ወሒድ የዕቅበተ ኢሥላም መጣጥፍት"Wahid Articles of Islamic Apologetics"
59.2K subscribers
68 photos
70 videos
19 files
1.73K links
ዳዒ ወሒድ በኢሥላም እና በክርስትና መካከል ያለውን ልዩነት እና አንድነት በንጽጽር የሚያስቀምጥ ወንድም ነው። ለዚህም የቋንቋ፣ የሰዋስው፣ የዐውድ፣ የተዛማች እና የሥነ አመክንዮ ሙግት በማቅረብ የሚታወቅ ተሟጋች እና ጦማሪ ነው። ለሙግቱ ነጥብ በዋነኝነት የሚጠቀምባቸው ቋንቋ ዐማርኛ፣ ግዕዝ፣ እንግሊዝኛ፣ ዐረቢኛ፣ ዕብራይስጥ እና ግሪክ ናቸው። መልካም የንባብ፣ የጥናት፣ የማነጻጸር ጊዜ ይሁንልዎ!
Download Telegram
በአሰባሰቡ ጉዳይ ላይ ሚሽነሪዎች የሚያነሱት የመርሳት ጉዳይ ነው፤ አንድ ነብይ ማንኛውም ሰው እንደሚዘነጋ ይዘነጋል፤ አደም፣ ሙሳ፣ ነብያችንም"ﷺ" ቢሆኑ ይረሳሉ፦
20፥115 ወደ አደምም ከዚህ በፊት ኪዳንን በእርግጥ አወረድን፡፡ *ረሳም*፡፡ ለእርሱም ቆራጥነትን አላገኘንለትም፡፡ وَلَقَدْ عَهِدْنَا إِلَىٰ آدَمَ مِن قَبْلُ فَنَسِيَ وَلَمْ نَجِدْ لَهُ عَزْمًا
18፥73 *«በረሳሁት ነገር አትያዘኝ፡፡ ከነገሬም ችግርን አታሸክመኝ»* አለው፡፡ قَالَ لَا تُؤَاخِذْنِى بِمَا نَسِيتُ وَلَا تُرْهِقْنِى مِنْ أَمْرِى عُسْرًۭا
ሱነን ኢብኑ ማጃህ መጽሐፍ 5, ሐዲስ 1260 
ዐብደላህ እንደተረከው፦ *"የአላህ መልእክተኛ"ﷺ" ሶላት ላይ ይጨምሩ ወይም ይቀንሱ ነበር፤ ኢብራሂምም፦ "ይህ መወዛገብ ከእኔ ነው" አለ፤ እንዲህ አለ፦ "የአላህ መልእክተኛ ሆይ! አንዳንድ ጊዜ ሶላት ላይ ይጨምራሉን? እርሳቸውም፦ "እኔ ሰው ብቻ ነኝ፤ እናንተ እንደምትረሱ እኔም እረሳለው፤ ማንም ከረሳ ሁለት ረከዐት ይስገድ። ከዚያም ነብዩ"ﷺ" ተመልሰው ሁለቴ ሰገዱ*። عَنْ عَبْدِ اللَّهِ، قَالَ صَلَّى رَسُولُ اللَّهِ ـ صلى الله عليه وسلم ـ فَزَادَ أَوْ نَقَصَ - قَالَ إِبْرَاهِيمُ وَالْوَهْمُ مِنِّي - فَقِيلَ لَهُ يَا رَسُولَ اللَّهِ أَزِيدَ فِي الصَّلاَةِ شَىْءٌ قَالَ ‏ "‏ إِنَّمَا أَنَا بَشَرٌ أَنْسَى كَمَا تَنْسَوْنَ فَإِذَا نَسِيَ أَحَدُكُمْ فَلْيَسْجُدْ سَجْدَتَيْنِ وَهُوَ جَالِسٌ ‏"‏ ‏.‏ ثُمَّ تَحَوَّلَ النَّبِيُّ ـ صلى الله عليه وسلم ـ فَسَجَدَ سَجْدَتَيْنِ ‏.‏

እዚህ ሐዲስ ላይ ነብያችን"ﷺ" እኔ ሰው ብቻ ነኝ፤ እናንተ እንደምትረሱት እኔም እረሳለው" ያሉት ሶላት ላይ ረከዐትን መጨመርና መቀነስ እንጂ በፍጹም ስለ ቁርኣን መርሳት ሽታው እንኳን የለም። ሌላው ሂስ ይህ ሐዲስ ነው፦
ኢማም ቡኻርይ: መጽሐፍ 66, ሐዲስ 62
ዓኢሻህ እንደተረከችው፦ *"የአላህ መልእክተኛም"ﷺ" አንድ ሰው በሌሊት ሱራህን ሲቀራ እና እንዲህ ሲል ሰምተውታል፦ "የአላህ ምህረት በእርሱ ላይ ይሁን! የረሳኃትን እንዲህና እንዲያ የሚሉ ከሱራህ አንቀጽ አስታወሰኝ*። عَنْ عَائِشَةَ، قَالَتْ سَمِعَ رَسُولُ اللَّهِ صلى الله عليه وسلم رَجُلاً يَقْرَأُ فِي سُورَةٍ بِاللَّيْلِ فَقَالَ ‏ "‏ يَرْحَمُهُ اللَّهُ لَقَدْ أَذْكَرَنِي كَذَا وَكَذَا آيَةً كُنْتُ أُنْسِيتُهَا مِنْ سُورَةِ كَذَا وَكَذَا ‏"‌‏.‏

ሐዲሱ ላይ እረሳሁት የሚለው ሰው በሌሊት ሲቀራ የነበረው ሰው እንጂ እርሳቸው አይደሉም።
ሲቀጥል የሐዲሱ አርስት ላይ፦ "የቁርኣን መርሳት እና "እንዲህና እንዲያ የሚሉ አንቀጽ እረሳሁኝ" የሚል" بَابُ نِسْيَانِ الْقُرْآنِ وَهَلْ يَقُولُ نَسِيتُ آيَةَ كَذَا وَكَذَا
ተብሎ ተቀምጧል።
ሢሰልስ በሌሎች ሐዲሶች ላይ እንዲህና እንዲያ የሚሉ አናቅጽ የሚረሳው ማን እንደሆነ በስፋት ተብራርቷል፦
ኢማም ቡኻርይ: መጽሐፍ 66, ሐዲስ 63
ዐብደሏህ እንደተረከው፦ *"ነብዩም"ﷺ" አሉ፦ "ለምን ከእነርሱ አንዱ፦ "እንዲህና እንዲያ የሚሉ አናቅጽ እረስቻለው ይላል? በእርግጥም እረስቶታል*። عَنْ عَبْدِ اللَّهِ، قَالَ قَالَ النَّبِيُّ صلى الله عليه وسلم ‏ "‏ مَا لأَحَدِهِمْ يَقُولُ نَسِيتُ آيَةَ كَيْتَ وَكَيْتَ‏.‏ بَلْ هُوَ نُسِّيَ ‏"‌‏.‏
ኢማም ቡኻርይ: መጽሐፍ 66, ሐዲስ 54
ዐብደሏህ እንደተረከው፦ *"ነብዩም"ﷺ" አሉ፦ "አሳፋሪ ነገር ከእነርሱ አንዱ፦ "እንዲህና እንዲያ የሚሉ የቁርኣን አናቅጽ እረስቻለው" የሚል ነው፤ በእርግጥም እረስቶታል፤ ቁርኣንን ከግመል ፍጥነት ይልቅ ከሰው ልብ ያመልጣልና በደንብ ያዙት*። عَنْ عَبْدِ اللَّهِ، قَالَ قَالَ النَّبِيُّ صلى الله عليه وسلم ‏ "‏ بِئْسَ مَا لأَحَدِهِمْ أَنْ يَقُولَ نَسِيتُ آيَةَ كَيْتَ وَكَيْتَ بَلْ نُسِّيَ، وَاسْتَذْكِرُوا الْقُرْآنَ فَإِنَّهُ أَشَدُّ تَفَصِّيًا مِنْ صُدُورِ الرِّجَالِ مِنَ النَّعَمِ ‏

ሲያረብብ አምላካችን አላህ ቁርኣንን ለእርሳቸው አስቀርቶ እንደማይረሱት ቃል ገብቷል፦
87፥6 *ቁርኣንን በእርግጥ እናስነብብሃለን፤ አትረሳምም*፡፡ سَنُقْرِئُكَ فَلَا تَنسَىٰ
87፥7 *አላህ ከሻው በስተቀር*፡፡ እርሱ ግልጹን የሚሸሸገውንም ሁሉ ያውቃልና፡፡ إِلَّا مَا شَاءَ اللَّهُ ۚ إِنَّهُ يَعْلَمُ الْجَهْرَ وَمَا يَخْفَىٰ

"አላህ ከሻው በስተቀር" ማለት አላህ አንድን አንቀጽ በማስረሳት በሌላ አንቀጽ ከመለወጥ በስተቀር ማለት ነው፤ ይህ ነሥኽ ይባላል፤ “ነሥኽ” نسخ ማለት “ሽረት”abrogation” ማለት ሲሆን ይህም ሽረት አንደኛው “ናሢኽ” الناسخ ማለትም “ሻሪ አንቀጽ”Abrogator” ሲሆን ሁለተኛው “መንሡኽ” المنسوخ ማለትም “ተሻሪ አንቀጽ”Abrogated” ነው፦
2፥106 *ከአንቀጽ ብንለውጥ ወይም እርሷን ብናስረሳህ ከእርሷ የሚበልጥን ወይም ብጤዋን እናመጣለን*፤ አላህ በነገሩ ሁሉ ላይ ቻይ መኾኑን አታውቅምን? مَا نَنسَخْ مِنْ آيَةٍ أَوْ نُنسِهَا نَأْتِ بِخَيْرٍ مِّنْهَا أَوْ مِثْلِهَا ۗ أَلَمْ تَعْلَمْ أَنَّ اللَّهَ عَلَىٰ كُلِّ شَيْءٍ قَدِيرٌ
ነብያች"ﷺ" ሰው ናቸው ለጊዜው ቁርኣንን ይረሱ ነበር ቢባል እንኳን ጂብሪል በዓመት አንድ ጊዜ በረመዳን ወር ለዓመት ያክል ያስቀራቸውን ይደግምላቸው ነበር፤ እርሷቸውም ለዓመት የወረደውን በእርሱ ፊት ይቀሩ ነበር፤ ሊሞቱ ሲሉ ሁለቴ ደግሞላቸዋል፤ አንዱ ዓመታዊ ልማዱን ለመድገም ሲሆን ሁለተኛው አጠቃላይ ቁርኣንን ለማሳፈዝ ነው፦
ኢማም ቡኻርይ: መጽሐፍ 66, ሐዲስ 20
አቢ ሁረይራህ”ረ.ዐ” እንዳለው፦ *“ጂብሪል ቁርኣንን በየዓመት አንዴ ለነብዩ"ﷺ" ይደግምላቸው ነበር፤ በሚሞቱበት ዓመት ግን ሁለቴ ደገመላቸው*። عَنْ أَبِي هُرَيْرَةَ، قَالَ كَانَ يَعْرِضُ عَلَى النَّبِيِّ صلى الله عليه وسلم الْقُرْآنَ كُلَّ عَامٍ مَرَّةً، فَعَرَضَ عَلَيْهِ مَرَّتَيْنِ فِي الْعَامِ الَّذِي قُبِضَ،
ኢማም ቡኻርይ: መጽሐፍ 61, ሐዲስ 63
ኢብኑ ዐባሥ"ረ.ዐ." እንደተረከው፦ *"ነብዩ"ﷺ" ለሁሉም ሰው በጣም ለጋስ ነበሩ፤ የበለጠ በረመዷን ወር ጂብሪል በሚገናኛቸው ጊዜ ለጋስ ነበሩ፤ ሁልጊዜ በረመዳን ሌሊት ጂብሪል ሰላም በእርሱ ላይ ይሁን! ቁርኣንን ሊደግምላቸው ይገናኛቸው ነበር*። عَنِ ابْنِ عَبَّاسٍ ـ رضى الله عنهما ـ قَالَ كَانَ النَّبِيُّ صلى الله عليه وسلم أَجْوَدَ النَّاسِ، وَأَجْوَدُ مَا يَكُونُ فِي رَمَضَانَ، حِينَ يَلْقَاهُ جِبْرِيلُ، وَكَانَ جِبْرِيلُ ـ عَلَيْهِ السَّلاَمُ ـ يَلْقَاهُ فِي كُلِّ لَيْلَةٍ مِنْ رَمَضَانَ، فَيُدَارِسُهُ الْقُرْآنَ
ኢማም ቡኻርይ: መጽሐፍ 66, ሐዲስ 19
ኢብኑ ዐባሥ"ረ.ዐ." እንደተረከው፦ *"ነብዩ"ﷺ" በጣም ለጋስ ነበሩ፤ የበለጠ በረመዷን ወር ረመዷን እስኪያልቅ ድረስ ጂብሪል በሚገናኛቸው ጊዜ ለጋስ ነበሩ፤ የአላህ መልእክተኛም"ﷺ" ቁርኣንን ይቀሩለት ነበር። ጂብሪል በተገናኛቸው ጊዜ ከነፋስ ፍጥነት ይልቅ ለጋስ ነበሩ*። عَنِ ابْنِ عَبَّاسٍ ـ رضى الله عنهما ـ قَالَ كَانَ النَّبِيُّ صلى الله عليه وسلم أَجْوَدَ النَّاسِ بِالْخَيْرِ، وَأَجْوَدُ مَا يَكُونُ فِي شَهْرِ رَمَضَانَ لأَنَّ جِبْرِيلَ كَانَ يَلْقَاهُ فِي كُلِّ لَيْلَةٍ فِي شَهْرِ رَمَضَانَ حَتَّى يَنْسَلِخَ يَعْرِضُ عَلَيْهِ رَسُولُ اللَّهِ صلى الله عليه وسلم الْقُرْآنَ، فَإِذَا لَقِيَهُ جِبْرِيلُ كَانَ أَجْوَدَ بِالْخَيْرِ مِنَ الرِّيحِ الْمُرْسَلَةِ‏.‏

ይህ በቃል ደረጃ"oral form" የተሰበሰበው ቁርኣን በሙተዋቲር ከነብያችን"ﷺ" ወደ ሶሐባቦች፣ ከሶሐባዎች ወደ ታቢኢይዎች፣ ከታቢኢይዎች ወደ አትባኡ ታቢኢይዎች እያለ በሙተዋቲር አስራ አራት ትውልድ አሳልፎ መጥቷል፤ “ሙተዋቲር” مُتَواتِر ማለት ቁርኣን ከአንድ ኢስናድ በላይ በጀመዓ የሚደረግ ዘገባ ነው። አላህ ቁርኣንን እራሱ አውርዶ ከኋላውም ከፊቱም ውሸት እንዳይመጣበት እራሱ በአማኞች ልብ እንዲሰበሰብ ገር በማድረግ እና በምላስ እንዲቀራ ገር በማድረግ ይጠብቀዋል፦
15፥9 *እኛ ቁርኣንን እኛው አወረድነው፡፡ እኛም ለእርሱ ጠባቂዎቹ ነን*፡፡ إِنَّا نَحْنُ نَزَّلْنَا ٱلذِّكْرَ وَإِنَّا لَهُۥ لَحَٰفِظُونَ
41፥42 *ከኋላውም ከፊቱም ውሸት አይመጣበትም*፡፡ ጥበበኛ ምስጉን ከኾነው ጌታ የተወረደ ነው፡፡ لَّا يَأْتِيهِ ٱلْبَٰطِلُ مِنۢ بَيْنِ يَدَيْهِ وَلَا مِنْ خَلْفِهِۦ ۖ تَنزِيلٌۭ مِّنْ حَكِيمٍ حَمِيدٍۢ

ኢንሻላህ በገቢር ሁለት በጽሑፍ ደረጃ የተሰበሰበውን ሙስሐፍ ጥልልና ጥንፍፍ አርገን እናያለን....

ከወንድም ወሒድ ዑመር
https://tttttt.me/Wahidcom

ወሰላሙ አለይኩም
የቁርኣን አሰባሰብ

ገቢር ሁለት

በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው።

75፥17 *በልብህ ውስጥ መሰብሰቡ እና ማንበቡ በእኛ ላይ ነውና*፡፡ إِنَّ عَلَيْنَا جَمْعَهُ وَقُرْآنَهُ

ነጥብ ሁለት
"ሙስሐፍ"
አምላካችም አላህ ቁርኣንን በነብያችን"ﷺ" ልብ ላይ ያወረደው መነባነብ እንጂ በወረቀት የተጻፈን መጽሐፍ አላወረደም፦
26፥194 ከአስስጠንቃቂዎቹ ትኾን ዘንድ *በልብህ ላይ አወረደው*፡፡ عَلَىٰ قَلْبِكَ لِتَكُونَ مِنَ الْمُنذِرِينَ
2፥97 *በአላህ ፈቃድ በልብህ ላይ አውርዶታልና*፡፡ فَإِنَّهُ نَزَّلَهُ عَلَىٰ قَلْبِكَ بِإِذْنِ اللَّهِ
6፥7 *በአንተም ላይ በወረቀት የተጻፈን መጽሐፍ ባወረድን እና በእጆቻቸው በነኩት ኖሮ እነዚያ የካዱት ሰዎች «ይህ ግልጽ ድግምት እንጅ ሌላ አይደለም» ባሉ ነበር*፡፡ وَلَوْ نَزَّلْنَا عَلَيْكَ كِتَابًا فِي قِرْطَاسٍ فَلَمَسُوهُ بِأَيْدِيهِمْ لَقَالَ الَّذِينَ كَفَرُوا إِنْ هَـٰذَا إِلَّا سِحْرٌ مُّبِينٌ

“ቂርጧስ” قِرْطَاس ማለት በብራና የተጻፈ “ወረቀት” ነው፤ ቁርኣን በዚህ ቁስ ተጽፎ አልወረደም፤ ወደ ነብያችን"ﷺ" ልብ የተወረደው መጽሐፍ ወሕይ ወይም ተንዚል ነው፦
7፥2 *ይህ ወደ አንተ የተወረደ መጽሐፍ ነው፡፡ በደረትህም ውስጥ ከእርሱ ጭንቀት አይኑር*፡፡ كِتَابٌ أُنزِلَ إِلَيْكَ فَلَا يَكُن فِي صَدْرِكَ حَرَجٌ مِّنْهُ لِتُنذِرَ بِهِ وَذِكْرَىٰ لِلْمُؤْمِنِينَ

"ሙስሐፍ" مُصْحَف ማለት "የቁርአን ጥራዝ" ማለት ነው፤ ይህም ቁስ ብራና፣ ሰሌን፣ ስስ ድንጋይ፣ ሰሌዳ፣ የበግ አጥንት፣ የዘንባባ ቅርፊት፣ የቴምር ቅጠል፣ የከብት ቆዳ የመሳሰሉት ነው፤ ቁርኣን በነብያችን"ﷺ" የሕይወት ዘመን በተለያዩ ቁስ"Heterogeneous material" ማለትም በብራና፣ በሰሌን፣ በስስ ድንጋይ፣ በሰሌዳ፣ በበግ አጥንት፣ በዘንባባ ቅርፊት፣ በቴምር ቅጠል፣ በከብት ቆዳ በመሳሰሉት ላይ ተጻፈ። ነብያችን"ﷺ" ከስር ከስር የሚያጽፏቸው 48 የሚያክሉ ጸሐፊዎች እነ አቡበከር፣ ኡመር፣ ኡስማን፣ ዐሊይ፣ ዙበይር፣ ኡበይ፣ ሙአዊያህ፣ ዘይድ ኢብኑ ሣቢት ወዘተ ነበሯቸው። በጽሑፍ ደረጃም"graphic form" በዚህ መልኩ ተሰብስቧል፤ ዋቢ መጽሐፍ ይመልከቱ፦
ዛደል መዓድ መጽሐፍ 1 ቁጥር 117

ዋና ዋና ሰብሳቢዎቹ ኡባይ፣ ሙዐዝ ኢብኑ ጀበል፣ ዘይድ ኢብኑ ሣቢት እና አቡ ዘይድ ናቸው፦
ኢማም ቡኻሪይ: መጽሐፍ 66, ሐዲስ 25
ቃታዳህ እንደተረከው፤ እኔ አነሥ ኢብኑ ማሊክን"ረ.ዐ"፦ *"በነብዩ"ﷺ" የሕይወት ዘመን ቁርአንን የሰበሰቡት እነማን ናቸው? ብዬ ጠየኩት፤ እርሱም፦ "ሁሉም ከአንሷር ኡባይ፣ ሙዐዝ ኢብኑ ጀበል፣ ዘይድ ኢብኑ ሣቢት እና አቡ ዘይድ ናቸው" ብሎ መለሰልኝ*። حَدَّثَنَا قَتَادَةُ، قَالَ سَأَلْتُ أَنَسَ بْنَ مَالِكٍ ـ رضى الله عنه ـ مَنْ جَمَعَ الْقُرْآنَ عَلَى عَهْدِ النَّبِيِّ صلى الله عليه وسلم قَالَ أَرْبَعَةٌ كُلُّهُمْ مِنَ الأَنْصَارِ أُبَىُّ بْنُ كَعْبٍ وَمُعَاذُ بْنُ جَبَلٍ، وَزَيْدُ بْنُ ثَابِتٍ، وَأَبُو زَيْدٍ‏.‏
ኢማም ቡኻሪይ: መጽሐፍ 63, ሐዲስ 36
ቃታዳህ እንደተረከው፤ አነሥ"ረ.ዐ" እንደተናገረው፦ *"ቁርኣን በነብዩ"ﷺ" የሕይወት ዘመን በአራቱ ሰዎች ተሰብስቧል፤ ሁሉም ከአንሷር ኡባይ፣ ሙዐዝ ኢብኑ ጀበል፣ አቡ ዘይድ እና ዘይድ ኢብኑ ሣቢት ናቸው*። عَنْ قَتَادَةَ، عَنْ أَنَسٍ ـ رضى الله عنه ـ قَالَ جَمَعَ الْقُرْآنَ عَلَى عَهْدِ النَّبِيِّ صلى الله عليه وسلم أَرْبَعَةٌ، كُلُّهُمْ مِنَ الأَنْصَارِ أُبَىٌّ، وَمُعَاذُ بْنُ جَبَلٍ، وَأَبُو زَيْدٍ، وَزَيْدُ بْنُ ثَابِتٍ‏.‏
ኢማም ቡኻሪይ: መጽሐፍ 63, ሐዲስ 26
አነሥ"ረ.ዐ" እንደተረከው፦ *"ቁርኣን ነብዩ"ﷺ" በሞቱ ጊዜ በአራቱ ሰዎች እንጂ አልተሰበሰበም፤ እነርሱም፦ አቡ አድ-ደርዳ(ኡባይ)፤ ሙዐዝ ኢብኑ ጀበል፣ ዘይድ ኢብኑ ሣቢት እና አቡ ዘይድ ናቸው*። عَنْ أَنَسٍ، قَالَ مَاتَ النَّبِيُّ صلى الله عليه وسلم وَلَمْ يَجْمَعِ الْقُرْآنَ غَيْرُ أَرْبَعَةٍ أَبُو الدَّرْدَاءِ وَمُعَاذُ بْنُ جَبَلٍ وَزَيْدُ بْنُ ثَابِتٍ وَأَبُو زَيْد
ይህ በተለያየ ቁስ ማለትም በብራና፣ በሰሌን፣ በስስ ድንጋይ፣ በሰሌዳ፣ በበግ አጥንት፣ በዘንባባ ቅርፊት፣ በቴምር ቅጠል፣ በከብት ቆዳ በመሳሰሉት ላይ የነበረው የቁርኣን ጥራዝ በአንድ ቁስ"homogeneous material" ላይ ተቀመጠ፤ ይህ መርሃ-ግብር በየማማህ ፍልሚያ ብዙዎች ቃሪእዎች ስለሞቱ በዑመር አሳቢነትና በአቡ በከር መሪነት ዘይድ ኢብኑ ሳቢት ከተለያየ ጥራዝ በመሰብስብ በቃሪእዎች ልብ ካለው ጋር እያመሳከረ የሱራዎቹን ቅድመ-ተከለተል ጂብሪል በተናገረበት፣ ነቢያችን"ﷺ" ባስተላለፉበት፣ ሰሃባዎች ባፈዙበት ቅድመ-ተከተል ማለትም ከሱረቱል ፋቲሐህ እስከ ሱረቱ አን-ናስ በአንድ ቅጸ-ጥራዝ"one volume" ላይ ተጠርዞ እንዲቀመጥ አደረገው።
ይህ ወጥ አንድ ቅጸ-ጥራዝ"codex" አቡ በከር ዘንድ እስኪሞት ድረስ ተቀመጠ፤ ከዚያም ዑመር ዘንድ እስከ ሕይወቱ ማብቂያ ተቀመጠ፤ ከዚያም በስተመጨረሻ የዑመር ልጅ ሐፍሷህ ዘንድ ተቀመጠ፦
ኢማም ቡኻርይ: መጽሐፍ 66, ሐዲስ 8
ዘይድ ኢብኑ ሳቢት እንደተረከው"ረ.ዐ."፦ *"የየማማህ ሕዝቦች በተገደሉ ጊዜ አቡ በከር ወደ እርሱ እንድመጣ ላከብኝ። ወደ እርሱ ስሄድ ዑመር ኢብኑል ኸጧብ ከእርሱ ጋር ተቀምጧል*፤ አቡ በከርም"ረ.ዐ." እንዲህ አለኝ፦ *ዑመር ወደ እኔ መጥቶ እንዲህ አለ፦ በየማማህ ፍልሚያ አብዛኛውን የቁርኣን ቃሪእዎች ተገለዋል፤ በሌሎች የፍልሚያ መስኮች የበለጠ ከባድ ግድያ በቃሪእዎቹ ሊፈጸሙ እንደሚችሉ እና ከቁርኣን ብዙ እንዳይጠፋ እሰጋለሁ፤ ስለዚህ ቁርኣን እንዲሰበሰብ እንድታዝ አበረታታካለው*። እኔም ለዑመር፦ *"የአላህ መልእክተኛ"ﷺ" ያላደረጉትን ነገር እንዴት ላደርግ እችላለው? አልኩት፤ ዑመርም፦ "በአላህ ይሁንብህ! ይህ ሰናይ መርሃ-ግብር ነው" አለ። አላህም በዚህ ጉዳይ ልቤን እስከሚከፍትልኝ ድረስ ዑመር ያበረታታኝ ነበር፤ ያንን ዑመር ያጤነውን ሰናይ ሃልዮ እኔም ማጤን ጀመርኩኝ*።
ከዚያም አቡ በከር እኔን ዘይድን፦ *"አንተ ጥበበኛ ወጣት ነህ፤ ስለ አንተ ምንም አይነት ጥርጣሬ የለንም፤ አንተ ለአላህ መልእክተኛ"ﷺ" ወሕይ ትጽፍላቸው ነበር፤ የቁርኣንን ጽሑፎች ፈልግና በአንድ ጥራዝ ሰብስባቸው" አለኝ። በአላህ! ቁርኣንን ለመሰብሰብ ከሚያዙኝ ይልቅ ከተራራዎች አንዱን እንድቀይር ቢያዙኝ አይከብደኝም ነበር፤ እኔም ለአቡበከር፦ "የአላህ መልእክተኛ"ﷺ" ያላደረጉትን ነገር እንዴት ላደርግ እችላለው? አልኩት*፤ አቡ በከርም፦ *"በአላህ ይሁንብህ! ይህ ሰናይ መርሃ-ግብር ነው" አለ። በዚህ ጉዳይ ለአቡ በከር እና ለዑመር"ረ.ዐ" ልባቸውን የከፈተው አላህም በዚህ ጉዳይ ልቤን እስከሚከፍትልኝ ድረስ አቡ በከር ያበረታታኝ ነበር። ከዚያም እኔም ቁርኣንን መፈለግ ጀመርኩኝ፤ ከዘንባባ ቅጠል፣ ከስስ ነጭ ድንጋይ ወዘተ እና ከሰዎች ልቦች ፍለጋዬን እስከ በአቢ ኹዘይመተል አንሷሪይ ጋር ሁለት የሱረቱል ተውባህ የመጨረሻ አናቅጽ እስከማገኝ ድረስ ሰበሰብኩት። እነዚህ ሁለት አናቅጽ ከማንም ጋር አላገኘሁም ከእርሱ ጋር በስተቀር*፤ እነርሱም፦ *"ከጎሳችሁ የሆነ ችግራችሁ በእርሱ ላይ ጽኑ የሆነ፣ በእናንተ እምነት ላይ የሚጓጓ .."9፥128-129 የሚሉ አናቅጽ ናቸው*።
*ያም የተጠረዘው ጥራዝ አቡ በከር ዘንድ እስኪሞት ድረስ ተቀመጠ፤ ከዚያም ዑመር ዘንድ እስከ ሕይወቱ ማብቂያ ተቀመጠ፤ ከዚያም በስተመጨረሻ የዑመር ልጅ ሐፍሷህ"ረ.ዐ." ዘንድ ተቀመጠ*። أَنَّ زَيْدَ بْنَ ثَابِتٍ ـ رضى الله عنه ـ قَالَ أَرْسَلَ إِلَىَّ أَبُو بَكْرٍ مَقْتَلَ أَهْلِ الْيَمَامَةِ فَإِذَا عُمَرُ بْنُ الْخَطَّابِ عِنْدَهُ قَالَ أَبُو بَكْرٍ ـ رضى الله عنه ـ إِنَّ عُمَرَ أَتَانِي فَقَالَ إِنَّ الْقَتْلَ قَدِ اسْتَحَرَّ يَوْمَ الْيَمَامَةِ بِقُرَّاءِ الْقُرْآنِ وَإِنِّي أَخْشَى أَنْ يَسْتَحِرَّ الْقَتْلُ بِالْقُرَّاءِ بِالْمَوَاطِنِ، فَيَذْهَبَ كَثِيرٌ مِنَ الْقُرْآنِ وَإِنِّي أَرَى أَنْ تَأْمُرَ بِجَمْعِ الْقُرْآنِ‏.‏ قُلْتُ لِعُمَرَ كَيْفَ تَفْعَلُ شَيْئًا لَمْ يَفْعَلْهُ رَسُولُ اللَّهِ صلى الله عليه وسلم قَالَ عُمَرُ هَذَا وَاللَّهِ خَيْرٌ‏.‏ فَلَمْ يَزَلْ عُمَرُ يُرَاجِعُنِي حَتَّى شَرَحَ اللَّهُ صَدْرِي لِذَلِكَ، وَرَأَيْتُ فِي ذَلِكَ الَّذِي رَأَى عُمَرُ‏.‏ قَالَ زَيْدٌ قَالَ أَبُو بَكْرٍ إِنَّكَ رَجُلٌ شَابٌّ عَاقِلٌ لاَ نَتَّهِمُكَ، وَقَدْ كُنْتَ تَكْتُبُ الْوَحْىَ لِرَسُولِ اللَّهِ صلى الله عليه وسلم فَتَتَبَّعِ الْقُرْآنَ فَاجْمَعْهُ فَوَاللَّهِ لَوْ كَلَّفُونِي نَقْلَ جَبَلٍ مِنَ الْجِبَالِ مَا كَانَ أَثْقَلَ عَلَىَّ مِمَّا أَمَرَنِي مِنْ جَمْعِ الْقُرْآنِ قُلْتُ كَيْفَ تَفْعَلُونَ شَيْئًا لَمْ يَفْعَلْهُ رَسُولُ اللَّهِ صلى الله عليه وسلم قَالَ هُوَ وَاللَّهِ خَيْرٌ فَلَمْ يَزَلْ أَبُو بَكْرٍ يُرَاجِعُنِي حَتَّى شَرَحَ اللَّهُ صَدْرِي لِلَّذِي شَرَحَ لَهُ صَدْرَ أَبِي بَكْرٍ وَعُمَرَ ـ رضى الله عنهما ـ فَتَتَبَّعْتُ الْقُرْآنَ أَجْمَعُهُ مِنَ الْعُسُبِ وَاللِّخَافِ وَصُدُورِ الرِّجَالِ حَتَّى وَجَدْتُ آخِرَ سُورَةِ التَّوْبَةِ مَعَ أَبِي خُزَيْمَةَ الأَنْصَارِيِّ لَمْ أَجِدْهَا مَعَ أَحَدٍ غَيْرَهُ ‏{‏لَقَدْ جَاءَكُمْ رَسُولٌ مِنْ أَنْفُسِكُمْ عَزِيزٌ عَلَيْهِ مَا عَنِتُّمْ‏}‏ حَتَّى خَاتِمَةِ بَرَاءَةَ، فَكَانَتِ الصُّحُفُ عِنْدَ أَبِي بَكْرٍ حَتَّى تَوَفَّاهُ اللَّهُ ثُمَّ عِنْدَ عُمَرَ حَيَاتَهُ ثُمَّ عِنْدَ حَفْصَةَ بِنْتِ عُمَرَ ـ رضى الله عنه ـ‏.‏
ዘይድ ሱረቱል ተውባህ 9፥128-129 ሌላ ማንም ጋር አላገኘው ማለት ሌላ ሰው ጋር አልነበረም አያሰኝም። ምክንያቱም እርሱ ነው ፈልጎ ያላገኘው እንጂ ሁሉም ሶሐባዎች አይደሉም፤ ሲቀጥል የፈለገው በጽሑፍ ደረጃ ያሉትን ስብስብ እንጂ በቃል የታፈዙትን አይደለም። ምክንያቱም ሊፈልግ የቻለው በቃል ደረጃ ስለሚያውቀው ነው። ይህንን ሱረቱል አሕዛብ 33፥23 ያለውን እንዴት እንደፈለገ በመገንዘብ መረዳት ይቻላል፦
ኢማም ቡኻርይ: መጽሐፍ 56, ሐዲስ 23
ኻሪያህ ኢብኑ ዘይድ እንደተረከው፦ *"ዘይድ ኢብኑ ሳቢትም"ረ.ዐ." አለ፦ "ቁርኣን ከተለያዩ ጽሑፎች በተሰበሰበ ጊዜ ከሱረቱል አሕዛብ አንቀጽ ላይ የተረሳች ግን እኔ ከአላህ መልእክተኛ"ﷺ" ሲቀሯት የሰማኃትን ከማንም ጋር አላገኘኃትም፤ ያም ምስክርነት የአላህ መልእክተኛ"ﷺ" ስለ ሁለቱ ወንዶች እኩል ምስክርነት ነው፤ አንቀጹም፦ "ከአማኞቹ በእርሱ ላይ ለአላህ ቃል ኪዳን የገቡበትን በእውነት የፈጸሙ ወንዶች አሉ፤..."33፥23 የሚል ነው*። عَنْ خَارِجَةَ بْنِ زَيْدٍ، أَنَّ زَيْدَ بْنَ ثَابِتٍ ـ رضى الله عنه ـ قَالَ نَسَخْتُ الصُّحُفَ فِي الْمَصَاحِفِ، فَفَقَدْتُ آيَةً مِنْ سُورَةِ الأَحْزَابِ، كُنْتُ أَسْمَعُ رَسُولَ اللَّهِ صلى الله عليه وسلم يَقْرَأُ بِهَا، فَلَمْ أَجِدْهَا إِلاَّ مَعَ خُزَيْمَةَ بْنِ ثَابِتٍ الأَنْصَارِيِّ الَّذِي جَعَلَ رَسُولُ اللَّهِ صلى الله عليه وسلم شَهَادَتَهُ شَهَادَةَ رَجُلَيْنِ، وَهْوَ قَوْلُهُ ‏{‏مِنَ الْمُؤْمِنِينَ رِجَالٌ صَدَقُوا مَا عَاهَدُوا اللَّهَ عَلَيْهِ‏}‏

እነዚህ ሦስት አናቅጽ ከነብያችን"ﷺ" ሲቀሯት ባይሰማ ኖሮ ፍለጋ ባልወጣ ነበር። ምክንያቱም ቁርኣን ማለት በነጥብ አንድ እንደተመለከትነው በልብ የሚታፈዝ መነባነብ ነው። በጽሑፍ ደረጃ የተሰበሰቡት ጥራዞች ሁሉ ጠፉ ቢባል እንኳን ቁርኣን በቃሪእዎች ልብ ውስጥ አለ፦
ኢማም ቡኻርይ : መጽሐፍ 65, ሐዲስ 4937
ዓኢሻህ"ረ.ዐ." እንደተረከችው፦ *"ነብዩም"ﷺ" እንዲህ አሉ፦ "ያ ልክ ቁርኣንን በልቡ ሓፍዞ የሚቀራ በሰማይ ከተከበሩ ጸሐፊዎች(መላእክት) ጋር ይሆናል፤ ያ ልክ ቁርኣንን በልቡ እያወቀው በጣም እየከበደው የሚቀራ እጥፍ ምንዳ አለው*። عَنْ عَائِشَةَ، عَنِ النَّبِيِّ صلى الله عليه وسلم قَالَ ‏ "‏ مَثَلُ الَّذِي يَقْرَأُ الْقُرْآنَ وَهْوَ حَافِظٌ لَهُ مَعَ السَّفَرَةِ الْكِرَامِ الْبَرَرَةِ، وَمَثَلُ الَّذِي يَقْرَأُ الْقُرْآنَ وَهْوَ يَتَعَاهَدُهُ وَهْوَ عَلَيْهِ شَدِيدٌ، فَلَهُ أَجْرَانِ ‏"‌‏.‏

ነብያችን"ﷺ" በሕይወታቸው ዘመን ማብቂያ ላይ ስለ ሙሉ ቁርኣን በልብ ውስጥ እንዴት እንደሚቀራ እንዲህ ተናግረዋል፦
ኢማም ቡኻርይ: መጽሐፍ 66, ሐዲስ 78
ዐብደላህ ኢብኑ ዐምር እንደተረከው፦ *"ነብዩም"ﷺ" እኔን፦ "ሙሉ ቁርኣንን ቀርቶ ለመጨረስ ስንት ጊዜ ይወስድብሃል? ብለው ጠየቁኝ*። عَنْ عَبْدِ اللَّهِ بْنِ عَمْرٍو، قَالَ لِي النَّبِيُّ صلى الله عليه وسلم ‏ "‏ فِي كَمْ تَقْرَأُ الْقُرْآنَ ‏"‌‏.‏
ኢማም ቡኻርይ: መጽሐፍ 66, ሐዲስ 79
ዐብደላህ ኢብኑ ዐምር እንደተረከው፦ *"የአላህ መልእክተኛም"ﷺ" አሉ፦ "ሙሉ ቁርኣንን በአንድ ወር ጊዜ ቅራ"። እኔም፦ "ከዛ በታች ለመቅራት ችሎታው አለኝ" አልኩኝ፤ እርሳቸው፦ "በሰባት ቀናት ቅራው፤ ከዚያ በታች ሙሉውን ለመቅራት አይቻልም*። عَنْ عَبْدِ اللَّهِ بْنِ عَمْرٍو، قَالَ قَالَ رَسُولُ اللَّهِ صلى الله عليه وسلم ‏"‏ اقْرَإِ الْقُرْآنَ فِي شَهْرٍ ‏"‌‏.‏ قُلْتُ إِنِّي أَجِدُ قُوَّةً حَتَّى قَالَ ‏"‏ فَاقْرَأْهُ فِي سَبْعٍ وَلاَ تَزِدْ عَلَى ذَلِكَ ‏"‌‏.‏

በሰባት ቀናት ከፋፍሎ መቅራት "መንዚል" منزل ይባላል፤ ሌላው ቁርኣን ሠላሳ ጁዝዕ" አለው፤ "ጁዝዕ" جُزْءْ‎ ማለት "ክፍል"part" ማለት ሲሆን በሠላሳ ቀናት ከፋፍሎ መቀራትን ያሳያል፤ በተለይ በተራዊህ ሶላት ላይ ሙሉ ሠላሳ ጁዝዕ ይቀራል፤ “ተራዊህ” تراويح‌‎ ማለትም “በረመዳን የሌሊት ሶላት” ማለት ነው። ስለዚህ ቁርኣን ከትውልድ ወደ ትውልድ በቃሪእዎች ልብ ውስጥ በሙተዋቲር የሚተላለፍ ታምር ነው።

ከወንድም ወሒድ ዑመር
https://tttttt.me/Wahidcom

ወሰላሙ አለይኩም
ነሷራ

በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፤

5፥14 ከእነዚያም እኛ *ክርስቲያኖች* ነን ካሉት የጠበቀ ቃል ኪዳናቸውን ያዝን፡፡ *በእርሱም ከታዘዙበት ነገር ፈንታን ተውት*፡፡ ስለዚህ እስከ ትንሣኤ ቀን ድረስ በመካከላቸው ጠብንና ጥላቻን ጣልንባቸው፡፡ አላህም ይሠሩት የነበሩትን ሁሉ በእርግጥ ፡፡ وَمِنَ الَّذِينَ قَالُوا إِنَّا نَصَارَىٰ أَخَذْنَا مِيثَاقَهُمْ فَنَسُوا حَظًّا مِّمَّا ذُكِّرُوا بِهِ فَأَغْرَيْنَا بَيْنَهُمُ ይነግራቸዋልالْعَدَاوَةَ وَالْبَغْضَاءَ إِلَىٰ يَوْمِ الْقِيَامَةِ ۚ وَسَوْفَ يُنَبِّئُهُمُ اللَّهُ بِمَا كَانُوا يَصْنَعُونَ

አምላካችን አላህ ለዒሳ ወንጌልን ሰጠው፤ በዚያ ወንጌል ውስጥ፦ “የኢንጅልም ባለቤቶች በውስጡ አላህ ባወረደው ሕግ ይፍረዱ” የሚል መመሪያ አለ፦
5፥46 በፈለጎቻቸውም ላይ የመርየምን ልጅ ዒሳን ከተውራት በስተፊቱ ያለውን አረጋጋጭ ሲሆን፣ ፤ *ኢንጂልንም በውስጡ ቀጥታና ብርሃን ያለበት በስተፊቱ ያለችውን አስከተልንተውራትንም የሚያረጋግጥ ለጥንቁቆችም መሪና ሲሆን ሰጠነው*። وَقَفَّيْنَا عَلَىٰٓ ءَاثَٰرِهِم بِعِيسَى ٱبْنِ مَرْيَمَ مُصَدِّقًۭا لِّمَا بَيْنَ يَدَيْهِ مِنَ ٱلتَّوْرَىٰةِ ۖ وَءَاتَيْنَٰهُ ገሣጭٱلْإِنجِيلَ فِيهِ هُدًۭى وَنُورٌۭ وَمُصَدِّقًۭا لِّمَا بَيْنَ يَدَيْهِ مِنَ ٱلتَّوْرَىٰةِ وَهُدًۭى وَمَوْعِظَةًۭ لِّلْمُتَّقِينَ
5፥47 የኢንጅልም ባለቤቶች በውስጡ *አላህ ባወረደው ሕግ ይፍረዱ*፤ وَلْيَحْكُمْ أَهْلُ ٱلْإِنجِيلِ بِمَآ أَنزَلَ ٱللَّهُ فِيهِ

“ቀፈይና” قَفَّيْنَا ማለትም “አስከተልን” እና “አተይናሁ” آتَيْنَاهُ ማለትም “ሰጠነው” የሚሉት ያለቁ አላፊ ግስ ናቸው፤ “ልየሕኩም” َلْيَحْكُمْ ማለትም “ይፍረዱ” የሚለው ትዕዛዛዊ ግስ መነሻ ላይ “ወ” و ማለትም “እና” የሚል አያያዥ መስተጻምር አለ፤ ያ ማለት “ይፍረዱ” የሚለው ትዕዛዛዊ ግስ “አስከተልን” እና “ሰጠነው” ከሚሉት ግስ ጋር ተያይዞ የመጣ መሆኑ “አልን” የሚል ሙስጠጢር ማለትም ህቡዕ ግስ‘’headen verb‘’ አላፊ ሆኖ መጥቷል፣ ስለዚህ ‘’የኢንጅልም ባለቤቶች በውስጡ አላህ ባወረደው ሕግ ይፍረዱ አልን‘’ የሚል ፍቺ ይኖረዋል። ተፍሲሩል ጀላለይን በዚህ መልኩ ነው የፈሰረው፤ ለናሙና ያክል ሌላ ተጨማሪ ጥቅስ ብንመለከት ነገሩን የበለጠ ግልጽ ያደርገዋል፦
19:12 የሕያ ሆይ! መጽሐፉን በጥብቅ *ያዝ*፣ ጥበብንም በሕጻንነቱ *ሰጠነዉ*። يَٰيَحْيَىٰ خُذِ ٱلْكِتَٰبَ بِقُوَّةٍۢ ۖ وَءَاتَيْنَٰهُ ٱلْحُكْمَ صَبِيًّۭا

“ሁዚ” خُذِ ማለትም “ያዝ” ትዕዛዛዊ ግስ ነው፤ “አተይናሁ” آتَيْنَاهُ ማለትም “ሰጠነው” የሚለው ቃል ደግሞ ያለቀ አላፊ ግስ ነዉ፣ “አተይናሁ” ከሚለው የሚለቅቃል በፊት “ወ” و ማለትም “እና” የሚል አያያዥ መስተጻምር አለ፤ ያ ማለት “ያዝ” የሚለው ግስ “ሰጠነው” ከሚለው ግስ ጋር ተያይዞ የመጣ መሆኑ “አልን” የሚል ሙስጠጢር አላፊ ሆኖ መጥቷል፣ ትዕዛዛዊስለዚህ ‘’መጽሐፉን በጥብቅ ያዝ አልነዉ‘‘’ የሚል ፍቺ እንደሚኖረው ሁሉ ከላይ ያለውንም በዚህ ሒሳብ እንረዳዋለን።

አምላካችን አላህ የኢንጅል ባለቤቶችን ከነበሩት ከዒሳ ቀዳማይ ጋር የከበደ ኪዳን አድርጓል፦
5፥14 ከእነዚያም እኛ *ክርስቲያኖች* ነን ካሉትጣልንባቸው የጠበቀ ቃል ኪዳናቸውን ያዝን፡፡ *በእርሱም ከታዘዙበት ነገር ፈንታን ተውት*፡፡ ስለዚህ እስከ ትንሣኤ ቀን ድረስ በመካከላቸው ጠብንና ጥላቻን ፡፡ አላህም ይሠሩት የነበሩትን ሁሉ በእርግጥ ይነግራቸዋል፡፡ وَمِنَ الَّذِينَ قَالُوا إِنَّا نَصَارَىٰ أَخَذْنَا مِيثَاقَهُمْ فَنَسُوا حَظًّا مِّمَّا ذُكِّرُواተብሎ بِهِ فَأَغْرَيْنَا بَيْنَهُمُ الْعَدَاوَةَ وَالْبَغْضَاءَ إِلَىٰ يَوْمِ الْقِيَامَةِ ۚ وَسَوْفَ يُنَبِّئُهُمُ اللَّهُ بِمَا كَانُوا يَصْنَعُونَ

“ክርስቲያኖች” የተቀመጠው ቃል “ነሷራ” نَصَارَىٰ ነው፤ “ነስራኒይ” نَصْرَانِيّ የሚለው ቃል በነጠላ ሲሆን በብዜት ደግሞ “ነሷራ” نَصَارَىٰ ነው፤ ይህም ቃል “ነሰረ” نَصَرَ ማለትም “ረዳ” ከሚል ግስ መደብ ወይም “ነስር” نَصْر ማለትም “እርዳታ” ከሚል ከስም መደብ የረባ ሲሆን ቋንቋዊው ፍቺው “ረዳቶች” ማለት ነው።
“ነሲር” نَصِير ወይም “ናሲር” نَاصِر ማለትም “እረዳት”፣ “መንሱር” مَنصُور ማለትም “የተረዳ”፣ “ሙንተሲር” مُّنتَصِر ማለትም “ተረጂ” የሚሉት ቃላት ልክ እንደ “ነሳራ” ቃል “ነሰረ” ከሚል ግስ መደብ ወይም “ነስር” ከሚል የስም መደብ የረቡ ናቸው፤ ይህ ስም በቁርኣን 15 ጊዜ ተውስቷል፤ እነዚህ የአላህ እና የመልእክተኛ የዒሳ እረዳቶች ሐዋርያት ናቸው፦
60፥14 እናንተ ያመናችሁ ሆይ! የመርየም ልጅ ዒሳ ለሐዋርያቶቹ «ወደ አላህ *ረዳቴ* ማነው?» እንዳለ ሐወርያቶቹም «እኛ የአላህ *ረዳቶች* ነን» እንዳሉትላይ የአላህ ረዳቶች ኹኑ፡፡ ከእስራኤልም ልጆች አንደኛዋ ጭፍራ አመነች፡፡ ሌላይቱም ጭፍራ ካደች፡፡ እነዚያን ያመኑትንም በጠላታቸው አበረታናቸው፤ አሸናፊዎችም ኾኑ፡፡ يَٰٓأَيُّهَا ٱلَّذِينَ ءَامَنُوا۟ كُونُوٓا۟ أَنصَارَ ٱللَّهِ كَمَا قَالَ عِيسَى ٱبْنُ مَرْيَمَ لِلْحَوَارِيِّـۧنَ مَنْ أَنصَارِىٓ إِلَى ٱللَّهِ ۖ قَالَ ٱلْحَوَارِيُّونَ نَحْنُ أَنصَارُ ٱللَّهِ ۖ فَـَٔامَنَت طَّآئِفَةٌۭ مِّنۢ بَنِىٓ إِسْرَٰٓءِيلَ وَكَفَرَت طَّآئِفَةٌۭ ۖ فَأَيَّدْنَا ٱلَّذِينَ ءَامَنُوا۟ عَلَىٰ عَدُوِّهِمْ فَأَصْبَحُوا۟ ظَٰهِرِينَ
3፥52 ዒሳ ከእነርሱ ክህደት በተሰማውም ጊዜ፡- «ወደ አላህ *ረዳቶቼ* እነማን ናቸው» አለ፤ ሐዋርያት፡- «እኛ የአላህ *ረዳቶች* ነን፤ በአላህ አምነናል፤ እኛም ትክክለኛ ታዛዦች መኾናችንን መስክር» አሉ፡፡ فَلَمَّآ أَحَسَّ عِيسَىٰ مِنْهُمُ ٱلْكُفْرَ قَالَ مَنْ أَنصَارِىٓ إِلَى ٱللَّهِ ۖ قَالَ ٱلْحَوَارِيُّونَ نَحْنُ أَنصَارُ ٱللَّهِ ءَامَنَّا بِٱللَّهِ وَٱشْهَدْ بِأَنَّا مُسْلِمُونَ

አላህ ከእነዚህ የእርሱ እና የመልእክተኛ እረዳቶች ጋር የከበደ ቃል ኪዳን አድርጓል፤ ይህምም ቃል ኪዳን “በእኔ እና በመልክተኛዬ እመኑ» በማለት አዟል፤ አነዚህ የዒሳ ሐዋርያትም ይህንን ቃል አምነው ሙስሊሞች መሆናቸውን አስመስክረዋል፦
5፥111 ወደ *ሐዋርያትም* «በእኔ እና በመልክተኛዬ እመኑ» *በማለት ባዘዝኩ* ጊዜ አስታውስ፡፡ *«አመንን፤ እኛ ሙስሊሞች መኾናችንን መስክር»* አሉ፡፡ وَإِذْ أَوْحَيْتُ إِلَى ٱلْحَوَارِيِّـۧنَ أَنْ ءَامِنُوا۟ بِى وَبِرَسُولِى قَالُوٓا۟ ءَامَنَّا وَٱشْهَدْ بِأَنَّنَا مُسْلِمُونَ
3:52 ዒሳ ከእነርሱ ክሕደት በተሰማዉም ጊዜ ፡-ወደ አላህ *ረዳቶቼ እነማን ናቸዉ? አለ፤ ሐዋሪያት ፡ -እኛ የአላህ ረዳቶች ነን፤ በአላህም አምነናል፤ እኛም ትክክለኛ ”ታዛዦች”* መሆናችንን፥ መስክር፥ አሉ። فَلَمَّآ أَحَسَّ عِيسَىٰትተው مِنْهُمُ ٱلْكُفْرَ قَالَ مَنْ أَنصَارِىٓ إِلَى ٱللَّهِ ۖ

ነገር ግን ከሐዋርያት ህልፈት በኃላ ያሉት ነስራኒይዎች በእርሱም ከታዘዙት ፈንታ በአላህ ላይ በመቅጠፍ “ሦስት ነው” በማለት ወሰን አልፈዋል፦
4፥171 እናንተ የመጽሐፉ ሰዎች ሆይ! በሃይማኖታችሁ ወሰንን አትለፉ፡፡ *በአላህም ላይ እውነትን እንጅ አትናገሩ፡፡……. ሦስት ነው* አትበሉም፡፡ ተከልከሉ፤ ለእናንተ የተሻለ ይኾናልና፡፡ አላህ አንድ አምላክ ብቻ ነው፡፡ يَٰٓأَهْلَ ٱلْكِتَٰبِ لَا تَغْلُوا۟ فِى دِينِكُمْ وَلَا تَقُولُوا۟ عَلَى ٱللَّهِ إِلَّا ٱلْحَقَّ ۚ إِنَّمَا ٱلْمَسِيحُ عِيسَى ٱبْنُ مَرْيَمَ رَسُولُ ٱللَّهِ وَكَلِمَتُهُۥٓ أَلْقَىٰهَآ إِلَىٰ مَرْيَمَ وَرُوحٌۭ مِّنْهُ ۖ فَـَٔامِنُوا۟ بِٱللَّهِ وَرُسُلِهِۦ ۖ وَلَا تَقُولُوا۟ ثَلَٰثَةٌ ۚ ٱنتَهُوا۟ خَيْرًۭا لَّكُمْ ۚ إِنَّمَا ٱللَّهُ إِلَٰهٌۭ وَٰحِدٌۭ ۖ سُبْحَٰنَهُۥٓ أَن يَكُونَ لَهُۥ وَلَدٌۭ ۘ لَّهُۥ مَا فِى ٱلسَّمَٰوَٰتِ وَمَا فِى ٱلْأَرْضِ ۗ وَكَفَىٰ بِٱللَّهِ وَكِيلًۭا

አላህ የኢየሱስን ቀዳማይ ተከታይ በእነዚያ ኢየሱስን በካዱት አይሁዳውያን ላይ ሲያበልጣቸው በተቃራኒው በሁለተኛው ክፍለ-ዘመን ያሉት ተከታዮቹ ግን አላህ ያልተናገረውን ምንኩስና የእርሱን ውዴታ ለመጠበቅ ፈጠሯት፦
3፥55 አላህም ባለ ጊዜ አስታውስ፡፡ ዒሳ ሆይ! እኔአድራጊ ወሳጂህ ወደ እኔም አንሺህ ነኝ፡፡ ከነዚያም ከካዱት ሰዎች አጥሪህ ነኝ *እነዚያንም የተከተሉህን እስከ ትንሣኤ ቀን ድረስ ከነዚያ ከካዱት በላይ ነኝ*፡፡ إِذْ قَالَ ٱللَّهُ يَٰعِيسَىٰٓ إِنِّى مُتَوَفِّيكَ وَرَافِعُكَ إِلَىَّ وَمُطَهِّرُكَ مِنَ ٱلَّذِينَ كَفَرُوا۟ وَجَاعِلُ ٱلَّذِينَ ٱتَّبَعُوكَ فَوْقَ ٱلَّذِينَ كَفَرُوٓا۟ إِلَىٰ يَوْمِ ٱلْقِيَٰمَةِ
57፥27 ከዚያም በዱካዎቻቸው ላይ መልክተኞቻችንን አስከታተልን፡፡ የመርየምን ልጅ ዒሳንም አስከተልን፡፡ ኢንጂልንም ሰጠነው፡፡ *በእነዚያም በተከተሉት ልቦች ውሰጥ መለዘብንና እዝነትን፣ አዲስ የፈጠሩዋትንም ምንኩስና አደረግን፡፡ በእነርሱ ምንኩስናን አልጻፍናትም፡፡ ግን የአላህን ውዴታ ለመፈለግ ሲሉ ፈጠሩዋት፡፡ ተገቢ አጠባበቋንም፤ አልጠበቋትም*፡፡ ከእነርሱም ለእነዚያ ላመኑት ምንዳቸውን ሰጠናቸው፡፡፡ ከእነርሱም ብዙዎቹ አመጸኞች ናቸው፡፡ ثُمَّ قَفَّيْنَا عَلَىٰٓ ءَاثَٰرِهِم بِرُسُلِنَا وَقَفَّيْنَا بِعِيسَى ٱبْنِ مَرْيَمَ وَءَاتَيْنَٰهُ ٱلْإِنجِيلَ وَجَعَلْنَا فِى قُلُوبِ ٱلَّذِينَ ٱتَّبَعُوهُ رَأْفَةًۭ وَرَحْمَةًۭ وَرَهْبَانِيَّةً ٱبْتَدَعُوهَا مَا كَتَبْنَٰهَا عَلَيْهِمْ إِلَّا ٱبْتِغَآءَ رِضْوَٰنِ ٱللَّهِ فَمَا رَعَوْهَا حَقَّ رِعَايَتِهَا ۖ فَـَٔاتَيْنَا ٱلَّذِينَ ءَامَنُوا۟ مِنْهُمْ أَجْرَهُمْ ۖ وَكَثِيرٌۭ مِّنْهُمْ فَٰسِقُونَ

ከዒሳ ተከታዮች ብዙዎቹ አመጸኞች ናቸው፤ ነገር ግን አላህ ከእነርሱም ለእነዚያ ላመኑት ምንዳቸውን ሰጣቸው፤ በእነርሱ ላይ በሚነበብላቸውም ጊዜ «በእርሱ አምነናል፡፡ እርሱ ከጌታችን የኾነ እውነት ነው፤ እኛ ከእርሱ በፊት ሙስሊሞች ነበርን» ይላሉ፦
28፥52 እነዚያ ከእርሱ በፊት መጽሐፍን የሰጠናቸው እነርሱ *በእርሱ ያምናሉ*፡፡ الَّذِينَ آتَيْنَاهُمُ الْكِتَابَ مِن قَبْلِهِ هُم بِهِ يُؤْمِنُونَ
28፥53 በእነርሱ ላይ በሚነበብላቸውም ጊዜ «በእርሱ አምነናል፡፡ እርሱ ከጌታችን የኾነ እውነት ነው፡፡ *እኛ ከእርሱ በፊት ሙስሊሞች ነበርን*» ይላሉ፡፡ وَإِذَا يُتْلَىٰ عَلَيْهِمْ قَالُوا آمَنَّا بِهِ إِنَّهُ الْحَقُّ مِن رَّبِّنَا إِنَّا كُنَّا مِن قَبْلِهِ مُسْلِمِينَ

ልብ አድርግ “እኛ ከእርሱ ከመጽሐፉ ማለትም ከቁርአን መውረድ በፊት ሙስሊም ነበርን” ማለታቸው ምክንያታዊ ነው፤ ሙስሊም” مُسْلِم ትርጉሙ “አቢድ” عَابِدُ ማለትም “አምላኪ” አሊያም “ቃኒት” قَانِتِ ማለትም “ታዛዥ” ማለት ነው። እንደሚታወቀው የመጽሐፉ ሰዎች ብዙዎቹ አመጸኞች ናቸው፤ አይሁዳውያን አላህ የተቆጣባቸው ሲሆኑ ክርስቲያኖች ደግሞ የተሳቱተት ናቸው፦
ጃምዒ አት-ተርሚዚ መጽሐፍ 47, ሐዲስ 3212
ዐዲይ ኢብኑ ሓቲም እንደተረከው ነብዩም”ﷺ” አሉ፦ አይሁዳውያን የተቆጣባቸው ናቸው፤ ክርስቲያኖች የተሳቱተት ናቸው። عَنْ عَدِيِّ بْنِ حَاتِمٍ، عَنِ النَّبِيِّ صلى الله عليه وسلم قَالَ ‏ “‏ الْيَهُودُ مَغْضُوبٌ عَلَيْهِمْ وَالنَّصَارَى ضُلاَّلٌ ‏”‏ ‏.‏

ነገር ግን ከአይሁዳውያን ጥቂት ያልተቆጣቸው፤ እንዲሁ ከክርስቲያኖች ጥቂት ያልተሳሳቱ ነበሩ፤ እኛም ከመንገዱ እንዳንስት የእነዚያን በእነርሱ ላይ በጎ የዋለላቸውን መንገድ ምራን ብለን እንቀራለን፦
1፥7 የእነዚያን በእነርሱ ላይ በጎ የዋልክላቸውን፣ በእነርሱ ላይ *”ያልተቆጣህባቸውን እና ያልተሳሳቱትንም ሰዎች መንገድ ምራን”*፤ በሉ። صِرَٰطَ ٱلَّذِينَ أَنْعَمْتَ عَلَيْهِمْ غَيْرِ ٱلْمَغْضُوبِ عَلَيْهِمْ وَلَا ٱلضَّآلِّينَ
ኢማም ቡኻርይ : መጽሐፍ 65, ሐዲስ 4475
አቢ ሁረይራህ”ረ.ዐ.” እንደተረከው የአላህ መልእክተኛ”ﷺ” አሉ፦ “ኢማሙ፦ “ያልተቆጣህባቸውን እና ያልተሳሳቱትንም ሰዎች መንገድ ምራን” ባለ ጊዜ አሚን በሉ፤ عَنْ أَبِي هُرَيْرَةَ ـ رضى الله عنه ـ أَنَّ رَسُولَ اللَّهِ صلى الله عليه وسلم قَالَ ‏”‏ إِذَا قَالَ الإِمَامُአላህ ‏{‏غَيْرِ الْمَغْضُوبِ عَلَيْهِمْ وَلاَ الضَّالِّينَ‏}‏ فَقُولُوا آمِينَ‏.

“አሚን” آمين‌‎ ማለት ተስማምቻለው “ይሁን” “ይደረግ” ማለት ነው፤ አላህ ሆይ! ” ያልተቆጣህባቸውን እና ያልተሳሳቱትንም ሰዎች መንገድ ምራን፤ አሚን።

ከወንድም ወሒድ ዑመር
https://tttttt.me/Wahidcom

ወሰላሙ አለይኩም
አልተበረዘምን?

በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ በጣም አዛኛ በሆነው፡፡

መግቢያ
ሚሽነሪዎች አምላካችን አላህ በተከበረው ቃሉ ስለራሱ በሶስተኛ መደብ “የአላህ ቃላት መለወጥ የላትም” ብሎ የሚናገረው ንግግር ለቀድሞቹ መጽሐፍት ላለመበረዝ ማስረጃ ነው ብለው መሪ ሙግት ሲያቀርቡ ለጊዜው የሚያስኬድ ቢመስልም አበሳና አሳር ውስጥ እራሳቸውን እያስገቡ መሆኑ እሙን ነው፤ ምክንያቱም የቀድሞ መጽሐፍት ለመለወጣቸው በዋዛ ፈዛዛ ሊታዩ ያማይቻሉ አንቀፆች ስላሉ፤ ለምሳሌ፦”የአላህን ቃል የሚሰሙና ከዚያም ከተረዱት በኋላ እነርሱ እያወቁ “”የሚለውጡት” ሲኾኑ” ይላልና፤ ይህንን መረጃ ሲያገኙ ደግሞ እንደ ግጭትና ተቃርኖ ለማየት ይሞክራሉ፤ እኛ የምንለው ሙሾና ፌሽታ አብረው አይሔዱም ነው፤ ግራም ነፈሰ ቀኝ ሲጀመር “መለወጥ” የሚለው ቃል ተመሳሳይ ቃል ቢኖረው እንኳን ተመሳሳይ ሀሳብና ትርጉም አለው ማለት አይደለም፤ የአንድን ቃል አማራጭ ትርጒም የሚወስነው ቃሉ የሚገኝበት ዐረፍተ ነገር ወይም ዐውድ እንደ ሆነ ቅቡል ነው፤ ቃሉ ሳይሆን ቃሉ የወከለው ሐሳብ መታየት ያለበት።
ሲቀጥል የቁርአን ቅኝት የሆነው የአረብኛው ቃል “ተህሪፍ” تحريف, እና “ተብዲል” تَبْدِيل የአማርኛችን ጥበት ሁለቱንም “መለወጥ” ይበለው እንጂ ስሜቱ አንድ አይነት አይደለም፤ ይህንን ለመረዳት ጉባኤ ሆነ ሱባኤ አያስፈልግም ወደ ቁርአኑ ዘው ብሎ መግባት ብቻ ነው፦
ነጥብ አንድ
“ተህሪፍ”
“ተህሪፍ” تحريف, ማለት “ብርዘት” ማለት ሲሆን በመለወጥ የሚደረግ ብርዘት ሲሆን ይህ ጉዳይ አላህ በቃሉ ይነግረናል፦
2:75 ከነሱ የኾኑ ጭፍሮች “የአላህን ቃል የሚሰሙና ከዚያም ከተረዱት በኋላ እነርሱ እያወቁ “የሚለውጡት” يُحَرِّفُونَهُ ሲኾኑ ለናንተ ማመናቸውን ትከጅላላችሁን?
4:46 ከነዚያ ይሁዳውያን ከሆኑት ሰዎች “ንግግሮችን” ከሥፍራዎቹ “የሚለውጡ” يُحَرِّفُونَ አሉ፤
5:13 ቃልኪዳናቸውንም በማፍረሳቸው ረገምናቸው፤ ልቦቻቸውንም ደረቆች አደረግን፤ “ቃላትን” ከቦታዎቻቸው “ይለውጣሉ” يُحَرِّفُونَ ።

የመጸሐፉ ሰዎች አይሁድና ክርስቲያኖች ቃሉን የለወጡት የአላህ ቃልን ከሰው ቃል ጋር በመቀላቀል መጨመርና የአላህ ቃል በመደበቅ አፖክራፋ አድርጎ መቀነስ ነው፦
3:71 የመጸሐፉ ሰዎች ሆይ! “እዉነቱን በዉሸት” ለምን *ትቀላቅላላችሁ*? “እዉነቱንም” እናንተ የምታወቁ ስትሆኑ ለምን *ትደብቃላችሁ*?

“እውነት” የተባለው ከአላህ የወረደው ኪታብ፦
34:48 ፦ጌታዬ “እውነትን” ያወርዳል፤ ሩቅ የኾኑትን ሚስጢሮች ሁሉ ዐዋቂ ነው በላቸው።

“ውሸት” የተባለው ደግሞ መጽሐፉን በእጆቻቸው ፅፈው «ይህ ከአላህ ዘንድ ነው» ብለው የቀጠፉት ጭማሬ ነው፦
2:79 ለነዚያም መጽሐፉን በእጆቻቸው ለሚጽፉና ከዚያም በርሱ ጥቂትን ዋጋ ሊገዙበት «ይህ ከአላህ ዘንድ ነው» ለሚሉ ወዮላቸው፡፡ ለነርሱም ከዚያ እጆቻቸው ከጻፉት ወዮላቸው፡፡ ለነሱም ከዚያ ከሚያፈሩት ኃጢኣት ወዮላቸው፡፡

የነቢያችን ቅርብ ባልደረባ ኢብኑ ዓባስ”ረ.አ.” የሱረቱል በቀራ 2:79 አንቀጽ ሲፈስረው፦
ኢማም ቡሃሪ ቅጽ 3, መጽሃፍ 48, ቁጥር 850:
ኢብኑ አባስ ሲናገር፦ ሙስሊሞች ሆይ ለምን የመጽሐፉ ሰዎችን ትጠይቃላችሁ? በተመሳሳይ መጽሐፋችሁ ከአላህ ዘንድ ለነቢዩ የተወረደው ወቅታቂ ንግግርና የምትቀሩት እያለ? መጽሐፋ አልተበረዘምን? አላህ ለእናንተ የመጽሐፉ ሰዎች በእጆቻቸው በርዘው «ይህ ከአላህ ዘንድ ነው» እንደሚሉ አውርዷል።
حَدَّثَنَا يَحْيَى بْنُ بُكَيْرٍ، حَدَّثَنَا اللَّيْثُ، عَنْ يُونُسَ، عَنِ ابْنِ شِهَابٍ، عَنْ عُبَيْدِ اللَّهِ بْنِ عَبْدِ اللَّهِ بْنِ عُتْبَةَ، عَنِ ابْنِ عَبَّاسٍ ـ رضى الله عنهما ـ قَالَ يَا مَعْشَرَ الْمُسْلِمِينَ، كَيْفَ تَسْأَلُونَ أَهْلَ الْكِتَابِ، وَكِتَابُكُمُ الَّذِي أُنْزِلَ عَلَى نَبِيِّهِ صلى الله عليه وسلم أَحْدَثُ الأَخْبَارِ بِاللَّهِ، تَقْرَءُونَهُ لَمْ يُشَبْ، وَقَدْ حَدَّثَكُمُ اللَّهُ أَنَّ أَهْلَ الْكِتَابِ بَدَّلُوا مَا كَتَبَ اللَّهُ وَغَيَّرُوا بِأَيْدِيهِمُ الْكِتَابَ، فَقَالُوا هُوَ مِنْ عِنْدِ اللَّهِ، لِيَشْتَرُوا بِهِ ثَمَنًا قَلِيلاً أَفَلاَ يَنْهَاكُمْ مَا جَاءَكُمْ مِنَ الْعِلْمِ عَنْ مُسَاءَلَتِهِمْ، وَلاَ وَاللَّهِ مَا رَأَيْنَا مِنْهُمْ رَجُلاً قَطُّ يَسْأَلُكُمْ عَنِ الَّذِي أُنْزِلَ عَلَيْكُمْ. 
ነጥብ ሁለት
“ተብዲል”
“ተህሪፍ” تحريف, ማለት ቃልና መልዕክትን መለወጥ መሆኑን አይተን ነበር፤ “ተብዲል” تَبْدِيل ማለት ደግሞ “ማስቀየር” ነው፤ ተብዲል የንግግርን ሃሳብ፣ የውሳኔ ቃል እና የተስፋ ቃል ማስቀየርን ያመለክታል፤ አላህ የተናገረውን የውሳኔ ቃል አሊያም የትንቢትና የተስፋ ቃል ማንም ማስቆም አሊያም ማስቀረት እንደማይችል አላህ በቃሉ ይናገራል፦
6:115 “”የጌታህም ቃላት እውነተኛና ትክክለኛ ስትኾን “ተፈጸመች”፡፡ ለቃላቱ ለዋጭ የለም” لَا مُبَدِّلَ፡፡ እርሱም ሰሚው ዐዋቂው ነው፡፡
10:64 ለእነሱ በቅርቢቱ ሕይወትም በመጨረሻይቱም “ብስራት” አላቸው፤ “”የአላህ ቃላት “መለወጥ የላትም*لَا تَبْدِيلَ ፤ ይህ እርሱ ታላቅ ዕድል ነው፡፡
6:34 ከበፊትህም መልክተኞች በእርግጥ ተስተባበሉ፡፡ በተስተባበሉበትም ነገርና በተሰቃዩት ላይ እርዳታችን እስከመጣላቸው ድረስ ታገሱ፡፡ “”የአላህንም ንግግሮች *ለዋጭ የለም*وَلَا مُبَدَِّ፡፡

በተለይ “ተፈጸመች” እና “ብስራት” የሚሉት ቃላት የሚበሰርን እና የሚፈጸም ቃልን እንጂ በቀድሞ መጽሐፍት የተናገረውን መልእክት አያመለክትም፣ ኢማም ጦበራኒ ለሱረቱል አንአም 6፡115 የሰጡት ማብራሪያ እንዲህ ይላል፦
‹‹ለቃላቱ ለዋጭ የለም የሚለው ቃል አላህ በእርሱ መጽሀፍ ውስጥ ጉዳዩ ይከሰታል ብሎ ለመተግበሩ የሰጠው ቃል በጊዜው ከመተግበር ማንም አያግደውም እሱ እነደተናገረው ይፈጸማል ማለት ነው››
ኢማም ቁርጡቢም ተመሳሳይ ሀሳብ ያዘለ ማብራሪያቸውን እንዲህ ሲሉ ይገልጻል፦
‹‹ አልራሚኒ እንዳስተላለፉት አቡ ቀታዳ እንዲህ ይላሉ፡-ለኣላህ ፍርድ ምንም ለዋጭ የለውም የመጽሀፉ ሰዎች እንዳደረጉት ቃላቱን አንድ ሰው እንኳ ቢቀይረው የአላህ እውነተኛ ቃል ግን ከመፈጸም ወደ ኋላ አይልም የተለወጠው ቃል የሚፈጸመውን ቃል መለወጥ አይችልም፡፡››

ይህ የውሳኔ ቃል “ከሊማቱል-ከውኒያህ” ሲባል “ከሊማቱ አሽ-ሸርዒያህ” ደግሜ ወሕይ ነው፤  እንደው ሙግቱን ጠበብ ለማድረግ “ለቃላቱ ለዋጭ የለም” የሚለው ሃረግ መልእክቱን ነው ብንል እንኳን “ለቃላቱ ለዋጭ የለም” የሚለው የቀድሞ መጽሐፍትን ሳይሆን ቁርአንን ብቻና ብቻ ነው አራት ነጥብ። ምክንያት ከተባለ ማስረጀው ይኸው፦

18:27 ከጌታህም መጽሐፍ ወደ አንተ የተወረደውን አንብብ፤ “ለቃላቶቹ ለዋጭ የላቸውም” لَا مُبَدِّلَ፤

“ኢለይከ” إِلَيْكَ “ወደ አንተ” የሚል ነጠላ ተውላጠ-ስም ነቢያችንን ብቻ የሚያመለክት ሲሆን ወደ እርሳቸው የተወረደው የተስፋ ቃላት ለማመልከት ደግሞ “ኢለይ” إِلَيْ “ወደ” በሚል መስተዋድድ ተጠፍንጓል፣ ወደ ነብያችን ደግሞ የወረደው ቁርአን ብቻ ነው።
ተህሪፍ እና ተብዲል በመንስኤ ሆነ በውጤት ሁለት ለየቅል የሆኑ ቃላት እና እሳቦት ናቸውና የተነሳችሁበት ስሁት የሆነ ሙግት ስህተትና ግድፈት ነው ብዬ ስል ምፀታዊ ተምኔት ሳይሆን እርምት እና ትምህርት እንድትወስዱበት ነው። አይ ሌሎችንም መጽሐፍት ያመለክታል የሚል ተሟጋች ካለ ያቀረብነውን ሙግት የሚያስተባብልበት የአውድ፣ የቋንቋ፣ የሰዋስው ሙግት ጠቅሶና አጣቅሶ ማቅረብ ይጠበቅበታል። ስለዚህ “የአላህ ቃል መለወጥ የላትም” የሚለው ሃረግ የቀድሞ መጽሐፍት ላለመለወጣቸው ማስረጃ ሊሆን አይችልም።

ከወንድም ወሒድ ዑመር
https://tttttt.me/Wahidcom

ወሰላሙ አለይኩም
የቁርኣን አሻሻር

በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው።

2፥106 *ከአንቀጽ ብንለውጥ ወይም እርሷን ብናስረሳህ ከእርሷ የሚበልጥን ወይም ብጤዋን እናመጣለን*፤ አላህ በነገሩ ሁሉ ላይ ቻይ መኾኑን አታውቅምን? مَا نَنسَخْ مِنْ آيَةٍ أَوْ نُنسِهَا نَأْتِ بِخَيْرٍ مِّنْهَا أَوْ مِثْلِهَا ۗ أَلَمْ تَعْلَمْ أَنَّ اللَّهَ عَلَىٰ كُلِّ شَيْءٍ قَدِيرٌ

በሥነ-ጽሑፍ ጥናት "ተሕሪፍ" تَحريف ማለት "ብርዘት"corruption" ማለት ሲሆን አንድ ጽሑፍን የሚበርዘው "በራዥ" ደግሞ "ሙተሐሪፍ" تَدْعُونَ ይባላል፤ ቁርኣን የአላህ ንግግር ነው፤ በእርሱ ንግግር ላይ ጂብሪል፣ ነብያችን"ﷺ" ሶሐባዎች፣ ታቢኢይዎች፣ አትባኡ ታቢኢይዎች በእርሱ ንግግር ላይ የጨመሩት ወይም የቀነሱት አንዳችም ንግግር የለም። ቁርኣን የመጨረሻው ግህደተ-መለኮት ነው። ከነብያችን"ﷺ" በኃላ የሚመጣ ነቢይ፣ የሚወርድ ወሕይ፣ የሚላክ መልእክተኛ ስለሌለ ይህንን ቁርኣን አላህ ካወረደው በኃላ ፍጡራን እንዳይጨምሩበትና እንዳይቀንሱበት የሚጠብቀው እራሱ የዓለማቱ ጌታ አላህ ነው፦
15፥9 *እኛ ቁርኣንን እኛው አወረድነው፡፡ እኛም ለእርሱ ጠባቂዎቹ ነን*፡፡ إِنَّا نَحْنُ نَزَّلْنَا ٱلذِّكْرَ وَإِنَّا لَهُۥ لَحَٰفِظُونَ
41፥42 *ከኋላውም ከፊቱም ውሸት አይመጣበትም፤ ጥበበኛ ምስጉን ከኾነው ጌታ የተወረደ ነው*፡፡ لَّا يَأْتِيهِ ٱلْبَٰطِلُ مِنۢ بَيْنِ يَدَيْهِ وَلَا مِنْ خَلْفِهِۦ ۖ تَنزِيلٌۭ مِّنْ حَكِيمٍ حَمِيدٍۢ

ይህንን ከተረዳን ዘንድ በቁርኣን "ነሥኽ" የሚባል እሳቤ አለ፤ “ነሥኽ” نسخ ማለት “ሽረት”abrogation” ማለት ሲሆን ይህም ሽረት ሁለት ክፍል አለው፤ አንደኛው ክፍል “ናሢኽ” ناسخ ማለትም “ሻሪ አንቀጽ”Abrogator verse” ሲሆን ሁለተኛው “መንሡኽ” منسوخ ማለትም “ተሻሪ አንቀጽ”Abrogated verse” ነው፦
2፥106 *ከአንቀጽ ብንለውጥ ወይም እርሷን ብናስረሳህ ከእርሷ የሚበልጥን ወይም ብጤዋን እናመጣለን*፤ አላህ በነገሩ ሁሉ ላይ ቻይ መኾኑን አታውቅምን? مَا نَنسَخْ مِنْ آيَةٍ أَوْ نُنسِهَا نَأْتِ بِخَيْرٍ مِّنْهَا أَوْ مِثْلِهَا ۗ أَلَمْ تَعْلَمْ أَنَّ اللَّهَ عَلَىٰ كُلِّ شَيْءٍ قَدِيرٌ
16፥101 *በአንቀጽም ስፍራ አንቀጽን በለወጥን ጊዜ አላህም የሚያወርደውን ዐዋቂ ነው*፡፡ «አንተ ቀጣፊ እንጂ ሌላ አይደለህም» ይላሉ፡፡ በእውነቱ አብዛኞቻቸው አያውቁም፡፡ وَإِذَا بَدَّلْنَا آيَةً مَّكَانَ آيَةٍ ۙ وَاللَّهُ أَعْلَمُ بِمَا يُنَزِّلُ قَالُوا إِنَّمَا أَنتَ مُفْتَرٍ ۚ بَلْ أَكْثَرُهُمْ لَا يَعْلَمُونَ

ይህንን እሳቤ ምሁራን "አን-ናሲኽ ወል መንሱኽ" الناسخ والمنسوخ ይሉታል፤ ይህ ሽረት በቁርኣን ሕጉን ታሳቢና ዋቢ ያረደገ ሲሆን የማህበረሰቡትን ዕድገትና የአስተሳሰብ ደረጃ፣ የጊዜውን ቅድመ-ተከተል እና ዘመነ-መግቦት”dispensation” ያማከለ ነው፣ ይህም “ተከታታይ ግህደተ-መለኮትን”progressive revelation” እሴት እና ግብአት ነው፤ አላህ የሕጉን አንቀጽ በሌላ የሕግ አንቀጽ የመሻሩ ሂደት በሁለት ይከፈላል፤ ይህንን ነጥብ በነጥብ በአጽንዖትና በአንክሮት ማየት ይቻላል፦
ነጥብ አንድ
"ነሥኹል ሑክም"
“ሑክም” حُكْم ማለት "ሕግ" ማለት ሲሆን "መትን” مَتن ማለት ደግሞ "ጥሬ-ቃል" ማለት ነው፤ "ነሥኹል ሑክም" ማለት "ሕግ" ተነሥኾ ግን "ጥሬ-ቃል" የማይነሠኽበት ማለት ነው፤ ለምሳሌ ተሻሪ አንቀጽ ይህ አንቀጽ ነው፦
2፥240 *እነዚያ ከእናንተ ውስጥ የሚሞቱ ሚስቶችንም የሚተዉ፤ ለሚስቶቻቸው ከቤታቸው የማይወጡ ሲኾኑ ዓመት ድረስ መጠቀምን ኑዛዜን ይናዘዙ፡፡ በፈቃዳቸው ቢወጡም በሕግ ከታወቀው ነገር በነፍሶቻቸው በሠሩት በእናንተ በሟቹ ዘመዶች ላይ ኃጢኣት የለባችሁም አላህም አሸናፊ ጥበበኛ ነው*፡፡ وَالَّذِينَ يُتَوَفَّوْنَ مِنكُمْ وَيَذَرُونَ أَزْوَاجًا وَصِيَّةً لِّأَزْوَاجِهِم مَّتَاعًا إِلَى الْحَوْلِ غَيْرَ إِخْرَاجٍ ۚ فَإِنْ خَرَجْنَ فَلَا جُنَاحَ عَلَيْكُمْ فِي مَا فَعَلْنَ فِي أَنفُسِهِنَّ مِن مَّعْرُوفٍ ۗ وَاللَّهُ عَزِيزٌ حَكِيمٌ
ኢማም ቡኻርይ መጽሐፍ 65, ሐዲስ 4530
ኢብኑ አዝ-ዙበይር እንደተረከው፦ *"እኔም ለዑስማን ኢብኑ ዐፋል"ረ.ዐ."፦ " እነዚያ ከእናንተ ውስጥ የሚሞቱ ሚስቶችንም የሚተዉ.."2፥240 ስለዚህ ይህ አንቀጽ በሌላ አንቀጽ ተሽሯል፤ ለምንድን ነው የምትጽፈው ወይም የምትተወው? ዑስማንም፦ "የወንድሜ ልጅ ሆይ! እኔ ከቦታው ምንም ነገር አለውጥም" አለው*። قَالَ ابْنُ الزُّبَيْرِ قُلْتُ لِعُثْمَانَ بْنِ عَفَّانَ ‏{‏وَالَّذِينَ يُتَوَفَّوْنَ مِنْكُمْ وَيَذَرُونَ أَزْوَاجًا‏}‏ قَالَ قَدْ نَسَخَتْهَا الآيَةُ الأُخْرَى فَلِمَ تَكْتُبُهَا أَوْ تَدَعُهَا قَالَ يَا ابْنَ أَخِي، لاَ أُغَيِّرُ شَيْئًا مِنْهُ مِنْ مَكَانِهِ‏.‏

አላህ መትኑን ከሚነሥኸው ውጪ ሰዎች የመነሠኽ ሥልጣን እንደሌላቸው ይህ ሐዲስ ያሳያል፤ "ኢብዳል" إبـدال ማለት "ምትክ"replacement" ማለት ሲሆን የተተካበት ሻሪ አንቀጽ ደግሞ ይህ አንቀጽ ነው፦
4፥12 *ለእናንተም ሚስቶቻችሁ ከተዉት ንብረት ለእነርሱ ልጅ ባይኖራቸው ግማሹ አላችሁ፡፡ ለእነሱም ልጅ ቢኖራቸው ከተዉት ሀብት ከአራት አንድ አላችሁ፡፡ ይህም በእርሷ ከሚናዘዙባት ኑዛዜ ወይም ከዕዳ በኋላ ነው፡፡ ለናንተም ልጅ ባይኖራችሁ ከተዋችሁት ንብረት ለእነርሱ ለሚስቶች ከአራት አንድ አላቸው፡፡ ለእናንተም ልጅ ቢኖራችሁ ከተዋችሁት ንብረት ለእነርሱ ከስምንት አንድ አላቸው ይህም በርሷ ከምትናዘዙባት ኑዛዜ ወይም ከዕዳ በኋላ ነው፡፡ ወላጅም ልጅም የሌለው በጎን ወራሾች የሚወርስ ወንድ ወይም ሴት ቢገኝ ለእርሱም ለሟቹ ወንድም ወይም እኅት (ከእናቱ በኩል ብቻ የኾነ ቢኖር ከሁለቱ ለያንዳንዳቸው ከስድስት አንድ አላቸው፡፡ ከዚህም ከአንድ የበዙ ቢኾኑ እነርሱ በሲሶው ተጋሪዎች ናቸው፡፡ ይህም ወራሾችን የማይጎዳ ኾኖ በእርሷ ከሚናዘዙባት ኑዛዜ ወይም ከዕዳ በኋላ ነው፡፡ ከአላህም የኾነን ኑዛዜ ያዛችኋል፡፡ አላህም ዐዋቂ ቻይ ነው*፡፡ وَلَكُمْ نِصْفُ مَا تَرَكَ أَزْوَاجُكُمْ إِن لَّمْ يَكُن لَّهُنَّ وَلَدٌ ۚ فَإِن كَانَ لَهُنَّ وَلَدٌ فَلَكُمُ الرُّبُعُ مِمَّا تَرَكْنَ ۚ مِن بَعْدِ وَصِيَّةٍ يُوصِينَ بِهَا أَوْ دَيْنٍ ۚ وَلَهُنَّ الرُّبُعُ مِمَّا تَرَكْتُمْ إِن لَّمْ يَكُن لَّكُمْ وَلَدٌ ۚ فَإِن كَانَ لَكُمْ وَلَدٌ فَلَهُنَّ الثُّمُنُ مِمَّا تَرَكْتُم ۚ مِّن بَعْدِ وَصِيَّةٍ تُوصُونَ بِهَا أَوْ دَيْنٍ ۗ وَإِن كَانَ رَجُلٌ يُورَثُ كَلَالَةً أَوِ امْرَأَةٌ وَلَهُ أَخٌ أَوْ أُخْتٌ فَلِكُلِّ وَاحِدٍ مِّنْهُمَا السُّدُسُ ۚ فَإِن كَانُوا أَكْثَرَ مِن ذَٰلِكَ فَهُمْ شُرَكَاءُ فِي الثُّلُثِ ۚ مِن بَعْدِ وَصِيَّةٍ يُوصَىٰ بِهَا أَوْ دَيْنٍ غَيْرَ مُضَارٍّ ۚ وَصِيَّةً مِّنَ اللَّهِ ۗ وَاللَّهُ عَلِيمٌ حَلِيمٌ

"በአንቀጽም ስፍራ አንቀጽን በለወጥን ጊዜ አላህም የሚያወርደውን ዐዋቂ ነው" የሚለው ይህንን እሳቤ ዋቢ ያደረገ ነው፦
16፥101 *በአንቀጽም ስፍራ አንቀጽን በለወጥን ጊዜ አላህም የሚያወርደውን ዐዋቂ ነው*፡፡ «አንተ ቀጣፊ እንጂ ሌላ አይደለህም» ይላሉ፡፡ በእውነቱ አብዛኞቻቸው አያውቁም፡፡ وَإِذَا بَدَّلْنَا آيَةً مَّكَانَ آيَةٍ ۙ وَاللَّهُ أَعْلَمُ بِمَا يُنَزِّلُ قَالُوا إِنَّمَا أَنتَ مُفْتَرٍ ۚ بَلْ أَكْثَرُهُمْ لَا يَعْلَمُونَ
ነጥብ ሁለት
"ነሥኹል መትን"
"ነሥኹል መትን" ማለት "ሕግ" ተነሥኾ ግን "ጥሬ-ቃል" የሚነሠኽበት ማለት ነው፤ "ኢብታል" إبـتال ማለት "ማንሳት"nullification" ማለት ሲሆን አምላካችን አላህ ጥሬ ቃሉ በማንሳት ይነሥኸዋል፦
2፥106 *ከአንቀጽ ብንለውጥ ወይም እርሷን ብናስረሳህ ከእርሷ የሚበልጥን ወይም ብጤዋን እናመጣለን*፤ አላህ በነገሩ ሁሉ ላይ ቻይ መኾኑን አታውቅምን? مَا نَنسَخْ مِنْ آيَةٍ أَوْ نُنسِهَا نَأْتِ بِخَيْرٍ مِّنْهَا أَوْ مِثْلِهَا ۗ أَلَمْ تَعْلَمْ أَنَّ اللَّهَ عَلَىٰ كُلِّ شَيْءٍ قَدِيرٌ
87፥6 *ቁርኣንን በእርግጥ እናስነብብሃለን፤ አትረሳምም*፡፡ سَنُقْرِئُكَ فَلَا تَنسَىٰ
87፥7 *አላህ ከሻው በስተቀር*፡፡ እርሱ ግልጹን የሚሸሸገውንም ሁሉ ያውቃልና፡፡ إِلَّا مَا شَاءَ اللَّهُ ۚ إِنَّهُ يَعْلَمُ الْجَهْرَ وَمَا يَخْفَىٰ

ነብያችን"ﷺ" ከሚወርድላቸው አንቀጽ ምንም አይረሱም አላህ ከሻው በስተቀር፤ “አላህ ከሻው በስተቀር” ማለት አላህ አንድን አንቀጽ በማስረሳት በሌላ አንቀጽ ከመለወጥ በስተቀር ማለት ነው፤ "ብናስረሳህ" የሚለው ሃይለ-ቃል ይሰመርበት፤ ለዛ ነው የተነሰኹ አናቅጽ ሐዲስ ላይ የምናገኘው፤ ለምሳሌ አንድ ናሙና ማየት ይቻላል፦
ኢማም ሙስሊም መጽሐፍ 5, ሐዲስ 264:
አል-በረራዒ ኢብኑ ዓዚብ እንደተረከው፦ *“በሶላቶች እና በአስር ሶላት ላይ ተጠባበቁ” ይህ አንቀፅ ወርዶ ነበር፤ አላህ እስከሻው ድረስ እንቀራው ነበር፤ ከዚያም *አላህ ነሠኸውና፦ “በሶላቶች በመካከለኛይቱም ሶላት ላይ ተጠባበቁ፡፡ ታዛዦች ኾናችሁም ለአላህ ቁሙ” የሚለውን አንቀፅ አወረደ*። عَنِ الْبَرَاءِ بْنِ عَازِبٍ، قَالَ نَزَلَتْ هَذِهِ الآيَةُ حَافِظُوا عَلَى الصَّلَوَاتِ وَصَلاَةِ الْعَصْرِ ‏.‏ فَقَرَأْنَاهَا مَا شَاءَ اللَّهُ ثُمَّ نَسَخَهَا اللَّهُ فَنَزَلَتْ ‏{‏ حَافِظُوا عَلَى الصَّلَوَاتِ وَالصَّلاَةِ الْوُسْطَى‏}‏

ሶሐባዎችም መትኑ የተነሠኸውን አንቀጾች አላህ እስከ ነሠኸው ድረስ በቂራኣታቸው ውስጥ አያካትቱም ነበር፦
ኢማም ቡኻርይ መጽሐፍ 65, ሐዲስ 4481
ኢብኑ ዐባሥ እንደተረከው፦ *"ዑመር"ረ.ዐ." አለ፦ " የእኛ ምርጥ ቃሪእ ኡበይ ነው፤ የእኛ ምርጥ ዳኛ ዐሊይ ነው፤ ሆኖም ግን የዑበይን አንዳንድ ንግግር እንተወው ነበር፤ እርሱም፦ "ከአላህ መልእክተኛ"ﷺ" ከምሰማው ምንም አልተውኩም፤ አላህ እንዳለው ከሚረሳው በቀር፦ "ከአንቀጽ ብንለውጥ ወይም እርሷን ብናስረሳህ"*። عَنِ ابْنِ عَبَّاسٍ، قَالَ قَالَ عُمَرُ ـ رضى الله عنه ـ أَقْرَؤُنَا أُبَىٌّ، وَأَقْضَانَا عَلِيٌّ، وَإِنَّا لَنَدَعُ مِنْ قَوْلِ أُبَىٍّ، وَذَاكَ أَنَّ أُبَيًّا يَقُولُ لاَ أَدَعُ شَيْئًا سَمِعْتُهُ مِنْ رَسُولِ اللَّهِ صلى الله عليه وسلم وَقَدْ قَالَ اللَّهُ تَعَالَى ‏{‏مَا نَنْسَخْ مِنْ آيَةٍ أَوْ نَنْسَأْهَا‏}‏

አምላካችን አላህ አንቀጹን ሽሮ ከሚያስረሳው በቀር ሰዎች በግላቸው የቁርኣንን አንቀጽ የቀነሱበት የጨመሩበት የለም። ለነብያችን"ﷺ" የሚወርደው ቁርኣን ብቻ ሳይሆን ሐዲሱል ቁድስ እና ሐዲሱል ነበውይም ጭምር ነው፤ ነብያችን"ﷺ" በዐቂዳህ እና በፊቅህ ነጥብ ላይ የሚናገሩት ወሕይ ነው፦
53፥4 *እርሱ ንግግሩ የሚወርረድ ራእይ እንጅ ሌላ አይደለም*፡፡ إِنْ هُوَ إِلَّا وَحْيٌ يُوحَىٰ
ከወረዱት አንዱ ልክ እንደ ሱረቱል በቀራህ እርዝመት እና ክብደት ያለው ምእራፍ ነበር፦
ኢማም ሙስሊም መጽሐፍ 12, ሐዲስ 156
አቡ ሐርብ ኢብኑ አቢይ እንደተረከው፦ *"አል-ኢሥወድ ከአባቱ አግኝቶ እንዲህ አለ፦ አቡ ሙሳ አል-ዐሻሪይ የበስሯ ቃሪእዎችን ልኮ አስጠራ፤ እነርሱም መጡ፤ በቁጥር ሦስት መቶ ይሆናሉ፤ ቁርኣንን ቀሩ*፤ ከዚያም እንዲህ አለ፦ *"እናንተ ከበስሯ ነዋሪዎች በላጮች ናችሁ፤ ምክንያቱም ከእነርሱ መካከል ቃሪእዎች ናችሁ፤ ስለዚህ መቅራታችሁን ቀጥሉ፤ ነገር ግን ይህንን እወቁ! ከእናንተ በፊት ለረጅም ጊዜ በመቅራታችሁ ልባቸው እንደ ደነደነባቸው ልቦቻችሁ እንዳያደነድነው። አንድ ምእራፍ በርዝመቱና በክብደቱ ከሱረቱል በራትን(በቀራህ) የሚያክል እናነብ ነበር። ነገር ግን "የአዳም ልጅ በወርቅ የተሞላ ሸለቆ ቢኖረው ኖሮ፣ እንደ እርሱ ዓይነት ሌላ ሁለት ሸለቆ ለመያዝ ይፈልጋል፤ የአዳም ልጅም ሆዱን የሚሞላለት አፈር እንጂ ሌላ ነገር አይደለም" ከሚለው በቀር እኔ ረስቼዋለሁ*። عَنْ أَبِي حَرْبِ بْنِ أَبِي، الأَسْوَدِ عَنْ أَبِيهِ، قَالَ بَعَثَ أَبُو مُوسَى الأَشْعَرِيُّ إِلَى قُرَّاءِ أَهْلِ الْبَصْرَةِ فَدَخَلَ عَلَيْهِ ثَلاَثُمِائَةِ رَجُلٍ قَدْ قَرَءُوا الْقُرْآنَ فَقَالَ أَنْتُمْ خِيَارُ أَهْلِ الْبَصْرَةِ وَقُرَّاؤُهُمْ فَاتْلُوهُ وَلاَ يَطُولَنَّ عَلَيْكُمُ الأَمَدُ فَتَقْسُوَ قُلُوبُكُمْ كَمَا قَسَتْ قُلُوبُ مَنْ كَانَ قَبْلَكُمْ وَإِنَّا كُنَّا نَقْرَأُ سُورَةً كُنَّا نُشَبِّهُهَا فِي الطُّولِ وَالشِّدَّةِ بِبَرَاءَةَ فَأُنْسِيتُهَا غَيْرَ أَنِّي قَدْ حَفِظْتُ مِنْهَا لَوْ كَانَ لاِبْنِ آدَمَ وَادِيَانِ مِنْ مَالٍ لاَبْتَغَى وَادِيًا ثَالِثًا وَلاَ يَمْلأُ جَوْفَ ابْنِ آدَمَ إِلاَّ التُّرَابُ ‏

የአደም ልጆች በወርቅ ሸለቆ የሚለው የነብያችን"ﷺ" ንግግር እንጂ የአላህ ንግግር አይደለም፦
ኢማም ቡኻርይ መጽሐፍ 81, ሐዲስ 28
አነሥ ኢብኑ ማሊክ እንደተረከው፦ *"የአላህ መልእክተኛ"ﷺ" አሉ፦ "የአዳም ልጅ በወርቅ የተሞላ ሸለቆ ቢኖረው ኖሮ፣ እንደ እርሱ ዓይነት ሌላ ሁለት ሸለቆ ለመያዝ ይፈልጋል፤ የአዳም ልጅም አፉን የሚሞላለት አፈር እንጂ ሌላ ነገር አይደለም፤ አላህ ወደ እርሱ የሚመለሱት ይቅር ይላል*። قَالَ أَخْبَرَنِي أَنَسُ بْنُ مَالِكٍ، أَنَّ رَسُولَ اللَّهِ صلى الله عليه وسلم قَالَ ‏ "‏ لَوْ أَنَّ لاِبْنِ آدَمَ وَادِيًا مِنْ ذَهَبٍ أَحَبَّ أَنْ يَكُونَ لَهُ وَادِيَانِ، وَلَنْ يَمْلأَ فَاهُ إِلاَّ التُّرَابُ، وَيَتُوبُ اللَّهُ عَلَى مَنْ تَابَ ‏"‌‏.‏

ይህ ንግግር ነብያችን"ﷺ" በተናገሩበት ጊዜ ኢብኑ ዐባሥ"ረ.ዐ." "ከቁርኣን ይሁን አይሁን ዐላወቀም ነበር" ብሏል፦
ኢማም ቡኻርይ መጽሐፍ 81, ሐዲስ 26
ኢብኑ ዐባሥ እንደተረከው፦ *የአላህ መልእክተኛ"ﷺ" እንዲህ ሲሉ ሰምቻለው፦ "የአዳም ልጅ በወርቅ የተሞላ ሸለቆ ቢኖረው ኖሮ፣ እንደ እርሱ ዓይነት ሌላ ሁለት ሸለቆ ለመያዝ ይፈልጋል፤ የአዳም ልጅም በዐይኑ ፊት አፉን የሚሞላለት አፈር እንጂ ሌላ ነገር አይደለም፤ አላህ ወደ እርሱ የሚመለሱት ይቅር ይላል" ኢብኑ ዐባስም፦ "ይህ ንግግር ከቁርኣን ይሁን አይሁን ዐላውቅም ነበር" አለ*። حَدَّثَنِي مُحَمَّدٌ، أَخْبَرَنَا مَخْلَدٌ، أَخْبَرَنَا ابْنُ جُرَيْجٍ، قَالَ سَمِعْتُ عَطَاءً، يَقُولُ سَمِعْتُ ابْنَ عَبَّاسٍ، يَقُولُ سَمِعْتُ رَسُولَ اللَّهِ صلى الله عليه وسلم يَقُولُ ‏ "‏ لَوْ أَنَّ لاِبْنِ آدَمَ مِثْلَ وَادٍ مَالاً لأَحَبَّ أَنَّ لَهُ إِلَيْهِ مِثْلَهُ، وَلاَ يَمْلأُ عَيْنَ ابْنِ آدَمَ إِلاَّ التُّرَابُ، وَيَتُوبُ اللَّهُ عَلَى مَنْ تَابَ ‏"‌‏.‏ قَالَ ابْنُ عَبَّاسٍ فَلاَ أَدْرِي مِنَ الْقُرْآنِ هُوَ أَمْ لاَ‏.

ያ ማለት ከቁርኣን አይደለም ማለት ነው፤ ዑበይ"ረ.ዐ." ይህ ንግግር ሱረቱል ተካሱር የቁርኣን ሱራህ እስከሚወርድ ድረስ ከቁርኣን ሱራህ ነው ብለን እናስብ ነበር" ብሏል፤ ያ ማለት የቁርኣን ሱራህ አይደለም ማለት ነው፦
ኢማም ቡኻርይ መጽሐፍ 81, ሐዲስ 27
ኢብኑ ሠዕድ እንደተረከው፦ *"ኢብኑ አዝ-ዙበይር በመካህ ሚንበር ላይ ሆኖ ኹጥባህ ሲሰጥ ሰማሁት፤ እንዲህም አለ፦ "እናንተ ሰዎች ሆይ! ነብዩ"ﷺ"፦ "የአዳም ልጅ በወርቅ የተሞላ ሸለቆ ቢኖረው፣ እንደ እርሱ ዓይነት ሌላ ሁለተኛ ሸለቆ ለመያዝ ይፈልጋል፤ ሁለተኛ ቢሰጠው ሌላ ሦስተኛ ሸለቆ ለመያዝ ይፈልጋል፤ የአዳም ልጅም ሆዱን የሚሞላለት አፈር እንጂ ሌላ ነገር አይደለም፤ አላህ ወደ እርሱ የሚመለሱት ይቅር ይላል" እያሉ ሲናገሩ ነበር። ዑበይም አለ፦ "ይህ ንግግር "በብዛት መፎካከር ጌታችሁን ከመገዛት አዘነጋችሁ"102፥1 የሚለው ሱራህ እስከሚወርድ ድረስ ከቁርኣን ነው ብለን እናስብ ነበር*። حَدَّثَنَا أَبُو نُعَيْمٍ، حَدَّثَنَا عَبْدُ الرَّحْمَنِ بْنُ سُلَيْمَانَ بْنِ الْغَسِيلِ، عَنْ عَبَّاسِ بْنِ سَهْلِ بْنِ سَعْدٍ، قَالَ سَمِعْتُ ابْنَ الزُّبَيْرِ، عَلَى الْمِنْبَرِ بِمَكَّةَ فِي خُطْبَتِهِ يَقُولُ يَا أَيُّهَا النَّاسُ إِنَّ النَّبِيَّ صلى الله عليه وسلم كَانَ يَقُولُ ‏ "‏ لَوْ أَنَّ ابْنَ آدَمَ أُعْطِيَ وَادِيًا مَلأً مِنْ ذَهَبٍ أَحَبَّ إِلَيْهِ ثَانِيًا، وَلَوْ أُعْطِيَ ثَانِيًا أَحَبَّ إِلَيْهِ ثَالِثًا، وَلاَ يَسُدُّ جَوْفَ ابْنِ آدَمَ إِلاَّ التُّرَابُ، وَيَتُوبُ اللَّهُ عَلَى مَنْ تَابَ ‏"‌‏.‏
Ubbay ibn Ka'ab said "We considered this as a saying from the Qur'an untill the Sura፦ 'The mutual rivalry for piling up of worldly things diverts you..' (102.1) was revealed."

ስለ ነሥኽ ያለው እሳቤ በግርድፉና በሌጣው ይህንን ይመስላል።

ከወንድም ወሒድ ዑመር
https://tttttt.me/Wahidcom

ወሰላሙ አለይኩም
ሥነ-ፅንስ

ክፍል አንድ

በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው።

31:34 አላህ የሰዓቲቱ እውቀት እርሱ ዘንድ ብቻ ነው፤ ዝናምንም ያወርዳል፤ #በማሕፀኖችም #ውስጥ #ያለን #ሁሉ #ያውቃል

መግቢያ
ሥነ-ፅንስ ጥናት ኢምብሪዮሎጂይ”Embryology” ሲባል “ኢምብሮ” ἔμβρυον “ያልተወለደ” እና “ሎጂአ” λογία, “ጥናት” ከሚል ሁለት የግሪክ ቃል የተዋቀረ ነው፤ ይህንን ፅንስ እናቱ ማህፀን ውስጥ በሚፈልገው መልኩ የሚቀርፀው አንዱ አምላክ አላህ ነው፦
3:6 እርሱ ያ “በማሕፀኖች” ዉሰጥ እንደሚሻ አድርጎ “የሚቀርጻችሁ” ነዉ፤ ከእርሱ በስተቀር ሌላ አምላክ የለም፤

ይህ ፅንስ ማህፀን ውስጥ እንዴት እንደሚፈጠር ሙሉ እውቀት ያለው የዓለማቱ ጌታ አላህ ብቻ ነው፦
31:34 አላህ የሰዓቲቱ ዕውቀት እርሱ ዘንድ ብቻ ነው፤ ዝናምንም ያወርዳል፤ “በማሕፀኖችም ውስጥ ያለን ሁሉ ያውቃል”፤
53:32 ከምድር በፈጠራችሁ ጊዜ እናንተም በእናቶቻችሁ “ማሕፀኖች” ውስጥ ሽሎች በሆናችሁ ጊዜ እርሱ በእናንተ ሁኔታ “አዋቂ” ነው።
13:8 አላህ ሴት ሁሉ የምታረግዘውን ያውቃል፤ “ማሕፀኖችም የሚያጐድሉትን የሚጨምሩትንም፥ ያውቃል”፤ ነገሩም ሁሉ እርሱ ዘንድ በልክ የተወሰነ ነው።

በማሕፀኖችም ውስጥ ያለውን ሁሉ የሚያውቀ አምላክ የሥነ-ፅንስ እውቀት ወደፊት እንደሚያሳየና እንደሚያሳውቀን ለማመልከት፦ “በራሶቻችሁ ውስጥ ያሉትም ታምራት ወደፊት ያሳያችኋል፤ ታውቁታላችሁ” በማለት ቃል ገብቷል፦
41፥53 እርሱም ቁርአን እውነት መሆኑ ለነርሱ እስከሚገለጽላቸው ድረስ፣ በአጽናፎቹ ውስጥ እና #በራሶቻቸውም ውስጥ ያሉትን #ታምራቶቻችንን በእርግጥ #እናሳያቸዋለን፤ ጌታህም እርሱ በነገሩ ሁሉ ላይ አዋቂ መሆኑ አይበቃቸውምን?
27:93 ምስጋና ለአላህ ነው፤ #ታምራቶቹን #ወደፊት #ያሳያችኋል#ታውቁታላችሁ በላቸው።

አላህ ይህንን እውቀት በራሳችን አካላት ከማሳየቱ በፊት በቁርአን አንድ ሽል በማህፀን ውስጥ እንዴት የተለያየ ደረጃዎችን”stages” እንደሚያሳልፍ በተከበረ ቃሉ ይነግረናል፦
23:12 በእርግጥም ሰውን ከነጠረ ጭቃ ፈጠርነው፤ ከዚያም በተጠበቀ መርጊያ ውስጥ “የፍትወት ጠብታ” النُّطْفَةَ አደረግነው፤ ከዚያም ጠብታዋን “የረጋ ደም” عَلَقَةً አድርገን ፈጠርን፤ የረጋውንም ደም “ቁራጭ ሥጋ” مُضْغَةً አድርገን ፈጠርን፤ ቁራጯንም ሥጋ “አጥንቶች” عِظَامًا አድርገን ፈጠርን፤ አጥንቶቹንም ሥጋን لَحْمًا አለበስናቸው፤ ከዚያም “ሌላ ፍጥረትን” خَلْقًا آخَرَ አድርገን “አስገኘነው” أَنْشَأْنَاهُ፤ ከሰዓሊዎችም ሁሉ በላጭ የሆነው አላህ ላቀ፡፡
ደረጃ አንድ
“ኑጥፋህ”
የአንድ ሽል በማህፀን ያለው የመጀመሪያ ደረጃ “ኑጥፋህ” نُّطْفَة ነው፤ “ኑጥፋህ” ማለት “የፍትወት ጠብታ” ሲሆን ይህም የተባእት ዘር ህዋስ” sperm cell” እና የእንሥት እንቁላል ህዋስ”egg cells” ነው፤ እነዚህ የፍትወት ጠብጣዎች በሥነ-ፅንስ ምሁራን “ፍናፍንት”hermaphroditic” በመባል ይታወቃሉ፤ አላህ ስለዚህ የፍትወት ጠብታ በተከበረ ቃሉ እንዲህ ይለናል፦
53:45-46 እርሱም ሁለቱን ዓይነቶች ወንድና ሴትን ፈጠረ። “ከፍትወት ጠብታ” نُطْفَةٍ በማኅፀን ውስጥ በምትፈስ ጊዜ፤
80:19 “ከፍትወት ጠብታ” نُطْفَةٍ ፈጠረው መጠነውም።
16:4 ሰውን “ከፍትወት ጠብታ” نُطْفَةٍ ፈጠረው፤ ከዚያም እርሱ ወዲያውኑ ትንሣኤን በመካድ ግልጽ ተከራካሪ ይሆናል።
35:11 አላህም ከአፈር፣ ከዚያም “ከፍትወት ጠብታ” نُطْفَةٍ ፈጠራችሁ፤
36:77 ሰውየው እኛ “ከፍቶት ጠብታ” የፈጠርነው መሆናችን አላወቀምን?
40:67 እርሱ ያ ከአፈር፣ ከዚያም “ከፍትወት ጠብታ” نُطْفَةٍ ፣ ከዚያም ከረጋ ደም፣ የፈጠራችሁ ነው።

የሴት ልጅ ማህፀን ዘር በሚዘራበት “እርሻ” ሲመሰል፤ የእንሥት ማህፀን ላይ ላይ የሚገናኘው የተባእት ዘር ህዋስ ደግሞ ገበሬ እርሻ ላይ በሚዘራው “ዘር” ተመስሏል፤ ምክንያቱም አንድ ገበሬ እርሻው ላይ ከዘራ በኃላ ዘሩ ዳብሮ ለፍሬ የሚበቃው በእርሻ ውስጥ እንደሆነ ሁሉ አንድ ተባእትም አንድ እንስት ማህፀን ውስጥ ዘሩን ተገናኝ ሆኖ ከዘራ በኃላ ሂደቱ ሁሉ ተከናውኖ ለፍሬ የሚበቃው ማህፀን ውስጥ ነው፦
2:223 ሴቶቻችሁ ለእናንተ “እርሻ” ናቸው፤ እርሻችሁንም በፈለጋችሁት ኹኔታ ድረሱ፤ ለነፍሶቻችሁም መልካም ሥራን አስቀድሙ፤ አላህንም ፍሩ፤ እናንተም “”ተገናኝዎቹ”” መኾናችሁን ዕወቁ፡፡
56:57-59 እኛ ፈጠርናችሁ፤ አታምኑምን? “በማኅፀኖች “የምታፈሱትን አያችሁትን”? እናንተ ትፈጥሩታላችሁን? ወይስ እኛ ፈጣሪዎቹ ነን።
56:63-64 “የምትዘሩትንም አያችሁን”? እናንተ ታበቅሉታላችሁን? ወይስ እኛ አብቃዮቹ ነን?
32:7-8 ያ የፈጠረውን ነገር ሁሉ ያሳመረው፣ የሰውንም ፍጥረት ከጭቃ የጀመረው፥ ነው፤ ከዚያም “ዘሮቹን”፣ ከተጣለለ “ከደካማ ውሃ” ያደረገ፣ ነው።
77:20-21 “ከደካማ ውሃ” አልፈጠርናችሁምን? “በተጠበቀ መርጊያ በማሕፀን ውስጥም” አደረግነው፤

አላህ በማህፀን ያለውን የመጀመሪያ ደረጃ ሰው እንዴት የተባእት ዘር ህዋስ እና የእንሥት እንቁላል ህዋስ ፍናፍንት ሆኖ ተቀላቅሎ እንደሚፈጠር ቀድሞውኑ በማሕፀኖችም ውስጥ ያለንውን ሁሉ አዋቂ አምላክ መሆኑን ለእኛ ለማሳየት “አምሻጅ” أَمْشَاج “ቅልቅል”mixture” በማለት ይናገራል፦
76:2 እኛ ሰዉን በሕግ ግዳጅ የምንሞክረዉ ስንሆን፥ “ቅልቅሎች” أَمْشَاجٍ ከሆኑ “የፍትወት ጠብታ” نُطْفَةٍ ፈጠርነዉ፤ ሰሚ ተመልካችም አደረግነዉ። ኢንሻላህ ይቀጥላል…..

ከወንድም ወሒድ ዑመር
https://tttttt.me/Wahidcom

ወሰላሙ አለይኩም
ሥነ-ፅንስ

ክፍል ሁለት

በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው።

31:34 አላህ የሰዓቲቱ እውቀት እርሱ ዘንድ ብቻ ነው፤ ዝናምንም ያወርዳል፤ #በማሕፀኖችም #ውስጥ #ያለን #ሁሉ #ያውቃል

“ደረጃ ሁለት”
“ዐለቃ”
“ዐለቃ” عَلَقَة አንስታይ ሲሆን “ዐለቅ” عَلَق ደግሞ ተባእታይ ነው፤ ትርጉሙም “አልቅት”leech” ወይም “የረጋ ደም”blood-clot” ማለት ነው፤ ይህን የፅንስ ሁለተኛው ደረጃ ከሚታይ አልቅት ከሚባል የባህር ትል”insect” እና ከረጋ ደም ጋር ስለሚመሳሰል ነው፤ ወደዚህ ሂደት ለመምጣት በህዋሳት ውህደት ወቅት “ክሮሞሶም”Chromosomes” ከአንዱ ለጋሽ ወላጅ ወደሌላው ለጋሽ ወላጅ ይተላለፋል፤ እያንዳንዱ ተሣታፊ ህዋስ የለጋሾችን ግማሽ ክሮሞሶም ይይዛል፤ የአባት ክሮሞሶም ግማሽ 23% የእናት ክሮሞሶም 23% ተገናኛተው 46% ይዋሃዳሉ ማለት ነው፤ ተወራሽ የዘር ምልክቶች በምፃረ-ቃል “ዲ-ኤን-ኤ”(DNA) ወይም በዝርዝር “ዲኦክሲሪቦ ኒውክሊክ አሲድ”(deoxyribonucleic acid) በመባል በሚታወቀው በክሮሞሶሞች ውስጥ የሚገኝ ንጥረ-ነገር ውስጥ ሰፍረው ይገኛሉ። ክሮሞሶሞች “በጥንድ” ሆነው በሚገኙበት ጊዜ “ዳይፕሎይድ”(diploid) ይባላሉ፤ ክሮሞሶሞች በነጠላ ግዜ “ሃፕሎይድ”(haploid) ይባላሉ፤ በዚህ ሂደት አንድ ሴል የነበረው የወንድ የዘር ህዋስ ከሴት የእንቁላል ህዋስ ጋር ከተዋሐደ በኃላ 2, 4, 8, 16, 32, 64 እያለ በቲሪልየን ብዜት በ 21 ቀን የረጋ ደም”blood-clot” የሚለው ደረጃ ይጀምራል፤ ይህንን ደረጃ አምላካችን አላህ እንዲህ ይለናል፦
22:5 እላንተ ሰዎች ሆይ! ከመቀስቀስ፣ በመጠራጠር ዉስጥ እንደ ሆናችሁ አፈጣጠራችሁን ተመልከቱ፤ እኛም ከአፈር ፈጠርናችሁ ከዚያም ከፍቶት ጠብታ፣ ከዚያም “ከረጋ ደም” عَلَقَةٍ ፣ ከዚያም ከቁራጭ፣ ስጋ ፍጥረትዋ ሙሉ ከኾነችና ሙሉ ካልሆነች ችሎታችንን ለእናንተ ልንገልጽላችሁ ፈጠርናችሁ፤
40:67 እርሱ ያ ከአፈር፣ ከዚያም ከፍትወት ጠብታ፣ ከዚያም “ከረጋ ደም” عَلَقَةٍ፣ የፈጠራችሁ ነው።
96:1-2 አንብብ በዚያ ሁሉን በፈጠረው ጌታህ ስም፤ ሰውን “ከረጋ ደም” عَلَقٍ በፈጠረው ጌታህ ስም።

ከፍትወት ህዋስ ወደ የረጋ ደም የሚሄድበት ሂደት እና ደረጃ ለማመልከት “ሱምመ” ثُمَّ “ከዚያም” የሚል መስተፃምር ይጠቀማል፤ ከዚህ ከተቀላቀለው የፍትወት ህዋስ ሁለት ዓይነቶችን ወንድና ሴትን ይመጣል፦
75፥36-39 ሰው ስድ ሆኖ መትተውን ይጠረጥራልን? የሚፈስስ ከሆነ የፍትወት ጠብታ አልነበረምን? “ከዚያም” ثُمَّ “የረጋ ደም” عَلَقَةً ሆነ፤ ሰው አድርጎ ፈጠረውም፤ አስተካከለውም። “ከእርሱም” ሁለት ዓይነቶችን “ወንድና ሴትን” አደረገ።

“የዘረ-መል ጥናት”(Genetic) እንደሚያስተነትነው የተባእት ክሮሞሶም ‘XY’ ሲሆን የእንስት ክሮሞሶም ደግሞ ‘XX’ ነው፤ ከወንድ ‘Y” መጥቶ ከሴት ‘X’ ከመጣ ሽሉ የአባቱን ፆታ በመያዝ ወንድ ይሆናል፤ ከወንድ ‘X” መጥቶ ከሴት ‘X’ ከመጣ ሽሉ የእናቱን ፆታ በመያዝ ሴት ይሆናል፤ ልብ አድርግ የወንድ ክሮሞሶም ‘XY’ ሲሆን የሴት ክሮሞሶም ደግሞ ‘XX’ መሆኑ ማለቴ ነው፤ የዘረ-መል ጥናት ይህንን ከማወቁ በፊት አላህ ለመልእክተኛው ይህንን የሩቅ ነገር ሚስጥር አሳውቋል፦
ኢማም ቡሃሪ መጽሐፍ 60 , ቁጥር 4 :
وَأَمَّا الشَّبَهُ فِي الْوَلَدِ فَإِنَّ الرَّجُلَ إِذَا غَشِيَ الْمَرْأَةَ فَسَبَقَهَا مَاؤُهُ كَانَ الشَّبَهُ لَهُ، وَإِذَا سَبَقَ مَاؤُهَا كَانَ الشَّبَهُ لَهَا ‏”‌‏.‏
የአላህ መልክተኛ አሉ፦ የልጆች ከወላጆቻቸው መመሳሰል እንዲህ ነው፤ ተባእት ከሚስቱ ጋር ተራክቦ ሲያደርግ የእርሱ ከተለቀቀ ህፃኑ እርሱን ይመስላል፤ የእንስት ከተለቀቀ ደግሞ ህፃኗ እርሷን ትመስላለች።

እውነት ነው፤ አላህም ከወንድ ክሮሞሶም ‘XY’ ወንድን እና ከሴት ክሮሞሶም ‘XX’ ደግሞ ሴትን በምድር ላይ ፈጥሮ የበተነ ነው፤ ይህም የሁለቱ አስተዋእፆ የአባት ክሮሞሶም ግማሽ 23% የእናት ክሮሞሶም 23% ተገናኛተው 46% ሲሆኑ ነው፦
4:1 እላንተ ሰዎች ሆይ! ያንን ከአንዲት ነፍስ(ከአዳም) የፈጠራችሁን፣ ከእርስዋም መቀናጆዋን(ሔዋንን) የፈጠረውን፣ #ከእነርሱም ብዙ “ወንዶችን” እና “ሴቶችን” የበተነውን፣ ጌታችሁን ፍሩ።
49፥13 እናንተ ሰዎች ሆይ! እኛ “ከወንድ እና ከሴት ፈጠርናችሁ”፡፡ ኢንሻላህ ይቀጥላል…..

ከወንድም ወሒድ ዑመር
https://tttttt.me/Wahidcom

ወሰላሙ አለይኩም
ሱረቱል ፋቲሓህ

በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው።

15፥87 *ከሚደጋገሙ የኾኑን ሰባትን እና ታላቁንም ቁርኣን በእርግጥ ሰጠንህ*፡፡ وَلَقَدْ آتَيْنَاكَ سَبْعًا مِّنَ الْمَثَانِي وَالْقُرْآنَ الْعَظِيمَ

አምላካችን አላህ “ሙርሲል” مُرْسِل ማለትም “ላኪ” ነው፤ ነብያችን”ﷺ” ደግሞ “ረሱል” رِسَالَة ማለትም “መልክተኛው” ናቸው፤ እንዲሁ ቁርኣን የአላህ “ሪሳላ” رِسَالَ ማለትም “መልእክት” ነው።
የመልእክቱ “ሙአለፍ” مؤلف ማለትም “አመንጪ”author” አምላካችን አላህ ሲሆን፤ ነብያችን”ﷺ” ደግሞ የመልእክቱ “ሙራሲል” مراسل ማለት “አስተላላፊ”reporter” ናቸው፤ አምላካችን አላህ ለነብያችን”ﷺ”፦ “ቁል” قُلْ ማለትም “በል” በሚል ትዕዛዛዊ ግስ ያዛቸዋል፦
112፥1 *በል «እርሱ አላህ አንድ ነው*፡፡ قُلْ هُوَ اللَّهُ أَحَدٌ
13፥30 እንደዚሁ ከበፊትዋ ብዙ ሕዝቦች በእርግጥ ያለፉ ወደኾነችው ሕዝብ እነርሱ በአልረሕማን የሚክዱ ሲኾኑ ያንን *ወደ አንተ ያወረድነውን ቁርኣን በእነርሱ ላይ ታነብላቸው ዘንድ ላክንህ፡፡ «እርሱ አልረሕማን ጌታዬ ነው፡፡ ከእርሱ ሌላ አምላክ የለም፡፡ በእርሱ ላይ ተጠጋሁ፡፡ መመለሻዬም ወደ እርሱ ብቻ ነው» በላቸው*፡፡ كَذَٰلِكَ أَرْسَلْنَاكَ فِي أُمَّةٍ قَدْ خَلَتْ مِن قَبْلِهَا أُمَمٌ لِّتَتْلُوَ عَلَيْهِمُ الَّذِي أَوْحَيْنَا إِلَيْكَ وَهُمْ يَكْفُرُونَ بِالرَّحْمَـٰنِ ۚ قُلْ هُوَ رَبِّي لَا إِلَـٰهَ إِلَّا هُوَ عَلَيْهِ تَوَكَّلْتُ وَإِلَيْهِ مَتَابِ

“ወደ አንተ ያወረድነውን ቁርኣን በእነርሱ ላይ ታነብላቸው ዘንድ ላክንህ” የሚለው ሃይለ-ቃል ቁርኣንን አውራጅና ነብያችንን”ﷺ” ላኪው አላህ እራሱ “በል” ማለቱን እንረዳለን፤ በመቀጠል እዛው አንቀጽ ላይ “ቁል” قُلْ ብሎ መናገሩ በራሱ “በል” የሚለው ማንነት አላህ መሆኑን ቁልጭ አድርጎ ያሳያል፤ በተጨማሪም “በልን” ወደ ነብያችን”ﷺ” የሚጥለው እራሱ እንደሆነ ይናገራል፦
73፥5 *እኛ በአንተ ላይ ከባድ ቃልን እንጥላለንና*፡፡ إِنَّا سَنُلْقِي عَلَيْكَ قَوْلًا ثَقِيلًا

እዚህ አንቀጽ ላይ “ቃል” ለሚለው የተቀመው ቃላት “ቀውል” قَوْل ሲሆን “ቁል” قُلْ ከሚል ትዕዛዛዊ ግስ የመጣ ነው፤ ስለዚህ “በል” እያለ የሚያስነብባቸው እራሱ አላህ ነው፤ ሱረቱል ፋቲሓህ የሚደጋገሙ ሰባት አንቀጾች ናት፤ ምክንያቱም ሱረቱል ፋቲሓህ ሰባት አናቅጽ አላት፤ በተጨማሪም ነብያችን”ﷺ” ሱረቱል ፋቲሓህ የሚደጋገሙ ሰባት አንቀጾች ናት ብለው ነግረውናል፦
15፥87 *ከሚደጋገሙ የኾኑን ሰባትን እና ታላቁንም ቁርኣን በእርግጥ ሰጠንህ*፡፡ وَلَقَدْ آتَيْنَاكَ سَبْعًا مِّنَ الْمَثَانِي وَالْقُرْآنَ الْعَظِيمَ
ኢማም ቡኻርይ: መጽሐፍ 66, ሐዲስ 28
አቢ ሠዒድ ኢብኑ ሙዐላ እንደተረከው *ሶላት ላይ ሆኜ ነብዩ”ﷺ” ጠሩኝ፤ ነገር ጥሪያቸውን አልመለስኩላቸውም፤ በኃላ ላይ፦ “የአላህ መልእክተኛ ሆይ! ሶላት ላይ ነበርኩኝ” አልኩኝ፤ እሳቸውም፦ አላህ፦ “(መልእክተኛው) በጠራችሁ ጊዜ ለአላህ እና ለመልክተኛው ታዘዙ”8፥24 አላለምን? ከዚያም፦ “በቁርኣን ውስጥ ታላቂቱን ሱራህ ላስተምርህን? እርሷም፦ “ምስጋና ለአላህ ይገባው የዓለማት ጌታ ለኾነው የምትለዋ የሚደጋገሙ የሆኑ ሰባት ሱረቱል ፋቲሐህን እና ታላቁ ቁርኣንን ተሰጠኝ”*። عَنْ أَبِي سَعِيدِ بْنِ الْمُعَلَّى، قَالَ كُنْتُ أُصَلِّي فَدَعَانِي النَّبِيُّ صلى الله عليه وسلم فَلَمْ أُجِبْهُ قُلْتُ يَا رَسُولَ اللَّهِ إِنِّي كُنْتُ أُصَلِّي‏.‏ قَالَ ‏”‏ أَلَمْ يَقُلِ اللَّهُ ‏{‏اسْتَجِيبُوا لِلَّهِ وَلِلرَّسُولِ إِذَا دَعَاكُمْ‏}‏ ثُمَّ قَالَ أَلاَ أُعَلِّمُكَ أَعْظَمَ سُورَةٍ فِي الْقُرْآنِ قَبْلَ أَنْ تَخْرُجَ مِنَ الْمَسْجِدِ ‏”‌‏.‏ فَأَخَذَ بِيَدِي فَلَمَّا أَرَدْنَا أَنْ نَخْرُجَ قُلْتُ يَا رَسُولَ اللَّهِ إِنَّكَ قُلْتَ لأُعَلِّمَنَّكَ أَعْظَمَ سُورَةٍ مِنَ الْقُرْآنِ‏.‏ قَالَ ‏”‌‏{‏الْحَمْدُ لِلَّهِ رَبِّ الْعَالَمِينَ‏}‏ هِيَ السَّبْعُ الْمَثَانِي وَالْقُرْآنُ الْعَظِيمُ الَّذِي أُوتِيتُهُ ‏”‌‏.‏
ጃምዒ አት-ተርሚዚ መጽሐፍ 47, ሐዲስ 3415
አቢ ሁረይራህ”ረ.ዐ” እንደተረከው፦ “የአላህ መልእክተኛ”ﷺ” እንዲህ አሉ፦ *አል-ሐምዱሊሏህ የቁርኣን እናት፣ የመጽሐፉ እናት እና ሰባት የተደጋገሙ ናት*። عَنِ ابْنِ أَبِي ذِئْبٍ، عَنِ الْمَقْبُرِيِّ، عَنْ أَبِي هُرَيْرَةَ، قَالَ قَالَ رَسُولُ اللَّهِ صلى الله عليه وسلم ‏ “‏ الْحَمْدُ لِلَّهِ أُمُّ الْقُرْآنِ وَأُمُّ الْكِتَابِ وَالسَّبْعُ الْمَثَانِي ‏”
ሱረቱል ፋቲሓህ ላይ ከሚሽነሪዎች የሚነሳው ጥያቄ “ቀጥተኛውን መንገድ ምራን“ የሚለው የአላህ ንግግር ከሆነ አላህ ማንን ነው ምራን የሚለው? የሚል ነው፤ መልሱ "ቀጥተኛውን መንገድ ምራን" እኛ እንድንል ለእኛ ያለው ነው፤ ይህንም "ቁል" قُلْ የሚል ትዕዛዛዊ ግስ "ሙስተቲር" ْمُسْتَتِر ማለትም "ህቡዕ-ግስ"headen verb" ሆኖ የመጣ ነው፦
1፥6 *ቀጥተኛውን መንገድ ምራን*፡፡ اهْدِنَا الصِّرَاطَ الْمُسْتَقِيمَ

"ኢህዲና" اهْدِنَا ማለትም "ምራን" ብዙ ቁጥር ሲሆን ይህ ባለቤት ግስ አማኞችን ያመለክታል፤ ተሳቢው ግስ ደግሞ መሪውን ያመለክታል፤ ስለዚህ "ቁሉ" قُلُوا የሚለው ሙስተቱር ሆኖ የመጣ ነው፤ ለምሳሌ በሱረቱል በቀራህ 2፥187 ላይ "ከተበ" كَتَبَ ማለትም "ጻፈ" የሚለውን ወደ ኢንግሊሽ ሲቀየር "He wrote" ነው፣ "He" ደግሞ ወደ ዐረቢኛ "ሁወ" هُوَ ማለትም "እርሱ" ነው፤ "ሁወ" هُوَ የሚለው "ከተበ" كَتَبَ ላይ ሚስተቲር ሆኖ የመጣ ነው፤ "ቁል" ወይም "ቁሉ" ተደብቀው በሙስተቲር የሚመጡበት ብዙ ቦታ ነው፦
11፥2 *አላህን እንጂ ሌላን አታምልኩ፤ እኔ ለእናንተ ከእርሱ የተላክሁ አስጠንቃቂ እና አብሳሪ ነኝ*፡፡ أَلَّا تَعْبُدُوا إِلَّا اللَّهَ ۚ إِنَّنِي لَكُم مِّنْهُ نَذِيرٌ وَبَشِيرٌ

እዚህ አንቀጽ ላይ "ቁል" የሚለው የለም፤ ያ ማለት "አስጠንቃቂ እና አብሳሪ ነኝ" የሚለው አላህ ነው ማለት ቂልነት ነው፤ ምክንያቱም "ሚንሁ" مِّنْهُ የሚል ሃይለ-ቃል አለ፤ "ሚን" مِّن ማለት "ከ" ሲሆን መስተዋድድ ነው፤ በሚን ላይ "ሁ" هُ ማለት "እርሱ" የሚል ተሳቢ አለ፤ "እርሱ" የተባለው ላኪ አላህ ነው "አስጠንቃቂ እና አብሳሪ ነኝ" የሚሉት ደግሞ የተላኩት ነብያችን"ﷺ" ናቸው፦
35፥24 *እኛ አብሳሪ እና አስጠንቃቂ አድርገን በእውነቱ ላክንህ*፡፡ إِنَّا أَرْسَلْنَاكَ بِالْحَقِّ بَشِيرًا وَنَذِيرًا
7፥188 *እኔ ለሚያምኑ ሕዝቦች አስጠንቃቂ እና አብሳሪ እንጂ ሌላ አይደለሁም» በላቸው*፡፡ قُل لَّا أَمْلِكُ لِنَفْسِي نَفْعًا وَلَا ضَرًّا إِلَّا مَا شَاءَ اللَّهُ ۚ وَلَوْ كُنتُ أَعْلَمُ الْغَيْبَ لَاسْتَكْثَرْتُ مِنَ الْخَيْرِ وَمَا مَسَّنِيَ السُّوءُ ۚ إِنْ أَنَا إِلَّا نَذِيرٌ وَبَشِيرٌ لِّقَوْمٍ يُؤْمِنُونَ
"በል" ሳይል በአንድ አንቀጽ ላይ በውስጠ ታዋቂነት "እኔም በእናንተ ላይ ጠባቂ አይደለሁም" ይልና፤ ሌላ አንቀጽ ላይ "እኔም በእናንተ ላይ ጠባቂ አይደለሁም በል" የሚል ይጠቀማል፦
6፥104 *እኔም በእናንተ ላይ ጠባቂ አይደለሁም*፡፡ وَمَا أَنَا عَلَيْكُم بِحَفِيظٍ
6፥66 *በላቸው፡- «በእናንተ ላይ ጠባቂ አይደለሁም፡፡»* قُل لَّسْتُ عَلَيْكُم بِوَكِيلٍ

"በል" ሳይል በአንድ አንቀጽ ላይ በውስጠ ታዋቂነት "እኔም የሙስሊሞች መጀመሪያ ነኝ" ይልና፤ ሌላ አንቀጽ ላይ "እኔም የሙስሊሞች መጀመሪያ ነኝ በል" የሚል ይጠቀማል፦
6፥163 *«ለእርሱ ተጋሪ የለውም፡፡ በዚህም በማጥራት ታዘዝኩ፡፡ እኔም የሙስሊሞች መጀመሪያ ነኝ»*፡፡ لَا شَرِيكَ لَهُ ۖ وَبِذَٰلِكَ أُمِرْتُ وَأَنَا أَوَّلُ الْمُسْلِمِينَ
39፥11 *በል* «እኔ አላህን ሃይማኖትን ለርሱ ያጠራሁ ኾኜ እንድግገዛው ታዘዝኩ፡፡ قُلْ إِنِّي أُمِرْتُ أَنْ أَعْبُدَ اللَّهَ مُخْلِصًا لَّهُ الدِّينَ
39፥12 *«የሙስሊሞችም መጀመሪያ እንድኾን ታዘዝኩ፡፡»* وَأُمِرْتُ لِأَنْ أَكُونَ أَوَّلَ الْمُسْلِمِينَ

ይህንን ከተረዳን ሱረቱል ፋቲሓህ ላይ "አንተን" ብለው በሚሉት ላይ "በል" ሳይል ሌላ አንቀጽ ላይ "አንተ በል" የሚል ይጠቀማል፦
3፥26 *በል*፡- «የንግስና ባለቤት የኾንክ አላህ ሆይ! ለምትሻው ሰው ንግሥናን ትሰጣለህ፡፡ ከምትሻውም ሰው ንግሥናን ትገፍፋለህ፡፡ የምትሻውንም ሰው ታልቃለህ፡፡ የምትሻውንም ሰው ታዋርዳለህ፡፡ መልካም ነገር ሁሉ በእጅህ በችሎታህ ነው፤ *"አንተ"* በነገሩ ሁሉ ላይ ቻይ ነህና፡፡ قُلِ اللَّهُمَّ مَالِكَ الْمُلْكِ تُؤْتِي الْمُلْكَ مَن تَشَاءُ وَتَنزِعُ الْمُلْكَ مِمَّن تَشَاءُ وَتُعِزُّ مَن تَشَاءُ وَتُذِلُّ مَن تَشَاءُ ۖ بِيَدِكَ الْخَيْرُ ۖ إِنَّكَ عَلَىٰ كُلِّ شَيْءٍ قَدِيرٌ

በተጨማሪም ነብያችን"ﷺ" በሐዲስ ላይ ሱረቱል ፋቲሓን የሚለው የአላህ ባሪያ ወደ አላህ መሆኑን በግልጽ እና በማያሻማ መልኩ ነግረውናል፦
ኢማም ሙስሊም መጽሐፍ 4 ሐዲስ 41
አቢ ሁረይራ"ረ.ዐ" እንደተረከው *ነብዩ"ﷺ" አሉ፦ "የቁርአን እናት ሳያነብ የሰገደ ሰው ሶላቱ ጎዶሎ ነው"* አንድ ሰው ለአቢ ሁረይራ፦ "ከአሰጋጁ በኋላ ብንሆንም እንኳን"? አለው፤ እርሱም አለ፦ "ለራስህ አንብብ ምክንያቱም ነብዩ"ﷺ" እንዲህ ሲሉ ሰምቻለሁና፦ *"ኃያሉና የተከበረው አላህ እንዲህ ብሏል፦ "ሶላትን በእኔ እና በባሪያዬ መካከል ለሁለት ከፍየዋለሁ እናም ባሪያዬየጠየቀውን ያገኛል*፤ ባሪያው፦ *"ምስጋና ለአላህ ይገባውየዓለማት ጌታ ለኾነው" ሲል አላህ፦ "ባሪያዬአመሰገነኝ" ይላል*፤ ባሪያው፦ *"እጅግ በጣም ርኅሩህ በጣም አዛኝ" ሲልደግሞ አላህ፦ "ባሪያዬአሞገሰኝ’ ይላል*፤ ባሪያው፦ *"የፍርዱ ቀን ባለቤት ለኾነው" ሲል አላህ፦ ባሪያዬ አላቀኝ" ይላል*፤ ባሪያው፦ *"አንተን ብቻ እንግገዛለን፤ አንተንም ብቻ እርዳታን እንለምናለን" በሚል ግዜ አላህ፦ "ይህ በእኔ እና
በባሪያዬ መካከል ነው እናም ባሪያዬ የጠየቀውን ያገኛል" ይላል*፤ ባሪያው፦ *"ቀጥተኛውን መንገድ ምራን የእነዚያን በእነርሱ ላይበጎ የዋልክላቸውን በነሱ ላይያልተቆጣህባቸውንና ያልተሳሳቱትንም ሰዎች መንገድ ምራን" በሚል ግዜ ደግሞ አላህ፦ "ይህ ለባሪያዬ ነው፤ እናም ባሪያዬየጠየቀውን ያገኛል" ይላል*፡፡ عَنْ أَبِي هُرَيْرَةَ، عَنِ النَّبِيِّ صلى الله عليه وسلم قَالَ ‏"‏ مَنْ صَلَّى صَلاَةً لَمْ يَقْرَأْ فِيهَا بِأُمِّ الْقُرْآنِ فَهْىَ خِدَاجٌ - ثَلاَثًا - غَيْرُ تَمَامٍ ‏"‏ ‏.‏ فَقِيلَ لأَبِي هُرَيْرَةَ إِنَّا نَكُونُ وَرَاءَ الإِمَامِ ‏.‏ فَقَالَ اقْرَأْ بِهَا فِي نَفْسِكَ فَإِنِّي سَمِعْتُ رَسُولَ اللَّهِ صلى الله عليه وسلم يَقُولُ ‏"‏ قَالَ اللَّهُ تَعَالَى قَسَمْتُ الصَّلاَةَ بَيْنِي وَبَيْنَ عَبْدِي نِصْفَيْنِ وَلِعَبْدِي مَا سَأَلَ فَإِذَا قَالَ الْعَبْدُ ‏{‏ الْحَمْدُ لِلَّهِ رَبِّ الْعَالَمِينَ‏}‏ ‏.‏ قَالَ اللَّهُ تَعَالَى حَمِدَنِي عَبْدِي وَإِذَا قَالَ ‏{‏ الرَّحْمَنِ الرَّحِيمِ‏}‏ ‏.‏ قَالَ اللَّهُ تَعَالَى أَثْنَى عَلَىَّ عَبْدِي ‏.‏ وَإِذَا قَالَ ‏{‏ مَالِكِ يَوْمِ الدِّينِ‏}‏ ‏.‏ قَالَ مَجَّدَنِي عَبْدِي - وَقَالَ مَرَّةً فَوَّضَ إِلَىَّ عَبْدِي - فَإِذَا قَالَ ‏{‏ إِيَّاكَ نَعْبُدُ وَإِيَّاكَ نَسْتَعِينُ‏}‏ ‏.‏ قَالَ هَذَا بَيْنِي وَبَيْنَ عَبْدِي وَلِعَبْدِي مَا سَأَلَ ‏.‏ فَإِذَا قَالَ ‏{‏ اهْدِنَا الصِّرَاطَ الْمُسْتَقِيمَ * صِرَاطَ الَّذِينَ أَنْعَمْتَ عَلَيْهِمْ غَيْرِ الْمَغْضُوبِ عَلَيْهِمْ وَلاَ الضَّالِّينَ‏}‏ ‏.‏ قَالَ هَذَا لِعَبْدِي وَلِعَبْدِي مَا سَأَلَ ‏"‏ ‏.‏ قَالَ سُفْيَانُ حَدَّثَنِي بِهِ الْعَلاَءُ بْنُ عَبْدِ الرَّحْمَنِ بْنِ يَعْقُوبَ دَخَلْتُ عَلَيْهِ وَهُوَ مَرِيضٌ فِي بَيْتِهِ فَسَأَلْتُهُ أَنَا عَنْهُ ‏.‏

በዚህ መልኩ መረዳት ካልቻላችሁ አንድ ናሙና ከባይብል ላቅርብ፦ ዮሐንስ 20፥17 ኢየሱስም፦ ገና ወደ አባቴ አላረግሁምና አትንኪኝ፤ ነገር ግን ወደ ወንድሞቼ ሄደሽ፦ እኔ ወደ አባቴና ወደ አባታችሁ ወደ አምላኬና ወደ አምላካችሁ *ዓርጋለሁ ብለሽ ንገሪአቸው* አላት።

ወደ አምላኩ አራጊው ኢየሱስ ሆኖ ሳለ "ዓርጋለሁ ብለሽ ንገሪአቸው" ሲላት አራጊዋ መቅደላዊት ማርያም ሆና ነውን? አይ "ይላል" በይ ለማለት ተፈልጎ ነው ከተባለ "ይላል" የሚለውን የት አለ? በውስጠ-ታዋቂነት ይኖራል ከሆነ መልሱ እንግዲያውስ ሱረቱል ፋቲሐህንም በዚህ መልኩ መረዳት ይቻላል። ያለበለዚያ አራጊዋ መቅደላዊት ማርያም ትሆናለች።

ከወንድም ወሒድ ዑመር
https://tttttt.me/Wahidcom

ወሰላሙ አለይኩም