮጵያ በምርጫ ሥርዓቷ “አንድ እርምጃ ወደፊት መራመድ የሚያስችላት” ከመሆኑ ባለፈ፤ በምርጫው ሂደት ላይ “ግልፅነትና ተጠያቂነትን” ለማስፈን ያስችላል ብለዋል።
የውይይቱ ተሳታፊ የፖለቲካ ፓርቲዎች በበኩላቸው ሶፍትዌሩ ጊዜ ቆጣቢና እንግልት የሚቀንስ መሆኑን ጠቅሰው፤ ለግልፅነትና ለተጠያቂነት ምቹ መደላድል እንደሚፈጥር ተናግረዋል ሲል ኤፍ ኤም ሲ ዘግቧል፡፡
ባሳለፍነው ወር ቦርዱ ለ7ኛው ዙር ሀገራዊ ምርጫ፤ ሁለተኛ ዙር የምርጫ ጣቢያዎችን በዲጂታል ሲስተም የመመዝገብ ሥራ ማከናወኑን ማስታወቁ ይታወሳል።
ቦርዱ ለ7ኛው ዙር ሀገራዊ ምርጫ የተለያዩ የቅድመ ዝግጅት ሥራዎችን በማከናወን ላይ መሆኑን ገልጾ ከዚህ በፊት ከተካሄዱት ምርጫዎች በአፈጻጸም ቀልጣፋና ጊዜው የሚጠይቀውን ዘመናዊነት የተከተለ ለማድረግ እየተሰራ መሆኑን ጠቁሟል።
@Yenetube @Fikerassefa
❤19👎19😁11🔥1
ኦነግ አዲስ አበባ የሚገኘው ዋና ቢሮው ከአራት ዓመታት በኋላ እንደተመለሰለት አስታወቀ!
የኦሮሞ ነፃነት ግንባር (ኦነግ) ከነሃሴ 2012 ዓ.ም ጀምሮ ተዘግቶ የነበረውን እና በአዲስ አበባ የሚገኘውን ዋና ቢሮው በይፋ እንደተመለሰለት የፓርቲው የህዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ ለሚ ገመቹ ለአዲስ ስታንዳርድ ገለጹ።
"በይበልጥ የአዲስአበባ ከተማ የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት የቻለውን ያህል ጫና ሲያደርግ ነበረ" ያሉት አቶ ለሚ የምክር ቤቱ እንዲሁም ሌሎች ተወካዮች በተገኙበት ቢሯችን ለማስመለስ ችለናል ብለዋል።
አክለውም "ወደ ቢሯችን እንድንመለስ የኢትዮጵያ ምርጫ ቦርድ የራሱን አስተዋጽኦ አድርጓል" ሲሉ አስታውቀዋል።አያይዘውም ፓርቲያቸው ከ200 በላይ ጽህፈት ቤቶች እንዳሉት ጠቅሰው በቀጣይ በተዋረድ የተዘጉ ጽሕፈት ቤቶቻችን እንዲከፈቱልን ውትወታችን ይቀጥላል ብለዋል። ወደፊትም አደረጃጀቶቻችንን ለማጠናከር ተስፋ አድርገን እንሰራለን ሲሉ ተናግረዋል።
Via AS
@YeneTube @FikerAssefa
የኦሮሞ ነፃነት ግንባር (ኦነግ) ከነሃሴ 2012 ዓ.ም ጀምሮ ተዘግቶ የነበረውን እና በአዲስ አበባ የሚገኘውን ዋና ቢሮው በይፋ እንደተመለሰለት የፓርቲው የህዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ ለሚ ገመቹ ለአዲስ ስታንዳርድ ገለጹ።
"በይበልጥ የአዲስአበባ ከተማ የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት የቻለውን ያህል ጫና ሲያደርግ ነበረ" ያሉት አቶ ለሚ የምክር ቤቱ እንዲሁም ሌሎች ተወካዮች በተገኙበት ቢሯችን ለማስመለስ ችለናል ብለዋል።
አክለውም "ወደ ቢሯችን እንድንመለስ የኢትዮጵያ ምርጫ ቦርድ የራሱን አስተዋጽኦ አድርጓል" ሲሉ አስታውቀዋል።አያይዘውም ፓርቲያቸው ከ200 በላይ ጽህፈት ቤቶች እንዳሉት ጠቅሰው በቀጣይ በተዋረድ የተዘጉ ጽሕፈት ቤቶቻችን እንዲከፈቱልን ውትወታችን ይቀጥላል ብለዋል። ወደፊትም አደረጃጀቶቻችንን ለማጠናከር ተስፋ አድርገን እንሰራለን ሲሉ ተናግረዋል።
Via AS
@YeneTube @FikerAssefa
❤14👎11😁6
ቲክቶከሯ ጃኒ ተጨማሪ 7 ቀን በእስር ቤት ታሳልፋለች
ቲክቶከሯ ጃኒ ገብሩ በአዲስ አበባ ከተማ ተይዛ ወደ ድሬደዋ ከተወሰደች በኋላ ከዚራ ፖሊስ ጣቢያ ትገኛለች።
ወጣቷ ለእስር ያበቃት በቲክቶክ ቀጥታ ስርጭት ተናግራለች በተባለ ንግግር ሲሆን ዛሬ በድሬዳዋ የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ቀርባ ነበር።
ፖሊስ ከተከሳሿ ስልክ ጋር ያልሰራናቸው ምርመራዎች ስላሉኝ ተጨማሪ ቀናት ይሰጡኝ በማለቱ 7 ቀን በፍርድ ቤት ተፈቅዶለት ለሰኔ 9/2017 ዓም ተለዋጭ ቀጠሮ መስጠቱን ከኢትዮጲካሊንክ ሰምቷል።
ቲክቶከሯ ይፋዊ መጠሪያ ስሟ በሶሻል ሚዲያ እንደሚገለጸው "ስመኝ ገብሩ" ሳይሆን በፍርድ ቤት ወደ "ጃኒ ገብሩ" በመቀየሩ በዛሬው ችሎት በይፋዊ መጠሪያ በማድረግ ጃኒ ገብሩን ማስመዝገቧን ከኢትዮጲካሊንክ ዘገባ ተመልክተናል።
@Yenetube @Fikerassef
ቲክቶከሯ ጃኒ ገብሩ በአዲስ አበባ ከተማ ተይዛ ወደ ድሬደዋ ከተወሰደች በኋላ ከዚራ ፖሊስ ጣቢያ ትገኛለች።
ወጣቷ ለእስር ያበቃት በቲክቶክ ቀጥታ ስርጭት ተናግራለች በተባለ ንግግር ሲሆን ዛሬ በድሬዳዋ የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ቀርባ ነበር።
ፖሊስ ከተከሳሿ ስልክ ጋር ያልሰራናቸው ምርመራዎች ስላሉኝ ተጨማሪ ቀናት ይሰጡኝ በማለቱ 7 ቀን በፍርድ ቤት ተፈቅዶለት ለሰኔ 9/2017 ዓም ተለዋጭ ቀጠሮ መስጠቱን ከኢትዮጲካሊንክ ሰምቷል።
ቲክቶከሯ ይፋዊ መጠሪያ ስሟ በሶሻል ሚዲያ እንደሚገለጸው "ስመኝ ገብሩ" ሳይሆን በፍርድ ቤት ወደ "ጃኒ ገብሩ" በመቀየሩ በዛሬው ችሎት በይፋዊ መጠሪያ በማድረግ ጃኒ ገብሩን ማስመዝገቧን ከኢትዮጲካሊንክ ዘገባ ተመልክተናል።
@Yenetube @Fikerassef
😁52❤24👎6👀5🔥2
ከኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ የተሰጠ ወቅታዊ መረጃ
በትላንትናው ዕለት በአዲስ አበባ ስታዲየም በሲዳማ ቡናና ወላይታ ዲቻ መካከል የኢትዮጵያ ዋንጫ ፍጻሜ የእግር ኳስ ውድድር መካሄዱ ይታወሳል፡፡
ሁለቱን ክለቦች ለመደገፍ ከሀዋሳ፣ ከወላይታ ሶዶ እና ከአካባቢው የመጡ በርካታ ደጋፊዎች መካከል አለመግባባት በመፈጠሩ ጨዋታው በዝግ ስታዲየም እንዲካሄድ ተደርጎ ፖሊስ በደጋፊዎች መካከል ይፈጠር የነበረውን ግጭት በማስቀረት አስፈላጊውን ወቅታዊና ሕጋዊ ተግባር በመፈፀም ሕግና ሥርዓት አስከብሯል፡፡
ነገር ግን የሀገራችን ሰላምና መረጋጋት የሚመራቸው በሀገር ውስጥና በውጭ ሀገራት ያሉ አካላት ተናበው የሰዎች ሕይወት እንዳለፈ አስመስለው በመዘገብ ግጭት ለማባባስ እየሞከሩ እንደሆነ ታዝበናል፡፡
ፖሊስ ግጭቱን ለማባባስ ሲንቀሳቀሱ የነበሩ ውስን ግለሰቦችን በቁጥጥር ሥር አውሎ ምርመራ እያጣራ ሲሆን ውጤቱንም በየጊዜው ለሕዝብ ይፋ ያደርጋል። ከዚህ ውጭ በአንድም ሆነ በሌላው መልኩ የእርስ በርስ ግጭት የሚፈልጉ አካላት ሰው ሞቷል እያሉ የሚያሰራጩት ወሬ ሀሰተኛ መሆኑን እና በአንድም ሰው ላይ የሞትም ይሁን የአካል መጉደል ጉዳት ያልደረሰ መሆኑን አረጋግጧል፡፡
ስፖርት በባህሪው የተጣላን የሚያቀራርብ ሆኖ ሳለ በሁለቱ ደጋፊዎች መካከል የተፈጠረው አለመግባባት ወደ ሌላ እንዳይሰፋ ፖሊስ በወሰደው ህጋዊ እርምጃ ግጭቱን ተቆጣጥሯል፡፡
ይሁን እንጂ በሀሰተኛ ወሬ ሕብረተሰቡን ወደ ግጭት እንዲያመራ እና የሕዝብ አለኝታና ጠባቂ የሆነውን ፖሊስ ስም ለማጉደፍ በሚንቀሳቀሱት ላይ ፖሊስ ጥብቅ ሕጋዊ እርምጃ እንደሚወስድና በቀጣይም ስፖርቱ ለእንዲህ ዓይነት ሥርዓት አልበኝነት ተገዢ እንዳይሆን ፖሊስ ከሚመለከታቸው አጋር አካላት ጋር ተቀራርቦ እንደሚሰራ ያስታውቃል፡፡
@YeneTube @FikerAssefa
በትላንትናው ዕለት በአዲስ አበባ ስታዲየም በሲዳማ ቡናና ወላይታ ዲቻ መካከል የኢትዮጵያ ዋንጫ ፍጻሜ የእግር ኳስ ውድድር መካሄዱ ይታወሳል፡፡
ሁለቱን ክለቦች ለመደገፍ ከሀዋሳ፣ ከወላይታ ሶዶ እና ከአካባቢው የመጡ በርካታ ደጋፊዎች መካከል አለመግባባት በመፈጠሩ ጨዋታው በዝግ ስታዲየም እንዲካሄድ ተደርጎ ፖሊስ በደጋፊዎች መካከል ይፈጠር የነበረውን ግጭት በማስቀረት አስፈላጊውን ወቅታዊና ሕጋዊ ተግባር በመፈፀም ሕግና ሥርዓት አስከብሯል፡፡
ነገር ግን የሀገራችን ሰላምና መረጋጋት የሚመራቸው በሀገር ውስጥና በውጭ ሀገራት ያሉ አካላት ተናበው የሰዎች ሕይወት እንዳለፈ አስመስለው በመዘገብ ግጭት ለማባባስ እየሞከሩ እንደሆነ ታዝበናል፡፡
ፖሊስ ግጭቱን ለማባባስ ሲንቀሳቀሱ የነበሩ ውስን ግለሰቦችን በቁጥጥር ሥር አውሎ ምርመራ እያጣራ ሲሆን ውጤቱንም በየጊዜው ለሕዝብ ይፋ ያደርጋል። ከዚህ ውጭ በአንድም ሆነ በሌላው መልኩ የእርስ በርስ ግጭት የሚፈልጉ አካላት ሰው ሞቷል እያሉ የሚያሰራጩት ወሬ ሀሰተኛ መሆኑን እና በአንድም ሰው ላይ የሞትም ይሁን የአካል መጉደል ጉዳት ያልደረሰ መሆኑን አረጋግጧል፡፡
ስፖርት በባህሪው የተጣላን የሚያቀራርብ ሆኖ ሳለ በሁለቱ ደጋፊዎች መካከል የተፈጠረው አለመግባባት ወደ ሌላ እንዳይሰፋ ፖሊስ በወሰደው ህጋዊ እርምጃ ግጭቱን ተቆጣጥሯል፡፡
ይሁን እንጂ በሀሰተኛ ወሬ ሕብረተሰቡን ወደ ግጭት እንዲያመራ እና የሕዝብ አለኝታና ጠባቂ የሆነውን ፖሊስ ስም ለማጉደፍ በሚንቀሳቀሱት ላይ ፖሊስ ጥብቅ ሕጋዊ እርምጃ እንደሚወስድና በቀጣይም ስፖርቱ ለእንዲህ ዓይነት ሥርዓት አልበኝነት ተገዢ እንዳይሆን ፖሊስ ከሚመለከታቸው አጋር አካላት ጋር ተቀራርቦ እንደሚሰራ ያስታውቃል፡፡
@YeneTube @FikerAssefa
❤35👎24👍2😁1
ለመገናኛ ብዙሃን !
የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን በአትሌት "ገለቴ ቡርቃ" ጉዳይ ለመገናኛ ብዙሃን ጋዜጣዊ መግለጫ ይሰጣል።
ስለሆነም ነገ ሰኔ 03/2017 ዓ.ም ከጠዋቱ 4:00 ጀምሮ በፌዴሬሽኑ በመገኘት መረጃውን ለስፖርት ቤተሰብ እንድታደርሱ በአክብሮት እንጠይቃለን ።
@Yenetube @Fikerassefa
የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ኮሚኒኬሽን
የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን በአትሌት "ገለቴ ቡርቃ" ጉዳይ ለመገናኛ ብዙሃን ጋዜጣዊ መግለጫ ይሰጣል።
ስለሆነም ነገ ሰኔ 03/2017 ዓ.ም ከጠዋቱ 4:00 ጀምሮ በፌዴሬሽኑ በመገኘት መረጃውን ለስፖርት ቤተሰብ እንድታደርሱ በአክብሮት እንጠይቃለን ።
@Yenetube @Fikerassefa
የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ኮሚኒኬሽን
👍28❤17😭2
አፕል የአለም ትልቁ ኩባንያ ነው። እአአ ከ2011 ጀምሮ የኩባንያው ዋጋ በቀን ከ700 ሚሊዮን ዶላር በላይ ይጨምራል። ይህ ስኬት ግን ያለ ቻይና የሚታሰብ አልነበረም። አፕል እና ቻይና ያለፉትን ሃያ ምናምን አመታት ቸበርቸስ ብለውበታል። ይሁን እንጂ ይህ የአሜሪካ ኩባንያ ሳያስበው ይሁን እያወቀ ካለቻይና መኖር የማይችልበት ሁኔታ ውስጥ ገብቷል። በዚህ ዙሪያ የሰራነው አጠር ያለ ልዩ ዝግጅት ነው ሊንኩን ተጭነው ይከታተሉት፤ መሰል ዝግጅቶችን በየጊዜው ለመከታተል ቻናሉን ሰብስክራይብ ያድርጉ።
https://youtu.be/GEAHr2Xqf5Q
https://youtu.be/GEAHr2Xqf5Q
YouTube
አፕል እና ቻይና
አፕል ዛሬ ላይ የአለም ትልቁ ኩባንያ ነው። ምን ያህል ትልቅ እንደሆነ ለማስረዳት የሚከተሉትን ቁጥሮች ልንገራችሁ። የአፕል ጥቅል ሃብቱ 3 ትሪሊዮን ዶላር ሲሆን አሜሪካ ውስጥ ባለፈው አመት ብቻ 60 ሚሊዮን አይፎን ስልኮችን ሸጧል። በአንድ ፋብሪካ ብቻ በቀን እስከ ግማሽ ሚሊዮን አይፎን ይመረታል። አምና ብቻ ጠቅላላ ገቢው 391 ቢሊዮን ዶላር ነበር።
Music track: Dreaming by Pufino…
Music track: Dreaming by Pufino…
❤20
Forwarded from The Urban Center ( Kebet Eske Ketema)
Ethiopian Building Code Standards
Private Sector Engagement in Code Revision: Week 2 Sessions
We’re back with five expert-led sessions in Week 2 of our 14-part workshop series, continuing the dialogue between private sector professionals and code developers:
🏢 Building Facility Management
🧯 Fire Safety & OHS
🏗 Structural Design Fundamentals
🚿 Building Plumbing Systems
📐 Spatial Design in Buildings
📅 June 10, 12 & 14, 2025
📍 The Urban Center
🖥 Also, live on TUC Facebook page & Google Meet
☕️ Free sessions with refreshments
✨ Participants are encouraged to register only for the sessions most relevant to them.
📲 Register now: https://forms.gle/NewtRdbnasiUFW6r7
🔗 Google Meet links will be shared 30 minutes before each session.
Many thanks to our partners for making this possible!
#EBCS #CodeRevision #BuiltEnvironment #ECA #CoTBE #TUC #FireSafety #StructuralDesign #Plumbing #FacilityManagement #SpatialDesign
Private Sector Engagement in Code Revision: Week 2 Sessions
We’re back with five expert-led sessions in Week 2 of our 14-part workshop series, continuing the dialogue between private sector professionals and code developers:
🏢 Building Facility Management
🧯 Fire Safety & OHS
🏗 Structural Design Fundamentals
🚿 Building Plumbing Systems
📐 Spatial Design in Buildings
📅 June 10, 12 & 14, 2025
📍 The Urban Center
🖥 Also, live on TUC Facebook page & Google Meet
☕️ Free sessions with refreshments
✨ Participants are encouraged to register only for the sessions most relevant to them.
📲 Register now: https://forms.gle/NewtRdbnasiUFW6r7
🔗 Google Meet links will be shared 30 minutes before each session.
Many thanks to our partners for making this possible!
#EBCS #CodeRevision #BuiltEnvironment #ECA #CoTBE #TUC #FireSafety #StructuralDesign #Plumbing #FacilityManagement #SpatialDesign
❤4
Forwarded from YeneTube
#ከቴምር ሪልስቴት
7ሳይቶችን ስርተን አስረክበናል አሁን ላይ ደግሞ መሀል ሣር ቤት አፓርትመንት እና ሱቅ ፒያሳ ለሽያጭ ያወጣነው
🎯የክፍያ አማራጮች 40/60 ለሚከፍል
👉1መኝታ 75ካሬ 4,815,000ብር ሙሉ ክፍያ
👉2መኝታ 94ካሬ 6,034,800ብር ሙሉ ክፍያ
👉2መኝታ 103ካሬ 6,612,600ብርሙሉክፍያ
👉3መኝታ 132ካሬ 8,474,400ብር ሙሉ ክፍያ
👉3መኝታ 146ካሬ 9,373,200ብር ሙሉ ክፍያ 9,373,000ብር
‼️ፒያሳ ሱቅ ሽያጭ
👉3.9ሚሊዮን 20ካሬ ቅድመ ክፍያ900,000ብር 4ተኛ እና 5ተኛ
👉4.2ሚሊዮን 20ካሬ ቅድመ ክፍያ 1.2ሚሊዮን 3ተኛ
👉4.8ሚሊዮን 20ካሬ ቅድመ ክፍያ 1.5ሚሊዮን 2ተኛ
👉5.5ሚሊዮን 20ካሬ ቅድመ ክፍያ 2ሚሊዮን 1ኛ
👉 7ሚሊዮን 20ካሬ ቅድመ ክፍያ 2.8ሚሊዮን ግራውንድ በውስጥ በኩል
👉10ሚሊዮን 20ካሬ ቅድመ ክፍያ 4ሚሊዮን ግራውንድ በውጪ
ለበለጠ መረጃ ይደውሉ
👇👇👇👇👇👇
+251939770177
+251996856273
https://tttttt.me/TemerRealEstateSalesConsultant
WhatsApp. https://wa.me/251939770177
7ሳይቶችን ስርተን አስረክበናል አሁን ላይ ደግሞ መሀል ሣር ቤት አፓርትመንት እና ሱቅ ፒያሳ ለሽያጭ ያወጣነው
🎯የክፍያ አማራጮች 40/60 ለሚከፍል
👉1መኝታ 75ካሬ 4,815,000ብር ሙሉ ክፍያ
👉2መኝታ 94ካሬ 6,034,800ብር ሙሉ ክፍያ
👉2መኝታ 103ካሬ 6,612,600ብርሙሉክፍያ
👉3መኝታ 132ካሬ 8,474,400ብር ሙሉ ክፍያ
👉3መኝታ 146ካሬ 9,373,200ብር ሙሉ ክፍያ 9,373,000ብር
‼️ፒያሳ ሱቅ ሽያጭ
👉3.9ሚሊዮን 20ካሬ ቅድመ ክፍያ900,000ብር 4ተኛ እና 5ተኛ
👉4.2ሚሊዮን 20ካሬ ቅድመ ክፍያ 1.2ሚሊዮን 3ተኛ
👉4.8ሚሊዮን 20ካሬ ቅድመ ክፍያ 1.5ሚሊዮን 2ተኛ
👉5.5ሚሊዮን 20ካሬ ቅድመ ክፍያ 2ሚሊዮን 1ኛ
👉 7ሚሊዮን 20ካሬ ቅድመ ክፍያ 2.8ሚሊዮን ግራውንድ በውስጥ በኩል
👉10ሚሊዮን 20ካሬ ቅድመ ክፍያ 4ሚሊዮን ግራውንድ በውጪ
ለበለጠ መረጃ ይደውሉ
👇👇👇👇👇👇
+251939770177
+251996856273
https://tttttt.me/TemerRealEstateSalesConsultant
WhatsApp. https://wa.me/251939770177
❤1
Forwarded from YeneTube
🌺🌸 #ግእዝን_በርቀት 🌺🌸
የግእዝን ቋንቋ በ፲፬ ዙሮች እስካኹን ለብዙ ሺሕ ተማሪዎች በቀላል መንገድ ማስተማር ተችሏል። አኹን ደግሞ በ፲፭ኛ ዙር በቴሌግራም ለኹለት ወራት ( ከሐምሌ ፩ እስከ ነሐሴ ፴፥ ፳፻፲፯ ዓ.ም. በተመጣጣኝ ክፍያ ለጀማሪ ተማሪዎች የሚኾን ትምህርት ለመስጠት ስለታሰበ ባሉበት ኾነው በቀላሉ መማር ከፈለጉ አኹኑኑ
@geezdistance15
የሚለውን የቴሌግራም የመጠቀሚያ ስም በመጫን ወደ ትምህርት መስጫ ቻናሉ መግባት ይችላሉ።
🌺🌸 #ግእዝን_በርቀት 🌺🌸
የግእዝን ቋንቋ በ፲፬ ዙሮች እስካኹን ለብዙ ሺሕ ተማሪዎች በቀላል መንገድ ማስተማር ተችሏል። አኹን ደግሞ በ፲፭ኛ ዙር በቴሌግራም ለኹለት ወራት ( ከሐምሌ ፩ እስከ ነሐሴ ፴፥ ፳፻፲፯ ዓ.ም. በተመጣጣኝ ክፍያ ለጀማሪ ተማሪዎች የሚኾን ትምህርት ለመስጠት ስለታሰበ ባሉበት ኾነው በቀላሉ መማር ከፈለጉ አኹኑኑ
@geezdistance15
የሚለውን የቴሌግራም የመጠቀሚያ ስም በመጫን ወደ ትምህርት መስጫ ቻናሉ መግባት ይችላሉ።
🌺🌸 #ግእዝን_በርቀት 🌺🌸
❤9
ከተማ አቀፉ የ2017 ዓ.ም የ8ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ተጀመረ።
በማስጀመሪያ መርሀ ግብሩ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ኃላፊ ዶክተር ዘላለም ሙላቱ ፤ የአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ አለማየሁ በገላን ቁጥር 2 አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ተገኝተው ፈተናውን በማስጀመር ተማሪዎችን አበረታተዋል።
ከተማ አቀፉ የ8ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና በሁሉም የመፈተኛ ጣቢያዎች ሰላማዊ ሆኖ በስኬት እንዲጠናቀቅ ከከተማ ጀምሮ እስከ ትምህርት ቤት ድረስ ሂደቱን የሚከታተል የኮማንድ ፖስት አደረጃጀት ከማዋቀር አንስቶ በቂ የፈተና አስፈጻሚዎች ተመልምለው ወደ ስራ መግባታቸውን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ኃላፊ ዶክተር ዘላለም ሙላቱ ተናግረዋል፡፡
በአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ 6,828 ተማሪዎች በ24 የመፈተኛ ጣቢያዎች ከተማ አቀፉን የ2017ዓ.ም የ8ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ለመውሰድ መመዝገባቸውን የክፍለ ከተማው ትምህርት ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ከበደ ድሪባ ገልጸዋል፡፡
በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር 71,972 ተማሪዎች በ194 የፈተና ጣቢያዎች የ2017ዓ.ም የ8ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተናን ለመውሰድ መመዝገባቸው እና በቂ ፈታኞች፣ጣቢያ ኃላፊዎች እንዲሁም ሱፐርቫይዘሮችን ጨምሮ የፈተና አስፈጻሚዎች መመደባቸው የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ አሳውቋል፡፡
Via Ethio FM
@YeneTube @FikerAssefa
በማስጀመሪያ መርሀ ግብሩ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ኃላፊ ዶክተር ዘላለም ሙላቱ ፤ የአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ አለማየሁ በገላን ቁጥር 2 አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ተገኝተው ፈተናውን በማስጀመር ተማሪዎችን አበረታተዋል።
ከተማ አቀፉ የ8ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና በሁሉም የመፈተኛ ጣቢያዎች ሰላማዊ ሆኖ በስኬት እንዲጠናቀቅ ከከተማ ጀምሮ እስከ ትምህርት ቤት ድረስ ሂደቱን የሚከታተል የኮማንድ ፖስት አደረጃጀት ከማዋቀር አንስቶ በቂ የፈተና አስፈጻሚዎች ተመልምለው ወደ ስራ መግባታቸውን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ኃላፊ ዶክተር ዘላለም ሙላቱ ተናግረዋል፡፡
በአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ 6,828 ተማሪዎች በ24 የመፈተኛ ጣቢያዎች ከተማ አቀፉን የ2017ዓ.ም የ8ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ለመውሰድ መመዝገባቸውን የክፍለ ከተማው ትምህርት ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ከበደ ድሪባ ገልጸዋል፡፡
በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር 71,972 ተማሪዎች በ194 የፈተና ጣቢያዎች የ2017ዓ.ም የ8ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተናን ለመውሰድ መመዝገባቸው እና በቂ ፈታኞች፣ጣቢያ ኃላፊዎች እንዲሁም ሱፐርቫይዘሮችን ጨምሮ የፈተና አስፈጻሚዎች መመደባቸው የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ አሳውቋል፡፡
Via Ethio FM
@YeneTube @FikerAssefa
❤12👍3
የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን በአትሌት ገለቴ ቡርቃ ጉዳይ ጋዜጣዊ መግለጫ እየሰጠ ይገኛል።
የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ፕሬዚዳንት ኮማንደር አትሌት ስለሺ ስህን፣የፌዴሬሽኑ ምክትል ፕሬዚዳንት አትሌት መሰረት ደፋር፣የፌዴሬሽኑ የስራ አስፈፃሚ ኮሚቴ አባልና የኮሚኒኬሽን ንኡስ ኮሚቴ ሰብሳቢ አቶ ቢኒያም ምሩፅ፣የፌዴሬሽኑ የስራ አስፈፃሚ ኮሚቴ አባልና የአትሌቶች ማህበር ፕሬዚዳንት ሌተናል ኮነሬል አትሌት የማነ ፀጋይ እና የፌዴሬሽኑ የስራ አስፈፃሚ ኮሚቴ አባልና የአትሌቶች ማህበር ምክትል ፕሬዚዳንት አትሌት በላይነሽ ዋቅጅራ እና የፌዴሬሽኑ ከፍተኛ የህክምና ባለሙያ ዶክተር አያሌው ጥላሁን በጋራ በመሆን በቶፕ ቴን ሆቴል መግለጫ እየሰጡ ይገኛሉ።
@YeneTube @FikerAssefa
የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ፕሬዚዳንት ኮማንደር አትሌት ስለሺ ስህን፣የፌዴሬሽኑ ምክትል ፕሬዚዳንት አትሌት መሰረት ደፋር፣የፌዴሬሽኑ የስራ አስፈፃሚ ኮሚቴ አባልና የኮሚኒኬሽን ንኡስ ኮሚቴ ሰብሳቢ አቶ ቢኒያም ምሩፅ፣የፌዴሬሽኑ የስራ አስፈፃሚ ኮሚቴ አባልና የአትሌቶች ማህበር ፕሬዚዳንት ሌተናል ኮነሬል አትሌት የማነ ፀጋይ እና የፌዴሬሽኑ የስራ አስፈፃሚ ኮሚቴ አባልና የአትሌቶች ማህበር ምክትል ፕሬዚዳንት አትሌት በላይነሽ ዋቅጅራ እና የፌዴሬሽኑ ከፍተኛ የህክምና ባለሙያ ዶክተር አያሌው ጥላሁን በጋራ በመሆን በቶፕ ቴን ሆቴል መግለጫ እየሰጡ ይገኛሉ።
@YeneTube @FikerAssefa
❤35
አትሌት ገለቴ ቡርቃ ከመጀመርያው አንስቶ የገጠማት ችግር ተነግሮ የሚያልቅ አይደለም፦ አትሌት መሠረት ደፋር
ለሀገሯ ይህን ያክል ዋጋ የከፈለችው አትሌት ከ2010 ዓ.ም ጀምሮ የገጠማትን ችግር ለመፍታት በፍርድ ቤት ስለመንከራተቷ በቅርበት አውቃለሁ ያለችው የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌደሬሽን ምክትል ፕሬዚዳንት አትሌት መሠረት ደፋር፤ ሕግ ለዚህች የሀገር ባለውለታ ትክክለኛውን ፍትህ እንዲሰጣት እጠይቃለሁ ብላለች።
መንግሥትም ለጉዳዩ ትኩረት እንዲሰጠው የኦሎምፒክ ሻምፒዮኗ መሠረት ደፋር አሳስባለች።
Via EBC
@YeneTube @FikerAssefa
ለሀገሯ ይህን ያክል ዋጋ የከፈለችው አትሌት ከ2010 ዓ.ም ጀምሮ የገጠማትን ችግር ለመፍታት በፍርድ ቤት ስለመንከራተቷ በቅርበት አውቃለሁ ያለችው የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌደሬሽን ምክትል ፕሬዚዳንት አትሌት መሠረት ደፋር፤ ሕግ ለዚህች የሀገር ባለውለታ ትክክለኛውን ፍትህ እንዲሰጣት እጠይቃለሁ ብላለች።
መንግሥትም ለጉዳዩ ትኩረት እንዲሰጠው የኦሎምፒክ ሻምፒዮኗ መሠረት ደፋር አሳስባለች።
Via EBC
@YeneTube @FikerAssefa
❤50👍6🔥1
YeneTube
አትሌት ገለቴ ቡርቃ ከመጀመርያው አንስቶ የገጠማት ችግር ተነግሮ የሚያልቅ አይደለም፦ አትሌት መሠረት ደፋር ለሀገሯ ይህን ያክል ዋጋ የከፈለችው አትሌት ከ2010 ዓ.ም ጀምሮ የገጠማትን ችግር ለመፍታት በፍርድ ቤት ስለመንከራተቷ በቅርበት አውቃለሁ ያለችው የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌደሬሽን ምክትል ፕሬዚዳንት አትሌት መሠረት ደፋር፤ ሕግ ለዚህች የሀገር ባለውለታ ትክክለኛውን ፍትህ እንዲሰጣት እጠይቃለሁ ብላለች።…
"ብዙ ገለቴዎች አሉን!"
- አትሌት ስለሺ ስህን
" ...ትክክለኛውን ፍትህ እንዲሰጣት እጠይቃለሁ"
- አትሌት መሠረት ደፋር
#Ethiopia | የኢትዮጲያ አትሌቲክስ ፌደሬሽን ፕሬዝዳንት አትሌት ስለሺ ስህን "ገለቴ ቡርቃ አደባባይ ወጥታ ጉዳቷን ተናገረች እንጂ ሌሎች ተመሳሳይ በደል እየደረሰባቸው ያሉ አደጋ የደረሰባቸው ብዙ አትሌቶች አሉ" ሲል ተናግሯል።
ፕሬዝዳንቱ አክሎም "ፌደሬሽኑ ላለፉት 3 ወራት ይሄንን ለመከላከል የሚያስችሉ ስራዎችን ስንሰራ ነበር። አሁን ላይ አትሌቶችን ከአደጋ የሚከላከል ኢንስቲቲዩት ከባህልና ስፖርት ሚኒስቴር ጋር በመሆን አቋቁመናል ሲል ፕሬዝዳንቱ ተናግሯል።
ብዙ የተጎዱ አትሌቶች አሉ። ብዙ ገለቴዎች አሉን። በወንዶች አትሌቶች ላይም ጭምር ነው አደጋው ያለው። ይሄንን ለማስቀረት እየሰራን ነው ብሏል።
እኛ እንደ ፌደሬሽን ከገለቴ ጎን መቆማችንን ለማሳወቅ እንወዳለን። ለሌሎች አትሌቶችም ከጎናቸው እንዳለን የኢትዮጲያ ህዝብ እንዲያውቅልን እንፈልጋለን" ብለዋል።
አትሌት ገለቴ ቡርቃ ከመጀመርያው አንስቶ የገጠማት ችግር ተነግሮ የሚያልቅ አይደለም፦ አትሌት መሠረት ደፋር
ለሀገሯ ይህን ያክል ዋጋ የከፈለችው አትሌት ከ2010 ዓ.ም ጀምሮ የገጠማትን ችግር ለመፍታት በፍርድ ቤት ስለመንከራተቷ በቅርበት አውቃለሁ ያለችው የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌደሬሽን ምክትል ፕሬዚዳንት አትሌት መሠረት ደፋር፤ ሕግ ለዚህች የሀገር ባለውለታ ትክክለኛውን ፍትህ እንዲሰጣት እጠይቃለሁ ብላለች።
መንግሥትም ለጉዳዩ ትኩረት እንዲሰጠው የኦሎምፒክ ሻምፒዮኗ መሠረት ደፋር አሳስባለች።
@Yenetube @Fikerassefa
- አትሌት ስለሺ ስህን
" ...ትክክለኛውን ፍትህ እንዲሰጣት እጠይቃለሁ"
- አትሌት መሠረት ደፋር
#Ethiopia | የኢትዮጲያ አትሌቲክስ ፌደሬሽን ፕሬዝዳንት አትሌት ስለሺ ስህን "ገለቴ ቡርቃ አደባባይ ወጥታ ጉዳቷን ተናገረች እንጂ ሌሎች ተመሳሳይ በደል እየደረሰባቸው ያሉ አደጋ የደረሰባቸው ብዙ አትሌቶች አሉ" ሲል ተናግሯል።
ፕሬዝዳንቱ አክሎም "ፌደሬሽኑ ላለፉት 3 ወራት ይሄንን ለመከላከል የሚያስችሉ ስራዎችን ስንሰራ ነበር። አሁን ላይ አትሌቶችን ከአደጋ የሚከላከል ኢንስቲቲዩት ከባህልና ስፖርት ሚኒስቴር ጋር በመሆን አቋቁመናል ሲል ፕሬዝዳንቱ ተናግሯል።
ብዙ የተጎዱ አትሌቶች አሉ። ብዙ ገለቴዎች አሉን። በወንዶች አትሌቶች ላይም ጭምር ነው አደጋው ያለው። ይሄንን ለማስቀረት እየሰራን ነው ብሏል።
እኛ እንደ ፌደሬሽን ከገለቴ ጎን መቆማችንን ለማሳወቅ እንወዳለን። ለሌሎች አትሌቶችም ከጎናቸው እንዳለን የኢትዮጲያ ህዝብ እንዲያውቅልን እንፈልጋለን" ብለዋል።
አትሌት ገለቴ ቡርቃ ከመጀመርያው አንስቶ የገጠማት ችግር ተነግሮ የሚያልቅ አይደለም፦ አትሌት መሠረት ደፋር
ለሀገሯ ይህን ያክል ዋጋ የከፈለችው አትሌት ከ2010 ዓ.ም ጀምሮ የገጠማትን ችግር ለመፍታት በፍርድ ቤት ስለመንከራተቷ በቅርበት አውቃለሁ ያለችው የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌደሬሽን ምክትል ፕሬዚዳንት አትሌት መሠረት ደፋር፤ ሕግ ለዚህች የሀገር ባለውለታ ትክክለኛውን ፍትህ እንዲሰጣት እጠይቃለሁ ብላለች።
መንግሥትም ለጉዳዩ ትኩረት እንዲሰጠው የኦሎምፒክ ሻምፒዮኗ መሠረት ደፋር አሳስባለች።
@Yenetube @Fikerassefa
❤49👍4👎2🔥1
የፌዴራል መንግስት የ2018 በጀት ዓመት ረቂቅ በጀት 1.93 ትሪሊዮን ብር ሆኖ ለህዝብ ተወካዮች ምክርቤት ቀረበ፡፡
የገንዘብ ሚኒስትር አሕመድ ሺዴ ዛሬ ለህዝብ ተወካዮች ምክርቤት እንዳቀረቡት ከ2018 ረቂቅ በጀት 1.2 ትሪሊዮን ብር ለመደበኛ ወጪ፣ 415 ቢሊዮን ብር ለካፒታል ወጪ፣ 315 ቢሊዮን ብር ለክልል መንግስታት ድጋፍ እንዲሁም 14 ቢሊዮን ብር ለክልሎች የዘላቂ ልማት ግቦች ማስፈፀሚያ ድጋፍ የሚውል ነው።
ከረቂቅ በጀቱ 1 ትሪሊዮን ብር ወይም 73 በመቶውን ከታክስ ገቢ 236 ቢሊዮን ብር ከልማት አጋሮች ቀሪውን ደግሞ ከፕሮጀክቶች ድጋፍ እና ልዩ ልዩ ገቢዎች ለማግኘት መታቀዱን ተገልጿል።
@YeneTube @FikerAssefa
የገንዘብ ሚኒስትር አሕመድ ሺዴ ዛሬ ለህዝብ ተወካዮች ምክርቤት እንዳቀረቡት ከ2018 ረቂቅ በጀት 1.2 ትሪሊዮን ብር ለመደበኛ ወጪ፣ 415 ቢሊዮን ብር ለካፒታል ወጪ፣ 315 ቢሊዮን ብር ለክልል መንግስታት ድጋፍ እንዲሁም 14 ቢሊዮን ብር ለክልሎች የዘላቂ ልማት ግቦች ማስፈፀሚያ ድጋፍ የሚውል ነው።
ከረቂቅ በጀቱ 1 ትሪሊዮን ብር ወይም 73 በመቶውን ከታክስ ገቢ 236 ቢሊዮን ብር ከልማት አጋሮች ቀሪውን ደግሞ ከፕሮጀክቶች ድጋፍ እና ልዩ ልዩ ገቢዎች ለማግኘት መታቀዱን ተገልጿል።
@YeneTube @FikerAssefa
❤27👎13😁7
ሰላም
የቻናላችን ቤተሰቦች የጋርመንት( Men Boxer ) በማምረት ዘርፍ የተሰማራቹ እንዲሁም Boxer ጨርቅ አቅራቢዎች በውስጥ መስመር አውሩን።
@Fikerassefa
የቻናላችን ቤተሰቦች የጋርመንት( Men Boxer ) በማምረት ዘርፍ የተሰማራቹ እንዲሁም Boxer ጨርቅ አቅራቢዎች በውስጥ መስመር አውሩን።
@Fikerassefa
👍7❤6
ህወሓትን በመቃወም የትጥቅ ትግል ውስጥ የገቡት ብርጋዴር ጄነራል ገብረእግዚአብሄር በየነ፤ በ #አፋር እና በ #ትግራይ ክልሎች ውስጥ “አራት ክፍለ ጦር” ያለው የራሳቸውን ሠራዊት ማደራጀታቸውን ተናገሩ።
#ከትግራይ ኃይሎች በመለየት የራሳቸውን ሠራዊት እየገነቡ መሆናቸውን የጠቀሱት ብርጋዴር ጄነራል ገብረእግዚአብሄር፤ "አዲስ ነገር ለመፍጠር" ወደ በረሃ መውደረዳቸውን እና "ከፓርቲ ነጻ የሆነ ኃይል ለመፍጠር፣... ፓርቲ የማያዝዘው ሠራዊት ለመፍጠር" እየተንቀሳቀሱ መሆኑን ገልፀዋል።
ጄነራሉ ከቢቢሲ ትግርኛ ጋር ባደረጉት ቃለ ምልልስ፤ ከትግራይ ሠራዊት አመራሮች ጋር የተለያዩት ከጥር 15/20017 ዓ.ም. ጀምሮ መሆኑን አስረድተዋል።
የትግራይ ሠራዊት ከፍተኛ አመራሮች ጥር 15 ተሰብስበው በአቶ ጌታቸው ረዳ የሚመራውን ጊዜያዊ አስተዳደር ሲያወግዙ፣ ተቃውመው ስብሰባውን ረግጠው ከወጡ አመራሮች መካከል አንዱ ጄነራል ገብረ እግዚአብሄር በየነ ናቸው።
ይህንንም ተከትሎ የሠራዊቱ አመራሮች ጄነራል ገብረ እግዚአብሄር በየነን እና ሌሎች የሠራዊቱን ውሳኔ የተቃወሙትን ማገዳቸው ይታወሳል።
ጄነራል ገብረ እግዚአብሄር "ከፓርቲ ጋር ተጣብቆ ማህተም የሚነጥቅ፣ ከፓርቲ ጋር ተጣብቆ የሚሾም እና የሚሽር ኃይል ለወጣቱ ትውልድ ትተን መሄድ አንፈልግም። ወገንተኛ ያልሆነ ፍትሃዊ ኃይል ለመፍጠር እንጂ፣ የሆነ ፓርቲ አሽከርነት የለንም፤ አናደርገውም" ብለዋል።
ለተቃውሟቸው ጠመንጃ ማንሳትን መምረጣቸው በጦርነት ውስጥ የቆየውን የትግራይ ክልል ዳግም ወደ ግጭት አዙሪት አይከተውም ወይ ተብለው የተጠየቁት ጄነራሉ "እኔ ኢንተርናሽናል ጄነራል ነኝ። ይህንን ሆኜ የህወሓት ሚሊሻ መሆን አልፈልግም። ህወሓት ፓርቲያችን ነው የሚሉ የእርሱን ሚሊሻ እንደሆኑ ነው የሚቆጥረው። ሚሊሻነትን ደግሞ አልቀበልም" ብለዋል።
@Yenetube
#ከትግራይ ኃይሎች በመለየት የራሳቸውን ሠራዊት እየገነቡ መሆናቸውን የጠቀሱት ብርጋዴር ጄነራል ገብረእግዚአብሄር፤ "አዲስ ነገር ለመፍጠር" ወደ በረሃ መውደረዳቸውን እና "ከፓርቲ ነጻ የሆነ ኃይል ለመፍጠር፣... ፓርቲ የማያዝዘው ሠራዊት ለመፍጠር" እየተንቀሳቀሱ መሆኑን ገልፀዋል።
ጄነራሉ ከቢቢሲ ትግርኛ ጋር ባደረጉት ቃለ ምልልስ፤ ከትግራይ ሠራዊት አመራሮች ጋር የተለያዩት ከጥር 15/20017 ዓ.ም. ጀምሮ መሆኑን አስረድተዋል።
የትግራይ ሠራዊት ከፍተኛ አመራሮች ጥር 15 ተሰብስበው በአቶ ጌታቸው ረዳ የሚመራውን ጊዜያዊ አስተዳደር ሲያወግዙ፣ ተቃውመው ስብሰባውን ረግጠው ከወጡ አመራሮች መካከል አንዱ ጄነራል ገብረ እግዚአብሄር በየነ ናቸው።
ይህንንም ተከትሎ የሠራዊቱ አመራሮች ጄነራል ገብረ እግዚአብሄር በየነን እና ሌሎች የሠራዊቱን ውሳኔ የተቃወሙትን ማገዳቸው ይታወሳል።
ጄነራል ገብረ እግዚአብሄር "ከፓርቲ ጋር ተጣብቆ ማህተም የሚነጥቅ፣ ከፓርቲ ጋር ተጣብቆ የሚሾም እና የሚሽር ኃይል ለወጣቱ ትውልድ ትተን መሄድ አንፈልግም። ወገንተኛ ያልሆነ ፍትሃዊ ኃይል ለመፍጠር እንጂ፣ የሆነ ፓርቲ አሽከርነት የለንም፤ አናደርገውም" ብለዋል።
ለተቃውሟቸው ጠመንጃ ማንሳትን መምረጣቸው በጦርነት ውስጥ የቆየውን የትግራይ ክልል ዳግም ወደ ግጭት አዙሪት አይከተውም ወይ ተብለው የተጠየቁት ጄነራሉ "እኔ ኢንተርናሽናል ጄነራል ነኝ። ይህንን ሆኜ የህወሓት ሚሊሻ መሆን አልፈልግም። ህወሓት ፓርቲያችን ነው የሚሉ የእርሱን ሚሊሻ እንደሆኑ ነው የሚቆጥረው። ሚሊሻነትን ደግሞ አልቀበልም" ብለዋል።
@Yenetube
❤43😁15👀1
በዲላ ከተማ የፖራዳይዝ ቫሊ ኮሌጅ ተማሪዎች የዩኒቨርስቲ መዉጫ ፈተና አለመዉሰዳቸዉን ተናገሩ
ለብስራት ሬዲዮ ቅሬታቸዉን የገለፁ በዲላ ከተማ የፖራዳይዝ ቫሊ ኮሌጅ ተፈታኝ ተማሪዎች እንደተናገሩት ከሆነ ፈተናዉን ለመዉሰድ አምና ጥር ወር ላይ 500 ብር ከፍለዉ እንደነበር ገልፀዋል ።
ባልታወቀ ምክንያት ፈተናዉ መቅረቱንና በቀጣይ ትፈተናላችሁ ተብለዉ በዚህ አመት ለፈተናዉ 200 ብር እንዲጨምሩ ብሎም ባሳለፍነዉ እሁድ የመፈተኛ ሚስጥራዊ እና መለያ ቁጥር እንዲወስዱ እንደተነገራቸው ተናግረዋል፡፡ ተፈታኞቹ ትምህርቱን ሲከታተሉ የነበረዉ በቅዳሜና እሁድ መርሃግብር ሲሆን ከተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች የተወጣጡ መሆናቸዉንም ገልጸዋል ።
ከያሉበት አከባቢ ፈተናዉን ለመዉሰድ ከፍተኛ ወጪ አዉጥተዉ መምጣታቸዉንና በተባሉት መሠረት እሁድ ሚስጥራዊ እና መለያ ቁጥር ለመዉሰድ ወደ ተቋሙ ሲያመሩ የሚያናግራቸዉ አንድም አካል አለማግኘታቸዉን ተናግረዋል ።ብስራት ሬዲዮ ጉዳዩን ለማጣራት የተቋሙን አመራሮች የናገረ ሲሆን ፈተናዉን ለመዉሰድ ከትምህርት ሚኒስቴር የፋይዳ መታወቂያ አስፈላጊ መሆኑ በተላለፈዉ መመሪያ መሠረት በጊዜዉ ያላቀረቡ ተማሪዎች በመኖራቸዉ ፈተናዉ ለቀጣይ አመት መተላለፉን ተናግረዋል ።
አክለዉም ተማሪዎቹን ለፈተና በበቂ ሁኔታ ማዘጋጀታቸውን አብዛኞቹ ተማሪዎችም የተባሉትን የፋይዳ ቁጥር በጊዜዉ መላካቸዉን ገልፀው እንዲፈተኑም ጥሪ ማቅረባቸዉን ክፍያዉንም እንዲከፍሉ ማድረጋቸዉንና ባለቀ ሰዓት ይህ ክስተት መፈጠሩን አስረድተዋል ። ተፈታኞቹም ይህ መልዕክት የተነገራቸዉ ፈተናዉን ለመዉሰድ ከያሉበት አከባቢ ወደ ከተማዋ ገብተዉ ፈተናዉ አንድ ቀን ሲቀረዉ መሆኑን ገልፀዋል ። የፋይዳ መታወቂያ በተባልነዉ ጊዜ ያቀረብን ተማሪዎች ያለ በቂ ምክንያት በዚህ ዓመት አለመፈተናችን ቅሬታ ፈጥሮብናል ሲሉ ተናግረዋል ።
@Yenetube @Fikerassefa
ለብስራት ሬዲዮ ቅሬታቸዉን የገለፁ በዲላ ከተማ የፖራዳይዝ ቫሊ ኮሌጅ ተፈታኝ ተማሪዎች እንደተናገሩት ከሆነ ፈተናዉን ለመዉሰድ አምና ጥር ወር ላይ 500 ብር ከፍለዉ እንደነበር ገልፀዋል ።
ባልታወቀ ምክንያት ፈተናዉ መቅረቱንና በቀጣይ ትፈተናላችሁ ተብለዉ በዚህ አመት ለፈተናዉ 200 ብር እንዲጨምሩ ብሎም ባሳለፍነዉ እሁድ የመፈተኛ ሚስጥራዊ እና መለያ ቁጥር እንዲወስዱ እንደተነገራቸው ተናግረዋል፡፡ ተፈታኞቹ ትምህርቱን ሲከታተሉ የነበረዉ በቅዳሜና እሁድ መርሃግብር ሲሆን ከተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች የተወጣጡ መሆናቸዉንም ገልጸዋል ።
ከያሉበት አከባቢ ፈተናዉን ለመዉሰድ ከፍተኛ ወጪ አዉጥተዉ መምጣታቸዉንና በተባሉት መሠረት እሁድ ሚስጥራዊ እና መለያ ቁጥር ለመዉሰድ ወደ ተቋሙ ሲያመሩ የሚያናግራቸዉ አንድም አካል አለማግኘታቸዉን ተናግረዋል ።ብስራት ሬዲዮ ጉዳዩን ለማጣራት የተቋሙን አመራሮች የናገረ ሲሆን ፈተናዉን ለመዉሰድ ከትምህርት ሚኒስቴር የፋይዳ መታወቂያ አስፈላጊ መሆኑ በተላለፈዉ መመሪያ መሠረት በጊዜዉ ያላቀረቡ ተማሪዎች በመኖራቸዉ ፈተናዉ ለቀጣይ አመት መተላለፉን ተናግረዋል ።
አክለዉም ተማሪዎቹን ለፈተና በበቂ ሁኔታ ማዘጋጀታቸውን አብዛኞቹ ተማሪዎችም የተባሉትን የፋይዳ ቁጥር በጊዜዉ መላካቸዉን ገልፀው እንዲፈተኑም ጥሪ ማቅረባቸዉን ክፍያዉንም እንዲከፍሉ ማድረጋቸዉንና ባለቀ ሰዓት ይህ ክስተት መፈጠሩን አስረድተዋል ። ተፈታኞቹም ይህ መልዕክት የተነገራቸዉ ፈተናዉን ለመዉሰድ ከያሉበት አከባቢ ወደ ከተማዋ ገብተዉ ፈተናዉ አንድ ቀን ሲቀረዉ መሆኑን ገልፀዋል ። የፋይዳ መታወቂያ በተባልነዉ ጊዜ ያቀረብን ተማሪዎች ያለ በቂ ምክንያት በዚህ ዓመት አለመፈተናችን ቅሬታ ፈጥሮብናል ሲሉ ተናግረዋል ።
@Yenetube @Fikerassefa
❤23