TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
62.8K photos
1.61K videos
216 files
4.37K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

መረጃ እና መልዕክት ፦ 0919743630

ማርኬቲንግ ፦ 0979222111 ወይም
0979333111

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#Alert😷

በአ/አ እና በተወሰኑ ክልሎች የኦክስጅን እጥረት አጋጠመ።

በኢትዮጵያ ውስጥ በኮቪድ-19 ምክንያት በ "ጽኑ የሚታመሙ" ሰዎች ቁጥር እጅግ በመጨመሩ በአዲስ አበባ እና በተወሰኑ የክልል ከተሞች ከፍተኛ የሆነ #የኦክስጅን እጥረት ማጋጠሙ ተሰማ።

አሁን ላይ 597 ከፍተኛ ክትትል እና የፅኑ ሕክምና የሚፈልጉ ወገኖች እንዳሉ የጤና ሚኒስቴር የህክምና አገልግሎት ዳይሬክተር ያዕቆብ ሰማን ገልፀዋል።

ትላንት የፅኑ ታማሚዎች ቁጥር 591 የነበረ ሲሆን ዛሬ 597 ደርሷል።

ዳይሬክተሩ ያዕቆብ፤ በፍጥነት የወረሽኙን የመከላከያ መንገዶች ትግበራ ወደ #አስገዳጅነት እንዲገባ ካልተደረገ እና ሁሉም በሚገባ ካልተጠነቀቀ የከፋ ጊዜ ሊመጣ እንደሚችል አስገንዝበዋል።

@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
#እጅግ_በጣም_አሳሳቢ

የዛሬ የኮቪድ19 ሪፖርት ምን ይመስላል ?

- 624 ከፍተኛ ክትትል እና ፅኑ ሕክምና የሚፈልጉ ወገኖች
- 24% ሀገራቀፍ በበሽታ የመያዝ ምጣኔ
- 16 ሕይወታቸው ያጡ ዜጎች

በዛሬው ቀን ከተመረመሩት ዉስጥ 6 ክልሎች ከፍተኛ (ከ20% በላይ) የበሽታ ስርጭት ታይቶባቸዋል ፦
1. ሲዳማ-48%
3. ድሬዳዋ-22%
3. አዲስ አበባ-25%
4. ኦሮሚያ- 25%
5. ደቡብ- 21%
6. አማራ- 24%

በፀና የሚታመሙ ሰዎች ቁጥር እጅግ ከመጨመሩ ጋር ተያይዞ በአዲስ አበባ እና በተወሰኑ የክልል ከተሞች ከፍተኛ የሆነ #የኦክስጅን እጥረት አጋጥሟል።

በፍጥነት የመከላከያ መንገዶች ትግበራ ወደ አስገዳጅነት እንዲገባ ካላደረግን እና ሁላችንም በሚገባ ካልተጠነቀቅን የከፋ ጊዜ ሊመጣ እንደሚችል ከእነዚህ ቁጥሮች በላይ ምስክር የለም::

ሁላችንም የበሽታውን ስርጭት በመግታት የራሳችን እና የምንወዳቸው ቤተሰቦቻችን ሕይወት እናድን።

ያዕቆብ ሰማን
ጤና ሚኒስቴር
የሕክምና አገልግሎት ዳይሬክተር

@tikvahethiopia
😢1