እውነቱን በውሸት ለምን ትቀላቅላላችሁ?
ክፍል አንድ
በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኛ በሆነው፡፡
3፥71 የመጽሐፉ ሰዎች ሆይ! እውነቱን በውሸት ለምን ትቀላቅላላችሁ እውነቱንም እናንተ የምታውቁ ስትኾኑ ለምን ትደብቃላችሁ?
ቅጥፈት አንድ
የሐዋርያት ሥራ 7:15-16 ያዕቆብም ወደ ግብፅ ወረደ እርሱም ሞተ “አባቶቻችንም”፤ ወደ ሴኬምም አፍልሰው #አብርሃም #ከሴኬም #አባት #ከኤሞር ልጆች #በብር በገዛው መቃብር “ቀበሩአቸው”።
በአብርሃምና በሴኬም መካከል የትውልድ ልዩነት አለ፤ ሴኬም ይቅርና የሴኬም አባት ኤሞር የነበረው በአብርሃም ጊዜ ሳይሆን የአብርሃም የልጅ ልጅ በሆነው በያዕቆብ ጊዜ ነው፦
ዘፍጥረት 34:4-6 #ሴኬምም አባቱን #ኤሞርን ይህችን ብላቴና አጋባኝ ብሎ ነገረው። #ያዕቆብም ልጁን ዲናን እንዳስነወራት ሰማ፤ ልጆቹም ከከብቶቻቸው ጋር በምድረ በዳ ነበሩ፤ ያዕቆብም እስኪመጡ ድረስ ዝም አለ። #የሴኬም #አባት #ኤሞርም ይነግረው ዘንድ ወደ #ያዕቆብ ወጣ።
ልብ በሉ ሴኬም የያዕቆብን ልጅ ዲናን ሲያስነውር ማለት ሲደፍራት አይደለም አብርሃም አያቱ ይቅርና አባቱ ይስሐቅ ሞቷል፤ ታዲያ አብርሃም ከሴኬም አባት ከኤሞር ልጆች በብር መቃብር የገዛው መቼ ነው? ይህ እልም ያለ ቅጥፈት ነው፤ ታዲያ ማን ነው መቃብሩን ከሴኬም አባት ከኤሞር ልጆች የገዛው? ስንል የዘፍጥረት ዘጋቢ ያዕቆብ ነው ይለናል፦ ዘፍጥረት 33:18-19 #ያዕቆብም ከሁለት ወንዞች መካከል በተመለሰ ጊዜ በከነዓን ምድር ወዳለችው ወደ #ሴኬም ከተማ በደኅንነት መጣ፤ በከተማይቱም ፊት ሰፈረ። ድንኳኑን ተክሎበት የነበረውንም የእርሻውን ክፍል #ከሴኬም #አባት #ከኤሞር #ልጆች #በመቶ #በጎች ገዛው።
ውሸት ሁሌም ውሸት ነው፤ ልብ በሉ አብርሃም በህይወት ሳይኖር ያልገዛውን ገዛ ማለቱ ሲገርመን አብርሃም ገዛ የተባለው #በብር ሲሆን ያዕቆብ ግን #በመቶ #በጎች ነው፦
ኢያሱ 24:32 የእስራኤልም ልጆች ከግብፅ ያወጡትን የዮሴፍን አጥንት #ያዕቆብ #ከሴኬም #አባት #ከኤሞር ልጆች #በመቶ #በግ በገዛው #እርሻ በሴኬም ቀበሩት፤ እርሻውም ለዮሴፍ ልጆች ርስት ሆነ።
የሐዋርያት ሥራ ጸሐፊ ሉቃስ ወይም እስጢፋኖስ አሊያም የግሪክ እደ-ክታባትን ገልባጮች ቀጥፈዋል፤ አብርሃም በእርግጥም የመቃብር ስፍራ ገዝቷል የገዛው ከሴኬም አባት ከኤሞር ልጆች ሳይሆን ከኬጢያዊ ከኤፍሮን እርሻ ላይ ነው፤ የገዛውም በመቶ በግ ሳይሆን #በአራት #መቶ #ሰቅል ነው፦
ዘፍጥረት 23፥16-17 *አብርሃምም* የኤፍሮንን ነገር ሰማ አብርሃምም በኬጢ ልጆች ፊት የነገረውን #አራት #መቶ #ሰቅል መዝኖ #ለኤፍሮን ሰጠው ብሩም ለመሸጫ ለመለወጫ የሚተላለፍ ነበረ። በመምሬ ፊት ያለው ባለድርብ ክፍል የሆነው የኤፍሮን እርሻ ለአብርሃም ጸና።
ዘፍጥረት 49፥29-30 እንዲህ ብሎም አዘዛቸው። እኔ ወደ ወገኖቼ እሰበሰባለሁ በኬጢያዊ በኤፍሮን እርሻ ላይ ባለችው ዋሻ ከአባቶቼ ጋር ቅበሩኝ፤ እርስዋም በከነዓን ምድር በመምሬ ፊት ያለች፥ #አብርሃም ለመቃብር ርስት #ከኬጢያዊ #ከኤፍሮን ከእርሻው ጋር የገዛት፥ ባለ ድርብ ክፍል ዋሻ ናት።
ቅጥፈትን በጋራ እንከላከል፤ ኢንሻላህ ይቀጥላል……
✍ከወንድም ወሒድ ዑመር
https://tttttt.me/Wahidcom
ወሰላሙ አለይኩም
ክፍል አንድ
በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኛ በሆነው፡፡
3፥71 የመጽሐፉ ሰዎች ሆይ! እውነቱን በውሸት ለምን ትቀላቅላላችሁ እውነቱንም እናንተ የምታውቁ ስትኾኑ ለምን ትደብቃላችሁ?
ቅጥፈት አንድ
የሐዋርያት ሥራ 7:15-16 ያዕቆብም ወደ ግብፅ ወረደ እርሱም ሞተ “አባቶቻችንም”፤ ወደ ሴኬምም አፍልሰው #አብርሃም #ከሴኬም #አባት #ከኤሞር ልጆች #በብር በገዛው መቃብር “ቀበሩአቸው”።
በአብርሃምና በሴኬም መካከል የትውልድ ልዩነት አለ፤ ሴኬም ይቅርና የሴኬም አባት ኤሞር የነበረው በአብርሃም ጊዜ ሳይሆን የአብርሃም የልጅ ልጅ በሆነው በያዕቆብ ጊዜ ነው፦
ዘፍጥረት 34:4-6 #ሴኬምም አባቱን #ኤሞርን ይህችን ብላቴና አጋባኝ ብሎ ነገረው። #ያዕቆብም ልጁን ዲናን እንዳስነወራት ሰማ፤ ልጆቹም ከከብቶቻቸው ጋር በምድረ በዳ ነበሩ፤ ያዕቆብም እስኪመጡ ድረስ ዝም አለ። #የሴኬም #አባት #ኤሞርም ይነግረው ዘንድ ወደ #ያዕቆብ ወጣ።
ልብ በሉ ሴኬም የያዕቆብን ልጅ ዲናን ሲያስነውር ማለት ሲደፍራት አይደለም አብርሃም አያቱ ይቅርና አባቱ ይስሐቅ ሞቷል፤ ታዲያ አብርሃም ከሴኬም አባት ከኤሞር ልጆች በብር መቃብር የገዛው መቼ ነው? ይህ እልም ያለ ቅጥፈት ነው፤ ታዲያ ማን ነው መቃብሩን ከሴኬም አባት ከኤሞር ልጆች የገዛው? ስንል የዘፍጥረት ዘጋቢ ያዕቆብ ነው ይለናል፦ ዘፍጥረት 33:18-19 #ያዕቆብም ከሁለት ወንዞች መካከል በተመለሰ ጊዜ በከነዓን ምድር ወዳለችው ወደ #ሴኬም ከተማ በደኅንነት መጣ፤ በከተማይቱም ፊት ሰፈረ። ድንኳኑን ተክሎበት የነበረውንም የእርሻውን ክፍል #ከሴኬም #አባት #ከኤሞር #ልጆች #በመቶ #በጎች ገዛው።
ውሸት ሁሌም ውሸት ነው፤ ልብ በሉ አብርሃም በህይወት ሳይኖር ያልገዛውን ገዛ ማለቱ ሲገርመን አብርሃም ገዛ የተባለው #በብር ሲሆን ያዕቆብ ግን #በመቶ #በጎች ነው፦
ኢያሱ 24:32 የእስራኤልም ልጆች ከግብፅ ያወጡትን የዮሴፍን አጥንት #ያዕቆብ #ከሴኬም #አባት #ከኤሞር ልጆች #በመቶ #በግ በገዛው #እርሻ በሴኬም ቀበሩት፤ እርሻውም ለዮሴፍ ልጆች ርስት ሆነ።
የሐዋርያት ሥራ ጸሐፊ ሉቃስ ወይም እስጢፋኖስ አሊያም የግሪክ እደ-ክታባትን ገልባጮች ቀጥፈዋል፤ አብርሃም በእርግጥም የመቃብር ስፍራ ገዝቷል የገዛው ከሴኬም አባት ከኤሞር ልጆች ሳይሆን ከኬጢያዊ ከኤፍሮን እርሻ ላይ ነው፤ የገዛውም በመቶ በግ ሳይሆን #በአራት #መቶ #ሰቅል ነው፦
ዘፍጥረት 23፥16-17 *አብርሃምም* የኤፍሮንን ነገር ሰማ አብርሃምም በኬጢ ልጆች ፊት የነገረውን #አራት #መቶ #ሰቅል መዝኖ #ለኤፍሮን ሰጠው ብሩም ለመሸጫ ለመለወጫ የሚተላለፍ ነበረ። በመምሬ ፊት ያለው ባለድርብ ክፍል የሆነው የኤፍሮን እርሻ ለአብርሃም ጸና።
ዘፍጥረት 49፥29-30 እንዲህ ብሎም አዘዛቸው። እኔ ወደ ወገኖቼ እሰበሰባለሁ በኬጢያዊ በኤፍሮን እርሻ ላይ ባለችው ዋሻ ከአባቶቼ ጋር ቅበሩኝ፤ እርስዋም በከነዓን ምድር በመምሬ ፊት ያለች፥ #አብርሃም ለመቃብር ርስት #ከኬጢያዊ #ከኤፍሮን ከእርሻው ጋር የገዛት፥ ባለ ድርብ ክፍል ዋሻ ናት።
ቅጥፈትን በጋራ እንከላከል፤ ኢንሻላህ ይቀጥላል……
✍ከወንድም ወሒድ ዑመር
https://tttttt.me/Wahidcom
ወሰላሙ አለይኩም