TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
63K photos
1.61K videos
217 files
4.38K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

መረጃ እና መልዕክት ፦ 0919743630

ማርኬቲንግ ፦ 0979222111 ወይም
0979333111

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#ALERT🚨

የ24 ሰዓት የኮቪድ-19 ሪፖርት ፦

• የተደረገ የላብራቶሪ ምርመራ 👉 10,861
• ቫይረሱ የተገኘባቸው 👉 2,269
• ህይወታቸው ያለፈ 👉 24
• ከበሽታው ያገገሙ 👉 1,416
• ፅኑ ታማሚዎች 👉 443

ዛሬ እና ትላንት በድምሩ የ48 ሰዎች ህይወት አልፏል።

@tikvahethiopia
😱213😢186👍109😁39👎2915🔥15🤩12
#ALERT🚨

የ24 ሰዓት የኮቪድ-19 ሪፖርት ፦

• የተደረገ የላብራቶሪ ምርመራ 👉 10,073
• ቫይረሱ የተገኘባቸው 👉 2,131
• ህይወታቸው ያለፈ 👉 19
• ከበሽታው ያገገሙ 👉 835
• ፅኑ ታማሚዎች 👉 433

ዛሬ እና ትላንት በድምሩ የ43 የሰዎች ህይወት አልፏል።

@tikvahethiopia
😢262👍93😱74😁40👎32🔥1811🤩8
#Alert

የጤና ሚኒስቴር የትዊተር አካውንት ተጠለፈ።

ከ204 ሺ በላይ ተከታዮች ያሉት የሚኒስቴሩ የትዊተር አካውንት ተጠልፏል።

የኢ.ፌ.ዴ.ሪ. ጤና ሚኒስቴር ይፋዊ የትዊተር አካውንቱ #FMoHealth ዛሬ መጋቢት 24 መጠለፉን (ሃክ መደረጉን) አስታውቋል።

ሚኒስቴሩ ችግሩ እስኪቀረፍ ድረስ በትዊተር ገጹ ላይ የሚለቀቁ ማንኛውም መረጃዎች እንደማይወክሉት ገልጿል።

@tikvahethiopia
👍558😱136👏100👎84🥰33😢185
#Alert🚨

በራስ ጠቆሮ ጥብቅ ደን ላይ የተነሳውን እሳት መቆጣጠር አልተቻለም።

በደቡብ ወሎ ዞን አምባሰል ወረዳ 016 ቀበሌ በተለምዶ ራስ ጠቆሮ እየተባለ በሚጠራ ጥብቅ ደን ላይ ሰኔ 6/2014 ሌሊት ጀምሮ የተከሰተው የእሳት አደጋን እስካሁን ድረስ መቆጣጠር አልተቻለም።

በጥብቅ ደኑ ውስጥ ወይራ፣ ጥድ፣ ኮሶ፣ ዝግባና ሌሎች የደን ሐብቶች እንዲሁም የተለያዩ እንሰሳትና አዕዋፋት እንደሚገኙ ተጠቁሟል።

ከመልክዓ ምድራዊ አቀማመጡ አመቺ አለመሆን እና በደኑ ውስጥ ተቀጣጣይ ሳር ከመብዛቱ ጋር ተያይዞም የእሳት አደጋውን ለማጥፋት የሚደረገውን ጥረት ሥራውን ፈታኝ እንዳደረገው ተገልጿል።

የአደጋው መንስኤ በተመለከተ እሳቱ ከግለሰብ ማሳ ተነስቶ ወደ ደኑ እንደተዛመተ የአምባሰል ወረዳ መንግስት ኮሙኒኬሽን ጽ/ቤት አሳውቋል።

@tikvahethiopia
👍3👎1
#ALERT🚨

" ሰባ ሰባት እንኳን አንዲህ አልነበረም "

ሰሀላ ሰዬምት ወረዳ በከባድ ድርቅ መመታቱ ተገልጿል።

በዋግ ኽምራ ብሄረሰብ አስተዳደር ስር ያለው ሰሀላ ሰዬምት ወረዳ 13 ቀበሌዎች አሉት።

ወረዳው የ2015/2016 የምርት ዘመን #ድርቅ ክፉኛ መትቶታል።

ወረዳው በከፊል አርብቶ አድር የሚታወቅ ሲሆን ከማሳው በሚያገኛት ጥቂት ኩንታል እህል በይበልጥ ለገለባው ዋጋ ሰጥቶ በእንሰሳቱ ኑሮውን የሚገፈ አርሶና አርብቶ አደር አካባቢ ነው።

በወረዳው ከፍተኛ የእንስሳት ሀብትም ይገኛል።

ጠቅላላ ካለው የእንስሳት ሀብት የዳልጋ ከብት 104,430፣ የጋማ ከብት 22,121 በግ እና ፍየል 465,428 ይገኙበታል።

ከዚህ ውስጥ ለድርቅ የተጋለጡ የዳልጋ ከብት 92,430፣ የጋማ ከብት 16,121፣ በግ እና ፍየል 396,760 ናቸው።

ወደአጎራባች ዞን የተሰደዱ የዳልጋ ከብት 20,328 ፣ በግ እና ፍየል 116,900 ሲሆኑ እስካሁን በድርቅ ምክንያት የሞተ የዳልጋ ከብት 1320 ፣ የጋማ ከብት 71 በግ እና ፍየል 2457 ናቸው።

በወረዳው ከ52 ሺህ በላይ ህዝብ የሚኖርበት ሲሆን 46ሺ የሚሆነው አፋጣኝ እርዳታ ካለገኘ አደጋ ውስጥ እንደሆነ የወረዳው አስተዳዳሪ አቶ ሲሳይ ብሩ ተናግረዋል።

አቶ ሲሳይ፤ " ምንም እንኳን ድርቅ ቢሆንም ከዚህ በፊት ለእንስሳት የሚሆን ሳር አይጠፋም ነበር። ዛሬ ግን የተቃጠለ መሬት ብቻ ነው የሚታየው፤ ለጥርስ ስጋ ማውጫ የሚሆን የሳር ስንጥር እንኳን አይታይም፤ የወረዳው ነዋሪዎች እንደነገሩን እንደ ወረዳችን እንዲህ አይነት ድርቅ አይተን አናውቅም፤ ሰባሰባት እንኳን አንዲህ አልነበረም " በማለት የድርቁን አስከፊነት ገልጸዋል።

በወረዳው የአርሶ አደሩ ማሳ ርቃኑን ቀርቷል፣ እንስሳት ቆዳቸው ከስጋቸው መጣበቅ ብቻ ሳይሆን ነፍሳቸው በጣዕረሞት ላይ ናት፣  ህጻናት፣ እናቶችና አረጋውያን በርሀብ ተገርፈው ነፍሳቸው ከጉንጫቸው ተጣብቃ ይዛቸው ልትጠፋ አፋፍ ላይ ነች። ተሎ መድረስ ካልተቻለ አሳዛኝ ክስተት በሰሀላ ሰዬምት ወረዳ ሊከሰት ይቻላል።

የአስተዳደሩ የአደጋ መከላከልና ምግብ ዋስትና ተጠሪ ጽ/ቤት ጉዞ አዘጋጅቶ የነበረ ሲሆን የብሄረሰቡ ከፍተኛ አመራሮችና አንዳንድ ግብረሰናይ ድርጅቶች በወረዳው ተገኝተው ቀበሌዎቹን ጎብኝተው ከነዋሪዎች ጋር ውይይት አድርገው ነበር።

የቀበሌው ማህበረሰብ በውይይቱ ላይ " ከእግዚአብሄር በታች መንግስት ነበር ለሰው ልጅ ዋስትና፣ ዛሬ ግን መንግስትም ፊቱን አዞረብን " ብለዋል።

" በዚህ ሳምንት ውስጥ የሚበላ ካልቀረበ ልጆቻችን አናገኛቸውም ፤ አሁንም ቢሆን አንዲት እንጀራ ለ10 ሰው ነው የምንሻማው፤ ከዛ ውጭ ግን ጨው በውሀ በጥብጠን ነው የምንጠጣው " ብለዋል።

እስካሁንም በወረዳው በርሀብ ምክኒያት የ2  ሰዎች ሂይወት አልፏል ሲሉ አሳውቀዋል።

እንስሳትን በተመለከተ " በወረዳችን ትንሽ እህል ካገኘን እንሰሳ ስለምናረባ ከብት እና ፍየሎቻችንን ሸጠን እህል ስለምንሸምት ብዙም አያሳስበንም ነበር፤ ዘንድሮ ግን ለከብቶችም ሆነ ለፍየሎችና በጎች የሚሆን የሚጋጥ ሳር ስለሌለ ተስፋ አስቆርጦናል " ብለዋል።

የአደጋ መከላከልና ምግብ ዋስትና ተጠሪ ጽ/ቤት ሀላፊ አቶ ምህረት መላኩ፤ የተለያዩ ግብረ ሰናይ ድርጅቶች ቃል ከመግባት የዘለለ በመንግስት በኩልም ምንም የቀረበ ነገር የለም።

ለክልሉ አደጋ መከላከልና ምግብ ዋስትና ተጠሪ ጽ/ቤት ሪፖርት ከማድረግ ባለፈ የችግሩን አሳሳቢነት ብንገልጽም እስካሁን የተሰጠ ምላሽ የለም ብለዋል።

መረጃው ከዋግኽምራ ኮሚኒኬሽን ነው የደረሰን።

@tikvahethiopia
😢1.41K123🕊36🙏30😱16🥰8😡8
TIKVAH-ETHIOPIA
#ALERT🚨 " ሰባ ሰባት እንኳን አንዲህ አልነበረም " ሰሀላ ሰዬምት ወረዳ በከባድ ድርቅ መመታቱ ተገልጿል። በዋግ ኽምራ ብሄረሰብ አስተዳደር ስር ያለው ሰሀላ ሰዬምት ወረዳ 13 ቀበሌዎች አሉት። ወረዳው የ2015/2016 የምርት ዘመን #ድርቅ ክፉኛ መትቶታል። ወረዳው በከፊል አርብቶ አድር የሚታወቅ ሲሆን ከማሳው በሚያገኛት ጥቂት ኩንታል እህል በይበልጥ ለገለባው ዋጋ ሰጥቶ በእንሰሳቱ ኑሮውን…
#ALERT🚨

አንድ አንጀራ ለ10 ተሻምተው የሚበሉ ወገኖቻችን እንዳሉ እናውቅ ይሆን ?

በዋግ ኽምራ ብሄረሰብ አስተዳደር ስር ያለው ሰሀላ ሰዬምት ወረዳ በከፍተኛ ድርቅ ተመቷል።

ነዋሪው ችግር ላይ ወድቋል።

ሰው በረሃብ #ሞቷል ፣ እንስሳት ሞተዋል ፣ ተሰደዋል።

ወገኖቻችን በቂ ምግብ አጥተው 1 እንጀራ ለአስር እየተሻሙ እየበሉ ነው። ካዛ ውጭ ጨው በውሃ በጥብጠው ነው የሚጠጡት።

" በዚህ ሳምንት የሚበላ ካልቀረበ ልጆቻችንን አናገኛቸውም " ብለዋል።

የግብረሰናይ ድርጅቶች ቃል መግባት እንጂ ጠብ የሚል ነገር አላደረጉም። መንግሥትም ለገዛ ዜጎቹ እየደረሰ አይደለም።

ከፈጣሪ በታች ለህዝቡ ዋስትና ነው የሚባለው መንግሥት ፊቱን እንዳዞረባቸው ነዋሪዎች ተናግረዋል።

ሁኔታው ከሰባ ሰባቱም የከፋ ነው።

via @BirlikEthiopia

@tikvahethiopia
😢2.76K80🙏62🕊56😱46😡23🥰17
TIKVAH-ETHIOPIA
ፎቶ፦ ይህ በወላይታ ዞን ካዎ ኮይሻ ወረዳ ጤፓ ቀበሌ የተከሰተ የመሬት መንሸራተት ነው። ትላንት ቀን 10:30 በጣለው ከፍተኛ ዝናብ ምክንያት በተከሰተው የመሬት መንሸራተት አደጋ 1 ሰው ሲሞት ፣ 1 ሰው ላይ ከባድ የአካል ጉዳት ደርሷል። 8 የአከባቢው ነዋሪዎች ከቤት ንብረታቸው ተፈናቅለዋል። በተከሰተው ናዳ አደጋ ህይወቷ ያለፈው የ11 ዓመት ሴት ልጅ ናት። አብራት የነበረችው ወላጅ እናቷ ደግሞ ከአደጋው…
#Alert🚨

" እስካሁን የ11 ሰዎች አክስሬን ተገኝቷል " - የካዎ ኮይሻ ወረዳ

በወላይታ ዞን ካዎ ኮይሻ ወረዳ ጤፓ ቀበሌ ዛሬ ረፋድ 5 ሠዓት አካባቢ በተከሰተ የመሬት ናዳ አደጋ የ11 ሰዎች ሕይወት ማለፉ ተሰምቷል፡፡

በተከሰተው አደጋ እስካሁን በተደረገ ፍለጋ የ11 ሰዎች አስከሬን ተገኝቷል።

የሟቾች ቁጥር ሊያሻቅብ እንደሚችል የካዎ ኮይሻ ወረዳ አስተዳደር አሳውቋል።

ከቀናት በፊት በዚሁ አካባቢ በተከሰተ የመሬት ናዳ 1 ሰው ህይወቱ ማለፉ እና 1 ሰው ከባድ ጉዳት እንደረሰበት ይታወሳል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ መረጃውን ከወረዳው ኮሚኒኬሽን ነው ያገኘው።

@tikvahethiopia
😭1.69K😢171102🙏48😱45🕊30👏18🤔17🥰15😡10
#Alert🚨

የዝንጀሮ ፈንጣጣ (MPox) የዓለም አቀፍ አሳሳቢ የህዝብ ጤና ደኅንነት ስጋት (PHEIC) እንደሆነ የዓለም ጤና ድርጅት ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር ቴድሮስ አድሃኖም ወሰኑ።

የዝንጀሮ ፈንጣጣ በዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ (DRC) እና በአፍሪካ የሥርጭት መጠኑ እየጨመረ መምጣቱን አሳውቀዋል።

ከዚህ ባለፈ፣ የዝንጀሮ ፈንጣጣን የአፍሪካ ሲዲሲ የህብረተሰብ ጤና አህጉራዊ ደህንነት ስጋት እንደሆነ ገልጿል።

በሌላ በኩል ፤ እስካሁን ድረስ በኢትዮጵያ ውስጥ የተያዘ ሰው #አለመኖሩን የኢትዮጵያ ጤና ሚኒስቴር ዛሬ አመልክቷል።

በቦሌ ዓለም አቀፍ ኤርፖርት እና ሞያሌን ጨምሮ በሌሎች የመግቢያ ቦታ ላይ የቁጥጥርና ማጣራት ስራ እየተሰራ ነው።

በሽታው እስካሁን በ13 የአፍሪካ ሀገራት መከሰቱን እንዲሁም፣ 2,863 ሰዎች በበሽታው መያዛቸው እና 517 ለህልፈት መዳረጋቸዉ መረጋገጡን የአፍሪካ ሲዲሲ መረጃ ያሳያል።

@tikvahethmagazine @tikvahethiopia
😱551😢146🙏8680🕊49😭21😡20👏17🤔13🥰10
TIKVAH-ETHIOPIA
#Alert🚨 የዝንጀሮ ፈንጣጣ (MPox) የዓለም አቀፍ አሳሳቢ የህዝብ ጤና ደኅንነት ስጋት (PHEIC) እንደሆነ የዓለም ጤና ድርጅት ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር ቴድሮስ አድሃኖም ወሰኑ። የዝንጀሮ ፈንጣጣ በዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ (DRC) እና በአፍሪካ የሥርጭት መጠኑ እየጨመረ መምጣቱን አሳውቀዋል። ከዚህ ባለፈ፣ የዝንጀሮ ፈንጣጣን የአፍሪካ ሲዲሲ የህብረተሰብ ጤና አህጉራዊ ደህንነት ስጋት እንደሆነ…
#Alert🚨

ከተ.መ.ድ የጤና ኤጀንሲ እንደተገኘው መረጃ በቅርቡ ኤምፖክስ (Mpox) ለመጀመሪያ ጊዜ በ4 የምስራቅ አፍሪካ ሀገራት ማለትም ፦
- በጎረቤታችን ኬንያ ፣
- በቡሩንዲ ፣
- በሩዋንዳ
- በኡጋንዳ ተገኝቷል። ሀገራቱም ሪፖርት አድርገዋል። በነዚህ ሀገራት ውስጥ የታየው በሽታ በኮንጎ ካለው ጋር የተገናኘ ነው።

የዝንጀሮ ፈንጣጣ ወይም Mpox በሽታ የሚከሰተው በቫይረስ አማካኝነት ነው።

ከሰው ወደ ሰው ይተላለፋል። በወሲባዊ ግንኙነት ፣ በቆዳ ንክኪ ፣ በቅርብ ርቀት ሆኖ ማውራት/ መተንፈስ ፣ በበሽታው ከተያዘ ሰው ጋር ባለ የቅርብ ግንኙነት ይተላለፋል።

አሁን ላይ #ዋነኛዎቹ ናቸው የሚባሉት ሁለቱ የቫይረሱ ዝርያዎች Clade 1 - በማእከላዊ አፍሪካ ውስጥ ያለ ፤  Clade 1b - እጅግ በጣም አደገኛ የሆነው አዲስ የቫይረሱ ዝርያ ነው።

@tikvahethiopia
😱1.12K🙏291😢200😭161142😡58🕊53🥰45🤔45👏3
TIKVAH-ETHIOPIA
#Omo የኦሞ ወንዝ ሙላት ከቁጥጥር ውጭ መሆኑን ተከትሎ የአካባቢው አርሶአደር በ4ቱም አቅጣጫ ንብረቱን ጥሎ መሸሽ ላይ ነው። ችግሩ እንደሚከሰት ታውቆ በርካታ ስራ ሲሰራ ቢቆይም የኦሞ ወንዝ መጠን ከተለመደውና ከታሰበው ውጭ መሆኑን ተከትሎ ግን ለዞኑ መንግስትም ሆነ ለግብረሰናይ ድርጅቶች ሁኔታው ከባድ ሆኖባቸዋል። የወንዙ ሙላት ከባድ መሆኑን በመግለጽ አሁን ላይ አርብቶ አደሩን በአራት ጊዜያዊ…
#ALERT🚨

⚠️ " በውሀ ተውጠን ከማለቃችን በፊት ድረሱልን " - የኦሞራቴ ከተማ ነዋሪዎች

🔴 " የውሀው አመጣጥ እጅግ አስፈሪ ነው ፤ የፌደራል መንግስት ማሽነሪዎች ቶሎ እንዲያቀርብልን እየጠየቅን ነው " - የአካባቢዉ አስተዳደር

የኦሞ ወንዝ መሙላቱን ተከትሎ ሀብት ንብረቴ የሚላቸዉ ከብቶች ማለቁን ያየዉ የደቡብ ኦሞ አርብቶ አደር በአራቱም አቅጣጫ እየተሰደደ መሆኑን ጠቅሰን አካባቢው ትኩረት ይሻል ስንል ከቀናት በፊት መዘገባችን ይታወሳል።

ይሁንና አሁን ላይ የኦሞ ወንዝ ከአቅም በላይ በመሙላቱና የአካባቢዉ መሬት ላይ በከፍተኛ ሁኔታ መተኛቱን ተከትሎ የወረዳዉ ዋና ከተማ የሆነችዉን ኦሞራቴን ደሴት ሲያደርጋት ህዝቡም መዉጫ በማጣት ጭንቀት ውስጦ መግባቱን ሰምተናል።

የድረሱልን ጥሪያቸዉን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ያደረሱት የአካባቢው ነዋሪዎች እንደሚገልጹት ለአመታት በወንዙ ሙላት ሲቸገሩ መቆየታቸውንና አሁን ግን ከርቀት ወደምትገኘው ኦሞራቴ ከተማ በእጅጉ መጠጋቱ እንዳስደነገጣቸው በመግለጽ ከመዋጣቸው በፊት የሚመለከተዉ አካል እንዲደርስላቸው ተማጽነዋል።
 
በአካባቢው የነበሩት አርብቶ አደሮች በበኩላቸው ሙሉ በሙሉ የግጦሽ መሬቶች በወንዙ ተቆርሶ መወሰዱንና ከብቶቻቸው ማለቃቸውን ገልጸዉ አሁን ላይ የተጠለሉባቸው ጊዜያዊ መጠለያዎች በውሀው እየተጥለቀለቁ በመሆኑ ህይወታቸዉ አደጋ ላይ መውደቁን አስተድተዋል።

ስለሁኔታዉ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ አስተያየታቸውን የሰጡን የወረዳዉ አስተዳዳሪ አቶ ታደለ ሀቴ " የዉሀዉ አመጣጥ እጅግ አስፈሪ ነው " ብለዋል።

ማህበረሰቡ አፈር በማዳበሪያ እየቋጠረ ግድብ መስራቱ ውሀውን ስላላስቆመው የፌደራል መንግስት ማሽነሪዎች ቶሎ እንዲያቀርብልን እየጠየቅን ብለዋል።

" አሁን ላይ የኦሞራቴ ከተማ ከጊዜያዊ መጠለያዎችም ሆነ ራቅ ካሉ አካባቢዎች ለመገናኘትም ሆነ ለመሸሽ ቱርሚን የሚያገናኘዉ ድልድይ በመሰበሩና ወደኬኒያ የሚወስደዉ ዋና መንገድ በውሀው ክራክ በማድረጉ ደሴት ሆናል " ሲሉ ገልጸዋል።

በመሆኑም " የኦሞራቴ ህዝብ የከፋ ችግር ላይ በመሆኑ የሚመለከተው አካል አፋጣኝ ድጋፍ ሊያደርግለት ይገባል ሲሉ " ጥሪያቸውን አስተላልፈዋል።

#TikvahEthiopiaFamilyHW

@tikvahethiopia
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
😭683137🙏57😢46😱33🕊32👏16🥰14🤔14
TIKVAH-ETHIOPIA
#ALERT🚨 ⚠️ " በውሀ ተውጠን ከማለቃችን በፊት ድረሱልን " - የኦሞራቴ ከተማ ነዋሪዎች 🔴 " የውሀው አመጣጥ እጅግ አስፈሪ ነው ፤ የፌደራል መንግስት ማሽነሪዎች ቶሎ እንዲያቀርብልን እየጠየቅን ነው " - የአካባቢዉ አስተዳደር የኦሞ ወንዝ መሙላቱን ተከትሎ ሀብት ንብረቴ የሚላቸዉ ከብቶች ማለቁን ያየዉ የደቡብ ኦሞ አርብቶ አደር በአራቱም አቅጣጫ እየተሰደደ መሆኑን ጠቅሰን አካባቢው ትኩረት ይሻል…
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
#Alert🚨

ኦሞ ወንዝ በከፍተኛ ሁኔታ በመሙላቱ የወንዙ ውሃ እና የቱርካና ሀይቅ ይዞታውን እያሰፋ በመሆኑ በኦሞራቴ ከተማ በ1.9 ኪ/ሜ ርቀት አከባቢ በተለያዩ ቦታዎች የመሬት መሰንጠቅ እዲሁም ውሃው ውስጥ ለውስጥ እየሄደ በመሆኑ ከፍተኛ ጥንቃቄ እንዲደረግ የዳሰነች ወረዳ አስተዳደር ጥሪ አቅርቧል።

@tikvahethiopia
😱803😢181😭135🙏128126🕊37🥰24🤔23😡14👏1
TIKVAH-ETHIOPIA
" ለመሬት መንቀጥቀጡ ምክንያት የሆነው ቅልጥ አለት መሬት ውስጥ መምጣቱ ነው " - ኤልያስ ሌዊ (ዶ/ር) ዛሬ ጠዋት 1 ሰዓት ከ37 ደቂቃ ከ50 ሴኮንድ ላይ የመሬት መንቀጥቀጥ ተከስቷል። ቦታው  ባለፈው በተከሰተበት አዋሽ ፈንታሌ አካባቢ ሲሆን በሬክተር ስኬል 4.6 አካባቢ እነደሆነ ተገልጿል። የዛሬው የመሬት መንቀጥቀጥ ንዝረት አዲስ አበባ ድረስ በደንብ ተሰምቷል። በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የጂኦፊዚክስና…
#Alert🚨

ከደቂቃዎች በፊት በአዲስ አበባ የተለያዩ አካባቢዎች የመሬት መንቀጥቀጥ ንዘረት እንደሰሙ ነዋሪዎች ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ጠቁመዋል።

" በተለይም ፎቅ ላይ በደንብ ይታወቅ ነበር " ብለዋል።

ጎተራ፣ አያት ፣ ባልደራስ ፣ ሰሚት ፣ መካኒሳ ፣ ጀሞ ፣ ኮዬ ፣ ጣፎ ፣ ቱሉ ዲምቱ ፣ ጦር ኃይሎች ፣ ቀጨኔ፣ ጎፋ ... እንዲሁም ከሌሎች በርካታ አካባቢዎች ቲክቫህ ኢትዮጵያ ንዝረቱ መሰማቱን የሚመለከቱ መልዕክቶችን ተቀብሏል።

ይህ የመሬት መንቀጥቀጥ ንዝረት በቀናት ውስጥ ለሶስተኛ ጊዜ ነው።

ሰሞኑን በአዋሽ ፈንታሌ አካባቢ የመሬት መንቀጥቀጥ እየተከሰተ መሆኑ ይታወቃል።

ይህም የመሬት መንቀጥቀጥ ንዝረቱ አዲስ አበባ እና ሌሎች ከተሞች ድረስ እየተሰማ ነው።

@tikvahethiopia
😭1.74K🙏330188😱147🕊94🤔48😢46🥰39😡34👏31
#Alert🚨

ከመቐለ ወደ ዓዲግራት የሚወሰደው ዋና የመኪና መንገድ አጉላዕ በተባለ ቦታ መዘጋቱ ተጓዦች ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።

" መንገዱ ከዲሞብላይዜሽን (DDR) ጋር በተያያዘ ጥያቄ ባነሱ የቀድሞ የትግራይ ታዋጊ አባላት ነው የተዘጋው " ብለዋል።

ጥያቄው በዝርዝር ምን እንደሆነ የሚታወቅ ነገር የለም።

መንገዱ ከዛሬ ታህሳስ 1/2017 ዓ.ም ጠዋት ጀምሮ ይህ መረጃ እስከወጣበት ከቀኑ 7:00 ድረስ ተዘግቷል።

መንገዱ በመዘጋቱ ምክንያት ከመቐለ የተነሱ መኪኖች 40 ኪሎ ሜትር ከተጓዙ በኋላ አጉላዕ ከተማ ደርሰው ወደ ውቕሮ ዓዲግራት እና ሌሎች ቦታዎች ማለፍ አይችሉም።

ከዓዲግራት ፣ ወቕሮ እና ሌሎች ከተሞች የመጡት ደግሞ አጉላዕ ደርሰው ወደ መቐለ ከተማ ማለፍ አይችሉም ብለዋል ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ቃላቸውን የሰጡ መንገደኞች።

ተጓዦች መንገዱ በመዘጋቱ ምክንያት ለከፍተኛ እንግልት መጋለጣቸው ገልፀው ፤ እስካሁን መንገዱን የዘጉትን የቀድሞ ተዋጊዎች አባላትን ጥያቄ ሰምቶ መልስ የሰጣቸው የለም ብለዋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ የመቐለ ቤተሰብ ጉዳዩ ተከታትሎ ያለውን መረጃ እንደሚያቀርብ ከወዲሁ ይጠቁማል።

#TikvahEthiopiaFamilyMekelle

@tikvahethiopia
👏390115🕊75😭72😱50🤔40😡39😢30🙏29🥰16
TIKVAH-ETHIOPIA
#Earthquake : ከጥቂት ደቂቃዎች በፊት ንዝረቱ አዲስ አበባ ድረስ የተሰማ የመሬት መንቀጥቀጥ አዋሽ አካባቢ ተከስቶ ነበር። በርካታ የቲክቫህ ቤተሰብ አባላት  መንቀጥቀጡ እና ንዝረቱ ከእንቅልፋቸው እንደቀሰቀሳቸውና ጠንክሮ እንደተሰማቸው መልዕክት ልከዋል። በተለይ አዲስ አበባ የጋራ መኖሪያ ቤቶች ላይ ጠንከር ብሎ ንዝረቱ ተሰምቷል። ከንዝረቱ ጋር በተያያዘ መልዕክት የላከ የቤተሰባችን አባል ፥…
🚨 #Alert

ከጥቂት ደቂቃዎች በፊት ተከስቶ የነበረው የመሬት መንቀጥቀጥ ከአዋሽ 23 ኪሎሜትር ርቀት ላይ ሲሆን የጀርመኑ የጂኦሳይንስ ሪሰርች ማዕከል መንቀጥቀጡ በሬክተር ስኬል 5.0 መመዝገቡን አሳውቋል።

የአሜሪካ ጃኦሎጂካል ሰርቬይ ደግሞ በሬክተር ስኬል 4.9 መለካቱን አመላክቷል።

ንዝረቱ አዲስ አበባ የተለያዩ ሰፈሮች ተሰምቷል።

@tikvahethiopia
😢732😭295🙏207194🕊108👏58🤔53🥰50😱44😡9
TIKVAH-ETHIOPIA
የትግራይ ጉዳይ ወዴት ? በትግራይ ክልል ያሉ የበላይ ወታደራዊ ኃይል አመራሮች እንደሆኑ የገለጹ መኮንኖች ዛሬ መግለጫ ሰጥተው ነበር። በዚህም ' የተዳከመ ' ያሉት በአቶ ጌታቸው ረዳ የሚመራው የክልሉ ጊዜያዊ አስተዳደር ተነስቶ በሌላ እንዲዋቀር መወሰናቸውን ገልጸዋል። " የጊዜያዊ አስተዳደሩ እንደ አዲስ እንዲዋቀር ውሳኔ አሳልፈናል " ብለዋል። " በፕሪቶሪያ ስምምነት መሠረት የተቋቋመው የትግራይ…
🚨#Alert

" የወጣው መግለጫ ግልፅ የሆነ መፈንቀለ መንግስት ያወጀ እና የፕሪቶሪያውን ውል ለአደጋ የሚያጋልጥ ነው ! " - የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር

" ህጋዊ ያልሆነ ቡድን ደግፎ ጊዚያዊ አስተዳደሩ ለማፍረስ ፤ ስርዓት አልበኝነት ለማስፈን እና ሰራዊቱን ለመበተን መንቀሳቀስ ተቀባይነት የሌለው እንደሆነ " የትግራይ ጊዚያዊ  አስተዳደር አስታወቀ።

ጊዚያዊ አስተዳደሩ ዛሬ ጥር 15/2017 ዓ.ም በትግራይ ሰራዊት ከፍተኛ አመራሮች ስም የወጣው መግለጫ አላማውን የሳተ እና ሰራዊቱ ከተሰጠው ተልእኮ ውጭ ነው ብሏል።

ጊዚያዊ አስተዳደሩ ፤ " በሰራዊት ከፍተኛ አዣዦች ስም የወጣው መግለጫ እንደማያውቀው በማንኛውም መመዘኛ ተቀባይነት የሌለው ያልተለመደ ተግባር ነው " ብሎታል።

የጊዚያዊ አስተዳደሩ ካቢኔ " ያልተለመደ ተግባር " ሲል የገለፀውን ውሳኔ አስመልክቶ ለመወያየት አስቸኳይ ስብሰባ መጥራቱን እና ሁኔታውን መርምሮ ዝርዝር ማብራርያ እንደሚሰጥ አስታውቀዋል።

" በከፍተኛ የሰራዊት አዛዦች ስም የወጣው መግለጫ ግልፅ የሆነ መፈንቀለ መንግስት ያወጀ እና የፕሪቶሪያውን ውል ለአደጋ የሚያጋልጥ ነው " ብሏል ጊዚያዊ አስተዳደሩ።

" ሃላፊነት የጎደለውን ውሳኔው ወደ ታች ለማውረድ ጥድፍያ የተሞላበት እንቅስቃሴ በመደረግ ላይ መሆኑ ደርሼቤታለሁ " ያለው የጊዚያዊ አስተዳደሩ " የሚያስከትለው አደጋው እጅግ ከፍተኛ  መሆኑ በመረዳት ተግባሩ በአስቸኳይ መቆም አለበት " ሲል አስጠንቅቋል።

" መላው የፀጥታ አካላት ህገ-ወጥ ውሳኔው የህዝቡን ችግር የሚያባብስ የጦርነት አዋጅ እና ስርዓት አልበኝነት የሚያስከትል መሆኑ በመገንዘብ በፅናት እንድትቃወሙት ትእዛዙን ተግባራዊ እንዳታደርጉ አስታውቃለሁ " ሲልም አክሏል።

#TikvahEthiopiaFamilyMekelle

@tikvahethiopia
🕊507155😡73🤔72👏33🙏27😱26😭20😢19🥰15
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
🚨#Alert

ከደቂቃዎች በፊት ከፍ ያለ የመሬት መንቀጥቀጥ አዋሽ አካባቢ ተከስቷል።

ንዝሩት በአዲስ አበባና ሌሎች ከተሞች ተሰምቷል።

ቃላቸውን የላኩልን የቤተሰባች አባላት " ዛሬ በጣም የሚያስፈራ ነበር። ሰሞኑን ድግግሞሹ ቀንሶ ነበር። ዛሬ በድንገት በሚያስፈራ ሁኔታ ነው የተሰማን " ብለዋል።

@tikvahethiopia
😭1.14K🙏313😢134😱115106🕊96👏38🤔37😡28🥰13
🚨 #ALERT

አሁን ከደቂቃዎች በፊት በርካቶችን ከተኙበት የቀሰቀሰቀሰ የመሬት መንቀጥቀጥ ተከስቷል።

ንዝረቱ በአዲስ አበባ እና የተለያዩ ከተሞች ከፍ ብሎ ተሰምቷል።

መልዕክታቸውን የላኩ የቲክቫህ ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት " የዛሬው ንዝረት ከእስካሁኑ የተለየና የሚያስደነግጥ ነበር " ሲሉ ገልጸዋል።

በርካቶችም በንዝረቱ ምክንያት ከእንቅልፍ መባነናቸውን ጠቁመዋል።

@tikvahethiopia
😭1.44K🙏334😱173168😢60🕊60🤔41👏40😡22🥰16
TIKVAH-ETHIOPIA
🔈#የኢትዮጵያውያንድምጽ 🔴 “ደስ ካላቸው በቀን ሁለት ጊዜ ካልሆነ አንድ ጊዜ ነው ምግብ የሚሰጡን። ምግብ ባጋጣሚ ስናገኝ ነው የምንመገበው” - ኢትዮጵያውያን በማይናማር ➡️ “ ቶኪዮ ያለው የኢትዮጵያ ኤምባሲ ‘የጎሳ ጦርነት አለ (ማይናማር)። ልጆቹን አስገድደው ወደ ጦርነት እንዳይከቷቸው ስጋት አለኝ’ ብሏል” - የወላጆች ኮሚቴ ወደ 600 የሚሆኑ ኢትዮጵያውያን ከእገታው ቦታ ወጥተው አስቸጋሪውን ስራ…
🚨 #Alert

“ ባለንባቸው ካምፓች የመሬት መንቀጥቀጥ ተከስቷል። ህንፃው ተሰነጣጥቋል። ካጠገባችን የተደረመሰም አለ” - ከ730 በላይ ኢትዮጵያውን በማይናማር

በማይናማር ከ730 በላይ ኢትዮጵያውያን ባሉባቸው የተለያዩ ካምፓች 7.7 የተመመዘገበ መሬት መንቀጥቀጥ መከሰቱን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።

“ለሞት እሩብ ጉዳይ ላይ ነን። ህንፃዎቹ ተሰነጣጥቀዋል። ከኛ አጠገብ የተደረመሰም አለ። እዚህ ባለመውጣታችን ስቃያችን በዝቷል። እባካችሁ አስወጡን” ሲሉ በሀዘን ስሜት ተማጽነዋል።

BGF ካምፕ በሦስት ህንጻዎች በተከታይ 204፣ 118፣ 59 በድምሩ 381፤ KK2 PARK አካባቢ 62፣ KK4 PARK አካባቢ 37፤ በአጠቃላይ ቢዲኤፍ ካምፕ 480፣ DKBA ካምፕ 255 ኢትዮጵያውያን እንዳሉ፤ በነዚሁ በሁሉም ህንፃዎች መሬት መንቀጥቀጡ እንደተከሰተ ገልጸዋል።

ኢትዮጵያውያኑ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በዝርዝር ምን አሉ?

“ዛሬ ኢትዮጵያውያን ባለንባቸው ህንጻዎች የመሬት መንቀጥቀጥ ተከስቶ ነበር። እኛ ለጊዜው ተርፈናል፤ የተጎዳም የለም።

ያለንበት ህንፃ ግን ተሰነጣጥቋል። የተደረመሰ ህንፃም አለ ካለንበት ትንሽ ራቅ ያለ። ከ40 በላይ የሥፍራው ሰራተኞች ተጎድተዋል።

ኬቢጅኤፍ ካምፕ 480፣ ዲኬቢኤ 255 ኢትዮጵያውያን አለን። በፍጥነት ወደ ታይላንድ ብሎም ኢትዮጵያ አለመጓዛችን ለዘርፈ ብዙ ችግሮች እየዳረገን ነው።

ተደራራቢና ጽኑ ህመም የሚሰቃዩ፣ እንዳናጣቸው እያሰጉን ያሉ ልጆች አብረውን አሉ። የጦርነቱም ድምጽ ከእለት እለት ወዳለንበት አካባቢ እየተጠጋ ነው።

የኢትዮጵያ አየር መንገድ ቻርተር ፕሌን ልኮም ቢሆን በቶሎ የምንወጣበትን ሁኔታ ካልተፈጠረ አስቸጋሪ ነው። አሁን ላይ ስጋት፣ ድብርት፣ ጭንቀት ጽኑ ህመም፣ የብዙዎቻችን ፈተና ሆኗል።

ቢዲኤፍ ካምፕ ላይ 260 ኢትዮጵያውያን አለን። የመሬት መንቀጥቀጡ እኛም ጋ ተከስቷል። ዶርም ውስጥ ነበርን ውጭ ወጣን ሲከሰት። 

እግዚአብሔር ይመስገን በዛሬው መሬት መንቀጥቀጥ ጉዳት አልደርሰብን። ለቀጣዩ ግን ከሌላው ስቃያችን በተጨማሪ ይህን ከፍተኛ ስጋት ደቅኖብናል።

መንግስት ምነው እንደዚህ እከምሆን ዝም አለን?” ሲሉ ጠይቀዋል።

የአሜሪካ ጂኦሎጂካል ሰርቬይ (USGS) በማይናማር የተከሰተውን መሬት መንቀጥቀጥ በሬክተር ስኬል 7.7 የመዘገበው ሲሆን፣ የቻይናው የመሬት መንቀጥቀጥ ኔትወርክ (CENC) ደግሞ በሬክተር ስኬል 7.9 የተመዘገበ መሆኑን አሳውቋል።

(ቪድዮ እና ፎቶ፦ ባንኮክ እና ማይናማር)

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia
😭588111😢55🙏40😡17😱16🕊16🥰10👏10💔6🤔3
🚨#Alert

በትግራይ ክልል ላጋጠመ የደን ቃጠሎ የፌደራል መንግስት እገዛ ተጠየቀ። በሄሊኮፕተር የተደገፈ የውሃ ርጭት እገዛ እንዲደረግ ነው የተጠየቀው።

የትግራይ ክልል የአደጋ ስጋት አመራር ኮሚሽን ዛሬ ሰኔ 18/2017 ዓ.ም ለፌደራል የአደጋ ስጋትና አመራር ኮሚሽን በደብዳቤ እንዳስታወቀው ፤ በትግራይ ምስራቃዊ ዞን አፅቢ ወረዳ ቃልአሚን ቀበሌ  ሓይለ-ቡሐለ ልዩ ቦታ በሚገኘው የዱስኣ ጥብቅ ደን የእሳት ቃጠሎ አጋጥሟል።

" በዓፋር ክልል ልዩ ቦታ ገረብ ዋሕለ የጀመረው ቃጠሎ በሃይለኛ ንፋስ እየተስፋፋ ከፍተኛ ጉዳት በማድረስ ላይ ይገኛል " ብሏል።

" የአከባቢው ማህበረሰብ ቃጠሎው በባህላዊ መንገድ ለማጥፋት ከፍተኛ ርብርብ በማድረግ ላይ ይገኛል " ያለው ኮሚሽኑ " ባለው ደረቅ የአየር ሁኔታና ሃይለኛ ንፋስ እየተባባሰ የከፋ ጉዳት በማድረስ ላይ ነው " ሲል ገልጿል።

የተከሰተው የእሳት ቃጠሎ ከአከባቢው ማህበረሰብ አቅም በላይ በመሆኑ የክልሉ ጊዚያዊ አስተዳደርና የፌደራል መንግስት እገዛ ተጠይቋል።

የእሳት ቃጠሎው በቁጥጥር ስር ለማዋል የፌደራል መንግስት በሄሊኮፕተር የተደገፈ የውሃ ርጭት እገዛ በአስቸኳይ እንዲያደርግ ኮሚሽኑ ጠይቀዋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ
መቐለ
#TikvahEthiopiaFamilyMekelle

@tikvahethiopia            
1.03K😢257😭116🕊84🤔29😡23👏22🙏22😱19🥰4
#Alert🚨

" በጥቆማው መሰረት መድኃኒቱ ችግር ያለበት መሆኑን በመታወቁ ከሁሉም ተቋማት እንዲወገድ ተደርጓል " - የምግብ እና መድኃኒት ባለሥልጣን

የኢትዮጵያን ምግብ እና መድኃኒት ባለሥልጣን " NURATION (10mg Thiamine monohydrate+3mg Pyridoxine Hydrochloride+15mcg Cyanocobalamin) sugar coated tablet supplement " የተሰኘ መድኃኒት ከደረጃ በታች ሆኖ በመገኘቱ ማህበረሰቡ እንዳይጠቀመው አሳስቧል።

ይህ ከደረጃ በታች የሆነ ፕሮዳክት የ ሦስት (ቢ 1 ፣ቢ 6 እና ቢ 12 የተሰኙ) ቫይታሚኖች ስብጥር ሲሆን የቫይታሚን እጥረት እና የነርቭ ችግር ላለባቸው ሰዎች የሚታዘዝ መድኃኒት መሆኑን ባለሥልጣኑ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ አሳውቋል።

ባለሥልጣኑ " በህጋዊ መንገድ የተመዘገበው መድኃኒት ገበያ ላይ አለ ነገር ግን በማመሳሰል የተሰራው እና ማህበረሰቡ እንዲያውቀው ያልነው መድኃኒት ከህጋዊው መድኃኒት ጋር በይዘት (Content) በማመሳሰል ገበያ ላይ የወጣውን ነው "  ብሏል።

ሃሰተኛው መድኃኒት ማሸጊያ ላይ " Zhejiang Medicine and Health care product " የሚል ጽሁፍ ስለመኖሩም አሳውቋል።

በኢትዮጵያ የምግብ እና መድኃኒት ባለሥልጣን የመድኃኒት ደህንነት እና ማርኬቲንግ ሰርቬላንስ ዴስክ ሃላፊ አቶ ተሽታ ሹቴ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በሰጡት ቃል ምን አሉ ?

" ይህ ቫይታሚን ከፍተኛ የሆኑ የ ይዘት (Content) ችግር አለበት።

የተቀመጡት ቫይታሚኖች መጠንም :-

° ' ቫይታሚን ቢ 1 ' 100 mg መሆን ሲገባው የያዘው 10 mg ነው።

° ' ቫይታሚን ቢ 6 ' 200 mg መሆን ሲገባው የያዘው 3 mg ነው።

° ' ቫይታሚን ቢ 12 ' 1000 micro gram መሆን ሲገባው የያዘው 15 micro gram ብቻ ነው።

ይህ ከፍተኛ የሆነ የይዘት ልዩነት ከመኖሩም በላይ መድኃኒት ነው ብለን መጥራትም አንችልም።

እስካልተመዘገበ እና ፈዋሽነቱም እስካልተረጋገጠ ድረስ በአናሳ ሚሊ ግራምም ቢሆን መድኃኒት ነው ብለን የምንቀበልበት ምክንያት የለም።

ህብረተሰቡ መድኃኒት ነው ብሎ እንዳይጠቀም፣ ጤና ባለሞያዎችም እንዳያዙ፣ የክልል ተቆጣጣሪዎችም የራሳቸውን እርምጃ እንዲወስዱ በሚል አሳውቀናል።

ይህንን ያሰራጨው አቅራቢ የብቃት ማረጋገጫው ተሰርዞበታል በህጋዊ መንገድም ፍርድ ቤት ይቀርባል።

ራስ ደስታ ሆስፒታል በጨረታ ከአቅራቢው እነዚህን መድኃኒቶች ወስዶ እየተጠቀመው ነበር።

መድኃኒቱ በ ጴጥሮስ ሆስፒታል ላይ እጥረት ባጋጠመበት ወቅት በመንግስት ሆስፒታሎች መካከል የመድኃኒቶች የውስጥ ዝውውር ስለሚፈቀድ ከራስ ደስታ ሆስፒታል የተጠቀሰው መድኃኒት ወደ ጴጥሮስ ሆስፒታል በሄደበት ወቅት ከጴጥሮስ ሆስፒታል ለ ባለሥልጣን መስሪያ ቤቱ መድኃኒቱ ችግር ያለበት ስለመሆኑ ጥቆማ ደርሷል።

በጥቆማው መሰረት መድኃኒቱ ችግር ያለበት መሆኑን በመታወቁ ከሁሉም ተቋማት እንዲወገድ ተደርጓል።

በአቅርቦት ሰንሰለቱ ውስጥ ሌላ ቦታ የተጠቀሰው ፕሮዳክት አለ ወይ የሚል ማጣራት ተደርጓል ባጣራነው መሰረትም መድኃኒቱን አላገኘንም በሁለቱ ሆስፒታሎች የነበረውም እንዲወገድ ተደርጓል።

አቅራቢውም በፍርድ ቤት ለመጠየቅ እየተንቀሳቀስን ነው " ብለዋል።

NB. ህጋዊው እና ህገወጥ መድኃኒቱ ስላላቸው ልዩነት ከተያያዘው ምስል ላይ ይመልከቱ።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvahEthiopiaFamliyAA

@tikvahethiopia
1.09K😭83🙏55🤔16😱16🕊13😡11👏9🥰8😢7💔5