ደስታችን በጥንቃቄ ይታጀብ
የመቀሌን ነፃ መውጣት ተከትሎ ህዝቡ የተሰማውን ደስታ እየገለፀ ነው።
የአማራ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን በማህበራዊ ትስስር ገፁ እንዳለው በአሁኑ ሰአት በክልላችን ሁሉም አካባቢዎች ህብረተሰቡ ደስታውን እየገለፀ ሲሆን የደስታ አገላለፃችን ለሰርጎ ገቦች እንዳያጋልጠን አሁንም ወንጀለኞቹ በህግ ቁጥጥር ስር እስኪውሉ አካባቢያችንን በጥንቃቄ እንድንጠብቅ በማለት አሳስቧል።
@Yenetube @FikerAssefa
የመቀሌን ነፃ መውጣት ተከትሎ ህዝቡ የተሰማውን ደስታ እየገለፀ ነው።
የአማራ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን በማህበራዊ ትስስር ገፁ እንዳለው በአሁኑ ሰአት በክልላችን ሁሉም አካባቢዎች ህብረተሰቡ ደስታውን እየገለፀ ሲሆን የደስታ አገላለፃችን ለሰርጎ ገቦች እንዳያጋልጠን አሁንም ወንጀለኞቹ በህግ ቁጥጥር ስር እስኪውሉ አካባቢያችንን በጥንቃቄ እንድንጠብቅ በማለት አሳስቧል።
@Yenetube @FikerAssefa
#ሰበር_ዜና
ዛሬም የኤርትራ ዋና ከተማ አስመራ እንዲሁም ማንደፍራ በሮኬት ተመተዋል - ኤርትሪያ ፕረስ
ከምሽቱ አራት ሰዓት አከባቢ ላይ አስመራ በሮኬት መመቷቷን ከኤርትሪያ ፕረስ የፌስቡክ ገፅ ተመልክተናል።
@Yenetube @Fikerassefa
ዛሬም የኤርትራ ዋና ከተማ አስመራ እንዲሁም ማንደፍራ በሮኬት ተመተዋል - ኤርትሪያ ፕረስ
ከምሽቱ አራት ሰዓት አከባቢ ላይ አስመራ በሮኬት መመቷቷን ከኤርትሪያ ፕረስ የፌስቡክ ገፅ ተመልክተናል።
@Yenetube @Fikerassefa
#HappeningNow
የአዲስ አበባ ከተማ ነዋሪዎች የሀገር መከላከያ ሰራዊት በትላንትናው ምሽት የተቀዳጀውን ድል በማስመልከት በኢፌዴሪ ሀገር መከላከያ ሚኒስቴር በመገኘት የድጋፍ ሰልፍ በማድረግ ላይ ይገኛሉ ።
በተያያዘም ነዋሪዎቹ 15ኛውን የኢትዮጵያ ብሄር ብሄረሰቦች እና ህዘቦች በዓል በማክበር ላይ ናቸው ።
Via Addis Ababa City PS
@YeneTube @FikerAssefa
የአዲስ አበባ ከተማ ነዋሪዎች የሀገር መከላከያ ሰራዊት በትላንትናው ምሽት የተቀዳጀውን ድል በማስመልከት በኢፌዴሪ ሀገር መከላከያ ሚኒስቴር በመገኘት የድጋፍ ሰልፍ በማድረግ ላይ ይገኛሉ ።
በተያያዘም ነዋሪዎቹ 15ኛውን የኢትዮጵያ ብሄር ብሄረሰቦች እና ህዘቦች በዓል በማክበር ላይ ናቸው ።
Via Addis Ababa City PS
@YeneTube @FikerAssefa
"የራያ ህዝብ እጣ ፋንታ ድህረ-ትህነግ" በሚል ምክረ ሃሳብ የምሁራን ውይይት በአዲስ አበባ በመካሄድ ላይ ነው።
የትግራይ ህዝብ ነጻነት ግንባር (ትህነግ) ቡድን ድል በተደረገበት ማግስት የራያ ህዝብ እጣ ፋንታ ምን መሂን አለበት በሚል ሃሳብ የአካባቢው ተወላጆች እና ሙህራን በዛሬው እለት በአዲስ አበባ እየመከሩ ይገኛሉ፡፡በዚህ ውይይት ላይ የተገኙት የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ እና የአገልግሎት ዘርፎች ክላስተር አስተባባሪ አቶ ጃንጥራር አባይ የራያ ህዝብ ውብ ባህሉ እና ማንነቱ ተከብሮ ወደ ሚፈልገው እና ወደ ሚመስለው የወሎ ህዝብ እንዲጠቃለል የምሁራን ውይይት አስፈላጊ ነው ብለዋል፡፡ጊዜው ችግሮችን በውይይት የምንፈታበት እንደመሆኑ ህዝቡ ምን ይላል የሚለውን አዳምጦ በትህነግ ጭቆና ውስጥ የነበረውን ማህበረሰብ የነጻነት አየር የሚተነፍስበት ሁኔታ ሊፈጠር እንደሚገባ አሳስበዋል፡፡
በመድረኩ የመወያያ ሃሳብ ያቀረቡት ምህራን ትህነግ የአማርኛ ስም መጠሪያ ያላቸውን ስፍራዎች ወደ ትግርኛ ቀይሮ መቆየቱን እና ህጻናት በአፍ መፍቻ ቋንቋቸው እንዳይማሩ ተደርገው ስለመቆየታቸው አውስተዋል፡፡ማህበረሰቡ ላይ የተፈጸመውን በኢኮኖሚያ አሻጥር አስመልክቶም ተጽእኖ ለግዙፍ ፋብሪካ የተዘጋጁ ማሽነሪዎች ተነቅለው ወደ ትግራይ እንዲወሰዱ መደረጉ ምን ያህል የአካባቢ ነዋሪ ከምጣኔ ሃብት እድገት ተነጥሎ እንደኖረ ማሳያ ነውም ይላሉ ምሁራኑ፡፡ለገበሬው የተቆረፉ የውሃ ጉድጓዶች እንዲደፈኑ መደረግና በኢንቨስትመንት ስም ከፍተኛ የሆነ የመሬት ወረራ መፈጸም ሌላኛው የራያ አካባቢዎች ላይ በትህነግ የተፈጸመ ድርጊት ነው የሚሉት ምሁራኑ ለትህነግ ፋብሪካዎች ግብዓት እንዲሆን ከፍተኛ የሆነ የደን ጭፍጨፋ መፈጸሙንም አንስተዋል፡፡
በዚህም በአካባቢው ከፍተኛ የሆነ በረሃማነት እንዲስፋፋ ሆኗል ብለዋል፡፡የአካባቢው ተወላጃም በትህነግ የተነጠቀውን ማንነቱን ለማስጠበቅ በግፍ ተገድሏል ተብሏል፡፡ አካባቢውንም ለቆ እንዲሰደድ ተደርጓል ብለዋል፡፡ዛሬም ድረስ የት እንዳሉ በማይታወቅበት ሁኔታ ታፍነው የተወሰዱ የአካባቢው ተወላጆች እንዳሉም ተነስቷል፡፡የራያ ህዝብ በትግራይ እና በአማራ ክልሎች ያለፍላጎቱ ተከፋፍሎ እንዲኖር ያደረገው የትህነግ ሃይል መወገዱን ተከትሎ ዛሬም በፖለቲከኞች ጉተታ አሁን ያገኘውን እድል እንዳያጣ በጥንቃቄ መሰራት እንዳለበት አሳስበዋል፡፡
Via Ethio FM
@YeneTube @FikerAssefa
የትግራይ ህዝብ ነጻነት ግንባር (ትህነግ) ቡድን ድል በተደረገበት ማግስት የራያ ህዝብ እጣ ፋንታ ምን መሂን አለበት በሚል ሃሳብ የአካባቢው ተወላጆች እና ሙህራን በዛሬው እለት በአዲስ አበባ እየመከሩ ይገኛሉ፡፡በዚህ ውይይት ላይ የተገኙት የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ እና የአገልግሎት ዘርፎች ክላስተር አስተባባሪ አቶ ጃንጥራር አባይ የራያ ህዝብ ውብ ባህሉ እና ማንነቱ ተከብሮ ወደ ሚፈልገው እና ወደ ሚመስለው የወሎ ህዝብ እንዲጠቃለል የምሁራን ውይይት አስፈላጊ ነው ብለዋል፡፡ጊዜው ችግሮችን በውይይት የምንፈታበት እንደመሆኑ ህዝቡ ምን ይላል የሚለውን አዳምጦ በትህነግ ጭቆና ውስጥ የነበረውን ማህበረሰብ የነጻነት አየር የሚተነፍስበት ሁኔታ ሊፈጠር እንደሚገባ አሳስበዋል፡፡
በመድረኩ የመወያያ ሃሳብ ያቀረቡት ምህራን ትህነግ የአማርኛ ስም መጠሪያ ያላቸውን ስፍራዎች ወደ ትግርኛ ቀይሮ መቆየቱን እና ህጻናት በአፍ መፍቻ ቋንቋቸው እንዳይማሩ ተደርገው ስለመቆየታቸው አውስተዋል፡፡ማህበረሰቡ ላይ የተፈጸመውን በኢኮኖሚያ አሻጥር አስመልክቶም ተጽእኖ ለግዙፍ ፋብሪካ የተዘጋጁ ማሽነሪዎች ተነቅለው ወደ ትግራይ እንዲወሰዱ መደረጉ ምን ያህል የአካባቢ ነዋሪ ከምጣኔ ሃብት እድገት ተነጥሎ እንደኖረ ማሳያ ነውም ይላሉ ምሁራኑ፡፡ለገበሬው የተቆረፉ የውሃ ጉድጓዶች እንዲደፈኑ መደረግና በኢንቨስትመንት ስም ከፍተኛ የሆነ የመሬት ወረራ መፈጸም ሌላኛው የራያ አካባቢዎች ላይ በትህነግ የተፈጸመ ድርጊት ነው የሚሉት ምሁራኑ ለትህነግ ፋብሪካዎች ግብዓት እንዲሆን ከፍተኛ የሆነ የደን ጭፍጨፋ መፈጸሙንም አንስተዋል፡፡
በዚህም በአካባቢው ከፍተኛ የሆነ በረሃማነት እንዲስፋፋ ሆኗል ብለዋል፡፡የአካባቢው ተወላጃም በትህነግ የተነጠቀውን ማንነቱን ለማስጠበቅ በግፍ ተገድሏል ተብሏል፡፡ አካባቢውንም ለቆ እንዲሰደድ ተደርጓል ብለዋል፡፡ዛሬም ድረስ የት እንዳሉ በማይታወቅበት ሁኔታ ታፍነው የተወሰዱ የአካባቢው ተወላጆች እንዳሉም ተነስቷል፡፡የራያ ህዝብ በትግራይ እና በአማራ ክልሎች ያለፍላጎቱ ተከፋፍሎ እንዲኖር ያደረገው የትህነግ ሃይል መወገዱን ተከትሎ ዛሬም በፖለቲከኞች ጉተታ አሁን ያገኘውን እድል እንዳያጣ በጥንቃቄ መሰራት እንዳለበት አሳስበዋል፡፡
Via Ethio FM
@YeneTube @FikerAssefa
ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ ነገ በወቅታዊ አገራዊ ጉዳዮች ላይ ለምክር ቤት አባላት ማብራሪያ ይሰጣሉ!
የኢፌዲሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር አብይ አህመድ ነገ በወቅታዊ አገራዊ ጉዳዮች ላይ ከምክር ቤት አባላት ለሚቀርቡላቸው ጥያቄዎች ማብራሪያ እንደሚሰጡ ተገለጸ።የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ 5ኛው የሕዝብ ተወካዮች ም/ቤት 6ኛ ዓመት የስራ ዘመን 2ኛ ልዩ ስብሰባ ህዳር 21 ቀን 2013 ዓ.ም በጠቅላይ ሚኒስትር ጽ/ቤት በሚገኘው መሰብሰቢያ አደራሽ ከጠዋቱ 3:00 ጀምሮ ማካሄድ ይጀምራል፡፡
አጀንዳዎቹም
1. የም/ቤቱን 6ኛ አመት የስራ ዘመን 4ኛ መደበኛ ስብሰባ ቃለ ጉባኤ መርምሮ ማጽደቅ፣
2. የኢፌዲሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ክቡር ዶ/ር አብይ አህመድ በወቅታዊ አገራዊ ጉዳዮች ላይ ከምክር ቤት አባላት ለሚቀርቡላቸው ጥያቄዎች የሚሰጡትን መልስ ማዳመጥ እንደሆነ ምክር ቤቱ አስታውቋል።
@YeneTube @FikerAssefa
የኢፌዲሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር አብይ አህመድ ነገ በወቅታዊ አገራዊ ጉዳዮች ላይ ከምክር ቤት አባላት ለሚቀርቡላቸው ጥያቄዎች ማብራሪያ እንደሚሰጡ ተገለጸ።የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ 5ኛው የሕዝብ ተወካዮች ም/ቤት 6ኛ ዓመት የስራ ዘመን 2ኛ ልዩ ስብሰባ ህዳር 21 ቀን 2013 ዓ.ም በጠቅላይ ሚኒስትር ጽ/ቤት በሚገኘው መሰብሰቢያ አደራሽ ከጠዋቱ 3:00 ጀምሮ ማካሄድ ይጀምራል፡፡
አጀንዳዎቹም
1. የም/ቤቱን 6ኛ አመት የስራ ዘመን 4ኛ መደበኛ ስብሰባ ቃለ ጉባኤ መርምሮ ማጽደቅ፣
2. የኢፌዲሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ክቡር ዶ/ር አብይ አህመድ በወቅታዊ አገራዊ ጉዳዮች ላይ ከምክር ቤት አባላት ለሚቀርቡላቸው ጥያቄዎች የሚሰጡትን መልስ ማዳመጥ እንደሆነ ምክር ቤቱ አስታውቋል።
@YeneTube @FikerAssefa
ፕሬዝዳንት ሳህለ ወርቅ ዘውዴ ለይፋዊ የስራ ጉብኝት ጁቡቲ ገቡ!
ፕሬዝዳንቷ ጁቡቲ ሲደርሱ ፕሬዝዳንት እስማኤል ኦማር ጊዘሌ እና ሌሎች ከፍተኛ ባለስልጣናት አቀባበል አድርገውላቸዋል።ፕሬዝዳንቷ በጅቡቲ በሚኖራቸው ቆይታ ከጅቡቲው ፕሬዝዳንት እስማኤል ኦማር ጊሌ ጋር በሁለትዮሽ በቀጠናዊ እና ወቅታዊ የኢትዮጵያ ሁኔታ በተመለከተ ውይይት ያደርጋሉ ተብሎ ይጠበቃል።
[EBC]
@YeneTube @FikerAssefa
ፕሬዝዳንቷ ጁቡቲ ሲደርሱ ፕሬዝዳንት እስማኤል ኦማር ጊዘሌ እና ሌሎች ከፍተኛ ባለስልጣናት አቀባበል አድርገውላቸዋል።ፕሬዝዳንቷ በጅቡቲ በሚኖራቸው ቆይታ ከጅቡቲው ፕሬዝዳንት እስማኤል ኦማር ጊሌ ጋር በሁለትዮሽ በቀጠናዊ እና ወቅታዊ የኢትዮጵያ ሁኔታ በተመለከተ ውይይት ያደርጋሉ ተብሎ ይጠበቃል።
[EBC]
@YeneTube @FikerAssefa
የ2012 ዓ.ም ተመራቂ ለነበሩ ተማሪዎች ከነገ ጀምሮ ጥሪ እንደሚደረግ የሳይንስ እና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር አስታወቀ!
በ2012 ዓ.ም ተመራቂ የነበሩ ተማሪዎች ከነገ ኅዳር 21 ቀን 2013 ዓ.ም ጀምሮ ጥሪ እንደሚደረግ የሳይንስ እና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር አስታወቀ፡፡ሚኒስቴሩ ለመገናኛ ብዙኃን በላከው መግለጫ ከአንድ ሳምንት በኋላ ሌሎች ቀሪ ተማሪዎች እንዲገቡ እና በዚህ የትምህርት ዘመን የሚጠበቅባቸውን ሦስት የትምህርት ሴሚስቴር እንዲያጠናቅቁ በቂ ድጋፍ እና ክትትል ሊደረግላቸው ይገባል ሲል ገልጿል።ተመራቂ ተማሪዎች በቀሪዎቹ አጭር ወራት ውስጥ ያልተጠናቀቁ የትምህርት እና ሥልጠና ተግባራትን በተቻለ ቅልጥፍና እና ዝግጁነት በማጠናቀቅ ተመርቀው ወደ ሥራ ዓለም እንዲትቀላቀሉ እና የኢትዮጵያ የብልጽግና ጉዞ ላይ አሻራቸውን እንዲያኖሩ አሳስቧል።
ሌሎች በ2013 ትምህርት እና ሥልጠና ዘመን ሙሉ ዓመቱን በተቋማት ቆይታ የሚደርጉት ተማሪዎች በሙሉ፣ ትምህርታቸውን በአግባቡ እየተማሩ ለአገራችን እና ለሕዝባችን አንድነት እና ኅብረት እንዲሁም ብልጽግና ጉዞ ፋይዳ ያላቸው ሰብአዊ እና ማኅበራዊ በጎ አድራጎት ተግባራት እና አገልግሎቶች በንቃት በመሳተፍ ወገንተኝነታቸውን እንዲገልጹ ሚኒስቴር መሥሪያ ቤቱ ጥሪ አድርጓል።የከፍተኛ ትምህርት እና ሥልጠና ማኅበረሰብ በሙሉ የተለመደውን ቀና ድጋፍ እና ትብብር በማከል የ2013 ትምህርት እና ሥልጠና ዘመን የተሳካ እንዲሆን የበኩላቸውን ሚና እንዲጫወቱ ከአደራ ጭምር አሳስቧል።
[Walta]
@YeneTube @FikerAssefa
በ2012 ዓ.ም ተመራቂ የነበሩ ተማሪዎች ከነገ ኅዳር 21 ቀን 2013 ዓ.ም ጀምሮ ጥሪ እንደሚደረግ የሳይንስ እና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር አስታወቀ፡፡ሚኒስቴሩ ለመገናኛ ብዙኃን በላከው መግለጫ ከአንድ ሳምንት በኋላ ሌሎች ቀሪ ተማሪዎች እንዲገቡ እና በዚህ የትምህርት ዘመን የሚጠበቅባቸውን ሦስት የትምህርት ሴሚስቴር እንዲያጠናቅቁ በቂ ድጋፍ እና ክትትል ሊደረግላቸው ይገባል ሲል ገልጿል።ተመራቂ ተማሪዎች በቀሪዎቹ አጭር ወራት ውስጥ ያልተጠናቀቁ የትምህርት እና ሥልጠና ተግባራትን በተቻለ ቅልጥፍና እና ዝግጁነት በማጠናቀቅ ተመርቀው ወደ ሥራ ዓለም እንዲትቀላቀሉ እና የኢትዮጵያ የብልጽግና ጉዞ ላይ አሻራቸውን እንዲያኖሩ አሳስቧል።
ሌሎች በ2013 ትምህርት እና ሥልጠና ዘመን ሙሉ ዓመቱን በተቋማት ቆይታ የሚደርጉት ተማሪዎች በሙሉ፣ ትምህርታቸውን በአግባቡ እየተማሩ ለአገራችን እና ለሕዝባችን አንድነት እና ኅብረት እንዲሁም ብልጽግና ጉዞ ፋይዳ ያላቸው ሰብአዊ እና ማኅበራዊ በጎ አድራጎት ተግባራት እና አገልግሎቶች በንቃት በመሳተፍ ወገንተኝነታቸውን እንዲገልጹ ሚኒስቴር መሥሪያ ቤቱ ጥሪ አድርጓል።የከፍተኛ ትምህርት እና ሥልጠና ማኅበረሰብ በሙሉ የተለመደውን ቀና ድጋፍ እና ትብብር በማከል የ2013 ትምህርት እና ሥልጠና ዘመን የተሳካ እንዲሆን የበኩላቸውን ሚና እንዲጫወቱ ከአደራ ጭምር አሳስቧል።
[Walta]
@YeneTube @FikerAssefa
ሦስተኛው ምዕራፍ የህግ ማስከበሩ ዘመቻ በድል መጠናቀቁን እና አሁን ላይ ወደ መልሶ ማደራጀት መገባቱን ሌተናል ጄኔራል ባጫ ደበሌ ገለጹ፡፡
“ብንማረክ እንኳን በእነርሱ አንማረክም፤ እኛን የሚማርከን የኢትዮጵያ ሕዝብ ነው” ያሉት የራያ ግንባር የጦር አዛዥ ሌተናል ጄኔራል ባጫ ደበሌ ወቅታዊ የህግ ማስከበር ሥራን በተመለከተ በትግራይ ክልል ማእከላዊ ዞን ተራሮች ለጋዜጠኞች መግለጫ ሰጥተዋል፡፡ በመግለጫቸው ሦስተኛው ምእራፍ የህግ ማስከበሩ ዘመቻ በድል መጠናቀቁን እና አሁን ላይ ወደ መልሶ ማደራጀት መሸጋገራቸውን ተናግረዋል፡፡
የጁንታው ርዝራዦች የጦር መሪዎችን ማርከናል እያሉ የሚነዙት የሀሰት ፕሮፓጋንዳ ስለ ጦርነት አውድ ያላቸው እውቀት አናሳነት የሚያሳይ መሆኑን ገልጸዋል፡፡አንድን የጦር አዛዥ ለመማረክ ሰራዊቱን ሰብሮ መግባት እንደሚጠይቅ በማብራራት፤ የትህነግ ጁንታ ቡድን ሀይል ሰራዊቱን ሰብሮ መግባት ቁመናም እንደሌለው አይተናል ብለዋል ሌተናል ጄኔራል ባጫ ደበሌ፡፡ በሚቀጥሉት ሁለት ቀናት ዘመቻውን አስመልክቶ እና በቀጣይ ሁኔታ ላይ ከጄኔራል አበባው ታደሰ ጋር በመቀሌ ከተማ መግለጫ እንደሚሰጡ አስታውቀዋል።
[አብመድ]
@YeneTube @FikerAssefa
“ብንማረክ እንኳን በእነርሱ አንማረክም፤ እኛን የሚማርከን የኢትዮጵያ ሕዝብ ነው” ያሉት የራያ ግንባር የጦር አዛዥ ሌተናል ጄኔራል ባጫ ደበሌ ወቅታዊ የህግ ማስከበር ሥራን በተመለከተ በትግራይ ክልል ማእከላዊ ዞን ተራሮች ለጋዜጠኞች መግለጫ ሰጥተዋል፡፡ በመግለጫቸው ሦስተኛው ምእራፍ የህግ ማስከበሩ ዘመቻ በድል መጠናቀቁን እና አሁን ላይ ወደ መልሶ ማደራጀት መሸጋገራቸውን ተናግረዋል፡፡
የጁንታው ርዝራዦች የጦር መሪዎችን ማርከናል እያሉ የሚነዙት የሀሰት ፕሮፓጋንዳ ስለ ጦርነት አውድ ያላቸው እውቀት አናሳነት የሚያሳይ መሆኑን ገልጸዋል፡፡አንድን የጦር አዛዥ ለመማረክ ሰራዊቱን ሰብሮ መግባት እንደሚጠይቅ በማብራራት፤ የትህነግ ጁንታ ቡድን ሀይል ሰራዊቱን ሰብሮ መግባት ቁመናም እንደሌለው አይተናል ብለዋል ሌተናል ጄኔራል ባጫ ደበሌ፡፡ በሚቀጥሉት ሁለት ቀናት ዘመቻውን አስመልክቶ እና በቀጣይ ሁኔታ ላይ ከጄኔራል አበባው ታደሰ ጋር በመቀሌ ከተማ መግለጫ እንደሚሰጡ አስታውቀዋል።
[አብመድ]
@YeneTube @FikerAssefa
በሀገር ክህደት ወንጀል ተጠርጥረዉ በእስር ላይ የሚገኙ የጦር መኮነኖች ቤት ከፍተኛ ጉዳት ማድረስ የሚችሉ የጦር መሳሪያዎች መያዛቸው ተገለፀ!
በሀገር ክህደት ተጠርጥረዉ በእስር ላይ የሚገኙ የጦር መኮነኖች ቤት በተደረገው ፍተሻ የጦር ሜዳ መነጽሮች፣ ጂፒኤስ፣ በሳተላይት የሚሰሩ ስልኮች፣ ቦምቦች ፣ ክላሽንኮቭ፣ ብሬን፣ለእኩይተግባር ማስፈፀሚያ የሚዉሉ የተቀየረው የሰራዉይቱ የደንብ ልብሶች እና ሌሎች በግለሰብ እጅ መያዝ የሌለባቸዉ መሳሪያዎች በፍተሻ መያዛቸወረን የፌዴራልፖሊስ ኮሚሽን አስታውቋል፡፡
የሕወሓት ቡድን በሀገር መከላከያ ሠራዊት ላይ ጥቃት ማድረስ ከጀመረበት እለት አንስቶ በተደረጉ ፍተሻዎችና ብርበራዎች ከፍተኛ ቁጥር ያላቸው የተለያዩ የጦር መሳሪያዎች መያዛቸዉ ይታወቃል።
ምንጭ: አብመድ
@YeneTube @FikerAssefa
በሀገር ክህደት ተጠርጥረዉ በእስር ላይ የሚገኙ የጦር መኮነኖች ቤት በተደረገው ፍተሻ የጦር ሜዳ መነጽሮች፣ ጂፒኤስ፣ በሳተላይት የሚሰሩ ስልኮች፣ ቦምቦች ፣ ክላሽንኮቭ፣ ብሬን፣ለእኩይተግባር ማስፈፀሚያ የሚዉሉ የተቀየረው የሰራዉይቱ የደንብ ልብሶች እና ሌሎች በግለሰብ እጅ መያዝ የሌለባቸዉ መሳሪያዎች በፍተሻ መያዛቸወረን የፌዴራልፖሊስ ኮሚሽን አስታውቋል፡፡
የሕወሓት ቡድን በሀገር መከላከያ ሠራዊት ላይ ጥቃት ማድረስ ከጀመረበት እለት አንስቶ በተደረጉ ፍተሻዎችና ብርበራዎች ከፍተኛ ቁጥር ያላቸው የተለያዩ የጦር መሳሪያዎች መያዛቸዉ ይታወቃል።
ምንጭ: አብመድ
@YeneTube @FikerAssefa
አለም አቀፉ የቀይ መስቀል ኮሚቴ በመቀሌ ከተማ የሚገኙ ሆስፒታሎች ቁስለኞችን ለማከም የሕክምና ግብዓቶች እጥረት እንደገጠማቸው አስታወቀ። በከተማው የሚገኝ ሆስፒታል የአስከሬን ማስቀመጫ ከረጢት እንደሌለው የገለጸው ዓለም አቀፉ የቀይ መስቀል ኮሚቴ የእጅ ጓንትን ጨምሮ መሰረታዊ አቅርቦቶች እያለቁ መሆኑን ዛሬ ባወጣው መግለጫ ጠቁሟል። ዓለም አቀፉ የቀይ መስቀል ኮሚቴ እንዳለው 500 ሺሕ ገደማ ነዋሪዎች ያሏት መቀሌ ዛሬ እሁድ እረጭ ብላ ውላለች።
[DW]
@YeneTube @FikerAssefa
[DW]
@YeneTube @FikerAssefa
ሁለት ሻንጣ ሙሉ ብር ይዘው ሲንቀሳቀሱ የነበሩ ግለሰቦች በፖሊስ ቁጥጥር ስር ዋሉ።
ዋና ሳጅን ታከለ እሸቴ ይባላል የምዕራብ ጎንደር ዞን ፖሊስ መምሪያ ባልደረባ ሲሆን በአሁኑ ሰዓት ደግሞ በሁመራ ከተማ ሰላም እያስከበረ ይገኛል።
በቀን 19/03/2013 ዓ.ም ሰላም እያስከበረ በሚገኝበት ሁመራ ከተማ ላይ በአንድ በባለ ሶስት እግር ተሽከርካሪ(ባጃጅ) ላይ ሁለት ግለሰቦች ሁለት ሻንጣ ይዘው በመጓዝ ላይ ሳሉ ካለው ወቅታዊ ሁኔታ አኳያ ፍተሻ በሚያደርግበት ጊዜ ሁለቱም ሻንጣ ሙሉ ብር ሆኖ ተገኝቷል።
በወቅቱ ግለሰቦች አንዱን ሻንጣ ሙሉ ብር እንስጥህና ልቀቀን ቢሉትም ቃል የገባለትን ህዝብ እና ሙያውን በማስበለጥ ተጠርጣሪዎችን በቁጥጥር ስር አውሏቸዋል።
Via Amhara Police Commission
@YeneTube @FikerAssefa
ዋና ሳጅን ታከለ እሸቴ ይባላል የምዕራብ ጎንደር ዞን ፖሊስ መምሪያ ባልደረባ ሲሆን በአሁኑ ሰዓት ደግሞ በሁመራ ከተማ ሰላም እያስከበረ ይገኛል።
በቀን 19/03/2013 ዓ.ም ሰላም እያስከበረ በሚገኝበት ሁመራ ከተማ ላይ በአንድ በባለ ሶስት እግር ተሽከርካሪ(ባጃጅ) ላይ ሁለት ግለሰቦች ሁለት ሻንጣ ይዘው በመጓዝ ላይ ሳሉ ካለው ወቅታዊ ሁኔታ አኳያ ፍተሻ በሚያደርግበት ጊዜ ሁለቱም ሻንጣ ሙሉ ብር ሆኖ ተገኝቷል።
በወቅቱ ግለሰቦች አንዱን ሻንጣ ሙሉ ብር እንስጥህና ልቀቀን ቢሉትም ቃል የገባለትን ህዝብ እና ሙያውን በማስበለጥ ተጠርጣሪዎችን በቁጥጥር ስር አውሏቸዋል።
Via Amhara Police Commission
@YeneTube @FikerAssefa
የራያ ግንባር አዛዥ ሌተና ጄነራል ባጫ ደበሌ የፅንፈኛው የህወሓት ታጣቂ ቡድን ንብረታቸውን የዘረፈባቸውና ከቤት ንብረታቸው ተፈናቅለው በተለያዩ አካባቢዎች ለሚገኙ ተጎጂዎች ድጋፍ አደረጉ።
[EBC]
@YeneTube @FikerAssefa
[EBC]
@YeneTube @FikerAssefa
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አሕመድ ዛሬ በወቅታዊ ጉዳይ ላይ ማብራሪያ ይሰጣሉ
የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ዛሬ ኀዳር 21/2013 ከጠዋቱ 3:00 ሰዓት ጀምሮ ኹለተኛ ልዩ ስብሰባውን የሚያካሂድ ሲሆን በስብሰባው ላይም ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ (ዶ/ር) ይገኛሉ።
ከምክር ቤቱ አባላትም በወቅታዊ አገራዊ ጉዳዮችን በተመለከተ ለሚያነሱላቸው ጥያቄዎች ምላሽና ማብራሪያ ይሰጣሉ ተብሎም ይጠበቃል።
በስብሰባው ላይ የሐይማኖት አባቶች ፣ በአዲስ አበባ የሚገኙ አምባሳደሮችና የዓለም አቀፍ ተቋማት ተጠሪዎች እና ታዋቂ ግለሰቦች እንደሚገኙ ከምክር ቤቱ የተገኘው መረጃ ያመለክታል።
@Yenetube @FikerAssefa
የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ዛሬ ኀዳር 21/2013 ከጠዋቱ 3:00 ሰዓት ጀምሮ ኹለተኛ ልዩ ስብሰባውን የሚያካሂድ ሲሆን በስብሰባው ላይም ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ (ዶ/ር) ይገኛሉ።
ከምክር ቤቱ አባላትም በወቅታዊ አገራዊ ጉዳዮችን በተመለከተ ለሚያነሱላቸው ጥያቄዎች ምላሽና ማብራሪያ ይሰጣሉ ተብሎም ይጠበቃል።
በስብሰባው ላይ የሐይማኖት አባቶች ፣ በአዲስ አበባ የሚገኙ አምባሳደሮችና የዓለም አቀፍ ተቋማት ተጠሪዎች እና ታዋቂ ግለሰቦች እንደሚገኙ ከምክር ቤቱ የተገኘው መረጃ ያመለክታል።
@Yenetube @FikerAssefa
ከበደ ጫኔ ከኃለፊነታቸው ተነሱ!
የኢትዮጵያ የስደትና ከስደት ተመላሾች ጉዳይ ኤጀንሲ ዋና ዳይሬክተር ከበደ ጫኔ ከኃለፊነታቸው ተነሱ።በምትካቸውም የጠቅላይ ሚንስትሩ የብሔራዊ ደህንነት ጉዳዮች አማካሪ ሚንስትር ዴኤታ የነበሩት ተስፋሁን ጎበዛይ ተተክተዋል።
ከበደ ጫኔ ከዚህ ቀደም በተለያዩ መሥሪያ ቤቶች ያገለገሉ ሲሆን ለአብነትም የገቢዎች ሚኒስቴር፤ የንግድና ኢንዱስትሪ ሚኒስቴር እና በአማራ ክልል ለብዙ ዓመታትም የክልሉ የአስተዳደርና ፀጥታ ቢሮ ኃላፊ ሆነው ማገልገላቸውም የሚታወስ ነው።
[Addis Maleda]
@YeneTube @FikerAssefa
የኢትዮጵያ የስደትና ከስደት ተመላሾች ጉዳይ ኤጀንሲ ዋና ዳይሬክተር ከበደ ጫኔ ከኃለፊነታቸው ተነሱ።በምትካቸውም የጠቅላይ ሚንስትሩ የብሔራዊ ደህንነት ጉዳዮች አማካሪ ሚንስትር ዴኤታ የነበሩት ተስፋሁን ጎበዛይ ተተክተዋል።
ከበደ ጫኔ ከዚህ ቀደም በተለያዩ መሥሪያ ቤቶች ያገለገሉ ሲሆን ለአብነትም የገቢዎች ሚኒስቴር፤ የንግድና ኢንዱስትሪ ሚኒስቴር እና በአማራ ክልል ለብዙ ዓመታትም የክልሉ የአስተዳደርና ፀጥታ ቢሮ ኃላፊ ሆነው ማገልገላቸውም የሚታወስ ነው።
[Addis Maleda]
@YeneTube @FikerAssefa
#FakeNewsAlert
ሱዳን ፖስት የተባለ ድረ-ገጽ ደቡብ ሱዳን በሀገሯ የሚገኙትን የኢትዮጵያ አምባሳደር ስለማባረሯ እንዲሁም ኢትዮጵያ በአዲስ አበባ በሚገኙ የደቡብ ሱዳን ዲፕሎማቶች ላይ ተመሳሳይ እርምጃ ስለመውሰዷ በትናንትናው እለት አስነብቧል። መረጃውንም በርካታ ተከታይ ያላቸው ግለሰቦች ጭምር አጋርተውታል።
ሱዳን ፖስት ያሰራጨው መረጃ "ውሸት" መሆኑን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ቃል አቀባይ አምባሳደር ዲና ሙፍቲ ለኢትዮጵያ ቼክ ዛሬ ጠዋት አረጋግጠዋል። ኢትዮጵያ ቼክ ከደቡብ ሱዳን ኤምባሲም ተመሳሳይ ማረጋገጫ ያገኘ ሲሆን "ይህ ፍፁም ውሸት ነው፣ እንዲህ አይነት ነገር አልነበረም፣ ሆን ተብሎ ሀገራቱን ለማጋጨት የሚደረግ ሴራ ነው" ተብሏል።
በቅርብ ወራትም "ደቡብ ሱዳን ለግብፅ የጦር ሰፈር መገንቢያ ሰጠች" የሚል የሀሰት ዜና ተሰራጭቶ እንደነበር ይታወሳል።
Via @EthiopiaCheck
@YeneTube @FikerAssefa
ሱዳን ፖስት የተባለ ድረ-ገጽ ደቡብ ሱዳን በሀገሯ የሚገኙትን የኢትዮጵያ አምባሳደር ስለማባረሯ እንዲሁም ኢትዮጵያ በአዲስ አበባ በሚገኙ የደቡብ ሱዳን ዲፕሎማቶች ላይ ተመሳሳይ እርምጃ ስለመውሰዷ በትናንትናው እለት አስነብቧል። መረጃውንም በርካታ ተከታይ ያላቸው ግለሰቦች ጭምር አጋርተውታል።
ሱዳን ፖስት ያሰራጨው መረጃ "ውሸት" መሆኑን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ቃል አቀባይ አምባሳደር ዲና ሙፍቲ ለኢትዮጵያ ቼክ ዛሬ ጠዋት አረጋግጠዋል። ኢትዮጵያ ቼክ ከደቡብ ሱዳን ኤምባሲም ተመሳሳይ ማረጋገጫ ያገኘ ሲሆን "ይህ ፍፁም ውሸት ነው፣ እንዲህ አይነት ነገር አልነበረም፣ ሆን ተብሎ ሀገራቱን ለማጋጨት የሚደረግ ሴራ ነው" ተብሏል።
በቅርብ ወራትም "ደቡብ ሱዳን ለግብፅ የጦር ሰፈር መገንቢያ ሰጠች" የሚል የሀሰት ዜና ተሰራጭቶ እንደነበር ይታወሳል።
Via @EthiopiaCheck
@YeneTube @FikerAssefa