ትላንት አመሻሽ ላይ በጎፋ ዞን ሳውላ ከተማ ጠጥቶ በማሽከርከር በደረሰ የትራፊክ አደጋ በንብረትና በሰው ላይ ጉዳት ደርሷል ረዳቱ ከባድ ጉዳት ሲደርስበት ሾፌሩ መጠነኛ ጉዳት ደርሶበታል።
@YeneTube @Fikerassefa
@YeneTube @Fikerassefa
YeneTube
ትላንት አመሻሽ ላይ በጎፋ ዞን ሳውላ ከተማ ጠጥቶ በማሽከርከር በደረሰ የትራፊክ አደጋ በንብረትና በሰው ላይ ጉዳት ደርሷል ረዳቱ ከባድ ጉዳት ሲደርስበት ሾፌሩ መጠነኛ ጉዳት ደርሶበታል። @YeneTube @Fikerassefa
በደቡብ ክልል የመንገድ ትራፊክ አደጋ እየጨመረ መሆኑን ተገለጸ።
በደቡብ ክልል የመንገድ ትራፊክ አደጋ እየጨመረ መሆኑን የደቡብ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን አስታወቀ፡፡ከባለፈው ሐሙስ እስከ እሁድ መስከረም 18/2012 ዓ.ም በአራት ቀናት ብቻ 22 አደጋ የደረሰ ሲሆን ከዚህም ውስጥ 6 የሞት አደጋ፣ 14 ከባድ የአካል ጉዳት እና 2 ቀላል የአካል ጉዳት ያስከተለ አደጋ ተመዝግቧል ሲሉ በደቡብ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን የትራፊክ አደጋ መከላከልና መቆጣጠር የትንተና ባለሙያ ምክትል ሳጂን ተመስጌን አረጋ ገልፀዋል፡፡
አብዛኛው የአደጋዎቹ መንስኤዎች የአሽከርካሪዎች ጥንቃቄ ጉድለትና ለእግረኛ ቅድሚያ አለመስጠት መሆኑን ተናግረዋል፡፡ያሳለፍነው ሳምንት የበዓል ሳምንት መሆኑ ለአደጋው መጨመር እንደ ምክንያት ሊሆን ይችላል ተብሎ ይታሰባል ሲሉ ምክትል ሳጂን ተመስጌን አረጋ አክለዋል፡፡በመሆኑም በአራቱ ቀናት ብቻ 9 ሰዎች ሕይወታቸው ሲያልፍ 19 ሰዎች ላይ ከባድና ቀላል የአካል ጉዳት ደርሶባቸዋል፡፡
ምንጭ: SRTA
@YeneTube @FikerAssefa
በደቡብ ክልል የመንገድ ትራፊክ አደጋ እየጨመረ መሆኑን የደቡብ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን አስታወቀ፡፡ከባለፈው ሐሙስ እስከ እሁድ መስከረም 18/2012 ዓ.ም በአራት ቀናት ብቻ 22 አደጋ የደረሰ ሲሆን ከዚህም ውስጥ 6 የሞት አደጋ፣ 14 ከባድ የአካል ጉዳት እና 2 ቀላል የአካል ጉዳት ያስከተለ አደጋ ተመዝግቧል ሲሉ በደቡብ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን የትራፊክ አደጋ መከላከልና መቆጣጠር የትንተና ባለሙያ ምክትል ሳጂን ተመስጌን አረጋ ገልፀዋል፡፡
አብዛኛው የአደጋዎቹ መንስኤዎች የአሽከርካሪዎች ጥንቃቄ ጉድለትና ለእግረኛ ቅድሚያ አለመስጠት መሆኑን ተናግረዋል፡፡ያሳለፍነው ሳምንት የበዓል ሳምንት መሆኑ ለአደጋው መጨመር እንደ ምክንያት ሊሆን ይችላል ተብሎ ይታሰባል ሲሉ ምክትል ሳጂን ተመስጌን አረጋ አክለዋል፡፡በመሆኑም በአራቱ ቀናት ብቻ 9 ሰዎች ሕይወታቸው ሲያልፍ 19 ሰዎች ላይ ከባድና ቀላል የአካል ጉዳት ደርሶባቸዋል፡፡
ምንጭ: SRTA
@YeneTube @FikerAssefa
Happening Now…
በአዲስ አበባ የሚኖሩ የአገው እና ቅማንት ተወላጆች፡ በቅማንት ብሄር እየደረሰ ያለው ስቃይ በመቃወም ሰላማዊ ሰልፍ እያደረጉ ነው።
@YeneTube @FikerAssefa
በአዲስ አበባ የሚኖሩ የአገው እና ቅማንት ተወላጆች፡ በቅማንት ብሄር እየደረሰ ያለው ስቃይ በመቃወም ሰላማዊ ሰልፍ እያደረጉ ነው።
@YeneTube @FikerAssefa
ኢትዮ ቴሌኮም በሲስተም አለመናበብ ምክንያት የተፈጠሩ ችግሮችን ለመፍታት እየሰራ መሆኑን አስታወቀ!
ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በደንበኞች ቅሬታ መሰረት በሲስተም አለመናበብ ምክንያት የሚፈጠሩ ችግሮችን ለመፍታት እየሰራ እንደሆነ ኢትዮቴሌኮም አስታውቋል፡፡አንድ ደንበኛ ስልኩ ውስጥ በቂ ሂሣብ ሳይኖረው ሲቀር "የደንበኛው ቀሪ ሂሣብ በቂ ስላልሆነ ጥሪው አይደርስም" በሚል የሚተላለፈው መልእክት በሲስተም መናበብ ችግር የተፈጠረ መሆኑን የኢትዮ ቴሌኮም ምክትል ዋና ዳይሬክተር ወ/ሮ ጨረር አክሊሉ ገልፀዋል።እንደዚህ ዓይነቱ መልእክት እንዲተላለፍ ኢትዮ ቴሌኮም አዲስ አሠራር ተግባራዊ አለማድጉን ነው የገለጹት፡፡
ችግሩ በዋናነት ሊፈጠር የቻለው “ኔትወርክ የለም” በሚለው እና “ያልተሳካ ጥሪ ማሳወቂያ - 824" ሲስተም መካከል መሆኑን ተናግረዋል።ከኔትዎርክ ውጭ የሆኑ ሰዎች ምናልባት ስልካቸው ላይ በቂ ሂሣብ ስለሌለ የሉም ከማለት ይልቅ "ቀሪ ሂሣብ የላቸውም" የሚለውን እያስቀደመ እንደሚሆን ግምታቸውን ሰጥተዋል።በጉዳዩ ላይ ጥቆማ ከደረሳቸው በኋላ ችግሩን ለመፍታት እየሠሩ መሆኑን እና የተፈጠረው ሁኔታ ተገቢ ባለመሆኑ ኢትዮ ቴሌኮም ይቅርታ መጠየቁን ገልጸዋል።
Via EBC
@YeneTube @FikerAssefa
ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በደንበኞች ቅሬታ መሰረት በሲስተም አለመናበብ ምክንያት የሚፈጠሩ ችግሮችን ለመፍታት እየሰራ እንደሆነ ኢትዮቴሌኮም አስታውቋል፡፡አንድ ደንበኛ ስልኩ ውስጥ በቂ ሂሣብ ሳይኖረው ሲቀር "የደንበኛው ቀሪ ሂሣብ በቂ ስላልሆነ ጥሪው አይደርስም" በሚል የሚተላለፈው መልእክት በሲስተም መናበብ ችግር የተፈጠረ መሆኑን የኢትዮ ቴሌኮም ምክትል ዋና ዳይሬክተር ወ/ሮ ጨረር አክሊሉ ገልፀዋል።እንደዚህ ዓይነቱ መልእክት እንዲተላለፍ ኢትዮ ቴሌኮም አዲስ አሠራር ተግባራዊ አለማድጉን ነው የገለጹት፡፡
ችግሩ በዋናነት ሊፈጠር የቻለው “ኔትወርክ የለም” በሚለው እና “ያልተሳካ ጥሪ ማሳወቂያ - 824" ሲስተም መካከል መሆኑን ተናግረዋል።ከኔትዎርክ ውጭ የሆኑ ሰዎች ምናልባት ስልካቸው ላይ በቂ ሂሣብ ስለሌለ የሉም ከማለት ይልቅ "ቀሪ ሂሣብ የላቸውም" የሚለውን እያስቀደመ እንደሚሆን ግምታቸውን ሰጥተዋል።በጉዳዩ ላይ ጥቆማ ከደረሳቸው በኋላ ችግሩን ለመፍታት እየሠሩ መሆኑን እና የተፈጠረው ሁኔታ ተገቢ ባለመሆኑ ኢትዮ ቴሌኮም ይቅርታ መጠየቁን ገልጸዋል።
Via EBC
@YeneTube @FikerAssefa
ቀዳማዊት እመቤት ዝናሽ ታያቸዉ ወደ ናይጀሪያው ሮቻስ ፋዉንዴሽን ለነጻ የትምህርት እድል የሚልኳቸዉን አምስት ወላጅ አልባ ታዳጊዎችን በቢሮአቸዉ አነጋገሩ፡፡ታዳጊዎቹ ከ4 ህጻናት ማሳደጊያዎች የተመረጡ የ7ኛ ክፍል ተማሪዎች ናቸዉ፡፡
@YeneTube @FikerAssefa
@YeneTube @FikerAssefa
በታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የውሃ ሙሌትና አለቃቀቅ ዙሪያ የተቋቋመው የኢትዮጵያ፣ሱዳን እና ግብጽ የሦስትዮሽ ብሔራዊ ገለልተኛ የሳይንሳዊ ጥናት ቡድን 5ኛ ስብስባውን በካርቱም ሱዳን ማካሄድ ጀምሯል።
የጥናት ቡድኑ እ.አ.አ ከመስከረም 15-16, 2019 በካይሮ በተደረገው ስብሰባ ወቅት በሦስቱ አገራት የውሃ ጉዳይ ሚኒስትሮች በተለዩ አጀንዳዎች ላይ በመወያየት እ.አ.አ ከጥቅምት 4-5 2019 በካርቱም በሚካሄደው የሦስቱ አገራት ውሃ ሚኒስትሮች ስብሰባ ላይ ሪፖርት እንደሚያቀርብ ይጠበቃል።
Via Ethiopian Embassy in Sudan
@YeneTube @FikerAssefa
የጥናት ቡድኑ እ.አ.አ ከመስከረም 15-16, 2019 በካይሮ በተደረገው ስብሰባ ወቅት በሦስቱ አገራት የውሃ ጉዳይ ሚኒስትሮች በተለዩ አጀንዳዎች ላይ በመወያየት እ.አ.አ ከጥቅምት 4-5 2019 በካርቱም በሚካሄደው የሦስቱ አገራት ውሃ ሚኒስትሮች ስብሰባ ላይ ሪፖርት እንደሚያቀርብ ይጠበቃል።
Via Ethiopian Embassy in Sudan
@YeneTube @FikerAssefa
በቦሌ ብራስ አካባቢ ባለው የደመራ የባህል ምግብ ቤት አስተናጋጆች ተጣልተው የአንድ ሰው ህይወት ማለፉ ተገለጸ።
በቦሌ ብራስ ሆስፒታል አካባቢ በሚገኘው የደመራ የባህል ምግብ ቤት የመስተንግዶ ሰራተኞች መካከል በተፈጠረ የግል ጸብ አንድ ሰው ህይወቱ ማለፉ ተገልጿል።ኢትዮ ኤፍ ኤም ከአይን እማኞች እንዳረገጋጠው ጸቡ የተፈጠረው በምግብ ቤቱ ሁለት አስተናጋጆች መካከል ነው።አንዱ አስተናጋጅም በደረሰበት የስለት ጥቃት ወደ ብራስ ሆስፒታል ተወስዶ ህይወቱን ለማዳን ርብርብ ቢደረግም ህይወቱን ማትረፍ አልተቻለም።ድብደባውን የፈጸመው ግለሰብ ለማምለጥ የሞከረ ቢሆንም በአካባቢው ሰዎች በቁጥጥር ስር መዋሉ ተነግሯል።
via:- ETHIO FM
@YeneTube @FikerAssefa
በቦሌ ብራስ ሆስፒታል አካባቢ በሚገኘው የደመራ የባህል ምግብ ቤት የመስተንግዶ ሰራተኞች መካከል በተፈጠረ የግል ጸብ አንድ ሰው ህይወቱ ማለፉ ተገልጿል።ኢትዮ ኤፍ ኤም ከአይን እማኞች እንዳረገጋጠው ጸቡ የተፈጠረው በምግብ ቤቱ ሁለት አስተናጋጆች መካከል ነው።አንዱ አስተናጋጅም በደረሰበት የስለት ጥቃት ወደ ብራስ ሆስፒታል ተወስዶ ህይወቱን ለማዳን ርብርብ ቢደረግም ህይወቱን ማትረፍ አልተቻለም።ድብደባውን የፈጸመው ግለሰብ ለማምለጥ የሞከረ ቢሆንም በአካባቢው ሰዎች በቁጥጥር ስር መዋሉ ተነግሯል።
via:- ETHIO FM
@YeneTube @FikerAssefa
በኦሞ ሸለቆ ተፋሰስ ላይ በተገነቡ ኹለት የስኳር ፋብሪካዎች በማገልገል ላይ የሚገኙ አራት ሠራተኞች በሥራ ላይ እያሉ መገደላቸውና ሠራተኞች የጸጥታ ሥጋት ላይ በመወደቃቸው ፋብሪካው ሥራ እንዳቆመ የኢትዮጵያ ስኳር ኮርፖሬሽን የሠራተኞች ማኅበር አስታወቀ።
በአካባቢው ላይ ያለው የእርስ በእርስ ግጭትም በአካባቢው በሚንቀሳቀሱ ታጣቂዎች በደረሰ ጥቃት የሦስት ሰዎች ሕይወት ማለፉንም የኢትዮጵያ ስኳር ኮርፖሬሽን የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ ጋሻው አይችሉህም ተናግረዋል።
via:- Addis Maleda
@YeneTube @FikerAssefa
በአካባቢው ላይ ያለው የእርስ በእርስ ግጭትም በአካባቢው በሚንቀሳቀሱ ታጣቂዎች በደረሰ ጥቃት የሦስት ሰዎች ሕይወት ማለፉንም የኢትዮጵያ ስኳር ኮርፖሬሽን የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ ጋሻው አይችሉህም ተናግረዋል።
via:- Addis Maleda
@YeneTube @FikerAssefa
የአማራ ክልል የመንግሥት ግዥና ንብረት ማስወገድ ኤጀንሲ የትራክተርና ሌሎች የግንባታ ዕቃዎችን ግዥ ለማከናወን ከአንድ ዓመት ከስምንት ወር በፊት በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ 400 ሚሊዮን ብር ገቢ በማድረግ ለጨረታ አሸናፊዎች የሚከፈል የውጭ ምንዛሬ ቢጠይቅም ማግኘት አለመቻሉን አስታወቀ።
በአማራ ክልል የግንባታ እና ሌሎች መሣሪያዎችን ለመግዛት ከ22 ወራት በላይ የውጭ ምንዛሬ በመጠበቅ ተፈላጊ ማሽነሪዎች ተገዝተው ባለመቅረባቸው በክልሉ ልማት ላይ ተጽዕኖ እያሳደረ ነው ሲል የአማራ ክልል የመንግሥት ግዥና ንብረት ማስወገድ ኤጀንሲ ገልጾል።
@YeneTube @FikerAssefa
በአማራ ክልል የግንባታ እና ሌሎች መሣሪያዎችን ለመግዛት ከ22 ወራት በላይ የውጭ ምንዛሬ በመጠበቅ ተፈላጊ ማሽነሪዎች ተገዝተው ባለመቅረባቸው በክልሉ ልማት ላይ ተጽዕኖ እያሳደረ ነው ሲል የአማራ ክልል የመንግሥት ግዥና ንብረት ማስወገድ ኤጀንሲ ገልጾል።
@YeneTube @FikerAssefa
በማዕከላዊ ጎንደር፣ ጭልጋ ወረዳ የቅማንት አርሶ አደሮች ከአማራ ክልል ልዩ ሃይል ጋር ግጭት ውስጥ መሆናቸውን ዋዜማ ዘግቧል፡፡
መስከረም 16 የክልሉ ልዩ ሃይል አይከል ከተማ ሲገባ፣ ታጣቂዎች ተኩስ ስለከፈቱበት ግጭቱ መቀስቀሱን የዐይን እማኞች ገልጸዋል፡፡ ጉላንግ እና ቡሆና በሚባሉ ቦታዎች እስከ ትናንት ተኩስ ተሰምቷል፡፡ የክልሉ መንግሥት በበኩሉ ታጣቂዎቹ ከሌላ ወገን ድጋፍ ያገኛሉ ይላል፡፡
@YeneTube @FikerAssefa
መስከረም 16 የክልሉ ልዩ ሃይል አይከል ከተማ ሲገባ፣ ታጣቂዎች ተኩስ ስለከፈቱበት ግጭቱ መቀስቀሱን የዐይን እማኞች ገልጸዋል፡፡ ጉላንግ እና ቡሆና በሚባሉ ቦታዎች እስከ ትናንት ተኩስ ተሰምቷል፡፡ የክልሉ መንግሥት በበኩሉ ታጣቂዎቹ ከሌላ ወገን ድጋፍ ያገኛሉ ይላል፡፡
@YeneTube @FikerAssefa
ኦዳ አዋርድ ለሶስተኛ ጊዜ ሊካሄድ ነው!
የኦዳ አዋርድ ሽልማት ለ3ኛ ግዜ በመጭው ጥቅምት 7 በሸራተን አዲስ እንደሚካሄድ ተገለፀ። በ15/1/2012 ዓ.ም በኢሊያና ሆቴል በተሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ እንደተገለጸው የሽልማቱ አላማ የኦሮሞን የኪነ ጥበብ ስራዎች በአዎንታዊ መልኩ ማበረታታትና የዘርፉን ባለሙያዎች ይበልጥ ማነቃቃት ነው።በዚህ ረገድ የበሻቱ ቶለማርያም መልቲ ሚዲያ በፋና ወጊነት የሚጠቀስ ሲሆን የሽልማት ስርአቱን በተመለከተ የኦሮምያ ባህልና ቱሪዝም ትብብር እንዳለም ተጠቅሷል።
Via Gulele Post
@YeneTube @FikerAssefa
የኦዳ አዋርድ ሽልማት ለ3ኛ ግዜ በመጭው ጥቅምት 7 በሸራተን አዲስ እንደሚካሄድ ተገለፀ። በ15/1/2012 ዓ.ም በኢሊያና ሆቴል በተሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ እንደተገለጸው የሽልማቱ አላማ የኦሮሞን የኪነ ጥበብ ስራዎች በአዎንታዊ መልኩ ማበረታታትና የዘርፉን ባለሙያዎች ይበልጥ ማነቃቃት ነው።በዚህ ረገድ የበሻቱ ቶለማርያም መልቲ ሚዲያ በፋና ወጊነት የሚጠቀስ ሲሆን የሽልማት ስርአቱን በተመለከተ የኦሮምያ ባህልና ቱሪዝም ትብብር እንዳለም ተጠቅሷል።
Via Gulele Post
@YeneTube @FikerAssefa
1702 ኪግ የሚመዝን አደንዛዥ ዕፅ ካናቢስ ተያዘ!
በቀን 18/01/2012 ከህብረተሰቡ በደረሰ ጥቆማ መሰረት በአፋር ክልል ዞን ሶስት ውስጥ ወረር(ልዩ ቦታ አምባሽ) በሚባል ስፍራ በአዋሽ ጉምሩክ ቅ/ፅ/ቤት የመረጃ ሰራተኞች እና ፌዴራል ፖሊስ ባደረጉት ከፍተኛ ክትትል በአብዱልከሪም መሀመድ(ተጠርጣሪ ግለሰብ) መጋዘን ውስጥ ተከማችቶ ያለው 1702 ኪሎ ግራም የሚመዝን ካናቢስ(kanabis) የሚባል አደገኛ እፅ በቁጥጥር ስር ዉሏል፡፡
Via የገቢዎች ሚኒስቴር
@YeneTube @FikerAssefa
በቀን 18/01/2012 ከህብረተሰቡ በደረሰ ጥቆማ መሰረት በአፋር ክልል ዞን ሶስት ውስጥ ወረር(ልዩ ቦታ አምባሽ) በሚባል ስፍራ በአዋሽ ጉምሩክ ቅ/ፅ/ቤት የመረጃ ሰራተኞች እና ፌዴራል ፖሊስ ባደረጉት ከፍተኛ ክትትል በአብዱልከሪም መሀመድ(ተጠርጣሪ ግለሰብ) መጋዘን ውስጥ ተከማችቶ ያለው 1702 ኪሎ ግራም የሚመዝን ካናቢስ(kanabis) የሚባል አደገኛ እፅ በቁጥጥር ስር ዉሏል፡፡
Via የገቢዎች ሚኒስቴር
@YeneTube @FikerAssefa
በካታር ዶሃ እየተካሄደ በሚገኘው የአለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና ኢትዮጵያ በወንዶች 5ሺህ ሜትር በሙክታር እንድሪስ ወርቅ በሰለሞን ባረጋ የብር ሜዳልያ አግኝታለች።
@YeneTube @FikerAssefa
@YeneTube @FikerAssefa
Literal meaning of country's name.
India: Land of the Indus
Iran: Land of Aryans
Japan: Land of rising sun
Egypt: Frontier
Nigeria: Land of the Niger river
Italy: Land of young cattle
France: Land of the Franks
Germany: Fertile land
China: Qin state
Indonesia: Indian islands
#Ethiopia: Land of burnt faces (Greece)
@YeneTube @FikerAssefa
India: Land of the Indus
Iran: Land of Aryans
Japan: Land of rising sun
Egypt: Frontier
Nigeria: Land of the Niger river
Italy: Land of young cattle
France: Land of the Franks
Germany: Fertile land
China: Qin state
Indonesia: Indian islands
#Ethiopia: Land of burnt faces (Greece)
@YeneTube @FikerAssefa
በካታር ዶሃ የአትሌቲክስ ቡድናችንን ለመደገፍ ወደ ስቴድዮም የገቡ ኢትዮጵያውያንን ልዩ ድባብ IAAF በአድናቆት በትዊተር ገፁ አጋርቶታል!
@YeneTube @FikerAssefa
@YeneTube @FikerAssefa
በታደሉ ዩኒፎርሞች ላይ ቅሬታ ያለው ማንኛውም ግለሰብ እንዲያሳውቅና አፋጣኝ ማስተካከያ እንደሚወስድ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር አሳውቋል።
"ከዩኒፎርም ስርጭት ጋር በተያያዘ መጠነኛ ቅሬታዎች እየቀረቡልን ይገኛሉ።
የከተማ አስተዳደሩ ዋነኛ አላማው ተማሪዎች በተለያዩ ችግሮች ምክንያት ትምህርታቸውን እንዳያቋርጡ ማድረግና እንዲሁም ወላጆችን ከጭንቀት ለማዳን ነው።የከተማ አስተዳደሩ የየትኛውንም ሀይማኖት አስተምህሮትም ይሁን ስርአት ያከብራል።ለተማሪዎች በነጻ የዩኒፎርም ስናዘጋጅም ይህን ባገናዘበ መልኩ ነው።
ነገር ግን አሁን እየተነሱ ያሉ ጥያቄዎች በስርጭት ወቅት የተፈጠሩ በመሆናቸው መስተካከል ይችላሉ።ከዩኒፎርም አቅራቢ ድርጅቶች ጋር ስምምነት ያለን በመሆኑ ለተማሪዎች በታደሉ ዩኒፎርሞች ላይ ቅሬታ ያለው ማንኛውም ግለሰብ እንዲያሳውቅና አፋጣኝ ማስተካከያ የምንወስድ መሆኑን እናስታውቃለን።"
- የከንቲባው ጽ/ቤት
@YeneTube @FikerAssefa
"ከዩኒፎርም ስርጭት ጋር በተያያዘ መጠነኛ ቅሬታዎች እየቀረቡልን ይገኛሉ።
የከተማ አስተዳደሩ ዋነኛ አላማው ተማሪዎች በተለያዩ ችግሮች ምክንያት ትምህርታቸውን እንዳያቋርጡ ማድረግና እንዲሁም ወላጆችን ከጭንቀት ለማዳን ነው።የከተማ አስተዳደሩ የየትኛውንም ሀይማኖት አስተምህሮትም ይሁን ስርአት ያከብራል።ለተማሪዎች በነጻ የዩኒፎርም ስናዘጋጅም ይህን ባገናዘበ መልኩ ነው።
ነገር ግን አሁን እየተነሱ ያሉ ጥያቄዎች በስርጭት ወቅት የተፈጠሩ በመሆናቸው መስተካከል ይችላሉ።ከዩኒፎርም አቅራቢ ድርጅቶች ጋር ስምምነት ያለን በመሆኑ ለተማሪዎች በታደሉ ዩኒፎርሞች ላይ ቅሬታ ያለው ማንኛውም ግለሰብ እንዲያሳውቅና አፋጣኝ ማስተካከያ የምንወስድ መሆኑን እናስታውቃለን።"
- የከንቲባው ጽ/ቤት
@YeneTube @FikerAssefa
ከመንግሥት ልማት ድርጅቶች መካከል አንዱ የሆነው የኢትዮጵያ ባዮፊዩል ኮርፖሬሽን የሚያስተዳድረው የቀንጢቻ ታንታለም ፋብሪካ ላለፉት ኹለት ዓመታት ሥራ በማቆሙ ለሠራተኞቹ ደሞዝ እንዲሁም ለሥራ ማስጀመርያ የሚሆን 132 ሚሊዮን ብር ከገንዘብ ሚኒስቴር እርዳታ ጠየቀ።
በኮርፖሬሽኑ የሕዝብ ግንኙነት ባለሙያ ቡልቲ ወዳጆ ለአዲስ ማለዳ እንደተናገሩት፣ ፋብሪካው ከተዘጋ አንስቶ ምንም ዓይነት ገቢ ባለማግኘቱ ላለፉት ስድስት ወራት ከመንግሥት በተገኛ 47 ሚሊዮን ብር የሠራተኞቹን ደሞዝ ሲከፍል የቆየ ቢሆንም በአሁኑ ወቅት ለሠራተኞቹ የሚከፍለው ገንዘብ የለውም።
ምንጭ: አዲስ ማለዳ
@YeneTube @FikerAssefa
በኮርፖሬሽኑ የሕዝብ ግንኙነት ባለሙያ ቡልቲ ወዳጆ ለአዲስ ማለዳ እንደተናገሩት፣ ፋብሪካው ከተዘጋ አንስቶ ምንም ዓይነት ገቢ ባለማግኘቱ ላለፉት ስድስት ወራት ከመንግሥት በተገኛ 47 ሚሊዮን ብር የሠራተኞቹን ደሞዝ ሲከፍል የቆየ ቢሆንም በአሁኑ ወቅት ለሠራተኞቹ የሚከፍለው ገንዘብ የለውም።
ምንጭ: አዲስ ማለዳ
@YeneTube @FikerAssefa
ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ ደመቀ መኮንን የኤካ ኮተቤ አጠቃላይ ሆስፒታል እና የኢትዮጵያ የአእምሮ ጤና ምርመር ኢንስቲትዩት ህንፃን በይፋ መርቀው ከፍተዋል።
#DPMOEthiopia
@YeneTube @FikerAssefa
#DPMOEthiopia
@YeneTube @FikerAssefa
የባህል መድሃኒት ጥናትና ምርምር ፍኖተ- ካርታ ይፋ ሆነ፡፡
የጤና ሚኒስቴር ከኢትዮጵያ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ጋር በመተባበር የባህል መድሃኒት ጥናትና ምርምር ፍኖተ ካርታ ይፋ አድርገዋል፡፡የፍኖተ-ካርታው ዋና አላማ ሃገር በቀል ዕዉቀትን በመሰነድና በመጠበቅ የተጠናከረ ጥናትና ምርምር ማከናወን፣ እንዲሁም ደረጃውን የጠበቀ የባህል ህክምና አገልግሎት በአገሪቱ እንዲሰጥ ለማድረግ የተዘጋጀ ተብላል፡፡ዶክተር ኤባ አባተ የኢንስቲትዩቱ ዋና ዳይሬክተር እንደገለጹት በአገራችን በአማካይ ወደ 80 በመቶ የሚሆነው ህዝብ የባህል መድሃኒት ተጠቃሚ ቢሆንም ለዘርፉ የተሰጠው ትኩረት ግን እምብዛም ነው ብለዋል፡፡
የጤና ጥበቃ ሚኒስትር ዶ/ር አሚር አማን በበኩላቸው ኢትዮጵያ ከ6 ሺህ 500 በላይ ፈዋሽ እጸዋት ቢኖራትም መጠቀም ግን አልተቻለም ብለዋል፡፡በመሆኑም ፍኖተ ካርታው በባህላዊ መድሃኒቶች ዙሪያ ጥናትና ምርምር እንዲደረግ ለባህላዊ መድሃኒት ቀማሚዎች ድጋፍ ለማድረግና ሌሎች ዘርፉን ማሳደግ የሚያስችሉ ስራዎች እንዲከናወኑ ያስችላል ተብሏል።በቀጣይ በባህል መድሃኒቶች ላይ የተለያዩ ጥናትና ምርምር በጋራ ለማድረግ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ከሁሉም የሃገሪቱ ዩኒቨርሲቲዎችና ከምርምር ተቋማት ጋር የመግባቢያ ሰነድ ተፈራርሟል፡፡ ጤና ጥበቃ ሚኒስቴር ፍኖተ ካርታው ተግባራዊ ለማድረግ 90 ሚሊዮን ብር እንደመደበ ነው የተገለጸው፡፡
Via Ethio FM
@YeneTube @FikerAssefa
የጤና ሚኒስቴር ከኢትዮጵያ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ጋር በመተባበር የባህል መድሃኒት ጥናትና ምርምር ፍኖተ ካርታ ይፋ አድርገዋል፡፡የፍኖተ-ካርታው ዋና አላማ ሃገር በቀል ዕዉቀትን በመሰነድና በመጠበቅ የተጠናከረ ጥናትና ምርምር ማከናወን፣ እንዲሁም ደረጃውን የጠበቀ የባህል ህክምና አገልግሎት በአገሪቱ እንዲሰጥ ለማድረግ የተዘጋጀ ተብላል፡፡ዶክተር ኤባ አባተ የኢንስቲትዩቱ ዋና ዳይሬክተር እንደገለጹት በአገራችን በአማካይ ወደ 80 በመቶ የሚሆነው ህዝብ የባህል መድሃኒት ተጠቃሚ ቢሆንም ለዘርፉ የተሰጠው ትኩረት ግን እምብዛም ነው ብለዋል፡፡
የጤና ጥበቃ ሚኒስትር ዶ/ር አሚር አማን በበኩላቸው ኢትዮጵያ ከ6 ሺህ 500 በላይ ፈዋሽ እጸዋት ቢኖራትም መጠቀም ግን አልተቻለም ብለዋል፡፡በመሆኑም ፍኖተ ካርታው በባህላዊ መድሃኒቶች ዙሪያ ጥናትና ምርምር እንዲደረግ ለባህላዊ መድሃኒት ቀማሚዎች ድጋፍ ለማድረግና ሌሎች ዘርፉን ማሳደግ የሚያስችሉ ስራዎች እንዲከናወኑ ያስችላል ተብሏል።በቀጣይ በባህል መድሃኒቶች ላይ የተለያዩ ጥናትና ምርምር በጋራ ለማድረግ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ከሁሉም የሃገሪቱ ዩኒቨርሲቲዎችና ከምርምር ተቋማት ጋር የመግባቢያ ሰነድ ተፈራርሟል፡፡ ጤና ጥበቃ ሚኒስቴር ፍኖተ ካርታው ተግባራዊ ለማድረግ 90 ሚሊዮን ብር እንደመደበ ነው የተገለጸው፡፡
Via Ethio FM
@YeneTube @FikerAssefa
ለጎንደር ዮኒቨርሲቲ ተማሪዎች በሙሉ፦
የ2012 የትምህርት ዘመን መግቢያ ቀናት ለነባር ተማሪዎች መስከረም 22 እና 23/2012ዓም እና ለአዲስ ገቢ ተማሪዎች ተማሪዎች መስከረም 28 እና 29/2012ዓ.ም እንደሆነ ማሳወቃችን ይታወሳል።
ነገር ግን በወቅታዊ ችግሮች ምክንያት የመግቢያ ቀናትን ማራዘም አስፈልጓል። ስለሆነም የነባር ተማሪዎች መግቢያ ቀናት ወደ መስከረም 29 እና 30/2012ዓ.ም እንዲሁም የአዲስ ገቢ ተማሪዎች መግቢያ ወደ ጥቅምት 6 እና 7 ቀን 2012ዓ.ም የተቀየረ መሆኑን ከይቅርታ ጋር እናሳውቃለን።
Via:- የጎንደር ዮኒቨርሲቲ
@YeneTube @Fikerassefa
የ2012 የትምህርት ዘመን መግቢያ ቀናት ለነባር ተማሪዎች መስከረም 22 እና 23/2012ዓም እና ለአዲስ ገቢ ተማሪዎች ተማሪዎች መስከረም 28 እና 29/2012ዓ.ም እንደሆነ ማሳወቃችን ይታወሳል።
ነገር ግን በወቅታዊ ችግሮች ምክንያት የመግቢያ ቀናትን ማራዘም አስፈልጓል። ስለሆነም የነባር ተማሪዎች መግቢያ ቀናት ወደ መስከረም 29 እና 30/2012ዓ.ም እንዲሁም የአዲስ ገቢ ተማሪዎች መግቢያ ወደ ጥቅምት 6 እና 7 ቀን 2012ዓ.ም የተቀየረ መሆኑን ከይቅርታ ጋር እናሳውቃለን።
Via:- የጎንደር ዮኒቨርሲቲ
@YeneTube @Fikerassefa