YeneTube
118K subscribers
31.4K photos
485 videos
79 files
3.87K links
መረጃዎችን ለመላክ @Fikerassefa
Download Telegram
የሀ ዲጂታል አርት ኤክስፒሪያን በአሁኑ ሰአት በደማቅ ሁኔታ በመካሄድ ላይ ይገኛል ያልተካፈላችሁ የቻናላችን ቤተሰቦች እንድትሳተፉ እንመክራለን።

@Yenetube @Fikerassefa
የኦሮሚያ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት በምዕራብ ኦሮሚያ ወለጋ ዞኖች ውስጥ የኦነግ ሸኔ አባላት እየፈጸሙት ያለውን ህገ ወጥ ድርጊት ለማስቆም ከምን ጊዜውም በላይ የተጠናከረ እርምጃ እየወሰድል ነው ብሏል።

የኦሮሚያ ፖሊስ ኮሚሽን ምክትል ኮሚሽነር ግርማ ጋላን በስፍራው እየተወሰደ ያለውን እርምጃ አስመልክቶ ዛሬ በሰጡት መግለጫ ላይ መንግስት ልክ እንደከዚህ ቀደሙ ጥንቃቄ በተሞላበት መልኩ የተደራጀ የህግ የበላይነት ማስከበርን ያለመ እርምጃ እየወሰደ እንደሚገኝ ተናግረዋል።ምክትል ኮሚሽነሩ በመግለጫቸው የኦነግ ሸኔ አባላት በአካባቢው ላይ በንፁሃን ዜጎች፣ በፖሊስ አባላት እና በውጭ ሀገራት ዜጎች ላይ ግድያ መፈፀማቸውን ነው ያነሱት።ከዚህ ባለፈም አባላቱ እያደረሱት ባለው ጥፋት በርካታ ንፁሃን ዜጎች ከቤት ንብረታቸው መፈናቀላቸውንም አመልክተዋል።

በሴቶች ላይ አስገድዶ መድፈርን ጨምሮ በርከት ያሉ የሰብዓዊ መብት ጥሰቶችንም በመፈፀም ላይ ይገኛሉም ብለዋል።ፖሊስ እስካሁን እየወሰደ ያለው እርምጃ አባላቱ ከፈፀሙት ድርጊት ጋር ተመጣጣኝ ያልሆነ ዝቅተኛ መሆኑን ነው ያስረዱት።አሁን ላይ የህግ የበላይነትን ለማስከበር የክልሉ ፖሊስ ከአካባቢው ህብረተሰብ ፣ ከፌደራል ፖሊስ እና ከመከላከያ ሰራዊት ጋር በመሆን በቅንጅት የተጠናከረ እና የተደራጀ እርምጃ መውሰድ ጀምሯል ብለዋል።

የኦነግ ሸኔ አባላትን በሎጀስቲክ እና በሌላ መልኩ ድጋፍ እየደረጉ ያሉ ግለሰቦች እና ቡድኖች መኖራቸውን በመግለፅም እነዚህ አካላትን በተመለከተ ፖሊስ ጥናት እያደረገ መሆኑንና የጥናቱን ውጤት ለህዝብ ይፋ እንደሚያደርግ ነው የገለፁት።

ምንጭ: ፋና
@YeneTube @FikerAssefa
ኢዜማና ኦፌኮን ጨምሮ 6 የፖለቲካ ድርጅቶች ላቀረቡት አቤቱታ ምርጫ ቦርድ የመንግስት ኃላፊዎችን ምላሽ ተቀበለ!

ኢዜማና ኦፌኮን ጨምሮ ከስድስት የፖለቲካ ድርጅቶች ለቀረቡ አቤቱታዎች የሚመለከታቸው የመንግሥት አካላት ማብራሪያና ምላሽ እንዲሰጡ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ያሳሰበ ሲሆን፤ በዚህ መሰረት ምላሾቹን ትናንትና ከትናንት በስቲያ ሲቀበል ውሏል፡፡ለቦርዱ አቤቱታ ያቀረቡት ድርጅቶች፡- የትግራይ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ (ትዴፓ)፣ የኢትዮጵያ ዜጐች ለማህበራዊ ፍትህ (ኢዜማ) ኦሮሚያ ብሔራዊ ፓርቲ (ኦብፓ)፣ የኦሮሞ ፌደራላዊ ኮንግረስ (ኦፌኮ)፤ የኦሮሞ ነፃነት ግንባር (ኦነግ) እና የጌድዮ ሕዝብ ዴሞክራሲያዊ ድርጅት (ጌህዴድ) መሆናቸው ታውቋል፡፡

በዶ/ር አረጋዊ በርሄ የሚመራው ትዴፓ፤ በትግራይ ክልል አባላቶች ላይ እስር፣ ማስፈራራትና የቢሮ መዘጋት ችግር እንደገጠመው ሲያመለክት፤ ኢዜማ በበኩሉ፤ ህዝባዊ የህዝባዊ ስብሰባዎች መሰናክል በጐንደርና በደብረ ብርሃን እንዳጋጠመው አቤቱታ አቅርቧል፡፡ኦፌኮ በበኩሉ፤ የአባላት እስርና ማስፈራራት እንደደረሰበት በብ/ጀነራል ከማል ገልቹ የሚመራው ኦብፓ ደግሞ የአባላት እስራት፣ የቢሮ መዘጋት፣ ታፔላ መነቀልና አባላት ማስፈራራት አጋጥሞኛል ብሏል፡፡ኦነግ ደግሞ የፓርቲ መመስረቻ ፊርማ መነጠቅ አጋጥሞኛል፤ በተለያዩ የኦሮሚያ አካባቢዎችም አባላቶቼ ታስረውብኛል ሲል አቤቱታውን ማቅረቡ ታውቋል፡፡

የጌድኦ ሕዝብ ዴሞክራሲያዊ ድርጅት በበኩሉ፤ የፓርቲ ምስረታ ማሟያ ፊርማ የማሰባሰብ ሂደት መደናቀፍ ገጥሞኛል ማለቱን የምርጫ ቦርድ መረጃ ያመለክታል፡፡የፓርቲዎቹን አቤቱታ የተቀበለው ምርጫ ቦርድም፤ ጉዳዩ ይመለከታቸዋል ያላቸው አካላት የካቲት 26 እና 27 ቀን 2012 ዓ.ም በቀረቡባቸው ስሞታዎች ላይ ምላሻቸውን እንዲያቀርቡ ጠይቋል፡፡

የትግራይ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት መስተዳድር፤ የኦሮሚያ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት መስተዳድር፣ የአማራ ፖሊስ ኮሚሽን፣ የደቡብ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን፣ የኦሮሚያ ፖሊስ ኮሚሽንና የኦሮሚያ ክልል ምስራቅ ሸዋ ዞን፣ የዝዋይ (ባቱ) ከተማ ፖሊስ ምላሽ እንዲያቀርቡ የተጠየቀ ሲሆን፤ ቦርዱ ትላንትና ከትናንት በስቲያ ምላሻቸውን ሲያቀርቡ እንደነበር ለማወቅ ተችሏል፡፡

ምንጭ: አዲስ አድማስ
@YeneTube @FikerAssefa
በተባበሩት አረብ ኤሚሬቶች ትናንት የኮሮና ተሕዋሲ ከተገኘባቸው 13 ሰዎች 2ቱ ኢትዮጵያውያን መሆናቸውን የአገሪቱ ጤና ጥበቃ ሚኒስቴር አስታወቀ። ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ እንዳለው ተሕዋሲው የተገኘባቸው 13ት ሰዎች በሙሉ ከሌላ አገር የተጓዙ ናቸው።

የጤና ጥበቃ ምኒስትር ድዔታ ዶክተር ሊያ ታደሰ መረጃው እንደደረሳቸው አረጋግጠው ጉዳዩን እየተከታተሉ መሆኑን ገልጸዋል። የአረብ ኤሚሬቶች የጤና ጥበቃ ሚኒስቴር «ሁሉም ለ24 ሰዓታት ክትትል እየተደረገላቸው ሲሆን በጥሩ ሁኔታ ላይ ይገኛሉ» ብሏል።

Via Eshete Bekele
@YeneTube @FikerAssefa
በትግራይ ክልል የሚገኘው እና 18 ሺሕ ገደማ ኤርትራውያን የሚኖሩበት ሕንፃፅ የስደተኞች መጠለያ ሊዘጋ መሆኑ በኢትዮጵያ መንግሥት እንደተነገራቸው በዚያው የሚኖሩ ስደተኞ ተናገሩ።

በመጠለያው የሚኖሩ ስደተኞች በአስር ቀናት ውስጥ ሕንፃጽ መጠለያን እንዲለቁ በኢትዮጵያ ስደተኞች እና ከስደት ተመላሾች ጉዳይ አስተዳደር ባለፈው ሐሙስ ትዕዛዝ እንደተሰጣቸው ለዶይቼ ቬለ አስረድተዋል። በመጠለያ ጣቢያው የሚኖረው ሐዱሽ ታደለ «እዚህ ያለ ስደተኛ በምንም ተዓምር የማይቀበለው ነገር ነው» ሲል ተናግሯል።

የትግራይ ክልል መንግስት ኤርትራውያን ስደተኞች ወደ ኢትዮጵያ እንዳይገቡ፣ የተቋቋሙ የስደተኞች መጠልያ ጣብያዎች እንዲዘጉ መንግስታት "እያሴሩ ነው" ሲል ሲከስ ቆይቷል፡፡ የትግራይ ክልል ምክትል ርእሰ መስተዳድር ዶክተር ደብረፅዮን ገብረሚካኤል 45ኛ ዓመት የህወሓት ምስረታ የካቲት 11 በሚከበርበት ወቅት ባደረጉት ንግግር "ማነኛውም ሐይል" የኤርትራ ስደቸኞች መጠለያ ጣብያዎች መዝጋት አይችልም ሲሉ ገልፀው እንደነበረ ይታወሳል፡፡

Via DW
@YeneTube @FikerAssefa
Forwarded from Bruh Club
Last day of @yehadigitalart Festival … we hope to see you there.

Augmented Reality ማለት ምስል/ፖስተርን ወደ ተንቀሳቃሽ 2D-3D ሞዴል በመቀየር ልዩ ሰራዎችን ማየት የሚያስችል የጥበብ ዘርፍ አይነት ነው።

በዚህ አመት የሀ ዲጅታል አርት ላይ ያሉትን 10 Augmented Reality ስራዎች ለመመልከት የሚያስፈልጉት ከታች ያሉት 3 የAndroid App ብቻ ናቸው

1. Dede/Beth Molla art works
2. Dot Advertising
3. Yeha digital art poster

የተጠቀሱትን App ከቴሌግታም ቻናላችን https://tttttt.me/yehadigitalart ላይ ዳውንሎድ በማድረግ ወይንም በእለቱ ከአዘጋጆች እና አርቲስቶች በXender በመቀበል እና ስልክ ላይ በመጫን አስደናቂ ስራዎቹን በቀላሉ መመልከት ይችላሉ።
ኢትዮጵያ፣ሱዳንና ግብጽ ከህዳሴዉ ግድብ ጋር ተያይዞ ያላቸዉን ልዩነት በመነጋገር እንዲፈቱ የአፍሪካ ህብረት አሳሰበ፡፡

የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር ሙሳፋቂ ማህማት፣በሱዳን ሲያደርጉት የነበረዉን የሶስት ቀናት ጉብኝት ሲያጠናቅቁ እንዳሉት፣ተፈጥሯዊ ሀብቶቻችን የዕድገት እንጂ የግጭት መንስኤ ሊሆኑብን አይገባም ብለዋል፡፡

ሙሳፋቂ ማህማት ከሱዳኑ ጠቅላይ ሚንስትር አብደላ ሃምዶክ ጋር ባደረጉት ዉይይትም ሶስቱንም ሀገራት ተጠቃሚ በሚያደርግ መልኩ ተነጋግረዉ ልዩነቶቻቸዉን እንዲፈቱ ጠይቀዋል፡፡

የዋሽንግተኑ ድርድር ተስፋ የተጣለበት እንደነበር ጠቅሰዉ ይህ ዳር ባይደርስም ግን አሁንም ሀገራቱ መነጋገር እንደሚገባቸዉ ነዉ ያስታወቁት፡፡

ሱዳንን በተመለከተ ባደረጉት ንግግራቸዉ፣ሀገሪቱ በመልካም የሽግግር ሂደት ላይ እንደምትገኝ ጠቅሰዉ የተዳከመዉን ኢኮኖሚዋን እንዲያገግም ለማድረግ ግን ዓለም አቀፋ ማህበረሰብ ድጋፍ እንዲያደርግ ጠይቀዋል፡፡

አብደላ ሃምዶክ ወደ ስልጣን ከመጡ በኋላ በሱዳን ፖለቲካዉን ከማከም ባሻገር ኢኮኖሚዉ እንዲነቃቃ ለማድረግ ከፍተኛ ጥረት እያደረጉ ይገኛሉ መባሉን ሱዳን ትሪቡን ዘግቧል፡፡

Via:- Ethio FM
@YeneTube @Fikerassefa
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ ጂንካ ከተማ ገቡ!

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ በዛሬው ዕለት ለስራ ጉብኝት ደቡብ ኦሞ ዞን ጂንካ ከተማ ገብተዋል።ጠቅላይ ሚኒስትሩ ጂንካ አውሮፕላን ማረፊያ ሲደርሱ የደቡብ ክልል እና የዞኑ ከፍተኛ አመራሮች እንዲሁም የአገር ሽማግሌዎች ደማቅ አቀባበል አድርገውላቸዋል፡፡ጠቅላይ ሚኒስትሩ በጂንካ ከተማ ስታዲየም ለህዝቡ ንግግር እንደሚያደርጉ እና ከደቡብ ኦሞ ዞን ብሔረሰቦች ተወካዮች ጋር እንደሚወያዩ ይጠበቃል፡፡የሰላም ሚኒስትር ወ/ሮ ሙፈሪያት ካሚልን ጨምሮ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ኃላፊዎችም ከጠቅላይ ሚኒስትሩ ጋር በጂንካ ተገኝተዋል።

Via ETV
@YeneTube @FikerAssefa
የሸገር ዳቦ ፋብሪካ የግንባታ ስራው ተጠናቆ የማሽን ተከላ እየተከናወነ ነው።

ኢ/ር ታከለ ኡማ ፋብሪካው ያለበት ደረጃን ተመልክተዋል።ከወራት በፊት ግንባታው የተጀመረው የሸገር ዳቦ ፋብሪካ የሲቪል ስራው የተጠናቀቀ ሲሆን በአሁኑ ወቅትም የማሽን ተከላው እየተከናወነ ይገኛል።ኢ/ር ታከለ ኡማ የፋብሪካው ግንባታ ያለበትን ደረጃ ተመልክተዋል።የማምረቻ ማሽን ተከላው በውጪ ባለሙያዎች እየተከናወነ የሚገኝ ሲሆን ማሽኑ የተለያዩ ቴክኖሎጂዎችን ያማሏ ዘመናዊ ማሽን ነው።

ፋብሪካው የሚያስፈልገውን ሀይል ማቅረብ የሚችል ትራንስፎርመር በግዢ ሂደት ላይ የሚገኝ ሲሆን ከቀናት በኋላ ይጠናቀቃል።ከዳቦ ፋብሪካው ግንባታ ጎን ለጎንም የዱቄት ፋብሪካ ግንባታ ተጠናቆ የማሽን ተከላ ላይ ይገኛል።
ዳቦ ፋብሪካው ከቅርብ ጊዜ በኋላ ስራውን የሚጀምር ሲሆን ምርቱን በየክፍለ—ከተማዎች የሚያሰራጩ ተሽከርካሪዎችም ተዘጋጅተዋል።የዳቦ ምርቱን ለተጠቃሚዎች ለማድረስ ወጣቶች የተደራጁ ሲሆን ለመሸጫ የሚሆኑ አራት መቶ ከአገልግሎት ውጪ የነበሩ አንበሳ የከተማ አውቶብሶች ዝግጁ ተደርገዋል።

Via Mayor Office
@YeneTube @FikerAssefa
እንኳን ለማርች 8 የሴቶች ቀን በዓል አደረሳችሁ፡፡

@YeneTube @FikerAssefa
የኢትዮጵያ የመንግስት ዩኒቨርስቲዎች የምክክር መድረክ የህዳሴ ግድብ በተመለከተ ወቅታዊ የአቋም መግለጫ

እኛ የመንግስት ዩኒቨርስቲ ፕሬዜዳንቶች እና ምክትል ፕሬዜዳንቶች በታላቁ የህዳሴ ግድብ ግንባታ ዙሪያ ኢፍትሃዊ የሆነ ውሳኔ ለመወሰንና ለማስወሰን እንዳንድ ሀገራት የተዛባ ውሳኔ እንዲሰጥ ጫና ለመፍጠር እየጣሩ ይገኛሉ፡
በአንድ ወቅት ተመሳሳይ የተዛባ ውሳኔ በ League of Nations ሲተላለፍ በ1949 የወቅቱ የውጭ ጉዳይ ሚኒስተር የነበሩት የሚከተለውን ብለው ነበር፡፡

‹‹ሀገሬ ኢትዮጵያ በአለም ሸንጎ ላይ ፍርድ ተነፍጓት ስታዝን የመጀመሪያ ጊዜ አይደለም፡፡ ለነፃነቷና ለመብቷ ከኮሎኒያልስት ጣሊያን ጋር በየጊዜው ስትዋጋ ያሸነፈችውም ብቻዋን ነው፡፡ የተጠቃችውም ብቻዋን ስለሆነ ሀገሬ መቼውንም በሚደርስባት አደጋ ከማንም እርዳታ አገኛለሁ ብላ አትጠብቅም፡፡››
ዛሬም ሆነ ነገ ነፃነቷን ለመጠበቅ ታሪኳን ለማስከበር አስፈላጊውን ዝግጅት ማድረግ አለባት፡፡

እሷ እራሷ ብቻ ናት! እንዳሉት ሁሉ አሁንም ያለን ትውልዶች የተዛባውን ሚዛን ማስተካከል ያለብን እኛው ነን እና የአድዋውን ድል በተባበረው በአያቶቻችን ክንድ እዳሸነፍነው ሁሉ የህዳሴውንም ግድብ በተባበረው አንድነታችን፣ ክንዳችን እና ሀብታችን ሰርተን የምንጨርሰው መሆናችን እያረጋገጥን አቋማችንን በጋራ ስንገልፅ መነሻ ያደረግነው

1. የግድቡ መገንባት በአገሪቱ ፍትሐዊ ተጠቃሚነት ላይ ልዩነት እንደሌለው፣

2. ኮሎኒያሊስቶች አፍረካን እና ሀብቷን ለመቀራመት አውጥተውት የነበረና አሁን የሚያፍሩበት የ1029 እና የ1929 ዓ/ም ኢትዮጵያ ባልተወከለችበት የሕግ ተገዥ የምትሆንበት ሕጋዊም ሆነ አመክኒያዊ ነገር የሌለ መሆኑን፣

3. የሀገራችን ምሁራን በሰሯቸው ጥናቶች ግድቡ የሚገነባው ለመሬት መንቀጥቀጥ ተጋላጭ ባልሆነ ቦታ ከመሆኑ በተጨማሪ ውኃው ግብፅ ወይም ሱዳን ላይ ቢከማች ኖሮ በትንነት የሚባክነውን ውኃ ስለሚያስቀር ተመራጭ የሚያደርገው መሆኑን ነው፡፡
ከዚህ በላይ በቀረበው መነሻነትም ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን ባለ ስድስት ነጠብ የአቋም መግለጫ አውጥተናል፡፡

1ኛ/ የጀመርነው እውን ለማድረግ ሁለንተናዊ ድጋፍ እንደምናደርግ እናረጋግጣለን፡፡

2ኛ/ የህዳሴው ግድብ የአንድነታችን ተምሣሌት በመሆኑ በዘር፣ በኃይማኖትና በፖለቲካ አመለካከት ልዩነት ሳይኖር የመንግስትን አቋም የኢትዮጵያ ሕዝብ እንዲደግፍ እንጠይቃለን፡፡

3ኛ/ እኛ ጠግበን በብርሃን እየኖርን እናንተ በረሃብና በጨለማ ኑሮ ከሚል እና እራስ ወዳድ አስተሳሰብን በፅኑ እናወግዛለን፡፡

4ኛ/ እኛ የኢትዮጵያ የመንግስ ዩኒቨርስቲ አመራሮች በመላው ዓለም የሚገኙ ኢትዮጵያውያን እና ትውልደ ኢትዮጵያውን የየድርሻቸውን እንዲወጡና ዲፕሎማሲያዊ ጫና እንደያሳድሩ ጥሪያችንን እናስተላልፋለን፡፡

5ኛ/ የአረብ ሊግ በኢትዮጵያ ህዳሴ ላይ ሰሞኑን የወሰደውን ኢ-ፍትሐዊ ውሣኔ እየተቃወምን የአፍሪካ ህብረት እንዲህ ዓይነት ጣልቃ ገብነትን እንዲቃወምና መርህን እና ሕግን መሠረት በማድረግ ከኢትዮጵያ ጐን እንዲቆም እንጠይቃለን፡፡

6ኛ/ የአሜሪካ መንግስት በታዛቢነት ገብቶ ሀብት እና የዲፕሎማሲያዊ ኃይሉን በመጠቀም ወደ አደራዳሪነት እራሱን ከማሸጋገር በላይ የወሣኝነት ሚና ያለው የሚመስል መግለጫ ማውጣቱን አጥብቀን እንቃወማለን፡፡

የካቲት 28 /2012 ዓ/ም
ካፒታል ሆቴል
አዲስ አበባ

ምንጭ: አዲስ አበባ ዩንቨርስቲ
@YeneTube @FikerAssefa
እነ አቶ በረከት ስምዖን የተፋጠነ ፍትሕ ጠየቁ!

ለገጠማቸው የጤና ችግር በአካባቢው ሕክምና ማግኘት እንደማይችሉ ተናግረዋል።ከጥረት ኮርፖሬት ድርጅቶች ጋር በተያያዘ በከባድ የሙስና ወንጀል ተከሰው በእስር ላይ የሚገኙ እነ አቶ በረከት ስምዖን፣ ‹‹በሕመም እየተሰቃየን ስለሆነ የተፋጠነ ፍትሕ ይሰጠን፤›› ሲሉ ለፍርድ ቤት አመለከቱ፡፡አቶ በረከት ስምዖን፣ አቶ ታደሰ ካሳና አቶ ዳንኤል ግዛው ሐሙስ የካቲት 26 ቀን 2012 ዓ.ም. በአማራ ክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ቀርበው፣  የተከሰሱበት የሙስና ወንጀል ተመርምሮ አፋጣኝ ፍትሕ ማግኘት ሲገባቸው መዘግየቱን ተናግረዋል፡፡

አቶ በረከት ለፍርድ ቤቱ እንዳስረዱት፣ ቀደም ብሎ የጀመራቸው የጤና መታወክ እየተባባሰባቸው ነው፡፡ ባህር ዳር ውስጥ ያሉ የሕክምና ማዕከላት የተወሰዱ ቢሆንም፣ ተገቢ የሆነ ሕክምና ማግኘት ባለመቻላቸው ሕመማቸው እየተባባሰባቸው መሆኑን ገልጸዋል፡፡ተከሳሾቹ የመከላከያ ምስክሮቻችን አሰምተው እንደ ጨረሱ የክርክር ማቆሚያ ንግግር ማድረግ ሲገባቸው፣ ራሳቸው በጠየቁት ተጨማሪ የማብራሪያ ሰነድ ላይ አስተያየት እሰጣለሁ በሚል ዓቃቤ ሕግ ለሚያቀርበው ጥያቄ ሊፈቀድለት እንደማይገባ አስረድተዋል፡፡

አቶ ታደሰ ካሳም ለፍርድ ቤቱ የክስ ሒደቱ ሆን ተብሎ እንዲዘገይ እየተደረገ መሆኑን በመግለጽ፣ በአጭር ቀጠሮ ውሳኔ እንዲሰጣቸው ጠይቀዋል፡፡ ያላግባብ የሆነ ተደጋጋሚ የጊዜ ቀጠሮ እየተሰጠ እየተጉላሉ እንደሆነም አክለዋል፡፡ተከሳሾቹ ለፍርድ ቤት አቤቱታቸውን ያቀረቡት የመከላከያ ምስክሮቻቸውን አሰምተው ከጨረሱ በኋላ፣ አስፈላጊ የሆኑና በዳሸን ቢራ አክሲዮን ማኅበር ውስጥ የሚገኙ የሰነድ ማስረጃዎች በትዕዛዝ እንዲቀርቡላቸው ያቀረቡት ጥያቄ ፍርድ ቤቱ የተቀበለው ቢሆንም፣ ዓቃቤ ሕግ ግን በሰነዶቹ ላይ አስተያየት ለመስጠት ጊዜ እየወሰደ እንደሆነ አስረድተዋል፡፡

የግራ ቀኙን አቤቱታ የሰማው የአማራ ክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤት በሰጠው ምላሽ፣ እንኳን የጤና ችግር ያለባቸውን ተከሳሾች ቀርቶ ለሌሎች ተከሳሾችም ቢሆን ሕገ መንግሥቱን መሠረት ያደረገ የተፋጠነ ፍትሕ የማግኘት መብት እንዳላቸው ገልጿል፡፡ከጉዳዩ ውስብስብነት አንፃር አጫጭር ቀጠሮዎችን በመስጠት ማስረጃዎችን በማሰባሰብና በመመርመር አፋጣኝ መፍትሔ ለመስጠት ጥረት እየተደረገ መሆኑንም አክሏል፡፡ ምንም እንኳን ፍርድ ቤቱ ብዙ መዝገቦች ቢኖሩትም ጎን ለጎን በማየት በተፋጠነ ጊዜ ውሳኔ ለመስጠት እንደሚሠራ ገልጿል፡፡ ተከሳሾች ከምርመራ መዝገቡ ጋር ባያያዙት ማስረጃ ላይ ዓቃቤ ሕግ መጋቢት 4 ቀን 2012 ዓ.ም. መልስ እንዲሰጥ ትዕዛዝ ሰጥቷል፡፡    

ምንጭ: ሪፖርተር
@YeneTube @FikerAssefa
የኦሮሚያ ፖሊስ ኮሌጅ በቡልቡላ ማሰልጠኛ ማዕከል ለ30ኛ ዙር ያሰለጠናቸውን ልዩ የፖሊስ ኃይል አባላትን ከፍተኛ የመንግሥት ባለሥልጣናት በተገኙበት በዛሬው ዕለት አስመርቋል።

በምረቃ ሥነ-ሥርዓቱ ላይ የተገኙት የኦሮሚያ ክልላዊ መንግሥት ፕሬዚዳንት አቶ ሽመልስ አብዲሳ፣ "በዚህ ሀገር ውስጥ ሁሉም ብሔር ብሔረሰቦች በእኩልነት፣ በነፃነት እና በሰላም ከወንድም የኦሮሞ ሕዝብ ጋር እንዲኖሩ ለማድረግ ሁላችንም ከፍተኛ ኃላፊነት አለብን፤ በተለይ ደግሞ እናንተ ልዩ ኃላፊነት አለባችሁ" ሲሉ ለተመራቂዎቹ መልእክት አስተላልፈዋል።

ተመራቂ ፖሊሶቹ ኃላፊነታችውን ሕግ እና ሥርዓትን እንዲሁም የሕዝብ ፍላጎትን መሠረት አድርገው ሊወጡ እንደሚገባም አሳስበዋል።የኦሮሚያ ፖሊስ የኦሮሚያን ሰላም ከማስጠበቅ ባሻገር ማንኛውንም በኢትዮጵያ ላይ የሚቃጣ አደጋን መመከት ይገባዋልም ብለዋል። ኦሮሚያን ለመገንባት እና ኢትዮጵያን ለማሻገር የድርሻቸውን እንዲወጡ ለተመራቂዎቹ ጥሪ አስተላልፈዋል።

Via ETV/OBN
@YeneTube @FikerAssefa
All women functioned flight ceremony in pictures
ዛሬ በአዲስ አበባ የስብሰባ አዳራሽ እናት ፓርቲ ተመስርቷል

በጠቅላላ ጉባኤ የተመረጡ የእናት ፓርቲ አመሬሮች

የፓርቲው አመራሮች⬇️

-ፕሬዝደንት፡ ዶ/ር ኃ/ኢየሱስ ሙሉቀን

-ም/ፕሬዝደንት፡ ዶ/ር ሠይፈሥላሴ አያሌው

-ጠቅላይ ፀሐፊ፡ አቶ ጌትነት ወርቁ

መሆናቸውን ለማወቅ ችለናል።
@Yenetube @Fikerassefa