YeneTube
119K subscribers
31.3K photos
484 videos
79 files
3.86K links
መረጃዎችን ለመላክ @Fikerassefa
Download Telegram
የካናዳው ጠቅላይ ሚኒስትር ጀስቲን ቱሩዶ በኢራን የተከሰከሰው አውሮፕላን በሚሳኤል ተመቶ ስለመውደቁ መረጃዎች ደርሰውናል አሉ፡፡

ምእራባዊያን መሪዎች ረቡዕ እለት በቴህራን የተከሰከሰው የዩክሬን የመንገደኞች አውሮፕላን፤ በኢራን ሚሳኤል ተመቶ መውደቁን #ማስረጃዎች_ያሳያሉ_እያሉ ነው፡፡

የካናዳና የእንግሊዝ መሪዎች 176 ሰዎች ለሞቱበት አደጋ የተሟላ ምርመራ እንዲደረግ ጥሪ እቅርበዋል፡፡

አደጋው የተከሰተው ኢራን በኢራቅ የሚገኙ የአሜሪካ የጦር ሰፈሮች ላይ የሚሳኤል ጥቃት ከፈጸመች ከሰዓታት በኋላ ነበር፡፡

ከዚህ ከመነሳትም የአሜሪካ ብዙሃን መገናኛዎች አውሮፕላኑ ከአሜሪካ ለአጸፋ እርምጃ የተላከ የጦር አውሮፕላን መስሏት ኢራን በስህተት መታዋለች ሲሉ ግምታቸውን አስቀምጠዋል፡፡

የአሜሪካ የደህንነት ባለስልጣናትም አውሮፕላኑ በሩሲያ ሰራሽ ሚሳኤል መመታቱን ተናግረዋል፡፡

አደጋውን ተከትሎ ኢራን የመረጃ ሳጥኑን ለአሜሪካም ሆነ ለአምራች ድርጅቱ ቦይንግ አልሰጥም ብትልም፤ የውጪ ጉዳይ ሚኒስትሩ ሞሃመድ ጃቫድ ዛሪፍ በአደጋው ላይ ለሚነሱ ጥያቄዎች ቦይንግን መጋበዛቸው ተሰምቷ፡፡

በአደጋው ከኢራን ቀጥሎ ከፍተኛ ቁጥር ያላቸው ዜጎቿን ያጣችው ካናዳ ስትሆን 63 ዜጎቿ ሞተዋል፡፡

ጠቅላይ ሚኒስትር ጀስቲን ቱሩዶ አውሮፕላኑ በኢራን የአየር መቃወሚያ ሚሳኤል መመታቱን የሚያመላክቱ መረጃዎች ከተለያዩ ምንጮች እየደረሷቸው መሆኑን ገልጸው፤ይህም በስህተት የተፈጠረ መሆኑን ተናግረዋል፡፡

የእንግሊዙ ጠቅላይ ሚኒስትር ቦሪስ ጆንሰን የቱሩዶና ሃሳብ አጠናክረው ከሌሎች በአደጋው ዜጎቻቸውን ካጡ ሃገራት ጋር በቅርበት እጠሰሩ መሆናቸውን አስታውቀዋል፡፡

ኢራን በበኩሏ ውንጀላውን ውድቅ ውድቅ ማድረጓን #ቢቢሲ_ዘግቧል፡፡

ምንጭ:- Ethio FM
@YeneTube @Fikerassefa