YeneTube
117K subscribers
31.5K photos
485 videos
79 files
3.9K links
መረጃዎችን ለመላክ @Fikerassefa
Download Telegram
የውሃ እና ኢነርጅ ሚንስትሩ ስለሺ ጌታሁን ዛሬ መግለጫ ሰጥተዋል፡፡

በካርቱሙ የሕዳሴው ግድብ ስብሰባ ግብጽ ኢትዮጵያ በዐመት 49 ቢሊዮን ኪውቢክ ውሃ ትልቀቅልኝ፤ የአስዋን ግድብ ከፍታ ከ165 ሜትር ዝቅ አይበልብኝ የሚል አቋሟን ትታለች ብለዋል፡፡ የአባይ ወንዝ ተፈጥሯዊ ፍሰት ይጠበቅ የሚለውን አዲስ ሃሳቧን ግን ኢትዮጵያ አልተቀበለችውም፡፡ ኢትዮጵያ ድርቅ ማለት ከ35 ቢሊዮን ሜትሪክ በታች ውሃ ሲፈስ ነው ስትል፣ ግብጽ ከ40 ቢሊዮን በታች ከሆነ ነው በማለቷ በድርቅ ትርጓሜ ላይ ስምምነት አለመደረሱን ዋዜማ ራዲዮ ዘግቧል፡፡

@YeneTube @FikerAssefa
በወላይታ ዞን እስር ላይ የነበሩ ግለሰቦች መፈታታቸው ተገለፀ!

የወላይታ ዞን ክልልነት ጥያቄን ተከትሎ ከታኅሳስ 9/2012 ጀምሮ የታሰሩ ግለሰቦች ከወላይታ ብሔራዊ ንቅናቄ ጽሕፈት ቤት ኃላፊ አንዱዓለም ታደሰ ውጪ ከእስር መፈታታቸው ተገለፀ። በደቡብ ክልል ወላይታ ዞን ወላይታ ሶዶ ከተማ ከትናንት ታኅሳስ 9/2012 ምሽት ጀምሮ እስከ አርብ ጠዋት ድረስ ስድስት ሰዎች በቁጥጥር ስር ውለው የቆዩ ሲሆን ከግለሰቦቹ መካከል ከወብን ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ውጪ ሁሉም መለቀቃቸውን የወላይታ ብሔራዊ ንቅናቄ አስታውቋል።

በቁጥጥር ስር ውለው የቆዩት ግለሰቦች በማኅበራዊ ትስስር ገጾች የክልልነት ጥያቄውን አስመልክቶ ሰፊ ንቅናቄ ሲያደርጉ የነበረ ሲሆን፣ በቁጥጥር ስር የዋሉትም ታኅሳስ 10/2012 ከሚደረገው ሰላማዊ ሰልፍ ጋር ግንኙነት አላቸው በሚል ምክንያት እንደነበር ተገልጿል።ታኅሳስ 10 ረፋዱ ላይም ወርቅነህ ገበየሁ እና አሸናፊ ከበደ የተባሉ ግለሰቦች የተለቀቁ ሲሆንኅ ከሰዓት በኋላ ደግም የቀሩት ተለቀዋል። የወብን ጽሕፈት ቤት ኃላፊ አንዱዓለም ታደሰ ትላንት አመሻሹ ላይ በቁጥጥር ስር መዋላቸውን የገለፁት ተከተል ላቤና፤ አሸናፊ ከበደ፣ ወርቅነህ ገበየሁ እና ቡዟየሁ ቡቼ የተባሉት ከእስር የተፈቱ ግለሰቦች በማኅበራዊ ትስስር ገጾች የሚሟገቱ እንደሆኑ ገልፀዋል።

ብርቱካን የተባሉ አንዲት ሴት ግለሰብም በቁጥጥር ስር ውለው መቆየታቸውን የወላይታ ብሔራዊ ንቅናቄ የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ ተከተል ላቤና ለአዲስ ማለዳ ገልፀዋል።ኃላፊው በቁጥጥር ስር እንዲቆይ መደረጉ አግባብነት የሌለው ነው ያሉ ሲሆን፣ ለመጠየቅ ወደ ፖሊስ ጣቢያ ስንሔድ ለማየት ተከልክለናል ብለዋል። ‹‹በመልካም ሁኔታ ላይ እንደሚገኝ ለማረጋገጥ ችለናል፤ ሆኖም ሊያሳስረው የሚችል ምንም ዓይነት ምክንያት ባለመኖሩ በአፋጣኝ ሊፈታ ይገባል›› ሲሉ ለአዲስ ማለዳ ተናግረዋል።

የክልልነት ጥያቄው በተባለው ጊዜ ምላሽ አለማግኘቱንም ተከትሎ፣ በወላይታ ዞን ካሉት 22 ወረዳዎች ሶዶ እና አረካ ሳይጨምር በ20 ወረዳዎች ላይ ሰላማዊ ሰልፍ መደረጉንም ጨምረው ገልፀዋል። ሰልፉ ፍፁም ሰላማዊ እንደነበር እና በሰዎች ላይ ምንም ዓይነት ጉዳት እንዳልደረሰም ተገልጿል።ሕዝቡ በሰላማዊ ሰልፉ ወቅት ፍፁም ሰላማዊ ነበር። ይሄንንም ተከትሎ ምንም ዓይነት ጉዳት በሰዎች ላይ እንዳልደረሰ የመከላከያ ሰራዊት አባላት በዞኑ እና በሶዶ ከተማ በስፋት እየተንቀሳቀሱ መሆኑን ተከተል ተናግረዋል።

በወረዳዎቹ ከተደረገው ሰላማዊ ሰልፍ በኋላም በወላይታ ሶዶ ከተማ የደቡብ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳደር ጌታሁን ጋረደው እና የዞኑ አስተዳዳሪ እንዲሁም አገር ሽማግሌዎች እና የሀይማኖት አባቶች የተሳተፉበት ውይይት ተደርጓል። የክልሉ ምክር ቤት ሕገ መንግሥቱን በተከተለ መንገድ የዞኑን ጥያቄ ማስተናገድ እንዳለበትም በውይይቱ እንደተጠቆመ ታውቋል።‹‹በከተማዋ ተዘግተው የነበሩ የንግድ ማእከላት ወደ ቀድሞ ሥራቸው በመመለስ ላይ ይገኛሉ›› ያሉት ተከተል፣ የክልልነት ጥያቄው ተገቢውን ምላሽ እስኪያገኝ ድረስ የክልልነት ጥያቄው በሰላማዊ መንገድ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ገልጸዋል።የወላይታ ዞን አስተዳዳሪን በጉዳዩ ላይ በስልክ እና በጽሑፍ መልዕክት ለማነጋገር አዲስ ማለዳ በተደጋጋሚ ጥረት ብታደርግም ሳይሳካላት ቀርቷል።

Via Addis Maleda
@YeneTube @FikerAssefa
ዶክተር አሚን ጤና ሚኒስቴርን በዚህ ሳምንት በይፋ ይሰናበታሉ።ለሌላም ስራ ወደ አሜሪካ ያቀናሉ።

የስራ መልቀቂያ እንዳስገቡ ከወራት በፊት የተነገረላቸው የጤና ሚኒስትሩ ወጣቱ ዶክተር አሚን አማን ዛሬ የመልቀቂያቸው ደብዳቤ ተቀባይነት አግኝቶ ከሚኒስትር መ/ቤቱን ላገለገሉበት የምስጋና ሰርተክፌት እንደተዘጋጀ ተነግሮኛል ። ጎዴ ለስራ የሚገኙት ዶ/ አሚን ነገ ወይም ከነገ ወዲያ የመልቀቂያ ደብዳቤያቸን ተቀብለው ጤና ሚኒስቴርን ይሰናበታሉ።ዶክተር አሚን አሜሪካ የሚገኝ ለግዜው ስሙ ያልተነገረኝ አለም አቀፍ ተቋም ስራ እንደገኙም ከቅርብ ምንጮች አረጋግጫለው።

Via Tesfaye Getinet
@YeneTube @FikerAssefa
በሞጣ የሐይማኖት ተቋማት ቃጠሎን ለማውገዝ በተደረገ የጅግጅጋ ሰልፍ የሰው ሕይወት አለፈ «በመጨረሻ በተፈጠረ ብጥብጥብ 1 ግለሰብ ሕይወታቸው እንዳለፈ ማረጋገጥ እንችላለን» ሲሉ የሶማሌ ክልል ፕሬዝዳንት አማካሪ መሐመድ ኦላድ ለዶይቼ ቬለ ተናግረዋል

@YeneTube @FikerAssefa
ፕሬዝደንት ሳህለ ወርቅ ወ/ሮ ፍሬወይኒ መብርሀቱን አነጋገሩ!

የኢፌዲሪ ፕሬዝደንት ሣህለ ወርቅ ዘውዴ የአለም አቀፉ መገናኛ ብዙሀን CNN የ2019 አመት ጀግና በሚል የተሸለመችውን ወ/ሮ ፍሬወይኒ መብርሀቱን ዛሬ ምሽት በፅ/ቤታቸው ተቀብለው አነጋግረዋል፡፡ፕሬዚዳንቷ ሽልማቱ ትልቅ መነሳሳትን የሚፈጥር ስለሆነ ከዚህ የበለጠ ውጤት ለማስመዝገብና ሴት ኢትዮጵያውያንን ተጠቃሚ ለማድረግ ተሸላሚዋ ጠንክራ እንድትሰራ ያሳሰቡ ሲሆን ለዚህም የመንግስት ድጋፍ እንደማይለያት አረጋግጠዋል፡፡

ወይዘሮ ፍሬወይኒ በበኩሏ በፕሬዚዳንቷ በተደረገላት አቀባበል መደሰቷን በመግለፅ ክብሩ ለሁሉም ኢትዮጵውያን ሴቶች እንደሆነ ተናግራለች፡፡ በሽልማቱ ያገኘችውን መነሳሳትም ሰፊ ስራዎችን በመስራት እንደምታስቀጥል እና በዘርፉ በርካታ የስራ እድል የመፍጠር ውጥን እንዳላት ገልፃለች፡፡ወይዘሮ ፍሬወይኒ በሴቶች የወር አበባ ወቅት ተገቢው የንፅሕና መጠበቂያ በማይገኝባት ኢትዮጵያ ዳግም አገልግሎት መስጠት የሚችል የወር አበባ መቀበያ አዘጋጅታ ለተማሪዎች እንዲዳረስ ማስቻሏ ለሽልማት እንዳበቃት ይታወሳል፡፡

Via EPA
@YeneTube @FikerAssefa
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
በምርጫ 2012 የተሻሉ ፖሊሲዎችን ለህዝብ እንደሚያስተዋውቅ የኦሮሞ ፌደራሊስት ኮንግረስ ፓርቲ /ኦፌኮ/ አስታወቀ፡፡

@YeneTube @Fikeeassefa
Merry Christmas to all Christians around the world. I wish you a joyous holiday season and may it be an occasion to count all blessings.

Doctor Abiy Ahmed
@Yenetube @Fikerassefa
Forwarded from YeneTube
እንኳን አደረሳችሁ

በ አዲስ አበባ የተለያዩ እቃዎች አስመጪ
ብራንድ የወንድና የሴት ሰዓቶች
የሴት ቦራሳዎች
የመዋቢያ እቃዎች
አልባሳት

የምናስመጣቸው እቃዎች ጥራት እና በቀላሉ ገበያ ላይ አለመገኘት እንዲሁም ወደ ክልል ከተሞች መላክ መቻላችን ለየት ያደርገናል ።

ቦሌ መዳንአለም ሞል
+251993014846

ከታች ባለው ሊንክ ገብተው ይጎብኙን ይምረጡ ይዘዙን

👇👇👇👇👇
https://tttttt.me/joinchat/AAAAAENXyUTam6WMV6_hmg
የውጪ ንግድ.m4a
2.6 MB
የኢትዮጵያ የወጪ እና ገቢ ንግድ ሚዛን መካከል ያለው ልዩነት መንበርቀቁን ቀጥሎበታል፡፡ የባለፈው አመትም 15 ቢሊዮን ዶላር ጉድለት ማሳየቱ ተነግሯል፡፡

Via:- Sheger FM

@Yenetube @Fikerassefa
የኤርትራው ፕሬዚዳንት ኢሳያስ አፈወርቂ ለይፋዊ የስራ ጉብኝት ዛሬ አዲስ አበባ ገቡ።

ከፕሬዚዳንት ኢሳያስ ጋርም የሀገሪቱ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ኦስማን ሳሌህ እና የፕሬዚዳንቱ አማካሪ የማነ ገብረአብ በጉብኝቱ ተካተዋል።

ፕሬዚዳንት ኢሳያስ አፈወርቂ ቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ሲደርሱም የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ አህመድን ጨምሮ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ኃላፊዎች አቀባበል አድርገውላቸዋል።

ፕሬዚዳንቱ ለሁለት አስርት ዓመታት ተቋርጦ የነበረው የኢትዮጵያ እና ኤርትራ ግንኙነት ከታደሰ በኋላ በተደጋጋሚ ኢትዮጵያን ጎብኝተዋል።
በአሁኑ ጉብኝታቸውም የሁለቱን ሀገራት ግንኙነት ወደላቀ ደረጃ ለማሳደግ ከከፍተኛ የመንግስት የስራ ኃላፊዎች ጋር ይወያያሉ ተብሎ ነው የሚጠበቀው።

Via:- FBC
@Yenetube @Fikerassefa
በጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት የሚዘጋጀው አዲስ ወግ የውይይት መድረክ በሂልተን ሆቴል እየተካሄደ ነው።

መድረኩ “የሚዲያው ሚና ሃሳቦችን ለማቀራረብ” በሚል መሪ ቃል ነው እየተካሄደ የሚገኘው።

አዲስ ወግ የውይይት መድረክ ከዚህ ቀደም በተለያዩ ርዕሰ ጉዳዮች ላይ በአዲስ አበባ እና ድሬዳዋ ከተሞች መካሄዱ ይታወሳል።

በዛሬው መድረክ በዋናነት የሚዲያ አካላት የሃገርን ሰላም እና አንድነት ከማስጠበቅ አንጻር በሚኖራቸው ሚና ላይ ውይይት ይደረጋል ተብሏል።

አዲስ ወግ የውይይት መድረክ በተለያዩ ሃገራዊ እና ወቅታዊ ጉዳዮች ላይ ምክክር በማድረግ የንግግር ባህል ማሳደግን አላማው ያደረገ መድረክ ነው።

@Yenetube @Fikerassefa
💥እናመሰግናለን💥
በናንተ ልፋት እና ድካም 90 ሺ አድርሳችሁታል ቻናላችሁን እናመሰግናለን።

አብሮነታችሁን እጅግ በጣም እንፈልገዋለን 🙏
ቻናላችሁን ለጓደኛዎ ማስተዋወቅ እንዳይረሱ👏

T.me/Yenetube
በአዲስ አበባ የፊታችን ቅዳሜ እና እሁድ በአራት ክፍለ ከተሞች ውሃ በከፊል ይቋረጣል ተባለ

የአዲስ አበባ ውሃና ፍሳሽ ባለሥልጣን የፊታችን ቅዳሜ ታህሳስ 18 እና ዕሁድ ታህሳስ 19 ቀን 2012 ዓ.ም. ከጠዋቱ 1 ሰዓት ጀምሮ እስከ ምሽቱ 12፡00 ሰዓት ድረስ በአራት ክፍለ ከተሞች ውሃ በከፊል አይኖርም ብሏል።

ከላይ በተጠቀሱት ቀናትም የገፈርሣ ውሃ ማጣሪያ ጣቢያ የገንዳ አጠባ ሥራ ስለሚከናወን ቀጥሎ በተጠቀሱት ወረዳዎች ውሃ አይኖርም ብሏል።

#አዲስ ከተማ ክ/ከተማ ከወረዳ 4 እስከ10፣
#ጉለሌ ክ/ከተማ ከወረዳ 1 እስከ 8፣
#አራዳ ክ/ከተማ ወረዳ 1፣ 8፣ 9 እና 1ዐ፣
#ኮልፌ ቀራንዮ ክ/ከተማ ከወረዳ 9 እስከ 15

የውሃ አገልግሎት በከፊል ስለሚቋረጥ የባለሥልጣኑ ደንበኞች ከወዲሁ ጥንቃቄ አድርጉ ተብላችኋል።

Via:- ኢትዮ ኤፍ ኤም
@Yenetube @Fikerassefa
ሰበር ዜና

የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ዛሬ ባወጣው መግለጫ ለአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት 5 አፋጣኝ ምላሽ የሚሹ ያላቸውን ጥያቄዎችን ያቀረበ ሲሆን የክልሉ መንግስትም ለጣያቄዎቹ አስቸኳይ ምላሽ እንዲሰጥ ተጠይቋል፡፡

1. በሞጣ የደረሰውን ችግር ለማጣራት በፌዴራል እስልምና ም/ቤቱ ለተሰየመው አጣሪ ኮሚቴ ክልሉ አስፈላጊውን እገዛ እንዲደረግ፣

2. ይህን ወንጀል ከመፈጸም በተጨማሪ ከባሕልና ልማዳችን ውጪ በኾነ መንገድ እምነት ተቋማት አቃጥለው ፉከራ እና ጭፈራ ሲያሰሙ የነበሩ ግለሰቦችና አካላትን በአስቸኳይ በመያዝ ተገቢውን ፍርድ አንዲያገኙ እንዲያደርግ፣

3. የንብረትም ሆነ ሌላ ጉዳት የደረሰባቸው ግለሰቦች እና ድርጅቶች ተገቢው ካሳ እንዲሰጣቸውና በክልሉ መንግሥት ይቅርታ እንዲጠየቁ፣

4. የተቃጠሉ መስጂዶችን በአፋጣኝ በማስገንባትየ ዘወተር አገልግሎታቸውን እንዲሰጡ እንዲደረግ፣

5. በአጠቃላይ በክልሉ የሚገኙ ሙስሊሞች ያለባቸውን ችግር የሚያጣራ እና የሚፈታ ኮሚቴ በአጭር ጊዜ ተቋቁሞ ወደ ተግባር እንዲገባ እንዲያደርግ በድጋሚ እናሳስባለን በማለት አምስቱን ጥያቄዎች ምክር ቤቱ አስቀምጧል፡፡

@Yenetube @Fikerassefa
👍1
የአጼ ፋሲል ቤተ መንግስት ህንጻዎች ለመጠገን የ400 ሚሊየን ብር የፕሮጀክት ጥናት መጠናቀቁን የጎንደር የአለም አቀፍ ቅርሶች አስተዳዳሪ አስታወቁ፡፡

አስተዳዳሪው አቶ ጌታሁን ስዩም ለኢዜአ እንደገለፁት የፕሮጀክት ጥናቱ በቀጣዮቹ አምስት አመታት የጥገና ስራውን ደረጃ በደረጃ ለማካሄድ የሚያስችል ነው፡፡

በጥናቱ አማራ ክልልን ጨምሮ የፌደራል የቅርስ ጥናትና ጥበቃ ባለስልጣን ከፍተኛ ባለሙያዎች ተሳታፊ መሆናቸውን አስተዳዳሪው ተናግረዋል፡፡
የጥገና በጀቱ በፌዴራል መንግስት ድጋፍ እንደሚሸፈንና አለም አቀፍ ለጋሽ ድርጅቶችም ድጋፍ እንደሚያደርጉ ገልጸዋል።

ይህ በእንዲህ እንዳለ ከክልሉ መንግስት በተመደበ በጀትና ከጎብኝዎች ገቢ በ36 ሚሊየን ብር የቤተ-መንግስቱ ዙሪያ አጥር ጥገና መጀመሩን አስተዳዳሪው ተናግረዋል።

የፌዴራል የቅርስ ጥናትና ጥበቃ ባለስልጣን ምክትል ዋና ዳይሬክተር ረዳት ፕሮፌሰር አበባው አያሌው የአጼ ፋሲል ቤተ መንግስት ህንጻዎች ከተጋረጠባቸው አደጋ ለመታደግ ጥናቶች መጠናቀቃቸውን አስታውቀዋል።

በ16ኛው ክፍለ ዘመን የታነጸው የአጼ ፋሲል ቤተ መንግስት ህንፃ እንደ አውሮፓውያን የቀመር ዘመን በ1979 በዩኔስኮ በአለም የሰው ሰራሽ ቅርስነት የተመዘገበ መሆኑ ይታወቃል፡፡

@YeneTube @Fikerassefa
የባሕር ዳር ዩኒቨርስቲ ከ2002 ዓ.ም ጀምሮ ላለፉት 10 ዓመታት አቋርጦት የነበረውን ‹ኦሪጅናል› የትምህርት ማስረጃ መስጠት ዳግም መጀመሩ ተገለጸ፡፡

በተለያዩ የትምህርት መስኮች ከባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ የተመረቁ ተማሪዎች ‹ኦሪጅናል› የትምህርት ማስረጃቸውን ላለፉት 10 ዓመታት ሳያገኙ መቆየታቸውን እና በቅርቡ ችግሩ መቀረፉን የዩኒቨርስቲው የሬጅስተራርና አልሙናይ ማኔጅመንት ዳይሬክተር አቶ ዘውዱ ጸጋየ ተናግረዋል።

ከጥቅምት 17/2012 ዓ.ም ጀምሮ የተማሪዎች ኦሪጅናል የትምህርት ማስረጃዎች ደረጃውን በጠበቀ ምሥጢራዊ ሕትመት ተዘጋጅቶ ባለጉዳይ በጠየቀ አንድ ወር ባልሞላ ጊዜ ውስጥ መስጠት መቻሉንም ነው ዳይሬክተሩ የገለፁት።

ሕትመቶቹ በቀላሉ ለሀሰተኛ ማስረጃ አገልግሎት እንዳይዉሉ ምሥጢራዊ በሆነ መንገድ እየተሠሩ መሆናቸውን አብመድ ዘግቧል።

@Yenetube @Fikerassefa
በጋምቤላ ክልል የጦር መሳሪያ ሲያዘዋውሩ የተገኙ ሰባት ግለሰቦች ቁጥጥር ስር ዋሉ!!

የጋምቤላ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን ህገ-ወጥ የጦር መሳሪያዎችን ሲያዘዋውሩ ያገኛቸውን ሰባት ተጠርጣሪዎች ባለፉት ሁለት ቀናት በቁጥጥር ስር ማዋሉን አስታወቀ።

የኮሚሽኑ ምክትል ኮሚሽነር ቱት ኮር ዛሬ ለኢዜአ እንደለጹት ተጠርጣሪዎቹ በቁጥጥር ስር የዋሉት ከ12 ህገ-ወጥ የጦር መሳሪዎችና ከ741 ጥይቶች ጋር ነው።

“ግለሰቦች የታያዙት ባለፉት ሁለት ቀናት በመንግስትና በግል ተሽከርካሪዎች የጦር መሳሪያዎችንና ጥይቶችን ጭነው ከኢታንግና ላሬ ወረዳዎች ወደ ጋምቤላ ከተማ ለማስገባት ሲሞክሩ ኢታንግ ኬላ ላይ በተደረገ ፍተሻ ነው” ብለዋል።

ተጠርጣሪዎቹ ታህሳስ 13/2012 ከምሽቱ 4፡00 ሰዓት አካባቢና ትላንት ረፋድ ላይ በተለያዩ ሁለት ተሽከርካሪዎች በመደበቅ በድምሩ 12 ክላሽንኮቭ ጠመንጃና 741 የክላሽና የብሬን ጠመንጃ ጥይትችን ወደ ጋምቤላ ሊያስገቡ ሲሉ መያዛቸውን ተናግረዋል።

በቁጥጥር ስር የዋሉት ተጠርጣሪዎቹ የምርመራ ሒደቱ እንደተጠናቀቀ ክስ እንደሚመሰረትባቸው የጠቆሙት ምክትል ኮሚሽነር ቱት ኮር መሰል የወንጀል ድርጊቶችን ለመከላከል የህብረተሰቡ ድጋፍ ተጠናክሮ እንዲቀጥልም ጥሪያቸውን አስተላልፈዋል።

Via:- EPA
@Yenetube @Fikerassefa
የንግድ ባንክ ጠቅላላ ተቀማጭ ከ7መቶ ቢሊዮን ብር በላይ መድረሱ ተገለፀ

በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የኮርፖሬት ኮሙዩኒኬሽን ተጠባባቂ ዳይሬክተር አቶ የአብስራ ከበደ ለኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት እንዳስታወቁት፣ የባንኩ ጠቅላላ ተቀማጭ ብር ከ7መቶ 12 ቢልዮን ብር በላይ የደረሰ ሲሆን ከተመሰረተም 77 ዓመታትን አስቆጥሯል። ባንኩ ሲመሰረት የመነሻ ካፒታሉ አንድ ሚሊዮን የማርያ ትሬዛ የነበረ ሲሆን፣ አሁኑ ላይ ከ7መቶ 12 ቢልዮን ብር በላይ ሃብት ማከማቸት ችሏል።
እንደዳይሬክተሩ ባንኩ አሁን ላይ ከ40ሺ በላይ ሰራተኞች እና ከ22ሚልዮን በላይ ደንበኞችን ማፍራት የቻለ ሲሆን በአገሪቱ ለተከናወኑ የልማት ስራዎች ባንኩ ዋንኛ የፋይናንስ ምንጭ በመሆን በማገልገል ላይ ነው።

@Yenetube @Fikerassefa
ሀዋሳ ሰላሟ ተረጋግጧል - ጥራቱ በየነ

የሀዋሳ ከተማ አስተዳደር ም/ከንቲባ አቶ ጥራቱ በየነ የቅዱስ ገብርኤል የንግስ በዓልን አስመልክቶ ከጋዜጤኞች ለቀረበ ጥያቄ መልስ ሰጡ፡፡

ከበዓላት ጋር ተያይዞ የሚደረግ የዋጋ ጭማሪ፣የቱሪስት ፍሰት እና የጸጥታ ሁኔታን አስመልክቶ ለቀረቡ ጥያቄዎች ምላሽ የሰጡት ም/ከንቲባው በከተማዋ ከሚስተናገዱ ታላላቅ መንፈሳዊ በዓል አንዱ የሆነውን የቅዱስ #ገብርኤል በዓል ስናስተናግድ ምንም አይነት #የዋጋ_ጭማሪ እንዳይኖር ከነጋዴው ማህበረሰብ ጋር ቅድመ ውይይት ተደርጓል ብለዋል፡፡

በተለይም በሀዋሳ ከተማ ከተካሄደው ሪፍረንደም በኃላ የከተማው ጸጥታ አስተማማኝ ደረጃ ላይ መድረሱን የገለጹት አቶ ጥራቱ በከተማዋ በርካታ ስብሰባዎች መካሄድ፣የከተማው ገቢ ማደግ እና የኢንቨስትመንት ፍላጎት ጥያቄ እየጨመረ መምጣት የሰላም መኖሩ አረጋጋጭ ነው ብለዋል፡፡

አቶ ጥራቱ አክለውም ከበዓሉ ዋዜማ ጀምሮ የከተማው ነዋሪ ሁሉ በዓሉ በሚከበርበት አካባቢ የጽዳት ዘመቻ እያደረጉ መሆኑን ሲገልጹ የበዓሉ ታዳሚዎች ያለምንም ስጋት ወደ ከተማዋ እንዲመጡ #በመጋበዝ_ጭምር ነው፡፡

Via:- ሀዋሳ ከተማ መንግስት ኮምንኬሽን
@Yenetube @Fikerassefa