ወሒድ የዕቅበተ ኢሥላም መጣጥፍት"Wahid Articles of Islamic Apologetics"
58.9K subscribers
68 photos
69 videos
19 files
1.72K links
ዳዒ ወሒድ በኢሥላም እና በክርስትና መካከል ያለውን ልዩነት እና አንድነት በንጽጽር የሚያስቀምጥ ወንድም ነው። ለዚህም የቋንቋ፣ የሰዋስው፣ የዐውድ፣ የተዛማች እና የሥነ አመክንዮ ሙግት በማቅረብ የሚታወቅ ተሟጋች እና ጦማሪ ነው። ለሙግቱ ነጥብ በዋነኝነት የሚጠቀምባቸው ቋንቋ ዐማርኛ፣ ግዕዝ፣ እንግሊዝኛ፣ ዐረቢኛ፣ ዕብራይስጥ እና ግሪክ ናቸው። መልካም የንባብ፣ የጥናት፣ የማነጻጸር ጊዜ ይሁንልዎ!
Download Telegram
የቁርአን ሱራህ

ክፍል አራት

በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡

“ዛሪያት”
“ዛሪያት” َالذَّارِيَات ማለት “በታኞች” ማለት ሲሆን አምሳ አንደኛው ሱራህ ነው፤ ይህም ስም በዚህ አንቀፅ ይገኛል፦
51፥1 መበተንን *በታኞች* وَالذَّارِيَاتِ በኾኑት ነፋሶች፡፡

“ጡር”
“ጡር” َالطُّورِ ማለት “የተራራ ስም” ሲሆን አምሳ ሁለተኛው ሱራህ ነው፤ ይህም ስም በዚህ አንቀፅ ይገኛል፦
52፥1 *በጡር* وَالطُّورِ እምላለሁ፡፡

“ነጅም”
“ነጅም” النَّجْمِ ማለት “ኮከብ” ማለት ሲሆን አምሳ ሶስተኛው ሱራህ ነው፤ ይህም ስም በዚህ አንቀፅ ይገኛል፦
53፥1 *በኮከብ* وَالنَّجْمِ እምላለሁ በወደቀ (በገባ) ጊዜ፡፡

“ቀመር”
“ቀመር” الْقَمَرُ ማለት “ጨረቃ” ማለት ሲሆን አምሳ አራተኛው ሱራህ ነው፤ ይህም ስም በዚህ አንቀፅ ይገኛል፦
54፥1 ሰዓቲቱ (የትንሣኤ ቀን) ተቃረበች፤ *ጨረቃም* الْقَمَرُ ተገመሰ፡፡

“ረሕማን”
“ረሕማን” الرَّحْمَٰنُ ማለት “እጅግ በጣም ሩኅሩህ” ማለት ሲሆን አምሳ አምስተኛው ሱራህ ነው፤ ይህም ስም በዚህ አንቀፅ ይገኛል፦
55፥1 *አል-ረሕማን* الرَّحْمَٰنُ ፤

“ዋቂዓህ”
“ዋቂዓህ” الْوَاقِعَةُ ማለት “መከራይት” ማለት ሲሆን አምሳ ስድስተኛው ሱራህ ነው፤ ይህም ስም በዚህ አንቀፅ ይገኛል፦
56፥1 *”መከራይቱ”* الْوَاقِعَةُ በወደቀች ጊዜ፡፡

“ሐዲድ”
“ሐዲድ” الْحَدِيدَ ማለት “ብረት” ማለት ሲሆን አምሳ ሰባተኛው ሱራህ ነው፤ ይህም ስም በዚህ አንቀፅ ይገኛል፦
57፥25 መልክተኞቻችንን በግልጽ ማስረጃዎች በእርግጥ ላክን፡፡ ሰዎችም በትክክል ቀጥ እንዲሉ መጽሐፎችንና ሚዛንን ወደእነርሱ አወረድን፤ *ብረትንም* الْحَدِيدَ በውስጡ ብርቱ ኀይልና ለሰዎችም መጠቃቀሚያዎች ያልሉበት ሲኾን አወረድን፡፡

“ሙጃደላህ”
“ሙጃደላህ” ወይም “ጂዳል” جِدَال ማለት “ክርክር” ማለት ሲሆን አምሳ ስምንተኛው ሱራህ ነው፤ ይህም ስም በዚህ አንቀፅ ይገኛል፦
58፥1 አላህ የዚያችን በባሏ ነገር *የምተከራከርህን* تُجَادِلُكَ እና ወደ አላህ የምታሰማውን ሴት ቃል በእርግጥ ሰማ፡፡ አላህም በንግግር መመላለሳችሁን ይሰማል፡፡ አላህ ሰሚ ተመልካች ነውና፡፡

“ሐሽር”
“ሐሽር” الْحَشْرِ ማለት “ማውጣት” ማለት ሲሆን አምሳ ዘጠነኛው ሱራህ ነው፤ ይህም ስም በዚህ አንቀፅ ይገኛል፦
59፥2 እርሱ ያ ከመጽሐፉ ሰዎች እነዚያን የካዱትን ከቤቶቻቸው ለመጀመሪያው *ማውጣት* الْحَشْرِ ያወጣቸው ነው፡፡

“ሙምተሒናህ”
“ሙምተሒናህ” مْتَحِنُوهُنَّ ማለት “ፈታኝት” ማለት ሲሆን ስልሳኛው ሱራህ ነው፤ ይህም ስም በዚህ አንቀፅ ይገኛል፦
60፥10 እላንተ ያመናችሁ ሆይ! ምእምናት ስደተኞች ኾነው በመጧችሁ ጊዜ ለሃይማኖት መሰደዳቸውን “ፈትኑዋቸው” فَامْتَحِنُوهُنَّ ፡፡

“ሶፍ”
“ሶፍ” ማለት صَفًّا “ሰልፍ” ማለት ሲሆን ስልሳ አንደኛው ሱራህ ነው፤ ይህም ስም በዚህ አንቀፅ ይገኛል፦
61፥4 አላህ እነዚያን እነርሱ ልክ እንደ ተናሰ ግንብ *የተሰለፉ* صَفًّا ኾነው በመንገዱ (በሃይማኖቱ) የሚጋደሉትን ይወዳል፡፡

“ጁሙዓህ”
“ጁሙዓህ” الْجُمُعَةِ ማለት “ስብስብ” ማለት ሲሆን ስልሳ ሁለተኛው ሱራህ ነው፤ ይህም ስም በዚህ አንቀፅ ይገኛል፦
62፥9 እናንተ ያመናችሁ ሆይ! *”በዐርብ”* الْجُمُعَةِ ቀን ለስግደት ጥሪ በተደረገ ጊዜ ወደ አላህ ማውሳት ኺዱ፡፡ መሸጥንም ተዉ፡፡ ይህ የምታውቁ ብትኾኑ ለእናንተ በጣም የተሻለ ነወ፡፡

“ሙናፊቁን”
“ሙናፊቁን” الْمُنَافِقُونَ ማለት “መናፍቃን” ማለት ሲሆን ስልሳ ሶስተኛው ሱራህ ነው፤ ይህም ስም በዚህ አንቀፅ ይገኛል፦
63፥1 *መናፍቃን* الْمُنَافِقُونَ በመጡህ ጊዜ «አንተ የአላህ መልክተኛ መኾንህን በእርግጥ ምለን እንመሰክራለን» ይላሉ፡፡
“ተጋቡን”
“ተጋቡን” التَّغَابُنِ ማለት “መጎዳዳት” ማለት ሲሆን ስልሳ አራተኛው ሱራህ ነው፤ ይህም ስም በዚህ አንቀፅ ይገኛል፦
64፥9 ለመሰብሰቢያ ቀን የሚሰበስብባችሁን ቀን አስታውሱ፤ ይህ *የመጎዳዳት* التَّغَابُنِ ቀን ነው፡፡

“ጦላቅ”
“ጦላቅ” طَلِّقُوهُنَّ ማለት “ፍቺ” ማለት ሲሆን ስልሳ አምስተኛው ሱራህ ነው፤ ይህም ስም በዚህ አንቀፅ ይገኛል፦
65፥1 አንተ ነቢዩ ሆይ! ሴቶችን መፍታት ባሰባችሁ ጊዜ፤ ለዒዳቸው *ፍቱዋቸው* فَطَلِّقُوهُنَّ ፡፡ ዒዳንም ቁጠሩ፡፡

“ተሕሪም”
“ተሕሪም” تُحَرِّمُ ማለት “እርም” ማለት ሲሆን ስልሳ ስድስተኛው ሱራህ ነው፤ ይህም ስም በዚህ አንቀፅ ይገኛል፦
66፥1 አንተ ነቢዩ ሆይ! አላህ ለአንተ የፈቀደልህን ነገር ሚስቶችህን ማስወደድን የምትፈልግ ስትኾን በአንተ ላይ ለምን *እርም* تُحَرِّمُ ታደርጋለህ? አላህም እጅግ መሓሪ አዛኝ ነው፡፡

“ሙልክ”
“ሙልክ” الْمُلْكُ ማለት “ንግሥና” ማለት ሲሆን ስልሳ ሰባተኛው ሱራህ ነው፤ ይህም ስም በዚህ አንቀፅ ይገኛል፦
67፥1 ያ ንግሥና الْمُلْكُ በእጁ የኾነው አምላክ ችሮታው በዛ፡፡ እርሱም በነገሩ ሁሉ ላይ ቻይ ነው፡፡

“ቀለም”
“ቀለም” الْقَلَمِ ማለት “ብርእ” ማለት ሲሆን ስልሳ ስምንተኛው ሱራህ ነው፤ ይህም ስም በዚህ አንቀፅ ይገኛል፦
68፥1 ኑን “በብርእ” وَالْقَلَمِ እምላለሁ በዚያም (መልአኮች) በሚጽፉት፡፡

“ሓቃህ”
“ሓቃህ” الْحَاقَّةُ ማለት “እውነት” ማለት ሲሆን ስልሳ ዘጠነኛው ሱራህ ነው፤ ይህም ስም በዚህ አንቀፅ ይገኛል፦
69፥1 *እውነትን* الْحَاقَّةُ አረጋጋጪቱ (ትንሣኤ)፡፡

“መዓሪጅ”
“መዓሪጅ” الْمَعَارِجِ ማለት “መሰላል” ማለት ሲሆን ሰባኛው ሱራህ ነው፤ ይህም ስም በዚህ አንቀፅ ይገኛል፦
70፥3 የሰማያት *መሰላሎች* الْمَعَارِجِ ባለቤት ከኾነው አላህ መላሽ የለውም፡፡

“ኑሕ”
“ኑሕ” نُوحًا ማለት “የአላህ መልእክተኝ” ሲሆን ሰባ አንደኛው ሱራህ ነው፤ ይህም ስም በዚህ አንቀፅ ይገኛል፦
71፥1 እኛ *ኑሕን* نُوحًا «ሕዝቦችህን አሳማሚ ቅጣት ሳይመጣባቸው በፊት አስጠንቅቅ በማለት ወደ ሕዝቦቹ ላክነው፡፡»

“ጂን”
“ጂን” الْجِنِّ ማለት “ስውራን” ማለት ሲሆን ሰባ ሁለተኛው ሱራህ ነው፤ ይህም ስም በዚህ አንቀፅ ይገኛል፦
72፥1 በል «እነሆ *ከጂን* الْجِنِّ የኾኑ ጭፈሮች ቁርአንን አዳመጡ፡፡‹እኛ አስደናቂ የኾነን ቁርአን ሰማንም› አሉ ማለት ወደ እኔ ተወረደ፡፡

“ሙዘሚል”
“ሙዘሚል” الْمُزَّمِّل ማለት “ተከናናቢ” ማለት ሲሆን ሰባ ሶስተኛው ሱራህ ነው፤ ይህም ስም በዚህ አንቀፅ ይገኛል፦
73፥1 አንተ *ተከናናቢው* الْمُزَّمِّلُ ሆይ፡፡

“ሙደሢር”
“ሙደሢር” الْمُدَّثِّرُ ማለት “ደራቢ” ማለት ሲሆን ሰባ አራተኛው ሱራህ ነው፤ ይህም ስም በዚህ አንቀፅ ይገኛል፦
74፥1 አንተ ልብስህን *ደራቢው* الْمُدَّثِّرُ ሆይ!

“ቂያማህ”
“ቂያማህ” الْقِيَامَةِ ማለት “ትንሣኤ” ማለት ሲሆን ሰባ አምስተኛው ሱራህ ነው፤ ይህም ስም በዚህ አንቀፅ ይገኛል፦
75፥1 (ነገሩ ከሓዲዎች እንደሚሉት) አይደለም፡፡ *በትንሣኤ* الْقِيَامَةِ ቀን እምላለሁ፡፡

“ደህር”
“ደህር” الدَّهْرِ ማለት “ዘመን” ማለት ሲሆን ሰባ ስድስተኛው ሱራህ ነው፤ ይህም ስም በዚህ አንቀፅ ይገኛል፦
76፥1 በሰው ላይ የሚታወስ ነገር ሳይኾን *ከዘመናት* الدَّهْرِ የተወሰነ ጊዜ በእርግጥ አልፎበታል፡፡

“ሙርሰላት”
“ሙርሰላት” َالْمُرْسَلَاتِ ማለት “የተላኩ” ማለት ሲሆን ሰባ ሰባተኛው ሱራህ ነው፤ ይህም ስም በዚህ አንቀፅ ይገኛል፦
77፥1 ተከታታይ ኾነው በተላኩት وَالْمُرْسَلَاتِ ፣

“ነበእ”
“ነበእ” النَّبَإِ ማለት “ዜና” ማለት ሲሆን ሰባ ስምንተኛው ሱራህ ነው፤ ይህም ስም በዚህ አንቀፅ ይገኛል፦
78፥2 ከታላቁ *ዜና* النَّبَإِ ከቁርአን ይጠያየቃሉ፡፡

“ናዚያት”
“ናዚያት” َالنَّازِعَاتِ ማለት “አውጪዎች” ማለት ሲሆን ሰባ ዘጠነኛው ሱራህ ነው፤ ይህም ስም በዚህ አንቀፅ ይገኛል፦
79፥1 በኃይል *አውጪዎች* وَالنَّازِعَاتِ በኾኑት፤

“ዐበስ”
“ዐበስ” عَبَسَ ማለት “ማጨፍገግ” ማለት ሲሆን ሰማንያኛው ሱራህ ነው፤ ይህም ስም በዚህ አንቀፅ ይገኛል፦
80፥1 ፊቱን *አጨፈገገ* عَبَسَ ፤ ዞረም፡፡

ኢንሻላህ ይቀጥላል…

ከወንድም ወሒድ ዑመር
https://tttttt.me/Wahidcom

ወሰላሙ አለይኩም
የቁርአን ሱራህ

የመጨረሻው ክፍል

በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡

“ተክዊር”
“ተክዊር” ማለት “መጠቅለል” ማለት ሲሆን ሰማንያ አንደኛው ሱራህ ነው፤ ይህም ስም በዚህ አንቀፅ ይገኛል፦
81፥1 ፀሐይ *”በተጠቀለለች”* ጊዜ፤ إِذَا الشَّمْسُ كُوِّرَتْ

“ኢንፊጣር”
“ኢንፊጣር” ማለት “መሰንጠቅ” ማለት ሲሆን ሰማንያ ሁለተኛው ሱራህ ነው፤ ይህም ስም በዚህ አንቀፅ ይገኛል፦
82፥1 ሰማይ *”በተሰነጠቀች”* ጊዜ፤ إِذَا السَّمَاءُ انفَطَرَتْ

“ሙጠፈፊን”
“ሙጠፈፊን” ማለት “ሰላቢዎች” ማለት ሲሆን ሰማንያ ሶስተኛው ሱራህ ነው፤ ይህም ስም በዚህ አንቀፅ ይገኛል፦
83፥1 *ለሰላቢዎች* ወዮላቸው፡፡ وَيْلٌ لِّلْمُطَفِّفِينَ

“ኢንሺቃት”
“ኢንሺቃት” ማለት “መቀደድ” ማለት ሲሆን ሰማንያ አራተኛው ሱራህ ነው፤ ይህም ስም በዚህ አንቀፅ ይገኛል፦
84፥1 ሰማይ *በተቀደደች* ጊዜ፤ إِذَا السَّمَاءُ انشَقَّتْ

“ቡሩጅ”
“ቡሩጅ” ማለት “ፈለካት” ማለት ሲሆን ሰማንያ አምስተኛው ሱራህ ነው፤ ይህም ስም በዚህ አንቀፅ ይገኛል፦
85፥1*የቡርጆች* ባለቤት በኾነችው ሰማይ እምላለሁ፡፡ وَالسَّمَاءِ ذَاتِ الْبُرُوجِ

“ጣሪቅ”
“ጣሪቅ” ማለት “መጪ” ማለት ሲሆን ሰማንያ ስድስተኛው ሱራህ ነው፤ ይህም ስም በዚህ አንቀፅ ይገኛል፦
86፥1 በሰማዩ በሌሊት *መጪውም* እምላለሁ፡፡ وَالسَّمَاءِ وَالطَّارِق ِ

“አዕላ”
“አዕላ” ማለት “የበላይ” ማለት ሲሆን ሰማንያ ሰባተኛው ሱራህ ነው፤ ይህም ስም በዚህ አንቀፅ ይገኛል፦
87፥1 *”ከሁሉ በላይ* የኾነውን ጌታህን ስም አሞግሥ፡፡ سَبِّحِ اسْمَ رَبِّكَ الْأَعْلَى

“ጋሺያህ”
“ጋሺያህ” ማለት “ሸፋኝቱ” ማለት ሲሆን ሰማንያ ስምንተኛው ሱራህ ነው፤ ይህም ስም በዚህ አንቀፅ ይገኛል፦
88፥1 *የሸፋኝቱ* (ትንሣኤ) ወሬ መጣህን? هَلْ أَتَاكَ حَدِيثُ الْغَاشِيَةِ

“ፈጅር”
“ፈጅር” ማለት “ጎህ” ማለት ሲሆን ሰማንያ ዘጠነኛው ሱራህ ነው፤ ይህም ስም በዚህ አንቀፅ ይገኛል፦
89፥1 *በጎህ* እምላለሁ፡፡ وَالْفَجْرِ

“በለድ”
“በለድ” ማለት “አገር” ማለት ሲሆን ዘጠናኛው ሱራህ ነው፤ ይህም ስም በዚህ አንቀፅ ይገኛል፦
90፥1 በዚህ *”አገር* (በመካ) እምላለሁ፡፡ لَا أُقْسِمُ بِهَٰذَا الْبَلَدِ

“ሸምስ”
“ሸምስ” ማለት “ፀሐይ” ማለት ሲሆን ዘጠና አንደኛው ሱራህ ነው፤ ይህም ስም በዚህ አንቀፅ ይገኛል፦
91፥1 *በፀሐይ* እና በብርሃኗ እምላለሁ፡፡ وَالشَّمْسِ وَضُحَاهَا

“ለይል”
“ለይል” ማለት “ሌሊት” ማለት ሲሆን ዘጠና ሁለተኛው ሱራህ ነው፤ ይህም ስም በዚህ አንቀፅ ይገኛል፦
92፥1 *በሌሊቱ* እምላለሁ (በጨለማው) በሚሸፍን ጊዜ፡፡ وَاللَّيْلِ إِذَا يَغْشَىٰ

“ዱሓ”
“ዱሓ” ማለት “ረፋድ” ማለት ሲሆን ዘጠና ሶስተኛው ሱራህ ነው፤ ይህም ስም በዚህ አንቀፅ ይገኛል፦
93፥1 በረፋዱ እምላለሁ፡፡ وَالضُّحَىٰ

“ኢንሻራህ”
“ኢንሻራህ” ማለት “ማስፋት” ማለት ሲሆን ዘጠና አራተኛው ሱራህ ነው፤ ይህም ስም በዚህ አንቀፅ ይገኛል፦
94፥1 ልብህን ለአንተ *አላሰፋንልህምን*? (አስፍተንልሃል)፡፡ أَلَمْ نَشْرَحْ لَكَ صَدْرَكَ

“ቲን”
“ቲን” ማለት “በለስ” ማለት ሲሆን ዘጠና አምስተኛው ሱራህ ነው፤ ይህም ስም በዚህ አንቀፅ ይገኛል፦
95፥1 *በበለስ* እና በዘይት ወይራ እምላለሁ፡፡ وَالتِّينِ وَالزَّيْتُونِ

“ዐለቅ”
“ዐለቅ” ማለት “የረጋ ደም” ማለት ሲሆን ዘጠና ስድስተኛው ሱራህ ነው፤ ይህም ስም በዚህ አንቀፅ ይገኛል፦
96፥2 ሰውን *ከረጋ ደም* በፈጠረው (ጌታህ ስም)፡፡ خَلَقَ الْإِنسَانَ مِنْ عَلَقٍ

“ቀድር”
“ቀድር” ማለት “ውሳኔ” ማለት ሲሆን ዘጠና ሰባተኛው ሱራህ ነው፤ ይህም ስም በዚህ አንቀፅ ይገኛል፦
97፥1 እኛ (ቁርኣኑን) *በመወሰኛይቱ* ሌሊት አወረድነው፡፡ إِنَّا أَنزَلْنَاهُ فِي لَيْلَةِ الْقَدْرِ

“በይናህ”
“በይናህ” ማለት “ግልፅ” ማለት ሲሆን ዘጠና ስምተኛው ሱራህ ነው፤ ይህም ስም በዚህ አንቀፅ ይገኛል፦
98፥1 እነዚያ ከመጽሐፉ ባለቤቶች ከአጋሪዎቹም የካዱት *ግልጹ* አስረጅ እስከ መጣላቸው ድረስ (ከነበሩበት ላይ) ተወጋጆች አልነበሩም፡፡ لَمْ يَكُنِ الَّذِينَ كَفَرُوا مِنْ أَهْلِ الْكِتَابِ وَالْمُشْرِكِينَ مُنفَكِّينَ حَتَّىٰ تَأْتِيَهُمُ الْبَيِّنَةُ

“ዘልዘላህ”
“ዘልዘላህ” ማለት “መንቀጥቀጥ” ማለት ሲሆን ዘጠና ዘጠነኛው ሱራህ ነው፤ ይህም ስም በዚህ አንቀፅ ይገኛል፦
99፥1 ምድር (በኀይል) *መንቀጥቀጥዋን* በተንቀጠቀጠች ጊዜ፤ إِذَا زُلْزِلَتِ الْأَرْضُ زِلْزَالَهَا

“ዓዲያት”
“ዓዲያት” ማለት “ሩዋጮች” ማለት ሲሆን መቶኛው ሱራህ ነው፤ ይህም ስም በዚህ አንቀፅ ይገኛል፦
100፥1 እያለከለኩ *ሩዋጮች* በኾኑት (ፈረሶች) እምላለሁ፡፡ وَالْعَادِيَاتِ ضَبْحًا

“ቃሪዓህ”
“ቃሪዓህ” ማለት “ቆርቋሪይቱ” ማለት ሲሆን መቶ አንደኛው ሱራህ ነው፤ ይህም ስም በዚህ አንቀፅ ይገኛል፦
101፥1 *ቆርቋሪይቱ* (ጩኸት)፤ الْقَارِعَةُ

“ተካሱር”
“ተካሱር” ማለት “መፎካከር” ማለት ሲሆን መቶ ሁለተኛው ሱራህ ነው፤ ይህም ስም በዚህ አንቀፅ ይገኛል፦
102፥1 በብዛት *መፎካከር* (ጌታችሁን ከመገዛት) አዘነጋችሁ፡፡ أَلْهَاكُمُ التَّكَاثُرُ
“ዐስር”
“ዐስር” ማለት “ጊዜ” ማለት ሲሆን መቶ ሶስተኛው ሱራህ ነው፤ ይህም ስም በዚህ አንቀፅ ይገኛል፦
103፥1 በጊዜያቱ እምላለሁ፡፡ وَالْعَصْرِ

“ሁመዛህ”
“ሁመዛህ” ማለት “ሃሜተኛ” ማለት ሲሆን መቶ አራተኛው ሱራህ ነው፤ ይህም ስም በዚህ አንቀፅ ይገኛል፦
104፥1 *ለሃሜተኛ* ለዘላፊ ሁሉ ወዮለት፡፡ وَيْلٌ لِّكُلِّ هُمَزَةٍ لُّمَزَةٍ

“ፊል”
“ፊል” ማለት “ዝሆን” ማለት ሲሆን መቶ አምስተኛው ሱራህ ነው፤ ይህም ስም በዚህ አንቀፅ ይገኛል፦
105፥1 *በዝሆኑ* ባለቤቶች ጌታህ እንዴት እንደሠራ አላወቅህምን? أَلَمْ تَرَ كَيْفَ فَعَلَ رَبُّكَ بِأَصْحَابِ الْفِيلِ

“ቁረይሽ”
“ቁረይሽ” ማለት “የጎሳ ስም” ሲሆን መቶ ስድስተኛው ሱራህ ነው፤ ይህም ስም በዚህ አንቀፅ ይገኛል፦
106፥1 *ቁረይሽን* ለማላመድ (ባለዝሆኖቹን አጠፋ)፡፡ لِإِيلَافِ قُرَيْشٍ

“ማዑን”
“ማዑን” ማለት “ትውስታ” ማለት ሲሆን መቶ ሰባተኛው ሱራህ ነው፤ ይህም ስም በዚህ አንቀፅ ይገኛል፦
107፥7 የዕቃ ትውስታንም (ሰዎችን) የሚከለክሉ ለኾኑት (ወዮላቸው)፡፡ وَيَمْنَعُونَ الْمَاعُونَ

“ከውሰር”
“ከውሰር” ማለት “በጎ ነገር” ማለት ሲሆን በጀነት ውስጥ የሚገኝ ፀጋ ነው፤ ከውሰር መቶ ስምንተኛው ሱራህ ነው፤ ይህም ስም በዚህ አንቀፅ ይገኛል፦
108፥1 እኛ በጣም ብዙ *በጎ ነገሮችን* ሰጠንህ፡፡ إِنَّا أَعْطَيْنَاكَ الْكَوْثَرَ

“ካፊሩን”
“ካፊሩን” ማለት “ከሃዲያን” ማለት ሲሆን መቶ ዘጠነኛው ሱራህ ነው፤ ይህም ስም በዚህ አንቀፅ ይገኛል፦
109፥1 በላቸው «እናንተ *ከሓዲዎች* ሆይ! قُلْ يَا أَيُّهَا الْكَافِرُونَ

“ነስር”
“ነስር” ማለት “እርዳታ” ማለት ሲሆን መቶ አስረኛው ሱራህ ነው፤ ይህም ስም በዚህ አንቀፅ ይገኛል፦
110÷1 የአላህ እርዳታና (መካን) መክፈት በመጣ ጊዜ፤ إِذَا جَاءَ نَصْرُ اللَّهِ وَالْفَتْحُ

“መሰድ”
“መሰድ” ማለት “ጭረታዊ ገመድ” ማለት ሲሆን መቶ አስራ አንደኛው ሱራህ ነው፤ ይህም ስም በዚህ አንቀፅ ይገኛል፦
111፥5 በአንገትዋ ላይ ከጭረት የኾነ ገመድ ያለባት ስትኾን፡፡ فِي جِيدِهَا حَبْلٌ مِّن مَّسَدٍ

“ፈለቅ”
“ፈለቅ” ማለት “ተፈልቃቂ” ማለት ሲሆን መቶ አስራ ሶስተኛው ሱራህ ነው፤ ይህም ስም በዚህ አንቀፅ ይገኛል፦
113፥1 በል «በተፈልቃቂው ጎህ ጌታ እጠበቃለሁ፡፡ قُلْ أَعُوذُ بِرَبِّ الْفَلَقِ

“ናስ”
“ናስ” ማለት “ሰዎች” ማለት ሲሆን መቶ አስራ አራተኛው ሱራህ ነው፤ ይህም ስም በዚህ አንቀፅ ይገኛል፦
114፥1 በል «በሰዎች ፈጣሪ እጠበቃለሁ፡፡ قُلْ أَعُوذُ بِرَبِّ النَّاسِ

መደምደሚያ
2:23 በባሪያችንም ላይ ካወረድነው በመጠራጠር ውስጥ ብትኾኑ *ከብጤው* مِثْلِهِ አንዲትን ሱራ አምጡ፡፡ እውነተኞችም እንደኾናችሁ ከአላህ ሌላ መስካሪዎቻችሁን ጥሩ፡፡

“ሚስል” مِثْل የሚለው ቃል “ብጤ” አሊያም “መሰል” ማለት ሲሆን ብጤነት ከምን አንጻር? ለአላህ ንግግር ብጤ አምጡ የሚለው ተግዳሮት ለመቋቋም ቁርአንን ቅዱ እና ኮፕይ አድርጉ ማለቱ ሳይሆን ከራሳችሁ ተባብራችሁ የቁርአንን ንግግር መሰረትና ውቅር፣ ዋልታና ማገር፣ ጥልቀትና ስፋት፣ ድርና ማግ አምጡ ማለት ነው፣ አላህ ንግግሩን ለነቢያችን ያወረደው በአረቢኛ ነው።
በአማርኛ፣ በእንግሊዝኛ፣ በፈረንሳይኛ ወዘተ የምናነባቸው የቁርአን ትርጉሞች ቁርአን ሳይሆኑ የቁርአን ትርጉም ናቸው፣ ቁርአን መሰረቱና ውቅሩ፣ ጥልቅቱና ስፋቱ አረቢኛ ነው፣ ይህ የቁርአን አንዱ አይነተኛ ባህርይ ነው፤ “ከላም” كَلَٰم ማለት “ቃል” አሊያም “ንግግር” ማለት ሲሆን ቃል ደግሞ የፊደላት ውቅር ነው፣ “ሃርፍ” حَرف በነጠላ “ፊደል” ማለት ሲሆን “ሁሩፍ” حروف ደግሞ በብዜት “ፊደላት” ማለት ነው፣ በቁርአን አሊፍ፣ ላም፣ ሚም፣ ሷድ፣ ራ፣ ካፍ፣ ሃ፣ ያ፣ ዓይን፣ ጧ፣ ሲን፣ ሐ፣ ቃፍ፣ ኑን ወዘተ እነዚህም በጥቅሉ 29 ሃርፎች ከአላህ ዘንድ የወረዱ የአላህ ንግግር ናቸው፤ የአነዚህ ሆሄያት ጥልቅ ትርጉማቸውን የሚያውቀው አላህ ብቻ ነው፣ እነዚህ ሃርፎች ቁርአን በወረደበት ጊዜ ለአረቦች ተግዳሮት ነበር፣ ይህ የቁርአን ዋልታና ማገር ሲሆን ታምር ነው፦
24፤1 ይህች *ያወረድናት* እና የደነገግናት *ሱራህ* سُورَةٌ ናት፡፡

ከወንድም ወሒድ ዑመር
https://tttttt.me/Wahidcom

ወሰላሙ አለይኩም
ፓለቲካ

ገቢር አንድ

በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡

5፥48 *በመካከላቸውም አላህ ባወረደው ሕግ ፍረድ*፡፡ فَاحْكُم بَيْنَهُم بِمَا أَنزَلَ اللَّه

ኢሥላም አጠቃላይ የሕይወት ዘይቤ ይዟል፤ ይህም ዘይቤ መንፈሳዊ፣ ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊ እና ፓለቲካዊ ዘይቤ ነው። "ፓለቲካ" πολιτικά የሚለው የግሪክ ቃል "ፓሊቲኮስ" πολιτικός ማለት "ዜግነት"citizen" ከሚል ቃል የመጣ ሲሆን "ፓሊስ" πόλις ማለትም "ከተማ" እና "ፓሊተስ" πολίτης ማለትም "ፓሊስይ" ያቀፈ የአስተዳደር ጥበብ ነው፤ በጥንቷ ሄለናዊ ግሪክ ከተማ የምትመራበት ፓሊሲይ ፓለቲካ ይባል ነበር።
በጥቅሉ ፓለቲካ ማለት በፓሊስይ ማለትም በመርሕ ዜጎችም የሚመራ ሥነ-መንግሥት ጥናት ነው፤ ሕገ-መንግሥት"constitution" ማለት ደግሞ የመንግሥት መርሕ፣ ሕግ እና መመሪያ ነው፤ "መንግሥት" አገዛዝ" "ኃይል" "ሥልጣን" በግሪክ "ክራቶስ" κράτος ይባላል፤ "ክራሲ" የሚለው ቃል "ክራቶስ" ከሚለው ግሪክ ቃል የመጣ ሲሆን የመንግሥት ቅርፅ መዳረሻ ቅጥያ ሆኖ ሲመጣ የተለያየ የመንግሥት እርከን ይሆናል፤ ይህንን ነጥብ በነጥብ እንመልከት፦

ነጥብ አንድ
"ፕሉቶ-ክራሲ"
"ፕሉቶ-ክራሲ" ማለት "የሃብት አገዛዝ" ማለት ነው፤ "ፕሉቶስ" πλοῦτος ማለት "ሃብት" ማለት ነው፤ ይህ አገዛዝ ሃብት ያላቸው ሃብታሞች ሃብት ስላላቸው በሃብታቸው የሚገዙበት ሥርዓት ነው፤ ይህ እሳቤ በድህረ ዘመነ አብርሆት ውድቅ ሆኗል።

ነጥብ ሁለት
"አርስቶ-ክራሲ"
"አርስቶ-ክራሲ" ማለት "የልዕልና አገዛዝ" ማለት ነው፤ "አርስቶስ" ἄριστος ማለት "ልዕልና" ማለት ነው፤ ይህ አገዛዝ ልዕልና ያላቸው ልዑላን በልዕልናቸው የሚገዙበት ሥርዓት ነው፤ እኛ ምርጥ ዘር ነን የሚል አቋም አላቸው፤ ይህ እሳቤ በድህረ ዘመነ አብርሆት ውድቅ ሆኗል።

ነጥብ ሥስት
"አውቶ-ክራሲ"
"አውቶ-ክራሲ" ማለት "የኃይል አገዛዝ" ማለት ነው፤ "አውቶስ" αὐτός ማለት "ኃይል" ማለት ነው፤ ይህ አገዛዝ ኃይል ያላቸው ኃያላን በኃይላቸው የሚገዙበት ሥርዓት ነው፤ ይህ እሳቤ በተለይ የሞናርኪስም እሳቤ በሳውዲ፣ በዖማን፣ በሲዊዘርላድ፣ በደቡብ ኮርያ ወዘተ ያለ እሳቤ
ነው፤ ይህ እሳቤ እየወደቀ ነው፤ ቅርብ ቀን ኢንሻላህ ሙሉ ለሙሉ ይወድቃል።

ነጥብ አራት
"ዲሞ-ክራሲ"
"ዲሞ-ክራሲ" ማለት "የሕዝብ አገዛዝ" ማለት ነው፤ "ዴሞስ" δημο ማለት "ሕዝብ" ማለት ነው፤ ይህ አገዛዝ በሕዝብ ምርጫ በተወካዮች ምክር ቤት ወይም በክልል ምክር ቤት ውስጥ የተመረጠው ሰው የሚገዛበት ሥርዓት ነው፤ ሕገ-መንግሥቱን የሚያረቁት ከአእምሮ አፍልቀው ነው።

ነጥብ አምስት
"ቴክኖ-ክራሲ"
"ቴክኖ-ክራሲ" ማለት "የሙያ አገዛዝ" ማለት ነው፤ "ቴክኖስ" τέχνη ማለት "ሙያ"skill" ወይም "እደ-ሙያ"art" ማለት ነው፤ ይህ አገዛዝ በእያንዳንዱ ሚኒስትሪ ሚኒስቴ መሆን ያለበት የሙያው ባለቤት ነው የሚል እሳቤ ነው፤ ለምሳሌ በጤና ሚኒስትሪ ሜዲካል ያጠና ዶክተር፤ በትምህርት ሚኒስቴር ፔዳጎጂ ያጠና ሚኒስተር፣ በግብርና ሚኒስትሪ ግብርና ያጠና ሚኒስቴር ወዘተ የሚመራበት እሳቤ ነው። "ሚንስትሪ" ማለት "አገልግሎት" ማለት ሲሆን "ሚንስተር" ማለት "አገልጋይ" ማለት ነው፤ ይህ እሳቤ በአንጻራዊ ተመራጭ ነው።

ነጥብ ስድስት ኢስላም የያዘውን ፓለቲካዊ ዘይቤ ቴኦ-ክራሲ ሲሆን ኢንሻላህ በክፍል ሁለት ይህንን እሳቤ እንቀጥላለን...

ከወንድም ወሒድ ዑመር
https://tttttt.me/Wahidcom

ወሰላሙ አለይኩም
ፓለቲካ

ገቢር ሁለት

በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡

3፥189 *የሰማያትና የምድር ንግሥና ለአላህ ብቻ ነው*፡፡ አላህም በነገሩ ሁሉ ላይ ቻይ ነው፡፡ وَلِلَّهِ مُلْكُ السَّمَاوَاتِ وَالْأَرْضِ ۗ وَاللَّهُ عَلَىٰ كُلِّ شَيْءٍ قَدِيرٌ

ነጥብ ሥድስት
"ቴኦ-ክራሲ"
"ቴኦ-ክራሲ" ማለት "የአምላክ አገዛዝ" ማለት ነው፤ "ቴኦስ" θεός ማለት "አምላክ" ማለት ነው፤ በክፍል አንድ ያየናቸው የአገዛዝ ቅርጽ ምክር ቤት ውስጥ ያሉትን ሕገ-መንግሥት የሚያረቁት ከሰው አእምሮ ነው፤ ነገር ግን በቴኦክራሲ ቅርጽ መመሪያው መለኮታዊ ብቻ ነው። "መጅሊስ" مجلس‎ የሚለው የዐረቢኛ ቃል "ሲኖዶስ" σῠ́νοδος የሚለው የግሪክ ቃል ትርጉማቸው "ምክር ቤት"council" ማለት ነው፤ እዚህ ምክር ቤት ውስጥ ሕገ-መንግሥቱ ሸሪዓህ ነው፤ “ሸሪዓህ” شَرِيعَة የሚለው ቃል "ሺርዓህ” شِرْعَة ማለትም "ሕግ" ከሚለው የስም መደብ የመጣ ሲሆን "ትክክለኛ ሕግ" ማለት ነው፦
45፥18 *ከዚያም ከነገሩ ከሃይማኖት "በትክክለኛይቱ ሕግ" ላይ አደረግንህ*፡፡ ثُمَّ جَعَلْنَاكَ عَلَىٰ شَرِيعَةٍ مِّنَ الْأَمْرِ
5፥48 *ከእናንተ ለሁሉም ሕግን እና መንገድን አደረግን*፡፡ لِكُلٍّ جَعَلْنَا مِنكُمْ شِرْعَةً وَمِنْهَاجًا

አላህ ለሁሉም መልእክተኞች "ሕግ" እና "መንገድ" አድርጓል፤ “መንገድ” ተብሎ የተቀመጠው ቃል “ሚንሃጅ” مِنْهَاج ማለትም "ፋና" ማለት ሲሆን “መንሃጅ” منہاج የሚለው ቃል ጋር ተመሳሳይ ነው፤ ይህ ሕግ የሚዋቀረው ውቅር አራት ሲሆኑ፤ እነርሱም፦
1ኛ. “ቁርኣን” قرآن‌‎ ማለትም የአላህ ቃል፣
2ኛ. “ሡናህ” سنة የነብያችን"ﷺ" ሰሒህ ሐዲስ፣
3ኛ. “ቂያሥ” قياس‌‎ “ማመጣጠን”Analogy”
4ኛ. “ኢጅማዕ” إجماع‌‎ ማለትም የዐሊሞች ስብስብ ናቸው።
ስለዚህ ፍርድ ከአላህ በወረደው ሕግ ይፈረዳል፦
5፥48 *በመካከላቸውም አላህ ባወረደው ሕግ ፍረድ*፡፡ فَاحْكُم بَيْنَهُم بِمَا أَنزَلَ اللَّه

“ፍረድ” ለሚለው ቃል የተጠቀመበት “ፈሕኩም” فَاحْكُمْ ሲሆን "ሑክም" ለሚለው የግስ መደብ ነው፤ “ሑክም” حُكْم የሚለው ቃል”ሐከመ” حَكَمَ ማለትም “ፈረደ” የመጣ ሲሆን ፍርድ” ወይም “ሕግ” ማለት ነው፤ “አሕካም” أحكام ደግሞ የሑክም ብዙ ቁጥር ነው፤ በኢስላም “ሕጎች” በአምስት ይከፈላሉ፤ እነርሱም፦
1ኛ. “ፈርድ” فرض ማለትም “የታዘዘ”
2ኛ. “ሙስተሐብ” مستحب” ማለትም “የተወደደ”
3ኛ. “ሙባሕ” مباح ማለትም “የተፈቀደ”
4ኛ. “መክሩህ” مكروه” ማለትም “የተጠላ”
5ኛ. “ሐራም” حرام” ማለትም “የተከለከለ” ናቸው።
“ፊቅህ” فقه ማለት “ጥልቅ መረዳት” ማለት ሲሆን የሥነ-ሕግ ጥናት”the study of law” ነው፤ ሕግ አዋቂ ደግሞ “ፈቂህ” فقيه ይባላል፤ “ፊቅህ” ማለት ቋንቋዊ ትርጉሙ “መረዳት” ማለት ነው፦
6፥98 *"ለሚያወቁ" ሕዝቦች አንቀጾችን በእርግጥ ዘረዘርን*፡፡ قَدْ فَصَّلْنَا الْآيَاتِ لِقَوْمٍ يَفْقَهُونَ

“ሚያወቁ” ተብሎ የተቀመጠው ቃል “የፍቀሁነ” يَفْقَهُونَ ሲሆን “ሚረዱ” ማለት ነው። ሙስሊሙ የስልጣን ባለቤቶች ለሆኑት ለአሚሮቻችን ይታዘዛል፤ የሚያወዘግብ ነገር ካለ ወደ አላህ ቁርኣን እና ወደ መልእክተኛው ሐዲስ መረጃ እና ማስረጃ ማግኘት ነው፦
4፥59 እናንተ ያመናችሁ ሆይ! አላህን ተገዙ፤ መልክተኛው እና *ከእናንተም የስልጣን ባለቤቶችን ታዘዙ*፡፡ በማንኛውም ነገር ብትከራከሩ በአላህ እና በመጨረሻው ቀን የምታምኑ ብትኾኑ *የተከራከራችሁበትን ነገር ወደ አላህ እና ወደ መልክተኛው መልሱት*፡፡ ይህ የተሻለ መጨረሻውም ያማረ ነው፡፡ يَا أَيُّهَا الَّذِينَ آمَنُوا أَطِيعُوا اللَّهَ وَأَطِيعُوا الرَّسُولَ وَأُولِي الْأَمْرِ مِنكُمْ ۖ فَإِن تَنَازَعْتُمْ فِي شَيْءٍ فَرُدُّوهُ إِلَى اللَّهِ وَالرَّسُولِ إِن كُنتُمْ تُؤْمِنُونَ بِاللَّهِ وَالْيَوْمِ الْآخِرِ ۚ ذَٰلِكَ خَيْرٌ وَأَحْسَنُ تَأْوِيلًا

ቀደምት ሰለፎች የስልጣን ባለቤቶች የሆኑትን ኸሊፋዎች ይታዘዙ ነበር። "ኸሊፋህ" خَلِيفَة ማለት "ምትክ" ማለት ሲሆን "ኺላፋህ" خِلافَة ማለት ደግሞ "ተተኪ" ማለት ነው።
ከ 632–661 ድህረ-ልደት"AD" የነበሩት "አል-ኺላፈቱ አር-ረሺዳህ" اَلْخِلَافَةُ ٱلرَّاشِدَة ማለትም "ትክክለኛ ተተኪ" አቡበከር ሲዲቅ፣ ዑመር ኢብኑል ኸጧብ፣ ዑስማን ኢብኑ ዐፋን እና ዐሊይ ኢብኑ አቡ ጧሊብ ናቸው። ስለ እነርሱ ዘመነ-መግቦት ነብያችን"ﷺ" እንዲህ በትንቢት ይናገራሉ፦
ሱነን አቢ ዳውድ መጽሐፍ 42, ሐዲስ 51
ሠፊናህ እንደተረከው፦ *"የአላህ መልእክተኛም"ﷺ" አሉ፦ "የነብያዊ ኺላፋህነት ሰላሳ ዓመት ነው፤ ከዚያም አላህ መንግሥትን ለሚሻው ይሰጣል፤ ወይም የእርሱን መንግሥት ለሚሻው ያመጣል፤ ሠዒድም ለሠፊናህ እንደተናገረው፦ "የአቡበከር ኸሊፋነት ሁለት ዓመት፣ ዑመር አስር ዓመት፣ ዑስማን አስራ ሁለት ዓመት፣ ዐሊይ እንዲህና እንዲያ(6 ዓመት) አሰላው*። عَنْ سَفِينَةَ، قَالَ قَالَ رَسُولُ اللَّهِ صلى الله عليه وسلم ‏ "‏ خِلاَفَةُ النُّبُوَّةِ ثَلاَثُونَ سَنَةً ثُمَّ يُؤْتِي اللَّهُ الْمُلْكَ - أَوْ مُلْكَهُ - مَنْ يَشَاءُ ‏"‏ ‏.‏ قَالَ سَعِيدٌ قَالَ لِي سَفِينَةُ أَمْسِكْ عَلَيْكَ أَبَا بَكْرٍ سَنَتَيْنِ وَعُمَرَ عَشْرًا وَعُثْمَانَ اثْنَتَىْ عَشْرَةَ وَعَلِيٌّ كَذَا ‏.‏
እንደሚታወቀው የመጨረሻው ዘመን ጥናት"Eschatology" በኢስላም "አል-አኺሩል ዘማን" لَلْآخِر لَلْزَمَان ይባላል፤ የመጨረሻው ዘመን ምልክቶች በሁለት ይከፈላሉ፤ አንዱ ንዑሣን ምልክቶች ሲሆኑ ሁለተኛ ዐበይት ምልክቶች ናቸው፤ የኺላፋህ ሥርዓት ተመልሶ መምጣት ከንዑሳን ምልክቶች አንዱ ሲሆን በነብያችን"ﷺ" ትንቢት ውስጥ እንዲህ ይነበባል፦
ኢማም አሕመድ መጽሐፍ 14, ሐዲስ 163
ሑደይፋህ ኢብኑል-የማን እንደተረከው፦ "የአላህ መልእክተኛ"ﷺ" እንዲህ አሉ፦ *"ነብይነት አላህ እስከፈቀደው ጊዜ ይቆያል፤ ከዚያም በነብይነት ሚንሃጅ ኺላፋህ ይጀመርና አላህ እስከፈቀደው ጊዜ ይቆያል፤ ከዚያም ዘውዳዊ ንግሥና ቦታውን ይይዝና አላህ እስከፈቀደው ጊዜ ይቆያል፤ ከዚያም የወንጀለኛ ንግሥና ይነሳልና አላህ እስከፈቀደው ጊዜ ይቆያል፤ ከዚያም በስተመጨረሻም በነብይነት ሚንሃጅ ኺላፋህ ከእንደገና ይመጣል*። فَقَالَ حُذَيْفَةُ: قَالَ رَسُولُ اللَّهِ - صَلَّى اللَّهُ عَلَيْهِ وَسَلَّمَ -: « تَكُونُ النُّبُوَّةُ فِيكُمْ مَا شَاءَ اللَّهُ أَنْ تَكُونَ ثُمَّ يَرْفَعُهَا إِذَا شَاءَ أَنْ يَرْفَعَهَا، ثُمَّ تَكُونُ خِلَافَةٌ عَلَى مِنْهَاجِ النُّبُوَّةِ فَتَكُونُ مَا شَاءَ اللَّهُ أَنْ تَكُونَ ثُمَّ يَرْفَعُهَا إِذَا شَاءَ اللَّهُ أَنْ يَرْفَعَهَا، ثُمَّ تَكُونُ مُلْكًا عَاضًّا فَيَكُونُ مَا شَاءَ اللَّهُ أَنْ يَكُونَ ثُمَّ يَرْفَعُهَا إِذَا شَاءَ أَنْ يَرْفَعَهَا، ثُمَّ تَكُونُ مُلْكًا جَبْرِيَّةً فَتَكُونُ مَا شَاءَ اللَّهُ أَنْ تَكُونَ ثُمَّ يَرْفَعُهَا إِذَا شَاءَ أَنْ يَرْفَعَهَا، ثُمَّ تَكُونُ خِلَافَةً عَلَى مِنْهَاجِ النُّبُوَّةِ

የነብያችን"ﷺ" ነብይነት ቆይታው እንደ ጎርጎሮሳውን አቆጣጠር ከ 610-632 ድህረ-ልደት ነበር፤ ከዚያም በነብያችን"ﷺ" ፋና አል-ኺላፈቱ አር-ረሺዳህ ከ 632-631 ድህረ-ልደት ነበር፤ ከዚያ የበኑ ኡመያድ ሥርወ-መንግሥት እና የበኑ ዐባሥ ሥርወ-መንግሥት ዘውዳዊ ንግሥና ሆኖ ከ 661-1258 ድህረ-ልደት ነበር፤ ከዚያም ከ 1258 ድህረ-ልደት እስከ ዘመናችን የነገሥታት ጊዜ ውስጥ ነን፤ ከዚያም ኢንሻላህ በነብያችን"ﷺ" ፋና እንደገና የኺላፋህ ሥርዓት ይመለሳል። ኢንሻላህ በክፍል ሦስት ስለ ሥነ-መንግሥት እናጠቃልላለን፤ ይቀጥላል....

ከወንድም ወሒድ ዑመር
https://tttttt.me/Wahidcom

ወሰላሙ አለይኩም
ፓለቲካ

ገቢር ሦስት

በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡

25፥26 *እውነተኛው ንግሥና በዚያ ቀን ለአልራሕማን ብቻ ነው*፡፡ በከሓዲዎችም ላይ አስቸጋሪ ቀን ነው፡፡ الْمُلْكُ يَوْمَئِذٍ الْحَقُّ لِلرَّحْمَـٰنِ ۚ وَكَانَ يَوْمًا عَلَى الْكَافِرِينَ عَسِيرًا

የኢስላም ሊሂቃን የመጨረሻው ዘመን ጥናት ዘርፈ ብዙ እና መጠነ ሰፊ እንደሆነ ያትታሉ፤ ከእነዚህ ጥናት አንዱ ቴኦክራሲ በትክክል የሚያመጣው መሪ ነው፤ ይህ መሪ የተጸውዖ ስሙ ሙሐመድ ሲሆን የአባቱ ስም አብደሏህ ነው፦
ሱነን አቢ ዳውድ መጽሐፍ 38, ሐዲስ 4
ዐብደላህ ኢብኑ መሥዑድ እንደተረከው፦ *"ነብዩም"ﷺ" አሉ፦ "ከቀን በስተቀር ከዱንያህ ምንም ባይቀር(ዛዒዳህ በሐዲሱ እንደተናገረው) አላህ ያንን ቀን እስከ ከእኔ ወይም ከአህለል በይት እስከሚነሳው ሰው ድረስ ያረዝመዋል፤ እርሱም ስሙ የእኔን ስም የአባቱ ስም የአባቴ ስም ይሆናል። ምድር በበደል እንደተሞላች በፍትሕ እና በእኩልነት ያስተዳድራል*። عَنْ عَبْدِ اللَّهِ، عَنِ النَّبِيِّ صلى الله عليه وسلم قَالَ ‏"‏ لَوْ لَمْ يَبْقَ مِنَ الدُّنْيَا إِلاَّ يَوْمٌ ‏"‏ ‏.‏ قَالَ زَائِدَةُ فِي حَدِيثِهِ ‏"‏ لَطَوَّلَ اللَّهُ ذَلِكَ الْيَوْمَ ‏"‏ ‏.‏ ثُمَّ اتَّفَقُوا ‏"‏ حَتَّى يَبْعَثَ فِيهِ رَجُلاً مِنِّي ‏"‏ ‏.‏ أَوْ ‏"‏ مِنْ أَهْلِ بَيْتِي يُوَاطِئُ اسْمُهُ اسْمِي وَاسْمُ أَبِيهِ اسْمَ أَبِي ‏ ‏.‏ زَادَ فِي حَدِيثِ فِطْرٍ

ይህ መሪ የማዕረግ ስሙ ደግሞ አል-መህዲ ይባላል፤ "አል-መህዲ" الْمَهْدِيُّ ማለት "መሪው"The Guided one" ማለት ነው፤ ይህ መህዲ የሚመጣው ከአህለል በይት ነው። "አህለል በይት" أَهْلَ الْبَيْت ማለት "የነብያችን"ﷺ" ቤተሰብ" ማለት ነው፦
ሱነን ኢብኑ ማጃህ  መጽሐፍ 36, ሐዲስ 160
ዐሊይ እንደተረከው፦ የአላህ መልእክተኛ"ﷺ" እንዲህ አሉ፦ *"አል-መህዲ ከአህለል በይት ነው፤ አላህ በአንድ ሌሊት ያስነሳዋል"*። عَنْ عَلِيٍّ، قَالَ قَالَ رَسُولُ اللَّهِ ـ صلى الله عليه وسلم ـ ‏ "‏ الْمَهْدِيُّ مِنَّا أَهْلَ الْبَيْتِ يُصْلِحُهُ اللَّهُ فِي لَيْلَةٍ ‏"‏
ሱነን አቢ ዳውድ መጽሐፍ 38, ሐዲስ 6
ኡሙ ሠለማህ ከአላህ መልእክተኛ"ﷺ" ሰምታ እንደተረከችው፦ እርሳቸው፦ *"አል-መህዲ ከእኔ ቤተሰብ ነው፤ ከፋጢማህ የዘር-ሃረግ ነው" አሉ*። عَنْ أُمِّ سَلَمَةَ، قَالَتْ سَمِعْتُ رَسُولَ اللَّهِ صلى الله عليه وسلم يَقُولُ ‏ الْمَهْدِيُّ مِنْ عِتْرَتِي مِنْ وَلَدِ فَاطِمَةَ ‏

ይህ መህዲ ከፋጢማህ የዘር-ሃረግ የሚመጣ ሲሆን ጭቆና እና አምናገነንነት አስወግዶ ምድርን በእኩልነት እና በፍትሕ ምድርን በመሙላት ለሰባት ዓመት ይገዛል፦
ሱነን አቢ ዳውድ መጽሐፍ 38, ሐዲስ 7
አቢ ሠዒድ አል-ኹድሪይ እንደተረከው፦ *"የአላህ መልእክተኛም"ﷺ" አሉ፦ "አል-መህዲ ከእኔ አብራክ ነው፤ ሰፊ ግንባር የታወቀ አፍንጫ ይኖረዋል፤ ጭቆና እና አምናገነንነት ምድርን እንደተሞላች በእኩልነት እና በፍትሕ ይሞላታል፤ ሰባት ዓመት ይገዛል*። عَنْ أَبِي سَعِيدٍ الْخُدْرِيِّ، قَالَ قَالَ رَسُولُ اللَّهِ صلى الله عليه وسلم ‏ "‏ الْمَهْدِيُّ مِنِّي أَجْلَى الْجَبْهَةِ أَقْنَى الأَنْفِ يَمْلأُ الأَرْضَ قِسْطًا وَعَدْلاً كَمَا مُلِئَتْ جَوْرًا وَظُلْمًا يَمْلِكُ سَبْعَ سِنِينَ ‏"‏
ይህ መሪ የመርየምን ልጅ ዒሣን እንዲያሰግድ ይጋብዘዋል፦
ኢማም ሙስሊም መጽሐፍ 1, ሐዲስ 302
ጃቢ ኢብኑ ዐብደላህ እንደዘገበው፦ "ነብዩ"ﷺ" እንዲህ ሲሉ ሰምቻለው፦ *"ከእኔ ኡማ የሆኑ በእውነት ቢሆን እንጂ አይታገሉም፤ እስከ ትንሳኤ ቀን ድረስ ያሸንፋሉ። ከዚያም ዒሣ የመርየም ልጅ ይወርዳል፤ መሪያቸውም ዒሣን በሶላት እንዲመራ ይጠይቀዋል፤ ዒሣም፦ "አይሆንም! በመካከላችሁ መሪ አለ" ይላል፤ ይህ ከአላህ ለዚህ ኡማህ ክብር ነው*። أَنَّهُ سَمِعَ جَابِرَ بْنَ عَبْدِ اللَّهِ، يَقُولُ سَمِعْتُ النَّبِيَّ صلى الله عليه وسلم يَقُولُ‏ "‏ لاَ تَزَالُ طَائِفَةٌ مِنْ أُمَّتِي يُقَاتِلُونَ عَلَى الْحَقِّ ظَاهِرِينَ إِلَى يَوْمِ الْقِيَامَةِ - قَالَ - فَيَنْزِلُ عِيسَى ابْنُ مَرْيَمَ صلى الله عليه وسلم فَيَقُولُ أَمِيرُهُمْ تَعَالَ صَلِّ لَنَا ‏.‏ فَيَقُولُ لاَ ‏.‏ إِنَّ بَعْضَكُمْ عَلَى بَعْضٍ أُمَرَاءُ ‏.‏ تَكْرِمَةَ اللَّهِ هَذِهِ الأُمَّةَ ‏"‏ ‏

የመርየምን ልጅ ዒሣም ተመልሶ ሲመጣ የሙስሊሙ መሪ ይሆናል፤ መሪ የሚሆነውም በቁርኣን እና በነብያችን"ﷺ" ሱና መመሪያ ነው፦
ኢማም ሙስሊም መጽሐፍ 1, ሐዲስ 300
አቢ ሁረይራ"ረ.ዐ" እንደተረከው፦ *"የአላህ መልእክተኛም"ﷺ" እንዲህ አሉ፦ "በመካከላችሁ የመርየም ልጅ በወረደ ጊዜ እና ሲመራችሁ ምን ታደርጋላችሁ? "*። قَالَ رَسُولُ اللَّهِ صلى الله عليه وسلم ‏ "‏ كَيْفَ أَنْتُمْ إِذَا نَزَلَ ابْنُ مَرْيَمَ فِيكُمْ وَأَمَّكُمْ ‏
ኢማም ሙስሊም መጽሐፍ 1, ሐዲስ 301
አቢ ሁረይራ"ረ.ዐ" እንደተረከው፦ *"የአላህ መልእክተኛም"ﷺ" እንዲህ አሉ፦ "በመካከላችሁ የመርየም ልጅ በወረደ ጊዜ እና ሲመራችሁ ምን ታደርጋላችሁ? ኢብኑ አቢ ዚዕብም አቢ ሁረይራ የዘገበው መሰረት አድርጎ፦ "ሲመራችሁ ምን ታደርጋላችሁ?" ምን ማለት ነው? አለ፤ እኔም ለእኔ አብራራልኝ አልኩኝ፤ እርሱም አለ፦ "በጌታችሁ ተባረከ ወተዓላ መጽሐፍ እና በመልእክተኛው በነብያችሁ"ﷺ" ፈለግ ይመራችኃል" አለ*። أَنَّ رَسُولَ اللَّهِ صلى الله عليه وسلم قَالَ ‏"‏ كَيْفَ أَنْتُمْ إِذَا نَزَلَ فِيكُمُ ابْنُ مَرْيَمَ فَأَمَّكُمْ مِنْكُمْ ‏"‏ ‏.‏ فَقُلْتُ لاِبْنِ أَبِي ذِئْبٍ إِنَّ الأَوْزَاعِيَّ حَدَّثَنَا عَنِ الزُّهْرِيِّ عَنْ نَافِعٍ عَنْ أَبِي هُرَيْرَةَ ‏"‏ وَإِمَامُكُمْ مِنْكُمْ ‏"‏ ‏.‏ قَالَ ابْنُ أَبِي ذِئْبٍ تَدْرِي مَا أَمَّكُمْ مِنْكُمْ قُلْتُ تُخْبِرُنِي ‏.‏ قَالَ فَأَمَّكُمْ بِكِتَابِ رَبِّكُمْ تَبَارَكَ وَتَعَالَى وَسُنَّةِ نَبِيِّكُمْ صلى الله عليه وسلم ‏.‏

ማንኛውም ንጉሥ፣ ኸሊፍህ ወይም አሚር ሟች ነው፤ አላህ ግን በምንነቱ የማይሞት እውነተኛ ንጉሥ ነው፦
20፥114 *እውነተኛው ንጉሥ አላህም ከሓዲዎች ከሚሉት ላቀ*፡፡ ወደ አንተ መወረዱም ከመፈጸሙ በፊት በማንበብ አትቸኩል፡፡ «ጌታዬ ሆይ! ዕውቀትንም ጨምርልኝ» በል፡፡ فَتَعَالَى اللَّهُ الْمَلِكُ الْحَقُّ ۗ وَلَا تَعْجَلْ بِالْقُرْآنِ مِن قَبْلِ أَن يُقْضَىٰ إِلَيْكَ وَحْيُهُ ۖ وَقُل رَّبِّ زِدْنِي عِلْمًا

እውነተኛ መንግሥት የአላህ መንግሥት ነው፤ ማንኛው ምድራዊ ንጉሥ ንግሥናው ጅማሬ አለው እንዲሁ ፍጻሜ አለው፤ ግን አላህ ንግሥናው መነሻ የሌለው ቀዳማይ መዳረሻ የሌለው ደኃራይ ነው። “ሙልክ” مُلْك የሚለው ቃል “መሊክ” مَلِك ማለትም “ንጉሥ” ከሚል የስም መደብ የመጣ ሲሆን “ንግሥና” “መንግሥት” ማለት ነው፤ የእርሱ ንግሥና ደግሞ የእርሱ ባህርይ ነው፤ የሰማያትና የምድር ንግሥና ሁሉ በትንሳኤ ቀን እውነተኛ ንጉሥ ለሆነው ለአላህ ብቻ ይሆናል፦
25፥26 *እውነተኛው ንግሥና በዚያ ቀን ለአልራሕማን ብቻ ነው*፡፡ በከሓዲዎችም ላይ አስቸጋሪ ቀን ነው፡፡ الْمُلْكُ يَوْمَئِذٍ الْحَقُّ لِلرَّحْمَـٰنِ ۚ وَكَانَ يَوْمًا عَلَى الْكَافِرِينَ عَسِيرًا

እንግዲያውስ እውነተኛ ፓለቲካ ቴኦክራሲ ብቻ ነው።

ከወንድም ወሒድ ዑመር
https://tttttt.me/Wahidcom

ወሰላሙ አለይኩም
👉🏼የዳዒ ወሂድ ዑመር ለክርስትና ምላሽ እንዲሁም ተጨማሪ ዳዕዋዎች ከኢስላማዊ እውነታ ( fb.com/islamictrueth ) ስብስብ ዳዕዋዎችንበኦዲዮ መልክ እንዲያደምጡ ጀባ ብለኖታል።

👉🏼 ከርዕሶቹ ስር ያሉትን ሊንኮች በመንካት ያድምጡ👇🏼

ስለ አክፍሮተ ሃይላት ሴራቸውን
በዳዒ ወሂድ ዑመር
http://bit.ly/2k5mVd2

ተውሂድ በዳዒ ወሂድ ዑመር
P1 http://bit.ly/2jJERsy
P2 http://bit.ly/2jilXwY
P3 http://bit.ly/2jE4uh3
P4 http://bit.ly/2kfBYTz
P5 http://bit.ly/2kGE77Q

ጥያቄ ና መልስ በዳዒ ወሂድ ዑመር
http://bit.ly/2jijzWG

ፈጣሪ ማን ነው በዳዒ ወሂድ ዑመር
http://bit.ly/2jru31t

ሙስሊም ሳትሆኑ አትሙቱ በዳዒ ወሂድ ዑመር
http://bit.ly/2kGNgNH

ተውሂድ ወይስ ተስሊስ በዳዒ ወሂድ ዑመር
http://bit.ly/2kfMBWf

ፈጣሪ ስንት ማንነት በዳዒ ወሂድ ዑመር
http://bit.ly/2kAH76d

ኢየሱስ የቱ ጌታ ነው በዳዒ ወሂድ ዑመር
http://bit.ly/2kGvHBd

አላህ 1 ነው በዳዒ ወሂድ ዑመር
http://bit.ly/2jK4XLZ

የባአላትን ቀን ጠብቀን እንኳን አደረሳችሁ ይባላልን? በዳዒ ወሂድ ዑመር
http://bit.ly/2jJOhEF

ወለድ(ሪባ) በዳዒ ወሂድ ዑመር
http://bit.ly/2kfXqbf

እየሱስ አርጓልን? በዳዒ ወሂድ ዑመር
http://bit.ly/2jJSWGr

አንድ አምላክ ወይስ ስላሴ
በዳዒ ወሂድ ዑመር
http://bit.ly/2fLP4Tp

ለተክሉ ተመስገን የተሰጠ መልስ
በዳዒ ወሂድ ዑመር
ክ1 http://bit.ly/2h8XWUt
ክ 2 http://bit.ly/2h8wysq

ሀጀሩል አስወድ the black stone
በዳዒ ወሂድ ዑመር
http://bit.ly/2hAxVxq

Q1 ለአደም ቃል አልተገባለትም
Q2 የአላህ ስም በዳዒ ወሂድ ዑመር
http://bit.ly/2hxGED3

ከልጅ ልጅህ ተወልጀ አድንሃለው እና የአላህ ስም በተመለከተ በዳዒ ወሂድ ዑመር
http://bit.ly/2ih7gGE .

ቁርአንና ባይብል አፃፃፉ
በዳዒ ቀሂድ ዑመር
http://bit.ly/2hQaSOz

ሱረቱ ተህሪምና የጎግል ተርጓሚዎች
http://bit.ly/2iIe03c

ያመነ የተጠመቀ ይድናል?
በዳዒ ወሂድ ዑመር
http://bit.ly/2itAl1e

አይሁድና ክርስቲያኖች ልዩነታቸው ምንድን ነው በዳዒ ወሂድ ዑመር
http://bit.ly/2ib2vAi

ኢየሱስ
በዳዒ ወሂድ ዑመር
http://bit.ly/2iHSPdN

በክርስቶስ እየሱስ ተፈጠርን ኤፌሶን_2_10
በዳዒ ወሂድ ዑመር
http://bit.ly/2ikCj6Q
.
የኢሳ ስቅለት መመሳሰል በወንድም
በዳዒ ዋሂድ ዑመር
http://bit.ly/2j7hSqz

ከ1 በላይ ማግባት በኢስላም? ና ከሞት ቡሀላ ሂወት አለ?
በዳዒ ወሂድ ዑመር
http://bit.ly/2ieaF84

ቢድዓ ምንድን ነው
በዳዒ ወሂድ ዑመር
http://bit.ly/2iHcs6H

እየሱስ ጌታ ነው ሲባል ምን ማለት ነው?
በዳዒ ወሂድ ዑመር
http://bit.ly/2j85M5e

እየሱስ የአላህ ባሪያ ነው
በዳዒ ወሂድ ዑመር
http://bit.ly/2jiR5Y0

እየሱስ የአላህ ባሪያ ነው
በዳዒ ወሂድ ዑመር
http://bit.ly/2gFC9rb

ኢትዩጵያ በመፅሀፍ ቅዱስ
በዳዒ ወሂድ ዑመር
http://bit.ly/2jdoA2A

ምንኩስና ቢድዓ (ጭማሪ) ነው
በዳዒ ወሂድ ዑመር
http://bit.ly/2hUcExk

ወደፊት የሚለቀቁ የዳዒ ወሂድ ዑመርን ዳዕዋዎች በተከታዩ ሊንክ ያገኙታል

https://goo.gl/LA9Z8v

⇄⇄⇄⇄⇄⇄⇄⇄⇄⇄⇄⇄
For more daawa
on facebook
fb.com/islamictrueth

On wordpress
amharicmp3daawa.wordpress.com

On telegram
https://telegram.me/islamictrueth
በወንድም ወሒድ ዑመር የተዘጋጁ በተለያዩ ጊዜያት ሙስልም ባልሆኑ ወገኖች የተጠየቁ ጥያቄዎች መልሶቻቸው እና ኢስላማዊ አስተምህሮዎችን የሚያገኙበት የዩቱብ ሊንክ

አላህ እና እግዚአብሔር ወሒድ ዑመር https://youtu.be/74sPvupjrqc

ቁርአን የማን ንግግር ነው? ወሒድ ዑመር
https://youtu.be/CLN6JNAHlLY

እውን ዘፍጥረት 18 ስላሴን ያሳያል https://youtu.be/Uc-wHo6KeD0

ስላሴ ምንድን ነው? ወሒድ ዑመር https://youtu.be/F2UstBt5_SA

እየሱስ አብም እግዚአብሔርም አይደለም ወሒድ ዑመር https://youtu.be/lgNY2wY05Vk

የማቴዎስ ወንጌል 28 19:20 ስላሴን ያሳያል ወሒድ ዑመር https://youtu.be/bgtzsNKX_Qg

መስጁዶች ላይ ኮከብና ጨረቃ ለምን ይቀመጣል መች ተጀመረ ወሒድ ዑመር
https://youtu.be/1PKfWCHo_PA

ኦርቶዶክሶች ስለማርያም ያላቸው የተሳሳተ ግንዛቤ ወሒድ ዑመር https://youtu.be/Nl6yaSCbRMY

ተዋህዶ ምንታዌ ወይስ ውላጤ ወሒድ ዑመር https://youtu.be/UgiY8Q7s08A

ሁለተኛው አፅናኝ ወሒድ ዑመር https://youtu.be/RkpWQhHqoVU

ወንጌል ክፍል 1 ወሒድ ዑመር https://youtu.be/Ev5aa0lNFr4

ወንጌል ክፍል 2 ወሒድ ዑመር https://youtu.be/ydT59S4fomw

የአምላክ ስም ማን ነው ወይይት ወሒድ ዑመር
https://youtu.be/NJkzRRwlqcU

በእየሱስ ማንነት ዙሪያ ከክርስቲያ ወገናችን ጋር የተደረገ ውይይት ወሒድ ዑመር
https://youtu.be/YqzvsVjZxbc

አምላክ አንድ እንጅ ሶስት አይደለም ባይብል ምን ይላል? ወሒድ ኡመር: http://youtu.be/rpgTTY8KPZs

እየሱስ አርጓል! ወሒድ ኡመር: http://youtu.be/hXufXprUTJk

እየሱስ ጌታ ነው ሲባል ምን ማለት ነው? ወሒድ ኡመር: http://youtu.be/kLW-bqYM2-s

ዳኢ ኡስታዝ ወሒድ በአክፍሮት ሀይላት ላይ የሰጠው አስ…: http://youtu.be/DneCHrU-9-s

የመስቀል ደመራ እና ማተብ መችና እንዴት ተጀመረ? ወሒድ ኡመር: http://youtu.be/l9G0WvIrjdc

አንዱ አምላክ ማን ነው ወሒድ ኡመር: http://youtu.be/5WTkP6MYMAk

አልፍና ኦሜጋ ወሒድ ኡመር: http://youtu.be/1ztM22Rpu9A

ኢትዮጵያ በመፅሐፍ ቅዱስ ወሒድ ኡመር: http://youtu.be/yvhjbIGSFrU

ምንኩስና ቢድአ ( ጭማሪ) ነው ወሒድ ኡመር: http://youtu.be/2SbBsND0LmY

ከአንድ በላይ ማግባት በኢስላምና ከሞት በኃላ ሕይወት ወሒድ ኡመር: http://youtu.be/58iZOiwncEI

ኢየሱስ? ወሒድ ኡመር: http://youtu.be/TW6cHzniDtw

አይሁድና ክርስቲያኖች ልዩነታቸው ምንድን ነው ወሒድ ኡመር: http://youtu.be/YwVrCAKgi7I

ያመነ የተጠመቀ ይድናል ዋሂድ ኡመር: http://youtu.be/75oAUYIt7VA

የተገደሉት የአላህ ነብያት እነማን ናቸው? ዋሂድ ኡመር: http://youtu.be/KP_KxTZnci8

ቁርአንና ባይብል አፃፃፉ ዋሂድ ኡመር: http://youtu.be/2jAytbGLKME

ሐጀሩል አስወድ the black stone ወሂድ ኡመር: http://youtu.be/cOxdifxY4ik

ከልጅ ልጅህ ተወልጀ አድንሃለው እና የአላህ ስም በተመለከተ በ ዋሂድ ኡመር: http://youtu.be/iBeDaT1MBfQ

በኢየሱስ ና በአንዱ አምላክ መካከል ያለው የኑባሬ ልዩነት በ ወንድም ወሂድ …: http://youtu.be/qX6mB7HYick

አንድ አምላክ ወይስ ስላሴ? ዋሂድ ኡመር: http://youtu.be/9rv0fNGOfCY

ለተጨማሪ ትምህርቶች

የፌስቡክ አድራሻችን፦ https://www.facebook.com/Hidayatube/

በቴሌግራም ሒዳያ https://telegram.me/hidayaislam

በቴሌግራም ወሒድ የሃይማኖት ንፅፅር መድረክ https://tttttt.me/yahtam
ቀኖና

ገቢር አንድ

በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኛ በሆነው፡፡

3፥71 *የመጽሐፉ ሰዎች ሆይ! እውነቱን በውሸት ለምን ትቀላቅላላችሁ እውነቱንም እናንተ የምታውቁ ስትኾኑ ለምን ትደብቃላችሁ?* يَا أَهْلَ الْكِتَابِ لِمَ تَلْبِسُونَ الْحَقَّ بِالْبَاطِلِ وَتَكْتُمُونَ الْحَقَّ وَأَنتُمْ تَعْلَمُونَ

“አህለል ኪታብ” أَهْلَ الْكِتَاب ማለት “የመጽሐፉ ሰዎች” “የመጽሐፉ ሕዝብ” “የመጸሐፉ ባለቤት”The People of the Book” ማለት ሲሆን እነዚህም ሕዝቦች አይሁዳውያን እና ክርስቲያኖች ናቸው፤ "ኪታብ" كِتَاب የተባለው ከአላህ የወረደው ወሕይ እና በእጆቻቸው ጽፈው ከአላህ ሳይሆን ከአላህ ነው ብለው ከአላህ ንግግር ጋር የቀላቀሉት የሰው ንግግር ነው፦
2፥79 *ለእነዚያም መጽሐፉን በእጆቻቸው ለሚጽፉና ከዚያም በእርሱ ጥቂትን ዋጋ ሊገዙበት «ይህ ከአላህ ዘንድ ነው» ለሚሉ ወዮላቸው፡፡ ለእነርሱም ከዚያ እጆቻቸው ከጻፉት ወዮላቸው፡፡ ለእነሱም ከዚያ ከሚያፈሩት ኃጢኣት ወዮላቸው*፡፡ فَوَيْلٌۭ لِّلَّذِينَ يَكْتُبُونَ ٱلْكِتَٰبَ بِأَيْدِيهِمْ ثُمَّ يَقُولُونَ هَٰذَا مِنْ عِندِ ٱللَّهِ لِيَشْتَرُوا۟ بِهِۦ ثَمَنًۭا قَلِيلًۭا ۖ فَوَيْلٌۭ لَّهُم مِّمَّا كَتَبَتْ أَيْدِيهِمْ وَوَيْلٌۭ لَّهُم مِّمَّا يَكْسِبُونَ

የመጽሐፉ ባለቤቶች ከአላህ የወረደውን ንግግር ከሰው ንግግር ቃል ቀላቅለውታል፤ ከዚያም ባሻገር ከአላህ የወረደውንን ንግግር ደብቀውታል፦
3፥71 *የመጽሐፉ ሰዎች ሆይ! እውነቱን በውሸት ለምን ትቀላቅላላችሁ እውነቱንም እናንተ የምታውቁ ስትኾኑ ለምን ትደብቃላችሁ?* يَا أَهْلَ الْكِتَابِ لِمَ تَلْبِسُونَ الْحَقَّ بِالْبَاطِلِ وَتَكْتُمُونَ الْحَقَّ وَأَنتُمْ تَعْلَمُونَ

እስቲ ይህንን ነጥብ በታሪካዊ ዳራ እንቃኝ፤ በዚህ ምህዋር እና ዐውድ ላይ "ቀኖና" ስንል የዶግማ ተቃራኒ የሆነውን የሚለወጠው ሕግ ወይም ሥርዓት ሳይሆን የቅዱሳን መጽሐፍትን "መለኪያ" ታሳቢና ዋቢ ያደረገ ነው። "ቀኖና" የሚለው ቃል የአማርኛችን ቃል "ካኑን" κανών ከሚል ግሪክ ቃል የተገኘ ነው፤ ይህም ቃል "ካና" κάννα ማለት "አሰመረ" "ለካ" ከሚል የኮይኔ ግሪክ ሥርወ-ቃል የተገኘ ሲሆን "ልኬት" ማለት ነው። አይሁዳውን በ 90 ድህረ-ልደት"AD" በጀሚኒያ ጉባኤ እንዲሁ ክርስቲያኖች በ 387 ድህረ-ልደት"AD" በካርቴጅ ጉባኤ በመጨመርና በመቀነስ ቀኖና እያሉ ሲያስወጡና ሲያስገቡ ነበር፤ በተለይ የካርቴጅ ጉባኤ መጽሐፍቶችን በሁለት ከፍለው ብሉይ እና አዲስ ብለው አስቀምጠውታል፤ እስቲ ይህንን ነጥብ በነጥብ እንመልከት፦
ነጥብ አንድ
"ብሉይ ኪዳን"
ብሉይ ኪዳን ላይ ስላሉት መጽሐፍት የተለያዩ አንጃዎች አንድ አቋም የላቸውም፤ እነርሱን በተናጥን እስቲ እንይ፦

A. "የፕሮቴስታንት ቀኖና"
ፕሮቴስታንት የሚቀበለው ሁሉም ጋር ተቀባይነት ያለው አቆጣጠር
የብሉይ ኪዳን መጻሕፍት 39 ናቸው፤ እነርሱም፦
1. ኦሪት ዘፍጥረት
2. ኦሪት ዘጸአት
3 ኦሪት ዘኁልቁ
4. ኦሪት ዘሌዋውያን
5. ኦሪት ዘዳግም
6. መጽሐፈ ኢያሱ
7. መጽሐፈ መሳፍንት
8. መጽሐፈ ሩት
9. መጽሐፈ ሳሙኤል ቀዳማዊ
10. መጽሐፈ ሳሙኤል ካልዕ
11. መጽሐፈ ነገሥት ቀዳማዊ
12. መጽሐፈ ነገሥት ካልዕ
13. ዜና መዋዕል ቀዳማዊ
14. ዜና መዋዕል ካልዕ
15. መጽሐፈ ዕዝራ
16. መጽሐፈ ነህምያ
17. መጽሐፈ አስቴር
18. መጽሐፈ ኢዮብ
19. መዝሙረ ዳዊት
20. መጽሐፈ ምሳሌ
21. መጽሐፈ መክብብ
22. መኃልየ መኃልይ ዘሰሎሞን
23. ትንቢተ ኢሳይያስ
24. ትንቢተ ኤርምያስ
25. ሰቆቃው ኤርምያስ
26. ትንቢተ ሕዝቅኤል
27. ትንቢተ ዳንኤል
28. ትንቢተ ሆሴዕ
29. ትንቢተ አሞጽ
30. ትንቢተ ሚክያስ
31. ትንቢተ ኢዮኤል
32. ትንቢተ አብድዩ
33. ትንቢተ ዮናስ
34. ትንቢተ ናሆም
35. ትንቢተ ዕንባቆም
36. ትንቢተ ሶፎንያስ
37. ትንቢተ ሐጌ
38. ትንቢተ ዘካርያስ
39. ትንቢተ ሚልክያስ ናቸው።

B. "የአይሁዳውያን ቀኖና"
39 መጽሐፍት አይሁዳውያን እንደጎሮሳውያን አቆጣጠር በ 90 ድህረ-ልደት"AD" በጀሚኒያ 24 የቀኖና መጽሐፍት አርገዋቸዋል፤ አቆጣጠራቸው ግን ይለያል፦
1. መጽሐፈ ሳሙኤል ቀዳማዊ እና መጽሐፈ ሳሙኤል ካልዕ አንድ መጽሐፍ ሻሙኤል ብለው፣
2. መጽሐፈ ነገሥት ቀዳማዊ እና መጽሐፈ ነገሥት ካልዕ አንድ መጽሐፍ መላክሂም ብለው፣
3. ዜና መዋዕል ቀዳማዊ እና ዜና መዋዕል ካልዕ አንድ መጽሐፍ ሃያሚን ብለው፣
4. መጽሐፈ ዕዝራ እና መጽሐፈ ነህምያ አንድ መጽሐፍ አዝራ ብለው፣
5. ከሆሴዕ እስከ ሚልኪያስ ያሉት 12 መጽሐፍት አንድ መጽሐፍ ትሬአሳር ብለው ይቆጥሩታል።

ከሆሴዕ እስከ ሚልኪያስ ያሉት በአንድ የተጣፉትን 11 መጽሐፍት እና የተጣፉትን 4 መጽሐፍት ስንደምር 15 ይሆናል፤ 15+24= 39 መጽሐፍት ይሆናሉ። አይሁዳውያን መጽሐፍቶቻቸውን "ታንካህ" תַּנַ”ךְ, ሲሉት የሶስቱ መጽሐፍት መነሻ ላይ ያሉት ቃላት መሰረት አርገው ነው፤ እነዚህም "ታ" תַּ ቶራህ፣ "ና" נַ ነቢኢም፣ "ካ" ךְ ኬቱዊም ናቸው። "ቶራህ" תּוֹרָה ማለት "ኦሪት" "ሕግ" "መርሕ" ማለት ነው፣ ከዘፍጥረት እስከ ዘዳግም ያሉትን ለማመልከት ይጠቀሙብታል።
"ነቢኢም" נְבִיאִים ማለት "ነቢያት" ማለት ሲሆን የኢሳያስ ትንቢት፣ የኤርሚያስ ትንቢት፣ የህዝቅኤል ትንቢት ወዘተ ለማመልከት ይጠቀሙብታል።
"ኬቱዊም" כְּתוּבִים ማለት "መጻሕፍት" ማለት ሲሆን የኢዮብ መጽሐፍ፣ የመዝሙር መጽሐፍ፣ የምሳሌ መጽሐፍ፣ የመክብብ መጽሐፍ፣ የመኃልየ መኃልይ መጽሐፍ ወዘተ ለማመልከት ይጠቀሙብታል።

C. "የካቶሊክ ቀኖና"
የሮማ ካቶሊክ የብሉይ ኪዳን መጽሐፍት ቀኖና 46 ናቸው፤ ካቶሊክ በ 39 ላይ እራሳቸውን የቻሉ 7 ጭማሬ መጽሐፍት ሲኖራቸው እነዚህ ጭማሬ፦
1. መጽሐፈ ጦቢት፣
2. መጽሐፈ ዮዲት፣
3. መጽሐፈ ጥበብ፣
4. መጽሐፈ ሲራክ፣
5. መጽሐፈ ባሮክ፣
6. መጽሐፈ መቃብያን ቀዳማዊ
7. መጽሐፈ መቃብያን ካልዕ ናቸው።

D. "የኦርቶዶክስ ቀኖና"
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ የብሉይ ኪዳን መጽሐፍት ቀኖና 46 ናቸው፤ የብሉይ ኪዳን መደበኛ የቀኖና መጽሐፍት 39 ሲሆኑ ተጨማሪ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ የብሉይ ኪዳን መጽሐፍት ቀኖና 18 ናቸው፤ ነገር ግን አቆጣረራቸው ልክ እንደ አይሁድ ይለያል። እራሳቸውን የቻሉ 10 ጭማሬ መጽሐፍት ሲኖራቸው እነዚህ ጭማሬ አቆጣጠራቸው፦
1. መጽሐፈ ሄኖክ፣
2. መጽሐፈ ኩፋሌ(ጁብሊይ)፣
3. መጽሐፈ ጦቢት፣
4. መጽሐፈ ዮዲት፣
5. መጽሐፈ ተግሣጽ፣
6. መጽሐፈ ጥበብ፣
7. መጽሐፈ ሲራክ
8. መጽሐፈ ዕዝራ ሱቱኤል ቀዳማይ እና መጽሐፈ ዕዝራ ሱቱኤል ካልዕ፣
9. መጽሐፈ መቃብያን ቀዳማይ እና መጽሐፈ መቃብያን ካልዕ፣
10. መጽሐፈ መቃብያን ሣልስ ናቸው።

ነባር መጽሐፍት ላይ በመቀነስ ተጨፍልቀው የሚቆጠሩ 2 መጽሐፍት ናቸው፤ እነርሱም፦
11. መጽሐፈ ሳሙኤል ቀዳማይ እና መጽሐፈ ሳሙኤል ካልዕ ናቸው፣
12. መጽሐፈ ዕዝራ ቀዳማይ እና መጽሐፈ ዕዝራ ካልዕ(ነህምያ) ናቸው።

ከነባር መጽሐፍት ጋር ተደምረው የሚቆጠሩ ደግሞ 8 መጽሐፍት ናቸው፤ እነርሱም፦
13. ከትንቢተ ኢሳይያስ ጋር የሚቆጠረው ጸሎተ ምናሴ ነው።
14. ከትንቢተ ኤርምያስ ጋር የሚቆጠሩ፦ ሰቆቃወ ኤርምያስ፣ ተረፈ ኤርምያስ፣ መጽሐፈ ባሮክ፣ ተረፈ ባሮክ ናቸው።
15. ከትንቢተ ዳንኤል ጋር የሚቆጠሩ መጽሐፈ ሶስና፣ ጸሎተ ሠለስቱ ደቂቅ እና ተረፈ ዳንኤል ናቸው።

ከ 39 ላይ 8 መጽሐፍት፦ ሳሙኤል ቀዳማይ፣ ሳሙኤል ካልዕ፣ መጽሐፈ ዕዝራ፣ መጽሐፈ ነህምያ፣ ትንቢተ ኢሳይያስ፣ ትንቢተ ኤርሚያ፣ ሰቆቃው ኤርሚያስ እና ትንቢተ ዳንኤል ሲቀነሱ 31 መጽሐፍት ይሆናሉ። 31+15= 46 ይሆናል።

F. "የሰፕቱአጀንት ቀኖና"
የሰፕቱአጀንት ቀኖና የብሉይ ኪዳን መጽሐፍት ቀኖና 56 ናቸው፤ የሰፕቱአጀንት"LXX" በ 39 ላይ እራሳቸውን የቻሉ 17 ጭማሬ መጽሐፍት ሲኖራቸው እነዚህ ጭማሬ፦
1. መጽሐፈ ጦቢት፣
2. መጽሐፈ ዮዲት፣
3. መጽሐፈ ጥበብ፣
4. መጽሐፈ ሲራክ፣
5. መጽሐፈ ባሮክ፣
6. ተረፈ ኤርምያስ፣
7. ጸሎተ ሠለስቱ ደቂቅ፣
8. መጽሐፈ ሶስና፣
9. ቤልና ድራጎን፣
10. ጸሎተ ምናሴ፣
11.1ኛ መቃብያን፣
12. 2ኛ መቃብያን፣
13. 3ኛ መቃብያን፣
14. 4ኛ. መቃብያን፣
15. ዕዝራ ሱቱኤል፣
16. የአዛርያ ጸሎት፣
17. መዝሙር 151 ናቸው።

G. "የቩልጌት ቀኖና"
ጄሮም በ 382 ድህረ-ልደት በላቲን ቩልጌት ባዘጋጀው ደግሞ የመጽሐፍት ቀኖና 45 ናቸው፤ የቩልጌት በ 39 ላይ እራሳቸውን የቻሉ 6 ጭማሬ መጽሐፍት ሲኖራቸው እነዚህ ጭማሬ፦
1. መጽሐፈ ጦቢት፣
2. መጽሐፈ ዮዲት፣
3.1ኛ መቃብያን፣
4. 2ኛ መቃብያን፣
5. መጽሐፈ ዕዝራ ሱቱኤል ቀዳማይ፣
6. መጽሐፈ ዕዝራ ሱቱኤል ካልዕ

ኢንሻላህ ስለ አዲስ ኪዳን በክፍል ሁለት ይቀጥላል...

ከወንድም ወሒድ ዑመር
https://tttttt.me/Wahidcom

ወሰላሙ አለይኩም
ቀኖና

ገቢር ሁለት

በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኛ በሆነው፡፡

5፥15 *የመጽሐፉ ባለቤቶች ሆይ! ከመጽሐፉ ትሸሽጉት ከነበራችሁት ነገር ብዙውን ለእናንተ የሚገልጽ ከብዙውም የሚተው ሲኾን መልክተኛችን በእርግጥ መጣላችሁ*፡፡ يَا أَهْلَ الْكِتَابِ قَدْ جَاءَكُمْ رَسُولُنَا يُبَيِّنُ لَكُمْ كَثِيرًا مِّمَّا كُنتُمْ تُخْفُونَ مِنَ الْكِتَابِ وَيَعْفُو عَن كَثِيرٍ

ነጥብ ሁለት
"አዲስ ኪዳን"
የአዲስ ኪዳን መደበኛ መጻሕፍት 27 ናቸው፤ እነርሱም እንደሚከተለው ነው፦
1. የማቴዎስ ወንጌል
2. የማርቆስ ወንጌል
3. የሉቃስ ወንጌል
4. የዮሐንስ ወንጌል
5. የሐዋርያት ሥራ
6. የሮሜ ሰዎች
7. 1ኛ. የቆሮንቶስ ሰዎች
8. 2ኛ. የቆሮንቶስ ሰዎች
9. የገላትያ ሰዎች
10. የኤፌሶን ሰዎች
11. ያፊልጵስዩስ ሰዎች
12. የቆላስይስ ሰዎች
13. 1ኛ. የተሰሎንቄ ሰዎች
14. 2ኛ. የተሰሎንቄ ሰዎች
15. 1ኛ. ጢሞቴዎስ
16. 2ኛ. ጢሞቴዎስ
17. ቲቶ
18. ፊልሞና
19. የዕብራዊያን ሰዎች
20. 1ኛ. ጴጥሮስ መልእክት
21. 2ኛ. ጴጥሮስ መልእክት
22. 1ኛ. ዮሐንስ መልእክት
23. 2ኛ. ዮሐንስ መልእክት
24 3ኛ. ዮሐንስ መልእክት
25. የያዕቆብ መልእክት
26. የይሁዳ መልእክት
27. የዮሐንስ ራዕይ

በእነዚህ መጽሐፍት ላይ ሁሉም የጋራ አቆጣጠር ቢኖራቸውም ነገር ግን የጭማሬ እና የቅነሳ ነገር ይታይበታል። ይህንንም በግርድፉ እንይ፦
A. "የኦርቶዶክስ ቀኖና"
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ የአዲስ ኪዳን መጽሐፍት ቀኖና 35 ናቸው፤ የአዲስ ኪዳን መደበኛ የቀኖና መጽሐፍት 27 ሲሆኑ ተጨማሪ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ መጽሐፍት ቀኖና 8 ናቸው፤ እነዚህም፦
1. መጽሐፈ ኪዳን ቀዳማይ፣
2. መጽሐፈ ኪዳን ካልዕ
3. መጽሐፈ ሥርዓተ ጽዮን
4. መጽሐፈ አብጥሊስ
5. መጽሐፈ ግጽው፣
6.መጽሐፈ ትእዛዝ፣
7. መጽሐፈ ዲድስቅልያ እና
8. መጽሐፈ ቀሌምንጦስ ናቸው።

B. "የአርመንያ ቀኖና"
የአርመንያ ቤተክርስቲያን በ 27 ቀኖና ላይ 5 መጽሐፍትን ትጨምራለች፤ እነርሱም፦
1. 3ኛ የቆሮንቶስ ሰዎች መልእክት
2. የሎዶቅያ ሰዎች መልእክት
3. የበርናባስ መልእክት
4. 1ኛ የክሌመንት መልእክት
5. 2ኛ የክሌመንት መልእክት

C. "የሉተር ቀኖና"
የፕሮቴስታንት ተሃድሶ ንቅናቄ መሪ ማርቲን ሉተር ከ 27 ላይ 4 መጽሐፍትን ቀንሶ 23 ብቻ ነው የተቀበለው፤ እነርሱም፦
1. የዕብራዊያን ሰዎች
2. የያዕቆብ መልእክት
3. የይሁዳ መልእክት
4. የዮሐንስ ራዕይ
ማጠቃለያ
አይሁዳውያን ለሙሳ የተሰጠውን መጽሐፍ በመከፋፈል ኦሪት ዘፍጥረት፣ ኦሪት ዘጸአት፣ ኦሪት ዘኁልቁ፣ ኦሪት ዘሌዋውያን፣ ኦሪት ዘዳግም በማለት ከፋፍለውታል፤ እነርሱም የማይመቻቸውን አፓክራፋ ማለት ድብቅ በማለት በመቀነስ ደብቀውታል፤ ከዚያም ባሻገር አባቶቻቸውም የማያውቁት ንግግር በአምላክ ንግግር ላይ ጨምረዋል፦
6፥61 እንዲህ በላቸው፡- «ያንን ብርሃን እና ለሰዎች መሪ ኾኖ *ሙሳ ያመጣውን መጽሐፍ ክፍልፍሎች የምታደርጉት ስትኾኑ ማን አወረደው? የወደዳችኋትን ትገልጿታላችሁ ብዙውንም ትደብቃላችሁ፤ እናንተም አባቶቻችሁም ያላወቃችሁትን ተስተማራችሁ*። قُلْ مَنْ أَنزَلَ الْكِتَابَ الَّذِي جَاءَ بِهِ مُوسَىٰ نُورًا وَهُدًى لِّلنَّاسِ ۖ تَجْعَلُونَهُ قَرَاطِيسَ تُبْدُونَهَا وَتُخْفُونَ كَثِيرًا ۖ وَعُلِّمْتُم مَّا لَمْ تَعْلَمُوا أَنتُمْ وَلَا آبَاؤُكُمْ ۖ قُلِ اللَّهُ ۖ ثُمَّ ذَرْهُمْ فِي خَوْضِهِمْ يَلْعَبُونَ

አይሁዳውን በ 90 ድህረ-ልደት”AD” በጀሚኒያ ጉባኤ የአርመንያ ቀኖና ውስጥ የሚገኘውን የአስራ ሁለቱ ነገዶችን መጽሐፍ፣ የአብርሃምን የቃል ኪዳን መጽሐፍ፣ የነቢዩ ሸማያ፣ የነቢዩ አዶ፣ የነቢዩ ናታን፣ የነቢዩ ኦሒያ፣ የነቢዩ ዖዴድ የትንቢት መጽሐፍት፣ መጽሐፈ ሄኖክ፣ መጽሐፈ ኩፋሌ፣ መጽሐፈ ጦቢት፣ መጽሐፈ ዮዲት፣ መጽሐፈ ጥበብ፣ መጽሐፈ ሲራክ፣ መጽሐፈ ባሮክ፣ የመሳሰሉትን "አፓክራፋ" ማለትም "ድብቅ" ብለው ሲቀንሱ በተቃራኒው የሰው ንግግር የሆኑትን መጽሐፈ ኢያሱ፣ መጽሐፈ መሳፍንት፣ መጽሐፈ ሩት፣ መጽሐፈ ሳሙኤል ቀዳማዊ፣ መጽሐፈ ሳሙኤል ካልዕ ወዘተ በአምላክ ንግግር ላይ ጨምረዋል። ዋቢ መጽሐፍት ይመልከቱ፦
1. Bruce, Frederick (1988). The Canon of Scripture. Downers Grove, Illinois, U.S.: IVP Academic.
2. The Writings: The Third Division of the Old Testament Canon. George Allen & Unwin Ltd., 1963,
3. Michael Coogan. A Brief Introduction to the Old Testament: The Hebrew Bible in Its Context. Oxford University Press, 2009,

ክርስቲያኖች በ 387 ድህረ-ልደት”AD” በካርቴጅ ጉባኤ ከወንጌላት የቶማስ፣ የይሁዳ፣ የጴጥሮስ፣ የያዕቆብ፣ የበርናባስ፣ የፊሊጶስ፣ የበርተሎሞዎስ፣ የመቅደላዊት ማርያም የተባሉትን ወንጌላትን ቀንሰዋል።
ከሥራም ዘገባ የጴጥሮስ ስራ፣ የእንድሪያስ ስራ፣ የፊሊጶስ ስራ፣ የበርናባስ ስራ፣ የጳውሎስ ስራ፣ የዮሐንስ ስራ፣ የቶማስ ስራ ቀንሰዋል።
ከመልእክታትም 3ኛ የቆሮንቶስ ሰዎች መልእክት፣ የሎዶቅያ ሰዎች መልእክት፣ የበርናባስ መልእክት፣ 1ኛ የክሌመንት መልእክት፣ 2ኛ የክሌመንት መልእክት፣ የሄርሜኑ እረኛ መልእክት ወዘተ ቀንሰዋል።
ከአፓልካሊፕስም(ራዕይ) የጴጥሮስ አፖልካሊፕስ፣ የጳውሎስ አፖልካሊፕስ፣ የቶማስ አፖልካሊፕስ፣ የያዕቆብ አፖልካሊፕስ ቀንሰዋል።
ልብ አድርግ እነዚህ አፓክራፋ በጥንታዊያን እደ-ክታባት ለምሳሌ በክላሮሞንታነስ እደ-ክታብ"Codex Claromontanus" ውስጥ የጳውሎስ ስራ፣ የጴጥሮስ ራዕይ፣ የሄርሜኑ እረኛ መልእክት፣ የበርናባስ መልእክት ይገኛሉ፤ በአሌክሳንድሪየስ እደ-ክታብ"Codex Alexandrinus" ውስጥ 2ኛ የክሌመንት መልእክት ይገኛሉ፤ በሳይናቲከስ እደ-ክታብ"Codex Sinaiticus" ውስጥ የሄርሜኑ እረኛ መልእክት እና የበርናባስ መልእክት ይገኛሉ።
ከዚያም ባሻገር የሰው ንግግር የሆኑትን ታሪክና መልእክት በወንጌል ላይ ቀላቅለዋል። ዋቢ መጽሐፍት ይመልከቱ፦
1. Lost Scriptures: Books that Did Not Make It into the New Testament. Oxford University Press, USA. 2003
2. The New Testament and Other Early Christian Writings: A Reader. Oxford University Press, USA. 2003
3. The Other Gospels: Accounts of Jesus from Outside the New Testament. Oxford University Press, USA. 2013 by Bart D. Ehrman.
ይህ በእንዲህ እንዳለ አምላካችን አላህ የመጽሐፉ ባለቤቶች ከመጽሐፉ ይሸሽጉት ከነበሩት ብዙውን የሚገልጽ ከብዙውም የሚተው ሲኾን መልክተኛውን በእርግጥ ልኳል፦
5፥15 *የመጽሐፉ ባለቤቶች ሆይ! ከመጽሐፉ ትሸሽጉት ከነበራችሁት ነገር ብዙውን ለእናንተ የሚገልጽ ከብዙውም የሚተው ሲኾን መልክተኛችን በእርግጥ መጣላችሁ*፡፡ يَا أَهْلَ الْكِتَابِ قَدْ جَاءَكُمْ رَسُولُنَا يُبَيِّنُ لَكُمْ كَثِيرًا مِّمَّا كُنتُمْ تُخْفُونَ مِنَ الْكِتَابِ وَيَعْفُو عَن كَثِيرٍ

“አፓክራፋ” የሚለው ቃል “አፓክራፈስ” ἀπόκρυφος ከሚለው ግሪክ ቃል የመጣ ሲሆን “ድብቅ” ማለት ነው፤ ከደበቁት መጽሐፍት ውስጥ ካሉት መለኮታዊ ቅሪት አስፈላጊውን አላህ የገለጸ ሲሆን ከደበቁት መጽሐፍት ውስጥ ካሉት መለኮታዊ ቅሪት ብዙውን ትቶታል፤ ወደ ነብያት ምን ተወርዶ እንደነበረ መልእክተኛው እንዲገልጹ ቁርኣንን አውርዷል፦
16፥44 በግልጽ ማስረጃዎችና በመጻሕፍት ላክናቸው፡፡ *ወደ አንተም ለሰዎች ወደ እነርሱ የተወረደውን ልትገልጽላቸው እና ያስተነትኑም ዘንድ ቁርኣንን አወረድን*፡፡ بِالْبَيِّنَاتِ وَالزُّبُرِ ۗ وَأَنزَلْنَا إِلَيْكَ الذِّكْرَ لِتُبَيِّنَ لِلنَّاسِ مَا نُزِّلَ إِلَيْهِمْ وَلَعَلَّهُمْ يَتَفَكَّرُونَ

ይህ ቁርኣን ከበፊቱ ከአላህ የተወረዱትን የአላህ ንግግሮች የሚያረጋግጥ እና በእነዚያ ንግግሮች ውስጥ ያለውን ጭብጥ የሚዘረዝር ነው፦
10፥37 ይህም ቁርኣን ከአላህ ሌላ ከሆነ ፍጡር የተቀጠፈ ሊሆን አይገባውም፤ *ግን ያንን ከእርሱ በፊት ያለውን የሚያረጋግጥ እና በመጽሐፉ ውስጥ ያለውን የሚዘረዝር በእርሱ ጥርጣሬ የሌለበት ሲሆን ከዓለማት ጌታ የተወረደ ነው*፡፡ وَمَا كَانَ هَـٰذَا الْقُرْآنُ أَن يُفْتَرَىٰ مِن دُونِ اللَّهِ وَلَـٰكِن تَصْدِيقَ الَّذِي بَيْنَ يَدَيْهِ وَتَفْصِيلَ الْكِتَابِ لَا رَيْبَ فِيهِ مِن رَّبِّ الْعَالَمِينَ

የአዲስ ኪዳን እና የብሉይ ኪዳን ጽንፈኛ ሆነ ለዘብተኛ ምሁራን የባይብል ሥረ-መሰረት"orgin" ማለትም ጥንታዊ ነቢያት የተሰጣቸው ኪታባት የተዋቀረበት አንጓ፣ የተናገሩበት ቋንቋ፣ የመልዕክቱ ምጥቀት ሆነ የቃላቱ ልቀት በዘመናችን እንደሌሉ ይናገራሉ፤ ባይብል ሙሉ ለሙሉ የፈጣሪ ንግግር ነው ብለው አያምኑም፤ "ፈጣሪ ሰዎችን የራሳቸውን ቃላት፣ ቋንቋ፣ ክህሎት እና ንግግር ተጠቅመው እንዲናገሩ ፈቀደላቸው" ይላሉ፤ ይህ ስህተት ነው። ለዛ ነው የፈጣሪ ንግግር ተበርዟል የምንለው፤ እውነትን በውሸት ሲቀላቅሉ እውነት የሆነው የአላህ ንግግር ከሰው ንግግር ጋር ስለተቀላቀለ እውነትን ከሐሰት ለመለየት አምላካችን አላህ ቁርአንን ፉርቃን አድርጎ አውርዷል፤ “ፉርቃን” فُرْقَان ማለት “እውነትን ከሐሰት የሚለይ” ማለት ነው፦
3:71 የመጸሐፉ ሰዎች ሆይ! *“እዉነቱን በዉሸት” ለምን ትቀላቅላላችሁ*? “እዉነቱንም” እናንተ የምታወቁ ስትሆኑ ለምን ትደብቃላችሁ? يَٰٓأَهْلَ ٱلْكِتَٰبِ لِمَ تَلْبِسُونَ ٱلْحَقَّ بِٱلْبَٰطِلِ وَتَكْتُمُونَ ٱلْحَقَّ وَأَنتُمْ تَعْلَمُونَ
25፥1 ያ *ፉርቃንን በባሪያው ላይ ለዓለማት አስጠንቃቂ ይኾን ዘንድ ያወረደው አምላክ ክብርና ጥራት ተገባው*፡፡ تَبَارَكَ ٱلَّذِى نَزَّلَ ٱلْفُرْقَانَ عَلَىٰ عَبْدِهِۦ لِيَكُونَ لِلْعَٰلَمِينَ نَذِيرًا

ከወንድም ወሒድ ዑመር
https://tttttt.me/Wahidcom

ወሰላሙ አለይኩም
ጽንፈኝነት

በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡

2፥190 *እነዚያንም የሚጋደሉዋችሁን ከሓዲዎች በአላህ መንገድ ተጋደሉ፡፡ ወሰንንም አትለፉ፤ አላህ ወሰን አላፊዎን አይወድምና*፡፡ وَقَاتِلُوا فِي سَبِيلِ اللَّهِ الَّذِينَ يُقَاتِلُونَكُمْ وَلَا تَعْتَدُوا ۚ إِنَّ اللَّهَ لَا يُحِبُّ الْمُعْتَدِينَ

ክርስቲያን ሆነው ክርስትና የሚያጠኑ ወይም ሙስሊም ሆነው እስልምናን የሚያጠኑ ምሁራን "ጽንፈኛ ምሁራን"conservative scholar" ሲባሉ በተቃራኒው ክርስትያን ሳይሆኑ ክርስትና የሚያጠኑ ወይም ሙስሊም ሳይሆኑ እስልምናን የሚያጠኑ ምሁራን "ለዘብተኛ ምሁራን"liberal scholar" ይባላሉ። ነገር ግን እዚህ መጣጥፍ ላይ "ጽንፈኛ" የምንለው "ወሰን አላፊ" "ድንበር አላፊ" ጠርዘኛ"Extremist" በሚለው ዐውድና ምህዋር ነው፤ በቁርኣን እነዚህ ሰዎች "ሙዕተዲን" مُعْتَدِين ይባላሉ፤ "ጽንፈኝነት" ወይም "ጠርዘኝነት"Extremism" ደግሞ "ዑድዋን" عُدْوَٰن ይባላል፦
2፥190 *እነዚያንም የሚጋደሉዋችሁን ከሓዲዎች በአላህ መንገድ ተጋደሉ፡፡ ወሰንንም አትለፉ፤ አላህ ወሰን አላፊዎን አይወድምና*፡፡ وَقَاتِلُوا فِي سَبِيلِ اللَّهِ الَّذِينَ يُقَاتِلُونَكُمْ وَلَا تَعْتَدُوا ۚ إِنَّ اللَّهَ لَا يُحِبُّ الْمُعْتَدِينَ

"ወሰን አትለፉ" የሚለውን ሃይለ-ቃል ይሰመርበት፤ ምክንያቱም አላህ ወሰን አላፊዎን አይወድምና፤ ጅሃድ ስሜትን፣ ዝንባሌን፣ ዘረኝነትን፣ ጎጠኝነትን፣ ጠርዘኝነትን ታሳቢ ያደረገ ሳይሆን “ፊ ሰብሊልላህ” فِي سَبِيلِ ٱللَّه ማለትም “በአላህ መንገድ” ብቻ ነው፤ በአላህ መንገድ ለአላህ ተብሎ ወይም አላህ ባስቀመጠልን መስፈርት ብቻ ማለት ነው፤ የሰውን ሕይወት ይቅርርና ገንዘቡን መብላት እንኳን በቁርኣን ወሰን ማለፍ ነው፦
4፥30 እናንተ ያመናችሁ ሆይ! *ገንዘቦቻችሁን በመካከላችሁ ያለ አግባብ አትብሉ፡፡ ግን ከእናንተ በመዋደድ የኾነችውን ንግድ ብሉ፡፡ እራሳችሁንም አትግደሉ*፡፡ አላህ ለእናንተ አዛኝ ነውና፡፡ يَٰٓأَيُّهَا ٱلَّذِينَ ءَامَنُوا۟ لَا تَأْكُلُوٓا۟ أَمْوَٰلَكُم بَيْنَكُم بِٱلْبَٰطِلِ إِلَّآ أَن تَكُونَ تِجَٰرَةً عَن تَرَاضٍۢ مِّنكُمْ ۚ وَلَا تَقْتُلُوٓا۟ أَنفُسَكُمْ ۚ إِنَّ ٱللَّهَ كَانَ بِكُمْ رَحِيمًۭا
4፥30 *ወሰን በማለፍ እና በመበደልም ይህንን የሠራ ሰው እሳትን እናገባዋለን*፡፡ ይኸም በአላህ ላይ ገር ነው፡፡ وَمَن يَفْعَلْ ذَٰلِكَ عُدْوَانًا وَظُلْمًا فَسَوْفَ نُصْلِيهِ نَارًا ۚ وَكَانَ ذَٰلِكَ عَلَى اللَّهِ يَسِيرًا
እራሳችሁን አትግደሉ" የሚለው ይሰመርበት፤ ሀቅ በሦስት ይከፈላል፤ አንደኛው የአላህ ሃቅ ሲሆን በአላህ አምልኮ ላይ ሌላ ማንነትና ምንነት ማሻረክ ትልቁ ዙልም ነው፤ ሁለተኛው የራስ ሃቅ ነው፤ እራስን መበደል ነው፥ ለምሳሌ እራስን መግደል፣ እራስን የሚጎዱ አልኮል መጠጣት፣ የአሳማ ስጋ መብላት ወዘተ፤ ሦስተኛው የሰው ሃቅ ነው፤ የሰውን ገንዘብ፣ ንብረት፣ መብት መንካት፤ ሰው ላይ በመሳደብ፣ በማንቋሸሽ፣ በማማት መድረስ ዙልም ነው፦
5፥87 *እናንተ ያመናችሁ ሆይ! አላህ ለናንተ የፈቀደላችሁን ጣፋጮች እርም አታድርጉ፡፡ ወሰንንም አትለፉ፡፡ አላህ ወሰን አላፊዎችን አይወድምና*፡፡ يَا أَيُّهَا الَّذِينَ آمَنُوا لَا تُحَرِّمُوا طَيِّبَاتِ مَا أَحَلَّ اللَّهُ لَكُمْ وَلَا تَعْتَدُوا ۚ إِنَّ اللَّهَ لَا يُحِبُّ الْمُعْتَدِينَ
11፥112 *እንደ ታዘዝከውም ቀጥ በል፡፡ ከአንተ ጋር ያመኑትም ቀጥ ይበሉ፡፡ ወሰንንም አትለፉ፤ እርሱ የምትሠሩትን ሁሉ ተመልካች ነውና*፡፡ فَاسْتَقِمْ كَمَا أُمِرْتَ وَمَن تَابَ مَعَكَ وَلَا تَطْغَوْا ۚ إِنَّهُ بِمَا تَعْمَلُونَ بَصِيرٌ

በቁርኣን "ነፍስን አትግደሉ" የሚል ሃይለ ቃል ብዙ ቦታ አለ፦
4፥33 *ያቺንም አላህ ያወገዛትን ነፍስ ያለ ሕግ አትግደሉ፡፡ የተበደለም ኾኖ የተገደለ ሰው ለዘመዱ በገዳዩ ላይ በእርግጥ ስልጣንን አድርገናል፡፡ በመግደልም ወሰንን አይለፍ*፤ እርሱ የተረዳ ነውና፡፡ وَلَا تَقْتُلُوا النَّفْسَ الَّتِي حَرَّمَ اللَّهُ إِلَّا بِالْحَقِّ ۗ وَمَن قُتِلَ مَظْلُومًا فَقَدْ جَعَلْنَا لِوَلِيِّهِ سُلْطَانًا فَلَا يُسْرِف فِّي الْقَتْلِ ۖ إِنَّهُ كَانَ مَنصُورًا

"በሕግ ቢሆን እንጂ" የሚለው ይሰመርበት፤ የተገደለበት ሰው "በመግደልም ወሰንን አይለፍ" የሚለው ይሰመርበት፤ ታዲያ ሁለት ሰዎች ወይም ሁለት ቡድኖች ቢጋደሉ ውሳኔው ምንድን ነው? የመጀመሪያው እርምጃ በመካከላቸው ማስታረቅ ነው፤ ነገር ግን ከሁለቱ አንደኛይቱም በሌላይቱ ላይ ወሰን ብታልፍ ያችን ወሰን የምታልፈውን ወደ አላህ ትዕዛዝ እስከምትመለስ ድረስ መጋደል ነው፤ በነገር ሁሉ ዘርን፣ ሃይማኖትን፣ ፓለቲካን ዝንባሌ ሳናደርግ ፍትኸኛ መሆን ነው፤ አላህ ፍትኸኞችን ይወዳል፦
49፥9 *ከምዕምናንም የኾኑ ሁለት ጭፍሮች ቢጋደሉ በመካከላቸው አስታርቁ፡፡ ከሁለቱ አንደኛይቱም በሌላይቱ ላይ ወሰን ብታልፍ ያችን ወሰን የምታልፈውን ወደ አላህ ትዕዛዝ እስከምትመለስ ድረስ ተጋደሉ፡፡ ብትመለስም በመካከላቸው በትክክል አስታርቁ፡፡ በነገሩ ሁሉ አስተካክሉም፡፡ አላህ አስተካካዮችን ይወዳልና*፡፡ وَإِن طَائِفَتَانِ مِنَ الْمُؤْمِنِينَ اقْتَتَلُوا فَأَصْلِحُوا بَيْنَهُمَا ۖ فَإِن بَغَتْ إِحْدَاهُمَا عَلَى الْأُخْرَىٰ فَقَاتِلُوا الَّتِي تَبْغِي حَتَّىٰ تَفِيءَ إِلَىٰ أَمْرِ اللَّهِ ۚ فَإِن فَاءَتْ فَأَصْلِحُوا بَيْنَهُمَا بِالْعَدْلِ وَأَقْسِطُوا ۖ إِنَّ اللَّهَ يُحِبُّ الْمُقْسِطِينَ

ዝንባሉን ሳንከተል፣ ደሃ ሃብታም ሳንል እራስ፣ ወላጅ እና ቅርብ ዘመድን ሳንወግን ለአላህ ስልን በትክክል መስካሪዎች መሆን አለብን፤ ከንቱ እና ጭፍን ፍቅር አሊያም ከንቱ እና ጭፍን ጥላቻ ለአላህ ቀጥተኞች ወይም በትክክል መስካሪዎች እንዳንሆን ያደርገናል፦
4፥135 እናንተ ያመናችሁ ሆይ! *በትክክል ፍትሕ ቀዋሚዎች በራሳችሁ ወይም በወላጆች እና በቅርብ ዘመዶች ላይ ቢኾንም እንኳ ለአላህ መስካሪዎች ኹኑ፡፡ ሀብታም ወይም ድኻ ቢኾን አላህ በእነርሱ ከእናንተ ይበልጥ ተገቢ ነው፡፡ እንዳታደሉም ዝንባሌን አትከተሉ፡፡ ብታጠምሙም ወይም መመስከርን ብትተው አላህ በምትሠሩት ሁሉ ውስጠ ዐዋቂ ነው*፡፡ يَا أَيُّهَا الَّذِينَ آمَنُوا كُونُوا قَوَّامِينَ بِالْقِسْطِ شُهَدَاءَ لِلَّهِ وَلَوْ عَلَىٰ أَنفُسِكُمْ أَوِ الْوَالِدَيْنِ وَالْأَقْرَبِينَ ۚ إِن يَكُنْ غَنِيًّا أَوْ فَقِيرًا فَاللَّهُ أَوْلَىٰ بِهِمَا ۖ فَلَا تَتَّبِعُوا الْهَوَىٰ أَن تَعْدِلُوا ۚ وَإِن تَلْوُوا أَوْ تُعْرِضُوا فَإِنَّ اللَّهَ كَانَ بِمَا تَعْمَلُونَ خَبِيرًا
5፥8 እናንተ ያመናችሁ ሆይ! *ለአላህ ቀጥተኞች በትክክል መስካሪዎች ኹኑ፡፡ ሕዝቦችንም መጥላት ባለማስተካከል ላይ አይገፋፋችሁ፡፡ አስተካክሉ፡፡ እርሱ ማስተካከል ለአላህ ፍራቻ በጣም የቀረበ ነው፡፡ አላህንም ፍሩ፡፡ አላህ በምትሠሩት ሁሉ ውስጠ ዐዋቂ ነው*፡፡ يَا أَيُّهَا الَّذِينَ آمَنُوا كُونُوا قَوَّامِينَ لِلَّهِ شُهَدَاءَ بِالْقِسْطِ ۖ وَلَا يَجْرِمَنَّكُمْ شَنَآنُ قَوْمٍ عَلَىٰ أَلَّا تَعْدِلُوا ۚ اعْدِلُوا هُوَ أَقْرَبُ لِلتَّقْوَىٰ ۖ وَاتَّقُوا اللَّهَ ۚ إِنَّ اللَّهَ خَبِيرٌ بِمَا تَعْمَلُونَ

በምድር ላይ የሰው ንብረት፣ ሕይወት፣ መብት የሚያጠፉ አጥፊዎችን እና አባካኞችን አላህ አይወዳቸውም፦
27፥77 *አላህም በሰጠህ ሀብት የመጨረሻይቱን አገር ፈልግ፡፡ ከቅርቢቱም ዓለም ፋንታህን አትርሳ፡፡ አላህም ወደ አንተ መልካምን እንዳደረገልህ ለሰዎች መልካምን አድርግ፡፡ በምድርም ውስጥ ማጥፋትን አትፈልግ፡፡ አላህ አጥፊዎችን አይወድምና*፡፡ وَابْتَغِ فِيمَا آتَاكَ اللَّهُ الدَّارَ الْآخِرَةَ ۖ وَلَا تَنسَ نَصِيبَكَ مِنَ الدُّنْيَا ۖ وَأَحْسِن كَمَا أَحْسَنَ اللَّهُ إِلَيْكَ ۖ وَلَا تَبْغِ الْفَسَادَ فِي الْأَرْضِ ۖ إِنَّ اللَّهَ لَا يُحِبُّ الْمُفْسِدِينَ
6፥141 *አታባክኑም፡፡ እርሱ አባካኞችን አይወድምና*፡፡ وَلَا تُسْرِفُوا ۚ إِنَّهُ لَا يُحِبُّ الْمُسْرِفِينَ

በምድር ላይ የሰው ንብረት፣ ሕይወት፣ መብት የሚያጠፉ አጥፊዎችን እና አባካኞችን ወሰን አላፊዎች ናቸው፤ የሰውን ሰላም የሚነሱ፣ ሕይወቱን፣ ንብረቱን፣ መብቱን እና ነጻነቱን የሚያውኩ እንደነዚህ አይነት ወሰን አላፊዎች የሚያወጡትን ትእዛዝ አትከተል፦
26፥151 *የወሰን አላፊዎችንም ትዕዛዝ አትከተሉ*፡፡ وَلَا تُطِيعُوا أَمْرَ الْمُسْرِفِينَ

አላህ ድንበር ከሚያልፉ ጠርዘኞች ይጠብቀን! አሚን።

ከወንድም ወሒድ ዑመር
https://tttttt.me/Wahidcom

ወሰላሙ አለይኩም
በእኔም በእናንተም ምን እንደሚሠራም አላውቅም

በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡

43፥43 ያንንም ወደ አንተ የተወረደልህን አጥብቀህ ያዝ፡፡ *አንተ በቀጥተኛው መንገድ ላይ ነህና*፡፡ فَٱسْتَمْسِكْ بِٱلَّذِىٓ أُوحِىَ إِلَيْكَ ۖ إِنَّكَ عَلَىٰ صِرَٰطٍۢ مُّسْتَقِيمٍۢ

መግቢያ
መቼም ሚሽነሪዎች ቆዳዬ ጠበበኝ ብለው የሚያላዝኑት ነገር ቢገርምም የአገራችን ሰዎች ደግሞ እነርሱን በቁርአን ላይ የሚያነሷቸውን ሂሶች እንደ ገደል ማሚቱ ሲያስተጋቡ ማየት ያስደምማል፤ ሚሽነሪዎ እራሳቸው መጽሐፍት ላይ ያሉትን አበሳና አሳር እንደማይወጡት ስለሚያውቁት በጊዜ ቁርአን ላይ መደበቁን መርጠዋል፤ የእኛ ጥያቄ ግን ተከድኖ ይብሰል ከተባለ ይኸው ጊዜ አስቆጠረ፤ እኛም ጠቃሚውን ነገር ከማይጠቅም ነገር ጋር ሳይሆን ጠቃሚውን ነገር ከሚጐዳ ነገር ጋር እያነጻጸርነው እንገኛለን፤ መቼም ስላቅና ፈሊጥ በአሉታዊ ሳይሆን በአውንታዊ ተመልክተን እዳው ገብስ ስለሆነ ሰው እንዲማርበት መልስ እንሰጣለን፤ ወደ ጉዳዩ ስንገባ ነብያችን”ﷺ” ወሕይ ከመጣላቸው በኃላ በቀጥተኛው መንገድ ላይ እንደሆኑ አምላካችን አላህ ተናግሯል፦
43፥43 ያንንም ወደ አንተ የተወረደልህን አጥብቀህ ያዝ፡፡ *አንተ በቀጥተኛው መንገድ ላይ ነህና*፡፡ فَٱسْتَمْسِكْ بِٱلَّذِىٓ أُوحِىَ إِلَيْكَ ۖ إِنَّكَ عَلَىٰ صِرَٰطٍۢ مُّسْتَقِيمٍۢ

አላህ ነብያችን”ﷺ” በቀጥተኛ መንገድ መሆናቸው ብቻ ሳይሆን ጀነት ገብተውም በጀነት ያለው ፀጋ እንደሚሰጣቸው ቃል ገብቶላቸዋል፦
108፥1 *እኛ በጣም ብዙ በጎ ነገሮችን ሰጠንህ*፡፡ إِنَّآ أَعْطَيْنَٰكَ ٱلْكَوْثَرَ

“በጎ ነገር” ተብሎ የተቀመጠው ቃል “ከውሰር” كَوْثَر ሲሆን በጀነት ውስጥ ያለ ከወተት የነጻና ከማር የጣፈጠ ወንዝ ነው፤ ይህ ከውሰር ለነብያችን”ﷺ” የተሰጠ ዋስትና ነው፦
ጃምዒ አት-ተርሚዚ መጽሐፍ 47, ሐዲስ 3684
አነስ ኢብኑ ማሊክ እንደተረከው፦ “እኛ ከውሰርን ሰጠንህ” ነብዩም”ﷺ” አሉ፦ በጀነት ወንዝ ነው፤ በጀነት ወንዝ ድንኳኖቹ ከድንጋይ የተሠሩ አየው፤ ጂብሪል ሆይ! ምንድን ነው? አልኩት፤ እርሱም ከውሰር ነው፤ አላህ ለአንተ የሰጠህ” አለኝ። عَنْ أَنَسٍ ‏:‏ ‏(‏ إناَّ، أَعْطَيْنَاكَ الْكَوْثَرَ ‏)‏ أَنَّ النَّبِيَّ صلى الله عليه وسلم قَالَ ‏”‏ هُوَ نَهْرٌ فِي الْجَنَّةِ ‏”‏ ‏.‏ قَالَ فَقَالَ النَّبِيُّ صلى الله عليه وسلم ‏”‏ رَأَيْتُ نَهْرًا فِي الْجَنَّةِ حَافَتَاهُ قِبَابُ اللُّؤْلُؤِ قُلْتُ مَا هَذَا يَا جِبْرِيلُ قَالَ هَذَا الْكَوْثَرُ الَّذِي قَدْ أَعْطَاكَهُ اللَّهُ ‏”‏ ‏.‏ قَالَ أَبُو عِيسَى هَذَا حَدِيثٌ حَسَنٌ صَحِيحٌ

ነብያችን”ﷺ” ጀነት አይደለም መግባት በተጨማሪ የጀነት ጀረጃቸውንም አላህ እንደነገረን ከላይ ያለው አንቀጽ በወፍ በረር ለቅምሻ ያክል በቂ ነው፤ ታዲያ ይህ ዋስትና እያለ አላህ ነብያችንን”ﷺ” “በእኔም በእናንተም ምን እንደሚሠራም አላውቅም” በል ሲላቸው እውን ሚሽነሪዎች እንደሚሉት ወደ ፊት የት እንደምንገባ አናውቅም በል ማለታቸውን ያሳያልን? ይህንን የተንሸዋረረና የተወላገደ መረዳት ጥንልልና ጥንፍፍ ባለ መልኩ እንየው፦
46:9 *ከመልክተኞች ብጤ የሌለኝ አይደለሁም፤ በእኔም በእናንተም ምን እንደሚሠራም አላውቅም፤ ወደ እኔ የሚወረደውን እጅግ ሌላን አልከተልም፤ እኔም ግልጽ አስጠንቃቂ እንጅ ሌላ አይደለሁም* በላቸው። قُلْ مَا كُنتُ بِدْعًۭا مِّنَ ٱلرُّسُلِ وَمَآ أَدْرِى مَا يُفْعَلُ بِى وَلَا بِكُمْ ۖ إِنْ أَتَّبِعُ إِلَّا مَا يُوحَىٰٓ إِلَىَّ وَمَآ أَنَا۠ إِلَّا نَذِيرٌۭ مُّبِينٌۭ

ነጥብ አንድ
“ብጤ የሌለኝ አይደለሁም”
ከነቢያችን”ﷺ” በፊት የመጡት በእርግጥ ምግብን የሚበሉ፣ በገበያዎችም የሚሄዱ ሰዎች ነበሩ፣ በተመሳሳይም ነቢያችን”ﷺ” ሰው ናቸው፣ በደረጃ እንጂ በሃልዎት ከሰው የተለዩ አልነበሩም፣ ከበፊቱ መልክተኞች በእርግጥ ያለፉ የሆኑ መልክተኛ ነበሩ፦
36:3 አንተ በእርግጥ *ከመልክተኞቹ ነህ*። إِنَّكَ لَمِنَ ٱلْمُرْسَلِينَ
2:252 አንተም *በእርግጥ ከመልክተኞቹ ነህ*፡፡ وَإِنَّكَ لَمِنَ ٱلْمُرْسَلِينَ
3:144 ሙሐመድም *ከበፊቱ መልክተኞች በእርግጥ ያለፉ የሆነ መልክተኛ እንጅ ሌላ አይደለም*፤ وَمَا مُحَمَّدٌ إِلَّا رَسُولٌۭ قَدْ خَلَتْ مِن قَبْلِهِ ٱلرُّسُلُ

ነጥብ ሁለት
“አላውቅም”
ነቢያችን”ﷺ” በራሳቸውና በሰዎች ምን እንደሚከናወን የወደፊቱን አያውቁም፣ ያ ማለት ሰዎች የሚያስጠነቅቁበት ቅርብ ይሁን እሩቅ አያውቁም፣ ከሚወርድላቸው ግህደተ-መለኮት ውጪ ምንም አያውቁም፦
6:50 «ለእናንተ የአላህ ግምጃ ቤቶች እኔ ዘንድ ናቸው አልልም፡፡ *ሩቅንም አላውቅም*፡፡ ለእናንተም እኔ መልአክ ነኝ አልልም፡፡ *ወደእኔ የሚወርድልኝን እንጅ ሌላን አልከተልም*» በላቸው፡፡ قُل لَّآ أَقُولُ لَكُمْ عِندِى خَزَآئِنُ ٱللَّهِ وَلَآ أَعْلَمُ ٱلْغَيْبَ وَلَآ أَقُولُ لَكُمْ إِنِّى مَلَكٌ ۖ إِنْ أَتَّبِعُ إِلَّا مَا يُوحَىٰٓ إِلَىَّ ۚ قُلْ هَلْ يَسْتَوِى ٱلْأَعْمَىٰ وَٱلْبَصِيرُ ۚ أَفَلَا تَتَفَكَّرُونَ
7:188 አላህ የሻውን በስተቀር ለራሴ ጥቅምንም፣ ጉዳትንም፣ ማምጣት አልችልም፣ *ሩቅንም የማውቅ በነበርኩ ኖሮ* ከመልካም ነገር ባበዛሁና ክፉም ነገር ባልነካኝ ነበር፤ እኔ ለሚያምኑ ሕዝቦች አስጠንቃቂና አብሳሪ እንጂ ሌላ አይደለሁም” በላቸው። قُل لَّآ أَمْلِكُ لِنَفْسِى نَفْعًۭا وَلَا ضَرًّا إِلَّا مَا شَآءَ ٱللَّهُ ۚ وَلَوْ كُنتُ أَعْلَمُ ٱلْغَيْبَ لَٱسْتَكْثَرْتُ مِنَ ٱلْخَيْرِ وَمَا مَسَّنِىَ ٱلسُّوٓءُ ۚ إِنْ أَنَا۠ إِلَّا نَذِيرٌۭ وَبَشِيرٌۭ لِّقَوْمٍۢ يُؤْمِنُونَ
21:109 እምቢም ቢሉ በማወቅ በእኩልነት ላይ ሆነን የታዘዝኩትን አስታወቅኋችሁ፤ *የምትስፈራሩበትም ነገር ቅርብ፣ ወይም ሩቅ፣ መሆኑን አላውቅም*፤ በላቸው። فَإِن تَوَلَّوْا۟ فَقُلْ ءَاذَنتُكُمْ عَلَىٰ سَوَآءٍۢ ۖ وَإِنْ أَدْرِىٓ أَقَرِيبٌ أَم بَعِيدٌۭ مَّا تُوعَدُونَ
21:111 እርሱም *ቅጣትን ማቆየት ምናልባት ለእናንተ ፈተናና እስከ ጊዜው መጣቀሚያ እንደኾነም “አላውቅም”*፤ በላቸው። وَإِنْ أَدْرِى لَعَلَّهُۥ فِتْنَةٌۭ لَّكُمْ وَمَتَٰعٌ إِلَىٰ حِينٍۢ