YeneTube
118K subscribers
31.5K photos
485 videos
79 files
3.88K links
መረጃዎችን ለመላክ @Fikerassefa
Download Telegram
የአውሮፓያውያን አዲስ አመት 2020 በዓለም ዙሪያ በተለያዩ ክብረ በዓሎች፤ የርችት ተኩስ ትዕይንቶች እየተከበረ ነው።

ከሀገር ውጪ ያላችሁ የቻናላችን ቤተሰቦች እንኳን 2020 በሰላም አደረሳችሁ!!
ፎቶ፦ ሮይተርስ
@YeneTube @FikerAssefa
ብሩህ ቀን ይሁንላችሁ | ገጠሩ የሀገራችን ክፍል

- ከሰሜን እስከ ደቡብ ከምስራቅ እስከ ምዕራብ ብንጓዝ ገጠሩ የሀገራችን ክፍል ከዚህ ፎቶ ጋር ተመሳሳይነት አለሁ እኛ ኢትዮጵያዊያን ከልዩነታችን በላይ የሚያመሳስለን ይበልጣል።

-እንደለመድነው ዜናዎችን ሳይበርዱ ለናንተ እናደርሳለን።

- የኔቲዩብ ለጓደኟዎ መጋበዝ መቼም አይርሱ

በድጋሜ መልካም ቀን ተመኘንላችሁ አብራችሁን ቆዮ።

💚💛❤️ t.me/YeneTube 💚💛❤️
የመንግሥት ሠራተኞች የውሎ አበል መመሪያ ይሻሻል!

በመንግሥትም ይሁን በግል ተቋማት አንድ ሰራተኛ ከስራው ቦታ ወደ ሌላ አካባቢ አልያም ቢሮ ተንቀሳቅሶ እንዲሰራ ሲፈለግ የትራንስፖርት፣ የምግብና የማደሪያ ወጪውን ሊሸፍንለት የሚችል የውሎ አበል ይታሰብለታል። ይህ አሰራር በተለይ በግል ተቋማትና መንግስታዊ ባልሆኑ ድርጅቶች አካባቢ የተሻለ ገጽታ ቢኖረውም ወደ መንግስት ሰራተኞች ስንመጣ ግን አንዳንድ ጊዜ ‹‹እንዲህም ይኖራል›› ወይ የሚያሰኝ ሆኖ እናገኘዋለን።ከሐምሌ 1ቀን 2004 ዓ.ም ጀምሮ ስራ ላይ የዋለው የመንግስት ሠራተኞች የቀን ውሎ አበል መመሪያ እንደሚያመለክተው የመንግሥት ሠራተኛው በየትኛውም ክልል ሄዶ ቢሰራ ከፍተኛ ደመወዝ አለው የሚባለው 225 ብር የሚታሰብለት ሲሆን፤ አነስተኛ ደመወዝ ተከፋይ ነው የሚባለው ደግሞ በቀን የሚያገኘው 111 ብር ነው።

Via EPA
@YeneTube @FikerAssefa
"በአሁኑ ወቅት ለጡረተኞች የሚከፈለው ዝቅተኛ ወርሀዊ ክፍያ 1,258 ብር ሲሆን ትልቁ ደግሞ 153,000 ይደርሳል"--- የመንግሥት ሠራተኞች ማህበራዊ ዋስትና ኤጀንሲ

- በሀገሪቱ ለሚገኙ 750,000 የሚደርሱ ጡረተኞች በዓመት ከስድስት ቢሊዮን ብር በላይ ይከፈላል

- የማህበራዊ ዋስትና ሽፋን ካላቸው 2.1 ሚሊዮን ዜጎች በአመት አስራ ሁለት ቢሊዮን ብር እየተሰበሰበ ነው

- ከፍተኛ የጡረታ አበል የሚከፈላቸው ዜጎች ቁጥር አነስተኛ ሲሆን ከነዚህ ውስጥ ካፕቴኖች ይጠቀሳሉ

Via:- Ethiopian Press
@YeneTube @Fikerassefa
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በቻይና መንግስት ድጋፍ በሸራተን አካባቢ እየተገነባ ያለውን የወንዞች ዳርቻና አረንጓዴ ልማት አካል የሆነውን ፕሮጀክት እየጎበኙ ነው።

@YeneTube @Fikerassefa
በምዕራፍ ሱዳን ዳርፋር 16 ሰዎችን በታጣቂዎች ተገደሉ እንዲህም 12 ሰዎችን ታጣቂዎች ማቁሰላቸውን የአይን እማኞችን ጠቅሶ ሰቬንዲ ኒዊስ ዘግቧል።

Via:- Al Ain
@YeneTube @Fikerassefa
ጂማ ዩንቨርስቲ ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት ተማሪዎች በሙሉ⬆️
HOPE EDUCATIONAL CONSULTANT


YOUR FUTURE - OUR MISSION


🇹🇷 Türkiye'de eğitim🇹🇷


🔔አስደሳች ዜና በ ቱርክ ሀገር የትምህርት እድል ፈላጊዎች በሙሉ 🔔

በቱርክ ሀገር ዋና ከተማ ISTANBUL🌆

📜BACHELOR DEGREE AND MASTERS DEGREE

🔶ልዩ የ ትምህርት እድል ፈጣን እና በአጭር ጊዜ የሚጠናቀቅ process

🔶በመሆኑ በ ተመጣጣኝ ዋጋ የምናገለግል ስለሆነ ፈጥነው ቦታዎን ይያዙ

🔶ድርጅታችን የ ረጅም ጊዜ ልምድ ስላለው በ አገልግሎታችን ይኮራሉ

📚 DOCUMENTS
PASSPORT
HIGH SCHOOL CERTIFICATE
TRANSCRIPTS
PHOTO
BANK STATEMENT (250,000 &Above )


የ አገልግሎታችን ተጠቂሚ ስለሆኑ እናመሰግናለን

OLARAK SEÇME İÇİN TEŞEKKÜRLER

Channel link: https://tttttt.me/HopeEducationalConsulants

Contact as :
Telegram:@Abditade
Tel :+8613088257750 ( IMO ,what’s up)
WeChat ID :AbdiTade
Email:abditade54@gmail.com
1
በመተማ ወረዳ በመቃ ቀበሌ የሰሌዳ ቁጥሩ መከ 02488 የሆነ የመከላከያ ኦራል ተገልብጦ በንብረትና በሰው ህይወት ላይ አደጋ ደረሰ

ከባቢ በመቃ ቀበሌ ወደ ገንዳውሃ ከተማ ሲጓዝ እያለ ድንገት መስመሩ ላይ ላም በመግባቷ ላሚቱን አድናለሁ በሚል እሳቤ ኦራሉ በመገልበጡ ሹፌሩና ሌላ አንድ ጓድ ሲሞቱ ሁለቱ ደግሞ ከባድ የአካል ግዳት ደርሶባቸዋል፡፡

@YeneTube @Fikerassefa
በአንፆኪያ ገምዛ ወረዳ በደረሰ የመኪና መገልበጥ አደጋ ሁለት ሰዎች ወዲያው ህይወታቸው ሲያልፍ በአስራ አራት ሰዎች ከባድና ቀላል ጉዳት ደርሶባቸዋል፡፡

የወረዳው ፖሊስ ጽ/ቤት የወንጀል ምርመራ ዋና የስራ ሂደት ባለቤት ኮማንደር የሺ አሰፋ እንደገለፁት በሰ/ሸዋ ዞን በአንፆኪያ ገምዛ ወረዳ በትናንትናው እለት ኮድ 3-አአ 23637 ደረቅ አይሱዙ የጭነት መኪና 12፡30 መነሻውን በወረዳው ዋና ከተማ መኮይ መዳረሻውን ግሼ ራቤል በማድረግ የተለያዩ ሸቀጦችን የጫነ ሲሆን ከሸቀጡ በተጨማሪ ከሀያ በላይ ሰዎችን ጭኖ ስለነበር በጉዞ ላይ እያለ በወረዳው በመቅደሳ ቀበሌ ልዩ ስሙ አሮሬሳ ኮፎ ከተባለው ቦታ ሲደርስ ወደ ኋላ በመንሸራተት ሊገለበጥ ችሏል፡፡

በዚህም ሁለት ሰዎች ህይወታቸው ወዲያው ሲያልፍ በአስራ አራት ሰዎች ላይ ከባድና ቀላል ጉዳት በመድረሱ ተጎጂዎቹ በአሁኑ ሰዓት በኬሚሴ ሆስፒታል ህክምና በመውሰድ ላይ ይገኛሉ፡፡
@YeneTube @Fikerassefa
አሜሪካ ባግዳድ የሚገኘው ኤምባሲዋ በሰልፈኞች ጥቃት ከደረሰበት በኋላ ተጨማሪ ወታደሮችን ወደ መካከለኛው ምስራቅ ልታሰማራ መሆኑን አስታውቃለች።

አሜሪካ ባሳለፍነው እሁድ ዕለት በኢራን እንሚደገፉ በሚነገርላቸው እና በኢራቅ በሚንቀሳቀሱ የሂዝቦላህ ታጣቂዎች ላይ በፈጸመችው የአየር ጥቃት 25 የቡድኑ አባላት ህይወት ማለፉ ይታወሳል።

@YeneTube @Fikerassefa
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
በቡታጅራ ማረሚያ ቤት ታስረው የሚገኙ ተጠርጣሪዎች ህግ በሚፈቅደው ጊዜ ውስጥ ወደ ፍርድ ቤት እየቀረቡ አለመሆኑ ተገለጸ፡፡
@YeneTube @Fikerassefa
የፈረንጆቹን 2020 አስመልክቶ ኦነግ (ABO) ለኦሮሞ ህዝብ ; ለአባላቶቹ እንዲሁም ለደጋፊዎች ያስተላለፈው መልክት።

https://telegra.ph/ABO-01-01
"የኢትዮጵያ አየር መንገድ የሞባይል መተግበርያ (mobile app) ባለፈው ዘጠኝ ወር ብቻ የሁለት ቢልየን ብር ሽያጭ ተከናውኖበታል።"

Via:- BusinessInfoEth
@YeneTube @Fikerassefa
በአፋር እና በሱማሌ ክልል መካከል ያለውን ግጭት ለመፍታት በተካሄደ የምክክር ላይ የቀረበ የአቋም መግለጫ

👇👇👇👇👇
https://telegra.ph/AfarSomali-01-01
በኦሮሚያ በመሰራት ላይ ካሉ 27 የመንገድ ፕሮጀክቶች መካከል 9ኙ ዘንድሮ እንደሚጠናቀቁ ተገለጸ!

በኦሮሚያ ክልል 9.5 ቢሊዮን ብር ተመድቦላቸው በመሰራት ላይ ካሉ 27 የመንገድ ፕሮጀክቶች መካከል 9ኙ ዘንድሮ እንደሚጠናቀቁ የኦሮሚያ መንገዶች ባለስልጣን አስታወቀ፡፡
የባለስልጣን መስሪያ ቤቱ ዋና ዳይሬክተር አቶ ደጀኔ ፍቃዱ እንደገለፁት በክልሉ የተለያዩ የመንገድ ፕሮጀክቶች እየተከናወኑ እንዳሉ ጠቁመው በ2012 ዓ.ም ብቻ ለ23 አዳዲስ ፕሮጀክቶች 5.4 ቢሊዮን ብር በጀት ተመድቦላቸዋል።

Via EPA
@YeneTube @FikerAssefa
የጥላቻ ንግግር እና የሃሰተኛ መረጃ ስርጭትን ለመከላከል እና ለመቆጣጠር በወጣው ረቂቅ አዋጅ ላይ የህግ ፍትህ እና ዲሞክራሲ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ከባለ ድርሻ አካላት ጋር ውይይት አደረገ፡፡

👇👇👇👇👇
https://telegra.ph/HateSpeech-01-01
📌አስቸኳይ ማስታወቂያ ለወለጋ ዩንቨርስቲ ተማሪዎች በሙሉ
@YeneTube @Fikerassefa
በጊምቢ ወረዳ በተሽከርካሪ አደጋ የ13 ሰዎች ህይወት አለፈ!!

በምዕራብ ወለጋ ዞን ጊምቢ ወረዳ ዛሬ ከረፋዱ አምስት ሰዓት አካባቢ በደረሰ የተሽከርካሪ አደጋ የ13 ሰዎች ሕይወት ማለፉን ፖሊስ አስታወቀ።

በወረዳው ጆብር ቀበሌ ልዩ ስሙ  ቡሉል በተባለ ስፍራ የደረሰው ይሄው አደጋ የታርጋ ቁጥር ኮድ 3- 42548 ኦሮ ዶልፊን የህዝብ ማመላለሻ ከነቀምቴ ወደ ጊምቢ ከሚጓዝ የታርጋ ቁጥር ኮድ 3- 58995 ኢት  ከሆነ ተሳቢ የጭነት ተሽከርካሪ ጋር በመጋጨቱ ነው።

በዞኑ ፖሊስ  የትራፊክ ዲቭዥን ኃላፊ  ሳጅን ጋጃሳ አሰፋ እንዳሉት በአደጋው  12 ሰዎች ወዲያውኑ ሲሞቱ አንድ ሰው ደግሞ ጊምቢ ከተማ አድቨንትስት ሆስፒታል ለህክምና ከደረሰ በኋላ ህይወቱ አልፏል።

ህይወታቸው ካለፈው መካከል አስር ወንዶችና ቀሪዎቹ ሴቶች ሲሆኑ ከነዚህም የዶልፊኑ አሽከርካሪና  ረዳቱም ይገኙበታል። የጭነት ተሽከርካሪው ሾፌር  እጁን ለፖሊስ መስጠቱን ሳጅን ጋጃሳ አመልክተዋል።

የጊምቢ ከተማ አድቨንትስት ሆስፒታል ሜዲካል ዳይሬክተር ዶክተር ፍራፍያድ ጉደታ እንደተናገሩት በአደጋው ህይወታቸው ካለፈው ሌላ ስምንት ሰዎች ከበድና ቀላል የአካል ጉዳት ደርሶባቸው የህክምና እርዳታ እየተደረገላቸው ነው። ከእነዚህም ሶስት ሰዎች በአስጊ ሁኔታ ውስጥ እንደሚገኙ አመልክተዋል።

Via:- ENA
@YeneTube @Fikerassefa