«አቶ ጀዋር መሐመድ ኦፌኮን በአባልነት መቀላቀላቸው ዛሬ የተፈጠረ ሳይኾን ለረዥም ጊዜ ፓርቲውን ሲደግፉ ከቆዩ በኋላ የተፈጸመ ነው»
ፕሮፌሰር መረራ ጉዲና ለOBN Oromiyaa ከተናገሩት የተወሰደ
@YeneTube @FikerAssefa
ፕሮፌሰር መረራ ጉዲና ለOBN Oromiyaa ከተናገሩት የተወሰደ
@YeneTube @FikerAssefa
ታህሳስ 9 ቀን ከጠገዴ ወረዳ ከብት በመጠበቅ ላይ በነበሩበት ወቅት በታጣቂዎች ከታገቱ 8 ታዳጊዎች መካከል 6ቹ በአጋቾቻቸው መገደላቸው ተነገረ። ታዳጊዎቹ የተገደሉት አጋቾች በአንድ ሰው የጠየቁትን 100ሺህ ብር ወላጆች መክፈል ባለመቻላቸው ነው።
ከ8-15 ዕድሜ ክልል ውስጥ የሚገኙት ታደጊዎች ከጠገዴ ወረዳ ዳውጨና ቀበሌ ወደ ታች አርማጭሆ ወረዳ ከተወሰዱ በኅላ በትናንትናው ዕለት ነበር በጥይት ተመተው የተገደሉት። ከሟቾቹ መካከል የ4ቱ አስከሬን አሰሳ በሚያደርጉ የመንግስት ሚኒሻዎች ተገኝቷል።
@YeneTube @FikerAssefa
ከ8-15 ዕድሜ ክልል ውስጥ የሚገኙት ታደጊዎች ከጠገዴ ወረዳ ዳውጨና ቀበሌ ወደ ታች አርማጭሆ ወረዳ ከተወሰዱ በኅላ በትናንትናው ዕለት ነበር በጥይት ተመተው የተገደሉት። ከሟቾቹ መካከል የ4ቱ አስከሬን አሰሳ በሚያደርጉ የመንግስት ሚኒሻዎች ተገኝቷል።
@YeneTube @FikerAssefa
አንጀሊና ጆሊ ከፕሬዝደንት ሣህለ ወርቅ ዘውዴ ጋር ውይይት አድርጋለች፡፡
እሁድ አዲስ አበባ የገባችው አንጀሊና ጆሊ በብሄራዊ ቤተመንግስት ከፕሬዝደንቷ ጋር በልማት፣ በሴቶች እና በስደተኞች ጉዳይ ላይ የሀሳብ ልውውጥ አድርጋለች፡፡በዚህም ወቅት ፕሬዝደንት ሣህለ ወርቅ "የአንጀሊና ጆሊ ጉብኝት ኢትዮጵያ በአስገራሚ የለውጥ ጎዳና ላይ ባለችበትና የሴቶችን ጉዳይ ጨምሮ በሁሉም መስኮች አዲስ ምዕራፍ እየተከፈተ ባለበት ወቅት የተደረገ በመሆኑ ጉብኝቱ ስለ ኢትዮጵያ ብቻ ሳይሆን ስለ አፍሪካ ያለውን አተያይና አስተሳሰብ ለመለወጥ የማይናቅ አስተዋፅዎ አለዉ፡፡" ብለዋል በሰብዐዊ ስራዎቿ የምታወቀው አንጀሊና በበኩሏ "ወደኢትዮጵያ የመጣሁት በህጻናትና ሴቶች እንዲሁም ጤና ላይ መስራት የሚቻልባቸውን እድሎች ለማየት ነው" ብላለች::አንጀሊና ወደ ኢትዮጵያ የመጣችዉ ከልጆቿ ጋር ሲሆን ከእነርሱም መካከል የ14 አመቷ ዘሃራ በትውልድ ኢትዮጵያዊት ነች።
ምንጭ: የፕሬዝዳንት ጽ/ቤት
@YeneTube @FikerAssefa
እሁድ አዲስ አበባ የገባችው አንጀሊና ጆሊ በብሄራዊ ቤተመንግስት ከፕሬዝደንቷ ጋር በልማት፣ በሴቶች እና በስደተኞች ጉዳይ ላይ የሀሳብ ልውውጥ አድርጋለች፡፡በዚህም ወቅት ፕሬዝደንት ሣህለ ወርቅ "የአንጀሊና ጆሊ ጉብኝት ኢትዮጵያ በአስገራሚ የለውጥ ጎዳና ላይ ባለችበትና የሴቶችን ጉዳይ ጨምሮ በሁሉም መስኮች አዲስ ምዕራፍ እየተከፈተ ባለበት ወቅት የተደረገ በመሆኑ ጉብኝቱ ስለ ኢትዮጵያ ብቻ ሳይሆን ስለ አፍሪካ ያለውን አተያይና አስተሳሰብ ለመለወጥ የማይናቅ አስተዋፅዎ አለዉ፡፡" ብለዋል በሰብዐዊ ስራዎቿ የምታወቀው አንጀሊና በበኩሏ "ወደኢትዮጵያ የመጣሁት በህጻናትና ሴቶች እንዲሁም ጤና ላይ መስራት የሚቻልባቸውን እድሎች ለማየት ነው" ብላለች::አንጀሊና ወደ ኢትዮጵያ የመጣችዉ ከልጆቿ ጋር ሲሆን ከእነርሱም መካከል የ14 አመቷ ዘሃራ በትውልድ ኢትዮጵያዊት ነች።
ምንጭ: የፕሬዝዳንት ጽ/ቤት
@YeneTube @FikerAssefa
era vacancy.pdf
91 KB
ዛሬ የወጣ የስራ ማስታወቂያ የኢትዮጵያ መንገዶች ባለስልጣን የውጭአመልካቾችን አወዳድሮ በቋሚነት ለመቅጠር ይፈልጋል ።
91ኪሎ ባይት ናት download አድርጋችሁ በውስጡ ብዙ የዝራ ዝርዝር አለ ተመልከቱት።
@YeneTube @fikerassefa
91ኪሎ ባይት ናት download አድርጋችሁ በውስጡ ብዙ የዝራ ዝርዝር አለ ተመልከቱት።
@YeneTube @fikerassefa
በአምቦ ዩኒቨርሲቲ በተማሪዎችና በፀጥታ ኃይሎች መካከል በተፈጠረ ግጭት ጉዳት ደረሰ!
በድሬዳዋ ዩኒቨርስቲ የአንድ ተማሪ ህይወት ማለፉን ተከትሎ በአምቦ ዩኒቨርሲቲም በተማሪዎችና በፀጥታ ኃይሎች መካከል በተፈጠረ ግጭት አሥር ተማሪዎችና ሦስት የፀጥታ አካላት መቁሰላቸውን የዩኒቨርሲቲው ሪፈራል ሆስፒታል ገለፀ። የሣይንስና ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ሚኒስቴር "አለመረጋጋት ተፈጥሮባቸው ከነበሩ 22 ዩኒቨርስቲዎች ከ7 ውጭ ሌሎቹ ተረጋግተዋል" ብሏል።የቀሩትም ተረጋግተው ወደ ቀድሞ የመማር ማስተማር ሂደት እንዲመለሱ የኅብረተሰቡን ትብብር ጠይቋል።
Via VOA
@YeneTube @FikerAssefa
በድሬዳዋ ዩኒቨርስቲ የአንድ ተማሪ ህይወት ማለፉን ተከትሎ በአምቦ ዩኒቨርሲቲም በተማሪዎችና በፀጥታ ኃይሎች መካከል በተፈጠረ ግጭት አሥር ተማሪዎችና ሦስት የፀጥታ አካላት መቁሰላቸውን የዩኒቨርሲቲው ሪፈራል ሆስፒታል ገለፀ። የሣይንስና ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ሚኒስቴር "አለመረጋጋት ተፈጥሮባቸው ከነበሩ 22 ዩኒቨርስቲዎች ከ7 ውጭ ሌሎቹ ተረጋግተዋል" ብሏል።የቀሩትም ተረጋግተው ወደ ቀድሞ የመማር ማስተማር ሂደት እንዲመለሱ የኅብረተሰቡን ትብብር ጠይቋል።
Via VOA
@YeneTube @FikerAssefa
ድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ በቅርቡ ትምህርት እንደሚጀምር የሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር አስታወቀ፡፡
ከሰሞኑ በድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ አንድ የሶስተኛ አመት ተማሪ ህይወቱ ማለፉን ተከትሎ ዩኒቨርሲቲው ከትናነት ጀምሮ ላልተወሰነ ጊዜ የመማር ማስተማር ስራውን ማቋረጡን ማስታወቁ ይታወሳል፡፡ይህንን ውሳኔ ተከትሎም ተማሪዎች ጊቢውን ለቀው እንዲወጡ ሁነዋል፡፡ኢትዮ ኤፍ ኤም ለመሆኑ የዩኒቨርሲቲው የመዘጋት ውሳኔ እስከ መቼ ድረስ ሊቀጥል ይችላል ሲል የሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴርን ጠይቋል፡፡የሚኒስትሩ የህዝብ ግንኙነት ሃላፊ አቶ ደቻሳ ጉርሙ በአሁኑ ሰዓት ከድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ በስተቀር ሁሉም የመንግስት ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በማስተማር ስራቸው ላይ ናቸው፤ ድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲም እንዲዘጋ የወሰነው ጊዜያዊ ችግሮች እስከሚፈቱ ድረስ እንጂ አመቱን ሙሉ አይደለም ብለዋል፡፡
Via Ethio FM
@YeneTube @FikerAssefa
ከሰሞኑ በድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ አንድ የሶስተኛ አመት ተማሪ ህይወቱ ማለፉን ተከትሎ ዩኒቨርሲቲው ከትናነት ጀምሮ ላልተወሰነ ጊዜ የመማር ማስተማር ስራውን ማቋረጡን ማስታወቁ ይታወሳል፡፡ይህንን ውሳኔ ተከትሎም ተማሪዎች ጊቢውን ለቀው እንዲወጡ ሁነዋል፡፡ኢትዮ ኤፍ ኤም ለመሆኑ የዩኒቨርሲቲው የመዘጋት ውሳኔ እስከ መቼ ድረስ ሊቀጥል ይችላል ሲል የሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴርን ጠይቋል፡፡የሚኒስትሩ የህዝብ ግንኙነት ሃላፊ አቶ ደቻሳ ጉርሙ በአሁኑ ሰዓት ከድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ በስተቀር ሁሉም የመንግስት ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በማስተማር ስራቸው ላይ ናቸው፤ ድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲም እንዲዘጋ የወሰነው ጊዜያዊ ችግሮች እስከሚፈቱ ድረስ እንጂ አመቱን ሙሉ አይደለም ብለዋል፡፡
Via Ethio FM
@YeneTube @FikerAssefa
ለስልኮች የፊት ገጽ ማጠንከሪያ ተብሎ አገልግሎት ላይ እየዋለ ያለው የናኖ ቴክኖሎጂ ፈሳሽ ተፈትሾ ችግር አልተገኘበትም ብሏል የኢትዮጵያ ጨረራ መከላከያ ባለሥልጣን
ለስልኮች የፊት ገጽ ማጠንከሪያ ተብሎ አገልግሎት ላይ እየዋለ ያለው የናኖ ቴክኖሎጂ ፈሳሽ ተፈትሾ በሰው፣ በአካባቢ እና በንብረት ላይ ጉዳት የማያስከትል ስለመሆኑ መረጋገጡን የኢትዮጵያ ጨረራ መከላከያ ባለሥልጣን አስታወቀ፡፡የኢትዮጵያ ጨረራ መከላከያ ባለሥልጣን የሕዝብ ግንኙነት ሓላፊ አቶ አወቀ ሺፈራው በተለይ ለኢቲቪ እንደገለፁት መሥሪያ ቤታቸው በደረሰው ጥቆማ መሠረት ለስልኮች የፊት ገጽ ማጠንከሪያ ተብሎ አገልግሎት ላይ እየዋለ ያለው የናኖ ቴክኖሎጂ ፈሳሽ ላይ ፍተሻ አድርገዋል።
በመሥሪያ ቤቱ ባለሞያዎች በተደረገ ምርመራ ስልኮች ላይ የሚቀባው ፈሳሽ ምንም ዓይነት ጨረራ የማያመነጭ እና ችግር የማያስከትል ስለመሆኑ አመልክተዋል።የናኖ ፈሳሽ ቴክኖሎጂውን የተለያዩ አስመጪዎች ወደ አገር ውስጥ እንደሚያስገቡት የጠቆሙት፣ አቶ አወቀ መሥሪያ ቤታቸው አስመጪዎች ማናቸውም ዕቃዎች ከውጭ ማስገባታቸውን ለተቋማቸው ሲያሳውቁ ብቻ ፍተሻ የሚያደርጉ መሆኑን ከዚህ ባለፈ ግን ወጪ እና ገቢ ዕቃዎችን የሚመለከተው ገቢዎች ባለሥልጣን እንደሆነ በአጽንኦት ተናግረዋል።
ምንጭ: ኢቲቪ
@YeneTube @FikerAssefa
ለስልኮች የፊት ገጽ ማጠንከሪያ ተብሎ አገልግሎት ላይ እየዋለ ያለው የናኖ ቴክኖሎጂ ፈሳሽ ተፈትሾ በሰው፣ በአካባቢ እና በንብረት ላይ ጉዳት የማያስከትል ስለመሆኑ መረጋገጡን የኢትዮጵያ ጨረራ መከላከያ ባለሥልጣን አስታወቀ፡፡የኢትዮጵያ ጨረራ መከላከያ ባለሥልጣን የሕዝብ ግንኙነት ሓላፊ አቶ አወቀ ሺፈራው በተለይ ለኢቲቪ እንደገለፁት መሥሪያ ቤታቸው በደረሰው ጥቆማ መሠረት ለስልኮች የፊት ገጽ ማጠንከሪያ ተብሎ አገልግሎት ላይ እየዋለ ያለው የናኖ ቴክኖሎጂ ፈሳሽ ላይ ፍተሻ አድርገዋል።
በመሥሪያ ቤቱ ባለሞያዎች በተደረገ ምርመራ ስልኮች ላይ የሚቀባው ፈሳሽ ምንም ዓይነት ጨረራ የማያመነጭ እና ችግር የማያስከትል ስለመሆኑ አመልክተዋል።የናኖ ፈሳሽ ቴክኖሎጂውን የተለያዩ አስመጪዎች ወደ አገር ውስጥ እንደሚያስገቡት የጠቆሙት፣ አቶ አወቀ መሥሪያ ቤታቸው አስመጪዎች ማናቸውም ዕቃዎች ከውጭ ማስገባታቸውን ለተቋማቸው ሲያሳውቁ ብቻ ፍተሻ የሚያደርጉ መሆኑን ከዚህ ባለፈ ግን ወጪ እና ገቢ ዕቃዎችን የሚመለከተው ገቢዎች ባለሥልጣን እንደሆነ በአጽንኦት ተናግረዋል።
ምንጭ: ኢቲቪ
@YeneTube @FikerAssefa
አባይ ባንክ ከኢትዮጵያ አየር መንገድ ጋር የዲጂታል ክፍያ መላዎችን ጀመርኩ አለ፡፡
ባንኩ ከአየር መንገዱ ጋር የዲጂታል ክፍያ ሥርዓት መላዎችን አስመልክቶ ከኢትዮጵያ አየር መንገድ የስራ ሀላፊዎች ጋር ተፈራርሟል፡፡ለዚሁ መላ የባንኩ ደንቦች በኦንላይን ባንኪንግ በመጠቀም ትኬት መቁረጥ ይችላሉ፡፡ ሌሎችም አገልግሎቶችን ማግኘት ይችላሉ መባሉን ሰምተናል፡፡አባይ ባንክ አገልግሎቱን በጀመረ በአንድ ሳምንት ውስጥ 1 ሚሊየን ገደማ ጥሪት መንቀሳቀሱን የስራ ሀላፊዎች ተናግረዋል፡፡በተያያዘም፣ ይህንኑ አገልግሎት ከአማርኛ በተጨማሪ በሁለት የአገር ቤት ቋንቋዎች ማግኘት ይቻላል ተብሏል፡፡ የባንኩ የሞባይል ባንኪንግ ተጠቃሚዎች 125 000 የደረሰ ሲሆን አጠቃላይ የደንበኞቹ ቁጥርም 700 000 እንደደረሰ ሰምተናል፡፡
Via Sheger FM
@YeneTube @FikerAssefa
ባንኩ ከአየር መንገዱ ጋር የዲጂታል ክፍያ ሥርዓት መላዎችን አስመልክቶ ከኢትዮጵያ አየር መንገድ የስራ ሀላፊዎች ጋር ተፈራርሟል፡፡ለዚሁ መላ የባንኩ ደንቦች በኦንላይን ባንኪንግ በመጠቀም ትኬት መቁረጥ ይችላሉ፡፡ ሌሎችም አገልግሎቶችን ማግኘት ይችላሉ መባሉን ሰምተናል፡፡አባይ ባንክ አገልግሎቱን በጀመረ በአንድ ሳምንት ውስጥ 1 ሚሊየን ገደማ ጥሪት መንቀሳቀሱን የስራ ሀላፊዎች ተናግረዋል፡፡በተያያዘም፣ ይህንኑ አገልግሎት ከአማርኛ በተጨማሪ በሁለት የአገር ቤት ቋንቋዎች ማግኘት ይቻላል ተብሏል፡፡ የባንኩ የሞባይል ባንኪንግ ተጠቃሚዎች 125 000 የደረሰ ሲሆን አጠቃላይ የደንበኞቹ ቁጥርም 700 000 እንደደረሰ ሰምተናል፡፡
Via Sheger FM
@YeneTube @FikerAssefa
የከተማ አስተዳደሩ ከጥር 2 ጀምሮ በህገወጥ መልኩ የተገነቡ ቤቶች ላይ እርምጃ እንደሚወስድ አስታወቀ፡፡
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከጥር 2 ጀምሮ በህገወጥ መልኩ የተገነቡ ቤቶች ላይ እርምጃ እንደሚወስድ አስታውቋል፡፡ እርምጃው በተለይ በቅርብ ጊዚያት እየተስፋፋ የመጣውን የህገወጥ የመሬት ወረራ ለመከላከል ያለመ ነው ተብሏል፡፡ እርምጃው በአዲስ አበባ በሚገኙ 116 ወረዳዎች የሚወሰድ ሲሆን የአዲስ አበባ ፖሊስ፣ የፌደራል ፖሊስ፣ የኦሮሚያ ፖሊስና የከተማዋ አጎራባች ወረዳዎች በመቀናጀት እርምጃ እንደሚወስድ የከንቲባ ጽ/ቤት ባወጣው መረጃ ተገልጿል፡፡በየወረዳው በህገወጥ መልኩ የተገነቡ ቤቶችን የመለየት ስራም እየተሰራ ይገኛል ተብሏል፡፡በከተማዋ ባሉ ወረዳዎች ቦታዎቸን ለመያዝ በህገወጥ መልኩ እየታጠሩ እንደሆነና ከላስቲክ ቤቶች ጀምሮ የተለያዩ ህገወጥ ግንባታዎች እየተደረጉ እንደሆነ የተሰበሰቡት መረጃዎች መጠቆማቸው የገለጸው አስተዳደሩ በጉዳዩ ላይ መግለጫ እንደሚሰጥ አስታውቋል፡፡
Via Addis TV
Photo: ©YeneTube
@YeneTube @FikerAssefa
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከጥር 2 ጀምሮ በህገወጥ መልኩ የተገነቡ ቤቶች ላይ እርምጃ እንደሚወስድ አስታውቋል፡፡ እርምጃው በተለይ በቅርብ ጊዚያት እየተስፋፋ የመጣውን የህገወጥ የመሬት ወረራ ለመከላከል ያለመ ነው ተብሏል፡፡ እርምጃው በአዲስ አበባ በሚገኙ 116 ወረዳዎች የሚወሰድ ሲሆን የአዲስ አበባ ፖሊስ፣ የፌደራል ፖሊስ፣ የኦሮሚያ ፖሊስና የከተማዋ አጎራባች ወረዳዎች በመቀናጀት እርምጃ እንደሚወስድ የከንቲባ ጽ/ቤት ባወጣው መረጃ ተገልጿል፡፡በየወረዳው በህገወጥ መልኩ የተገነቡ ቤቶችን የመለየት ስራም እየተሰራ ይገኛል ተብሏል፡፡በከተማዋ ባሉ ወረዳዎች ቦታዎቸን ለመያዝ በህገወጥ መልኩ እየታጠሩ እንደሆነና ከላስቲክ ቤቶች ጀምሮ የተለያዩ ህገወጥ ግንባታዎች እየተደረጉ እንደሆነ የተሰበሰቡት መረጃዎች መጠቆማቸው የገለጸው አስተዳደሩ በጉዳዩ ላይ መግለጫ እንደሚሰጥ አስታውቋል፡፡
Via Addis TV
Photo: ©YeneTube
@YeneTube @FikerAssefa
የቀድሞው የኢትዮጵያ ፕሬዝዳንት ሙላቱ ተሾመ ከፕሬዝዳንት ሣህለ ወርቅ ዘውዴ እና ጠቅላይ ምኒስትር ዐቢይ አሕመድ የተፃፉ ሁለት ደብዳቤዎች ለሳዑዲ አረቢያው ንጉስ ሳልማን አቅርበዋል። ስለ ደብዳቤዎቹ ይዘት የተባለ ነገር የለም።
Via Eshete Bekele
@YeneTube @FikerAssefa
Via Eshete Bekele
@YeneTube @FikerAssefa
የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ ቃቃል አቀባይ ክርስቲያን ታደለን ጨምሮ በከፍተኛ የመንግስት ባለስልጣናት ግድያ የተጠረጠሩ ግለሰቦች ዛሬ ፍርድ ቤት የቀረቡ ሲሆን፣ ለጥር 08/2012 ተለዋጭ ቀጠሮ ተሰጥቶባቸዋል፡፡ችሎት ለመታደም የተገኙ ቤተሰብና ደጋፊዎቻቸው የተቃውሞ ድምጽ አሰምተዋል፡፡
Via Ethiopia Live Updates
@YeneTube @FikerAssefa
Via Ethiopia Live Updates
@YeneTube @FikerAssefa
የጠቅላይ ምኒስትር ዐቢይ አሕመድ አማካሪ ዳንኤል ክብረት ወደ ሊቢያ አቅንተው በዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ እውቅና ከተሰጠው መንግሥት የውጭ ጉዳይ ምኒስትር መሐመድ ሳያላ ጋር በሊቢያ መረጋጋት እና የሁለቱ አገሮች ግንኙነት ላይ ተወያይተዋል
Via Eshete Bekele
@YeneTube @FikerAssefa
Via Eshete Bekele
@YeneTube @FikerAssefa
የኦሮሚያ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት ካቢኔ በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ተወያይቶ ውሳኔ አሳልፏል።
ካቢኔው በዛሬው እለት ባካሄደው ስብሰባው የባሌ ዞን በሁለት ዞኖች እንደ አዲስ እንዲደራጅ እና በሌሎች ጉዳዮች ላይ ተወያይቶ ውሳኔ በማሳለፍ እንዲጸድቁ ለጨፌ ኦሮሚያ መርቷል። በዚህም መሰረት የክልሉ ፐብሊክ ሰርቪስና የሰው ሀብት ልማት ቢሮ ለካቢኔው ባቀረበው ጥናት በዞኑ ባለው የመሰረተ ልማት እና የቦታ መራራቅ ችግር የተነሳ አገልግሎት ፍጥነት ማቅረብ ባለመቻሉ ለረጅም ጊዜ የመልካም አስተዳደር ችግር ምንጭ ሆኖ መቆየቱን ጠቁሟል። ካቢኔው ጥናቱን መነሻ በማድረግ ውይይት ካካሄደ በኋላ የባሌ ዞን የነበረው፤ ምስራቅ ባሌ ዞን እና ምእራብ ባሌ ዞን ሆኖ እንደ አዲስ እንዲደራጅ በሙሉ ድምጽ ወስኗል።
የምእራብ ባሌ ዞን ዋና ከተማ ሮቤ እንዲሁም የምስራቅ ባሌ ዞን ዋና ከተማ ደግሞ ጊኒር እንዲሆን የቀረበው ምክረ ሀሳብም በሙሉ ድምጽ መጽደቁ ነው የተገለፀው።
በሌላ በኩል የክልሉ መንግስት ካቢኔ ባካሄደው ስብሰባ የኦሮሚያ ክልል የማዕድን ልማት አስተዳደርን ለመወሰን የቀረበ ረቂቅ አዋጅ እና የኦሮሚያ መንገዶች ፈንድን ለማቋቋም የቀረቡ ረቂቅ አዋጆች ላይ በስፋት ከተወያየ በኋላ ለጨፌ ኦሮሚያ እንዲቀርብ ውሳኔ አሳልፏል።
Via FBC
@YeneTube @FikerAssefa
ካቢኔው በዛሬው እለት ባካሄደው ስብሰባው የባሌ ዞን በሁለት ዞኖች እንደ አዲስ እንዲደራጅ እና በሌሎች ጉዳዮች ላይ ተወያይቶ ውሳኔ በማሳለፍ እንዲጸድቁ ለጨፌ ኦሮሚያ መርቷል። በዚህም መሰረት የክልሉ ፐብሊክ ሰርቪስና የሰው ሀብት ልማት ቢሮ ለካቢኔው ባቀረበው ጥናት በዞኑ ባለው የመሰረተ ልማት እና የቦታ መራራቅ ችግር የተነሳ አገልግሎት ፍጥነት ማቅረብ ባለመቻሉ ለረጅም ጊዜ የመልካም አስተዳደር ችግር ምንጭ ሆኖ መቆየቱን ጠቁሟል። ካቢኔው ጥናቱን መነሻ በማድረግ ውይይት ካካሄደ በኋላ የባሌ ዞን የነበረው፤ ምስራቅ ባሌ ዞን እና ምእራብ ባሌ ዞን ሆኖ እንደ አዲስ እንዲደራጅ በሙሉ ድምጽ ወስኗል።
የምእራብ ባሌ ዞን ዋና ከተማ ሮቤ እንዲሁም የምስራቅ ባሌ ዞን ዋና ከተማ ደግሞ ጊኒር እንዲሆን የቀረበው ምክረ ሀሳብም በሙሉ ድምጽ መጽደቁ ነው የተገለፀው።
በሌላ በኩል የክልሉ መንግስት ካቢኔ ባካሄደው ስብሰባ የኦሮሚያ ክልል የማዕድን ልማት አስተዳደርን ለመወሰን የቀረበ ረቂቅ አዋጅ እና የኦሮሚያ መንገዶች ፈንድን ለማቋቋም የቀረቡ ረቂቅ አዋጆች ላይ በስፋት ከተወያየ በኋላ ለጨፌ ኦሮሚያ እንዲቀርብ ውሳኔ አሳልፏል።
Via FBC
@YeneTube @FikerAssefa
ዜና ሹመት
ዶ/ር ጥላዬ ጌቱ በፓሪስ የኢፌድሪ ሚሲዮን በመደብ መታወቂያ ቁጥር 15አአ-1107 በባለሙሉ ስልጣን ሚኒስትር የስራ ደረጃ የዩኔስኮ ምክትል ቋሚ መልክተኛ ሆነው እንዲሰሩ ተውስኗል።
- መሉውን መረጃ ከፎቶው ላይ ያገኛሉ
@Yenetube @Fikerassefa
ዶ/ር ጥላዬ ጌቱ በፓሪስ የኢፌድሪ ሚሲዮን በመደብ መታወቂያ ቁጥር 15አአ-1107 በባለሙሉ ስልጣን ሚኒስትር የስራ ደረጃ የዩኔስኮ ምክትል ቋሚ መልክተኛ ሆነው እንዲሰሩ ተውስኗል።
- መሉውን መረጃ ከፎቶው ላይ ያገኛሉ
@Yenetube @Fikerassefa
የዳዉሮ ህዝብ በክልል የመደራጀት ጥያቄ መልስ ባለማግኘቱ የቅሬታ ጥያቄ ለፌደሬሽን ምክር ቤት ቀረበ!
የዳዉሮ ዞን ም/ቤት ታህሳስ 2/2011 ዓ.ም በክልል ለመደራጀት ያስተላለፈዉ ዉሳኔ ምላሽ ሳይሰጥ ለአንድ ዓመት በመዘግየቱ ምክንያት የፌደሬሽን ምክር ቤት ስልጣንና ኃላፊነት ለመግለፅ በወጣዉ አዋጅ ቁጥር 251/1993 አንቀጽ 2 እና 3ን መሰረት ያደረገ የዳዉሮ ህዝብ በክልል የመደራጀት ጥያቄ ምላሽ ያለማግኘቱ ቅሬታ ለፌደረሽን ም/ቤት ቀርቧል::ከታህሣስ 13 እስከ 15/2012 ዓ.ም አድስ አበባ በመቆየት ቅሬታዉን ለፌደሬሽን ም/ቤት ያቀረቡት የሃገር ሽማግሌዎች ፣ የኃይማኖት አባቶች የዞኑ ም/ቤት አባላት በፓርላማ የዳዉሮ ህዝብ ተወካዮቻችን ጋር በመሆን የዳዉሮ ህዝብ ዉሳኔ ተግባራዊ እንዲሆን መጠየቃቸዉን ገልጸዋል::
በዚህ ጉዞአቸዉ በዞኑ አንገብጋቢ የነበሩትን የመሠረተ ልማት ጥያቄዎችን ለሚንስቴር መ/ቤቶች ማንሳታቸዉንም ያብራሩት የዳዉሮ ህዝብ ተወካዮች፣ በዞኑ በሁሉም ወረዳ እና ታርጫ ከተማ ያለዉን የንጹህ መጠጥ ዉኃ ፣ የመንገድ እና የመብራት ችግር እንዲሁም የወላይታ ሶዶ ዩንቨርስቲ ታርጫ ካምፓስ ወደ ዩንቨርስቲ እንድያድግ ለየዘርፉ ሚንስትር መ/ቤቶች በተደራጀ መልኩ ማቅረባቸዉን በሪፖርቱ ገልጸዋል።እንደ ተወካዮቹ ገለጻ በክልል የመደራጀት ጥያቄ የፌደረሽን ም/ቤት የተቀበለ ሲሆን ምላሹ ከሌሎቹ ተመሳሳይ ዞኖች ጥያቄ ጋር አብሮ እንደሚታይ መገለፁንም አሣዉቀዋል።የመሠረተ ልማት ጥያቄዎችን በሚመለከትም ምላሹን በፓርላማ የዳዉሮ ተወካዮቻችን እና የዞኑ መንግስት እንዲከታተሉ መገለጹን አሣዉቀዋል::
ምንጭ:የዳዉሮ ዞን ህዝብ ግኑኝነት ጽ/ቤት
@YeneTube @FikerAssefa
የዳዉሮ ዞን ም/ቤት ታህሳስ 2/2011 ዓ.ም በክልል ለመደራጀት ያስተላለፈዉ ዉሳኔ ምላሽ ሳይሰጥ ለአንድ ዓመት በመዘግየቱ ምክንያት የፌደሬሽን ምክር ቤት ስልጣንና ኃላፊነት ለመግለፅ በወጣዉ አዋጅ ቁጥር 251/1993 አንቀጽ 2 እና 3ን መሰረት ያደረገ የዳዉሮ ህዝብ በክልል የመደራጀት ጥያቄ ምላሽ ያለማግኘቱ ቅሬታ ለፌደረሽን ም/ቤት ቀርቧል::ከታህሣስ 13 እስከ 15/2012 ዓ.ም አድስ አበባ በመቆየት ቅሬታዉን ለፌደሬሽን ም/ቤት ያቀረቡት የሃገር ሽማግሌዎች ፣ የኃይማኖት አባቶች የዞኑ ም/ቤት አባላት በፓርላማ የዳዉሮ ህዝብ ተወካዮቻችን ጋር በመሆን የዳዉሮ ህዝብ ዉሳኔ ተግባራዊ እንዲሆን መጠየቃቸዉን ገልጸዋል::
በዚህ ጉዞአቸዉ በዞኑ አንገብጋቢ የነበሩትን የመሠረተ ልማት ጥያቄዎችን ለሚንስቴር መ/ቤቶች ማንሳታቸዉንም ያብራሩት የዳዉሮ ህዝብ ተወካዮች፣ በዞኑ በሁሉም ወረዳ እና ታርጫ ከተማ ያለዉን የንጹህ መጠጥ ዉኃ ፣ የመንገድ እና የመብራት ችግር እንዲሁም የወላይታ ሶዶ ዩንቨርስቲ ታርጫ ካምፓስ ወደ ዩንቨርስቲ እንድያድግ ለየዘርፉ ሚንስትር መ/ቤቶች በተደራጀ መልኩ ማቅረባቸዉን በሪፖርቱ ገልጸዋል።እንደ ተወካዮቹ ገለጻ በክልል የመደራጀት ጥያቄ የፌደረሽን ም/ቤት የተቀበለ ሲሆን ምላሹ ከሌሎቹ ተመሳሳይ ዞኖች ጥያቄ ጋር አብሮ እንደሚታይ መገለፁንም አሣዉቀዋል።የመሠረተ ልማት ጥያቄዎችን በሚመለከትም ምላሹን በፓርላማ የዳዉሮ ተወካዮቻችን እና የዞኑ መንግስት እንዲከታተሉ መገለጹን አሣዉቀዋል::
ምንጭ:የዳዉሮ ዞን ህዝብ ግኑኝነት ጽ/ቤት
@YeneTube @FikerAssefa
በአማራ ክልል በደቡብ ወሎ ዞን ደላንታ ወረዳ ወገል ጤና ከተማ ሙስሊሞች በምስራቅ ጎጃም በሞጣ ከተማ በሙስሊሞች ላይ የተፈፀመውን ጥቃትና የመብት ጥሰት በመቃወም ሰላማዊ ሰልፍ አደረጉ።
@YeneTube @Fikerassefa
@YeneTube @Fikerassefa
#FakepageAlerts
ይህ ገፅ በየኔቲዩብ ስም የተከፈተ ቻናል ነው የተለያዩ ስህተት ያላቸው ዜናዎችን እያቀረበ ይገኛል ከወዲሁ የኛ ቻናል አለመሆኑ ለማሳወቅ እንወዳለን።
ትክክለኛውን የኔቲዩብን ለወዳጅ ዘመዶ በማስተዋውቅ ከውሸት ዜና እራስዎን እንዲሁም ቤተሰቦን ያርቁ።
እንዴት ለምታቁት ሰው መላክ እንደምትችሉ ከከበዳችሁ ጠይቁን!!
እናመሰግናለን!!
@YeneTube @Fikerassefa
ይህ ገፅ በየኔቲዩብ ስም የተከፈተ ቻናል ነው የተለያዩ ስህተት ያላቸው ዜናዎችን እያቀረበ ይገኛል ከወዲሁ የኛ ቻናል አለመሆኑ ለማሳወቅ እንወዳለን።
ትክክለኛውን የኔቲዩብን ለወዳጅ ዘመዶ በማስተዋውቅ ከውሸት ዜና እራስዎን እንዲሁም ቤተሰቦን ያርቁ።
እንዴት ለምታቁት ሰው መላክ እንደምትችሉ ከከበዳችሁ ጠይቁን!!
እናመሰግናለን!!
@YeneTube @Fikerassefa
ጃዋር ሞሐመድ የአሜሪካ ዜግነቱን ትቶ የኢትዮጵያ ዜግነቱን በማግኘት ሂደት ላይ መሆኑን ለአዲስ ስታዳርድ በሰጠው ቃለ ምልልስ ገልጧል፡፡ የኦሮሞ ሜዲያ ኔትወርክ ሥራ አስኪያጅነቱን ለሌላ #እያሰረከበ ነው፡፡
ከኦፌኮ ጋር #የረጅም_ጊዜ_ግንኙነት አለኝ ብሏል፡፡ ኦፌኮ ከኦነግ እና ሌሎች የኦሮሞ ፓርቲዎች ጋር በክልል እና ፌደራል ደረጃ ለመጭው ምርጫ #ቅንጅት ለመፍጠር ንግግር ጀምሯል፡፡
@YeneTube @Fikerassefa
ከኦፌኮ ጋር #የረጅም_ጊዜ_ግንኙነት አለኝ ብሏል፡፡ ኦፌኮ ከኦነግ እና ሌሎች የኦሮሞ ፓርቲዎች ጋር በክልል እና ፌደራል ደረጃ ለመጭው ምርጫ #ቅንጅት ለመፍጠር ንግግር ጀምሯል፡፡
@YeneTube @Fikerassefa
የብልጽግና ፓርቲ ስራ አስፈጻሚ ኮሚቴ የመጀመሪያ ስብሰባውን ሊያካሂድ ነው!
የብልፅግና ፓርቲ ስራ አስፈፃሚ ኮሚቴ የመጀመሪያ ስብሰባውን ሊያደርግ እንደሆነ ተሰምቷል። ፓርቲው የተለያዩ ወቅታዊና ሀገራዊ ጉዳይ ላይ የሚያካሄደው የመጀመሪያው ስብሰባ ከሰሞኑ ያካሂዳል ተብሎ ይጠበቃል።
©ማለዳ ሚድያ
@YeneTube @FikerAssefa
የብልፅግና ፓርቲ ስራ አስፈፃሚ ኮሚቴ የመጀመሪያ ስብሰባውን ሊያደርግ እንደሆነ ተሰምቷል። ፓርቲው የተለያዩ ወቅታዊና ሀገራዊ ጉዳይ ላይ የሚያካሄደው የመጀመሪያው ስብሰባ ከሰሞኑ ያካሂዳል ተብሎ ይጠበቃል።
©ማለዳ ሚድያ
@YeneTube @FikerAssefa