ወሒድ የዕቅበተ ኢሥላም መጣጥፍት"Wahid Articles of Islamic Apologetics"
58.3K subscribers
68 photos
69 videos
19 files
1.72K links
ዳዒ ወሒድ በኢሥላም እና በክርስትና መካከል ያለውን ልዩነት እና አንድነት በንጽጽር የሚያስቀምጥ ወንድም ነው። ለዚህም የቋንቋ፣ የሰዋስው፣ የዐውድ፣ የተዛማች እና የሥነ አመክንዮ ሙግት በማቅረብ የሚታወቅ ተሟጋች እና ጦማሪ ነው። ለሙግቱ ነጥብ በዋነኝነት የሚጠቀምባቸው ቋንቋ ዐማርኛ፣ ግዕዝ፣ እንግሊዝኛ፣ ዐረቢኛ፣ ዕብራይስጥ እና ግሪክ ናቸው። መልካም የንባብ፣ የጥናት፣ የማነጻጸር ጊዜ ይሁንልዎ!
Download Telegram
“ከትእዛዛችን ያልሆነ አንድ ነገር ቢፈጥር ተቀባይነት የለውም” የሚለው የነብያችን”ﷺ” ንግግር ይሰመርበት፤ ማንኛውም መመሪያ ቁርአን እና የነብያችን”ﷺ” ሐዲስ ላይ ይገኛል፤ አላህን የሚወድ መልእክተኛውን ይከተላል፤ አላህም፦ “መልክተኛውም የሰጣችሁን ማንኛውንም ነገር ያዙት፤ ከእርሱም የከለከላችሁን ነገር ተከልከሉ” ብሎናል፦
3፥31 *በላቸው፡- አላህን የምትወዱ እንደኾናችሁ “ተከተሉኝ*፤ አላህ ይወዳችኋልና፤ ኀጢኣቶቻችሁንም ለእናንተ ይምራልና፤ አላህም መሓሪ አዛኝ ነው” قُلْ إِن كُنتُمْ تُحِبُّونَ ٱللَّهَ فَٱتَّبِعُونِى يُحْبِبْكُمُ ٱللَّهُ وَيَغْفِرْ لَكُمْ ذُنُوبَكُمْ ۗ وَٱللَّهُ غَفُورٌ رَّحِيمٌ ፡፡
59፥7 *መልክተኛውም የሰጣችሁን ማንኛውንም ነገር ያዙት፡፡ ከእርሱም የከለከላችሁን ነገር ተከልከሉ*፡፡ አላህንም ፍሩ፡፡ አላህ ቅጣተ ብርቱ ነውና وَمَآ ءَاتَىٰكُمُ ٱلرَّسُولُ فَخُذُوهُ وَمَا نَهَىٰكُمْ عَنْهُ فَٱنتَهُوا۟ ۚ وَٱتَّقُوا۟ ٱللَّهَ ۖ إِنَّ ٱللَّهَ شَدِيدُ ٱلْعِقَابِ ፡፡

ጥሩ ቢድዓ ካለ የሌሎችን ነብያት ልደት ለምን አይከበርም? ለምሳሌ “ገና” የዒሳ ልደት አይከበርም? ነብያችን”ﷺ” ወሕይ የመጣላቸው ቀን፣ ያረፉበት ቀን ወዘተ እየተባለ ልክ እንደ ኦርቶዶክስ ሰላሳውም ቀን ለምን አይከበርም? ይህ ደግሞ ዲኑን ያባሻል። አይ ዝንባሌአችን ደስ ያለውን መልካም ነገር በዒባዳህ ላይ እናካትት ማለት ዲኑ ሙሉ ነው የሚለንን አምላካችን አላህን እየተቃረንን ነው፦
5፥3 *ዛሬ ሃይማኖታችሁን ለናንተ ሞላሁላችሁ*፡፡ ጸጋዬንም በእናንተ ላይ ፈጸምኩ፡፡ ለእናንተም ኢስላምን ከሃይማኖት በኩል ወደድኩ፡፡ الْيَوْمَ أَكْمَلْتُ لَكُمْ دِينَكُمْ وَأَتْمَمْتُ عَلَيْكُمْ نِعْمَتِي وَرَضِيتُ لَكُمُ الْإِسْلَامَ دِينًا

“ነፍስያ” نفسيه ማለትም “የራስ ዝንባሌ” ጌታችን የጠበቃት ካልሆነች በስተቀር በመጥፎ ነገር በእርግጥ አዛዥ ነው፤ ነፍስም ሁሉ በራሷ ላይ እንጅ ክፉን አትሠራም፦
12፥53 ነፍሴንም ከስሕተት አላጠራም፡፡ *ነፍስ ሁሉ ጌታዬ የጠበቃት ካልሆነች በስተቀር በመጥፎ ነገር በእርግጥ አዛዥ ናትና*፡፡ ጌታዬ በጣም መሓሪ አዛኝ ነው» አለ፡፡ وَمَا أُبَرِّئُ نَفْسِي ۚ إِنَّ النَّفْ

سَ لَأَمَّارَةٌ بِالسُّوءِ إِلَّا مَا رَحِمَ رَبِّي ۚ إِنَّ رَبِّي غَفُورٌ رَّحِيمٌ
6፥164 በላቸው እርሱ የሁሉ ጌታ ሲኾን ከአላህ በቀር ሌላን ጌታ እፈልጋለሁን *ነፍስም ሁሉ በራሷ ላይ እንጅ ክፉን አትሠራም*፡፡ قُلْ أَغَيْرَ ٱللَّهِ أَبْغِى رَبًّۭا وَهُوَ رَبُّ كُلِّ شَىْءٍۢ ۚ وَلَا تَكْسِبُ كُلُّ نَفْسٍ إِلَّا عَلَيْهَا

ቢድዓ፣ ኩርፍ፣ ሽርክ እና ኒፋቅ ምንጫቸው ዝንባሌ ነው፤ ብዙ ጊዜ ሰርጎ-ገብ የሆኑት ቡድንተኝነት፣ ጎጠኝነት፣ ጠርዘኝነት መነሻቸው ዝንባሌ ነው፤ አንድ ሙስሊም ነፍሱንም ከዝንባሌዋ የከለከለ ገነት እርሷ በእርግጥ መኖሪያው ናት፦
79፥40-41 በጌታው ፊት መቆምን የፈራ ሰውማ *ነፍሱንም ከዝንባሌዋ የከለከለ ገነት እርሷ በእርግጥ መኖሪያው ናት*፡፡ وَأَمَّا مَنْ خَافَ مَقَامَ رَبِّهِ وَنَهَى النَّفْسَ عَنِ الْهَوَىٰ فَإِنَّ الْجَنَّةَ هِيَ الْمَأْوَىٰ

አላህ ከነፍሲያ ከሚመጣ ዝንባሌ ጠብቆን፤ እርሱንና መልእክተኛው ባስቀመጡልን ሑክም የምንመራ ያድርገን አሚን።

ከወንድም ወሒድ ዑመር
https://tttttt.me/Wahidcom

ወሰላሙ አለይኩም
ሸዋል

በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው።

59፥7 *መልክተኛውም የሰጣችሁን ማንኛውንም ነገር ያዙት፡፡ ከእርሱም የከለከላችሁን ነገር ተከልከሉ*፡፡ አላህንም ፍሩ፡፡ አላህ ቅጣተ ብርቱ ነውና፡፡ وَمَا آتَاكُمُ الرَّسُولُ فَخُذُوهُ وَمَا نَهَاكُمْ عَنْهُ فَانتَهُوا ۚ وَاتَّقُوا اللَّهَ ۖ إِنَّ اللَّهَ شَدِيدُ الْعِقَابِ

ሚሽነሪዎች የማያውቁትን ከመጠየቅ ይልቅ፦ "ዘካህ ከመቶ 2.5% ስጡ የሚል መረጃ የለም፣ ሪባህ ማለት አራጣ ማለት እንጂ ወለድ ማለት አይደለም፥ የቁርኣን አወራረድ ሁለት አይነት ነው የሚል መረጃ ከቁርኣንም ከሐዲስም መረጃ የለም" እያሉ ዲስኩራቸውን ሲደሶክሩ ነበር። ለእናንዳንዱ አርስት ከቁርኣና ከሐዲስ ከዚህ ቀደም ምላሽ ሰተናል። ዛሬ ደግሞ፦ "ሸዋልን ጹሙ! የሚል ቁርኣን ላይ የለም" እያሉ ይደሶክራሉ። ሚሽነሪዎች ሆይ! ጮቤ ረግጣችሁ አንባጒሮ አትፍጠሩ። ተረጋጉ! የጅብ ችኩል አትሁኑ! በሰላና በሰከነ መንፈስ ጠይቁ መልስ ይሰጣችኃል። ከሆያሄዬ ወደ አንቺሆዬ ትንሽ እንኳን እደጉ።
የወሮች ቁጥር አላህ ዘንድ በአላህ መጽሐፍ ዐሥራ ሁለት ወር ነው፥ እነዚህም፦
1ኛ ወር ሙሐረም
2ኛ ወር ሰፈር
3ኛ ወር ረቢዑል-አወል
4ኛ ወር ረቢዑ-ሣኒ
5ኛ ወር ጀማዱል-አወል
6ኛ ወር ጀማዱ-ሣኒ
7ኛ ወር ረጀብ
8ኛ ወር ሻዕባን
9ኛ ወር ረመዷን
10ኛ ወር ሸዋል
11ኛ ወር ዙል-ቀዒዳህ
12ኛ ወር ዙል-ሒጃህ ናቸው፦
9፥36 *የወሮች ቁጥር አላህ ዘንድ በአላህ መጽሐፍ ውስጥ ሰማያትንና ምድርን በፈጠረበት ቀን ዐሥራ ሁለት ወር ነው፡፡ ከእነርሱ አራቱ የተከበሩ ናቸው*፡፡ إِنَّ عِدَّةَ الشُّهُورِ عِندَ اللَّهِ اثْنَا عَشَرَ شَهْرًا فِي كِتَابِ اللَّهِ يَوْمَ خَلَقَ السَّمَاوَاتِ وَالْأَرْضَ مِنْهَا أَرْبَعَةٌ حُرُمٌ

ከእነዚህ አስራ ሁለት ወራት አንዱ 10ኛ ወር "ሸዋል" ነው፥ "ሸዋል" شَوَّال ማለት "ማንሳት" ወይም "መሸከም" ማለት ሲሆን የወር ስም ነው። ነቢያችን"ﷺ" እንድናደርገው ሙስተሐብ አድርገው ከሰጡት ሱና መካከል ከሸዋል ወር ስድስት ቀናትን መጾም ነው፦
ጃምዒ አት-ተርሚዚ መጽሐፍ 8, ሐዲስ 78
አቢ አዩብ እንደተረከው፦ "ነቢዩ"ﷺ" እንዲህ አሉ፦ *ማንም ረመዷንን የጾመ ከዚያም ከሸዋል ወር ስድስት ቀናትን ያስከተለ ዋጋው ዓመቱን ሙሉ እንደጾመ ነው"*። عَنْ أَبِي أَيُّوبَ، قَالَ قَالَ النَّبِيُّ صلى الله عليه وسلم ‏"‏ مَنْ صَامَ رَمَضَانَ ثُمَّ أَتْبَعَهُ سِتًّا مِنْ شَوَّالٍ فَذَلِكَ صِيَامُ الدَّهْرِ ‏

የረመዷን ሰላሳ ቀን እና የሸዋል ስድስት ቀን ጾም ጾመን ዓመት እንደጾምን የሚያስቆጥርበትን ስሌት ማወቅ ይቻላል። አምላካችን አላህ አንድ መልካም ሥራ ምንዳው አሥር እጥፍ እንደሆነ በቅዱስ ቃሉ ነግሮናል፦
6፥160 *"በመልካም ሥራ የመጣ ሰው ለእርሱ ዐሥር ብጤዎችዋ አሉት"*፡፡ በክፉ ሥራም የመጣ ሰው ብጤዋን እንጅ አይመነዳም፡፡ እነርሱም አይበደሉም፡፡ مَن جَاءَ بِالْحَسَنَةِ فَلَهُ عَشْرُ أَمْثَالِهَا ۖ وَمَن جَاءَ بِالسَّيِّئَةِ فَلَا يُجْزَىٰ إِلَّا مِثْلَهَا وَهُمْ لَا يُظْلَمُونَ

ስለዚህ አንድ መልካም ሥራ አሥር ብጤዎች ካሉት የረመዷን አንድ ወር መጾም የአሥር ወር ምንዳ አለው። 1×10=10 ወር ይሆናል። እንዲሁ የሸዋል ስድስት ቀን መጾም የስድሳ ቀን ምንዳ አለው፥ ስድስት ቀናት በአሥር እጥፍ ስድሳ ቀን ነውና፥ 6×10=60 ቀን ወይም 2 ወር ይሆናል። ሲጠቀለል የረመዷን የአሥር ወር ምንዳ እና የሸዋል ሁለት ወር ምንዳ 12 ወር ይሆናል፥ 10+2=12 ወር ይሆናል። አንድ ዓመት 12 ወር መሆኑ እሙን ነው። አምላካችን አላህ በተከበረ ቃሉ፦ "መልክተኛውም የሰጣችሁን ማንኛውንም ነገር ያዙት" ይለናል፦
59፥7 *መልክተኛውም የሰጣችሁን ማንኛውንም ነገር ያዙት፡፡ ከእርሱም የከለከላችሁን ነገር ተከልከሉ*፡፡ አላህንም ፍሩ፡፡ አላህ ቅጣተ ብርቱ ነውና፡፡ وَمَا آتَاكُمُ الرَّسُولُ فَخُذُوهُ وَمَا نَهَاكُمْ عَنْهُ فَانتَهُوا ۚ وَاتَّقُوا اللَّهَ ۖ إِنَّ اللَّهَ شَدِيدُ الْعِقَابِ

ስለዚህ ኢሥላም ሰው ሰራሽ ሕግና ሥርዓት ሳይሆን ዐቂደቱል ረባንያህ ነው። ይህንን ስንል አርቲ ቡርቲና ቶራ ቦራ የሆነ ስሁትና መሪር የቡና ወሬ ይዘን ሳይሆን ቁርኣንና ሐዲስን ያማከለ ስሙርና ጥዑም ማስረጃ ይዘን ነው።

ከወንድም ወሒድ ዑመር
https://tttttt.me/Wahidcom

ወሠላሙ ዐለይኩም
ግብረ-ሰዶም

በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡

15፥74 *ላይዋንም ከታችዋ አደረግን፡፡ በእነሱም ላይ የሸክላ ደንጊያዎችን አዘነብንባቸው*፡፡ فَجَعَلْنَا عَالِيَهَا سَافِلَهَا وَأَمْطَرْنَا عَلَيْهِمْ حِجَارَةً مِّن سِجِّيلٍ

ሥነ-ጋብቻ ጥናት””matrimony” ስለ ጋብቻ ሲናገር በዋነኝነት ለሁለት ይከፍሉታል፦ አንደኛ “ተቃራኒ ጾታ ጋብቻ”Hetero-sexual” ሲሆን ሁለተኛው “ተመሳሳይ ጾታ ጋብቻ”homo-sexual” ” ነው።
ተቃራኒ ጾታ ጋብቻ በመለኮት መጽሐፍት ውስጥ የተቀመጠ ሲሆን ተመሳሳይ ጾታ ጋብቻ ግን በመለኮት መጽሐፍት ውስጥ አንዳች ድጋፍ የሌለው ነው።
ግብረ-ሰዶም”homosexual” ማለት የሰዶማውያን ሥራ ማለት ነው፤ ግብረ-ሰዶም በራሱ ለሁለት ይከፈላል፤ እርሱም፦ በወንድ እና በወንድ መካከል ያለው የግብረ ሰዶማዊ ግንኙነት”Gays” አንዱ ሲሆን ሌላው ደግሞ በሴት እና በሴት መካከል ያለው የግብረ ሰዶማዊ ግንኙነት”Lesbians” ነው። አምላካችን አላህ ነብዩ ሉጥን በዚህ ድርጊት በተሰማሩ ሕዝቦች መካከል ፍርድንና ዕውቀትን ሰጥቶ ላከው፤ ሉጥም በእርግጥ ከመልክተኞቹ አንዱ ነው፦
37፥133 *ሉጥም በእርግጥ ከመልክተኞቹ ነው*። وَإِنَّ لُوطًا لَّمِنَ الْمُرْسَلِينَ
21፥74 *ሉጥንም ፍርድንና ዕውቀትን ሰጠነው፡፡ ከዚያችም መጥፎ ሥራዎችን ትሠራ ከነበረችው ከተማ አዳንነው፡፡ እነርሱ ክፉ ሰዎች አመጸኞች ነበሩና*፡፡ وَلُوطًا آتَيْنَاهُ حُكْمًا وَعِلْمًا وَنَجَّيْنَاهُ مِنَ الْقَرْيَةِ الَّتِي كَانَت تَّعْمَلُ الْخَبَائِثَ ۗ إِنَّهُمْ كَانُوا قَوْمَ سَوْءٍ فَاسِقِينَ

የሰዶም ከተማ ይሰሩት የነበረው መጥፎ ሥራ ይህ ነው፤ በዚህ ሥራቸው ክፉ ሰዎችና አመጸኞች ናቸው። ሉጥንም ለሕዝቦቹ፦ “እናንተ የምታዩ ስትኾኑ ፀያፍን ነገር ትሠራላችሁን? በእርሷ ከዓለማት አንድም አልቀደማችሁም” አላቸው፦
27፥54 ሉጥንም ለሕዝቦቹ ባለ ጊዜ አስታውስ፦ *”እናንተ የምታዩ ስትኾኑ ፀያፍን ነገር ትሠራላችሁን?”* وَلُوطًا إِذْ قَالَ لِقَوْمِهِ أَتَأْتُونَ الْفَاحِشَةَ وَأَنتُمْ تُبْصِرُونَ
29፥28 ሉጥንም ለሕዝቦቹ ባለ ጊዜ አስታውስ፦ *”እናንተ ጠያፍን ስራ ትሠራላችሁን? በእርሷ ከዓለማት አንድም አልቀደማችሁም”*፡፡ وَلُوطًا إِذْ قَالَ لِقَوْمِهِ إِنَّكُمْ لَتَأْتُونَ الْفَاحِشَةَ مَا سَبَقَكُم بِهَا مِنْ أَحَدٍ مِّنَ الْعَالَمِينَ
7፥80 ሉጥንም ለሕዝቦቹ ባለ ጊዜ አስታውስ፦ *”አስቀያሚን ሥራ ትሠራላችሁን? በእርሷ ከዓለማት አንድም አልቀደማችሁም”*፡፡ وَلُوطًا إِذْ قَالَ لِقَوْمِهِ أَتَأْتُونَ الْفَاحِشَةَ مَا سَبَقَكُم بِهَا مِنْ أَحَدٍ مِّنَ الْعَالَمِينَ

“ከዓለማት አንድም አልቀደማችሁም” ማለት ይህንን ድርጊት ጀማሪዎቹ እነርሱ መሆናቸውን ያሳያል። ወንዶቹ ሴቶች እያሉ ከወንድ ጋር መዳራታቸው ወሰን ማለፍ ነው፦
7፥81 *”እናንተ ከሴቶች ሌላ ወንዶችን በመከጀል በእርግጥ ትመጡባቸዋላችሁን? በእውነቱ እናንተ ወሰንን አላፊዎች ሕዝቦች ናችሁ”*፡፡ إِنَّكُمْ لَتَأْتُونَ الرِّجَالَ شَهْوَةً مِّن دُونِ النِّسَاءِ ۚ بَلْ أَنتُمْ قَوْمٌ مُّسْرِفُونَ
26፥166 *”ከሚስቶቻችሁም ጌታችሁ ለእናንተ የፈጠረላችሁን ትተዋላችሁን? በእውነቱ እናንተ ወሰን አላፊዎች ሕዝቦ ናችሁ”*፡፡ وَتَذَرُونَ مَا خَلَقَ لَكُمْ رَبُّكُم مِّنْ أَزْوَاجِكُم ۚ بَلْ أَنتُمْ قَوْمٌ عَادُونَ

ይህንን ድርጊት በጀመሩት በሰዶማውያን ላይ አላህ ጠጠርን ያዘለች ነፋስን በመላክ የሸክላ ደንጊያዎችን አዘነበባቸው፦
54፥34 *እኛ በእነርሱ ላይ ጠጠርን ያዘለች ነፋስን ላክን፡፡ የሉጥ ቤተሰቦች ብቻ ሲቀሩ እነርሱን በሌሊት መጨረሻ ላይ አዳንናቸው*፡፡ إِنَّا أَرْسَلْنَا عَلَيْهِمْ حَاصِبًا إِلَّا آلَ لُوطٍ ۖ نَّجَّيْنَاهُم بِسَحَرٍ
15፥74 *ላይዋንም ከታችዋ አደረግን፡፡ በእነሱም ላይ የሸክላ ደንጊያዎችን አዘነብንባቸው*፡፡ فَجَعَلْنَا عَالِيَهَا سَافِلَهَا وَأَمْطَرْنَا عَلَيْهِمْ حِجَارَةً مِّن سِجِّيلٍ
7፥84 *በእነርሱም ላይ ዝናብን አዘነብንባቸው፡፡ የኃጢአተኞችም መጨረሻ እንዴት እንደነበረ ተመልከት*፡፡ وَأَمْطَرْنَا عَلَيْهِم مَّطَرًا ۖ فَانظُرْ كَيْفَ كَانَ عَاقِبَةُ الْمُجْرِمِينَ
26፥173 *በእነርሱም ላይ የድንጋይን ዝናምን አዘነምንባቸው፤ የተስፈራሪዎቹም ዝናም ምንኛ ከፋ*፡፡ وَأَمْطَرْنَا عَلَيْهِم مَّطَرًا ۖ فَسَاءَ مَطَرُ الْمُنذَرِينَ

ይህ ድርጊት አላህ ዘንድ እጅግ ክፉ ስለነበር ከተማዎቹ ላይዋንም ከታችዋ ተገለበጡ፦
15፥74 *ላይዋንም ከታችዋ አደረግን፡፡ በእነሱም ላይ የሸክላ ደንጊያዎችን አዘነብንባቸው*፡፡ فَجَعَلْنَا عَالِيَهَا سَافِلَهَا وَأَمْطَرْنَا عَلَيْهِمْ حِجَارَةً مِّن سِجِّيلٍ
9፥70 የእነዚያ ከእናንተ በፊት የነበሩት የኑሕ ሕዝቦች፣ የዓድና የሰሙድም፣ የኢብራሂምም ሕዝቦች የመድየን ባለቤቶች እና *የተገልባጮቹም ከተሞች ወሬ አልመጣላቸውምን?* أَلَمْ يَأْتِهِمْ نَبَأُ الَّذِينَ مِن قَبْلِهِمْ قَوْمِ نُوحٍ وَعَادٍ وَثَمُودَ وَقَوْمِ إِبْرَاهِيمَ وَأَصْحَابِ مَدْيَنَ وَالْمُؤْتَفِكَاتِ
53፥53 *የተገለበጠችውንም ከተማ ደፋ*፡፡ وَالْمُؤْتَفِكَةَ أَهْوَىٰ

ከላይ ያየነው የሰዶማውያን ሥራ ወሰን ማለፍ እንደሆነ ሉጥ እንዳስጠነቀቃቸው ሀሉ አላህም በቁርኣን የነገረን ከተቃራኒ ጾታ ውጪ የያደርጉ እነርሱ ወሰን አላፊዎች ናቸው፤ ወሰንንም አትለፉ ተብለናል፦
23፥6 *በሚስቶቻቸው ወይም እጆቻቸው በያዟቸው ላይ ሲቀር፤ እነርሱ በእዚህ የማይወቀሱ ናቸውና፡፡ ከዚህም ወዲያ የፈለጉ ሰዎች እነዚያ እነርሱ ወሰን አላፊዎች ናቸው*፡፡ إِلَّا عَلَىٰ أَزْوَاجِهِمْ أَوْ مَا مَلَكَتْ أَيْمَانُهُمْ فَإِنَّهُمْ غَيْرُ مَلُومِينَ فَمَنِ ابْتَغَىٰ وَرَاءَ ذَٰلِكَ فَأُولَـٰئِكَ هُمُ الْعَادُونَ
11፥112 *እንደ ታዘዝከውም ቀጥ በል፡፡ ከአንተ ጋር ያመኑትም ቀጥ ይበሉ፡፡ ወሰንንም አትለፉ፤ እርሱ የምትሠሩትን ሁሉ ተመልካች ነውና*፡፡ فَاسْتَقِمْ كَمَا أُمِرْتَ وَمَن تَابَ مَعَكَ وَلَا تَطْغَوْا ۚ إِنَّهُ بِمَا تَعْمَلُونَ بَصِيرٌ
ይህ ድርጊት በማድረግ ወሰን ያለፈ የሚጠብቀው ቅጣት በአኺራ እሳት ነው፦
4፥30 *ወሰን በማለፍና በመበደልም ይህንን የሠራ ሰው እሳትን እናገባዋለን*፡፡ ይኸም በአላህ ላይ ገር ነው፡፡ وَمَن يَفْعَلْ ذَٰلِكَ عُدْوَانًا وَظُلْمًا فَسَوْفَ نُصْلِيهِ نَارًا ۚ وَكَانَ ذَٰلِكَ عَلَى اللَّهِ يَسِيرًا

በዱኒያህ ደግሞ ያለው ቅጣት በኢስላም የሙስሊም ሸሪዓ ባለበት ህገ-መንግሥት ግድያ ነው፦
ሱነን ኢብኑ ማጃህ መጽሐፍ 20, ሐዲስ 2658
ከኢብኑ ዐባሥ እንደተላለፈው የአላህ መልእክተኛ”ﷺ” አሉ፦ *”ማንም የሉጥ ሕዝብ የሚያደርጉት ድርጊት ሲያደርጉ ብታገኙ ሁለቱንም ግደሏቸው”*። عَنِ ابْنِ عَبَّاسٍ، أَنَّ رَسُولَ اللَّهِ صلى الله عليه وسلم قَالَ ‏ “‏ مَنْ وَجَدْتُمُوهُ يَعْمَلُ عَمَلَ قَوْمِ لُوطٍ فَاقْتُلُوا الْفَاعِلَ وَالْمَفْعُولَ بِهِ ‏”‏ ‏

ሚሽነሪዎች፦ “በኢስላም ግብረ-ሰዶም ሃራም የሆነበት ጥቅስና ቅጣት የለም” ብለው ሲቀጥፉ ተመልሰው ደግሞ፦ “እንዴት ይገደላል? መብቱ ነው” ይላሉ፤ ይህንን የሚሉት የምዕራባውያንን እሳቦትና ዕርዮት ይዘው ነው። መብቱ ከሆነ ለምን ፈጣሪ ሰዶማውያንን በዚህ ድርጊታቸው አጠፋቸው? ለምንስ ይህንን ድርጊት የሚፈጽሙ ይገደሉ አለ?፦
ዘፍጥረት 19፥24 *እግዚአብሔርም በሰዶምና በገሞራ ላይ ከእግዚአብሔር ዘንድ ከሰማይ እሳትና ዲን አዘነበ፤ እነዚያንም ከተሞች፥ በዙሪያቸው ያለውንም ሁሉ፥ በከተሞቹም የሚኖሩትን ሁሉ፥ የምድሩንም ቡቃያ ሁሉ ገለበጠ*።
ዘሌዋውያን 20፥13 *ማናቸውም ሰው ከሴት ጋር እንደሚተኛ ከወንድ ጋር ቢተኛ ሁለቱ ጸያፍ ነገር አድርገዋል፤ ፈጽመው ይገደሉ፤ ደማቸው በላያቸው ነው*።

ይህ ብሉይ ኪዳን ላይ ነው እንዳትሉ በአዲስ ኪዳን የተፈቀደበትን ጥቅስ ማምጣት ይጠበቅባችኃል። በአዲስ ኪዳን መፍቀድም መከልከልም የሚችል ነብይ ኢየሱስ ነው፤ ኢየሱስ ሕግን ለመሻር አልመጣሁም ብሏል፤ እንደውም ሰማይና ምድር እስከሚያልፍ ድረስ የሙሴ ሕግ እንደሚሰራ ይናገራል፦
ማቴዎስ 5፥17 *እኔ ሕግንና ነቢያትን ለመሻር የመጣሁ አይምሰላችሁ፤ ልፈጽም እንጂ ለመሻር አልመጣሁም። እውነት እላችኋለሁ፥ ሰማይና ምድር እስኪያልፍ ድረስ፥ ከሕግ አንዲት የውጣ ወይም አንዲት ነጥብ ከቶ አታልፍም፥ ሁሉ እስኪፈጸም ድረስ*።

ከወንድም ወሒድ ዑመር
https://tttttt.me/Wahidcom

ወሰላሙ አለይኩም
ኅሊና

በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው።

51፥21 *”በራሳችሁም ውስጥ” ምልክቶች አሉ፤ ታዲያ አትመለከቱምን?* وَفِي أَنفُسِكُمْ ۚ أَفَلَا تُبْصِرُونَ

“ኅሊና"Conscience" የሚለው ቃል “ኀለየ” ማለትም “አሰበ” ከሚል ሥርወ-ቃል የመጣ ሲሆን “ማሰቢያ” ማለት ነው። ኅሊና በሦስት ክፍል ይከፈላል፥ እነርሱም፦
1. ታህታይ ኅሊና"sub-Conscience
2. መደበኛ ኅሊና"normal-Conscience
3. ላዕላይ ኅሊና"super-Conscience

ነጥብ አንድ
"ታህታይ ኅሊና"
ታህታይ ኅሊና ማለት ከተፈጠርንበት ጊዜ ጀምሮ በስሜት የምናውቃቸው ግን በትውስታ ትዝ የማይሉን ነገር በኅሊና ተደብቀው የሚኖሩ ነገር፥ ለምሳሌ እናታችን ማህጸን ውስጥ እያለን የምንሰማው ድምጽ፣ ሕጻን ሆነን የምናየው ነገር ወዘተ ያጠቃልለ። ለምሳሌ አላህ ከአደም ልጆች ከጀርቦቻቸው ዘሮቻቸውን ባወጣ ጊዜ «ጌታችሁ አይደለሁምን?» በማለት ጥያቄ ያቀርባል፤ እኛም «ጌታችን ነህ መሰከርን» በማለት መልስ የሰጠንበት ነው፦
7:172 ጌታህም ከአደም ልጆች ከጀርቦቻቸው *ዘሮቻቸውን ባወጣ”* እና «ጌታችሁ አይደለሁምን» ሲል በነፍሶቻቸው ላይ *”ባስመሰከራቸው”* ጊዜ የኾነውን አስታውስ፡፡ *«ጌታችን ነህ መሰከርን»* አሉ፡፡ «በትንሣኤ ቀን ከዚህ ኪዳን ዘንጊዎች ነበርን እንዳትሉ፡፡» وَإِذْ أَخَذَ رَبُّكَ مِنۢ بَنِىٓ ءَادَمَ مِن ظُهُورِهِمْ ذُرِّيَّتَهُمْ وَأَشْهَدَهُمْ عَلَىٰٓ أَنفُسِهِمْ أَلَسْتُ بِرَبِّكُمْ ۖ قَالُوا۟ بَلَىٰ ۛ شَهِدْنَآ ۛ أَن تَقُولُوا۟ يَوْمَ ٱلْقِيَٰمَةِ إِنَّا كُنَّا عَنْ هَٰذَا غَٰفِلِينَ

ይህ ማንም ትዝ የሚለው የለም። ይህ የተነጋገርንበት የምናስታውሰው "በትንሣኤ ቀን ከዚህ ኪዳን ዘንጊዎች ነበርን እንዳትሉ" ነው ይለናል። በትንሳኤ ቀን ይህ ውስጣችን ያለው ሚስጥር ይገለጻል፦
100፥10 *"በልቦች ውስጥ ያለውም ሁሉ በተገለጸ ጊዜ እንዴት እንደሚኾን"*፡፡ وَحُصِّلَ مَا فِي الصُّدُورِ
86፥9 *"ምስጢሮች በሚገለጡበት ቀን"*፡፡ يَوْمَ تُبْلَى السَّرَائِرُ

ነጥብ ሁለት
"መደበኛ ኅሊና"
መደበኛ ኅሊና ማለት በስሜት ሕዋሳት የምንረዳው ውጫዊና ውስጣዊ ነው፥ ለምሳሌ "ሕውስታ"sensation" የሚባለው ነው፦
16፥78 አላህም *"ከእናቶቻችሁ ሆዶች ምንም የማታውቁ ሆናችሁ አወጣችሁ፡፡ ታመሰግኑም ዘንድ ለእናንተ መስሚያን ማያዎችንም ልቦችንም አደረገላችሁ"*፡፡ وَاللَّهُ أَخْرَجَكُم مِّن بُطُونِ أُمَّهَاتِكُمْ لَا تَعْلَمُونَ شَيْئًا وَجَعَلَ لَكُمُ السَّمْعَ وَالْأَبْصَارَ وَالْأَفْئِدَةَ ۙ لَعَلَّكُمْ تَشْكُرُونَ

በመደበኛ ኅሊና ምንም ሳናውቅ እንወለዳለን። "ሕዋስ"Sense" ከውጪ ማየትና መስማት ሲሆኑ ከውስጥ ደግሞ ልብ ነው፥ “ልብ” የሚለው ቃል “ለበወ” ማለትም “አመዛዘነ” ከሚል ሥርወ-ቃል የመጣ ሲሆን “ማመዛዘኛ” ማለት ነው። ይህ ዕውቀት በእርጅና ምንንም ነገር ወደ ዐለማወቅ ይሄዳል፦
16፥70 አላህም ፈጠራችሁ፤ ከዚያም ይገድላችኋል፡፡ *"ከእናንተም ከዕወቅት በኋላ ምንንም ነገር እንዳያውቅ ወደ ወራዳ ዕድሜ የሚመለስ ሰው አለ"*፡፡ አላህ ዐዋቂ ቻይ ነው፡፡ وَاللَّهُ خَلَقَكُمْ ثُمَّ يَتَوَفَّاكُمْ ۚ وَمِنكُم مَّن يُرَدُّ إِلَىٰ أَرْذَلِ الْعُمُرِ لِكَيْ لَا يَعْلَمَ بَعْدَ عِلْمٍ شَيْئًا ۚ إِنَّ اللَّهَ عَلِيمٌ قَدِيرٌ

ነጥብ ሦስት
"ላዕላይ ኅሊና"
ላዕላይ ኅሊና ከሰው በተለየ መልኩ የሚያሳውቀው ዕውቀት ነው፥ ለምሳሌ ነቅል ነው። “ነቅል” نقل ማለት "ግልጠተ-መለኮት" ማለት ነው፥ ለምሳሌ ቁርኣን ነቅል ነው፦
55፥2 *"ቁርኣንን ዐሳወቀው"*፡፡ عَلَّمَ الْقُرْآنَ
96፥5 *"ሰውን ያላወቀውን ሁሉ ያሳወቀ ሲኾን"*፡፡ عَلَّمَ الْإِنسَانَ مَا لَمْ يَعْلَمْ

“ዐቅል” عقل ማለት ከእንስሳ በተለየ መልኩ በውስጣዊ ስሜት የምንረዳው አእምሮ ነው፥ “አእምሮ” የሚለው ቃል “አእመረ” ማለትም “ዐወቀ” ከሚል ሥርወ-ቃል የመጣ ሲሆን “ማወቂያ” ማለት ነው። ነቅል ግን ከአላህ ዘንድ የሚወርድ ዕውቀት ነው፦
4፥113 አላህም *"በአንተ ላይ መጽሐፍንና ጥበብን አወረደ፡፡ "የማታውቀውንም ሁሉ ዐሳወቀህ"*፡፡ የአላህም ችሮታ በአንተ ላይ ታላቅ ነው፡፡ وَأَنزَلَ ٱللَّهُ عَلَيْكَ ٱلْكِتَٰبَ وَٱلْحِكْمَةَ وَعَلَّمَكَ مَا لَمْ تَكُن تَعْلَمُ ۚ وَكَانَ فَضْلُ ٱللَّهِ عَلَيْكَ عَظِيمًۭا

"የማታውቀውንም ሁሉ ዐሳወቀህ" የሚለው ይሰመርበት። ይህንን ዕውቀት የተረዳ ላዕላይ ኅሊና አለው። ሰው በውስጡ ያለውን ውሳጣዊ ተፈጥሮ ሰፊ ነው። ሙሉውን የሚያውቀውም አላህ ብቻ ነው፦
17፥25 *ጌታችሁ በራሳችሁ ውስጥ ያለውን ሁሉ አዋቂ ነው*፡፡ ታዛዦችም ብትኾኑ በመሳሳትም ብታጠፉ እርሱ ለተመላሾች መሓሪ ነው፡፡ رَّبُّكُمْ أَعْلَمُ بِمَا فِي نُفُوسِكُمْ ۚ إِن تَكُونُوا صَالِحِينَ فَإِنَّهُ كَانَ لِلْأَوَّابِينَ غَفُورًا

ይህንን ውሳጣዊ ማንነት በማጥራት ማስተንተን “አት-ተሰዉፍ” الْتَّصَوُّف‎ ይባላል፤ በማጥራት የሚያስተነትነው ሰው ደግሞ “ሙተሰዉፍ” مُتَصَوُّف‎ ይባላል። በራሳችን ውስጥ ያለው ውሳጣዊ ምልክትቶች ብዙ ናቸው፥ አላህ ይህንን ውሳጣዊ ነገር አትመለከቱምን? ይለናል፦
51፥21 *”በራሳችሁም ውስጥ” ምልክቶች አሉ፤ ታዲያ አትመለከቱምን?* وَفِي أَنفُسِكُمْ ۚ أَفَلَا تُبْصِرُونَ

ከወንድም ወሒድ ዑመር
https://tttttt.me/Wahidcom

ወሠላሙ ዐለይኩም
ፈራጅ ማን ነው?

በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡

95፥8 *አላህ ከፈራጆች ሁሉ ይበልጥ ፈራጅ አይደለምን? ነው*፡፡ أَلَيْسَ اللَّهُ بِأَحْكَمِ الْحَاكِمِين

“አል-ሐከም” الحَكَم ከአላህ ስሞች አንዱ ሲሆን ትርጉሙ “ፈራጅ" ወይም "ዳኛ” ማለት ሲሆን “ሁክም” حُكْم ማለትም “ፍርድ” ደግሞ የእርሱ ባሕርይ ነው። አምላካችን አላህ ከፈራጆች ሁሉ ይበልጥ በትክክል ፈራጅ ነው፥ በፍርዱ ቀን ፍርዱ የእርሱ ብቻ ነው። በዚያ ቀን በፍርዱ ማንንም አያጋራም፦
95፥8 *አላህ ከፈራጆች ሁሉ ይበልጥ ፈራጅ አይደለምን? ነው*፡፡ أَلَيْسَ اللَّهُ بِأَحْكَمِ الْحَاكِمِين
34፥26 «ጌታችን በመካከላችን ይሰበስባል፡፡ ከዚያም በመካከላችን በእውነት ይፈርዳል፡፡ *እርሱም በትክክል ፈራጁ ዐዋቂው ነው» በላቸው*፡፡ قُلْ يَجْمَعُ بَيْنَنَا رَبُّنَا ثُمَّ يَفْتَحُ بَيْنَنَا بِالْحَقِّ وَهُوَ الْفَتَّاحُ الْعَلِيمُ
18፥26 ለእነርሱ ከእርሱ በቀር ምንም ረዳት የላቸውም፡፡ *በፍርዱም አንድንም አያጋራም*፡፡ مَا لَهُم مِّن دُونِهِ مِن وَلِيٍّ وَلَا يُشْرِكُ فِي حُكْمِهِ أَحَدًا

አምላካችን አላህ የፈራጆች ሁሉ ፈራጅ ሲሆን በዱኒያህ ግን ለሁሉም ነቢያት ማለትም ለሉጥ፣ ለዩሱፍ፣ ለሙሳ፣ ለዳውድ፣ ለሱለይማን ወዘተ የሚፈርዱበት ፍርድ ሰቷቸዋል፦
21፥74 *ሉጥንም ፍርድንና ዕውቀትን ሰጠነው*፡፡ وَلُوطًا آتَيْنَاهُ حُكْمًا وَعِلْمًا
12፥22 *ጥንካሬውንም በደረሰ ጊዜ ፍርድን እና ዕውቀትን ሰጠነው*፡፡ እንደዚሁም መልካም ሠሪዎችን ሁሉ እንመነዳለን፡፡ وَلَمَّا بَلَغَ أَشُدَّهُ آتَيْنَاهُ حُكْمًا وَعِلْمًا ۚ وَكَذَٰلِكَ نَجْزِي الْمُحْسِنِينَ
28፥14 ብርታቱንም በደረሰና በተስተካከለ ጊዜ *ፍርድ እና ዕውቀትን ሰጠነው*፡፡ እንዲሁም መልካም ሠሪዎችን እንመነዳለን፡፡ وَلَمَّا بَلَغَ أَشُدَّهُ وَاسْتَوَىٰ آتَيْنَاهُ حُكْمًا وَعِلْمًا ۚ وَكَذَٰلِكَ نَجْزِي الْمُحْسِنِينَ
21፥79 *ለሱለይማንም ትክክለኛይቱን ፍርድ አሳወቅነው፡፡ ለሁሉም ፍርድ እና ዕውቀትን ሰጠን*፡፡ فَفَهَّمْنَاهَا سُلَيْمَانَ ۚ وَكُلًّا آتَيْنَا حُكْمًا وَعِلْمًا
5፥42 *ብትፈርድም በመካከላቸው በትክክል ፍረድ፤ አላህ በትክክል ፈራጆችን ይወዳልና*፡፡ وَإِنْ حَكَمْتَ فَاحْكُم بَيْنَهُم بِالْقِسْطِ ۚ إِنَّ اللَّهَ يُحِبُّ الْمُقْسِطِينَ

“ፈራጆች” የሚለው ቃል ይሰመርበት። በተመሳሳይም በባይብል ሊያድን ሊያጠፋም የሚችል የሁሉ ዳኛ አንድ ነው፦
ያዕቆብ 4፥12 *"ሕግን የሚሰጥና የሚፈርድ “አንድ” ነው፤ “እርሱም” ሊያድን ሊያጠፋም የሚችል ነው"*።
ዕብራውያን 12፥24 *“የሁሉም ዳኛ” ወደሚሆን ወደ “እግዚአብሔር”፥ ፍጹማንም ወደ ሆኑት ወደ ጻድቃን መንፈሶች፥ የአዲስም ኪዳን “መካከለኛ” ወደሚሆን ወደ “ኢየሱስ" ደም ደርሳችኋል*።

በተለይ የመጨረሻው ጥቅስ ላይ አንዱ እግዚአብሔር “የሁሉም ዳኛ” ተብሎ ተቀምጦ ኢየሱስን ግን በአንዱ እግዚአብሔርና በሰዎች መካከል ያለ “መካከለኛ” አርድጎ አስቀምጦታል፦
1ኛ ጢሞ 2፥5 *“አንድ እግዚአብሔር” አለና፥ በእግዚአብሔርና በሰውም መካከል ያለው “መካከለኛው” ደግሞ አንድ አለ፥ እርሱም “ሰው” የሆነ ክርስቶስ ኢየሱስ ነው"*።

ታዲያ አንዱ አምላክ የሁሉ ፈራጅ ከሆነ ኢየሱስ እንዴት ይፈርዳል? የሚል ጥያቄ ከተነሳ የሚፈርደው ኢየሱስ ብቻ ሳይሆን ሌሎች አካላትም ናቸው፣ ኢየሱስ ሆነ ሌሎች አካላት የመፍረድ ስልጣንና ፍርድ የተሰጣቸው ከአንዱ አምላክ ነው። ኢየሱስ ሰውና የሰው ልጅ ስለሆነ የመፍረድ ስልጣንና ፍርድ የተሰጠው ከፈጣሪው ነው፣ የሚፈርደው ከላከው ከአንዱ አምላክ እየሰማ እንጂ ከራሱ ምንም ማድረግ አይችልም፦
ዮሐንስ 5፥27 *“የሰው ልጅም” ስለ ሆነ “ይፈርድ” ዘንድ “ሥልጣን ሰጠው”*።
ዮሐንስ 5፥30 “እኔ ከራሴ” አንዳች ላደርግ አይቻለኝም፤ *“እንደ ሰማሁ እፈርዳለሁ ፍርዴም”* ቅን ነው።
ዮሐንስ 5፥23 ሰዎች ሁሉ አብን እንደሚያከብሩት ወልድን ያከብሩት ዘንድ፥ *“ፍርድን” ሁሉ ለወልድ “ሰጠው”"*።

በተለይ “ፍርድን ሁሉ ለወልድ ሰጠው” የሚለው ኃይለ-ቃል ይሰመርበት። “ሰጠው” የተባለው ለሰሎሞን ፍርድን በሰጠበት ስሌት ነው፦
መዝሙር 72፥1 አቤቱ፥ *“ፍርድህን” ለንጉሥ “ስጥ”*፥ ጽድቅህንም ለንጉሥ ልጅ፥

እንደ ባይብል ተስተምህሮት በፍርድ ቀን የሚፈርዱት የነነዌ ሰዎችና ንግሥተ ዓዜብ ናቸው፦
ማቴዎስ 12፥41 የነነዌ ሰዎች በፍርድ ቀን ከዚህ ትውልድ ጋር ተነሥተው *“ይፈርዱበታል”*።
ማቴዎስ 12፥42 ንግሥተ ዓዜብ በፍርድ ቀን ከዚህ ትውልድ ጋር ተነሥታ *“ትፈርድበታለች”*።

እንደ ባይብል ተስተምህሮት በፍርድ ቀን የሚፈርዱት ሐዋርያት ናቸው፦
ማቴዎስ 19፥28 ኢየሱስም እንዲህ አላቸው፦ እውነት እላችኋለሁ፥ እናንተስ የተከተላችሁኝ፥ በዳግመኛ ልደት የሰው ልጅ በክብሩ ዙፋን በሚቀመጥበት ጊዜ፥ *እናንተ ደግሞ በአሥራ ሁለቱ የእስራኤል ነገድ “ስትፈርዱ” በአሥራ ሁለት ዙፋን ትቀመጣላችሁ"*።
ራእይ 20፥4 *"ዙፋኖችንም አየሁ፥ በእነርሱም ላይ ለተቀመጡት “ዳኝነት” ተሰጣቸው"*።
1ኛ ቆሮ 6፥2 *"ቅዱሳን በዓለም ላይ “እንዲፈርዱ”* አታውቁምን?

አይ የነነዌ ሰዎች በፍርድ ቀን "የሚፈርዱት" ማለት "የሚመሰክሩት" ማለት ነው፥ ንግሥተ ዓዜብ በፍርድ ቀን "ትፈርድበታለች" ማለት "ትመሰክርበታለች" ማለት ነው፥ ሐዋርያት በፍርድ ቀን በአሥራ ሁለቱ የእስራኤል ነገድ “ስትፈርዱ" ማለት "ስትመሰክሩ' ማለት ነው ከተባለ እንግዲያውስ ኢየሱስ በፍርድ ቀን በሐሰተኛ አስተማሪዎቹ ላይ ይመሰክርባቸዋል፥ ለአማኙ ደግሞ በእግዚአብሔር እና በመላእክቱ ፊት ይመስክርለታል፦
ማቴዎስ 7፥22-23 በዚያ ቀን ብዙዎች፦ ጌታ ሆይ፥ ጌታ ሆይ፥ *በስምህ ትንቢት አልተናገርንምን፥ በስምህስ አጋንንትን አላወጣንምን፥ በስምህስ ብዙ ተአምራትን አላደረግንምን? ይሉኛል*። የዚያን ጊዜም፦ ከቶ አላወቅኋችሁም፤ እናንተ ዓመፀኞች፥ ከእኔ ራቁ፡ ብዬ *"እመሰክርባቸዋለሁ"*።
ማቴዎስ 10፥32 ስለዚህ በሰው ፊት ለሚመሰክርልኝ ሁሉ *እኔ ደግሞ በሰማያት ባለው በአባቴ ፊት እመሰክርለታለሁ*፤
ራእይ 3፥5 ድል የነሣው እንዲሁ በነጭ ልብስ ይጐናጸፋል፥ ስሙንም ከሕይወት መጽሐፍ አልደመስስም፥ *"በአባቴና በመላእክቱም ፊት ለስሙ እመሰክርለታለሁ"*።

እውነት ነው ዒሣ በትንሣኤም ቀን በአህለል ኪታብ ላይ መስካሪ ይኾናል፦
4፥159 ከመጽሐፉም ሰዎች ከመሞቱ በፊት በእርሱ (በዒሳ) በእርግጥ የሚያምን እንጅ አንድም የለም፡፡ *"በትንሣኤም ቀን በእነርሱ ላይ መስካሪ ይኾናል"*፡፡ وَإِن مِّنْ أَهْلِ الْكِتَابِ إِلَّا لَيُؤْمِنَنَّ بِهِ قَبْلَ مَوْتِهِ ۖ وَيَوْمَ الْقِيَامَةِ يَكُونُ عَلَيْهِمْ شَهِيدًا
በቁርኣን አናቅጽ ላይ “ሻሂድ” شَاهِد ማለት የሚመሰክር “መስካሪ” ማለት ሲሆን “መሽሁድ” مَشْهُود ማለት ደግሞ የሚመሰከርበት “ተመስካሪ” ማለት ነው። በተቀጠረው ቀን መስካሪ በተመስካሪ ላይ ይመሰክራሉ፦
85፥2 *”በተቀጠረው ቀንም እምላለው”*። وَالْيَوْمِ الْمَوْعُودِ
85፥3 *”በመስካሪ እና በተመስካሪ እምላለሁ”*፡፡ وَشَاهِدٍ وَمَشْهُودٍ
And by the witness and the witnessed.

አላህ በቁርኣን የማለባቸው ነገሮችን ሁሉ ጉዳዩን አጽንዖትና አንክሮት መስጠቱን የሚያመላክት ነው። ያ የተቀጠረው ቀን ሙታን የሚቀሰቀሱበት የትንሳኤ ቀን ነው፦
34፥30 *«ለእናንተ ከእርሱ አንዲትንም ሰዓት የማትዘገዩበት የማትቀድሙበትም “የቀጠሮ ቀን” አላችሁ»* በላቸው፡፡ قُل لَّكُم مِّيعَادُ يَوْمٍ لَّا تَسْتَأْخِرُونَ عَنْهُ سَاعَةً وَلَا تَسْتَقْدِمُونَ
36፥52 *«ወይ ጥፋታችን! ከመኝታችን ማን ቀሰቀሰን? “ይህ ያ አዛኙ ጌታ በእርሱ የቀጠረን” እና መልክተኞቹም እውነትን የነገሩን ነው»* ይላሉ፡፡ قَالُوا يَا وَيْلَنَا مَن بَعَثَنَا مِن مَّرْقَدِنَا ۜ ۗ هَـٰذَا مَا وَعَدَ الرَّحْمَـٰنُ وَصَدَقَ الْمُرْسَلُونَ
11፥103 በዚህ ውስጥ የመጨረሻውን ቀን ቅጣት ለሚፈሩ ሁሉ መገሰጫ አለ፡፡ *”ይህ የትንሣኤ ቀን ሰዎች በእርሱ የሚሰበሰቡበት ቀን ነው፡፡ ይህም የሚጣዱት ቀን ነው”*፡፡ إِنَّ فِي ذَٰلِكَ لَآيَةً لِّمَنْ خَافَ عَذَابَ الْآخِرَةِ ۚ ذَٰلِكَ يَوْمٌ مَّجْمُوعٌ لَّهُ النَّاسُ وَذَٰلِكَ يَوْمٌ مَّشْهُودٌ

የተቀጠረው ቀን የመሽሁድ ቀን ነው። አላህ፦ “በመስካሪው እና በሚመሰከርባቸው እምላለው” ብሏል፤ “መስካሪ” የተባሉት “ነቢያት” ሲሆኑ “የሚመሰከርባቸው” ደግሞ “ኡማቸው” ናቸው፦
16፥84 *”ከየሕዝቡም ሁሉ መስካሪን የምንቀሰቅስበትን ቀን አስታውስ”*፡፡ وَيَوْمَ نَبْعَثُ مِن كُلِّ أُمَّةٍ شَهِيدًا
4፥41 *”ከሕዝቦችም ሁሉ መስካሪን ባመጣን ጊዜ አንተንም በእነዚህ ሕዝብ ላይ መስካሪ አድርገን በምናመጣህ ጊዜ የከሓዲዎች ኹኔታ እንዴት ይኾን?”* فَكَيْفَ إِذَا جِئْنَا مِن كُلِّ أُمَّةٍ بِشَهِيدٍ وَجِئْنَا بِكَ عَلَىٰ هَـٰؤُلَاءِ شَهِيدًا
16፥89 *”በየሕዝቡም ሁሉ ውስጥ ከራሳቸው በእነርሱ ላይ መስካሪን የምንቀሰቅስበትን አንተንም በእነዚህ ሕዝብ ላይ መስካሪ አድርገን የምናመጣህን ቀን አስታውስ”*፡፡ وَيَوْمَ نَبْعَثُ فِي كُلِّ أُمَّةٍ شَهِيدًا عَلَيْهِم مِّنْ أَنفُسِهِمْ ۖ وَجِئْنَا بِكَ شَهِيدًا عَلَىٰ هَـٰؤُلَاء
28፥75 *”ከሕዝቦችም ሁሉ መስካሪን እናወጣለን፡፡ ያን ጊዜ እውነተኛውም አምላክነት ለአላህ ብቻ መኾኑን ያውቃሉ፡፡ ይቀጣጥፉት የነበሩትም ከእነርሱ ይጠፋቸዋል”*፡፡ وَنَزَعْنَا مِن كُلِّ أُمَّةٍ شَهِيدًا فَقُلْنَا هَاتُوا بُرْهَانَكُمْ فَعَلِمُوا أَنَّ الْحَقَّ لِلَّهِ وَضَلَّ عَنْهُم مَّا كَانُوا يَفْتَرُونَ

ስለዚህ ፈራጅ አንድ አምላክ አላህ ብቻ ነው። መስካሪዎች ነቢያት ናቸው።

ከወንድም ወሒድ ዑመር
https://tttttt.me/Wahidcom

ወሠላሙ ዐለይኩም
ድነሃልን?

በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው።

3፥103 *የአላህንም የማመን ገመድ ሁላችሁም ያዙ፡፡ አትለያዩም፡፡ ጠበኞችም በነበራችሁ ጊዜ በእናንተ ላይ የዋለውን የአላህን ጸጋ አስታውሱ፡፡ በልቦቻችሁም መካከል አስማማ፡፡ በጸጋውም ወንድማማቾች ኾናችሁ፡፡ በእሳት ጉድጓድ አፋፍም ላይ ነበራችሁ፡፡ ከእርስዋም አዳናችሁ*፡፡ እንደዚሁ ትመሩ ዘንድ አላህ ለእናንተ አንቀጾቹን ያብራራል፡፡ وَاعْتَصِمُوا بِحَبْلِ اللَّهِ جَمِيعًا وَلَا تَفَرَّقُوا ۚ وَاذْكُرُوا نِعْمَتَ اللَّهِ عَلَيْكُمْ إِذْ كُنتُمْ أَعْدَاءً فَأَلَّفَ بَيْنَ قُلُوبِكُمْ فَأَصْبَحْتُم بِنِعْمَتِهِ إِخْوَانًا وَكُنتُمْ عَلَىٰ شَفَا حُفْرَةٍ مِّنَ النَّارِ فَأَنقَذَكُم مِّنْهَا ۗ كَذَٰلِكَ يُبَيِّنُ اللَّهُ لَكُمْ آيَاتِهِ لَعَلَّكُمْ تَهْتَدُونَ

በየመንገዱ፣ በየትምህርት ቤት፣ በሥራ ቦታ ከክርስቲያኖች ወገኖች በተለይ ከፕሮቴስታንት አንጃ፦ “ድነሃልን? የሚል ዋስትና የሌለው ጥያቄ ተደጋግሞ ሲመጣ ይጤናል። ነገር ግን ከምን እንደሚዳን ጠቅሰውና አጣቅሰው በማስረጃ አይሞግቱም፥ አይሟገቱም። ከዚያ ይልቅ ስሜታውያን በመሆን ስሜታዊ ቃላት ይጠቀማሉ። አንዱ አምላክ አመጸኞችን በገሃነም ያጠፋል፥ ከዚህ ጥፋት የሚያድነውም እርሱ ነው፦
ማቴዎስ 10፥28 ሥጋንም የሚገድሉትን ነፍስን ግን መግደል የማይቻላቸውን አትፍሩ፤ ይልቅስ *"ነፍስንም ሥጋንም በገሃነም ሊያጠፋ የሚቻለውን ፍሩ"*።
ያዕቆብ 4፥12 ሕግን የሚሰጥና የሚፈርድ አንድ ነው፤ እርሱም ሊያድን ሊያጠፋም የሚችል ነው፤ በሌላው ግን የምትፈርድ አንተ ማን ነህ?

አንድ ሰው እምነት ኖሮት መጥፎ ሥራ ቢሠራ በፍጹም የእግዚአብሔርን መንግሥት አይወርስም፦
1 ቆሮንቶስ 6፥10 ወይም *ሌቦች ወይም ገንዘብን የሚመኙ ወይም ሰካሮች ወይም ተሳዳቢዎች ወይም ነጣቂዎች የእግዚአብሔርን መንግሥት አይወርሱም*።
ገላትያ 5፥21 *እንደዚህ ያሉትን የሚያደርጉ የእግዚአብሔርን መንግሥት አይወርሱም*።
ራእይ 21፥8 ዳሩ ግን *"የሚፈሩና የማያምኑ የርኵሳንም የነፍሰ ገዳዮችም የሴሰኛዎችም የአስማተኛዎችም ጣዖትንም የሚያመልኩ የሐሰተኛዎችም ሁሉ ዕድላቸው በዲንና በእሳት በሚቃጠል ባሕር ነው፤ ይኸውም ሁለተኛው ሞት ነው"*።

በተቃራኒው አምኖ መልካም ሥራ ቢሠራ ወደ እግዚአብሔር መንግሥት ይገባል፥ ሰው በእምነት ብቻ ሳይሆን በሥራ ይጸድቃል፦
ማቴዎስ 19፥17 እርሱም፦ ስለ መልካም ነገር ለምን ትጠይቀኛለህ? መልካም የሆነ አንድ ነው፤ *"ወደ ሕይወት መግባት ብትወድ ግን ትእዛዛትን ጠብቅ! አለው"*።
ያዕቆብ 2፥24 *"ሰው በእምነት ብቻ ሳይሆን በሥራ እንዲጸድቅ ታያላችሁ"*።

ሰለዚህ አንድ አማኝ አምኖ መልካም ሥራ ከሠራ በተስፋ ድኗል እንጂ አሁን ድኛለው ማለት በፍጹም አይችልም፦
ሮሜ 8፥24-25 *"በተስፋ ድነናልና፤ ነገር ግን ተስፋ የሚደረግበቱ ነገር ቢታይ ተስፋ አይደለም፤ የሚያየውንማ ማን ተስፋ ያደርገዋል? የማናየውን ግን ተስፋ ብናደርገው በትዕግሥት እንጠባበቃለን"*።

"ተስፋ" ወደፊት በትእግስት የምንጠባበቀው ነገር እንጂ አሁን እጃችን ላይ ያለ ዋስትና አይደለም። ይህንን ተስፋ በትእግስት እስከ ሞት ድረስ እየተጠባበቅን ከጸናን ከገሃነም እንድናለን፦
ማቴዎስ 24፥13 *"እስከ መጨረሻ የሚጸና ግን እርሱ ይድናል"*።
ራእይ 2፥10 *"እስከሞት ድረስ የታመንህ ሁን የሕይወትንም አክሊል እሰጥሃለሁ"*።

በአንድ ወቅት አማኝ የነበረ ግን እስከሞት መጨረሻ ድረስ ያታመነና ያልጸና ሰው እንዴት ይድናል? ነገ በእጁ ያልሆነ እንዴትስ ድኛለው ብሎ በድፍረት መናገር ይችላል? በተስፋ ከሆነ አዎ አላህ በእሳት ጉድጓድ አፋፍም ላይ ነበርን፥ ከእርስዋም አዳናነን፦
3፥103 *የአላህንም የማመን ገመድ ሁላችሁም ያዙ፡፡ አትለያዩም፡፡ ጠበኞችም በነበራችሁ ጊዜ በእናንተ ላይ የዋለውን የአላህን ጸጋ አስታውሱ፡፡ በልቦቻችሁም መካከል አስማማ፡፡ በጸጋውም ወንድማማቾች ኾናችሁ፡፡ በእሳት ጉድጓድ አፋፍም ላይ ነበራችሁ፡፡ ከእርስዋም አዳናችሁ*፡፡ እንደዚሁ ትመሩ ዘንድ አላህ ለእናንተ አንቀጾቹን ያብራራል፡፡ وَاعْتَصِمُوا بِحَبْلِ اللَّهِ جَمِيعًا وَلَا تَفَرَّقُوا ۚ وَاذْكُرُوا نِعْمَتَ اللَّهِ عَلَيْكُمْ إِذْ كُنتُمْ أَعْدَاءً فَأَلَّفَ بَيْنَ قُلُوبِكُمْ فَأَصْبَحْتُم بِنِعْمَتِهِ إِخْوَانًا وَكُنتُمْ عَلَىٰ شَفَا حُفْرَةٍ مِّنَ النَّارِ فَأَنقَذَكُم مِّنْهَا ۗ كَذَٰلِكَ يُبَيِّنُ اللَّهُ لَكُمْ آيَاتِهِ لَعَلَّكُمْ تَهْتَدُونَ

“ኢስቲቃማህ” استقامة ሰው በንስሃ በተጸጸተበት፣ ባመነበት ኢማን እና በሚሣራው መልካም ሥራ “መፅናት” ነው፤ “ፅናት” በያዝነው ነገር ቀጥ ብሎ መቆም ነው፥ በቀጥተኛው መንገድ ላይ መፅናት ፍርሃትና ሃዘን ሳይኖር የጀነት ለመሆን መበሰር ነው፦
46፥13 እነዚያ «ጌታችን አላህ ነው» ያሉ፣ *”ከዚያም ቀጥ ያሉ በነርሱ ላይ ፍርሃት የለባቸውም። እነርሱም አያዝኑም”*፡፡ إِنَّ الَّذِينَ قَالُوا رَبُّنَا اللَّهُ ثُمَّ اسْتَقَامُوا فَلَا خَوْفٌ عَلَيْهِمْ وَلَا هُمْ يَحْزَنُونَ
41፥30 እነዚያ «ጌታችን አላህ ነው» ያሉ ከዚያም *”ቀጥ ያሉ” «አትፍሩ፤ አትዘኑም፤ በዚያችም ተስፋ ቃል ትደረግላችሁ በነበራችሁት ገነት ተበሰሩ»* በማለት በእነርሱ ላይ መላእክት ይወርዳሉ፡፡ إِنَّ الَّذِينَ قَالُوا رَبُّنَا اللَّهُ ثُمَّ اسْتَقَامُوا تَتَنَزَّلُ عَلَيْهِمُ الْمَلَائِكَةُ أَلَّا تَخَافُوا وَلَا تَحْزَنُوا وَأَبْشِرُوا بِالْجَنَّةِ الَّتِي كُنتُمْ تُوعَدُون

“ቀጥ ያሉ” ለሚለው ቃል የገባው “ኢሥተቃሙ” اسْتَقَامُوا ሲሆን “የጸኑ” ማለት ነው። አላህ እስከ መጨረሻው በኢማን የሚጸኑ ያርገን! ከጀሃነም ቅጣት አድኖ የጀነት ያድርገን! አሚን።

ከወንድም ወሒድ ዑመር
https://tttttt.me/Wahidcom

ወሠላሙ ዐለይኩም
ዐቂቃህ

በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡

59፥7 *መልክተኛውም የሰጣችሁን ማንኛውንም ነገር ያዙት፡፡ ከእርሱም የከለከላችሁን ነገር ተከልከሉ*፡፡ አላህንም ፍሩ፡፡ አላህ ቅጣተ ብርቱ ነውና፡፡ وَمَا آتَاكُمُ الرَّسُولُ فَخُذُوهُ وَمَا نَهَاكُمْ عَنْهُ فَانتَهُوا ۚ وَاتَّقُوا اللَّهَ ۖ إِنَّ اللَّهَ شَدِيدُ الْعِقَابِ

"ዐቂቃህ" عَقِيقه ማለት አዲስ ለተወለደ ሕፃን ልጅ የሚታረድ መስዋዕት የሚደረግ እርድ ነው። የተወደደ እና የተፀና የተከበደ ነቢያዊ"ﷺ" ፈለግ የሆነ እርድ ነው። ዐቂቃህ ማረድ "ማሱና ሙአከዳ" ማለትም በጣም የጠበቀ እና የተወደደ ሱናህ ነው። የዐቂቃህ ዓላማው የተደነገገበት ምክንያት ለአላህ ምስጋና ለማድረስ ነው። ይህም አንድ ሰው ልጅ ስለተወለደለት በመደሰት በ 7ኛው ቀን ደስታውን ለመግለፅ፣ ይህንንም ደስታውን ሰዎች እንዲያውቁት ለማድረግ እና የተወለደውም ልጅ የማን እንደሆነ ለማሣወቅ ነውና። አላህ ደግሞ ልጁን እንደሚጠብቀው፥ እንዲሁ ሷሊህ ልጅ እንዲሆንለት ምክንያትም እንዲሆነው የሚደረግ አርዶ ሰውን የማብላት ሥርዓት ዐቂቃህ ይባላል፦
ሱነን ኢብኑ ማጃህ መጽሐፍ 27, ሐዲስ 3285
ሠሙራህ እንደተረከው፦ "ነቢዩ"ﷺ" እንዲህ አሉ፦ *"ማንኛውም ሕጻን በዐቂቃው መውጣት አለበት። በሰባተኛው ቀን እርድ ይታረድለት፣ የራሱ ጸጉር ይላጭ እንዲሁ ስም ይውጣለት"*። عَنْ سَمُرَةَ، عَنِ النَّبِيِّ ـ صلى الله عليه وسلم ـ قَالَ ‏ "‏ كُلُّ غُلاَمٍ مُرْتَهَنٌ بِعَقِيقَتِهِ تُذْبَحُ عَنْهُ يَوْمَ السَّابِعِ وَيُحْلَقُ رَأْسُهُ وَيُسَمَّى

በአብዛኞቹ ሙሥሊም ምሁራን እንዳሉት ዐቂቃህ መደረግ ያለበት ትልቅ ሱናህ ነው፥ እንደ አንዳንድ ምሁራን ደግሞ ዐቂቃ ማድረግ ዋጅብ ማለትም የውዴታ ግዴታ ነው የሚሉ ዑለማዎችም አሉ። በላጩና የተመረጠው የዐቂቃህ ማውጫ ጊዜም ልጅ በተወለደ በሰባተኛው ቀን ነው የሚሆነው።

ወላጆች አሊያም አያቶች ማለትም የወላጅ አባት እና እናት ለልጃቸው አሊያም ለልጅ ልጃቸው ዐቂቃህ ማውጣት አለባቸውም ይችላሉም።
የተወለደው ልጅ ወንድ ከሆነ ሁለት በግ ወይም ሁለት ፍየል ሴት ከሆነች ደግሞ አንድ በግ ወይም አንድ ፍየል ሊታረድ ይወደዳል።

እንዲሁም ስሙን ደህና ኢሥላማዊ ስም በመምረጥ ሊጠራው ይገባል።
ለምሳሌ ወንድ ከሆነ ዐብዱራሕማን፣ ዐብዱላህ፣ ሙሐመድ ወዘተ ....ሲሆን ሴት ከሆነችም ደግሞ አሲያ፣ መሪየም፣ ኸዲጃ፣ ፈጢማ ወዘተ...ብሎ ስም ቢያወጣላቸው ይወደዳል።

የመስኩ ምሁራን፦ "ሰባተኛው ቀን ያልታረደ እንደሆነ በ14ኛው ቀን ሊታረድ ይችላል ያም ካልሆነ በ 21ኛው ቀን ቢያወጣ ችግር የለውም" ይላሉ። በአጠቃላይ አንድ ልጅ እስኪጎረምስ ድረስ ዐቂቃህ ማውጣት ይችላል የሚሉ ዐሊሞች አሉ፣ እናም ቀኑ አልፎዋል ብለን ይህን የጠበቀና የተወደደ የነቢያችን"ﷺ" ሱናህ ከመተግበር አንዘናጋ። ዑለማዎች፦ "ምን አልባት ሕፃኑ ሰባት ቀን ሳይሞላው የሞተ እንደሆነ ዐቂቃህ ማረዱ አስፈላጊ አይሆንም" ብለዋል።

አንድ ሰው በህፃንነቱ ወላጆቹ ዐቂቃህ ካላወጡለትና ትልቅ ሰው ከሆነ በሁዋላና አቅሙ ካለው ጓደኞቹን ሰብስቦ አላማውን ነግሯቸው ማለትም ዐቂቃህ እንደሆነ ነግሯቸው ዐቂቃህ ማውጣት ይችላል። ስለዚህ ዕድሜያችን የፈለገ ያህል ቢሆንም ዐቂቃን ነይተን ማውጣት እንችላለንና አንዘናጋ።

የታረደው እንሠሣ ሥጋው በዒድ አል-አድሃ በዓል እንደሚደረገው ሁሉ ሦስት ቦታ መከፈል አለበት። አንድ ሦስተኛው- ለድሃ፣ አንድ ሦስተኛው- ለጓደኞች እና አንድ ሦስተኛው ደግሞ ለቤተሰብ ይሠጣል።
አንድ ሰው የታረደውን ሥጋ ሁሉንም ለድሆችና ችግረኛ ሰዎች መስጠት ይችላል።

ከወንድም ወሒድ ዑመር
https://tttttt.me/Wahidcom

ወሠላሙ ዐለይኩም
ሪባ

በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው።

2፥278 እናንተ ያመናችሁ ሆይ! *"አላህን ፍሩ፡፡ "ከአራጣም የቀረውን ተዉ"፡፡ አማኞች እንደኾናችሁ ተጠንቀቁ"*፡፡ يَا أَيُّهَا الَّذِينَ آمَنُوا اتَّقُوا اللَّهَ وَذَرُوا مَا بَقِيَ مِنَ الرِّبَا إِن كُنتُم مُّؤْمِنِينَ

"ምጣኔ ሃብት"economy" እሳቤ ውስጥ በዋነኝነት ድርሻ የሚወስደው ንዋይ ነው፥ "ንዋይ" ማለት "ገንዘብ"money" ማለት ሲሆን ይህንን ንዋይ በአላፍትና የሚይዙ ደግሞ ዐቃቤ ንዋይ"banker" ይባላሉ። ቤተ-ንዋይ"bank" ገንዘብን ለግለሰብ ወይም ለተቋማት የማስቀመጥ እና የተቀመጠውን ገንዘብ ለሌሎች ግለሰብ ወይም ተቋማት የማበደር ተግባር የሚያከናውን ተቋም ነው፥ ቤተ-ንዋይ የኢኮኖሚው ዘርፍ ዋነኛ ተዋናይ እና ለማህበራዊ ግብይት መሠረት ነው።

እዚህ ድረስ ከተግባባን ዛሬ ያሉት የምዕራባውያን ቤተ-ንዋይ ተቋማት ዋነኛ ዓላማ ካፒታል ያላቸውን ግለሰብ ወይም ተቋማት ከሌላቸው ወይም ብድር ከሚፈልጉ አልያም ማደግን ከሚፈልጉ ግለሰብ ወይም ተቋማት ጋር ማገናኘት ነው። እነዚህ በተቀማጭ መልክ ከግለሰብ ወይንም ከድርጅት ያገኙትን ገንዘብ ለተበዳሪዎች ወለድ ጨምረው በማበደር ለማትረፍ ይሰራሉ። ይህ በኢሥላም "ሪባ" ይባላል።
"ሪባ" رِّبَوٰا የሚለው ቃል "ረበየ" رَبَّيَ ማለትም "ተነባበረ" ከሚል ሥርወ-ቃል የመጣ ሲሆን "የተነባበረ" ማለት ነው፦
41፥39 አንተ ምድርን ደረቅ ኾና ማየትህም ከምልክቶቹ ነው፡፡ በእርሷም ላይ ውሃን ባወረድን ጊዜ በቡቃያዎችዋ ትላወሳለች፥ *"ትነፋለችም"*፡፡ ያ ሕያው ያደረጋት ጌታ በእርግጥ ሙታንን ሕያው አድራጊ ነው፡፡ እነርሱ በነገሩ ሁሉ ላይ ቻይ ነውና፡፡ وَمِنْ آيَاتِهِ أَنَّكَ تَرَى الْأَرْضَ خَاشِعَةً فَإِذَا أَنزَلْنَا عَلَيْهَا الْمَاءَ اهْتَزَّتْ وَرَبَتْ ۚ إِنَّ الَّذِي أَحْيَاهَا لَمُحْيِي الْمَوْتَىٰ ۚ إِنَّهُ عَلَىٰ كُلِّ شَيْءٍ قَدِيرٌ

"ትነፋለችም" ለሚለው አንስታይ ግስ የገባው ቃል "ረበት" رَبَتْ ሲሆን የስም መደቡ "ሪባ" رِّبَوٰا ነው። ይህ ቋንቋዊ ፍቺው ሲሆን ሃይማኖታዊ ፍቺው "ሪባ" رِّبَوٰا ማለት "ወለድ"interest" ወይም "አራጣ"Usury" ማለት ነው። አምላካችን አላህ፦ "ሪባን የተነባበሩ እጥፎች ሲኾኑ አትብሉ" ብሎ ከልክሎናል፦
3፥130 እናንተ ያመናችሁ ሆይ! *"ሪባን የተነባበሩ እጥፎች ሲኾኑ አትብሉ"*፡፡ ትድኑም ዘንድ አላህን ፍሩ፡፡ يَا أَيُّهَا الَّذِينَ آمَنُوا لَا تَأْكُلُوا الرِّبَا أَضْعَافًا مُّضَاعَفَةً ۖ وَاتَّقُوا اللَّهَ لَعَلَّكُمْ تُفْلِحُونَ

"ወለድ" ማለት አበዳሪ አካል በጭማሬ ንዋይ ለተበዳሪ አካል የሚያበድረው ተረፈ-እሴት ነው። ወለዱ የሚሰላው በዓመት ከመቶ እጅ ነው፥ በዚህ ስሌት ለወር ወይም ለሦስት ወር አሊያም ለመንፈቅ ተስተልቶ የሚከፈል ብድርና ዕዳ ነው።
ይህም ወለድ ሁለት አይነት ነው፥ አንደኛው የብድር ወለድ ሲሆን ሌላው የዕዳ ወለድ ነው።
የብድር ወለድ"Simple interest" ሆኖ ሲጀመር መርሑ "P" × "R" × "N" = "S" ነው። ይህ መርሕ ሲተነተን፦
1. "P" ማለት "ዋና ገንዘብ"Principal Amount" ማለት ነው።
2. "R" ማለት "የወለድ ልኬት"Interest Rate" ማለት ነው።
3. "N" ማለት "የብድር ጊዜ"Term of the loan"​ ማለት ነው።
4. "S" ማለት "የብድር ወለድ"Simple interest" ማለት ነው።
ለምሳሌ፦ 100,000 ዋና ገንዘብ ቢሆን፣ 0.05% የወለድ ልኬት ቢሆን፣ 3 ዓመት የብድር ጊዜ ቢሆን የብድር ወለዱ 15,000 ይሆናል። በዓመት ከ 100,000 ላይ 5% እየተወሰደ ለ 3 ዓመት ከተከፈለ የሚከፍለው ወለድ 15,000 ይመጣል፥ 100,000 x 0.05 x 3 =15,000 ይሆናል።

ይህ የብድር ወለድ በተባለው ሦስት ዓመት ካልተከፈለ የዕዳ ወለድ"Compound interest" ይሆናል፥ የዕዳ ወለድ የብድሩ መክፈያ ወቅት ደርሶ ተበዳሪው በቃሉ መሠረት መክፈል ሳይችል ሲቀር በብድሩ መጠን ላይ የሚደረግ ጭማሪ ነው፡፡ በዓመት ከ 100,000 ላይ 5% እየተወሰደ ለ 3 ዓመት የሚከፍለው ወለድ 4ኛ ዓመት ላይ 10% 5ኛ ዓመት ላይ 15% 6ኛ ዓመት 20% እያለ ዕዳው እየጨመረ ይመጣል።
4ኛ ዓመት ላይ 100,000 x 0.10 x 3 =30,000 ይሆናል።
5ኛ ዓመት ላይ 100,000 x 0.15 x 4 =60,000 ይሆናል።
6ኛ ዓመት ላይ 100,000 x 0.20 x 5 =100,000 ይሆናል።
እንዲህ እያለ እስከ በብድር ላይ ወለድ በልቶ ከኪሳራው እጁን ለማውጣት ማስያዣ"collateral" የቤት ካርታ፣ የሰው ዋስ እና የቋሚ ቅጥር ማስረጃ ድረስ ይሞለጭፉታል። ወለድ ወለድን ሲወልድ ዕዳው እልፍ፣ አእላፍ፣ አእላፋት፣ ትእልፊት፣ ምእልፊት እያለ ይቀጥላል።
ወለድ እየተነባበረ ሲመጣ በረከትን ያጠፋል፥ ከወለድ በሰዎች ገንዘቦች ውስጥ ይጨመር ዘንድ የሚሰጠው አላህ ዘንድ ኪሳራ እንጂ አይጨምርም፦
2፥276 *"አላህ ሪባን በረከቱን ያጠፋል፡፡ ምጽዋቶችንም ያፋፋል"*፡፡ አላህም ኃጠኢተኛ ከሓዲን ሁሉ አይወድም፡፡ يَمْحَقُ اللَّهُ الرِّبَا وَيُرْبِي الصَّدَقَاتِ ۗ وَاللَّهُ لَا يُحِبُّ كُلَّ كَفَّارٍ أَثِيمٍ
30፥39 *"ከሪባም በሰዎች ገንዘቦች ውስጥ ይጨመር ዘንድ የምትሰጡት አላህ ዘንድ አይጨምርም"*፡፡ ከምጽዋትም የአላህን ፊት የምትሹ ሆናችሁ የምትሰጡት እነዚያ ሰጪዎች አበርካቾች እነርሱ ናቸው፡፡ وَمَآ ءَاتَيْتُم مِّن رِّبًۭا لِّيَرْبُوَا۟ فِىٓ أَمْوَٰلِ ٱلنَّاسِ فَلَا يَرْبُوا۟ عِندَ ٱللَّهِ ۖ وَمَآ ءَاتَيْتُم مِّن زَكَوٰةٍۢ تُرِيدُونَ وَجْهَ ٱللَّهِ فَأُو۟لَٰٓئِكَ هُمُ ٱلْمُضْعِفُونَ

በጥንት ጊዜ "ወለድ" እራሱ ከብድር ወለድ ወደ ዕዳ ወለድ ሲሸጋገር "አራጣ" ይባላል። ነገር ግን ምዕራባውያን ለማምታታት "ወለድ" ማለት በተቋም የሚያበድር ሕጋዊ አካል ሲሆን "አራጣ" ማለት ግን በግለሰብ የሚያበድር ሕገወጥ አካል አርገው ነው ያስቀመጡት። በተቋም ደረጃ በወለድ የሚያበድር አካል ሆነ በግለሰብ ደረጃ በወለድ የሚያበድር አካል ልዩነታቸው ሕጋዊ ሌብነት እና ሕገወጥ ሌብነት ብቻ ነው። አምላካችም አላህ፦ "ገንዘቦቻችሁን በመካከላችሁ "ያለ አግባብ" ማለትም "በቁማር፣ በሪባ፣ በጉቦ፣ በስርቆት" አትብሉ" ብሎ ከልክሎናል፦
2፥188 *"ገንዘቦቻችሁንም በመካከላችሁ ያለ አግባብ አትብሉ፡፡ እናንተም የምታውቁ ስትኾኑ ከሰዎች ገንዘቦች ከፊልን በኃጢኣት ትበሉ ዘንድ ወደ ዳኞች አትጣሏት"*፡፡ وَلَا تَأْكُلُوا أَمْوَالَكُم بَيْنَكُم بِالْبَاطِلِ وَتُدْلُوا بِهَا إِلَى الْحُكَّامِ لِتَأْكُلُوا فَرِيقًا مِّنْ أَمْوَالِ النَّاسِ بِالْإِثْمِ وَأَنتُمْ تَعْلَمُون

ነገር ግን፦ "ከእናንተ በመዋደድ የኾነችውን "ንግድ" ማለትም "መግዛትና መሸጥ" ብሉ" ብሎናል፦
4፥29 እናንተ ያመናችሁ ሆይ! *"ገንዘቦቻችሁን በመካከላችሁ ያለ አግባብ አትብሉ፡፡ ግን ከእናንተ በመዋደድ የኾነችውን ንግድ ብሉ"*፡፡ ነፍሶቻችሁንም አትግደሉ፡፡ አላህ ለእናንተ አዛኝ ነውና፡፡ يَا أَيُّهَا الَّذِينَ آمَنُوا لَا تَأْكُلُوا أَمْوَالَكُم بَيْنَكُم بِالْبَاطِلِ إِلَّا أَن تَكُونَ تِجَارَةً عَن تَرَاضٍ مِّنكُمْ ۚ وَلَا تَقْتُلُوا أَنفُسَكُمْ ۚ إِنَّ اللَّهَ كَانَ بِكُمْ رَحِيمًا

ነጥብ አንድ
"ግብይት"
ኢሥላም አጠቃላይ የሕይወት ዘይቤ ይዟል፥ ይህም ዘይቤ መንፈሳዊ፣ ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊ እና ፓለቲካዊ ዘይቤ ነው። የኢሥላም ምጣኔ ሀብት ከካፒታሊዝም ሆነ ከሶሻሊዝም የተለየ እሳቦት እና ርዕዮት ነው። በኢሥላም ምጣኔ ሀብት "ሙዓመላት" معاملات‎ ማለትም "ግብይት"transaction" ይፈቀዳል። ይህ ግብይት የሸቀጥ ንዋይ"Commodity money" ላይ መሠረት ያረገ ነው፥ የሸቀጥ ንዋይ የሚባሉት በራሳቸው የራሳቸው የሆነ ዋጋ ያላቸው ከብት፣ እህል፣ ዛጎል፣ ጨው፣ መዳብ፣ ብረት፣ ብር፣ ወርቅ ወዘተ ናቸው።

ዛሬ ያለው የወለድ ቤተ-ንዋይ ግን የወረቀት ንዋይ"Fiat money" ግብይት ነው። የወረቀት ንዋይ አጀማመሩ ወርቅና ብር ነጋዴወች ለደንበኞቻቸው ደረሰኝ በመጻፍ፥ ያንን ደረሰኝ ደምበኞች በማምጣት በፈለጉት ሰዓት ወርቁንና ብሩን ማግኘት ቻሉ። ቀስ በቀስ ደረሰኙ በወርቁና በብሩ ቦታ ተተክቶ እንደ ሙሉ ገንዘብ በመሥራት የወረቀት ገንዘብ ለመጀመሪያ ጊዜ በቻይና በሶንግ ሥርወ-መንግስት በ 970 ድኅረ-ልደት"AD" ተጀመረ። የወረቀት ንዋይ በራሳቸው የራሳቸው የሆነ ዋጋ የላቸውም፥ ለምሳሌ ከተልባ እግር የተሰራው ዶላር በራሱ ዋጋ የለውም። ይህ አይነት የወረቀት ገንዘብ ዋጋው የሚመነጨው የአንድ አገር መንግሥት ሕጋዊ መገበባያ ብሎ ስላወጀው ብቻ ነው እንጂ ውስጡ ምንም ዋጋ የለውም። የወረቀት ገንዘብ ሸቀጥን ያለ ዋጋ በባዶ ነገር መመዝበዣ ቁማር ነው። የዓለምን ምጣኔ ሃብት ቀውስና ዝቅጠት መንስኤና ውጤት ይህ የወረቀት ንዋይ ነው። የወረቀት ገንዘብ ተለዋዋጭ"variable" የሚባሉት የዋጋ ርግበት"Deflation" እና የዋጋ ንረት"Inflation" ይታይበታል። የምንዛሪ ዋጋ ቅነሳ"Devaluation" ሆነ የምንዛሪ ዋጋ ጭመራ"Revaluation" መዘዝና ጠንቅ የወረቀት ንዋይ ነው።
ነጥብ ሁለት
"ብድር"
ዕዳ ማለት ከዜሮ በታች መቀነስ (-) ሲሆን አሉታዊ"negative" ነገር ነው፥ ትርፍ ደግሞ ከዜሮ በላይ መደመር(+) አውንታዊ"posetive" ነገር ነው። ብድር እዳ ነው፥ ክምችት ትርፍ ነው። የኢሥላም ቤተ-ንዋይ መበደር እና ማበደር ያቀፈ መርሕ አለው።
ይህም ብድር "ቀርዱል ሐሠን" ይባላል፥ "ቀርድ" قَرْض ማለት "ብድር" ማለት ሲሆን ከወለድ ነጻ የሆነው ብድር "ቀርዱል ሐሠን" قَرْض الْحَسَن ይባላል። በዚህ ሥርዓት አበዳሪ ቤተ-ንዋይ ሲያበድር በብድሩ ላይ ምንም አይነት ፐርሰንት የብድር ወለድ አይወስድም።

ነገር ግን አበዳሪ ተበዳሪው በተበደረው ንዋይ ከሚያተርፈው የሙአለ-ንዋይ"investment" ትርፍ ላይ በፐርሰንት ይወስዳል፥ ይህ ንግድ ሲሆን "ሙዷረባህ" ይባላል። "ሙዷረባህ" مضاربة ማለት የተበዳሪውን ትርፉንና ኪሳራን መጋራት ማለት ነው። ተበዳሪም ከአበዳሪ ቤተ-ንዋይ "ሙሻረካህ" مشاركة ማለትም "አክሲዮን" ማለት ሲሆን የቤተ-ንዋዩ ደንበኛ ትርፍን ለመጋራት የሚሰጥበት ዕድል ነው።
ይህ ለሁለቱም ለደንበኛው ለቤተ-ንዋዩ "ተካፉል" تكافل‎ ማለትም "ዋስትና" ይሆናል። ለምሳሌ 100,000 ትርፍ ቢገባ 40,000 ለቤተ-ንዋይ 60,000 ደግሞ ለደንበኞች የሚከፋፈል ነው።

በተጨማሪ የኢሥላም ቤተ-ንዋይ የገንዘብ አስቀማጩን ገንዘብ በመጠቀም ንብረት ገዝተው ለተበዳሪው ይሸጣሉ። ይህ ሙራባሓህ ይባላል፥ "ሙራባሓህ" مرابحة‎ ማለት የዱቤ ሽያጭ ነው፥ ዐቃቤ ንዋይ አንድን ንብረት የገዛበትን ዋጋ እና ትርፉን ለገዢ በማሳወቅ የሚደረግ ግብይት ነው።
የኢሥላም ቤተ-ንዋይ አንድ ሙዕሚን ምንም "ንብረት"property" ባይኖረው እንኳን ፕሮፖዛሉ ሃላልና ተጨባጭ መሆኑን አይቶ ያበድረዋል። የሙአለ ንዋይ ፍሰት"investment" አነስተኛና ትንሽን ይሁን ከፍተኛና ብዙ ይህ በተቋም የሚተዳደር ትልቅ የገንዘብ መጠን"finance" ይህንን ለመሸፈን ግዴታው ነው።

ይህ እሳቦት ለዓለማችን ምጣኔ ሃብት ርዕዮትና አብዮት እንደሚሆን ኢንሻላህ ተስፋ አለን። በምድሪቱ ላይ ረሃብ ያለው ምግብ ታጥቶ አሊያም ለእህል የሚሆን ተስማሚ የእርሻ ቦታ ታጥቶ ሳይሆን ክፋት፣ ጭካኔ፣ ስግብግብነት፣ ጥላቻ ስላለ ነው። በምድሪቱ ላይ ድህነት ያለው 80% የሚሆነውን የምድራችን ሃብት 20% የሚሆኑ የምድራችም ሃብታሞች በሞኖፓልና በስግብግብነት ስለያዙት ነው። ይህ የኢሥላም ምጣኔ ሃብት በፕላኔታችን ላይ ቢሰፍን ራብ፣ ቸነፈር፣ እርዛት፣ ጦርነት አይኖርም ነበር።

እንግዲህ ስለ ኢሥላም ሪባ በግርድፉና በሌጣው ይህንን ይመስላል፥ ደርዝና ፈርጅ ባለው መልክና ልክ ማብራራቱን ደግሞ እዚህ መስክ ላይ ለተሰማሩት ለመስኩ ምሁራን ትቼዋለው። ይህንን አርስት ለመጦመር ያነሳሳኝ ሚሽነሪዎች፦ "ሪባ ማለት አራጣ እንጂ ወለድ ማለት አይደለም፥ የኢሥላም ቤተ-ንዋይ አያስፈልግም" ብለው ለደሶኮሩት ዲስኩር መልስ ለመስጠት ነው። ኢሥላም በጥራዝ ጠለቅ ዕውቀት አቀንቃኝ ሲሆን በጥራዝ ነጠቅ ዕውቀት ተቀናቃኝ አይጠፋም። እኛም የኢሥላም ዐቃቤና አበጋዝ እንደመሆናችን መጠን መልስ መስጠት ተገቢ ነው። እነዚህ ዕቡያን የሚቆረቆሩለት የምዕባውያን የወለድ ብድር በራሳቸው ባይብል ሃራም ነው፦
ዘሌዋውያን 25፥36 *"ወንድምህ ከአንተ ጋር ይኖር ዘንድ ከእርሱ ምንም ወለድ ወይም ትርፍ አትውሰድ"*።
ዘሌዋውያን 25፥37 ነገር ግን አምላክህን ፍራ። *"ብርህን በወለድ አታበድረው"*፤ መኖህንም በትርፍ አትስጠው።
ዘዳግም 23፥19 *"ለወንድምህ በወለድ አታበድር"*፤ የብር ወይም የእህል ወይም የማናቸውንም ነገር ሁሉ ወለድ አትውሰድ።
ዘዳግም 23፥20 አምላክህ እግዚአብሔር ልትወርሳት በምትገባባት ምድር በሥራህ ሁሉ ይባርክህ ዘንድ *"ለወንድምህ በወለድ አታበድር"*።

ሙሥሊሙን በኢኮኖሚ ለማሳቀቅና ለማሸማቀቅ ሙከራ መቼም አይሳካም። ወደው ዐውቀው በድፍረት ተገደው ሳያውቁ በስህተት በአፋቸው የሚገዘግዙ፥ በብዕራቸው የሚበርዙ፥ ኢሥላም እንደ አቧራ የሚበን እንደ ጉም የሚተን መስሏቸው ከሆነ ሲበዛ ቂሎች ናቸው። ክርስትና በአውሮፓ ላይ የተሸመነበት ድርና ማግ እንደሆነ ሁሉ የተዋረደበት ማቅ፣ የተገነዘበት በፍታ፣ የተከፈነበት ግምዣ ነው። የምዕራቡን ካፒታል ደግፎ ኢሥላምን ለማነወርና ለማብጠልጠል ዐቅሙም፣ ሙራሉም፣ ብቃቱም ሆነ ዕውቀቱም የላቸውም። ግን በሞቀበት ለመጣድ የማያውቁትን ይዘባርቃሉ።

ስለ ሪባ፣ ስለ ምጣኔ እና ስለ ኢሥላም ቤተ--ንዋይ እነዚህን ዋቢ መጽሐፍት ይመልከቱ፦
1. Critical Issues on Islamic Banking and Financial Markets. by Saiful Azhar Rosly 2005
2. Islamic Finance for Dummies. By Faleel Jamaldeen 2012
3. Islamic finance in the global economy. by Ibrahim Warde 2000
4. Islamic Legal Maxims & Their Application in Islamic Finance. by Mohamad Akram Laldin, Mohamad Fairooz Abdul Khir, Riaz Ansari, and Said Bouheraoua. 2013

ከወንድም ወሒድ ዑመር
https://tttttt.me/Wahidcom

ወሠላሙ ዐለይኩም
ተወኩል

በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ በጣም አዛኝ በሆነው።

64፥13 *"አላህ ከእርሱ በቀር አምላክ የለም፤ በአላህም ላይ አማኞቹ ይመኩ"*፡፡ اللَّهُ لَا إِلَـٰهَ إِلَّا هُوَ ۚ وَعَلَى اللَّهِ فَلْيَتَوَكَّلِ الْمُؤْمِنُونَ

አንድ ጊዜ አሜሪካ አገር ውስጥ ትልቅ ድልድል ለመሥራት ፉቲንግ ፓድ ሲቀበር ብዙ የድልድይ ባለሙያዎች ባሕር ውስጥ እየወደቀ ተቸገሩ፥ በዚህ ጊዜ ሰው ቢዎድቅ አየር ላይ እንዲይዝ ዙሪያውን መረብ ተደረገ። ከዚያ ጊዜ በኃላ ማንም ሰው አልወደቀም፥ ምክንያቱም ሰራተኞቹ፦ "ብንወድቅ መረቡ ይይዘናል" ብለው በመረቡ ላይ ትምክት፣ አመኔታ፣ መተማመኛ ስለጣሉ ነው። በአላህ ላይ መመካትም ከዚህ ናሙና ጋር ይቀራረባል። አምላካችን አላህ ለእስራኤልም ልጆች፦ "ከእኔ ሌላ መጠጊያን አትያዙ" በማለት ተናግሯል፦
17፥2 ሙሳንም መጽሐፉን ሰጠነው፡፡ ለእስራኤልም ልጆች መሪ አደረግነው፡፡ *"ከእኔ ሌላ መጠጊያን አትያዙ፤ አልናቸውም"*፡፡ وَآتَيْنَا مُوسَى الْكِتَابَ وَجَعَلْنَاهُ هُدًى لِّبَنِي إِسْرَائِيلَ أَلَّا تَتَّخِذُوا مِن دُونِي وَكِيلًا

"አል-ወኪል" الْوَكِيل ማለት "መመኪያ" "መጠጊያ" "መሸሸጊያ" ማለት ሲሆን በቁርኣን ከተገለጹ 99 ስሞች አንዱ ነው፦
39፥9 እርሱም የምሥራቅና የምዕራብ ጌታ ነው፡፡ *"ከእርሱ ሌላ አምላክ የለም፡፡ መጠጊያ አድርገህም ያዘው"*፡፡ رَّبُّ الْمَشْرِقِ وَالْمَغْرِبِ لَا إِلَـٰهَ إِلَّا هُوَ فَاتَّخِذْهُ وَكِيلًا

አላህን መጠጊያ መመኪያ፣ መጠጊያ፣ መሸሸጊያ አድርጎ የያዘ ሰው ልክ እንደዛ በመረቡ ላይ እንደተማመኑት የድልድይ ባለሙያ ምንም አይነካቸውም። በአላህ ላይ መመካት "ተወኩል" تَوَكُّل‎ ይባላል። ሰይጧን በእነዚያ ባመኑት እና በአላህ ላይ በሚመኩት ላይ ስልጣን የለውም፦
16፥99 *"እርሱ በእነዚያ ባመኑት እና በጌታቸው ላይ በሚጠጉት ላይ ለእርሱ ስልጣን የለውምና"*፡፡ إِنَّهُ لَيْسَ لَهُ سُلْطَانٌ عَلَى الَّذِينَ آمَنُوا وَعَلَىٰ رَبِّهِمْ يَتَوَكَّلُونَ

"በሚጠጉት" ለሚለው ቃል የገባው "የተወከሉን" يَتَوَكَّلُون ሲሆን ቁርጥ ሐሳብም ባደረጉ ጊዜ አላህ በቂዬ ነው ብለው በአላህ ላይ ሙሉ ለሙሉ የተወከሉ ባሮቹ ደግሞ "ሙተወከሉን" مُتَوَكِّلُون ይባላል፦
39፥38 *«አላህ በቂዬ ነው፡፡ በእርሱ ላይ ተመኪዎች ይመካሉ»* በል፡፡ قُلْ حَسْبِيَ اللَّهُ ۖ عَلَيْهِ يَتَوَكَّلُ الْمُتَوَكِّلُونَ
6፥159 *"ቁርጥ ሐሳብም ባደረግህ ጊዜ በአላህ ላይ ተመካ፡፡ አላህ በእርሱ ላይ ተመኪዎችን ይወዳልና"*፡፡ فَإِذَا عَزَمْتَ فَتَوَكَّلْ عَلَى اللَّهِ ۚ إِنَّ اللَّهَ يُحِبُّ الْمُتَوَكِّلِينَ

አላህ በእርሱ ላይ ተመኪዎችን ይወዳል፥ በአላህ ላይ መመካት ሲሳይም ያመጣል። እርሱም፦ "በአላህም ላይ አማኞቹ ይመኩ" ይለናል፦
64፥13 *"አላህ ከርሱ በቀር አምላክ የለም፤ በአላህም ላይ አማኞቹ ይመኩ"*፡፡ اللَّهُ لَا إِلَـٰهَ إِلَّا هُوَ ۚ وَعَلَى اللَّهِ فَلْيَتَوَكَّلِ الْمُؤْمِنُونَ
ጃምዒ አት-ቲርሚዚይ መጽሐፍ 1, ሐዲስ 79
ዑመር"ረ.ዐ." እንደተረከው፦ "የአላህ መልእክተኛም"ﷺ" እንዲህ ሲሉ ሰምቻለው፦ *"እናንተ በአላህ ላይ በትክክል ተመክታችሁ ብትጠጉ ልክ ወፎችን በጠዋት በተራቡ ጊዜ እንደሚረዝቀውና ሆዳቸውን እንደሚሞላ ይረዝቃችኃል"*። عن عمر رضي الله عنه قال‏:‏ سمعت رسول الله صلى الله عليه وسلم يقول ‏:‏ ‏ "‏لو أنكم تتوكلون على الله حق توكله لرزقكم كما يرزق الطير ، تغدو خماصاً وتروح بطانا

በአላህ ላይ መመካት ሪዝቅ ማስገኘት ብቻ ሳይሆን ከማንወጣው ችግር ውስጥም ይታደገናል። "ሐሥቡነል ሏህ ወኒዕመል ወኪል" حَسْبُنَا اللَّهُ وَنِعْمَ الْوَكِيل ማለት "በቂያችንም አላህ ነው፥ ምን ያምርም መጠጊያ" ማለት ነው። ሰዎች አማንያንን ሲያስፈራሯቸው እና ኢብራሂም በእሳት ውስጥ ሆኖ የተናገረው ይህንን ቃል ነው፦
3፥173 እነዚያ ሰዎቹ ለእነርሱ፡- «ሰዎች ለእናንተ ጦርን አከማችተዋልና ፍሩዋቸው» ይሉዋቸውና ይህም እምነትን የጨመረላቸው *«በቂያችንም አላህ ነው፥ ምን ያምርም መጠጊያ!»* ያሉ ናቸው፡፡ الَّذِينَ قَالَ لَهُمُ النَّاسُ إِنَّ النَّاسَ قَدْ جَمَعُوا لَكُمْ فَاخْشَوْهُمْ فَزَادَهُمْ إِيمَانًا وَقَالُوا حَسْبُنَا اللَّهُ وَنِعْمَ الْوَكِيلُ
ኢማም ቡኻርይ መጽሐፍ 65, ሐዲስ 4564
ኢብኑ ዐባሥ እንደተረከው፦ "ኢብራሂም በእሳት ውስጥ እያለ የመጨረሻ ንግግሩ፦ *"በቂያችንም አላህ ነው፥ ምን ያምርም መጠጊያ"* የሚል ነበር"። عَنِ ابْنِ عَبَّاسٍ، قَالَ كَانَ آخِرَ قَوْلِ إِبْرَاهِيمَ حِينَ أُلْقِيَ فِي النَّارِ حَسْبِيَ اللَّهُ وَنِعْمَ الْوَكِيلُ‏

አምላካችን አላህ ሙተወከሉን ከሚላቸው ባሮቹ ያድርገን! አሚን።

ከወንድም ወሒድ ዑመር
https://tttttt.me/Wahidcom

ወሠላሙ ዐለይኩም
የአላህ ይቅርታ እና ምሕረት

በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡

15፥49 *"ባሮቼን እኔ ይቅርባዩ መሓሪው እኔው ብቻ መኾኔን ንገራቸው"*፡፡ نَبِّئْ عِبَادِي أَنِّي أَنَا الْغَفُورُ الرَّحِيمُ

በቁርኣን ከተጠቀሱ ዘጠና ዘጠኝ ከአላህ የተዋቡ ስሞች መካከል “አል-ገፋር” الغَفَّار ወይም “አል-ገፉር” الغَفُور ሲሆን “ይቅርባዩ” ማለት ነው። “መግፊራህ” مَّغْفِرَة ማለት “ይቅርታ” ማለት ሲሆን የእርሱ ባሕርይ ነው። እንዲሁ በቁርኣን ከተጠቀሱ ዘጠና ዘጠኝ ከአላህ የተዋቡ ስሞች መካከል “አር-ረሒም” ٱلرَّحِيمِ ማለት ደግሞ “እጅግ በጣም መሓሪ” ማለት ነው፥ የአር-ረሕማን ባሕርይ ደግሞ “ረሕማህ” رَّحْمَةً ማለትም "ምሕረት ነው። አምላካችን አላህ በመጀመሪያ መደብ እና በሦስተኛ መደብ፦ "እኔ ይቅርባዩ መሓሪው ነኝ" ይላል፦
15፥49 *"ባሮቼን እኔ ይቅርባዩ መሓሪው እኔው ብቻ መኾኔን ንገራቸው"*፡፡ نَبِّئْ عِبَادِي أَنِّي أَنَا الْغَفُورُ الرَّحِيمُ
49፥5 ወደ እነርሱም እስክትወጣ ድረስ እነርሱ በታገሱ ኖሮ ለእነርሱ በላጭ በኾነ ነበር፡፡ *"አላህም እጅግ ይቅርባይ መሓሪ ነው"*፡፡ وَلَوْ أَنَّهُمْ صَبَرُوا۟ حَتَّىٰ تَخْرُجَ إِلَيْهِمْ لَكَانَ خَيْرًۭا لَّهُمْ ۚ وَٱللَّهُ غَفُورٌۭ رَّحِيمٌۭ

የአላህ የይቅርታው ጥልቀትና ስፋት"un-comprehension፥ የምሕረቱ ምጥቀትና ልቀት"un-apprehension" የሚያጅብ ነው፦
ኢማም ቡኻርይ መጽሐፍ 81, ሐዲስ 56
ዓኢሻህ እንደተረከችው፦ "ነቢዩም"ﷺ" እንዲህ አሉ፦ *"ለሰናይ ሥራ ጣሩ፥ ተቃረቡ፥ ተበሰሩ። ማንም በሥራው ጀነት አይገባም። እነርሱም፦ "እርስዎም የአላህ መልእክተኛ ሆይ! እርሳቸውም፦ "እኔም ብሆን አላህ ይቅርታው እና ምሕረቱን እስከሚለግሰኝ ድረስ"*። عَنْ عَائِشَةَ، عَنِ النَّبِيِّ صلى الله عليه وسلم قَالَ ‏"‏ سَدِّدُوا وَقَارِبُوا، وَأَبْشِرُوا، فَإِنَّهُ لاَ يُدْخِلُ أَحَدًا الْجَنَّةَ عَمَلُهُ ‏"‌‏.‏ قَالُوا وَلاَ، أَنْتَ يَا رَسُولَ اللَّهِ قَالَ ‏"‏ وَلاَ أَنَا إِلاَّ أَنْ يَتَغَمَّدَنِي اللَّهُ بِمَغْفِرَةٍ وَرَحْمَةٍ

መልካም ሥራ ለጀነት ሰበብ እንጂ ሙሥሊም ጀነት የሚገባው በአላህ ይቅርታና ምሕረት ነው። የአላህን ይቅርታ እና ምሕረት ደግሞ የሚገኘው በተውበት በመቶበት ነው፦
16፥119 ከዚያም ጌታህ ለእነዚያ በስሕተት መጥፎን ለሠሩና ከዚያም ከዚህ በኋላ *"ለተጸጸቱ ሥራቸውንም ላበጁ ጌታህ ከእርሷ በኋላ በእርግጥ ይቅርባይ መሓሪ ነው"*፡፡ ثُمَّ إِنَّ رَبَّكَ لِلَّذِينَ عَمِلُوا السُّوءَ بِجَهَالَةٍ ثُمَّ تَابُوا مِن بَعْدِ ذَٰلِكَ وَأَصْلَحُوا إِنَّ رَبَّكَ مِن بَعْدِهَا لَغَفُورٌ رَّحِيمٌ
3፥89 *"እነዚያ ከዚህ በኋላ ንስሓ የገቡና ሥራቸውን ያሳመሩ ሲቀሩ፡፡ እነዚህንስ ይምራቸዋል፥ አላህ ይቅርባይ መሓሪ ነውና"*፡፡ إِلَّا الَّذِينَ تَابُوا مِن بَعْدِ ذَٰلِكَ وَأَصْلَحُوا فَإِنَّ اللَّهَ غَفُورٌ رَّحِيمٌ

ተውበት ሦስት ሸርጦች አሉት፥ እርሱም፦ ያንን እኩይ ሥራ መተው፣ በሠሩት እኩይ ሥራ መጸጸት እና ወደዚያ እኩይ ሥራ ላለመመለጥ ቆራጥነት ነው። አምላካችን አላህ በተውበት ወደ እርሱ ለሚመለሱ ባሮቹ የቱንም ያክል ወንጀላቸው ቢበዛ እጅግ በጣም ይቅርባይና መሓሪ ነው፦
ጃምዒ አት-ቲርሚዚይ መጽሐፍ 48, ሐዲስ 171
አነሥ ኢብኑ ማሊክ የአላህ መልእክተኛ"ﷺ" እንዲህ ሲሉ ሰምቻቸዋለሁ ብሎ እንደተረከው፦ "አላህም አለ፦ *"የአደም ልጅ ሆይ! አንተ በጠራከኝ እና በከጀልከኝ ግዜ ከአንተ ምንም ኀጢአት ቢኖርም እምርሐለሁ፥ ኀጢአትህ ቢበዛም ምንም አይመስለኝም። የአደም ልጅ ሆይ! ኀጢአትህ እስከ ሰማይ ደመና ቢደርስ እንኳን ከዚያም ይቅርታን ከጠየቅከኝ ይቅር እልካለው። የአደም ልጅ ሆይ! አንተ ምድርን የሞላ ኀጢአት ይዘህ በእኔ ግን ሳታጋራ ወደ እኔ ብትመጣ ከዚያም ብትገናኘኝ እኔም በሙሉ ይቅርታ ወደ አንተ እመጣለው"*። يَقُولُ حَدَّثَنَا أَنَسُ بْنُ مَالِكٍ، قَالَ سَمِعْتُ رَسُولَ اللَّهِ صلى الله عليه وسلم يَقُولُ ‏ "‏ قَالَ اللَّهُ يَا ابْنَ آدَمَ إِنَّكَ مَا دَعَوْتَنِي وَرَجَوْتَنِي غَفَرْتُ لَكَ عَلَى مَا كَانَ فِيكَ وَلاَ أُبَالِي يَا ابْنَ آدَمَ لَوْ بَلَغَتْ ذُنُوبُكَ عَنَانَ السَّمَاءِ ثُمَّ اسْتَغْفَرْتَنِي غَفَرْتُ لَكَ وَلاَ أُبَالِي يَا ابْنَ آدَمَ إِنَّكَ لَوْ أَتَيْتَنِي بِقُرَابِ الأَرْضِ خَطَايَا ثُمَّ لَقِيتَنِي لاَ تُشْرِكُ بِي شَيْئًا لأَتَيْتُكَ بِقُرَابِهَا مَغْفِرَةً

ማንም ሙሥሊም በመጨረሻይቱ ዓለም በአላህ እስካላሻረከ ድረስ ለሠራው እኩይ ሥራ ተቀጥቶ ቅጣቱን ሲጨርስ በአላህ ይቅርታና ምሕረት ወደ ጀነት ይገባል፦
ኢማም ቡኻርይ መጽሐፍ 97, ሐዲስ 113
አቡ ዘር እንደተረከው፦ "ነቢዩም"ﷺ" *"እንዲህ አሉ፦ ጂብሪል ወደ እኔ መጥቶ እንዲህ ሲል አበሰረኝ፦ "ማንም ምንም ነገር በአላህ ላይ ያላሻረከ ወደ ጀነት ይገባል። እኔም፦ "ቢሰርቅም፥ ቢያመነዝርም? ብዬ ጠየኩት። እርሱም፦ "ቢሰርቅም፥ ቢያመነዝርም" አለኝ"*። عَنِ الْمَعْرُورِ، قَالَ سَمِعْتُ أَبَا ذَرٍّ، عَنِ النَّبِيِّ صلى الله عليه وسلم قَالَ ‏"‏ أَتَانِي جِبْرِيلُ فَبَشَّرَنِي أَنَّهُ مَنْ مَاتَ لاَ يُشْرِكُ بِاللَّهِ شَيْئًا دَخَلَ الْجَنَّةَ ‏"‌‏.‏ قُلْتُ وَإِنْ سَرَقَ وَإِنْ زَنَى قَالَ ‏"‏ وَإِنْ سَرَقَ وَإِنْ زَنَى
ኢማም ቡኻርይ መጽሐፍ 10, ሐዲስ 201
አቢ ሁረይራ እንደተረከው፦ “የአላህ መልእክተኛም”ﷺ” እንዲህ አሉ፦…. *”ከሰዎች መካከል በሥራቸው ለዘላለም በጀሃነም ሲዘወትሩ ሌሎች ደግሞ ቅጣት ተቀብለው ከጀሃነም ይወጣሉ፣ አላህ የሻው ከጀሃነም ሰዎች መካከል ምሕረት ያደርግለታል። ለመላእክትም፦ “እርሱን ብቻ ያመለከውን አውጡ” ብሎ ያዛቸዋል”*። تَخْطَفُ النَّاسَ بِأَعْمَالِهِمْ، فَمِنْهُمْ مَنْ يُوبَقُ بِعَمَلِهِ، وَمِنْهُمْ مَنْ يُخَرْدَلُ ثُمَّ يَنْجُو، حَتَّى إِذَا أَرَادَ اللَّهُ رَحْمَةَ مَنْ أَرَادَ مِنْ أَهْلِ النَّارِ، أَمَرَ اللَّهُ الْمَلاَئِكَةَ أَنْ يُخْرِجُوا مَنْ كَانَ يَعْبُدُ اللَّهَ
“ከሰዎች መካከል ለዘላለም በጀሃነም የሚዘወተሩ” በአላህ ላይ ያጋሩ ናቸው። አላህ በእርሱ ማጋራትን በፍጹም አይምርም። የሚያጋራን ሰው አላህ ጀነትን በእርሱ ላይ በእርግጥ እርም አደረገ፥ የአጋሪው መኖሪያውም እሳት ናት፦
4፥48 *”አላህ በእርሱ ማጋራትን በፍጹም አይምርም፡፡ ከዚህ ሌላ ያለውንም ኀጢአት ለሚሻው ሰው ይምራል፡፡ በአላህም የሚያጋራ ሰው ታላቅን ኀጢአት በእርግጥ ቀጠፈ”*፡፡ إِنَّ اللَّهَ لَا يَغْفِرُ أَن يُشْرَكَ بِهِ وَيَغْفِرُ مَا دُونَ ذَٰلِكَ لِمَن يَشَاءُ ۚ وَمَن يُشْرِكْ بِاللَّهِ فَقَدِ افْتَرَىٰ إِثْمًا عَظِيمًا
5:72 *”እነሆ በአላህ የሚያጋራ ሰው አላህ በእርሱ ላይ ገነትን በእርግጥ እርም አደረገ፤ መኖሪያውም እሳት ናት”*። ለበዳዮችም ምንም ረዳቶች የሏቸውም። إِنَّهُ مَن يُشْرِكْ بِاللَّهِ فَقَدْ حَرَّمَ اللَّهُ عَلَيْهِ الْجَنَّةَ وَمَأْوَاهُ النَّارُ ۖ وَمَا لِلظَّالِمِينَ مِنْ أَنصَارٍ

"ከዚህ ሌላ ያለውንም ኀጢአት ለሚሻው ሰው ይምራል" የሚለው ኃይለ-ቃል ይሰመርበት።
አላህ ከሺርክ ሌላ ያለውንም ኀጢአት ለሚሻው ሰው ቀጥቶት አሊያም በነቢያችን”ﷺ” ሸፋዓ ይምራል፦
ኢማም ቡኻርይ መጽሐፍ 81, ሐዲስ 155
ዒምራን ኢብኑ ሑሴይን”ረ.ዐ.” እንደተረከው፦ “ነቢዩም”ﷺ” አሉ፦ *”ጥቂት ሕዝብ ከእሳት ወጥተው ወደ ጀነት በሙሐመድ”ﷺ” ምልጃ ይገባሉ፤ ጀሀነሚዪን ተብለው ይጠራሉ*። حَدَّثَنَا عِمْرَانُ بْنُ حُصَيْن ٍ ـ رضى الله عنهما ـ عَنِ النَّبِيِّ صلى الله عليه وسلم قَالَ ‏ “‏ يَخْرُجُ قَوْمٌ مِنَ النَّارِ بِشَفَاعَةِ مُحَمَّدٍ صلى الله عليه وسلم فَيَدْخُلُونَ الْجَنَّةَ، يُسَمَّوْنَ الْجَهَنَّمِيِّينَ ‏
ኢማም ቡኻርይ መጽሐፍ 3, ሐዲስ 41
አቢ ሁረይራ እንደተረከው፦ *”እኔም፦ የአላህ መልእክተኛ”ﷺ” ሆይ! በትንሳኤ ቀን ማነው እድለኛ ሰው የእርስዎን ምልጃ የሚያገኘው? አልኩኝ፤ የአላህ መልእክተኛም”ﷺ”፦ “አቢ ሁረይራ ሆይ! ንግግር ለመማር የአንተን ቆይታ ዐውቃለው፤ እንደማስበው ስለዚህ ጉዳይ ከአንተ በፊት ማንም አልጠየቀኝም። በትንሳኤ ቀን የእኔን ምልጃ የሚያገኝ እድለኛ ሰው ከልቡ ወይም ከነፍሱ፦ “ከአላህ በስተቀር በእውነት የሚመለክ አምላክ የለም” ያለ ነው*። عَنْ أَبِي هُرَيْرَةَ، أَنَّهُ قَالَ قِيلَ يَا رَسُولَ اللَّهِ، مَنْ أَسْعَدُ النَّاسِ بِشَفَاعَتِكَ يَوْمَ الْقِيَامَةِ قَالَ رَسُولُ اللَّهِ صلى الله عليه وسلم ‏ “‏ لَقَدْ ظَنَنْتُ يَا أَبَا هُرَيْرَةَ أَنْ لاَ يَسْأَلَنِي عَنْ هَذَا الْحَدِيثِ أَحَدٌ أَوَّلُ مِنْكَ، لِمَا رَأَيْتُ مِنْ حِرْصِكَ عَلَى الْحَدِيثِ، أَسْعَدُ النَّاسِ بِشَفَاعَتِي يَوْمَ الْقِيَامَةِ مَنْ قَالَ لاَ إِلَهَ إِلاَّ اللَّهُ، خَالِصًا مِنْ قَلْبِهِ أَوْ نَفْسِهِ ‏”‌‏.‏

አምላካችን አላህ የእርሱን ይቅርታና ምሕረት አግኝተው ጀነት ከሚገቡ ባሮቹ ያድርገን! አሚን።

ከወንድም ወሒድ ዑመር
https://tttttt.me/Wahidcom

ወሠላሙ ዐለይኩም
ጽላት እና ታቦት

በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡

7፥145 *ለእርሱም በሰሌዳዎቹ ላይ ከነገሩ ሁሉ ግሳጼንና ለነገሩም ሁሉ ማብራራትን ጻፍንለት*፡፡ وَكَتَبْنَا لَهُ فِي الْأَلْوَاحِ مِن كُلِّ شَيْءٍ

“ጽሌ” ማለት “ሰሌዳ” “ፊደል” ማለት ነው፤ የጽሌ ብዙ ቁጥር “ጽላት” ሲሆን “ሰሌዳዎች” ወይም “ፊደሎች” ማለት ነው፤ በዕብራይስጥ ደግሞ “ላሁት” לֻחֹ֣ת ሲሆን በዐረቢኛ “ለውሕ” لَوْح ነው፣ አምላካችን አላህ ለሙሳ ቃላትን በፊደል ላይ ጽፎ እንደሰጠው በተከበረ ቃሉ ይናገራል፦
7፥145 *ለእርሱም በሰሌዳዎቹ ላይ ከነገሩ ሁሉ ግሳጼንና ለነገሩም ሁሉ ማብራራትን ጻፍንለት*፡፡ وَكَتَبْنَا لَهُ فِي الْأَلْوَاحِ مِن كُلِّ شَيْءٍ
7፥154 *ከሙሳም ቁጣው በበረደ ጊዜ ሰሌዳዎቹን በግልባጫቸው ውስጥ ለእነዚያ እነርሱ ጌታቸውን የሚፈሩ ለኾኑት መምሪያና እዝነት ያለባቸው ሲኾኑ ያዘ*፡፡ وَلَمَّا سَكَتَ عَن مُّوسَى الْغَضَبُ أَخَذَ الْأَلْوَاحَ ۖ وَفِي نُسْخَتِهَا هُدًى وَرَحْمَةٌ لِّلَّذِينَ هُمْ لِرَبِّهِمْ يَرْهَبُونَ

ይህን ድርጊት በፔንታተች በተመሳሳይ መልኩ ተመዝግቧል፦
ዘጸአት 24፥12 እግዚአብሔርም ሙሴን፦ ወደ እኔ ወደ ተራራው ውጣ፥ በዚያም ሁን፤ *እነርሱን ታስተምር ዘንድ እኔ የጻፍሁትን ሕግና ትእዛዝ የድንጋይም ጽላት እሰጥሃለሁ አለው*።

“ታቦት” ማለት “ማህደር” “ሰገባ” “ሳጥን” “ማደሪያ” ማለት ነው፣ በዕብራይስጥ ደግሞ “አሮውን” אֲר֖וֹן ሲሆን በዐረቢኛ “አት-ታቡት” التَّابُوتُ ነው፣ አምላካችን አላህ ስለ ታቡት እንዲህ ይለናል፦
2፥248 ነቢያቸውም ለእነርሱ፡- *«የንግሥናው ምልክት ከጌታችሁ የኾነ እርጋታ የሙሳ ቤተሰብና የሃሩን ቤተሰብ ከተውትም ቅርስ በውስጡ ያለበት መላእክት የሚሸከሙት ኾኖ “ሳጥኑ” ሊመጣላችሁ ነው*፡፡ አማኞች ብትኾኑ በዚህ ለእናንተ እርግጠኛ ምልክት አልለ» አላቸው፡፡ وَقَالَ لَهُمْ نَبِيُّهُمْ إِنَّ آيَةَ مُلْكِهِ أَن يَأْتِيَكُمُ التَّابُوتُ فِيهِ سَكِينَةٌ مِّن رَّبِّكُمْ وَبَقِيَّةٌ مِّمَّا تَرَكَ آلُ مُوسَىٰ وَآلُ هَارُونَ تَحْمِلُهُ الْمَلَائِكَةُ ۚ إِنَّ فِي ذَٰلِكَ لَآيَةً لَّكُمْ إِن كُنتُم مُّؤْمِنِينَ

“ሳጥኑ” ለሚለው ቃል የገባው “አት-ታቡት” التَّابُوتُ ነው፤ ይህ ቃል የሙሳ እናት ለጣለችው ሳጥን አገልግሎት ላይ ውሏል፦
20፥39 *«ሕፃኑን በሳጥኑ ውስጥ ጣይው*፡፡ እርሱንም ሳጥኑን በባሕር ላይ ጣይው፡፡ ባሕሩም በዳርቻው ይጣለው፡፡ ለእኔ ጠላት ለእርሱም ጠላት የኾነ ሰው ይይዘዋልና በማለት ባሳወቅን ጊዜ ለገስንልህ፡፡ أَنِ اقْذِفِيهِ فِي التَّابُوتِ فَاقْذِفِيهِ فِي الْيَمِّ فَلْيُلْقِهِ الْيَمُّ بِالسَّاحِلِ يَأْخُذْهُ عَدُوٌّ لِّي وَعَدُوٌّ لَّهُ ۚ وَأَلْقَيْتُ عَلَيْكَ مَحَبَّةً مِّنِّي وَلِتُصْنَعَ عَلَىٰ عَيْنِي

ይህንን እንዲህ በእንዲህ ካየን ዘንዳ ታቦት የጽላቱ ማህደር ወይም ሰገባ ሲሆን ይህን ድርጊት በፔንታተች በተመሳሳይ መልኩ ተመዝግቧል፦
ዘጸአት 25፥10 *ከግራር እንጨትም “ታቦትን” ይሥሩ፤ ርዝመቱ ሁለት ክንድ ተኩል፥ ወርዱም አንድ ክንድ ተኩል፥ ቁመቱም አንድ ክንድ ተኩል ይሁን*።
ዘዳግም 10፥5 *ተመልሼም ከተራራው ወረድሁ፥ “ጽላቶችንም በሠራሁት ታቦት ውስጥ አደረግኋቸው” እግዚአብሔርም እንዳዘዘኝ በዚያ ኖሩ*።
ይህ እንዲህ ከሆነ ይህ ጽላት እና ታቦት የት ገባ? በተለይ የአገራችን ሰዎች እንደሚተርኩልን ይህን የቃል ኪዳን ታቦት ወደ አቢሲኒያ በዘጠነኛው ክፍለ-ዘመን በሰለሞን ዘመነ-መንግሥት እንደገባ ይነገራል፣ ነገር ግን በዓለማችን ታሪክ ላይ ታቦቱ በባቢሎን ምርኮ ጊዜ እንደጠፋና ከዚያ በፊት ኢየሩሳሌም ውስጥ እንደነበረ ተዘግቧል፤ በተጨማሪ የእዝራ ሱቱኤል ጸሐፊ ታቦቱ በባቢሎን ምርኮ ጊዜ እንደተማረከና እንደጠፋ ይዘግባል፦
እዝራ ሱቱኤል 9፥21-23 ቤተ መቅደሳችን እንደፈረሰ አታይም? ግናይቱ እንደጠፍች ምስጋና እንደቀረ ዘውዳችን እንደወደቀ ተድላ ደስታችን እንደጠፍ የህጋች ማደሪያ *ታቦተ ፅዮን እንደተማረከች ንዋየ ቅዱሳት አንዳደፉ ምልኮታችን እንደቀረ። ከዚህ ሁሉ የሚበልጥ ታቦተ ፅዮን እንደጠፍች ቀረች*፤ ከእሷም ንዋየ ቅድሳቱ ተማርኮ ሄደ በጠላቶቻችን በባቢሎን እጅ ወደቅን።

እንደውም በተረፈ ኤርሚያስ ላይ የሚያገለግሉበትን ንዋየ-ቅዱሳት ሁሉ ጌታ እንዳዘዛቸው ለምድር ሰጧት ምድርም ያን ጊዜ ተቀብላ ዋጠችው ይለናል፦
ተረፈ ኤርሚያስ 8፥13 *"ባሮክ እና ኤርምያስም ወደ ቤተ መቅደስ ገቡ የሚያገለግሉበትን ዕቃ ሁሉ ጌታ እንዳዘዛቸው ለምድር ሰጧት ምድርም ያን ጊዜ ተቀብላ ዋጠችው"*።

የአገራችን ታሪክ የተፋለሰ መሆኑን የምናውቀው ይህ ጥቅስ ታቦተ ጽዮን በባቢሎናውያን እንደጠፋች መናገሩ ነው። ከዚያም ባሻገር ከሰለሞን 400 ዓመት በኋላ በኢዮስያስ ዘመነ-መንግሥት ታቦቱ በኢየሩሳሌም መኖሩን በዜና መዋዕል ላይ ተዘግቧል፦
ዜና መዋዕል ካልዕ 35፥3 እስራኤልንም ሁሉ ያስተምሩ ለነበሩት፥ ለእግዚአብሔርም ለተቀደሱት ሌዋውያን እንዲህ አለ፦ *ቅዱሱን ታቦት የእስራኤል ንጉሥ የዳዊት ልጅ ሰሎሞን በሠራው ቤት ውስጥ *አኑሩት*፤ ከዚህም በኋላ በትከሻችሁ ላይ ሸክም አይሆንባችሁም፤

ታቦተ ጽዮን አክሱም ላይ አለች የሚለው ትረካ ከክብረ ነገሥት ውጪ የታሪክ፣ የባይብል እና የሥነ-ቅርፅ መረጃ ሆነ ማስረጃ የለም። ታቦቱ እና ጽላቱ ቢኖሩም እንኳን በአዲስ ኪዳን ጥቅም የላቸውም። የአዲስ ኪዳን ታላቁ ጸሐፊ ጳውሎስ እንደሚነግረን ከሆነ ሙሴ ንዋየ-ቅዱሳቱን የሚሰራው የሚመጣውን ነገር እያየ እንደነበር ተዘግቧል፦
ዕብራውያን 8፥5 እነርሱም *ሙሴ ድንኳኒቱን ሊሠራ ሳለ እንደ ተረዳ፥ ለሰማያዊ ነገር ምሳሌና ጥላ የሚሆነውን ያገለግላሉ። በተራራው እንደ ተገለጠልህ ምሳሌ ሁሉን ታደርግ ዘንድ ተጠንቀቅ ብሎት ነበርና*።
ዘጸአት 25፥40 በተራራ ላይ *እንዳሳየሁህ ምሳሌ እንድትሠራ ተጠንቀቅ*።
የሐዋርያት ሥራ 7፥44 *እንዳየው ምስል አድርጎ ይሠራት ዘንድ ሙሴን ተናግሮ እንዳዘዘው፥ የምስክር ድንኳን ከአባቶቻችን ዘንድ በምድረ በዳ ነበረች*፤
ይህንን ጳውሎስ ታቦትና ጽላት “ጥላ”typology” እንደሆነ ይናገራል፤ ብሉይ ላይ የነበረው ኪዳን በአዲስ ኪዳን ተሽሯል፤ ይህም ኪዳን ጥላነቱ ታቦቱ የሰው አካል ሲሆን የሚጻፍበት ፊደል ደግሞ ለሰው ልብ ምሳሌ ሆኖ አዲሱ ኪዳን በልብ የሚጻፍ መሆኑኑን ይነግረናል፦
ኤርምያስ 31፥31 እነሆ፥ ከእስራኤል ቤትና ከይሁዳ ቤት ጋር *አዲስ ቃል ኪዳን* የምገባበት ወራት ይመጣል፥ ይላል እግዚአብሔር፤ ከግብጽ አገር አወጣቸው ዘንድ እጃቸውን በያዝሁበት ቀን ከአባቶቻቸው ጋር እንደ ገባሁት ያለ ቃል ኪዳን አይደለም፤ እነርሱ በኪዳኔ አልጸኑምና፥ እኔም ቸል አልኋቸው፥ ይላል እግዚአብሔር፡፡ ከእነዚያ ወራት በኋላ ከእስራኤል ቤት ጋር *የምገባው ቃል ኪዳን ይህ* ነውና፥ ይላል እግዚአብሔር፤ *ሕጌን በልቡናቸው አኖራለሁ*፥ *በልባቸውም እጽፈዋለሁ*፤ እኔም አምላክ እሆናቸዋለሁ እነርሱም ሕዝብ ይሆኑኛል።
ዕብራውያን 8፥10-13 ከዚያ ወራት በኋላ ከእስራኤል ቤት ጋር የምገባው ቃል ኪዳን ይህ ነውና ይላል ጌታ፤ *ሕጌን በልቡናቸው አኖራለሁ በልባቸውም እጽፈዋለሁ*፥ እኔም አምላክ እሆንላቸዋለሁ እነርሱም ሕዝብ ይሆኑልኛል። .. *አዲስ በማለቱ ፊተኛውን አስረጅቶአል፤ አሮጌና ውራጅ የሆነውስ ሊጠፋ ቀርቦአል*።

ብሉይ ማለት አሮጌ ማለት ነው። አሮጌ ያሰኘው አዲሱ ነው፣ አሮጌው ኪዳን ህጉ በድንጋይ ጽላት ላይ የተጻፈበት ኪዳን ሲሆን አዲሱ ደግሞ በልብ ጽላት ላይ የተጻፈበት ኪዳን ነው፣ በድንጋይ ላይ የተጻፈው ኪዳን አሮጌና ውራጅ እንደተባለ አስተውሉ፣ ከዚያም ባሻገር በአዲሱ ኪዳን አሮጌው ኪዳን ተሽሯል ይላል፦
2ኛ ቆሮ 3፥3 እናንተም በሕያው እግዚአብሔር መንፈስ እንጂ በቀለም አይደለም፥ *ሥጋ በሆነ በልብ ጽላት* እንጂ *በድንጋይ ጽላት* ያልተጻፈ፥ በእኛም የተገለገለ የክርስቶስ መልእክት እንደ ሆናችሁ የተገለጠ ነው።
2ኛ ቆሮ 3፥7 ዳሩ ግን የእስራኤል ልጆች ስለዚያ ስለ *ተሻረው* ስለ ፊቱ ክብር የሙሴን ፊት ትኩር ብለው መመልከት እስኪሳናቸው ድረስ፥ *ያ በፊደላት በድንጋዮች ላይ የተቀረጸ የሞት አገልግሎት* በክብር ከሆነ፥ የመንፈስ አገልግሎት እንዴት ይልቅ በክብር አይሆንም?
2ኛ ቆሮ 3፥13 *የዚያንም ይሻር* የነበረውን መጨረሻ ትኵር ብለው የእስራኤል ልጆች እንዳይመለከቱ፥ በፊቱ መጋረጃ እንዳደረገ እንደ ሙሴ አይደለንም።
2ኛ ቆሮ 3፥14 ነገር ግን አሳባቸው ደነዘዘ፡፡ ብሉይ ኪዳን ሲነበብ ያ መጋረጃ ሳይወሰድ እስከ ዛሬ ድረስ ይኖራልና፤ በክርስቶስ ብቻ *የተሻረ* ነውና።

ምን ትፈልጋለህ? በፊደላት በድንጋዮች ላይ የተቀረጸው ጽላት በልብ ጽላት ተሽሯል፣ ቤተመቅደሱም ሰው ሆኗል፦
1ኛ ቆሮ 3፥16-17 *የእግዚአብሔር ቤተ መቅደስ እንደ ሆናችሁ* የእግዚአብሔርም መንፈስ እንዲኖርባችሁ አታውቁምን? ማንም *የእግዚአብሔርን ቤተ መቅደስ ቢያፈርስ እግዚአብሔር እርሱን ያፈርሰዋል፤ የእግዚአብሔር ቤተ መቅደስ ቅዱስ ነውና፥ ያውም እናንተ ናችሁ*።
1ኛ ቆሮ 6፥19-20 ወይስ *ሥጋችሁ ከእግዚአብሔር የተቀበላችሁት በእናንተ የሚኖረው የመንፈስ ቅዱስ ቤተ መቅደስ እንደ ሆነ አታውቁምን?*

አዲሱ ኪዳን ህጉ የተጻፈው በልብ ጽላት ላይ ከሆነ ቤተመቅደሱ የሰው አካል ከሆነ እግዚአብሔር ሰው በሰራው ቤተ መቅደስ አይኖርም ይለናል፦
የሐዋርያት ሥራ 17፥24 ዓለሙንና በእርሱ ያለውን ሁሉ የፈጠረ አምላክ እርሱ የሰማይና የምድር ጌታ ነውና **እጅ በሠራው መቅደስ አይኖርም**፤
የሐዋርያት ሥራ 7፥50 ነገር ግን ነቢዩ፦ ሰማይ ዙፋኔ ነው ምድርም የእግሬ መረገጫ ናት፤ ለእኔ ምን ዓይነት ቤት ትሠራላችሁ? ይላል ጌታ፥ ወይስ የማርፍበት ስፍራ ምንድር ነው? ይህንስ ሁሉ እጄ የሠራችው አይደለምን? እንዳለ፥ ልዑል *የሰው እጅ በሠራችው አይኖርም*።
ኢሳይያስ 66፥1 እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፦ ሰማይ ዙፋኔ ነው፥ ምድርም የእግሬ መረገጫ ናት፤ *የምትሠሩልኝ ቤት ምን ዓይነት ነው? የማርፍበትስ ስፍራ ምንድር ነው?*
ኤርምያስ 3፥16 በበዛችሁም ጊዜ በምድርም ላይ በረባችሁ ጊዜ፥ ይላል እግዚአብሔር፥ በዚያ ዘመን፦ *የእግዚአብሔር የቃል ኪዳኑ ታቦት ብለው ከእንግዲህ ወዲህ አይጠሩም* ልብ አያደርጉትም፥ አያስቡትምም፥ አይሹትምም፥ *ከእንግዲህ ወዲህም አይደረግም*።

የሚገርመው የአገራችን ክርስቲያኖች ከብሉይ ኪዳን ስንጠቅስ “ተሽሯል” ይሉናል፣ የተሻረው ታቦቱትና ጽላቱ እንጂ ሕጉ አይደለም። ሕጉማ በልብ ተጽፏል ተብሏል። የአገራችን ክርስቲያኖች ሕጉ ተሽሯል ይሉና የተጻፈበት ድንጋይ ሆነ የሚቀመጥበት ታቦት አልተሻረም ብለው ድርቅ ይላሉ፣ እራሳቸውን የሚያስጠጉበት ጳውሎስ በግልጽ የድንጋይ ጽላት እንደተሻረና አምላክ ሰው በሰራው ቤተመቅደስ እንደማይኖር ተናግሯል፣ ነገር ግን ዛሬ ያሉት ያገራችን ሰዎች ዛርኒሽ በተቀባ እንጨት ቀርጸው ታቦት ነው ብለው ለታቦቱ ሲሰግዱ፣ ሲለማመኑ፣ ሲማጸኑ፣ ሲሳሉ፣ ዕጣን ሲያጨሱ ይታያል፣ ይህ በትንቢት ስለ እነርሱ የተነገረው እየተፈጸመ ነውና በተውበት ወደ አላህ ተመለሱና አንዱን አምላክ በብቸኝነት አምልኩ፦
ኢሳይያስ 44፥15-19 *ለሰውም ማገዶ ይሆናል፤ ከእርሱም ወስዶ ይሞቃል፥ አንድዶም እንጀራ ይጋግርበታል፤ ከእርሱም አምላክ አበጅቶ ይሰግድለታል፥ የተቀረጸውንም ምስል ሠርቶ በእርሱ ፊት ይንበረከካል። ግማሹን በእሳት ያቃጥላል፥ በዚያ በግማሹ ሥጋ ይበላል፥ ሥጋም ይጠብስበትና ይጠግባል፤ ይሞቃልና፦ እሰይ ሞቅሁ፥ እሳቱን አይቻለሁ ይላል። የቀረውንም እንጨት አምላክ አድርጎ ምስል ይቀርጽበታል፤ በፊቱም ተጐንብሶ ይሰግዳል ወደ እርሱም እየጸለየ፦ አምላኬ ነህና አድነኝ ይላል። አያውቁም፥ አያስቡም፤ እንዳያዩ ዓይኖቻቸውን፥ እንዳያስተውሉ ልቦቻቸውን ጨፍነዋል። በልቡም ማንም አያስብም፦ ግማሽዋን በእሳት አቃጥያለሁ፥ በፍምዋም ላይ እንጀራን ጋግሬአለሁ፥ ሥጋም ጠብሼ በልቻለሁ፤ የቀረውንም አስጸያፊ ነገር አደርጋለሁን? ለዛፍስ ግንድ እሰግዳለሁን? እንዲልም እውቀትና ማስተዋል የለውም*።

ከወንድም ወሒድ ዑመር
https://tttttt.me/Wahidcom

ወሰላሙ አለይኩም
ውሸት ሲጋለጥ

በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡

17፥81 በልም *«እውነት መጣ ውሸትም ተወገደ፤ እነሆ ውሸት ተወጋጅ ነውና፡፡»* وَقُلْ جَآءَ ٱلْحَقُّ وَزَهَقَ ٱلْبَٰطِلُ ۚ إِنَّ ٱلْبَٰطِلَ كَانَ زَهُوقًۭا

ሰው የሚዋሸት ከሁለት ነገር አንጻር ነው፥ አንዱ ባለማወቅ ሲሆን ሁለተኛው ሆን ብሎ ህሊናውን በመሸጥ ነው። እውነት ሲገለጥ ውሸት ይጋለጣል፥ እውነት ሲመጣ ውሸት ሁልጊዜ መቋቋው አይችልም። ውሸት በእውነት ፊት እሳት የነካው ሰም፣ ጸሐይ ያየው ቅቤ፣ ነፋስ የጎበኘው አቧራ ይሆናል። እውነትን በውሸት ላይ ስትጥለው ያፈራርሰዋል፥ ምክንያቱም ውሸትም መነሻም መድረሻም የለውምና እነሆ ውሸት ተወጋጅ ነው፦
21፥18 በእርግጥ *እውነትን በውሸት ላይ እንጥላለን፡፡ አንጎሉን ያፈርሰዋልም፡፡ ወዲያውም እርሱ ጠፊ ነው፡፡ ለእናንተም ከዚያ ከምትመጥኑት ነገር ብርቱ ቅጣት አላችሁ፤ ወዮላችሁ*፡፡ بَلْ نَقْذِفُ بِٱلْحَقِّ عَلَى ٱلْبَٰطِلِ فَيَدْمَغُهُۥ فَإِذَا هُوَ زَاهِقٌۭ ۚ وَلَكُمُ ٱلْوَيْلُ مِمَّا تَصِفُونَ
34፥49 *«እውነቱ መጣ፤ ውሸትም መነሻም መድረሻም የለውም ተወገደ*» በላቸው፡፡ قُلْ جَآءَ ٱلْحَقُّ وَمَا يُبْدِئُ ٱلْبَٰطِلُ وَمَا يُعِيدُ

ይህንን ውሸት ለማጋለጥ እውነቱን እንግለጥ፦
ኢማም ቡኻሪይ መጽሐፍ 63 ሐዲስ 75
ኑዐይም ኢብኑ ሐማድ እንደተረከው፤ ዐምር ኢብኑ መይሙን አለ፦ “በዘመነ-ድንቁርና ጊዜ ሴት ዝንጀሮ በብዙ ዝንጀሮዎች ተከባ አየው፤ ሕጋዊ ያልሆነ ተራክቦ አድርጋለች በሚል ምክንያት ሁሉም በድንጋይ ወገሯት፤ እኔም ከእነሱ ጋር ወገርኳት። حَدَّثَنَا نُعَيْمُ بْنُ حَمَّادٍ، حَدَّثَنَا هُشَيْمٌ، عَنْ حُصَيْنٍ، عَنْ عَمْرِو بْنِ مَيْمُونٍ، قَالَ رَأَيْتُ فِي الْجَاهِلِيَّةِ قِرْدَةً اجْتَمَعَ عَلَيْهَا قِرَدَةٌ قَدْ زَنَتْ، فَرَجَمُوهَا فَرَجَمْتُهَا مَعَهُمْ‏.‏

ቀጣፊዎች ይህንን ሐዲስ ይዘው፦ “ነብያችሁ”ﷺ” ዝንጅሮ ወግሯል” እያሉ ይቀጥፋሉ፤ ሲጀመር ይህንን ድርጊት አደረኩኝ እያለ ያለው ዐምር ኢብኑ መይሙን እንጂ ነብያችን”ﷺ” አይደሉም፤ ይህን የተናገሩት ነብያችን”ﷺ” ቢሆኑ ኖሮ ሐዲሱ በግልጽ “ቃለ ነብይ” ወይም “ቃለ ረሱል” ብሎ ይጀምር ነበር፤ የነብያችን”ﷺ ንግግር ሽታው እንኳን እዚህ ሐዲስ ላይ የለም።
ሲቀጥል ዐምር ኢብኑ መይሙን የተናገረው በዘመነ-ድንቁርና ጊዜ ማለትም ቁርአን ከመውረዱ በፊት የነበረውን የጨለማ ጊዜ በአውንታዊ ሳይሆን በአሉታዊ ለመግለፅ ነው።
እውነት ተገለጠ ውሸት ተጋለጠ፤ በልም እውነት መጣ ውሸትም ተወገደ፤ እነሆ ውሸት ተወጋጅ ነው፦
17፥81 በልም *«እውነት መጣ ውሸትም ተወገደ፤ እነሆ ውሸት ተወጋጅ ነውና፡፡»* وَقُلْ جَآءَ ٱلْحَقُّ وَزَهَقَ ٱلْبَٰطِلُ ۚ إِنَّ ٱلْبَٰطِلَ كَانَ زَهُوقًۭا

ከወንድም ወሒድ ዑመር
https://tttttt.me/Wahidcom

ወሠላሙ ዐለይኩም
ኒፋቅ

በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡

4፥145 *መናፍቃን በእርግጥ ከእሳት በታችኛው አዘቅት ውስጥ ናቸው፡፡ ለእነርሱም ረዳትን አታገኝላቸውም*፡፡ إِنَّ الْمُنَافِقِينَ فِي الدَّرْكِ الْأَسْفَلِ مِنَ النَّارِ وَلَن تَجِدَ لَهُمْ نَصِيرًا

“ኒፋቅ” نِفَاق የሚለው ቃል “ናፈቀ” نَافَقَ ማለትም “ነፈቀ” ከሚል ሥርወ-ቃል የመጣ ሲሆን “ኑፋቄ” ወይም “ምንፍቅና” አሊያም “አስመሳይነት” “በአፉ አምኖ በልቡ የሚክድ” ማለት ነው፤ “ኑፋቄ” የሚለው የግዕዝ ቃል “ነፈቀ” ማለትም “ከፈለ” ከሚል ሥርወ-ቃል የመጣ ሲሆን “ክፍልፍል” ወይም “አራጥቃ” ማለት ነው፤ ዓመት ለሁለት ስንከፍለው ስድስት ወሩ “መንፈቅ” ይባላል። አለቃ ኪዳነ-ወልድ ክፍሌ ገፅ 645።

ስለዚህ “መናፍቅ” ማለት “በከፊሉ አምኖ በከፊሉ የሚክድ” ሙሉ ያልሆነ ጎደሎ እምነት ያለው ማለት ነው፤ ኒፋቅ በውስጥ ኩፍር በውጪ ኢማን የሆነ ሁለት አይነት ገጽታ ያለው ነገር ነው፤ ኒፋቅ ያለበት ግለሰብ ደግሞ በነጠላ “ሙናፊቅ” مُنَٰفِق ሲባል በብዜት “ሙናፊቁን” مُنَٰفِقُون ወይም “ሙናፊቂን” مُنَٰفِقِين ይባላል፤ በአማርኛችን በነጠላ “መናፍቅ” በብዜት “መናፍቃን” ማለት ነው። አላማቸው ኡማውን መከፋፈልና መበታተን ነው፦
63፥7 *እነርሱ እነዚያ ፡- «አላህ መልክተኛ ዘንድ ላሉት ሰዎች እስከሚበታተኑ ድረስ አትቀልቡ» የሚሉ ናቸው፡፡ የሰማያትና የምድር ድልቦችም የአላህ ናቸው፡፡ ግን መናፍቃን አያውቁም*፡፡ هُمُ الَّذِينَ يَقُولُونَ لَا تُنفِقُوا عَلَىٰ مَنْ عِندَ رَسُولِ اللَّهِ حَتَّىٰ يَنفَضُّوا ۗ وَلِلَّهِ خَزَائِنُ السَّمَاوَاتِ وَالْأَرْضِ وَلَـٰكِنَّ الْمُنَافِقِينَ لَا يَفْقَهُونَ

ውጪአቸው አማኝ ነው ውስጣቸው ግን ክህደት አለ፤ ወደ ሶላትም በቆሙ ጊዜ ታካቾች ስዎችን የሚያሳዩ ኾነው ይቆማሉ፤ አላህን እና እነዚያን ያመኑትን ያታልላሉ፤ የማያውቁ ሲኾኑ እራሳቸውን እንጅ ሌላን አያታልሉም፤ ወደ ቁርኣንና ወደ ሐዲስ አይመጡም፦
4፥142 *መናፍቃን አላህን ያታልላሉ፡፡ እርሱም አታላያቸው ነው፡፡ ወደ ሶላትም በቆሙ ጊዜ ታካቾች ስዎችን የሚያሳዩ ኾነው ይቆማሉ፡፡ አላህንም ጥቂትን እንጅ አያወሱም*፡፡ إِنَّ الْمُنَافِقِينَ يُخَادِعُونَ اللَّهَ وَهُوَ خَادِعُهُمْ وَإِذَا قَامُوا إِلَى الصَّلَاةِ قَامُوا كُسَالَىٰ يُرَاءُونَ النَّاسَ وَلَا يَذْكُرُونَ اللَّهَ إِلَّا قَلِيلًا
2፥8 *ከሰዎችም «በአላህና በመጨረሻው ቀን አምነናል» የሚሉ አሉ፤ እነርሱም አማኞች አይደሉም*፡፡ وَمِنَ النَّاسِ مَن يَقُولُ آمَنَّا بِاللَّهِ وَبِالْيَوْمِ الْآخِرِ وَمَا هُم بِمُؤْمِنِينَ
2፥9 *አላህን እና እነዚያን ያመኑትን ያታልላሉ፤ የማያውቁ ሲኾኑ እራሳቸውን እንጅ ሌላን አያታልሉም*፡፡ يُخَادِعُونَ اللَّهَ وَالَّذِينَ آمَنُوا وَمَا يَخْدَعُونَ إِلَّا أَنفُسَهُمْ وَمَا يَشْعُرُونَ
3፥167 *እነዚያንም የነፈቁትን* እና ለእነርሱ «ኑ፤ በአላህ መንገድ ተጋደሉ፤ ወይም ተከላከሉ፤» የተባሉትን ሊገልጽ ነው፡፡ «መዋጋት መኖሩን ብናውቅ ኖሮ በተከተልናችሁ ነበር» አሉ፡፡ *እነርሱ ያን ጊዜ ከእምነት ይልቅ ወደ ክህደት የቀረቡ ናቸው፡፡ በልቦቻቸው የሌለውን በአፎቻቸው ይናገራሉ፡፡ አላህም የሚደብቁትን ዐዋቂ ነው*፡፡ وَلِيَعْلَمَ الَّذِينَ نَافَقُوا ۚ وَقِيلَ لَهُمْ تَعَالَوْا قَاتِلُوا فِي سَبِيلِ اللَّهِ أَوِ ادْفَعُوا ۖ قَالُوا لَوْ نَعْلَمُ قِتَالًا لَّاتَّبَعْنَاكُمْ ۗ هُمْ لِلْكُفْرِ يَوْمَئِذٍ أَقْرَبُ مِنْهُمْ لِلْإِيمَانِ ۚ يَقُولُونَ بِأَفْوَاهِهِم مَّا لَيْسَ فِي قُلُوبِهِمْ ۗ وَاللَّهُ أَعْلَمُ بِمَا يَكْتُمُونَ
4፥61 ለእነርሱም፡- *«አላህ ወደ አወረደው ቁርኣን እና ወደ መልክተኛው ኑ» በተባሉ ጊዜ መናፍቃን ከአንተ መሸሽን ሲሸሹ ታያቸዋለህ*፡፡ وَإِذَا قِيلَ لَهُمْ تَعَالَوْا إِلَىٰ مَا أَنزَلَ اللَّهُ وَإِلَى الرَّسُولِ رَأَيْتَ الْمُنَافِقِينَ يَصُدُّونَ عَنكَ صُدُودًا
2፥14 *እነዚያንም ያመኑትን በተገናኙ ጊዜ «አምነናል» ይላሉ፡፡ ወደ ሰይጣኖቻቸውም ባገለሉ ጊዜ «እኛ ከእናንተ ጋር ነን፤ እኛ በእነርሱ ተሳላቂዎች ብቻ ነን»* ይላሉ፡፡ وَإِذَا لَقُوا الَّذِينَ آمَنُوا قَالُوا آمَنَّا وَإِذَا خَلَوْا إِلَىٰ شَيَاطِينِهِمْ قَالُوا إِنَّا مَعَكُمْ إِنَّمَا نَحْنُ مُسْتَهْزِئُونَ

የመናፍቃን ቅጣቱ ከእሳት በታችኛው አዘቅት ውስጥ ናቸው፦
4፥145 *መናፍቃን በእርግጥ ከእሳት በታችኛው አዘቅት ውስጥ ናቸው፡፡ ለእነርሱም ረዳትን አታገኝላቸውም*፡፡ إِنَّ الْمُنَافِقِينَ فِي الدَّرْكِ الْأَسْفَلِ مِنَ النَّارِ وَلَن تَجِدَ لَهُمْ نَصِيرًا
9፥68 *መናፍቃንንና መናፍቃትን፣ ከሓዲዎችንም አላህ የገሀነምን እሳት በውስጧ ዘውታሪዎች ሲኾኑ ቃል ገብቶላቸዋል፡፡ እርሷ በቂያቸው ናት፡፡ አላህም ረግሟቸዋል፡፡ ለእነርሱም ዘውታሪ ቅጣት አላቸው*፡፡ وَعَدَ اللَّهُ الْمُنَافِقِينَ وَالْمُنَافِقَاتِ وَالْكُفَّارَ نَارَ جَهَنَّمَ خَالِدِينَ فِيهَا ۚ هِيَ حَسْبُهُمْ ۚ وَلَعَنَهُمُ اللَّهُ ۖ وَلَهُمْ عَذَابٌ مُّقِيمٌ

የሙናፊቅ ምልክቶች ሦስት ናቸው፦ ሲናገር ይዋሻል፣ ሲያምኑት ይከዳል፣ ቃል የገባውን ያፈርሳል፦
ኢማም ቡኻሪይ መጽሐፍ 55, ሐዲስ 12
አቢ ሁረይራህ”ረ.ዐ” እንደተረከው ነብዩ”ﷺ” ሲናገሩ፦ *”የሙናፊቅ ምልክቶች ሦስት ናቸው፦ ሲናገር ይዋሻል፣ ሲያምኑት ይከዳል፣ ቃል የገባውን ያፈርሳል*። عَنْ أَبِي هُرَيْرَةَ ـ رضى الله عنه ـ عَنِ النَّبِيِّ صلى الله عليه وسلم قَالَ ‏ “‏ آيَةُ الْمُنَافِقِ ثَلاَثٌ، إِذَا حَدَّثَ كَذَبَ، وَإِذَا اؤْتُمِنَ خَانَ، وَإِذَا وَعَدَ أَخْلَفَ ‏.‏