TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
63K photos
1.61K videos
217 files
4.38K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

መረጃ እና መልዕክት ፦ 0919743630

ማርኬቲንግ ፦ 0979222111 ወይም
0979333111

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
TIKVAH-ETHIOPIA
#ይነበብ ትምህርት ሚኒስቴር በሀገሪቱ የትምህርት ጥራትን ለማስጠበቅ ተግባራዊ ማድረግ ከጀመራቸው ስራዎች አንዱ የሆነ የተመራቂ ተማሪዎች የመውጫ ፈተና ከነገ ሐምሌ 3 ቀን 2015 ዓ/ም ይጀምራል። በዚህ ፈተና ወቅት ከተማሪዎች እና ከፈታኞች ምን እጠበቃል ? [ ከተፈታኞች የሚጠበቅ ] - ተፈታኞች ወደ መፈተኛ ክፍላቸው ሲመጡ ማንኛውም አይነት ስልክ፣ ስማርት ሰዓት ፣ ታብሌት ፣ ላፕቶፕና ... ወዘተ…
#ይነበብ2

የመውጫ ፈተና በሚሰጥባቸው ቀናት ከሚኖሩ ዲስፕሊንና እና ፕሮቶኮል መካከል ፦

- ከተፈቀደላቸው የዩኒቨርስቲው ከፍተኛ አመራሮች፣ ለእለቱና ለዛ ፈተና ከተመደቡ አስተባባሪዎች፣ ለፈተናው ከተመደቡ ፈታኞች ውጭ የትኛውም አካል ወደ መፈተኛ ክፍል መግባት በጥብቅ የተከለከለ ነው።

- ፈተናው በኦንላይን ስለሚሰጥ የአይሲቲ ሙያተኞች በመፈተኛ ክፍሎች አቅራቢያ በመሆን ድጋፍ ይሰጣሉ፡፡

- የፀጥታ ሃይል ወደ መፈተኛ ክፍል እንዲገባ አስገዳጅ ሁኔታ ከተፈጠረ በማንኛውም ጊዜ ሊገባ ይችላል፡፡

- የዩኒቨርስቲ የበላይ ኃላፊዎችን ጨምሮ የትኛውም አካል በምንም ሁኔታ ስልክ፣ ስማርት ዋች፣ ታብሌት እና ተመሳሳይ ቁሶችን ይዞ ወደ መፈተኛ ክፍል መግባት አይችልም፡፡

- የአይሲቲ ሙያተኞች በመፈተኛ ክፍሎች የሚስጡት ድጋፍ ከትምህርት ሚኒስቴር ባልደረቦች ወይም ከዩኒቨርስቲው አመራር ድጋፍና አመራር ማግኘትን ስለሚያካትት በልዩ ሁኔታ በዩኒቨርስቲው ተመዝግቦ የሚያዝና የሚታወቅ ቁጥር ያለው ስልክ ይዘው ወደ መፈተኛ አዳራሽ እንዲገቡ ሊፈቀድ ይችላል፡፡

- በአንዳንድ ፕሮግራሞች #ካልኩሌተር ማምጣት ይፈቀዳል፡፡ በተጨማሪም በአንዳንድ ፕሮግራሞች ለማስልያ የሚረዳ ንፁህ ወረቀት በዩኒቨርሰቲዎች በኩል ሊፈቀድ ይችላል፡፡ ይህም ሆኖ ስልክ፣ ስማርት ዋች፤ ታብሌት እና ተመሳሳይ ቁሶችን እንደ ካልኩሌተር መጠቀም ፈፅሞ አይፈቀደም፡፡ ሥራ ላይ የሚውሉ ካልኩሌተሮች የተራቀቁና ፕሮግራ መብል እንዳይሆነ ተገቢውን ጥንቃቄ ማድረግ ይገባል፡፡

- በማንኛውም ወቅት ከተፈቀደላቸውና ለድጋፍ ከተመደቡ የአይ.ሲ.ቲ ባለሙያዎች በስተቀር የተፈታኙን መፈተኛ ኮምፒውተር መንካት በጥብቅ የተከለከለ ነው፡፡

(ተጨማሪ ከላይ ያንብቡ)

በድጋሚ መልካም ፈተና !

@tikvahethiopia
👍1.03K👎329106🕊36🙏23🥰21😱17😢17
#ExitExam

የቅድመ-ምረቃ መርሐግብር ተማሪዎች የመውጫ ፈተና ከነገ ሰኔ 2 ቀን 2017 ዓ.ም ጀምሮ እስከ ሰኔ 10 ቀን 2017 ዓ/ም ድረስ ይሰጣል።

ከ190 ሺህ በላይ ተፈታኞች የመውጫ ፈተናውን በ51 ዩኒቨርሲቲዎች በተዘጋጁ 87 የፈተና ማዕከላት ይወስዳሉ፡፡ ከእነዚህ ውስጥ 88 ሺህ የሚሆኑት ዳግም የመውጫ ፈተናውን የሚወስዱ ናቸው።

የመውጫ ፈተናው በ238 የትምህርት መርሐግብሮች በበይነ መረብ ነው የሚሰጠው።

የተከለከሉ ነገሮች ምንድናቸው ?

➡️ የማይፈቀዱ የሂሳብ ማሽኖች (በአንዳንድ ፕሮግራሞች #ካልኩሌተር ማምጣት ይፈቀዳል፡፡ ሆኖም ግን ስልክ፣ ስማርት ዋች፤ ታብሌትና ተመሳሳይ ቁሶችን እንደ ካልኩሌተር መጠቀም ፈፅሞ አይፈቀደም። ሥራ ላይ የሚውሉ ካልኩሌተሮች የተራቀቁ እንዲሁም ፕሮግራመብል እንዳይሆኑ ተገቢውን ጥንቃቄ ማድረግ ይገባል)፣
➡️ ተንቀሳቃሽ ስልክ፣
➡️ ሜሞሪ ያለው የእጅ ሰዓት፣
➡️ የተጭበረበሩ ሰነዶች፣
➡️ የራስ ያልሆነ መታወቂያ፣
➡️ አጫጭር ማስታወሻዎች፣
➡️ ማንኛውንም ዓይነት የጦር መሣሪያ ይዞ መገኘት ክልክል ነው።

በተጨማሪም ፦
⚠️ አደንዛዥ ዕጽ ተጠቅሞ መምጣት፣
⚠️ ከፈተና አስፈጻሚዎች ጋር አሉታዊ ተጽእኖ ያላቸው ውዝግቦችን መፍጠር፣
⚠️ያለመታወቂያ ካርድ ወደ ፈተና ማእከል መሄድ፣
⚠️ ያለፈቃድ ፈተና ማዕከል መገኘት፣
⚠️ ለሌላ ሰው መፈተን ፍጹም የተከለከሉ የዲሲፒሊን ጥሰቶች ናቸው።

ተፈታኝ ተማሪዎች ፈተናው ከመጀመሩ ከ30 ደቂቃ ቀድመው በተመደቡበት የፈተና ክፍል መገኘት የሚኖርባቸው ሲሆን ፤ ከተመደቡበት ክፍል ውጪ መፈተን ውጤት ያሰርዛል።

ተፈታኞች የፋይዳ መታወቂያ መያዝ ይኖርባቸዋል።

መያዝ የሚፈቀደው የፋይዳ መታወቂያ ፦
- በኢትዮ ቴሌኮም ወይም የኢትዮጵያ ፖስታ አገልግሎት አማካኝነት የታተመ የፋይዳ መታወቂያ፣
- ከ "Fayda ID" ሞባይል መተግበሪያ ፣ ከቴሌብር ሱፐር አፕ፣ እንዲሁም ሲቢኢ ብር ሞባይል መተግበሪያ ላይ #QR_ኮድ በማውረድ እና በወረቀት በማሳተም መያዝ ይቻላል።

📵 ዲጂታል የፋይዳ መታወቂያ ኮፒ በስልክ ይዞ መገኘት አይቻልም።

በሌላ ሰው ስም፣ User Name እና Pasword መፈተን አይቻልም፡፡

ከላይ የተዘረዘሩ የፈተና ስርአቶችን የጣሰ ተፈታኝ ውጤቱ ተሰርዞ በዲሲፒሊን ጥሰት የሚጠየቅ መሆኑ ተገልጿል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ ለመላው ተፈታኞች መልካም እና በውጤቱም የምትደሰቱበት የልፋታችሁን ፍሬ የምታዩበት የተሳካ ፈተና እንዲሆን ይመኛል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ
#TikvahEthiopiaFamily

@tikvahethiopia
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
1.29K🙏153😭64🕊39🥰20😱17😡14🤔12👏9😢3