YeneTube
118K subscribers
31.4K photos
485 videos
79 files
3.87K links
መረጃዎችን ለመላክ @Fikerassefa
Download Telegram
ይፍጠኑ

የሃምሳ ፐርሰንት ተጨማሪ የአየር ሰዓት ቦነስ በኀፃ የሚሰጥበት የመጨረሻው ቀን ነገ ነው።

ቦነሱን ለማግኘት በውጭ ሃገር ከሚኖር ወዳጅ ዘመድ የአየር ሰዓት በ remit.et ያስሞሉ።

ለምሳሌ የመቶ ብር የአየር ሰዓት ውጭ ሃገር ከሚኖር ወዳጆ በ remit.et ሲላክሎት ኢትዮ ቴሌኮም ሃምሳ ብር ጨምሮ በድምሩ የመቶ ሃምሳ ብር አየር ሰዓት ወዲያውኑ ይሞላሎታል።
__
In partnership with Ethio Telecom

ቻናላችንን በመቀላቀል በየጊዜው የሚኖረንን የካርድ ስጦታ ይቀበሉ @remiteth
ከ4 ሚሊየን 485 ሺህ ብር በላይ የሚገመት ሃሺሽ መያዙን የጉምሩክ ኮሚሽን አስታወቀ።

ሃሺሹ በተሽከርካሪ ተጭኖ ከሻሸመኔ ወደ ኬንያ በመጓጓዝ ላይ እያለ በሀዋሳ ጉምሩክ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት በጪጩ ጉምሩክ ጣብያ ጥሶ ለማለፍ ሲሞክር መያዙ ተገልጿል።
የመኪናው አሽከርካሪ ለፍተሻ ተባባሪ ባለመሆኑ ተረኛ ፌደራል ፖሊስ ጎማውን በጥይት
በመምታት በቁጥጥር ስር መዋሉም ተገልጿል።

የተያዘው ሃሺሽም በተገቢው መንገድ እንዲወገድ ለሚመለከተው አካል ገቢ መደረጉን ከገቢዎች ሚኒስቴር የተገኘነው መረጃ ያመላክታል።

Via:- addis Maleda
@YeneTube @Fikerassefa
የሀድያ ዞን ምክር ቤት የሀድያ ብሔር በክልል የመደራጀት ጥያቄዉን የክልሉ ምክር ቤት ባለማስፈጸሙ ለፌዴሬሽን ምክር ቤት ይግባኝ አቀረበ፡፡

@YeneTube @Fikerassefa
የህዳሴ ግድብ የሶስትዮሽ ውይይት ያለስምምነት ተጠናቀቀ!

ኢትዮጵያ፣ ግብጽና ሱዳን በታላቁ ህዳሴ ግድብ ዙሪያ በአዲስ አበባ ሲያካሂዱት የቆዩት የሶስትዮሽ ውይይት ያለስምምነት ተጠናቋል።የሶስትዮሽ ውይይቱ መጠናቀቁን ተከትሎ የውሃ፣ መስኖ እና ኢነርጂ ሚኒስትር ዶክተር ኢንጂነር ስለሺ በቀለ መግለጫ ሰጥተዋል። በመግለጫቸውም ውይይቱ ያለስምምነት የተጠናቀቀው ግብፅ የግድቡን የውሃ ሙሌት በተመለከተ አዲስ ሃሳብ ይዛ በመቅረቧ መሆኑን ተናግረዋል።

ትናንት በተጀመረው አራተኛው ዙር የሶስቱ ሀገራት የውሃ ሚኒስትሮች ስብሰባ ግብፅ ግድቡ ከ12 እስከ 21 ዓመት እንዲሞላ የሚል አዲስ ሀሳብ ማቅረቧ ተገልጿል።ኢትዮጵያ በበኩሏ ይህን ሃሳብ በማንኛውም መልኩ እንደማትቀበል መግለጿን ነው ሚኒስትሩ የተናገሩት።ሶስቱ ሀገራት ከዚህ በፊት የህዳሴው ግድብ በ7 ዓመት ውስጥ እንዲሞላ ስምምነት ላይ ደረሰው የነበረ መሆኑ ይታወሳል።

በቀጣይም የሶስቱ ሀገራት የውሃ ሚኒስትሮች የእስካሁኑን የሶስትዮሽ ስብሰባ ሂደት ሪፖርት ለሀገራቱ መሪዎች የሚያቀርቡ ይሆናል።በተጨማሪም ሚኒስትሮቹ የፊታችን ሰኞ ወደ ዋሽንግተን በማምራት የአለም ባንክ ፕሬዚዳንት እና የአሜሪካ ግምጃ ቤት ሃላፊ በተገኙበት በተካሄዱት አራት የቴክኒክ ስብሰባዎች ዙሪያ ገለፃ ያደርጋሉ።በዚህ ውይይት ላይም የሶሰቱ ሀገራት የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች የሚገኙ መሆኑ ተመላክቷል።

ምንጭ:ፋና
@YeneTube @FikerAssefa
Breakng news...


176 ሰዎችን አሳፍሮ ሰጓዝ የነበረውና ንብረትነቱ የዩክሬን የሆነው አውሮፕላን በስህተት ተኩሳ የጣለቸው ኢራን ነች ሲል የአሜሪካ የዜና ወኪል ዘግቧል።

አንድ የአሜሪካ ከፍተኛ ሀላፊ 'ሲቢኤስ' ለተባለው የዜና ድርጅት አሉት እንደተባለው ከሆነ ቦይንግ 737-800 አውሮፕላን በኢራን ሚሳኤል ነው ተመትቶ ወደቀው።

ዩክሬን ቀደም ብላ አውሮፕላኑን እንዲከሰከስ ያደረገው ከኢራን የተተኮሰ ሚሳኤል ሊሆን እንደሚችል ግምት አስቀምጣ የነበረ ሲሆን ኢራን ግን ሊሆን አይችልም በማለት አጣጥላው ነበር።


ሲቢኤስ የጠቀሳቸው ከፍተኛ የደህንነት ሀላፊ አውሮፕላኑን ያጠቁ የሁለት ሚሳኤሎች ድምጽ ከተሰማ በኋላ ሌላ ተጨማሪ ሶስተኛ ሚሳኤል እንደተከተለ ከሳተላይት የተገኘ መረጃ ይጠቁማል።

በሌላ በኩል 'ኒውስዊክ' በበኩሉ አንድ የፔንታጎን ከፍተኛ ሀላፊና የኢራቅ የደህንነት አባልን ጠቅሶ እንደዘገበው የዩክሬኑ አውሮፕላን ተመትቶ የወደቀው ሩሲያ ባመረተችው 'ቶር' በሚባል ሚሳኤል ነው።

ፕሬዝዳንት ትራምፕ ትናንት ባስተላለፉት መልእክት ''ከዚህ አውሮፕላን ጋር በተገናኘ ጥርጣሬ አለኝ። የሆነ ሰው ስህተት ሳይሰራ አይቀርም'' ብለው ነበር።

የዩክሬን ዓለም አቀፍ አየር መንገድ ንብረት የሆነው ቦይንግ አውሮፕላን ቴህራን ከሚገኘው ኢማም ኮሜይኒ አውሮፕላን ማረፊያ ከተነሳ ከጥቂት ደቂቃዎች በኋላ ነው የተከሰከሰው።
አውሮፕላኑ ጉዞውን ወደ ዩክሬን ዋና ከተማ ኪዬቭ አድርጎ ነበር የተነሳው።

Via:- ቢቢሲ
@Yenetube @FikerAssefa
Forwarded from YeneTube
💥ማስታወቂያ💥
School of American English

📌ቻይንኛ
📌ፈረንሳይኛ
📌ጀርመንኛ
📌ጣልያንኛ
📌አፋን ኦሮሞ
📌አረብኛ

አንቱታን ባተፈሩ መምህራን እናስተምራለን

አድራሻዎቻችን ⬇️
ሜክሲኮ ኬኬር ህንፃ +251919913021
ፒያሳ ፒያሳ ገበያ ማዕከል +251919913023
22 ጎላጎል ህንፃ 6ተኛ ፎቅ +251919913022


💥💥💥10% Discount 💥💥💥💥

ቅናሹን ለመጠቀም
ይህንን ፓስት screenshot አድርገው መያዝና ስመጡ ማሣየት ይኖርብዎታል

T.me/SCHOOLOFAMERICAN
Forwarded from YeneTube
https://tttttt.me/joinchat/AAAAAEO_AwEACCqYXy4L9A. 👈🏾👈🏾👈👈👈 🎄🎄🎄🎄🎄🎄🎄🎄🎄🎄🎄🎄
የተከበራችሁ የ SHOPIA®️ ቤተሰቦች እንኳን ለኢየሱስ ክርስቶስ የልደት በዐል በሰላም አደረሳችሁ ❤️ እያልን በዐሉን ምክንያት በማድረግ ከ 25/04/12(ቅዳሜ) ጀምሮ ለ 3 ተከታታይ ቀናት በቻናላችን በኩል በሚሸጡ ሁሉም ዕቃዎች ላይ 5-15%⬇️ ቅናሽ አድርገናል።🤗
🎉🛍 ይግዙ በዕድሉ ተጠቃሚ ይሁኑ ቅናሹ የሚቆየው እስከ በዐሉ ዋዜማ ድረስ ብቻ ነው🎁🛒

🎅🎄🎅🎄🎅🎄🎅🎄🎅🎄🎅
⭐️ መልካም የገና በዐል ⭐️
⭐️ SHOPIA ⭐️
🎅🎄🎅🎄🎅🎄🎅🎄🎅🎄🎅👇👇👇
https://tttttt.me/joinchat/AAAAAEO_AwEACCqYXy4L9A
Forwarded from YeneTube
🎊እንኳን አደረሳችሁ🎉
ፈረስ ለበዓሉ ስጦታዎችን አዘጋጅቶላችኋል 🎁🎁🎁

አንድ ሙክት በግ እና ሁለት ዶሮዎች አዘጋጅቶላችኋል

ከዚህ ሽልማት አሽናፊ ለመሆን

ፈረስ ይዘዙ እና የሄዱበትን ሂሳብ ስክሪን ሻት አድርገው ይላኩልን @FCS6090


ደንብና ግዴታዎች ተፈፃሚ ይሆናሉ።
Forwarded from TARGET MARKETS ®
Perfumes 👇👇👇👇👇
100 ml 👇👇👇👇👇👇
ALL AVILABLE NOW🔥🔥🔥
Contact @kiru04
0931607806

Miss dior-1100 birr
Miss dior-1500
Poison girl dior-1500 birr
Ysl manifesto-1100 birr
YSL-1100 birr

ALL AVILABLE NOW🔥🔥🔥
Contact @kiru04
0931607806
https://tttttt.me/joinchat/AAAAAEPkyxEP1snCoAkFGw
ዶ/ር አሚር አማን ከፍተኛ አማካሪ ሆነው ተሾሙ

በአሜሪካዊው ባለሀብት ዋረን ቡፌት ከ56 አመት በፊት የተመሰረተውና በሴቶች ወሊድና ፅንስ ክትትል አለም ላይ ያለትርፍ በሚሰራው ሱዛን ቶምፕሰን ቡፌት ፋውንዴሽን በተባለ ተቋም የቀድሞ ጤና ሚኒስትር ዶ/ር አሚር አማን ከፍተኛ አማካሪ ሆነው መሾማቸውን ማረጋገጡን ጋዜጠኛ ተስፋዬ ጌትነት ዘግቧል ። ፋውንዴሽኑ ዋና ቢሮ አሜሪካ ግዛት ባለቸው ኔቤሪስካ ኦማሃ ከተማ ውስጥ ይገኛል።

ምንጭ:- ጋዜጠኛ ተስፋዬ ጌትነት
@YeneTube @Fikerassefa
የካናዳው ጠቅላይ ሚኒስትር ጀስቲን ቱሩዶ በኢራን የተከሰከሰው አውሮፕላን በሚሳኤል ተመቶ ስለመውደቁ መረጃዎች ደርሰውናል አሉ፡፡

ምእራባዊያን መሪዎች ረቡዕ እለት በቴህራን የተከሰከሰው የዩክሬን የመንገደኞች አውሮፕላን፤ በኢራን ሚሳኤል ተመቶ መውደቁን #ማስረጃዎች_ያሳያሉ_እያሉ ነው፡፡

የካናዳና የእንግሊዝ መሪዎች 176 ሰዎች ለሞቱበት አደጋ የተሟላ ምርመራ እንዲደረግ ጥሪ እቅርበዋል፡፡

አደጋው የተከሰተው ኢራን በኢራቅ የሚገኙ የአሜሪካ የጦር ሰፈሮች ላይ የሚሳኤል ጥቃት ከፈጸመች ከሰዓታት በኋላ ነበር፡፡

ከዚህ ከመነሳትም የአሜሪካ ብዙሃን መገናኛዎች አውሮፕላኑ ከአሜሪካ ለአጸፋ እርምጃ የተላከ የጦር አውሮፕላን መስሏት ኢራን በስህተት መታዋለች ሲሉ ግምታቸውን አስቀምጠዋል፡፡

የአሜሪካ የደህንነት ባለስልጣናትም አውሮፕላኑ በሩሲያ ሰራሽ ሚሳኤል መመታቱን ተናግረዋል፡፡

አደጋውን ተከትሎ ኢራን የመረጃ ሳጥኑን ለአሜሪካም ሆነ ለአምራች ድርጅቱ ቦይንግ አልሰጥም ብትልም፤ የውጪ ጉዳይ ሚኒስትሩ ሞሃመድ ጃቫድ ዛሪፍ በአደጋው ላይ ለሚነሱ ጥያቄዎች ቦይንግን መጋበዛቸው ተሰምቷ፡፡

በአደጋው ከኢራን ቀጥሎ ከፍተኛ ቁጥር ያላቸው ዜጎቿን ያጣችው ካናዳ ስትሆን 63 ዜጎቿ ሞተዋል፡፡

ጠቅላይ ሚኒስትር ጀስቲን ቱሩዶ አውሮፕላኑ በኢራን የአየር መቃወሚያ ሚሳኤል መመታቱን የሚያመላክቱ መረጃዎች ከተለያዩ ምንጮች እየደረሷቸው መሆኑን ገልጸው፤ይህም በስህተት የተፈጠረ መሆኑን ተናግረዋል፡፡

የእንግሊዙ ጠቅላይ ሚኒስትር ቦሪስ ጆንሰን የቱሩዶና ሃሳብ አጠናክረው ከሌሎች በአደጋው ዜጎቻቸውን ካጡ ሃገራት ጋር በቅርበት እጠሰሩ መሆናቸውን አስታውቀዋል፡፡

ኢራን በበኩሏ ውንጀላውን ውድቅ ውድቅ ማድረጓን #ቢቢሲ_ዘግቧል፡፡

ምንጭ:- Ethio FM
@YeneTube @Fikerassefa
በአውስትራሊያ የተከሰተው እሣት 240 ሺ ሰዎች ርቀው እንዲሸሹ ማድረጉ ተነግሯል፡፡

የአውስትራሊያ ባለሥልጣናት ሩብ ሚሊዮን ህዝብ በአስቸኳይ ካለበት ሥፍራ ለቅቆ ይርቅ ዘንድ መደረጉን ተናግረዋል፡፡

በአውስትራሊያ የተነሣው እሣት በሙቀት መጠኑ መጨመር እየታገዘና በሃይለኛ የነፋስ ወጀብ እየተራገበ በምሥራቃዊ የሀገሪቱ ጠረፍ ያገኘውን ሁሉ እየበላ በመገሥገስ ላይ መሆኑም ነው የሚነገረው፡፡

በመላው አውስትራሊያ የሙቀት መጠን ከ40 ዲግሪ ሴልሺየስ መዝለሉንም ነው የሚገልፁት፡፡

ከ240 ሺ በላይ ህዝቦች በአሥቸኳይ ሥፍራቸውን ለቀው ይሸሹ ዘንድ የማስጠንቀቂያ ትዕዛዝ ተላልፎላቸዋል፡፡

Via:- ዘ-ቴሌግራም / አሐዱ
@YeneTube @FikerAssefa
በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ የተማሪዎች ጸብ ሕይወት አጠፋ

በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ በተማሪዎች መካከል በተነሳ ጸብ የአንድ ተማሪ ሕይወት ማለፉን ዩኒቨርሲቲው አስታወቀ።

ትናንት ምሽት በዩኒቨርሲቲው ዋና ግቢ በተከሰተው ጸብ የአንደኛ ዓመት የተፈጥሮ ሳይንስ ተማሪ ሕይወት ማለፉን የዩኒቨርሲቲው ፕሬዝዳንት ጽሕፈት ቤት ኃላፊ አቶ አየለ አዳቶ ለዶቼ ቬለ (DW) ገልጸዋል። የተማሪው አስክሬን በአዲስ አበባ ምንሊክ ሆስፒታል ምርመራ ከተደረገለት በኋላ ወደ ትውልድ ስፍራው ወልዲያ መላኩንም የጽሕፈት ቤቱ ኃላፊ ተናግረዋል። የነገሩ መነሻ የሁለት ተማሪዎች ጸብ መሆኑን የጠቀሱት አቶ አየለ ከጀርባው ሌላ ተልኮ ይኑረው ወይንም አይኑረው እየተጣራ ይገኛል ብለዋል። አክለውም « በአሁኑ ወቅት ከግድያው ጋር በተያያዘም 44 ተማሪዎች በቁጥጥር ሰር ውለው በፖሊስ ምርመራ እየተደረገባቸው ይገኛል።» ብለዋል።

«የዩኒቨርሲቲው ማኅበረሰብም በተፈጠረው ሁኔታ በከፍተኛ ሀዘን ውስጥ ቢገኝም የመማር ማስተማሩ ሂደት ግን ሳይቋረጥ ቀጥሏል» ሲሉም አክለዋል። የሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ እስካሁን ሰላማዊ ድባብ ከሚስተዋልባቸው ጥቂት የአገሪቱ ዩኒቨርሲቲዎች መካከል አንዱ በመሆን ይታወቃል።

አሁን የተባለው ጸብ የተነሳውና የሰው ሕይወትም ያለፈው ተማሪዎቹ ከፊታችን ሰኞ ጀምሮ የአንደኛ ወሰነ ትምህርት ፈተና ለመውሰድ በዝግጅት ላይ ባሉበት ውቅት መሆኑን DW ዘግቧል።

ምንጭ:- ጀርመን ድምፅ ራዲዮ
@YeneTube @Fikerassefa
በአባይ ጉዳይ አዲስ አበባ ላይ ለሁለት ቀናት የተካሄደው ቴክኒካዊ ውይይት ያለውጤት ለመጠናቀቁ ግብፅ ኢትዮጵያን በምክንያትነት ወቀሰች።

በአባይ ጉዳይ በሚካሄደው ድርድር የማማከር ትብብር የሚያደርጉት አቶ ተፈራ በየነ፤ በህዳሴው ግድብ ውኃ አሞላልና አለቃቀቅ ላይ ሦስቱ ሃገራት ሁሉንም በሚያስማማ መልክ ጉዳዩ መቋጫ ማግኘት ስላለበት ድርድራቸውን በአንድ ወይም በሌላ መንገድ ቀጥሎ እልባት ያገኛል የሚል ተስፋቸውን ገልጸዋል። ዶቼ ቬለ በጉዳዩ ላይ ያነጋገራቸው የአባይ ተፋሰስ ሃገራት ትብብር በሆነው ናይል ቤዚን ኢንሼቲቭ ለረዥም ጊዜ ያገለገሉት አቶ ተፈራ እንደሚሉት ኢትዮጵያ፣ ግብፅ እና ሱዳን በተከታታይ ባደረጓቸው ውይይቶች የሚያግባባ ደረጃ ላይ ይደርሳሉ የሚል እምነት አለ።

ከግብፅ በኩል የአባይ ውኃ በተመለከተ ጉዳዩ ስስ እና ኢትዮጵያ እና ግብፅን ወደግጭት ሊከት የሚችል እንደሆነ እንደሚታሰብ በማንሳት ከካይሮ በኩል የሚነሳው ግፊት ኢትዮጵያ ላይ ጫና ይኖረው እንደሁ ከዶቼ ቬለ ለቀረበላቸው ጥያቄም፤ የአባይ ጉዳይ ከብሔራዊ ጥቅም ጋር የተያያዘ መሆኑን ያመለከቱት አቶ ተፈራ፤ ሁሉም የተሻለ ጥቅም ለማግኘት የሚሄድበት አካሄድ እንዳለ ነገር ግን ይህ እንደማያዋጣ አመልክተዋል። «አባይ የጋራ ሃብት ነው፤ ይህን የጋራ ሃብት ሦስቱም አገሮች በፍትሃዊነት ሊጠቀሙበት ይገባል።

ይህ ሲደረግ የቆየው ጥረትም ምንም እንኳ ፕሮጀክቱ በኢትዮጵያ ምድር እና በኢትዮጵያ ወጪ፤ በኢትዮጵያ ሕዝብ ሃብት የሚገነባ ቢሆንም፤ ሃብቱ ከሚያጋጨው ይልቅ ተቻችሎ በጋራ ሃብቱ ለመጠቀም ትብብራቸውን እንዲያጠናክሩ ይጠበቃል።» ነው ያሉት።
ከዚህ ውጪ «አንዱ በሌላው ላይ ጫና የሚያሳድርበት፤ ወይም አንዱ ተጠቃሚ ሌላው ደግሞ ተመልካች የሚሆንበት አሠራር ሊኖር አይገባም፤» እናም ሁሉም ይህን ይገነዘባሉ ብለዋል።

ምንጭ:- Dw
የሃዘን መግለጫ ሀዋሳ ዩንቨርስቲ⬆️

የሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ 1ኛ ዓመት የተፈጥሮ ሳይንስ ተማሪ የሆነው ሱራፌል ሰሎሞን ፀጋዬ በትናንትው ዕለት አመሻሽ ላይ በደረሰበት ጉዳት ወደ ሪፌራል ሆስፒታል ተወስዶ ሕይወቱን ለማዳን ከፍተኛ ርብርብ ቢደረግም ሳይሳካ በመቅረቱ ሕይወቱ ሊያልፍ ችሏል፡፡

ዩኒቨርሲቲውም የተሰማውን ጥልቅ ሀዘን እየገለፀ ለተማሪ ሱራፌል ቤተሰብና ዘመድ ወዳጆቹም መጽናናትን እየተመኘ ከተማሪው ሞት ጋር በተያያዘ የተጠረጠሩ ተማሪዎች በቁጥጥር ሥር ሆነው ምርመራ እየተካሄደባቸው በመሆኑ ምርመራው እንደተጠናቀቀ ጥፋተኛ ሆነው በሚገኙት ላይ በወንጀል ህግና በአካዳሚክ ዲሲፕሊን ደንብ መሠረት አስፈላጊው እርምጃ የሚወሰድ መሆኑን ዩኒቨርሲቲው ይገልጻል፡፡

@YeneTube @Fikerassefa
በኦሮሚያ ክልል የታገቱ 17 የአማራ ክልል ተወላጅ ተማሪዎችን መንግሥት እንዲያስለቅቅ የአማራ ብሄራዊ ንቅናቄ ዛሬ በፌስቡክ ገጹ ባሰራጨው መግለጫ ጠይቋል፡፡ 14 ሴቶች እና 3 ወንድ ተማሪዎች ባልታወቁ አካላት ከታገቱ 1 ወር አልፏቸዋል፡፡ አጋቾቹ በአማራ ክልል ያሉ የኦሮሞ ተማሪዎች በክልላቸው ባሉ ዩኒቨርስቲዎች ካልተመደቡ አንለቃቸውም ማለታቸው ታውቋል፡፡

ምንጭ: ዋዜማ
@YeneTube @FikerAssefa
የኢትዮጵያ መድን ድርጅት በታሪኩ ሁለተኛ ከፍተኛ የተባለለትን የመድን ሽፋን በ2 ባቡሮችና 12 ፉርጎዎች ላይ ለደረሰ ጉዳት ከፍሏል።የድርጅቱ ስራ አስኪያጅ አቶ ነፃነት ለሜሳ የ95.1 ሚሊዮን ብር ቼክ ለኢትዮ ጅቡቲ ምድር ባቡር(EDR) ሀላፊ አቶ ጥላሁን ሳርካ አስረክበዋል።

ምንጭ: ፎርቹን
@YeneTube @FikerAssefa