ለኢትዮጵያ የመሮጥ ፍላጎት ኖሮኝ አያውቅም። ኦሮሚያ ነጻ ካልወጣች በቀር" በማለት አትሌት ሲፈን ሃሰን ከቢቢሲ ጋር በነበራት ቆይታ ተናግራለች።ለኔዘርላንድስ የምትሮጠው ሲፈን በአሁኑ ወቅት በዓለም አትሌቲክስ የሴቶች አጠቃላይ የደረጃ ሰንጠረዥ አናት ላይ በአንደኛ ደረጃ ላይ ተቀምጣለች።
ከቢቢሲ ጋር ያደረገችው ሰፋ ያለ ቆይታ👇👇👇
https://telegra.ph/Sifan-12-07
ከቢቢሲ ጋር ያደረገችው ሰፋ ያለ ቆይታ👇👇👇
https://telegra.ph/Sifan-12-07
የጎንደር ዩኒቨርሲቲ “አንድ ተማሪ ለአንድ ቤተሰብ" ፕሮጀክት በይፋ ተጀመረ
የጎንደር ዩኒቨርሲቲ “አንድ ተማሪ ለአንድ ቤተሰብ" ፕሮጀክት ዛሬ በይፋ ተጀምሯል።
ዩኒቨርሲቲው በተያዘው አመት ለማስተማር የተቀበላቸውን 5 ሺህ ተማሪዎች ከጎንደር ከተማ ቤተሰቦቻቸው ጋር ዛሬ አስተዋውቋል።
የሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስትሯ ፕሮፌሰር ሂሩት ወልደማርያም እንደገለፁት፥ ይህን የኢትዮጵያዊነት ስሜት የሚያጠናክር ተግባር በመውሰድና በማሻሻል ፕሮጀክቱ በሌሎች ዩኒቨርሲቲዎች ተግባራዊ ይደረጋል።
የጎንደር ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት ዶክተር አስራት አፀደወይን ተማሪዎች ከእውቀት ግብይት ባለፈ በማህበራዊ ግንኙነታቸው ውጤታማ እንዲሆኑና ደህንነታቸው እንዲጠበቅ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል።
የጎንደር ከተማ ምክትል ከንቲባ ኢንጂነር ማስተዋል ስዩም በበኩላቸው፥ እንግዳ ተቀባይነትን ብቻ ሳይሆን ዝምድናን ማጠናከር ባህላችን ነው ብለዋል።
አያይዘውም ይህ የጎንደር የቤተሰብ ፕሮጀክት ውጤታማ እንዲሆን የበኩላችንን እንወጣለንም ነው ያሉት።
የቃል ኪዳን ልጆቻቸውን ለመረከብ በዚህ መርሃ ግብር ላይ የተገኙት ወላጆችም ተማሪዎቹ ትምህርታቸውን አጠናቀው እስከሚወጡ ድረስ ከጎናቸው በመሆን እንደሚንከባከቧቸው ተናግረዋል።
ወላጆች አያይዘውም የተረከቧቸውን የቃልኪዳን ልጆች በትምህርታቸው እንዲጠነክሩ ከማገዝ ባሻገር ስለ አብሮነትና አንድነት እንዲሁም የሀገር ፍቅር እንደሚያስተምሩም አውስተዋል።
በፕሮጀክቱ ከጎንደር ቤተሰብ ያገኙ ተማሪዎችም ሁለተኛ ወላጅ በማግኘታቸው ያለፍርሃትና ያለጭንቀት ትምህርታቸውን ተረጋግተው ለመማር እንደሚረዳቸው ገልጸዋል።
Via:- Fana
@Yenetube @Fikerassefa
የጎንደር ዩኒቨርሲቲ “አንድ ተማሪ ለአንድ ቤተሰብ" ፕሮጀክት ዛሬ በይፋ ተጀምሯል።
ዩኒቨርሲቲው በተያዘው አመት ለማስተማር የተቀበላቸውን 5 ሺህ ተማሪዎች ከጎንደር ከተማ ቤተሰቦቻቸው ጋር ዛሬ አስተዋውቋል።
የሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስትሯ ፕሮፌሰር ሂሩት ወልደማርያም እንደገለፁት፥ ይህን የኢትዮጵያዊነት ስሜት የሚያጠናክር ተግባር በመውሰድና በማሻሻል ፕሮጀክቱ በሌሎች ዩኒቨርሲቲዎች ተግባራዊ ይደረጋል።
የጎንደር ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት ዶክተር አስራት አፀደወይን ተማሪዎች ከእውቀት ግብይት ባለፈ በማህበራዊ ግንኙነታቸው ውጤታማ እንዲሆኑና ደህንነታቸው እንዲጠበቅ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል።
የጎንደር ከተማ ምክትል ከንቲባ ኢንጂነር ማስተዋል ስዩም በበኩላቸው፥ እንግዳ ተቀባይነትን ብቻ ሳይሆን ዝምድናን ማጠናከር ባህላችን ነው ብለዋል።
አያይዘውም ይህ የጎንደር የቤተሰብ ፕሮጀክት ውጤታማ እንዲሆን የበኩላችንን እንወጣለንም ነው ያሉት።
የቃል ኪዳን ልጆቻቸውን ለመረከብ በዚህ መርሃ ግብር ላይ የተገኙት ወላጆችም ተማሪዎቹ ትምህርታቸውን አጠናቀው እስከሚወጡ ድረስ ከጎናቸው በመሆን እንደሚንከባከቧቸው ተናግረዋል።
ወላጆች አያይዘውም የተረከቧቸውን የቃልኪዳን ልጆች በትምህርታቸው እንዲጠነክሩ ከማገዝ ባሻገር ስለ አብሮነትና አንድነት እንዲሁም የሀገር ፍቅር እንደሚያስተምሩም አውስተዋል።
በፕሮጀክቱ ከጎንደር ቤተሰብ ያገኙ ተማሪዎችም ሁለተኛ ወላጅ በማግኘታቸው ያለፍርሃትና ያለጭንቀት ትምህርታቸውን ተረጋግተው ለመማር እንደሚረዳቸው ገልጸዋል።
Via:- Fana
@Yenetube @Fikerassefa
ከ40 በላይ አለም አቀፍ ብራንድ ሆቴሎች በኢትዮጵያ ሰራ ለመጀመር መስመር ላይ ናቸው።
ከሆቴል አማካሪዎች ባገኘሁት መረጃ አዲስ አበባን ጨምሮ በኢትዮጵያ ባሉ ክልሎች ከ40 በላይ አለም አቀፍ ብራንድ ሆቴሎች አገልግሎታቸውን ለመስጠት ከነባር ሀገር በቀል እና አየተገነቡ ካሉ ሆቴሎች ጋር ድርድር ላይ መሆናቸውን ነግረውኛል።
Via Tesfaye Getnet
@YeneTube @FikerAssefa
ከሆቴል አማካሪዎች ባገኘሁት መረጃ አዲስ አበባን ጨምሮ በኢትዮጵያ ባሉ ክልሎች ከ40 በላይ አለም አቀፍ ብራንድ ሆቴሎች አገልግሎታቸውን ለመስጠት ከነባር ሀገር በቀል እና አየተገነቡ ካሉ ሆቴሎች ጋር ድርድር ላይ መሆናቸውን ነግረውኛል።
Via Tesfaye Getnet
@YeneTube @FikerAssefa
“እንደርሳለን” በሚል መሪ ቃል የህዳር ወር የትራፊክ አደጋን የመከላከልና የግንዛቤ ንቅናቄ የባለድርሻ አካላት መድረክ እየተካሄደ ነው።
መድረኩ በአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን አዳራሽ ነው እየተካሄደ የሚገኘው። የኢፌዴሪ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ ደመቀ መኮንን፣ የትራንሰፖርት ሚኒስትር ወይዘሮ ዳግማዊት ሞገስን ጨምሮ ሚኒስትሮችና ከፍተኛ የመንግሥት የስራ ኃላፊዎች እየተሳተፉ ይገኛል።በመድረኩ በ2011 ዓ.ም ብቻ ህይወታቸውን ላጡ 4 ሺህ 597 ሰዎች የህሊና ፀሎት ተደርጓል።
የዛሬው ምክክር የትራንስፖርት ሚኒስቴር በሁሉም ከተሞች እያከናወነው የሚገኘውን የህዳር ወር ሃገር አቀፍ የመንገድ ትራፊክ አደጋ የግንዛቤ ማስጨበጫ አካል ነው ተብሏል። በመንገድ ትራፊክ አደጋ ምክንያት እየጠፋ ያለውን ህይወት፣ ሃገራዊ የንብረት ውድመትና የአካል ጉዳትን መቀነስ በሚቻልበት ሁኔታ ላይ ውይይት የሚደረግበትና ባለድርሻ አካላት የራሳቸውን የቤት ስራ የሚወስዱበት ነው።በመድረኩ ከዘጠኙም ክልሎች የተገኙ 122 ጠንቃቃ አሽከርካሪዎችና 6 ልዩ ተሸላሚዎች እውቅና እና ሽልማት እንደሚበረከትላቸው የዘገበው ኤፍቢሲ ነው።
@YeneTube @FikerAssefa
መድረኩ በአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን አዳራሽ ነው እየተካሄደ የሚገኘው። የኢፌዴሪ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ ደመቀ መኮንን፣ የትራንሰፖርት ሚኒስትር ወይዘሮ ዳግማዊት ሞገስን ጨምሮ ሚኒስትሮችና ከፍተኛ የመንግሥት የስራ ኃላፊዎች እየተሳተፉ ይገኛል።በመድረኩ በ2011 ዓ.ም ብቻ ህይወታቸውን ላጡ 4 ሺህ 597 ሰዎች የህሊና ፀሎት ተደርጓል።
የዛሬው ምክክር የትራንስፖርት ሚኒስቴር በሁሉም ከተሞች እያከናወነው የሚገኘውን የህዳር ወር ሃገር አቀፍ የመንገድ ትራፊክ አደጋ የግንዛቤ ማስጨበጫ አካል ነው ተብሏል። በመንገድ ትራፊክ አደጋ ምክንያት እየጠፋ ያለውን ህይወት፣ ሃገራዊ የንብረት ውድመትና የአካል ጉዳትን መቀነስ በሚቻልበት ሁኔታ ላይ ውይይት የሚደረግበትና ባለድርሻ አካላት የራሳቸውን የቤት ስራ የሚወስዱበት ነው።በመድረኩ ከዘጠኙም ክልሎች የተገኙ 122 ጠንቃቃ አሽከርካሪዎችና 6 ልዩ ተሸላሚዎች እውቅና እና ሽልማት እንደሚበረከትላቸው የዘገበው ኤፍቢሲ ነው።
@YeneTube @FikerAssefa
የኢፌደሪ መከላከያ ሰራዊት ምክትል ኢታማዦር ሹም ጀነራል ብርሀኑ ጁላ በቅርቡ የፀደቀውን የመከላከያ ሰራዊት መተዳደሪያ ደንብ በመተግበር የሰራዊቱን ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ ስራዎች እየተሰሩ መሆኑን ተናገሩ፡፡
ምክትል ኢታማዦር ሹሙ ይህን ያሉት በተሻሻለው የመከላከያ ሰራዊት መተዳደሪያ ደንብ እንዲሁም በወቅታዊ ሀገራዊ ጉዳዮች ላይ ለሰራዊቱ ሲሰጥ የነበረው ስልጠና ማጠናቀቂያ መርሀ ግብር ላይ ተገኝተው ነው፡፡
https://telegra.ph/YeneTube-12-07
ምክትል ኢታማዦር ሹሙ ይህን ያሉት በተሻሻለው የመከላከያ ሰራዊት መተዳደሪያ ደንብ እንዲሁም በወቅታዊ ሀገራዊ ጉዳዮች ላይ ለሰራዊቱ ሲሰጥ የነበረው ስልጠና ማጠናቀቂያ መርሀ ግብር ላይ ተገኝተው ነው፡፡
https://telegra.ph/YeneTube-12-07
ጀርመናዊው የጴንጤኮስታል ሰባኪው ሪናርድ ቦንኬ ከዚህ አለም በሞት ተለየ።
ኢትዮጰያን ጨምሮ በብዙ የአፍሪካና የአለም ሀገራት በጴንጤኮስታል ወይንም በፕሮቴስታንት ክርስቲያን እንቅስቃሴ ሰባኪነቱ የሚታወቀውና የክሪስት ኦል ኔሽን መስራቹ ጀርመናዊው ሪናርድ ቦንኬ ዛሬ መሞቱን ቤተሰቦቹ አሳውቀዋል።
የስስት ልጆች አባት የነበረው ቦንኬ በወንጌል ሰበካ አገልግሎት ከ60 አመት በላይ ቆይቷል።
ቤተሰቦቹም በሰባኪው ፌስ ቡክ ገፅ ባሰፈሩት መልእክት " አባታችን ፣አያታችን ፣ሰባኪያችን የነበረውን ሪናርድ ቦንኬ ዛሬ ቅዳሜ ህዳር 27 መሞቱን ስናሳውቃቹ ከባድ ሀዘን እየተሰማን ።ቦንኬ በቤተሰቦቹ እንደተከበበ በሰላም ይቺን አለም ተሰናብቷል" በማለት በፅሁፍ አስፈረዋል።
Via:- ትርጉም - Tesfay Getnet
@Yenetube @Fikerassefa
ኢትዮጰያን ጨምሮ በብዙ የአፍሪካና የአለም ሀገራት በጴንጤኮስታል ወይንም በፕሮቴስታንት ክርስቲያን እንቅስቃሴ ሰባኪነቱ የሚታወቀውና የክሪስት ኦል ኔሽን መስራቹ ጀርመናዊው ሪናርድ ቦንኬ ዛሬ መሞቱን ቤተሰቦቹ አሳውቀዋል።
የስስት ልጆች አባት የነበረው ቦንኬ በወንጌል ሰበካ አገልግሎት ከ60 አመት በላይ ቆይቷል።
ቤተሰቦቹም በሰባኪው ፌስ ቡክ ገፅ ባሰፈሩት መልእክት " አባታችን ፣አያታችን ፣ሰባኪያችን የነበረውን ሪናርድ ቦንኬ ዛሬ ቅዳሜ ህዳር 27 መሞቱን ስናሳውቃቹ ከባድ ሀዘን እየተሰማን ።ቦንኬ በቤተሰቦቹ እንደተከበበ በሰላም ይቺን አለም ተሰናብቷል" በማለት በፅሁፍ አስፈረዋል።
Via:- ትርጉም - Tesfay Getnet
@Yenetube @Fikerassefa
''Bulchiifni Magaalaa Finfinnee Maaster pilaanii haaraa baasuf, Kutaa magaalaa lakkoofsan baay’isuufi'' jedhamee, midiyaalee Hawaasaa adda addaa irra kan oofamaa jiru, #soba ta’uu Uummatni hubatee, ololli deemaa jiru, dhugummaa akka hin qabne bulchiifni Magaalaa Finfinnee Ni hubachiisa!
- Mayor Office
@YeneTube @FikerAssefa
- Mayor Office
@YeneTube @FikerAssefa
"የአዲስ አበባ ከተማ አሰተዳደር የከተማዋን ማስተርፕላን ሊያሻሽል ነው፤ በከተማዋ ያሉት የክፍለ ከተማዎች ቁጥርም ወደ 13 ከፍ ሊል ነው" በሚል በማህበራዊ ድረ ገጾች እየተዘዋወረ ያለው መረጃ የተሳሳተ መሆኑን የከተማ መስተዳድሩ አሳውቋል። የከተማ አስተዳደሩ ምንም አይነት አዲስ የከተማ አደረጃጀትም ሆነ ማስተርፕላን የመተግበር ሀሳብ የሌለው መሆኑን ገልጿል።
ምንጭ: የከንቲባው ጽ/ቤት
@YeneTube @FikerAssefa
ምንጭ: የከንቲባው ጽ/ቤት
@YeneTube @FikerAssefa
"እንኳን የኢትዮጵያዊነት ቀን ለሆነው የኢትዮጵያ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች በዓል አደረሳችሁ፡፡ ይህን በዓል ስናከብር ወደ ቀደመው አሐዳዊነትም ሆነ ወደ እጅ አዙር አሐዳዊነት ዳግም እንደማንመለስ እያረጋገጥን ነው፡፡ ከፊታችን ያለው ዘመን መንፈሳዊ፣ አእምሯዊና ቁሳዊ ብልጽግናችን የሚረጋገጥበት ዘመን ይሆናል፡፡ ባህሎቻችን፣ ቋንቋዎቻችን፣ ዕሴቶቻችን፣ የሚበለጽጉበት ዘመን ይሆናል፡፡ አንድነታችን፣ አብሮነታችን፣ ወንድማማችነታችን የሚበለጽግበት ዘመን ይሆናል፤ በዕውቀትና በሀብት የምንበለጽግበት ዘመን ይሆናል፡፡ በፍትሕ፣ በሰላም፣ በጋራ ደኅንነት፣ የምንበለጽግበት ዘመን ይሆናል፡፡ ካሳለፍናቸው ዘመናት ይልቅ ወደፊት የምናሳልፋቸው ዘመናት ብዙ ናቸው፡፡"
ጠ/ሚ አብይ አህመድ በነገው ዕለት ለሚከበረው የብሄሮችና ብሄረሰቦች ቀን አስመልክተው ካስተላለፉት
@YeneTube @FikerAssefa
ጠ/ሚ አብይ አህመድ በነገው ዕለት ለሚከበረው የብሄሮችና ብሄረሰቦች ቀን አስመልክተው ካስተላለፉት
@YeneTube @FikerAssefa
#ቡና_ኢንተርናሽናል ባንክ አስረኛ የምስረታ በዓሉን በሚሌኒየም አዳራሽ እያከበረ ይገኛል።በፕሮግራሙ ላይ የባንኩ አመራሮች እንዲሁም ባለአክሲዮኖች ተገኝተዋል።
@Yenetube @Fikerassefa
@Yenetube @Fikerassefa
#በቢራና #በሲጋራ ዋጋ ላይ 30 እና 40 በመቶ ኤክሳይዝ ታክስ ይጣላል!
በዚህ መሠረት በቢራ ላይ የሚጣለው ኤክሳይዝ ታክስ በጠርሙስ 40 በመቶ ወይም በሊትር 11 ብር እንዲከፈል በረቂቅ ድንጋጌነት ቀርቧል፡፡ ሃያ ፍሬዎችን በሚይዝ አንድ ፓኬት ሲጋራ መሸጫ ዋጋ ላይ 30 በመቶና ተጨማሪ አምስት ብር እንዲሰላ በድንጋጌው ተመልክቷል፡፡በእያንዳንዱ የቢራና የሲጋራ ምርት ላይ ኤክሳይዝ ታክስ የተከፈለበት መሆኑን የሚያመለክት ቴምብር መለጠፍ እንደሚኖርበት በአስገዳጅነት ተቀምጧል፡፡ከዚህ በተጨማሪም ኤክስይዝ ታክስ የሚከፈልበትን ምርት ለማምረትም ሆነ ለማስመጣት፣ እንዲሁም አገልግሎት ለመስጠት ከገቢዎች ሚኒስቴር ልዩ ፈቃድ መያዝ በአስገዳጅነት ተካቷል፡፡ በቢራ አምራችነት ፈቃድ ከተሰጣቸው ኩባንያዎች ውጪ በባር ወይ በምግብ ቤቶች አነስተኛ ቢራ ጠመቃ ለማካሄድ ተጨማሪ ፈቃድ ማግኘትም አስገዳጅ ሆኖ በረቂቁ ተካቷል፡፡
በሥራ ላይ ያለው አዋጅ በቢራ ምርቶች የማምረቻ ዋጋ ላይ የሚጥለው ኤክሳይዝ ታክስ 50 በመቶ ሲሆን፣ በትምባሆ ምርት የማምረቻ ዋጋ ላይ ደግሞ 75 በመቶ ይጥላል።በመሆኑም የማኅበረሰብ ጤናን በከፍተኛ ደረጃ ያቃውሳሉ የተባሉት በሁለቱ ምርቶች ላይ እንዲጣል የቀረበው አዲስ የኤክሳይዝ ታክስ፣ እጅግ ዝቅተኛና የማኅበረሰብ ጤናን ያላገናዘበ መሆኑን ባለሙያዎች ያስረዳሉ።
በተለይ በትምባሆ ምርት ላይ የዓለም የጤና ድርጅት የሚያስቀምጠው የታክስ ምጣኔ 70 በመቶ መሆኑን የሚናገሩት ባለሙያዎቹ፣ አሁን የተረቀቀው ኤክሳይዝ ታክስ ምጣኔ በዓለም የጤና ድርጅት ከተቀመጠውም ሆነ ከሰሃራ በታች የሚገኙ አገሮች በሲጋራ ላይ ከሚጥሉት ኤክሳይዝ ታክስ በእጅጉ እንደሚያንስ ይገልጻሉ።የኢትዮጵያ ፓርላማ ትምባሆን ለመቆጣጠር ባወጣው ጥብቅ ሕግ በዓለም ጤና ድርጅት ባለፈው ዓመት መሸለሙን የሚያስታውሱት ባለሙያዎቹ፣ አዲሱ ኤክሳይዝ ታክስ በሲጋራ ላይ ለመጣል ያቀደው የታክስ ምጣኔ የኅብረተሰብ ጤናን ለመጠበቅ ታስቦ የፀደቀውን የትምባሆ ቁጥጥር አዋጅ ዓላማ የሚቃረን በመሆኑ መንግሥት በድጋሚ ሊያጤነው ይገባል ብለዋል።
በዘንድሮው የበጀት አዋጅ መሠረት 4.2 ቢሊዮን ብር በአገር ውስጥ በሚመረቱ ቢራ መጠጦች ላይ ከሚጣል ኤክሳይዝ ታክስ ለመሰብሰብ፣ እንዲሁም 1.1 ቢሊዮን ብር ከሲጋራ ወይም ከትምባሆ ምርቶች ኤክሳይዝ ታክስ እንዲሰበስብ ለገቢዎች ሚኒስቴር ኃላፊነት ተሰጥቶታል።
በሥራ ላይ በሚገኘው አዋጅ ኤክሳይዝ ታክስ ካልተጣለባቸው ምርቶች በረቂቁ እንዲካተቱ ከተደረጉት መካከል አንዱ ሰው ሠራሽ ፀጉር ወይም “ሂዩማን ሄር” ሲሆን፣ 100 በመቶ ኤክሳይዝ ታክስ እንዲጣልበት በረቂቁ ተካቷል፡፡
Via:- ሪፖርተር
@Yenetube @Fikerassefa
በዚህ መሠረት በቢራ ላይ የሚጣለው ኤክሳይዝ ታክስ በጠርሙስ 40 በመቶ ወይም በሊትር 11 ብር እንዲከፈል በረቂቅ ድንጋጌነት ቀርቧል፡፡ ሃያ ፍሬዎችን በሚይዝ አንድ ፓኬት ሲጋራ መሸጫ ዋጋ ላይ 30 በመቶና ተጨማሪ አምስት ብር እንዲሰላ በድንጋጌው ተመልክቷል፡፡በእያንዳንዱ የቢራና የሲጋራ ምርት ላይ ኤክሳይዝ ታክስ የተከፈለበት መሆኑን የሚያመለክት ቴምብር መለጠፍ እንደሚኖርበት በአስገዳጅነት ተቀምጧል፡፡ከዚህ በተጨማሪም ኤክስይዝ ታክስ የሚከፈልበትን ምርት ለማምረትም ሆነ ለማስመጣት፣ እንዲሁም አገልግሎት ለመስጠት ከገቢዎች ሚኒስቴር ልዩ ፈቃድ መያዝ በአስገዳጅነት ተካቷል፡፡ በቢራ አምራችነት ፈቃድ ከተሰጣቸው ኩባንያዎች ውጪ በባር ወይ በምግብ ቤቶች አነስተኛ ቢራ ጠመቃ ለማካሄድ ተጨማሪ ፈቃድ ማግኘትም አስገዳጅ ሆኖ በረቂቁ ተካቷል፡፡
በሥራ ላይ ያለው አዋጅ በቢራ ምርቶች የማምረቻ ዋጋ ላይ የሚጥለው ኤክሳይዝ ታክስ 50 በመቶ ሲሆን፣ በትምባሆ ምርት የማምረቻ ዋጋ ላይ ደግሞ 75 በመቶ ይጥላል።በመሆኑም የማኅበረሰብ ጤናን በከፍተኛ ደረጃ ያቃውሳሉ የተባሉት በሁለቱ ምርቶች ላይ እንዲጣል የቀረበው አዲስ የኤክሳይዝ ታክስ፣ እጅግ ዝቅተኛና የማኅበረሰብ ጤናን ያላገናዘበ መሆኑን ባለሙያዎች ያስረዳሉ።
በተለይ በትምባሆ ምርት ላይ የዓለም የጤና ድርጅት የሚያስቀምጠው የታክስ ምጣኔ 70 በመቶ መሆኑን የሚናገሩት ባለሙያዎቹ፣ አሁን የተረቀቀው ኤክሳይዝ ታክስ ምጣኔ በዓለም የጤና ድርጅት ከተቀመጠውም ሆነ ከሰሃራ በታች የሚገኙ አገሮች በሲጋራ ላይ ከሚጥሉት ኤክሳይዝ ታክስ በእጅጉ እንደሚያንስ ይገልጻሉ።የኢትዮጵያ ፓርላማ ትምባሆን ለመቆጣጠር ባወጣው ጥብቅ ሕግ በዓለም ጤና ድርጅት ባለፈው ዓመት መሸለሙን የሚያስታውሱት ባለሙያዎቹ፣ አዲሱ ኤክሳይዝ ታክስ በሲጋራ ላይ ለመጣል ያቀደው የታክስ ምጣኔ የኅብረተሰብ ጤናን ለመጠበቅ ታስቦ የፀደቀውን የትምባሆ ቁጥጥር አዋጅ ዓላማ የሚቃረን በመሆኑ መንግሥት በድጋሚ ሊያጤነው ይገባል ብለዋል።
በዘንድሮው የበጀት አዋጅ መሠረት 4.2 ቢሊዮን ብር በአገር ውስጥ በሚመረቱ ቢራ መጠጦች ላይ ከሚጣል ኤክሳይዝ ታክስ ለመሰብሰብ፣ እንዲሁም 1.1 ቢሊዮን ብር ከሲጋራ ወይም ከትምባሆ ምርቶች ኤክሳይዝ ታክስ እንዲሰበስብ ለገቢዎች ሚኒስቴር ኃላፊነት ተሰጥቶታል።
በሥራ ላይ በሚገኘው አዋጅ ኤክሳይዝ ታክስ ካልተጣለባቸው ምርቶች በረቂቁ እንዲካተቱ ከተደረጉት መካከል አንዱ ሰው ሠራሽ ፀጉር ወይም “ሂዩማን ሄር” ሲሆን፣ 100 በመቶ ኤክሳይዝ ታክስ እንዲጣልበት በረቂቁ ተካቷል፡፡
Via:- ሪፖርተር
@Yenetube @Fikerassefa
ዜና እረፍት !
በተጫዋችን እንዲሁም ኢትዮ ኤሌክትሪክን ፣ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክን፣ ኢትዮጵያ መድን እና የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን በተለያዮ የዕድሜ እርከኖች በአሰልጣኝ የነበሩት አንጋፋው አሰልጣኝ ወንድማገኝ ከበደ ከዚህ ዓለም በሞት ተለይቷል።
የአዲስ አበባ እግርኳስ ፌዴሬሽን በአሰልጣኝ ወንድማገኝ ከበደ ዜና ህልፈት የተሰማውን ጥልቅ ሀዘን እየገለፀ ለወዳጅ ዘመዶቹ እና ቤተሰቦቹ መፅናናትን ተመኝቷል።
@Yenetube @Fikerassefa
በተጫዋችን እንዲሁም ኢትዮ ኤሌክትሪክን ፣ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክን፣ ኢትዮጵያ መድን እና የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን በተለያዮ የዕድሜ እርከኖች በአሰልጣኝ የነበሩት አንጋፋው አሰልጣኝ ወንድማገኝ ከበደ ከዚህ ዓለም በሞት ተለይቷል።
የአዲስ አበባ እግርኳስ ፌዴሬሽን በአሰልጣኝ ወንድማገኝ ከበደ ዜና ህልፈት የተሰማውን ጥልቅ ሀዘን እየገለፀ ለወዳጅ ዘመዶቹ እና ቤተሰቦቹ መፅናናትን ተመኝቷል።
@Yenetube @Fikerassefa
በቂሊንጦ ማርሚያ ቤት በታራሚዎች መካከል በተፈጠረ ግጭት ስድስት ታራሚዎች ከፍተኛ ጉዳት ደርሰባቸው፡፡
ዛሬ ሕዳር 28 ቀን 2012 ዓ.ም ረፋድ ላይ በአዲስ አበባ በሚገኘው በቂሊንጦ ማረምያ ቤት በእስረኞች መካከል በተፈጠረ ግጭት በስድስት ታራሚዎች ላይ ከፍተኛ ጉዳት እንደደረሰባቸው የፌደራል ማረሚያ ቤቶች አስታውቋል፡፡ጉዳት የደረሰባቸው ታራሚዎችም ወደ ፌደራል ማረሚያ ቤቶች ሆስፒታል እንደተወሰዱ የፌደራል ማረምያ ቤቶች የቀጠሮ ማረፊያ ቤት ዋና አስተዳዳሪ ኮማንደር ጫላ ጸጋ ለኢትዮ ኤፍ ኤም ተናግረዋል፡፡
ግጭቱ በታራሚዎች መካከል ከሆነ ፖሊስ ለምን ብዛት ያለው ጥይት ተኮሰ በሚል ለተነሳላቸው ጥያቄም ፖሊስ ጥይት የተኮሰው እስር ቤቱ ጣራ ላይ የተቀመጡትን ታራሚዎች እንዲወርዱ ለማድረግ በማሰብ ነው ብለውናል ኮማንድር ጫላ፡፡በግጭቱ ሳብያም እስካሁን የሞተ እንድም ታራሚ አለመኖሩን ኮማንደሩ ተናግረዋል፡፡በጊዜው የደረሰው ግጭት ወዲያውኑ እንደተቆጣጠሩት እና አሁን ላይም ማረሚያ ቤቱ መረጋጋቱን ኮማንደር ጫላ ተናግረዋል፡፡
Via Ethio FM
@YeneTube @FikerAssefa
ዛሬ ሕዳር 28 ቀን 2012 ዓ.ም ረፋድ ላይ በአዲስ አበባ በሚገኘው በቂሊንጦ ማረምያ ቤት በእስረኞች መካከል በተፈጠረ ግጭት በስድስት ታራሚዎች ላይ ከፍተኛ ጉዳት እንደደረሰባቸው የፌደራል ማረሚያ ቤቶች አስታውቋል፡፡ጉዳት የደረሰባቸው ታራሚዎችም ወደ ፌደራል ማረሚያ ቤቶች ሆስፒታል እንደተወሰዱ የፌደራል ማረምያ ቤቶች የቀጠሮ ማረፊያ ቤት ዋና አስተዳዳሪ ኮማንደር ጫላ ጸጋ ለኢትዮ ኤፍ ኤም ተናግረዋል፡፡
ግጭቱ በታራሚዎች መካከል ከሆነ ፖሊስ ለምን ብዛት ያለው ጥይት ተኮሰ በሚል ለተነሳላቸው ጥያቄም ፖሊስ ጥይት የተኮሰው እስር ቤቱ ጣራ ላይ የተቀመጡትን ታራሚዎች እንዲወርዱ ለማድረግ በማሰብ ነው ብለውናል ኮማንድር ጫላ፡፡በግጭቱ ሳብያም እስካሁን የሞተ እንድም ታራሚ አለመኖሩን ኮማንደሩ ተናግረዋል፡፡በጊዜው የደረሰው ግጭት ወዲያውኑ እንደተቆጣጠሩት እና አሁን ላይም ማረሚያ ቤቱ መረጋጋቱን ኮማንደር ጫላ ተናግረዋል፡፡
Via Ethio FM
@YeneTube @FikerAssefa
በአቶ ገዱ አንዳርጋቸው የተመራው የልዑካን ቡድን ዋሽንግተን ገባ!
በታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ዙሪያ ከግብጽና ሱዳን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች ጋር በሚደረገው ውይይት ለመሳተፍ ወደ አሜሪካ ያቀናውና በውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ክቡር አቶ ገዱ አንዳርጋቸው የተመራው የልዑካን ቡድን ዛሬ ህዳር 28 ቀን 2012 ዓ.ም ዋሽንግተን ገብቷል።የልዑካን ቡድኑ ዋሽንግተን ዳላስ አለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ሲደርስ በአምባሳደር ፍጹም አረጋና በኤምባሲው ዲፕሎማቶች አቀባበል ተደርጎለታል።በህዳሴው ግድብ ዙሪያ በሚካሄደው በዚህ ምክክር በቅርቡ በአዲስ አበባ እና በካይሮ ከተደረጉት የግድቡ የውሀ ሙሌትና ሌሎች ባልተቋጩ ነጥቦች ላይ እንደሚያተኩር ይጠበቃል።የአሜሪካ እና የአለም ባንክ ተወካዮች በስብሰባው በታዛቢነት ይሳተፋሉ።
ምንጭ: የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር
@YeneTube @FikerAssefa
በታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ዙሪያ ከግብጽና ሱዳን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች ጋር በሚደረገው ውይይት ለመሳተፍ ወደ አሜሪካ ያቀናውና በውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ክቡር አቶ ገዱ አንዳርጋቸው የተመራው የልዑካን ቡድን ዛሬ ህዳር 28 ቀን 2012 ዓ.ም ዋሽንግተን ገብቷል።የልዑካን ቡድኑ ዋሽንግተን ዳላስ አለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ሲደርስ በአምባሳደር ፍጹም አረጋና በኤምባሲው ዲፕሎማቶች አቀባበል ተደርጎለታል።በህዳሴው ግድብ ዙሪያ በሚካሄደው በዚህ ምክክር በቅርቡ በአዲስ አበባ እና በካይሮ ከተደረጉት የግድቡ የውሀ ሙሌትና ሌሎች ባልተቋጩ ነጥቦች ላይ እንደሚያተኩር ይጠበቃል።የአሜሪካ እና የአለም ባንክ ተወካዮች በስብሰባው በታዛቢነት ይሳተፋሉ።
ምንጭ: የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር
@YeneTube @FikerAssefa
🐴ፈረስ የታክሲ አገልግሎት🐴
ኮድ 1 ወይም 3 መኪና ካሎት ተጨማሪ ገቢ ለማግኘት አሁኑኑ በነፃ መኪናዎን ያስመዝግቡ።
🎯ቦታችን ጌቱ ኮሜርሻል ህንፃ አንደኛ ፎቅ ላይ እንገኛለን።
ይህንን ያውቃሉ? ፈረሰ ኮምሽን የሚወስደው 5% ብቻ ነው፣ ይህም ተመራጭ አድርጎታል።
ለበለጠ መረጃ
የቴሌግራም ቻናላችንን ይቀላቀሉ
@feresapps
ኮድ 1 ወይም 3 መኪና ካሎት ተጨማሪ ገቢ ለማግኘት አሁኑኑ በነፃ መኪናዎን ያስመዝግቡ።
🎯ቦታችን ጌቱ ኮሜርሻል ህንፃ አንደኛ ፎቅ ላይ እንገኛለን።
ይህንን ያውቃሉ? ፈረሰ ኮምሽን የሚወስደው 5% ብቻ ነው፣ ይህም ተመራጭ አድርጎታል።
ለበለጠ መረጃ
የቴሌግራም ቻናላችንን ይቀላቀሉ
@feresapps
ፍትህ መፅሄት ህዳር ወር ዕትም ቁጥር 57 ለማ በገበያ በሚል ርዕስ ይዞት ከወጣውን መፅሄት ላይ ዓለማየሁ ገላጋይ "ከድፍን ሀገር ቁራሽ ለትንሽ" በሚል ርዕስ ያስነበበውም በድምፅ ሰርተንላችዋል።
አድምጡት ⬇️
https://youtu.be/G5Oi51BuRBo
አድምጡት ⬇️
https://youtu.be/G5Oi51BuRBo
ኢትዮጵያዊቷ ፍሬወይኒ መብርሃቱ የCNN የአመቱ ጀግና(CNN Hero of The Year) በመባል ተመርጣለች!
እንኳን ደስ አለሽ!
እንኳን ደስ አለን!
@YeneTube @FikerAssefa
እንኳን ደስ አለሽ!
እንኳን ደስ አለን!
@YeneTube @FikerAssefa
ፍረወይኒ ለዛሬ አጥቢያ የ "CNN የአመቱ ጀግና" ተብላ የተመረጠችው ለፍፃሜ ከቀረቡት አስር ሰዎች እና ድርጅቶች መሀል ነው። የኬሚካል ኢንጂነሪንግ ትምህርት በአሜሪካ ያጠናችው ፍረወይኒ ተመልሶ ጥቅም ላይ ሊውል የሚችል የሴቶች ንፅህና መጠበቂያ ምርት ዲዛይን አድርጋ እና ለመጠቀሚያ ያቀረበችው የዛሬ 14 አመት ገደማ ነበር።
ከዛን ግዜ ጀምሮ 750,000 ገደማ የሚሆን ይህ ኢትዮጵያ ውስጥ የሚሰራ ምርት ለተጠቃሚዎች የተከፋፈለ ሲሆን 800,000 ሺህ ገደማ ሴቶች ከፍረወይኒ ስራ ተጠቃሚ ሆነዋል። ዛሬ ይህንን ሽልማት በማሸነፏም ስራዋን ለማስፋፋት እንዲያግዛት የ100,000 ዶላር ሽልማት ተቀብላለች።
Via ጋዜጠኛ ኤልያስ መሰረት
@YeneTube @FikerAssefa
ከዛን ግዜ ጀምሮ 750,000 ገደማ የሚሆን ይህ ኢትዮጵያ ውስጥ የሚሰራ ምርት ለተጠቃሚዎች የተከፋፈለ ሲሆን 800,000 ሺህ ገደማ ሴቶች ከፍረወይኒ ስራ ተጠቃሚ ሆነዋል። ዛሬ ይህንን ሽልማት በማሸነፏም ስራዋን ለማስፋፋት እንዲያግዛት የ100,000 ዶላር ሽልማት ተቀብላለች።
Via ጋዜጠኛ ኤልያስ መሰረት
@YeneTube @FikerAssefa
🐴ፈረስ የታክሲ አገልግሎት🐴
ኮድ 1 ወይም 3 መኪና ካሎት ተጨማሪ ገቢ ለማግኘት አሁኑኑ በነፃ መኪናዎን ያስመዝግቡ።
🎯ቦታችን ጌቱ ኮሜርሻል ህንፃ አንደኛ ፎቅ ላይ እንገኛለን።
ይህንን ያውቃሉ? ፈረሰ ኮምሽን የሚወስደው 5% ብቻ ነው፣ ይህም ተመራጭ አድርጎታል።
ለበለጠ መረጃ
የቴሌግራም ቻናላችንን ይቀላቀሉ
@feresapps
ኮድ 1 ወይም 3 መኪና ካሎት ተጨማሪ ገቢ ለማግኘት አሁኑኑ በነፃ መኪናዎን ያስመዝግቡ።
🎯ቦታችን ጌቱ ኮሜርሻል ህንፃ አንደኛ ፎቅ ላይ እንገኛለን።
ይህንን ያውቃሉ? ፈረሰ ኮምሽን የሚወስደው 5% ብቻ ነው፣ ይህም ተመራጭ አድርጎታል።
ለበለጠ መረጃ
የቴሌግራም ቻናላችንን ይቀላቀሉ
@feresapps