#እስካሁን 930 ሺህ 150 የተፈናቀሉ ዜጎች ወደ ቄያቸው ተመልስዋል፦ኮሚሽኑ
በሀገሪቱ በተፈጠረው ግጭት ምክንያት ከተፈናቀሉ ዜጎች መካከል እስካሁን 930 ሺህ 150 ገደማ ሰዎች ወደ ቄያቸው መመለስ መቻሉን ብሔራዊ የአደጋ ስጋት አመራር #ኮሚሽን አስታወቀ፡፡
በተለያዮ ጊዜያት በኢትዮጵያ በተፈጠረው ግጭት አያሌ ዜጎች ህይወታቸው አልፏል፡፡ በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ዜጎች ከቄያቸው ተፈናቅለው ለእንግልት #መዳረጋቸው ይታወቃል፡፡
ግጭቶቹም በዋናነት #በኦሮሚያና ሶማሌ ክልል፣ በምዕራብ ጉጂና ጌዲዮ፣ :በኦሮሚያና ቤንሻንጉል ጉሙዝ ባሉ አዋሳኝ አካባቢዎች እንዲሁም በሶማሊያ ክልልና በቡራዮ ከተማ #የተከሰቱ ናቸው፡፡
በእነዚህም ግጭቶች ከተፈናቀሉ ዜጎች መካከል እስካሁን 930 ሺህ 150 ገደማ ሰዎች ወደ ነበሩበት አካባቢ መመለስ መቻሉን በብሔራዊ የአደጋ ስጋት አመራር ኮሚሽን የህዝብ ግንኙነት ዳይሬክተር አቶ #ደበበ ዘውዴ በተለይ ለኢቢሲ ተናግረዋል፡፡
ተፈናቃዮቹንም ለመደገፍ መንግስት አስቸኳይ እርዳታ እያደረገ ነው ብለዋል፡፡
በአንዳንድ አካባቢዎች ለተፈናቃይ ዜጎች የሚደረገው የድጋፍ ጥረት የተለያዮ ተግዳሮቶች ቢያጋጥሙም ችግሮቹን ለመፍታት #ከባለድርሻ አካላት ጋር በቅንጅት እየተሰራ እንደሆነ ተናግረዋል ዳይሬክተሩ፡፡
መንግስት ህብረተሰቡንና ባለድርሻ አካላትን ባሳተፈ መልኩ ተፈናቃይ ዜጎችን የማቋቋም ስራ እየሰራ እንደሆነም ጠቁመዋል፡፡
ይህም ስራ የሚሰራው ተፈናቃዮቹ ካጋጠማቸው አደጋ የሚያገግሙበት ድጋፍ በመስጠትና የህዝብ ለህዝብ ግንኙነት በመፍጠር መሆኑን አቶ #ደበበ ተናግረዋል፡፡
ተፈናቃይ ዜጎች ወደ ነበሩበት አካባቢ ለመመለስ በሚደረገው ጥረት የሚያነሱትን የፀጥታ ስጋት ለማስወገድ የፀጥታ አካላትንና ባህላዊ የሰላም ማስፈኛ መንገዶችን በመጠቀም እየተሰራ ነው #ብለዋል፡፡
ባለፉት ስድስት ወራት በሀገሪቱ በተከሰተ ግጭት በደረሰ መፈናቀልና በድርቅ 8 ሚሊዮን የሚጠጉ ሰዎች ለጉዳት መዳረጋቸውን ከብሔራዊ የአደጋ ስጋት አመራር ኮሚሽን የተገኘው መረጃ ያመለክታል፡፡
ምንጭ ፦ኢቢሲ
@YeneTube @Mycase27
በሀገሪቱ በተፈጠረው ግጭት ምክንያት ከተፈናቀሉ ዜጎች መካከል እስካሁን 930 ሺህ 150 ገደማ ሰዎች ወደ ቄያቸው መመለስ መቻሉን ብሔራዊ የአደጋ ስጋት አመራር #ኮሚሽን አስታወቀ፡፡
በተለያዮ ጊዜያት በኢትዮጵያ በተፈጠረው ግጭት አያሌ ዜጎች ህይወታቸው አልፏል፡፡ በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ዜጎች ከቄያቸው ተፈናቅለው ለእንግልት #መዳረጋቸው ይታወቃል፡፡
ግጭቶቹም በዋናነት #በኦሮሚያና ሶማሌ ክልል፣ በምዕራብ ጉጂና ጌዲዮ፣ :በኦሮሚያና ቤንሻንጉል ጉሙዝ ባሉ አዋሳኝ አካባቢዎች እንዲሁም በሶማሊያ ክልልና በቡራዮ ከተማ #የተከሰቱ ናቸው፡፡
በእነዚህም ግጭቶች ከተፈናቀሉ ዜጎች መካከል እስካሁን 930 ሺህ 150 ገደማ ሰዎች ወደ ነበሩበት አካባቢ መመለስ መቻሉን በብሔራዊ የአደጋ ስጋት አመራር ኮሚሽን የህዝብ ግንኙነት ዳይሬክተር አቶ #ደበበ ዘውዴ በተለይ ለኢቢሲ ተናግረዋል፡፡
ተፈናቃዮቹንም ለመደገፍ መንግስት አስቸኳይ እርዳታ እያደረገ ነው ብለዋል፡፡
በአንዳንድ አካባቢዎች ለተፈናቃይ ዜጎች የሚደረገው የድጋፍ ጥረት የተለያዮ ተግዳሮቶች ቢያጋጥሙም ችግሮቹን ለመፍታት #ከባለድርሻ አካላት ጋር በቅንጅት እየተሰራ እንደሆነ ተናግረዋል ዳይሬክተሩ፡፡
መንግስት ህብረተሰቡንና ባለድርሻ አካላትን ባሳተፈ መልኩ ተፈናቃይ ዜጎችን የማቋቋም ስራ እየሰራ እንደሆነም ጠቁመዋል፡፡
ይህም ስራ የሚሰራው ተፈናቃዮቹ ካጋጠማቸው አደጋ የሚያገግሙበት ድጋፍ በመስጠትና የህዝብ ለህዝብ ግንኙነት በመፍጠር መሆኑን አቶ #ደበበ ተናግረዋል፡፡
ተፈናቃይ ዜጎች ወደ ነበሩበት አካባቢ ለመመለስ በሚደረገው ጥረት የሚያነሱትን የፀጥታ ስጋት ለማስወገድ የፀጥታ አካላትንና ባህላዊ የሰላም ማስፈኛ መንገዶችን በመጠቀም እየተሰራ ነው #ብለዋል፡፡
ባለፉት ስድስት ወራት በሀገሪቱ በተከሰተ ግጭት በደረሰ መፈናቀልና በድርቅ 8 ሚሊዮን የሚጠጉ ሰዎች ለጉዳት መዳረጋቸውን ከብሔራዊ የአደጋ ስጋት አመራር ኮሚሽን የተገኘው መረጃ ያመለክታል፡፡
ምንጭ ፦ኢቢሲ
@YeneTube @Mycase27
በአማራ ክልል ሰሜን #ጎንደር_ዞን ባለፉት ሁለት ሳምንታት በነበሩ ግጭቶች #90_ሺህ ሰዎች መፈናቀላቸውን የአውሮፓ #ኮሚሽን አስታወቀ። ከተፈናቃዮቹ ውስጥ 40 ሺህ የሚሆኑት በቅማንት እና በአማራ ብሔር ተወላጆች መካከል በተቀሰቀሰ ግጭት ምክንያት ቀያቸውን የለቀቁ ናቸው ብሏል ኮሚሽኑ።
በኮሚሽኑ የሲቪል ጥበቃ እና የሰብዓዊ ርዳታ ተልዕኮ ዳይሬክቶሬት ጄነራል ትላንት ባወጣው መግለጫ በሰሜን ጎንደሩ ግጭት በደርዘን የሚቆጠሩ ሰዎች ሞት እና የበርካታ ቤቶች ቃጠሎ እንደነበር መዘገቡን ገልጿል። የአማራ ክልል በአካባቢው የተከሰተው ሰብዓዊ ቀውስ ከአቅሙ በላይ መሆኑን ከሳምንት በፊት ማስታወቁን እና የሰብዓዊ ርዳታ አቅራቢዎችን ድጋፍ መጠየቁን መግለጫው ጠቁሟል።
በአማራ ክልል ጥያቄ መሰረት አስራ ስምንት ሺህ አባወራዎችን ለመርዳት 18 ሚሊዮን ዶላር ድጋፍ ያስፈልጋል። የአውሮፓ ኮሚሽን በበኩሉ በቅርቡ የተካሄዱ የሰብዓዊ ጉዳይ ዳሰሳዎች ተፈናቃዮች ያሉበት ሁኔታ አንገብጋቢ መሆኑን አመላክተዋል ብሏል። ተፈናቃዮቹ እንደ ምግብ፣ መጠለያ እና ከመብል ውጭ ያሉ ሌሎች የመሰረታዊ አቅርቦት ቁሳቁሶች በአስቸኳይ እንደሚያስፈልጓቸው አትቷል።
በሰሜን ጎንደር የቅማንት ብሔር ተወላጆች የራስ ገዝ አስተዳደርን ከመጠየቃቸው ጋር በተያያዘ በአካባቢው ከ2009 ዓ. ም ዓመት ወዲህ ውጥረቱ እያየለ መምጣቱን የአውሮፓ ኮሚሽን መግለጫ አስታውሷል። በአካባቢው ከህዳር 2010 ዓ. ም ወዲህ በተለይ ሁከት እና መፈናቀሎች መከሰታቸውን ጠቅሷል። በዚህም ምክንያት ከአንድ ሺህ የሚልቁ የቅማንት ተወላጆች ወደ ሱዳን መሰደዳቸውን እና ከእነርሱም ውስጥ በመቶዎች የሚቆጠሩት ጥገኝነት መጠየቃቸውን ገልጿል።
በአማራ ክልል በምዕራብ እና ማዕከላዊ ጎንደር የተከሰተውን የጸጥታ መድፍረስ ለመቆጣጠር ከሁለት ሳምንት ወዲህ የመከላከያ ሰራዊት በአካባቢዎቹ እንዲሰማራ መደረጉ ይታወሳል። የክልሉ መንግስት ከጎንደር እስከ መተማ በተዘረጋው አውራ ጎዳና እና ከጎንደር ወደ ሁመራ በሚወስደው መንገድ በአምስት ኪሎ ሜትር ክልል በግልም ይሁን በቡድን መሳሪያ ይዞ መንቀሳቀስም ከልክሏል።
ምንጭ:-Dw
@YeneTube @FikerAssefa
በኮሚሽኑ የሲቪል ጥበቃ እና የሰብዓዊ ርዳታ ተልዕኮ ዳይሬክቶሬት ጄነራል ትላንት ባወጣው መግለጫ በሰሜን ጎንደሩ ግጭት በደርዘን የሚቆጠሩ ሰዎች ሞት እና የበርካታ ቤቶች ቃጠሎ እንደነበር መዘገቡን ገልጿል። የአማራ ክልል በአካባቢው የተከሰተው ሰብዓዊ ቀውስ ከአቅሙ በላይ መሆኑን ከሳምንት በፊት ማስታወቁን እና የሰብዓዊ ርዳታ አቅራቢዎችን ድጋፍ መጠየቁን መግለጫው ጠቁሟል።
በአማራ ክልል ጥያቄ መሰረት አስራ ስምንት ሺህ አባወራዎችን ለመርዳት 18 ሚሊዮን ዶላር ድጋፍ ያስፈልጋል። የአውሮፓ ኮሚሽን በበኩሉ በቅርቡ የተካሄዱ የሰብዓዊ ጉዳይ ዳሰሳዎች ተፈናቃዮች ያሉበት ሁኔታ አንገብጋቢ መሆኑን አመላክተዋል ብሏል። ተፈናቃዮቹ እንደ ምግብ፣ መጠለያ እና ከመብል ውጭ ያሉ ሌሎች የመሰረታዊ አቅርቦት ቁሳቁሶች በአስቸኳይ እንደሚያስፈልጓቸው አትቷል።
በሰሜን ጎንደር የቅማንት ብሔር ተወላጆች የራስ ገዝ አስተዳደርን ከመጠየቃቸው ጋር በተያያዘ በአካባቢው ከ2009 ዓ. ም ዓመት ወዲህ ውጥረቱ እያየለ መምጣቱን የአውሮፓ ኮሚሽን መግለጫ አስታውሷል። በአካባቢው ከህዳር 2010 ዓ. ም ወዲህ በተለይ ሁከት እና መፈናቀሎች መከሰታቸውን ጠቅሷል። በዚህም ምክንያት ከአንድ ሺህ የሚልቁ የቅማንት ተወላጆች ወደ ሱዳን መሰደዳቸውን እና ከእነርሱም ውስጥ በመቶዎች የሚቆጠሩት ጥገኝነት መጠየቃቸውን ገልጿል።
በአማራ ክልል በምዕራብ እና ማዕከላዊ ጎንደር የተከሰተውን የጸጥታ መድፍረስ ለመቆጣጠር ከሁለት ሳምንት ወዲህ የመከላከያ ሰራዊት በአካባቢዎቹ እንዲሰማራ መደረጉ ይታወሳል። የክልሉ መንግስት ከጎንደር እስከ መተማ በተዘረጋው አውራ ጎዳና እና ከጎንደር ወደ ሁመራ በሚወስደው መንገድ በአምስት ኪሎ ሜትር ክልል በግልም ይሁን በቡድን መሳሪያ ይዞ መንቀሳቀስም ከልክሏል።
ምንጭ:-Dw
@YeneTube @FikerAssefa