ቀዳማዊት እመቤት ዝናሽ ታያቸዉ ከኦሮሚያ ት/ት ቢሮ የምስክር ወረቀትና ለላቀ የትምህርት ልማት አጋርነት ሽልማት ተበረከተላቸዉ፡፡ሽልማቱን የኦሮሚያ ክልል ም/ር/መ አቶ ሽመልስ አብዲሳ የሰጡ ሲሆን የጽ/ቤቱ ዳይሬክተር አቶ ሙሉቀን ፈንታ በወኪልነት ተቀበልዋል፡፡
@YeneTube @Fikerassefa
@YeneTube @Fikerassefa
አምባሳደር ፍጹም አረጋ ትናንት መስከረም 11 ቀን 2012 ዓ.ም በዋሽንግተን ዲ.ሲ. የቅዱስ ሚካኤል ቤተ-ክርስቲያን 25ኛ ዓመት ኢዮቤልዮ በዓል ላይ በመገኘት መልዕክት አስተላልፈዋል።
በመልዕክታቸውም ህዝበ ክርስቲያኑ አገሩን እንዲወድ፣ ወገኑን እንዲረዳ፣ ባህሉን እንዲያስተዋውቅ ቤተክርስቲያኗ እያከናወነች ላለው አርዓያነት ያለው ስራ ምስጋና አቅርበዋል።በኢትዮጵያ የተጀመረው ለውጥ ግቡን እንዲመታና በአገር ቤትም እዚህም ያለውን ኢትዮጵያውያንና ትውልደ ኢትዮጵያውያን የሚጠቅም ለውጥ እንዲሆን አሁንም በዕውቀት፣ በገንዘብ፣ በስልጠናና በምክር ድጋፉ ተጠናክሮ እንዲቀጥል ጠይቀዋል።ኤምባሲው በዚህ አገር ለሚገኘው ህብረተሰባችን ቀልጣፋና አርኪ አገልግሎት ለመስጠት ከምንጊዜውም በላይ ዝግጁ መሆኑን ክቡር አምባሳደሩ ገልጸዋል።
ምንጭ:በዋሽንግተን የኢትዮጵያ ኤምባሲ
@YeneTube @FikerAssefa
በመልዕክታቸውም ህዝበ ክርስቲያኑ አገሩን እንዲወድ፣ ወገኑን እንዲረዳ፣ ባህሉን እንዲያስተዋውቅ ቤተክርስቲያኗ እያከናወነች ላለው አርዓያነት ያለው ስራ ምስጋና አቅርበዋል።በኢትዮጵያ የተጀመረው ለውጥ ግቡን እንዲመታና በአገር ቤትም እዚህም ያለውን ኢትዮጵያውያንና ትውልደ ኢትዮጵያውያን የሚጠቅም ለውጥ እንዲሆን አሁንም በዕውቀት፣ በገንዘብ፣ በስልጠናና በምክር ድጋፉ ተጠናክሮ እንዲቀጥል ጠይቀዋል።ኤምባሲው በዚህ አገር ለሚገኘው ህብረተሰባችን ቀልጣፋና አርኪ አገልግሎት ለመስጠት ከምንጊዜውም በላይ ዝግጁ መሆኑን ክቡር አምባሳደሩ ገልጸዋል።
ምንጭ:በዋሽንግተን የኢትዮጵያ ኤምባሲ
@YeneTube @FikerAssefa
ከካናዳ መጥቶ የሞተው የ 10 ሚሊዮን ዶላር ሎተሪ እድለኛው ሚካኤል ገብሩ ቀብር ተፈጸመ፡፡ካናዳዊ ዜግነት ያለው ሚካኤል በተወለደባትና በድንገት ባረፈባት ኢትዮጵያ በዛሬው ዕለት ግብአተ መሬቱ መፈጸሙን ሲቢሲ ዘግቧል፡፡
@YeneTube @FikerAssefa
@YeneTube @FikerAssefa
ይህንን ያውቁ ኖሯል?
አዶልፍ ሂትለር ፣ ጆሴፍ ስታሊንና ቤኒቶ ሙሶሎኒ በተለያየ ጊዜ በሰላም ዘርፍ ለኖቤል ሽልማት ታጭተው ነበር።
ስታሊን 23 ሚልዮን
ሂትለር 17 ሚልዮን
ሙሶሎኒ ደግሞ 430 ሺህ ሰዎችን ያስገደሉ ሲሆን ከ430 ሺህ ውስጥ 30,000 የሚሆኑት #በጣሊያን_ወረራ ጊዜ የተገደሉ #ኢትዮጵያዊን ናቸው።
@YeneTube @FikerAssefa
አዶልፍ ሂትለር ፣ ጆሴፍ ስታሊንና ቤኒቶ ሙሶሎኒ በተለያየ ጊዜ በሰላም ዘርፍ ለኖቤል ሽልማት ታጭተው ነበር።
ስታሊን 23 ሚልዮን
ሂትለር 17 ሚልዮን
ሙሶሎኒ ደግሞ 430 ሺህ ሰዎችን ያስገደሉ ሲሆን ከ430 ሺህ ውስጥ 30,000 የሚሆኑት #በጣሊያን_ወረራ ጊዜ የተገደሉ #ኢትዮጵያዊን ናቸው።
@YeneTube @FikerAssefa
ባለፈው ሳምንት በሳውዲው የነዳጅ ማቀነባበሪያ የድሮን ጥቃት መድረሱ ይታወቃል።
ዛሬ ዩናይትድ ኪንግደም ፤ ፈረንሳይ መንግስት እና የጀርመን መንግስት ባወጡት መግለጫ ከሳውዲሁ የድሮን ጥቃት ጀርባ #ኢራን እንዳለችበት ሀገራቱ አስታውቀዋል።
@YeneTube @FikerAssefa
ዛሬ ዩናይትድ ኪንግደም ፤ ፈረንሳይ መንግስት እና የጀርመን መንግስት ባወጡት መግለጫ ከሳውዲሁ የድሮን ጥቃት ጀርባ #ኢራን እንዳለችበት ሀገራቱ አስታውቀዋል።
@YeneTube @FikerAssefa
#ታመናል♥
#አቡሽ_ዘለቀ
ይቅርታ ፕሮፌሰር አንድ ጥያቄ ነበረኝ
ዌል መጀመሪያ ሂድና በዘርህ ተደራጅተህ ና
ታመናል ታመናል ታመናል በጣም ...
ሃያ ሰላሳ አመት ፊደል ቆጥረን አውቀን
የተሻለ ሃሳብ እንዴት ማምጣት አቃተን
ዛሬም የዘር ሃረግ ገመድ የሚጠልፈን
ሁሉም የየራሱን ገንብቶ ካጠረ
ሁሉም የየራሱን ዘር ከመለመለ
የአብሮነትን ካባ ማን ሊያለብሰን መልሶ
ለሩብ ክ/ዘመን የበረደን መች አንሶ
ከየትኛው ክልል ነው ከየትኛው ከተማ
ከዚያኛው ሰፈር ነው ከዛ ጎሳ መጣ
መቼ ነው የሚለቀን እናስተውል ለአንድ አፍታ
ይበቃል እንራቀው ይህን ክፉ በሽታ
ታመናል
እርምእርም ርምርም ስንት ሺህ አመት ልኖር
እርምእርም ርምርም ከህሊናዬ ርቄ
እርምእርም ርምርም በቀል ተንኮል ክፋት ለትውልድ አውርሼ
እርምእርም ርምርም ከጎዳናው ልውደቅ ልለምን አንጥፌ
እርምእርም ርምርም ሆዴን ከምሞላው ሰው ከሰው አራርቄ
ሃያ ሰላሳ አመት ፊደል ቆጥረን አውቀን
የተሻለ ሃሳብ እንዴት ማምጣት አቃተን
ዛሬም የዘር ሃረግ ገመድ የሚጠልፈን
ምክንያት እየፈለግን ሰበብ እየፈጠርን
በትንሽ ትልቁ ጦር እየተማዘዝን
አይደለም የሚበጀን
አይደለም የሚጠቅመን
በቀን ሶስቴ እንኳን መብላት እያቃተን
የማን ዘር ነው ከእሳት ከመብረቅ የተሰራ
የማን ዘር ነው ከጭድ ከሰበዝ የተሰራ
አንዱን እያሳነስክ አንዱን አታግዝፈው
ሆዱ አምላክ አትሁን ፍቅር ስበክ አንተ ሰው
እርምእርም ርምርም የት ነው የተማሩት
እርምእርም ርምርም እነኛ የአድዋ ጀግኖች
እርምእርም ርምርም የት ነው የተማሩት
እርምእርም ርምርም እነኛ የአድዋ አርበኞች
እርምእርም ርምርም ከራሳቸው አልፈው
እርምእርም ርምርም ምሳሌ የሆኑት ለአለም
እርምእርም ርምርም ለሰው እንጂ ለፀብ ስለታደሉ አይደለም
...ጌጡ ተመስገን እንደፃፈው....
@YeneTube @Fikerassefa
#አቡሽ_ዘለቀ
ይቅርታ ፕሮፌሰር አንድ ጥያቄ ነበረኝ
ዌል መጀመሪያ ሂድና በዘርህ ተደራጅተህ ና
ታመናል ታመናል ታመናል በጣም ...
ሃያ ሰላሳ አመት ፊደል ቆጥረን አውቀን
የተሻለ ሃሳብ እንዴት ማምጣት አቃተን
ዛሬም የዘር ሃረግ ገመድ የሚጠልፈን
ሁሉም የየራሱን ገንብቶ ካጠረ
ሁሉም የየራሱን ዘር ከመለመለ
የአብሮነትን ካባ ማን ሊያለብሰን መልሶ
ለሩብ ክ/ዘመን የበረደን መች አንሶ
ከየትኛው ክልል ነው ከየትኛው ከተማ
ከዚያኛው ሰፈር ነው ከዛ ጎሳ መጣ
መቼ ነው የሚለቀን እናስተውል ለአንድ አፍታ
ይበቃል እንራቀው ይህን ክፉ በሽታ
ታመናል
እርምእርም ርምርም ስንት ሺህ አመት ልኖር
እርምእርም ርምርም ከህሊናዬ ርቄ
እርምእርም ርምርም በቀል ተንኮል ክፋት ለትውልድ አውርሼ
እርምእርም ርምርም ከጎዳናው ልውደቅ ልለምን አንጥፌ
እርምእርም ርምርም ሆዴን ከምሞላው ሰው ከሰው አራርቄ
ሃያ ሰላሳ አመት ፊደል ቆጥረን አውቀን
የተሻለ ሃሳብ እንዴት ማምጣት አቃተን
ዛሬም የዘር ሃረግ ገመድ የሚጠልፈን
ምክንያት እየፈለግን ሰበብ እየፈጠርን
በትንሽ ትልቁ ጦር እየተማዘዝን
አይደለም የሚበጀን
አይደለም የሚጠቅመን
በቀን ሶስቴ እንኳን መብላት እያቃተን
የማን ዘር ነው ከእሳት ከመብረቅ የተሰራ
የማን ዘር ነው ከጭድ ከሰበዝ የተሰራ
አንዱን እያሳነስክ አንዱን አታግዝፈው
ሆዱ አምላክ አትሁን ፍቅር ስበክ አንተ ሰው
እርምእርም ርምርም የት ነው የተማሩት
እርምእርም ርምርም እነኛ የአድዋ ጀግኖች
እርምእርም ርምርም የት ነው የተማሩት
እርምእርም ርምርም እነኛ የአድዋ አርበኞች
እርምእርም ርምርም ከራሳቸው አልፈው
እርምእርም ርምርም ምሳሌ የሆኑት ለአለም
እርምእርም ርምርም ለሰው እንጂ ለፀብ ስለታደሉ አይደለም
...ጌጡ ተመስገን እንደፃፈው....
@YeneTube @Fikerassefa
ስፖርት!!
የ2019 የፊፋ የዓመቱ ምርጦች በጣልያን ሚላን ይፋ ተደርገዋል!
📌የዓመቱ ምርጥ ወንድ ተጫዋች- ሊዮኔል ሜሲ
📌የዓመቱ ምርጥ ሴት ተጫዋች- ሜጋን ራፒኖ
📌የዓመቱ ምርጥ የወንድ አሰልጣኝ- የርገን ክሎፕ
📌የዓመቱ ምርጥ የሴት አሰልጣኝ- ጂል ኤሊስ
📌የዓመቱ ምርጥ ወንድ ግብ ጠባቂ- አሊሰን ቤከር
📌የዓመቱ ምርጥ ሴት ግብ ጠባቂ- ሳሪ ቫን ቬነንዳል
📌የዓመቱ ምርጥ ግብ/ ፑሽካሽ ሽልማት ዳንዬል ዝሶሪ
📌የዓመቱ ስፖርታዊ ጨዋነት ተሸላሚ- አሰልጣኝ ማርሴሎ ቤልሳ እና ሊድስ ዩናይትድ
📌የዓመቱ ምርጥ ደጋፊዎች- ሲልቫ ግሪኮ ተሸላሚ ሆነዋል።
@YeneTube @FikerAssefa
የ2019 የፊፋ የዓመቱ ምርጦች በጣልያን ሚላን ይፋ ተደርገዋል!
📌የዓመቱ ምርጥ ወንድ ተጫዋች- ሊዮኔል ሜሲ
📌የዓመቱ ምርጥ ሴት ተጫዋች- ሜጋን ራፒኖ
📌የዓመቱ ምርጥ የወንድ አሰልጣኝ- የርገን ክሎፕ
📌የዓመቱ ምርጥ የሴት አሰልጣኝ- ጂል ኤሊስ
📌የዓመቱ ምርጥ ወንድ ግብ ጠባቂ- አሊሰን ቤከር
📌የዓመቱ ምርጥ ሴት ግብ ጠባቂ- ሳሪ ቫን ቬነንዳል
📌የዓመቱ ምርጥ ግብ/ ፑሽካሽ ሽልማት ዳንዬል ዝሶሪ
📌የዓመቱ ስፖርታዊ ጨዋነት ተሸላሚ- አሰልጣኝ ማርሴሎ ቤልሳ እና ሊድስ ዩናይትድ
📌የዓመቱ ምርጥ ደጋፊዎች- ሲልቫ ግሪኮ ተሸላሚ ሆነዋል።
@YeneTube @FikerAssefa
መርማሪ ፖሊስ ላይ ቅጣት የጣሉት ዳኛ ጥቃት ደረሰባቸው።
በአማራ ክልል ምዕራብ ጎንደር አርማጨሆ የወረዳ ፍርድ ቤት ዳኛ የሆኑት አቤሴሎም ተበጀ ነሐሴ 29/ 2011 ለስምንት ተከታታይ ጊዜ የሰጡትን ትዕዛዝ ባለመፈፀም እና ችሎቱን በመድፈር አንድ የፖሊስ አባል ላይ የሰጡትን ፍርድ ተከትሎ፣ ዳኛውን ለማሰር ሙከራ የተደረገ ሲሆን ዳኛው በተፈጠረባቸው የደኅንነት ስጋት ከተማውን ለቀው እንዲወጡ ተደረገ።
በፍትሃብሔር ክርክር መዝገብ ተከሳሽ የሆኑትን አስናቀ አባተን ይዘው እንዲያቀርቡ ስምንት ተከታታይ ትዕዛዝ የተሰጣቸው ምክትል መርማሪ ብርሃኑ እንቁ ማርያም፣ ትዕዛዙን ያልፈፀሙ ሲሆን በችሎት ቀርበውም ምክንያታቸውን ለማስረዳት ፈቃደኛ አልነበሩም።
ምንጭ: አዲስ ማለዳ
@YeneTube @FikerAssefa
በአማራ ክልል ምዕራብ ጎንደር አርማጨሆ የወረዳ ፍርድ ቤት ዳኛ የሆኑት አቤሴሎም ተበጀ ነሐሴ 29/ 2011 ለስምንት ተከታታይ ጊዜ የሰጡትን ትዕዛዝ ባለመፈፀም እና ችሎቱን በመድፈር አንድ የፖሊስ አባል ላይ የሰጡትን ፍርድ ተከትሎ፣ ዳኛውን ለማሰር ሙከራ የተደረገ ሲሆን ዳኛው በተፈጠረባቸው የደኅንነት ስጋት ከተማውን ለቀው እንዲወጡ ተደረገ።
በፍትሃብሔር ክርክር መዝገብ ተከሳሽ የሆኑትን አስናቀ አባተን ይዘው እንዲያቀርቡ ስምንት ተከታታይ ትዕዛዝ የተሰጣቸው ምክትል መርማሪ ብርሃኑ እንቁ ማርያም፣ ትዕዛዙን ያልፈፀሙ ሲሆን በችሎት ቀርበውም ምክንያታቸውን ለማስረዳት ፈቃደኛ አልነበሩም።
ምንጭ: አዲስ ማለዳ
@YeneTube @FikerAssefa
ወደ ሲ ኤም ሲ የሚያመራው የባቡር መስመር ላይ አንድ የጭነት ተሽከርካሪ ወደ ሃዲዱ በመግባቱ የባቡር ትራንስፖርት ተቋረጠ!
የአዲስ አበባ ቀላል ባቡር አገልግሎት ወደ ሲኤምሲ የሚያቀናው መስመር ዛሬ ከነጋ ጀምሮ አገልግሎቱ ተቋርጧል። ለአገልግሎቱ መቋረጥ ምክንያት አንድ ኤፍ ኤስ አር አይሱዙ ተሽከርካሪ ለሌት ላይ በመሪና ሲኤም ሲ መካከል የባቡር አጥሩን ጥሶ ወደ ሃዲዱ በመግባቱ ዛሬ ከነጋ ጀምሮ አገልግሎት መስጠት አልቻለም ሲሉ የአዲስ አበባ ቀላል ባቡር ስራሲኪያጅ አቶ ሙሉቀን አሰፋ ለኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት ገልጸዋል።
ጉዳቱ የከፋ ባለመሆኑ መኪናውን አንስተን እና ባለሙያዎች ሁኔታውን ፈትሸው በ45 ደቂቃ ውስጥ አገልግሎቱ ይጀምራል ብለዋል ስራሰኪያጁ።አቶ ሙሉቀን አያይዘውም እንዲህ ያሉ አደጋዎች በተለያዩ አካባቢዎች በተደጋጋሚ እንደሚከሰቱ ገልጸው ጉዳቱ ከመሰረተ ልማቱ ባሻገር ደንበኞቻችንን ለእንግልት እየዳረጋቸው ነው ብለዋል።
Via EPA
@YeneTube @FikerAssefa
የአዲስ አበባ ቀላል ባቡር አገልግሎት ወደ ሲኤምሲ የሚያቀናው መስመር ዛሬ ከነጋ ጀምሮ አገልግሎቱ ተቋርጧል። ለአገልግሎቱ መቋረጥ ምክንያት አንድ ኤፍ ኤስ አር አይሱዙ ተሽከርካሪ ለሌት ላይ በመሪና ሲኤም ሲ መካከል የባቡር አጥሩን ጥሶ ወደ ሃዲዱ በመግባቱ ዛሬ ከነጋ ጀምሮ አገልግሎት መስጠት አልቻለም ሲሉ የአዲስ አበባ ቀላል ባቡር ስራሲኪያጅ አቶ ሙሉቀን አሰፋ ለኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት ገልጸዋል።
ጉዳቱ የከፋ ባለመሆኑ መኪናውን አንስተን እና ባለሙያዎች ሁኔታውን ፈትሸው በ45 ደቂቃ ውስጥ አገልግሎቱ ይጀምራል ብለዋል ስራሰኪያጁ።አቶ ሙሉቀን አያይዘውም እንዲህ ያሉ አደጋዎች በተለያዩ አካባቢዎች በተደጋጋሚ እንደሚከሰቱ ገልጸው ጉዳቱ ከመሰረተ ልማቱ ባሻገር ደንበኞቻችንን ለእንግልት እየዳረጋቸው ነው ብለዋል።
Via EPA
@YeneTube @FikerAssefa
በጋሞ ዞን አርባ ምንጭ ከተማ የ8ኪሎ ሜትር ተጓዥ የጎዳና ላይ ሩጫ ተካሄደ
በአርባ ምንጭ ከተማ ዛሬ ጧት ላይ የተካሄደው የ8ኪሎ ሜትር ተጓዥ የጎዳና ላይ ሩጫ ተተኪዎችን ለማፍራት፣ ከተማዋን ለማስተዋወቅ እና የሰላምና የፍቅር ትስስርን ለማዳበር ያለመ ነው ተብሏል።
በዚህ የጎዳና ላይ ሩጫ አሊ ቢፍቶ ማላ ከደቡብ ፖሊስ አትሌቲክስ ክለብ 1ኛ ሲወጣ ፣ የግል ተወዳዳሪ የሆነው እርገጤ ኤሌ እና ልኡል ወልዴ ከወላይታ ሶዶ በቅደም ተከተል 2ኛና 3ኛ ደረጃን ይዘው አጠናቀዋል።
የፓን ኢትዮጵያ መስራችና ስራ አስኪያጅ የሆነችው አትሌት ፋንቱ ሜጌሶ ውድድሩን ማዘጋጀቷ ተመልክቷል፡፡
በሩጫው ላይ አትሌት ፋንቱ ሜጌሶን ጨምሮ የቀድሞዋ ቀዳማዊት እመቤት ወይዘሮ ሮማን ተስፋዬ እና አትሌት መሃመድ አማን ተገኝተዋል።
የሩጫው መሪ ቃል “ትንሽ ጥላቻ ትልቅ ፍቅርን አያጠፋም” የሚል ነው።
ከሩጫው በመቀጠል በጎፋ ዞን በዛሬው ዕለትም የቋንቋ እና የባህል ሲምፖዚየም ይካሄዳል፡፡
ሪፖርተር᎓- EBC
@YeneTube @Fikerassefa
በአርባ ምንጭ ከተማ ዛሬ ጧት ላይ የተካሄደው የ8ኪሎ ሜትር ተጓዥ የጎዳና ላይ ሩጫ ተተኪዎችን ለማፍራት፣ ከተማዋን ለማስተዋወቅ እና የሰላምና የፍቅር ትስስርን ለማዳበር ያለመ ነው ተብሏል።
በዚህ የጎዳና ላይ ሩጫ አሊ ቢፍቶ ማላ ከደቡብ ፖሊስ አትሌቲክስ ክለብ 1ኛ ሲወጣ ፣ የግል ተወዳዳሪ የሆነው እርገጤ ኤሌ እና ልኡል ወልዴ ከወላይታ ሶዶ በቅደም ተከተል 2ኛና 3ኛ ደረጃን ይዘው አጠናቀዋል።
የፓን ኢትዮጵያ መስራችና ስራ አስኪያጅ የሆነችው አትሌት ፋንቱ ሜጌሶ ውድድሩን ማዘጋጀቷ ተመልክቷል፡፡
በሩጫው ላይ አትሌት ፋንቱ ሜጌሶን ጨምሮ የቀድሞዋ ቀዳማዊት እመቤት ወይዘሮ ሮማን ተስፋዬ እና አትሌት መሃመድ አማን ተገኝተዋል።
የሩጫው መሪ ቃል “ትንሽ ጥላቻ ትልቅ ፍቅርን አያጠፋም” የሚል ነው።
ከሩጫው በመቀጠል በጎፋ ዞን በዛሬው ዕለትም የቋንቋ እና የባህል ሲምፖዚየም ይካሄዳል፡፡
ሪፖርተር᎓- EBC
@YeneTube @Fikerassefa
የወላይታ ዞን ዋና አስተዳዳሪ በጋሞ ማስቃላ ክብረ-በዓል ላይ ለመታደም አርባ ምንጭ ናቸው፡፡
በወላይታ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ዳጋቶ ኩምቤ የተመራ ከፍተኛ አመራር በጋሞ "ዩ-ማስቃላ" ክብረ-በዓል ላይ ለመታደም ወደ አርባ ምንጭ አምርተዋል፡፡
አቶ ዳጋቶ የወንድም ወላይታ ህዝብን የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት ለጋሞ ህዝብ እንደሚያቀርቡ ተገልጿል፡፡
የወላይታ ህዝብ በወንድም የጋሞ ህዝብ የዘመን መለወጫ በዓል ላይ በመሪው መወከሉ የሁለቱ ህዝቦች ወንድማማችነት ከጉርብትናም በላይ ትልቅ ትርጉም ያለው መሆኑን የሚያሳይ እንደሆነ ተገልጿል፡፡
የአቶ ዳጋቶ ኩምቤ የአርባ ምንጭ ጉብኝት ለቀጣይ የጋሞ እና ወላይታ የህዝብ-ለህዝብ ግንኙነት መጠናከር ዓይነተኛ ሚና ይኖረዋል፡፡
Via:- GMN
@YeneTube @Fikerassefa
በወላይታ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ዳጋቶ ኩምቤ የተመራ ከፍተኛ አመራር በጋሞ "ዩ-ማስቃላ" ክብረ-በዓል ላይ ለመታደም ወደ አርባ ምንጭ አምርተዋል፡፡
አቶ ዳጋቶ የወንድም ወላይታ ህዝብን የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት ለጋሞ ህዝብ እንደሚያቀርቡ ተገልጿል፡፡
የወላይታ ህዝብ በወንድም የጋሞ ህዝብ የዘመን መለወጫ በዓል ላይ በመሪው መወከሉ የሁለቱ ህዝቦች ወንድማማችነት ከጉርብትናም በላይ ትልቅ ትርጉም ያለው መሆኑን የሚያሳይ እንደሆነ ተገልጿል፡፡
የአቶ ዳጋቶ ኩምቤ የአርባ ምንጭ ጉብኝት ለቀጣይ የጋሞ እና ወላይታ የህዝብ-ለህዝብ ግንኙነት መጠናከር ዓይነተኛ ሚና ይኖረዋል፡፡
Via:- GMN
@YeneTube @Fikerassefa
የኢትዮጵያ፣ የኤርትራና የሶማሊያ መሪዎች ሸልማት ተበረከተላቸው፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አህመድ፣ የሶማሊያው ፕሬዝዳንት ሞሃመድ ፋርማጆ እና ፕሬዝዳንት ኢሳያስ አፈወርቂ በጋራ በአፍሪካ ቀንድ አበረከቱት ለተባለ የለውጥና የመልካም ግንኙነት አስተዋጽኦ ሽልማት ተበረከተላቸው።የኮንኮርዲያ ሊደርሽፕ አዋርድ የተባለውን ሽልማት የተቀበሉት የሶማሊያው ፕሬዝዳንት ሲሆኑ፤ ሽልማቱ የሚበረከተው ኒው ዮርክ ውስጥ በየዓመቱ ከተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ጠቅላላ ጉባኤ ጎን ለጎን በሚካሄደው የኮንኮርዲያ ስብሰባ ላይ ነው።
የሽልማቱን መበርከት ይፋ ያደረገው የሶማሊያው ፕሬዝዳንት ጽህፈት ቤት በትዊተር ገጹ ላይ ባሰፈረው መልዕክትና ፎቶግራፍ ነው።የኮንኮርዲያ ሊደርሽፕ አዋርድ ውጤታማ ሥራን በማከናወን ሌሎችን አነሳስተዋል ተብለው የሚታመኑ፤ ለትርፍ ያልተቋቋሙ የሕዝብና የግል ተቋማት ውስጥ የመሪነት ሚና ለሚጫወቱ መሪዎች እንደሚበረከት የሽልማቱ አዘጋጆች በገጻቸው ላይ አስፍረዋል።
Via ቢቢሲ
@YeneTube @FikerAssefa
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አህመድ፣ የሶማሊያው ፕሬዝዳንት ሞሃመድ ፋርማጆ እና ፕሬዝዳንት ኢሳያስ አፈወርቂ በጋራ በአፍሪካ ቀንድ አበረከቱት ለተባለ የለውጥና የመልካም ግንኙነት አስተዋጽኦ ሽልማት ተበረከተላቸው።የኮንኮርዲያ ሊደርሽፕ አዋርድ የተባለውን ሽልማት የተቀበሉት የሶማሊያው ፕሬዝዳንት ሲሆኑ፤ ሽልማቱ የሚበረከተው ኒው ዮርክ ውስጥ በየዓመቱ ከተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ጠቅላላ ጉባኤ ጎን ለጎን በሚካሄደው የኮንኮርዲያ ስብሰባ ላይ ነው።
የሽልማቱን መበርከት ይፋ ያደረገው የሶማሊያው ፕሬዝዳንት ጽህፈት ቤት በትዊተር ገጹ ላይ ባሰፈረው መልዕክትና ፎቶግራፍ ነው።የኮንኮርዲያ ሊደርሽፕ አዋርድ ውጤታማ ሥራን በማከናወን ሌሎችን አነሳስተዋል ተብለው የሚታመኑ፤ ለትርፍ ያልተቋቋሙ የሕዝብና የግል ተቋማት ውስጥ የመሪነት ሚና ለሚጫወቱ መሪዎች እንደሚበረከት የሽልማቱ አዘጋጆች በገጻቸው ላይ አስፍረዋል።
Via ቢቢሲ
@YeneTube @FikerAssefa
በራይድ ትራንስፖርት አገልግሎት እና ዛይ ራይድ ሜትር ታክሲ መካከል ከንግድ ስም ባለቤትነት እና ከፈጠራ ባለቤትነት መብቶች ጋር በተያያዘ በተነሳው ውዝግብ ራይድ ባቀረበው አቤቱታ መሰረት በንግድ ውድድር እና ሸማቾች ጥበቃ ባለሥልጣን ምርመራ ተጀመረ።
ከአራት ወራት በፊት ራይድ ትራንስፖርት አገልግሎት የስያሜው የባለቤትነት መብት ይገባኛል በሚል ለኢትዮጵያ አእምሯዊ ንብረት ጽሕፈት ቤት እና ለንግድ ውድድር እና ሸማቾች መብት ጥበቃ ባለሥልጣን ማመልከቻ ማስገባቱን ተከትሎ ነው ምርመራው የተጀመረው።
Via:- Addis Maleda
@YeneTube @Fikerassefa
ከአራት ወራት በፊት ራይድ ትራንስፖርት አገልግሎት የስያሜው የባለቤትነት መብት ይገባኛል በሚል ለኢትዮጵያ አእምሯዊ ንብረት ጽሕፈት ቤት እና ለንግድ ውድድር እና ሸማቾች መብት ጥበቃ ባለሥልጣን ማመልከቻ ማስገባቱን ተከትሎ ነው ምርመራው የተጀመረው።
Via:- Addis Maleda
@YeneTube @Fikerassefa
የጋሞ ዞን አስተዳዳሪ ለወላይታ ዞን አቻቸው ደማቅ አቀባበል አደረጉላቸው፡፡
ም/አስተዳዳሪ ብርሃኑ ዘውዴ ለወላይታ ዞን ዋና አስተዳደሪ ዳጋቶ ኩምቤ እና ልዑካቸው ደማቅ አቀባበል አድርገዋል፡፡
አስተዳዳሪዎቹ የሁለቱን ወንድማማች ህዝቦች ግንኙነት ወደላቀ ደረጃ ለማሸጋገር እንደሚሰሩ የተገለፀ ሲሆን በህዝብ ለህዝብ ግንኙነቱ ዙሪያ እና ሌሎች ጉዳዮች ላይ ተነጋግረዋል፡፡
ዋና አስተዳዳሪ ዳጋቶ ኩምቤ በጋሞዎች ዩ ማሰቃላ በዓል ላይ ለመገኘት አርባ ምንጭ የመጡ ሲሆን የጋሞ ዞን አቻቸው በተመሣሣይ በወላይታ የጊፋታ በዓል ላይ እንደሚገኙ ተገልጿል፡፡
Via :- GMN
@YeneTube @Fikerassefa
ም/አስተዳዳሪ ብርሃኑ ዘውዴ ለወላይታ ዞን ዋና አስተዳደሪ ዳጋቶ ኩምቤ እና ልዑካቸው ደማቅ አቀባበል አድርገዋል፡፡
አስተዳዳሪዎቹ የሁለቱን ወንድማማች ህዝቦች ግንኙነት ወደላቀ ደረጃ ለማሸጋገር እንደሚሰሩ የተገለፀ ሲሆን በህዝብ ለህዝብ ግንኙነቱ ዙሪያ እና ሌሎች ጉዳዮች ላይ ተነጋግረዋል፡፡
ዋና አስተዳዳሪ ዳጋቶ ኩምቤ በጋሞዎች ዩ ማሰቃላ በዓል ላይ ለመገኘት አርባ ምንጭ የመጡ ሲሆን የጋሞ ዞን አቻቸው በተመሣሣይ በወላይታ የጊፋታ በዓል ላይ እንደሚገኙ ተገልጿል፡፡
Via :- GMN
@YeneTube @Fikerassefa
አራት የኢንዱስትሪ ፓርኮች በታኅሣሥ መጨረሻ ለባለሀብቶች ይተላለፋሉ
አራት ክልሎች በመገንባት ላይ የሚገኙ የግብርና ምርት ማቀነባበሪያ ኢንዱስትሪ ፓርኮች በታኅሣሥ መጨረሻ ለባለሀብቶች እንደሚተላለፉ የንግድና ኢንዱስትሪ ሚኒስቴር አስታወቀ።
«ክልሎች ባልተጠና መልኩ ሕገወጥ የኢንዱስትሪ ፓርክ ግንባታ መጀመራቸውም አስግቶኛል››ብሏል።
@YeneTube @Fikerassefa
አራት ክልሎች በመገንባት ላይ የሚገኙ የግብርና ምርት ማቀነባበሪያ ኢንዱስትሪ ፓርኮች በታኅሣሥ መጨረሻ ለባለሀብቶች እንደሚተላለፉ የንግድና ኢንዱስትሪ ሚኒስቴር አስታወቀ።
«ክልሎች ባልተጠና መልኩ ሕገወጥ የኢንዱስትሪ ፓርክ ግንባታ መጀመራቸውም አስግቶኛል››ብሏል።
@YeneTube @Fikerassefa
የአሜሪካው ቦይንግ ኩባንያ በቦይንግ 737 ማክስ 8 አውሮፕላን አደጋ ተጎጂ ቤተሰቦች ለእያንዳንዳቸው 144 ሺህ 500 የአሜሪካ ዶላር ድጋፍ ሊያደርግ መሆኑ ተገለፀ።
ድጋፉ ቦይንግ ባሳለፍነው ሰኔ ወር ላይ ድጋፍ ለማድረግ ቃል ከገባው 100 ሚሊየን የአሜሪካ ዶላይ የገንዘብ ድጋፍ ውስጥ የሚሰጥ መሆኑም ተነግሯል።
ከአውሮፓውያኑ 2020 በፊት ለሚያመለክቱ ለእያንዳንዱ የቦይንግ 737 ማክስ 8 አውሮፕላን አደጋ ተጎጂ ቤተሰቦች እና ዘመዶች ገንዘቡ የሚሰጥ መሆኑንም ነው ኩባንያው ያስታወቀው።
ቦይንግ ኩባንያ ገንዘቡ በኢትዮጵያ አየር መንገድ እና በኢንዶኒዢያው ላየን ኤይር ባጋጠመው ሁለት የአውሮፕላን አደጋዎች ህይወታቸውን ላጡ የ346 ሰዎች ቤተሰቦች እና ተፅዕኖ ለደረሰባቸው ማኅበረሰቦች መደገፊያ የሚውል መሆኑም ገልጾ ነበር።
ኩባንያው ከ100 ሚሊየን ዶላሩ ውስጥም ግማሹ ለተጎጂ ቤተሰቦች እና ዘመዶች በቀጥታ የሚከፈል መሆኑን እና ቀሪው 50 ሚሊየን ዶላር ደግሞ አደጋው ተዕእኖ ለተፈጠረባቸው ማህበረሰቦች ለትምህርት ቤትና ሌሎች የልማት ስራዎች እንደሚውል ነው ያስታወቀው።
ተጨማሪ ለማንበብ⬇️
https://telegra.ph/YYenetube-09-24
ድጋፉ ቦይንግ ባሳለፍነው ሰኔ ወር ላይ ድጋፍ ለማድረግ ቃል ከገባው 100 ሚሊየን የአሜሪካ ዶላይ የገንዘብ ድጋፍ ውስጥ የሚሰጥ መሆኑም ተነግሯል።
ከአውሮፓውያኑ 2020 በፊት ለሚያመለክቱ ለእያንዳንዱ የቦይንግ 737 ማክስ 8 አውሮፕላን አደጋ ተጎጂ ቤተሰቦች እና ዘመዶች ገንዘቡ የሚሰጥ መሆኑንም ነው ኩባንያው ያስታወቀው።
ቦይንግ ኩባንያ ገንዘቡ በኢትዮጵያ አየር መንገድ እና በኢንዶኒዢያው ላየን ኤይር ባጋጠመው ሁለት የአውሮፕላን አደጋዎች ህይወታቸውን ላጡ የ346 ሰዎች ቤተሰቦች እና ተፅዕኖ ለደረሰባቸው ማኅበረሰቦች መደገፊያ የሚውል መሆኑም ገልጾ ነበር።
ኩባንያው ከ100 ሚሊየን ዶላሩ ውስጥም ግማሹ ለተጎጂ ቤተሰቦች እና ዘመዶች በቀጥታ የሚከፈል መሆኑን እና ቀሪው 50 ሚሊየን ዶላር ደግሞ አደጋው ተዕእኖ ለተፈጠረባቸው ማህበረሰቦች ለትምህርት ቤትና ሌሎች የልማት ስራዎች እንደሚውል ነው ያስታወቀው።
ተጨማሪ ለማንበብ⬇️
https://telegra.ph/YYenetube-09-24
ፕሬዚዳንት ሳህለወርቅ ዘውዴ በአፍሪካ የሰላም፣ የደህንነትና የልማት ጉዳይ ላይ በመከረው መድረክ ላይ ተሳተፉ።
መድረኩ በጀርመኗ መራሄተ መንግስት አንጌላ ሜርክል የተመራ ሲሆን፥ የተለያዩ የአፍሪካ ሃገራት መሪዎች ተሳትፈዋል።
ውይይቱ በዋናነት በሰላም፣ ደህንነትና የልማት ጉዳዮች ላይ ያተኮረ እንደነበር ከፕሬዚዳንት ፅህፈት ቤት ያገኘነው መረጃ ያመላክታል።
የውይይት መድረኩ በኒውዮርክ እየተካሄደ ከሚገኘው የተመድ ጠቅላላ ጉባኤ ጎን ለጎን የተካሄደ ነው።
Via:- FBC
@YeneTube @Fikerassefa
መድረኩ በጀርመኗ መራሄተ መንግስት አንጌላ ሜርክል የተመራ ሲሆን፥ የተለያዩ የአፍሪካ ሃገራት መሪዎች ተሳትፈዋል።
ውይይቱ በዋናነት በሰላም፣ ደህንነትና የልማት ጉዳዮች ላይ ያተኮረ እንደነበር ከፕሬዚዳንት ፅህፈት ቤት ያገኘነው መረጃ ያመላክታል።
የውይይት መድረኩ በኒውዮርክ እየተካሄደ ከሚገኘው የተመድ ጠቅላላ ጉባኤ ጎን ለጎን የተካሄደ ነው።
Via:- FBC
@YeneTube @Fikerassefa
የዘንድሮ ዲቪ ምዝገባ መስከረም 21 ይጀምራል!
አዲስአበባ የሚገኘው የዩናይትድስቴትስ አሜሪካ ኤምባሲ እ.ኤአ. የ2021 የዲቪ ሎተሪ ምዝገባ ፕሮግራም በያዝነው መስከረም ወር እንደሚጀምር አስታወቀ፡፡ ስለፕሮግራሙ ዝርዝር መግለጫ ለመስጠትም ኤምባሲው ለጋዜጠኞች ጥሪ አቅርቧል፡፡ከሌሎች ታማኝ ምንጮች ባገኘነው መረጃ መሠረት የዘንድሮው የዲቪ ምዝገባ ፕሮግራም ከመስከረም 21 እስከ ጥቅምት 25 ቀን 2012 ዓ.ም (ኦክቶበር 2 እስከ ኖቬምበር 5 ቀን 2019 እ.ኤ.አ) ይከናወናል፡፡ዩናይትድ ስቴትስ አሜሪካ በ2021 እንደተለመደው በኦንላይን ምዝገባ የሚያከናውኑ ኢትዮጵያውያን እና ሌሎች የተፈቀደላቸው ሀገራት ዜጎች በዕጣ በመለየት 55 ሺ ዕድለኞችን ለመቀበል ተዘጋጅታለች፡፡
Via DireTube
@YeneTube @FikerAssefa
አዲስአበባ የሚገኘው የዩናይትድስቴትስ አሜሪካ ኤምባሲ እ.ኤአ. የ2021 የዲቪ ሎተሪ ምዝገባ ፕሮግራም በያዝነው መስከረም ወር እንደሚጀምር አስታወቀ፡፡ ስለፕሮግራሙ ዝርዝር መግለጫ ለመስጠትም ኤምባሲው ለጋዜጠኞች ጥሪ አቅርቧል፡፡ከሌሎች ታማኝ ምንጮች ባገኘነው መረጃ መሠረት የዘንድሮው የዲቪ ምዝገባ ፕሮግራም ከመስከረም 21 እስከ ጥቅምት 25 ቀን 2012 ዓ.ም (ኦክቶበር 2 እስከ ኖቬምበር 5 ቀን 2019 እ.ኤ.አ) ይከናወናል፡፡ዩናይትድ ስቴትስ አሜሪካ በ2021 እንደተለመደው በኦንላይን ምዝገባ የሚያከናውኑ ኢትዮጵያውያን እና ሌሎች የተፈቀደላቸው ሀገራት ዜጎች በዕጣ በመለየት 55 ሺ ዕድለኞችን ለመቀበል ተዘጋጅታለች፡፡
Via DireTube
@YeneTube @FikerAssefa
የኢሬቻ በዓልን ምክንያት በማድረግ የተዘጋጀው ኤግዚቢሽንና በዛር ዛሬ ተከፍቷል፡፡
በኤግዚቢሽንና በዛሩ ላይ የተለያዩ የኦሮሞ ባህላዊ አልባሳት፣ የባህል እቃዎች፣ ባህላዊ ምግቦችና መጽሐፍት ቀርበዋል፡፡ይህ ኤግዚቢሽንና በዛር እስከ መስከረም 23 ቀን 2012 እንደሚቆይ ከኦሮሚያ ኮሙኒኬሽን ቢሮ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል፡፡
Via EBC
@YeneTube @FikerAssefa
በኤግዚቢሽንና በዛሩ ላይ የተለያዩ የኦሮሞ ባህላዊ አልባሳት፣ የባህል እቃዎች፣ ባህላዊ ምግቦችና መጽሐፍት ቀርበዋል፡፡ይህ ኤግዚቢሽንና በዛር እስከ መስከረም 23 ቀን 2012 እንደሚቆይ ከኦሮሚያ ኮሙኒኬሽን ቢሮ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል፡፡
Via EBC
@YeneTube @FikerAssefa
#update
ከሃያት ጦር ሃይሎች መስመር ተቋርጦ የነበረው የባቡር አገልግሎት ስራውን ጀመረ፡፡
የተባበሩት አደባባይ አካባቢ በሚገኘው ሀዲድ ውስጥ በገባ ኤፍ.ኤስ.አር ተሽከርካሪ አማካኝነት ዛሬ ማለዳ ላይ ለ2 ሰዓታት ገደማ አገልግሎቱ ተቋርጦ ነበር፡፡የአዲስ አበባ ቀላል ባቡር ትራንዚት አገልግሎት ዋና ሥራ አስኪያጅ አቶ ሙሉቀን አሰፋ ቴክኒሺያኖች ወደ ስፍራው መሄዳቸውን እና ችግሩ በአፋጣኝ እንደሚፈታ በጠዋቱ አሐዱ ልሣን ማለዳ ላይ መናገራቸው ይታወሣል፡፡ሰሚት፣ ሲ.ኤም.ሲ እና ሃያት መስመር ተጓዥ ቤተሰቦቻችንም በመስመሩ ላይ ባጋጠመው ችግር ምክንያት መንገድ በመዘጋቱ መጉላላታቸውን ገልፀውልን የነበረ ሲሆን በአሁኑ ሰዓት የባቡር አገልግሎቱ መጀመሩን አሐዱ ሬዲዮ ዘግቧል፡፡
@YeneTube @FikerAssefa
ከሃያት ጦር ሃይሎች መስመር ተቋርጦ የነበረው የባቡር አገልግሎት ስራውን ጀመረ፡፡
የተባበሩት አደባባይ አካባቢ በሚገኘው ሀዲድ ውስጥ በገባ ኤፍ.ኤስ.አር ተሽከርካሪ አማካኝነት ዛሬ ማለዳ ላይ ለ2 ሰዓታት ገደማ አገልግሎቱ ተቋርጦ ነበር፡፡የአዲስ አበባ ቀላል ባቡር ትራንዚት አገልግሎት ዋና ሥራ አስኪያጅ አቶ ሙሉቀን አሰፋ ቴክኒሺያኖች ወደ ስፍራው መሄዳቸውን እና ችግሩ በአፋጣኝ እንደሚፈታ በጠዋቱ አሐዱ ልሣን ማለዳ ላይ መናገራቸው ይታወሣል፡፡ሰሚት፣ ሲ.ኤም.ሲ እና ሃያት መስመር ተጓዥ ቤተሰቦቻችንም በመስመሩ ላይ ባጋጠመው ችግር ምክንያት መንገድ በመዘጋቱ መጉላላታቸውን ገልፀውልን የነበረ ሲሆን በአሁኑ ሰዓት የባቡር አገልግሎቱ መጀመሩን አሐዱ ሬዲዮ ዘግቧል፡፡
@YeneTube @FikerAssefa