ግብፅ ባለፈው 24 ሰዓት ውስጥ 168 አዲስ የኮሮና ቫይረስ ተጠቂና 13 በበሽታው የሞቱ ሰዎችን ሪፖርት አድርጋለች። ይህንንም ተከትሎ በሀገሪቱ የተያዙ ሰዎች ቁጥር 2673 ሲደርስ 196 ሰዎች ደግሞ ሞተዋል።596 ሰዎች ደግሞ አገግመዋል።
ምንጭ:Daily News Egypt
@YeneTube @FikerAssefa
ምንጭ:Daily News Egypt
@YeneTube @FikerAssefa
የፌዴራል ፖሊስ ጋዜጠኛ ያየሰው ሽመልስን በሽብር ወንጀል ጠርጥሬዋለሁ በማለት በዛሬው እለት ችሎት እንዳቀረበው የጋዜጠኛው ጠበቃ አቶ ታደለ ገብረመድህን ለአውሎ ሚዲያ ተናግረዋል።
እንደ ጠበቃው ከሆነ ፖሊስ ጋዜጠኛውን በአማራ ክልል ሰ/ሸዋ ዞን ደራ ወረዳ ወጣቶችን በማደራጀት፤ በመንግስት ላይ አመፅ እንዲነሳ በማድረግ፤ የገንዘብ ዝውውር የሽብር ስራ ከሚሰሩ አካላት ጋር በመፈፀምና ለወጣቶች በመስጠት ጠርጥሬዋለሁ ብሏል።
ፍርድ ቤቱ ለሰኞ ሚያዚያ 12 ቀጠሮ ሰጥቷል። ጋዜጠኛ ያየሰው በኮሮና ቫይረስ ላይ ባሰራጨው መረጃ በሀሰተኛ መረጃ ማሰራጨት ተጠርጥሮ የታሰረው ከ3 ሳምንታት በፊት ሲሆን በትላንትናው እለት የአራዳ ምድብ ችሎት በ25 ሺ ብር ዋስ እንዲፈታ ወስኖ ነበር።
Via:- አውሎ ሚዲያ / ElU
@Yenetube @Fikerassefa
እንደ ጠበቃው ከሆነ ፖሊስ ጋዜጠኛውን በአማራ ክልል ሰ/ሸዋ ዞን ደራ ወረዳ ወጣቶችን በማደራጀት፤ በመንግስት ላይ አመፅ እንዲነሳ በማድረግ፤ የገንዘብ ዝውውር የሽብር ስራ ከሚሰሩ አካላት ጋር በመፈፀምና ለወጣቶች በመስጠት ጠርጥሬዋለሁ ብሏል።
ፍርድ ቤቱ ለሰኞ ሚያዚያ 12 ቀጠሮ ሰጥቷል። ጋዜጠኛ ያየሰው በኮሮና ቫይረስ ላይ ባሰራጨው መረጃ በሀሰተኛ መረጃ ማሰራጨት ተጠርጥሮ የታሰረው ከ3 ሳምንታት በፊት ሲሆን በትላንትናው እለት የአራዳ ምድብ ችሎት በ25 ሺ ብር ዋስ እንዲፈታ ወስኖ ነበር።
Via:- አውሎ ሚዲያ / ElU
@Yenetube @Fikerassefa
በስልጤ ዞን በሁሉም ወረዳ እና ከተማ አስተዳደሮች የቤት ለቤት የCOVID 19 በሽታ ተጠርጣሪዎች ልየታ ስራ ሊጀመር ነው ።
የስልጤ ዞን አዲስ አበባ እና ከአዳማ ከተሞች በቅርብ እርቀት ከመገኘት ባለፈ በተለያየ ማህበራዊ ትስስሮች የተገናኙ ከተሞች ናቸው፡፡ከነዚህ ከተሞች የሚመጡ መንገደኞችን 14 ቀናት Quarantine/በለይቶ ማቆያ እንዲቆዩ እና ምልክት ካላሳዩ ወደ ህብረተሰቡ እንዲቀላቀሉ እየተደረገ ይገኛል። ከዚሁ ጎን ለጎን የቤት ለቤት የቅኝት ስራችንን የጤና ኤክስቴንሽ ሰራተኞች አማካኝነተ ትኩሳት እና ሳል ያለባቸውን በቀበሌ ደረጃ በመለየት ለጤና ጣቢያ ሪፖርት በመድረግ በወረዳ ደረጃ የተቋቋሙት ምላሽ ሰጪ ኮሚቴዎች መረጃ በመስጠት በሀዋሳ በተቋቋመው የደቡብ ክልል ጤና ኢንስቲትዩት የተጠርጣሪ ናሙና የመላክ ስራ እንደሚሰራ ተገልፆል፡፡
ምንጭ: ስልጤ ዞን ጤና መምሪያ
@YeneTube @FikerAssefa
የስልጤ ዞን አዲስ አበባ እና ከአዳማ ከተሞች በቅርብ እርቀት ከመገኘት ባለፈ በተለያየ ማህበራዊ ትስስሮች የተገናኙ ከተሞች ናቸው፡፡ከነዚህ ከተሞች የሚመጡ መንገደኞችን 14 ቀናት Quarantine/በለይቶ ማቆያ እንዲቆዩ እና ምልክት ካላሳዩ ወደ ህብረተሰቡ እንዲቀላቀሉ እየተደረገ ይገኛል። ከዚሁ ጎን ለጎን የቤት ለቤት የቅኝት ስራችንን የጤና ኤክስቴንሽ ሰራተኞች አማካኝነተ ትኩሳት እና ሳል ያለባቸውን በቀበሌ ደረጃ በመለየት ለጤና ጣቢያ ሪፖርት በመድረግ በወረዳ ደረጃ የተቋቋሙት ምላሽ ሰጪ ኮሚቴዎች መረጃ በመስጠት በሀዋሳ በተቋቋመው የደቡብ ክልል ጤና ኢንስቲትዩት የተጠርጣሪ ናሙና የመላክ ስራ እንደሚሰራ ተገልፆል፡፡
ምንጭ: ስልጤ ዞን ጤና መምሪያ
@YeneTube @FikerAssefa
የብራዚሉ ፕሬዚዳንት ጃይር ቦልሴናሮ የሀገሪቱን የጤና ሚንስትር ከስልጣን አንስተዋል። ለዚህም ምክንያት ነው የተባለው ለኮሮና ቫይረስ ወረርኝ ምላሽ አሰጣጥ ላይ ሁለቱ ሰዎች የገቡበት ውዝግብ መሆኑን ዘ ጋርዲያን ዘግቧል ።
@YeneTube @FikerAssefa
@YeneTube @FikerAssefa
በአሜሪካ ቢያንስ 100 ኢትዮጵያውያን በኮሮናቫይረስ ሞተዋል ተባለ!
በአሜሪካ በኮሮናቫይረስ ምክንያት ከ100 ያላነሱ ኢትዮጵያውያን እና ትውልደ ኢትዮጵያውን መሞታቸውን በዩናይትድ ስቴትስ የኢትዮጵያ አምባሳደር ፍጹም አረጋ ተናገሩ።አምባሳደር ፍጹም "ቁጥሩን በትክክል ማስቀመጥ አስቸጋሪ ነው። ከምናገኛቸው መረጃዎችን እስካሁን ከ100 ያላሱ ህይወታቸውን እንዳጡ እየሰማን ነው" ብለዋል።
Via BBC
@YeneTube @FikerAssefa
በአሜሪካ በኮሮናቫይረስ ምክንያት ከ100 ያላነሱ ኢትዮጵያውያን እና ትውልደ ኢትዮጵያውን መሞታቸውን በዩናይትድ ስቴትስ የኢትዮጵያ አምባሳደር ፍጹም አረጋ ተናገሩ።አምባሳደር ፍጹም "ቁጥሩን በትክክል ማስቀመጥ አስቸጋሪ ነው። ከምናገኛቸው መረጃዎችን እስካሁን ከ100 ያላሱ ህይወታቸውን እንዳጡ እየሰማን ነው" ብለዋል።
Via BBC
@YeneTube @FikerAssefa
ድሬደዋ : - ከህዝብ ትራንስፖርት አገልግሎት አሰጣጥ ጋር በተያያዘ የተሠጠ ዉሳኔና መመሪያ
በሀገራችን ከኮረና ቫይረስ ወረርሽኝ ጋር በተያያዘ የአስቸኳይ ግዜ አዋጅ መታወጁ ይታወቃል::
በመሆኑም ይህንኑ የአስቸኳይ ግዜ አዋጅ ከማስፈፀም አንፃር በአስተዳደሩ ከህዝብ ትራንስፖርት አገልግሎት አሠጣጥ ጋር ተያይዞ ዉሳኔዎች ተላልፈዋል ::
በዉሳኔዉ መሰረት
1ኛ :-ገነገ ሚያዚያ 9 ቀን 2012 ጀምሮ በተሽከርካሪዎች የሰሌዳ ቁጥር ሙሉና ጎዶሎ በሚል በፈረቃ ይሰጥ የነበረዉ አገልግሎት ቀርቶ ሁሉም አገልግሎት መስጠት ይችላል::
2:-ከተሽከርካሪዎች ሰዉ የመጫን መጠን ጋር በተያያዘ ማንኛም የሶስት እግር ተሽከርካሪ መጫን የሚችለዉ የተሳፋሪ ሰዉ ብዛት 1ሰዉ ብቻ እንዲሆን ተወስኗል::
3ኛ:-ከዚሂ ቀደም እስከ ምሽቱ 3 ሰአት ብቻ እንዲሰጥ የተወሰነዉ የህዝብ ትራንስፖርት አገልግሎት መስጫ ሰአት ዉሳኔ እንደ ፀና የሚቆይ ይሆናል::
Via:- Dire Police
@Yenetube @Fikerassefa
በሀገራችን ከኮረና ቫይረስ ወረርሽኝ ጋር በተያያዘ የአስቸኳይ ግዜ አዋጅ መታወጁ ይታወቃል::
በመሆኑም ይህንኑ የአስቸኳይ ግዜ አዋጅ ከማስፈፀም አንፃር በአስተዳደሩ ከህዝብ ትራንስፖርት አገልግሎት አሠጣጥ ጋር ተያይዞ ዉሳኔዎች ተላልፈዋል ::
በዉሳኔዉ መሰረት
1ኛ :-ገነገ ሚያዚያ 9 ቀን 2012 ጀምሮ በተሽከርካሪዎች የሰሌዳ ቁጥር ሙሉና ጎዶሎ በሚል በፈረቃ ይሰጥ የነበረዉ አገልግሎት ቀርቶ ሁሉም አገልግሎት መስጠት ይችላል::
2:-ከተሽከርካሪዎች ሰዉ የመጫን መጠን ጋር በተያያዘ ማንኛም የሶስት እግር ተሽከርካሪ መጫን የሚችለዉ የተሳፋሪ ሰዉ ብዛት 1ሰዉ ብቻ እንዲሆን ተወስኗል::
3ኛ:-ከዚሂ ቀደም እስከ ምሽቱ 3 ሰአት ብቻ እንዲሰጥ የተወሰነዉ የህዝብ ትራንስፖርት አገልግሎት መስጫ ሰአት ዉሳኔ እንደ ፀና የሚቆይ ይሆናል::
Via:- Dire Police
@Yenetube @Fikerassefa
ወልቂጤ ከተማ ላይ የጸረ-ተህዋሲያን የኬሚካል እርጭት በዋናው የአስፓልት መንገድ ላይ ዛሬ መካሄዱን ከዞኑ ኮሚኒኬሽን ተመልክተናል።
@YeneTube @Fikerassefa
@YeneTube @Fikerassefa
የኦሮሚያ ፕሬዝዳንት ሽመልስ አብዲሳ 189 ትራክተሮችን እና 2000 ፓምፖችን ለአርሶ አደሮች አስረከቡ!
የኦሮሚያ ክልላዊ መንግስት ፕሬዝዳንት አቶ ሽመልስ አብዲሳ በዛሬው ዕለት ሻሸመኔ በሚገኘው ኬኛ የግብርና መሳሪያዎች ማምረቻ ፋብሪካ የተገጣጠሙ 189 ትራክተሮችን እና 2000 ፓምፖችን ለአርሶ አደሮች አስረክበዋል፡፡የኦሮሚያ ክልላዊ መንግስት የአርሶ አደሩን የአስተራርስ ዘይቤ በማዘመን ህይወቱን ለማሻሻል ከፍተኛ ጥረት በማድረግ ላይ መሆኑን በምክትል ርእሰ መስተዳድር ማዕረግ የማህበራዊ ክላስተር ሓላፊ አቶ አዲሱ አረጋ ገልፀዋል፡፡ኬኛ የግብርና መሳሪያዎች ማምረቻ ፋብሪካ እስካሁን 427 ትራክተሮችን በመገጣጠም ለተጠቃሚዎች ማቅረቡን አቶ አዲሱ ጨምረው ገልፀዋል፡፡
Via ETV
@YeneTube @FikerAssefa
የኦሮሚያ ክልላዊ መንግስት ፕሬዝዳንት አቶ ሽመልስ አብዲሳ በዛሬው ዕለት ሻሸመኔ በሚገኘው ኬኛ የግብርና መሳሪያዎች ማምረቻ ፋብሪካ የተገጣጠሙ 189 ትራክተሮችን እና 2000 ፓምፖችን ለአርሶ አደሮች አስረክበዋል፡፡የኦሮሚያ ክልላዊ መንግስት የአርሶ አደሩን የአስተራርስ ዘይቤ በማዘመን ህይወቱን ለማሻሻል ከፍተኛ ጥረት በማድረግ ላይ መሆኑን በምክትል ርእሰ መስተዳድር ማዕረግ የማህበራዊ ክላስተር ሓላፊ አቶ አዲሱ አረጋ ገልፀዋል፡፡ኬኛ የግብርና መሳሪያዎች ማምረቻ ፋብሪካ እስካሁን 427 ትራክተሮችን በመገጣጠም ለተጠቃሚዎች ማቅረቡን አቶ አዲሱ ጨምረው ገልፀዋል፡፡
Via ETV
@YeneTube @FikerAssefa
እንግሊዝ በኢትዮጵያ የኮሮና ቫይረስ ስርጭትን ለመከላከል የሚደረገውን ጥረት ለማገዝ የሚረዱ የህክምና ቁሳቁሶችን ልካለች።
የህክምና ቁሳቁሶች ዛሬ አዲስ አበባ የደረሱ ሲሆን፥ የኮቪድ-19 ስርጭትን ለመቆጣጠር እየተደረገ ያለውን ጥረት ለማገዝ ለኢትዮጵያ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት የሚሰጡ መሆናቸውን ከዩኒሴፍ ኢትዮጵያ ያገኘነው መረጃ ያመላክታል።
የህክምና ቁሳቁሶቹ የእንግሊዝ ዓለም አቀፍ የልማት ትብብር ክፍል ባደረገው የገንዘብ ድጋፍ በዩኒሴፍ ኢትዮጵያ አማካኝነት የተገዙ ናቸው።
የተደረገው ድጋፍ የህክምና ማስክ፣ የቀዶ ጥገና ጋዎኖች፣ የፊት መሸፈኛዎች፣ ሙሉ አካልን የሚሸፍኑ የህክምና አልባሳት እና ሌሎች ቁሳቁሶችን ያካተተ ነው።
Via:- FBC
@Yenetube @Fikerassefa
የህክምና ቁሳቁሶች ዛሬ አዲስ አበባ የደረሱ ሲሆን፥ የኮቪድ-19 ስርጭትን ለመቆጣጠር እየተደረገ ያለውን ጥረት ለማገዝ ለኢትዮጵያ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት የሚሰጡ መሆናቸውን ከዩኒሴፍ ኢትዮጵያ ያገኘነው መረጃ ያመላክታል።
የህክምና ቁሳቁሶቹ የእንግሊዝ ዓለም አቀፍ የልማት ትብብር ክፍል ባደረገው የገንዘብ ድጋፍ በዩኒሴፍ ኢትዮጵያ አማካኝነት የተገዙ ናቸው።
የተደረገው ድጋፍ የህክምና ማስክ፣ የቀዶ ጥገና ጋዎኖች፣ የፊት መሸፈኛዎች፣ ሙሉ አካልን የሚሸፍኑ የህክምና አልባሳት እና ሌሎች ቁሳቁሶችን ያካተተ ነው።
Via:- FBC
@Yenetube @Fikerassefa
የትንሳኤን በዓል ስናከብር ርቀታችንን ጠብቀንና ተገቢውን ጥንቃቄ በማድረግ መሆን አለበት... ዶክተር ሊያ ታደሰ
የትንሳኤ በዓልን ስናከብር እንደተለመደው በመሰባሰብ ሳይሆን ርቀታችንን ጠብቀንና ተገቢውን ጥንቃቄ በማድረግ መሆን እንዳለበት የጤና ሚኒስትር ዶክተር ሊያ ታደሰ አሳሰቡ። ዶክተር ሊያ የትንሳኤ በዓልን አስመልክቶ መልዕክት አስተላልፈዋል።በዓሉን የኮሮናቫይረስ ወረርሽኝን በመታገል ለሚያሳልፉ የጤና ባለሙያዎችና ሌሎች የህዝብ አገልግሎት መስጫ ሰራተኞችም ከወዲሁ ምስጋና አቅርበዋል።
የትንሳኤ በዓል በክርስትና እምነት ተከታዮች ዘንድ ትልቅ ቦታ የሚሰጠው እለት መሆኑን የተናገሩት ሚኒስትሯ፤ ኢትዮጵያዊያን ከዚህ ቀደም ይህንን በዓል በአብሮነትና በመሰባሰብ ያሳልፋሉ ብለዋል።ሆኖም አሁን ካለንበት ፈታኝ ወቅት አንጻር በዓሉን በመሰባሰብና በአብሮነት ማክበር እጅግ አደገኛ መሆኑንም አጽንኦት ሰጥተው ተናግረዋል።በመሆኑም በዓሉን ስናከብር እራሳችንና ቤተሰባችንን ከኮሮናቫይረስ በመከላከል መሆን እንዳለበት መክረዋል።በምግብ ዝግጅት ወቅት ያለምንም መዘናጋት ተገቢውን ጥንቃቄ ማድረግና ምግቦችን አብስሎ መመገብ ይገባልም ብለዋል።"አንዳችን ለሌላችን በማሰብ ይህንን አስቸጋሪ ወቅት ማለፍ አለብን" ሲሉም መልእክታቸውን አስተላልፈዋል።
Via ENA
@YeneTube @FikerAssefa
የትንሳኤ በዓልን ስናከብር እንደተለመደው በመሰባሰብ ሳይሆን ርቀታችንን ጠብቀንና ተገቢውን ጥንቃቄ በማድረግ መሆን እንዳለበት የጤና ሚኒስትር ዶክተር ሊያ ታደሰ አሳሰቡ። ዶክተር ሊያ የትንሳኤ በዓልን አስመልክቶ መልዕክት አስተላልፈዋል።በዓሉን የኮሮናቫይረስ ወረርሽኝን በመታገል ለሚያሳልፉ የጤና ባለሙያዎችና ሌሎች የህዝብ አገልግሎት መስጫ ሰራተኞችም ከወዲሁ ምስጋና አቅርበዋል።
የትንሳኤ በዓል በክርስትና እምነት ተከታዮች ዘንድ ትልቅ ቦታ የሚሰጠው እለት መሆኑን የተናገሩት ሚኒስትሯ፤ ኢትዮጵያዊያን ከዚህ ቀደም ይህንን በዓል በአብሮነትና በመሰባሰብ ያሳልፋሉ ብለዋል።ሆኖም አሁን ካለንበት ፈታኝ ወቅት አንጻር በዓሉን በመሰባሰብና በአብሮነት ማክበር እጅግ አደገኛ መሆኑንም አጽንኦት ሰጥተው ተናግረዋል።በመሆኑም በዓሉን ስናከብር እራሳችንና ቤተሰባችንን ከኮሮናቫይረስ በመከላከል መሆን እንዳለበት መክረዋል።በምግብ ዝግጅት ወቅት ያለምንም መዘናጋት ተገቢውን ጥንቃቄ ማድረግና ምግቦችን አብስሎ መመገብ ይገባልም ብለዋል።"አንዳችን ለሌላችን በማሰብ ይህንን አስቸጋሪ ወቅት ማለፍ አለብን" ሲሉም መልእክታቸውን አስተላልፈዋል።
Via ENA
@YeneTube @FikerAssefa
#96
በኢትዮጵያ በኮሮና የተያዙ ሰዎች ቁጥር 96 ደረሰ።
- ባለፉት 24 ሰዓታት በተደረጉ 842 ምርመራዎች አራት ሰዎች በኮሮና ቫይረስ መያዛቸው መረጋገጡን የጤና ሚኒስቴር እና የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት አስታውቀዋል። በአጠቃላይ 6231 ምርመራዎች ተደርገዋል
@YeneTube @FikerAssefa
በኢትዮጵያ በኮሮና የተያዙ ሰዎች ቁጥር 96 ደረሰ።
- ባለፉት 24 ሰዓታት በተደረጉ 842 ምርመራዎች አራት ሰዎች በኮሮና ቫይረስ መያዛቸው መረጋገጡን የጤና ሚኒስቴር እና የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት አስታውቀዋል። በአጠቃላይ 6231 ምርመራዎች ተደርገዋል
@YeneTube @FikerAssefa
የታማሚዎቹ ሁኔታ:
አራቱም ኢትዮጵያዊያን ሲሆኑ
1.ከዱባይ የመጣና በለይቶ ማቆያ ያለ የአዲስ አበባ ነዋሪ፣ ዕድሜ 22
2.በበሽታው ከተያዘ ሰው ጋር ንክኪ ያላት የአዲስ አበባ ነዋሪ፣ እድሜ 52
3.በበሽታው ከተያዘ ሰው ጋር ንክኪ ያለው የባህር ዳር ነዋሪ ፣ ዕድሜ 52
4.የጉዞ ታሪክ የሌላት፣ በበሽታው ከተያዘ ሰው ጋር ንክኪ ካላት እየተጣራ ያለ የአዲስ ቅድም ነዋሪ፣ዕድሜ 23
@YeneTube @FikerAssefa
አራቱም ኢትዮጵያዊያን ሲሆኑ
1.ከዱባይ የመጣና በለይቶ ማቆያ ያለ የአዲስ አበባ ነዋሪ፣ ዕድሜ 22
2.በበሽታው ከተያዘ ሰው ጋር ንክኪ ያላት የአዲስ አበባ ነዋሪ፣ እድሜ 52
3.በበሽታው ከተያዘ ሰው ጋር ንክኪ ያለው የባህር ዳር ነዋሪ ፣ ዕድሜ 52
4.የጉዞ ታሪክ የሌላት፣ በበሽታው ከተያዘ ሰው ጋር ንክኪ ካላት እየተጣራ ያለ የአዲስ ቅድም ነዋሪ፣ዕድሜ 23
@YeneTube @FikerAssefa
በአዲስ አበባ ኮድ 2 ተሽከርካሪዎች በፈረቃ ሊንቀሳቀሱ ነው
በአዲስ አበባ ከተማ የቤት ተሽከርካሪዎች (ኮድ-2) በፈረቃ ሊንቀሳቀሱ መሆኑ ተገለጸ።የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁን ለማስፈፀም በሚኒስትሮች ኮሚቴ የወጣ የትራንስፖርት ዘርፍ አፈፃጸም መመሪያ ላይ መግለጫ ተሰጥቷል።
በመግለጫው ላይ በአዲስ አበባ ከተማ ኮድ 2 የሆኑ የቤት ተሽከርካሪዎች በሌዳ ቁጥራቸው ሙሉና ጎዶሎነት በፈረቃ እንደሚንቀሳቀሱ ተገልጿል።በዚህም የሰሌዳቸው የመጨረሻ ቁጥር ሙሉ ወይም ዜሮ የሆኑ ተሽከርካሪዎች ዛሬ ዓርብ የሚንቀሳቀሱ ሲሆን፥ የሰሌዳ ቁጥራቸው መጨረሻ ጎዶሎ የሆነ ተሽከርካሪዎች ደግሞ ነገ ቅዳሜ ይንቀሳቀሳሉ ተብሏል።
ክልሎችም እንደራሳቸው ተጨባጭ ሁኔታ መመሪያ አውጥተው እንደሚተገብሩት ከትራንስፖርት ሚኒስቴር ያገኘነው መረጃ ያመላክታል። በመግለጫው ላይ የከተማ ታክሲ አገልግሎት በሚሰጡም ሆነ በሃገር አቋራጭ አውቶብሶች ላይ የወጣው መመሪያ በአግባቡ እንደሚተገበር ተነስቷል።
Via FBC
@YeneTube @FikerAssefa
በአዲስ አበባ ከተማ የቤት ተሽከርካሪዎች (ኮድ-2) በፈረቃ ሊንቀሳቀሱ መሆኑ ተገለጸ።የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁን ለማስፈፀም በሚኒስትሮች ኮሚቴ የወጣ የትራንስፖርት ዘርፍ አፈፃጸም መመሪያ ላይ መግለጫ ተሰጥቷል።
በመግለጫው ላይ በአዲስ አበባ ከተማ ኮድ 2 የሆኑ የቤት ተሽከርካሪዎች በሌዳ ቁጥራቸው ሙሉና ጎዶሎነት በፈረቃ እንደሚንቀሳቀሱ ተገልጿል።በዚህም የሰሌዳቸው የመጨረሻ ቁጥር ሙሉ ወይም ዜሮ የሆኑ ተሽከርካሪዎች ዛሬ ዓርብ የሚንቀሳቀሱ ሲሆን፥ የሰሌዳ ቁጥራቸው መጨረሻ ጎዶሎ የሆነ ተሽከርካሪዎች ደግሞ ነገ ቅዳሜ ይንቀሳቀሳሉ ተብሏል።
ክልሎችም እንደራሳቸው ተጨባጭ ሁኔታ መመሪያ አውጥተው እንደሚተገብሩት ከትራንስፖርት ሚኒስቴር ያገኘነው መረጃ ያመላክታል። በመግለጫው ላይ የከተማ ታክሲ አገልግሎት በሚሰጡም ሆነ በሃገር አቋራጭ አውቶብሶች ላይ የወጣው መመሪያ በአግባቡ እንደሚተገበር ተነስቷል።
Via FBC
@YeneTube @FikerAssefa
YeneTube
ዋፋ ሲናማ ( ሰይጣን ቤት) ለአረንጓዴ ፕሮጀክት ተብሎ ሊፈርስ ነው የአራዳ መሬት ልማት ማኔጅምነት ቤሮ ከዛሬ 112 አመት በፊት በአፄ ሚኒሊክ ጊዜ የተሰራውን በተለምዶ ስሙ ሜጋ አምፊ ቲያትር ወይንም ሰይጣን ቤት የተባለውን ሲኒማ ቤት ለአረንጓዴ ፕሮጀከት እንደሚያፈርሰው ለሲኒማ ቤቱ በድብዳቤ አሳውቋል። በቅርስነት የተመዘገበው ቤት መፍረስ እንደማይችል የከተማው ባህልና ቱሪዝም ቢሮ ማስታወቁ ይታወቃል።…
#ሰይጣን ቤት በአሁኑ ወቅት ዋፋ ሲኒማ ተብሎ የሚጠራው ቦታ እንደማይፈርስ አዲስ አበበ ከተማ አስተዳደር አረጋገጠ።
ቦታው በኢትዮጵያ የፊልም ኢንዱስትሪ ውስጥ ታሪካዊ እንደመሆኑ ታሪካዊ ይዞታውን በጠበቀ መልኩ የመስቀል አደባባይ እስከ ማዘጋጃ ቤት የሚገነባው የአረንጓዴ ልማት ፕሮጀክት አካል ሆኖ በአዲስ መልክ የሚገነባ ይሆናል ተብሏል።
ቦታው አሁን ላይ ያለበት ይዞታ ቦታውን በማይመጥን መልኩ በእቃ ማስቀመጫነት እያገለገለ እንደሚገኝ የከቲባ ፀ/ቤተ ተናግሯል ።
ቦታዉ ታሪካዊ ይዞታውን እንደጠበቀ በዘመናዊ መልኩ ተመልሶ ለአገልግሎት እንዲውል ይሰራል ተብሏል ።
#ሰሞኑንን_ሰይጣን ቤት ሊፈርስ እንደሆነ በሰፊው ሲነገር ቆይቷል።
@Yenetube @Fikerassefa
ቦታው በኢትዮጵያ የፊልም ኢንዱስትሪ ውስጥ ታሪካዊ እንደመሆኑ ታሪካዊ ይዞታውን በጠበቀ መልኩ የመስቀል አደባባይ እስከ ማዘጋጃ ቤት የሚገነባው የአረንጓዴ ልማት ፕሮጀክት አካል ሆኖ በአዲስ መልክ የሚገነባ ይሆናል ተብሏል።
ቦታው አሁን ላይ ያለበት ይዞታ ቦታውን በማይመጥን መልኩ በእቃ ማስቀመጫነት እያገለገለ እንደሚገኝ የከቲባ ፀ/ቤተ ተናግሯል ።
ቦታዉ ታሪካዊ ይዞታውን እንደጠበቀ በዘመናዊ መልኩ ተመልሶ ለአገልግሎት እንዲውል ይሰራል ተብሏል ።
#ሰሞኑንን_ሰይጣን ቤት ሊፈርስ እንደሆነ በሰፊው ሲነገር ቆይቷል።
@Yenetube @Fikerassefa
#News_Alert ጎረቤት ሀገር ጅቡቲ በ24 ሰዐት ውስጥ 141 ኬዝ ሪፓርት ተደርጓል። እስከዛሬ 732 ሰዎች በኮሮና ቫይረስ የተያዙ ሰዎች መኖራቸውን ተነግሯል።
@Yenetube @Fikerassefa
@Yenetube @Fikerassefa
በአፍሪካ በቀጣዮቹ 6 ወራት ውስጥ 10 ሚሊዮን ሰዎች በኮሮና ቫይረስ ሊጠቁ እንደሚችሉ የአለም ጤና ድርጅት አስታወቀ፡፡
በአፍሪካ የኮሮና ቫይረስ ወቅታዊ የስርጭት መጠን ግምት ውስጥ በማስገባት በቫይረሱ የተጠቁ ሰዎች ቁጥር በቀጣዮቹ 3 እና 6 ወራት 10 ሚሊየን ሊደርስ ይችላል ሲሉ አንድ የዓለም የጤና ድርጅት ባለሥልጣን አስታወቁ፡፡ በአፍሪካ የአለም ጤና ድርጅት የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ክንውን ሀላፊ ሚካኤል ያኦ እንዳሉት ቫይረሱ በአፍሪካ ያለውን ስርጭት መጠን በረጅም ጊዜ ለመገመት አስቸጋሪ ነው ብለዋል።
አሁን ባለው የስርጭት ሂደት በቀጣዮቹ 3 እና 6 ወራት የተጠቂ ሰዎች ቁጥር ወደ 10 ሚሊዮን ሊደርስ እንደሚችል አልጀዚራ ዘግቧል።አክለውም ምናልባትም በጤና ባለሙያዎችን ምክር እና መንግስታት የሚጥሉትን ገደቦች በትክክል የሚተገበሩ እንደሆነ ከግምቱ በብዙ እጥፍ ሊያሽቆለቁል እንደሚችል ተናግረዋል።
ሚካኤል ያኦ አክለውም ትንበያው ሊለወጥ አለያም ሊቀየር የሚችል መሆኑን የገለፁ ሲሆን ኢቦላን በተመለከተ እንጅግ የከፋ ትንበያዎች ሰዎች በወቅቱ ባህሪያቸውን በመለወጣቸው በተሰጡ መላምቶች ልክ ጉዳት አላመጣም ብለዋል፡፡
በአለም እጅግ ደሀ በሆነችው አህጉር አፍሪካ እስካሁን ከ 17 ሺህ በላይ የሚሆኑት ሰዎች በኮሮና ቫይረስ መጠቃታቸው ሲረጋገጥ 900 ገደማ የሚሆኑት ደግሞ በቫይረሱ ሞተዋል፡፡ይህ ቁጥር በቀጣዮቹ 6 ወራት በከፍተኛ መጠን ሊያሻቅብ እንደሚችል ነው ድርጅቱ ያስታወቀው
Via Ethio FM
@YeneTube @FikerAssefa
በአፍሪካ የኮሮና ቫይረስ ወቅታዊ የስርጭት መጠን ግምት ውስጥ በማስገባት በቫይረሱ የተጠቁ ሰዎች ቁጥር በቀጣዮቹ 3 እና 6 ወራት 10 ሚሊየን ሊደርስ ይችላል ሲሉ አንድ የዓለም የጤና ድርጅት ባለሥልጣን አስታወቁ፡፡ በአፍሪካ የአለም ጤና ድርጅት የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ክንውን ሀላፊ ሚካኤል ያኦ እንዳሉት ቫይረሱ በአፍሪካ ያለውን ስርጭት መጠን በረጅም ጊዜ ለመገመት አስቸጋሪ ነው ብለዋል።
አሁን ባለው የስርጭት ሂደት በቀጣዮቹ 3 እና 6 ወራት የተጠቂ ሰዎች ቁጥር ወደ 10 ሚሊዮን ሊደርስ እንደሚችል አልጀዚራ ዘግቧል።አክለውም ምናልባትም በጤና ባለሙያዎችን ምክር እና መንግስታት የሚጥሉትን ገደቦች በትክክል የሚተገበሩ እንደሆነ ከግምቱ በብዙ እጥፍ ሊያሽቆለቁል እንደሚችል ተናግረዋል።
ሚካኤል ያኦ አክለውም ትንበያው ሊለወጥ አለያም ሊቀየር የሚችል መሆኑን የገለፁ ሲሆን ኢቦላን በተመለከተ እንጅግ የከፋ ትንበያዎች ሰዎች በወቅቱ ባህሪያቸውን በመለወጣቸው በተሰጡ መላምቶች ልክ ጉዳት አላመጣም ብለዋል፡፡
በአለም እጅግ ደሀ በሆነችው አህጉር አፍሪካ እስካሁን ከ 17 ሺህ በላይ የሚሆኑት ሰዎች በኮሮና ቫይረስ መጠቃታቸው ሲረጋገጥ 900 ገደማ የሚሆኑት ደግሞ በቫይረሱ ሞተዋል፡፡ይህ ቁጥር በቀጣዮቹ 6 ወራት በከፍተኛ መጠን ሊያሻቅብ እንደሚችል ነው ድርጅቱ ያስታወቀው
Via Ethio FM
@YeneTube @FikerAssefa
በዓሉ እንቅስቃሴያችንን ገድበን የምናከብረው መሆን አለበት
- ዶ/ር ሊያ ታደሰ
ሰዎች የፋሲካ በዓልን እንቅስቃሴያቸውን በመገደብ ሊያከብሩ እንደሚገባ የጤና ሚኒስትር ዶ/ር ሊያ ታደሰ ገለፁ።
የጤና ሚኒስትሯ የትንሳዔ በዓልን ምክንያት በማድረግ መልዕክት አስተላልፈዋል።
በመልዕክታቸውም “በዓሉ እርስ በእርስ ማዕድ የምንቋደስበት፣ፍቅርን እና መተሳሰብን የምንገልፅበት ቢሆንም አሁን እንቀድሞ ጎረቤት፣ ዘመድ አዝማድ ተጠራርቶ የሚከበረው ሳይሆን አብረን ከምንኖራቸው የቤተሰብ አባላቶች ጋር ብቻ ሆነን የምናከብረው መሆን ይኖርበታል” ብለዋል።
ፍቅራችንንም አንዱ ለአንዱ በመጠንቀቅ የምንገልፅበት መሆን እንዳለበት ተናግረዋል፡፡
ወደ መገበያያ ስፍራዎችም ሲኬድ አካላዊ ርቀትን ጠብቀን እና የአፍ መሸፈኛዎችን በመጠቀም መሆን እንደሚገባው ነው ያሳሰቡት።
የእንሰሳት እርድ በሚካሄድበት ጊዜም በጥንቃቄ ሊሆን ይገባል ያሉት ዶ/ር ሊያ፥ ምግብንም አብስሎ መመገብ ይገባል ነው ያሉት።
እራሳችንን መገደባችን፣ መታግሳችን እና ዛሬ የምንወስዳቸው እርምጃዎች ለወደፊት በጥሩ ሁኔታ ማክበር እንድንችል ወሳኝ እርምጃዎች መሆናቸውንም አንስተዋል።
በመጨረሻም ይህንን በዓል ወረርሽኙን ለመከላከል በተለያዩ ቦታዎች በስራ ላይ የሚያሳልፉ የህክምና ባለሙያዎች እና ሌሎችም እያበረከቱ ላሉት አስተዋፅኦ ምስጋና አቅርበዋል።
Via:- FBC
@Yenetube @Fikerassefa
- ዶ/ር ሊያ ታደሰ
ሰዎች የፋሲካ በዓልን እንቅስቃሴያቸውን በመገደብ ሊያከብሩ እንደሚገባ የጤና ሚኒስትር ዶ/ር ሊያ ታደሰ ገለፁ።
የጤና ሚኒስትሯ የትንሳዔ በዓልን ምክንያት በማድረግ መልዕክት አስተላልፈዋል።
በመልዕክታቸውም “በዓሉ እርስ በእርስ ማዕድ የምንቋደስበት፣ፍቅርን እና መተሳሰብን የምንገልፅበት ቢሆንም አሁን እንቀድሞ ጎረቤት፣ ዘመድ አዝማድ ተጠራርቶ የሚከበረው ሳይሆን አብረን ከምንኖራቸው የቤተሰብ አባላቶች ጋር ብቻ ሆነን የምናከብረው መሆን ይኖርበታል” ብለዋል።
ፍቅራችንንም አንዱ ለአንዱ በመጠንቀቅ የምንገልፅበት መሆን እንዳለበት ተናግረዋል፡፡
ወደ መገበያያ ስፍራዎችም ሲኬድ አካላዊ ርቀትን ጠብቀን እና የአፍ መሸፈኛዎችን በመጠቀም መሆን እንደሚገባው ነው ያሳሰቡት።
የእንሰሳት እርድ በሚካሄድበት ጊዜም በጥንቃቄ ሊሆን ይገባል ያሉት ዶ/ር ሊያ፥ ምግብንም አብስሎ መመገብ ይገባል ነው ያሉት።
እራሳችንን መገደባችን፣ መታግሳችን እና ዛሬ የምንወስዳቸው እርምጃዎች ለወደፊት በጥሩ ሁኔታ ማክበር እንድንችል ወሳኝ እርምጃዎች መሆናቸውንም አንስተዋል።
በመጨረሻም ይህንን በዓል ወረርሽኙን ለመከላከል በተለያዩ ቦታዎች በስራ ላይ የሚያሳልፉ የህክምና ባለሙያዎች እና ሌሎችም እያበረከቱ ላሉት አስተዋፅኦ ምስጋና አቅርበዋል።
Via:- FBC
@Yenetube @Fikerassefa
በመተከል ዞን እና አዋሳኝ በሆነው አዊ ዞን በተደጋጋሚ የሚከሰተውን ሁከት በዘላቂነት መፍትሄ ለመስጠት በመከላከያ ሰራዊት የሚመራ ኮማንድ ፖስት መቋቋሙን የ22ኛ ክፍለ ጦር ዋና አዛዥ ብርጋዴር ጀኔራል ነገሪ ቶሊና አስታውቀዋል።
ከአሁን በፊት ታውጆ በፖለቲካ አመራሩ ሲመራ የነበረው ኮማንድ ፖስት አጥጋቢ ውጤት ባለማምጣቱ በሀገር መከላከያ ሰራዊት እንዲመራ ስምምነት ላይ ተደርሷል።በቀጠናው በተደጋጋሚ የሚስተዋሉ ግጭቶችን እልባት በመስጠት እስከ ግንቦት 30/2012 ዓ/ም ድረስ የተፈናቀሉ ዜጎችን ወደ ነበሩበት ቀየ ለማስመለስ ኮማንድ ፖስቱ እንደተቋቋመ ብርጋዴር ጄኔራሉ ጨምረው ተናግረዋል።
በሁለቱም ክልሎች አዋሳኝ አካባቢዎች ላይ ህገ ወጥ የጦር እና ድምፅ አልባ መሳሪዎችን ቁጥጥር በማድረግ የህብረተሰቡን የአብሮነት ዕሴት ለመመለስ ኮማንድ ፖስቱ በትኩረት እንደሚሰራም ተገልጿል።በሀገር መከላከያ ሰራዊት የሚመራው ይህ ኮማንድ ፖስት ከአሁን በፊት የተዘረፉ ንብረቶችን በማስመለስ እና ተጠርጣሪ ግለሰቦችን ለህግ ለማቅረብ በሚደረገው እንቅስቃሴ ላይ ሁከት በሚፈጥር አካል ላይ የሀይል እርምጃ እንደሚወሰድ ተጠቁሟል።
ምንጭ: የመተከል ዞን ኮምኒኬሽን መምሪያ
@YeneTube @FikerAssefa
ከአሁን በፊት ታውጆ በፖለቲካ አመራሩ ሲመራ የነበረው ኮማንድ ፖስት አጥጋቢ ውጤት ባለማምጣቱ በሀገር መከላከያ ሰራዊት እንዲመራ ስምምነት ላይ ተደርሷል።በቀጠናው በተደጋጋሚ የሚስተዋሉ ግጭቶችን እልባት በመስጠት እስከ ግንቦት 30/2012 ዓ/ም ድረስ የተፈናቀሉ ዜጎችን ወደ ነበሩበት ቀየ ለማስመለስ ኮማንድ ፖስቱ እንደተቋቋመ ብርጋዴር ጄኔራሉ ጨምረው ተናግረዋል።
በሁለቱም ክልሎች አዋሳኝ አካባቢዎች ላይ ህገ ወጥ የጦር እና ድምፅ አልባ መሳሪዎችን ቁጥጥር በማድረግ የህብረተሰቡን የአብሮነት ዕሴት ለመመለስ ኮማንድ ፖስቱ በትኩረት እንደሚሰራም ተገልጿል።በሀገር መከላከያ ሰራዊት የሚመራው ይህ ኮማንድ ፖስት ከአሁን በፊት የተዘረፉ ንብረቶችን በማስመለስ እና ተጠርጣሪ ግለሰቦችን ለህግ ለማቅረብ በሚደረገው እንቅስቃሴ ላይ ሁከት በሚፈጥር አካል ላይ የሀይል እርምጃ እንደሚወሰድ ተጠቁሟል።
ምንጭ: የመተከል ዞን ኮምኒኬሽን መምሪያ
@YeneTube @FikerAssefa
ጀርመን በዛሬው ሪፖርቷ 3,380 አዲስ የኮቪድ-19 ተጠቂዎችና 299 ሞት አሳውቃለች።በሀገሪቱ አጠቃላይ የተጠቂዎች ቁጥር 133,830 ሲደርስ የሟቾች ቁጥር 3,968 መድረሱን CGTN ዘግቧል።
@YeneTube @FikerAssefa
@YeneTube @FikerAssefa