#update አዲስ አበባ⬇️
አዲሱ የአዲስ አበባ አስተዳደር የኮንዶሚኒየምና የቀበሌ ቤቶች ቆጠራ #በድጋሚ እንዲካሄድ ትዕዛዝ መጠቱ ተሰማ፡፡
ካቢኔው ከ2003 ዓ.ም. ወዲህ ለመጀመርያ ጊዜ የመሬትና #መሬት ነክ አገልግሎት ዘርፍ #ኦዲት እንዲደረግ ወስኗል፡፡
በቀድሞ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ድሪባ ኩማ የሥልጣን ዘመን የኮንዶሚኒየም ቤቶችና የቀበሌ ቤቶች ቆጠራ ተካሂዶ የነበረ ቢሆንም አዲሱ አስተዳዳር “እንደገና ይቆጠር” ብሏል፡፡
©ዋዜማ ራድዮ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
አዲሱ የአዲስ አበባ አስተዳደር የኮንዶሚኒየምና የቀበሌ ቤቶች ቆጠራ #በድጋሚ እንዲካሄድ ትዕዛዝ መጠቱ ተሰማ፡፡
ካቢኔው ከ2003 ዓ.ም. ወዲህ ለመጀመርያ ጊዜ የመሬትና #መሬት ነክ አገልግሎት ዘርፍ #ኦዲት እንዲደረግ ወስኗል፡፡
በቀድሞ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ድሪባ ኩማ የሥልጣን ዘመን የኮንዶሚኒየም ቤቶችና የቀበሌ ቤቶች ቆጠራ ተካሂዶ የነበረ ቢሆንም አዲሱ አስተዳዳር “እንደገና ይቆጠር” ብሏል፡፡
©ዋዜማ ራድዮ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
👍1
TIKVAH-ETHIOPIA
#ETHIOPIA የፌዴራል ዋና ኦዲተር መ/ ቤት በመንግሥት ተቋማት በርካታና ሰፋ ያሉ የኦዲት ክፍተቶችን በኦዲት ሪፖርት ማረጋገጡን አስታውቋል። ባለፈው ፤ ማክሰኞ ለፓርላማው የፌዴራል ዋና ኦዲተር መሥሪያ ቤት ሪፖርት ቀርቦ ነበር። ይህ ሪፖርት እንደሚያመለክተው የ2014 ዓ.ም. በጀት አፈጻጸምን በተመለከተ በተደረገው የኦዲት ሥራ 6 ተቋማት አስተያየት ለመስጠት ያልተቻለባቸው ሲሆኑ 19 ተቋማት ደግሞ…
#ኦዲት
" በ86 የመንግስት መስሪያ ቤቶች 6 ቢሊዮን 838 ሚሊዮን 886 ብር ተመላሽ እንዲደረግ ሙያዊ አስተያየት ቢሰጥም 0.65 በመቶው ብቻ ነው ተመላሽ የሆነው " - የፌዴራል ዋና ኦዲተር መ/ቤት
የመንግስት ወጪ፣ አስተዳደርና ቁጥጥር ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ አቶ ክርስትያን ታደለ ፤ የመንግስት እና የሕዝብ ኃብት ለታለመለ ዓለማ እያዋለ ባለመሆኑ ሙስና እና ብልሹ አሰራር የብሔራዊ ስጋት እየሆነ ስለመጣ የፍትህ ተቋማት ኃላፊነታቸውን እንዲወጡ አሳሰቡ።
አቶ ክርስቲያን ታደለ ይህ ያሳሰቡት ከቀናት በፊት የፌዴራል ዋና ኦዲተር መ/ቤት ለፓርላማው የ2014 ዓ/ም የፌዴራል መስሪያ ቤቶች የፋይናንስ ክንዋኔ ሪፖርት ባቀረበበት ወቅት ነው።
" የመንግስት እና የሕዝብ ኃብት ለታለመለት ዓለማ በትክክል እንዲውል ዋና ኦዲተር መ/ቤት እያደረገ ያለውን ጥረት የሚበረታታ ነው " ያሉት አቶ ክርስቲያን " የክዋኔ ኦዲት ስራዎች በዓለም አቀፍ ደረጃ ጥራታቸውን የጠበቁ እንዲሆኑ በማድረግ የሪፖርቱን ተአማኒነት እና ተቀባይነትን ማረጋገጥ ይገባል " ብለዋል።
ዋና ኦዲተር የአስፈጻሚ መስሪያ ቤቶችን ዕቅድ እና ሪፖርት በወቅቱ በመገምገም የተሻለ ውጤት እንዲመጣ በይበልጥ ጥረቱን አጠናክሮ መስራት እንደሚጠበቅበት አስገንዝበዋል።
አቶ ክርስቲያን ፤ " አስፈጻሚው አካል ለኦዲት ግኝቶች ትኩረት ባለመስጠት የገንዝብ የመመለስ ምጣኔው በጣም ዝቅተኛ በመሆኑ፤ የሕዝብ ተወካዮች ም/ቤት ተቋማትን በመቆጣጠርና ተጠያቂነትን ማስፈን ይጠበቅበታል " ብለዋል።
" የመንግስት እና የሕዝብ ኃብት ለታለመለ ዓለማ እያዋለ ባለመሆኑ ሙስና እና ብልሹ አሰራር የብሔራዊ ስጋት እየሆነ የመጣ በመሆኑ የፍትህ ተቋማት ኃላፊነታቸውን በአግባቡ መወጣት አለባቸው " ሲሉም አሳስበዋል።
የፌደራል የዋና ኦዲተር መስሪያ ቤት ዋና ኦዲተር ወ/ሮ መሰረት ዳምጤ በበኩላቸው ፤ " በ86 የመንግስት መ/ ቤቶች 6 ቢለዮን 838 ሚሊዮን 886 ብር ተመላሽ እንዲደረግ ሙያዊ አስተያየት ቢሰጥም 0.65 በመቶው ብቻ ተመላሽ በመደረጉ የሚፈለገውን ለውጥ እያመጣ አይደለም። " ሲሉ ተናግረዋል።
ዋና ኦዲተሯ ፤ በተወሰኑ የመንግስት እና የህዝብ ሃብት ባባከኑ የስራ ኃላፊዎች ላይ የገንዘብ ቅጣት እና የፅሁፍ ማስጠንቀቂያ እርምጃ በገንዘብ ሚኒስቴር መወሰዱን ሲናገሩ ተደምጠዋል።
#HoPR
@tikvahethiopia
" በ86 የመንግስት መስሪያ ቤቶች 6 ቢሊዮን 838 ሚሊዮን 886 ብር ተመላሽ እንዲደረግ ሙያዊ አስተያየት ቢሰጥም 0.65 በመቶው ብቻ ነው ተመላሽ የሆነው " - የፌዴራል ዋና ኦዲተር መ/ቤት
የመንግስት ወጪ፣ አስተዳደርና ቁጥጥር ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ አቶ ክርስትያን ታደለ ፤ የመንግስት እና የሕዝብ ኃብት ለታለመለ ዓለማ እያዋለ ባለመሆኑ ሙስና እና ብልሹ አሰራር የብሔራዊ ስጋት እየሆነ ስለመጣ የፍትህ ተቋማት ኃላፊነታቸውን እንዲወጡ አሳሰቡ።
አቶ ክርስቲያን ታደለ ይህ ያሳሰቡት ከቀናት በፊት የፌዴራል ዋና ኦዲተር መ/ቤት ለፓርላማው የ2014 ዓ/ም የፌዴራል መስሪያ ቤቶች የፋይናንስ ክንዋኔ ሪፖርት ባቀረበበት ወቅት ነው።
" የመንግስት እና የሕዝብ ኃብት ለታለመለት ዓለማ በትክክል እንዲውል ዋና ኦዲተር መ/ቤት እያደረገ ያለውን ጥረት የሚበረታታ ነው " ያሉት አቶ ክርስቲያን " የክዋኔ ኦዲት ስራዎች በዓለም አቀፍ ደረጃ ጥራታቸውን የጠበቁ እንዲሆኑ በማድረግ የሪፖርቱን ተአማኒነት እና ተቀባይነትን ማረጋገጥ ይገባል " ብለዋል።
ዋና ኦዲተር የአስፈጻሚ መስሪያ ቤቶችን ዕቅድ እና ሪፖርት በወቅቱ በመገምገም የተሻለ ውጤት እንዲመጣ በይበልጥ ጥረቱን አጠናክሮ መስራት እንደሚጠበቅበት አስገንዝበዋል።
አቶ ክርስቲያን ፤ " አስፈጻሚው አካል ለኦዲት ግኝቶች ትኩረት ባለመስጠት የገንዝብ የመመለስ ምጣኔው በጣም ዝቅተኛ በመሆኑ፤ የሕዝብ ተወካዮች ም/ቤት ተቋማትን በመቆጣጠርና ተጠያቂነትን ማስፈን ይጠበቅበታል " ብለዋል።
" የመንግስት እና የሕዝብ ኃብት ለታለመለ ዓለማ እያዋለ ባለመሆኑ ሙስና እና ብልሹ አሰራር የብሔራዊ ስጋት እየሆነ የመጣ በመሆኑ የፍትህ ተቋማት ኃላፊነታቸውን በአግባቡ መወጣት አለባቸው " ሲሉም አሳስበዋል።
የፌደራል የዋና ኦዲተር መስሪያ ቤት ዋና ኦዲተር ወ/ሮ መሰረት ዳምጤ በበኩላቸው ፤ " በ86 የመንግስት መ/ ቤቶች 6 ቢለዮን 838 ሚሊዮን 886 ብር ተመላሽ እንዲደረግ ሙያዊ አስተያየት ቢሰጥም 0.65 በመቶው ብቻ ተመላሽ በመደረጉ የሚፈለገውን ለውጥ እያመጣ አይደለም። " ሲሉ ተናግረዋል።
ዋና ኦዲተሯ ፤ በተወሰኑ የመንግስት እና የህዝብ ሃብት ባባከኑ የስራ ኃላፊዎች ላይ የገንዘብ ቅጣት እና የፅሁፍ ማስጠንቀቂያ እርምጃ በገንዘብ ሚኒስቴር መወሰዱን ሲናገሩ ተደምጠዋል።
#HoPR
@tikvahethiopia
👍877❤108👎99😱36😢29🕊9🥰8🙏7
#ዓለምአቀፍ #ፖላንድ
በፖላንድ ፤ እ.አ.አ. ከ2011 ጀምሮ ለቪዛ ያመለከቱ ሰዎች ዝርዝር ላይ #ኦዲት ሊደረግ ነው ተባለ።
በፖላንድ ለአፍሪካውያን በክፍያ ቪዛ እየተሰጠ ነው በሚል መንግሥት ላይ ጥያቄ ማስነሳቱን ቢቢሲ በድረገፁ አስነብቧል።
የፖላንድ የላይኛው ምክር ቤት አፈ ጉባኤ ቶማዝ ግሮዲዚ በአገሪቱ ገንዘብ እየተቀበሉ ቪዛ የመስጠት አካሄድ ተባብሷል ብለዋል።
መንግሥት ስለ ጉዳዩ ምን መረጃ እንዳለው ይፋ እንዲያደርግም ጠይቀዋል። ነገሩ የአገሪቱን ስም እያጠለሸ ነው ብለዋል።
መንግሥት የተወሰነ መረጃ ይፋ ያደረገ ሲሆን ፤ እንደ መገናኛ ብዙኃን ዘገባ ግን ስደተኞች እስከ 5,000 ዶላር እየከፈሉ የሥራ ቪዛ የማግኘት ሂደቱን ያፋጥናሉ ተብሏል።
እስካሁን ሰባት ሰዎች ላይ ክስ ቢመሠረትም ከመካከላቸው የመንግሥት ባለሥልጣን እንደሌለ ታውቋል።
የአገሪቱ ምክትል የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ፒዮር ዋውዚክ ፤ ባለፈው ሳምንት ክሶችን ተከትሎ ከሥራ ተነስተዋል። የፖላንድ ፀረ ሙስና ኮሚሽን መሥሪያ ቤቱ ላይ ምርመራ ካደረገ በኋላ ነው የተባረሩት።
የሕግ ክፍሉ ዳይሬክተርም ተባረዋል።
እ.አ.አ. ከ2011 ጀምሮ ለቪዛ ያመለከቱ ሰዎች ዝርዝር ላይ ኦዲት እንደሚደረግ ተገልጿል።
ተቃዋሚ የምክር ቤት አባል ፤ እስከ 250,000 ቪዛዎች ሕግ ሳይከተሉ ለእስያ እና አፍሪካ አመልካቾች ተሰጥተዋል ሲሉ ገልጸዋል።
መንግሥት ግን ቁጥሩ በጥቂት መቶዎች ብቻ የሚቆጠር ነው ሲል አስተባብሏል።
የተቃዋሚ ፓርቲ መሪ ዶናልድ ተስክ ፤ " ከአፍሪካ ፖላንድ መምጣት የፈለገ ሁላ ከኤምባሲያችን ቪዛ ገዝቶ አገራችን በቀላሉ ይገባል " ብለዋል።
የፖላንድ ጠቅላይ ሚኒስትር ግን ይህ ንግግር ቀውስ እንደሚያስከትል ገልጸው ችግሩ የተባለውን ያህል እንዳልሆነ ተናግረዋል።
" አገራችን ኃላፊነት የሚሰማት ዴሞክራሲያዊ አገር ሆና ሳለ የነጻውን ዓለም ደኅንነት አደጋ ውስጥ የምትከት ሆና እንድትታይ የሚያደርግ አካሄድ ስለሆነ በጥልቀት ሊብራራ ይገባል። ይህ የ21ኛው ክፍለ ዘመን ትልቁ ቅሌት ነው። ሙስና በመንግሥታችን ተንሰራፍቷል " ሲሉ የላይኛው ምክር ቤት አባል አሳስበዋል።
የፍትሕ ሚኒስተሩ ዚግኒው ዚዎብሮ ፤ ይህ አባባል የተጋነነ ነው ሲሉ ለብሔራዊ ቴሌቭዥን ጣቢያ ተናግረዋል።
ይህ ጉዳይ ከስደተኞች ጉዳይ ጋር በተያያ በቀጣዩ የፓርላማ ምርጫ ተጽዕኖ እንደሚያሳድር መገለፁን ቢቢሲ ዘግቧል።
@tikvahethiopia
በፖላንድ ፤ እ.አ.አ. ከ2011 ጀምሮ ለቪዛ ያመለከቱ ሰዎች ዝርዝር ላይ #ኦዲት ሊደረግ ነው ተባለ።
በፖላንድ ለአፍሪካውያን በክፍያ ቪዛ እየተሰጠ ነው በሚል መንግሥት ላይ ጥያቄ ማስነሳቱን ቢቢሲ በድረገፁ አስነብቧል።
የፖላንድ የላይኛው ምክር ቤት አፈ ጉባኤ ቶማዝ ግሮዲዚ በአገሪቱ ገንዘብ እየተቀበሉ ቪዛ የመስጠት አካሄድ ተባብሷል ብለዋል።
መንግሥት ስለ ጉዳዩ ምን መረጃ እንዳለው ይፋ እንዲያደርግም ጠይቀዋል። ነገሩ የአገሪቱን ስም እያጠለሸ ነው ብለዋል።
መንግሥት የተወሰነ መረጃ ይፋ ያደረገ ሲሆን ፤ እንደ መገናኛ ብዙኃን ዘገባ ግን ስደተኞች እስከ 5,000 ዶላር እየከፈሉ የሥራ ቪዛ የማግኘት ሂደቱን ያፋጥናሉ ተብሏል።
እስካሁን ሰባት ሰዎች ላይ ክስ ቢመሠረትም ከመካከላቸው የመንግሥት ባለሥልጣን እንደሌለ ታውቋል።
የአገሪቱ ምክትል የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ፒዮር ዋውዚክ ፤ ባለፈው ሳምንት ክሶችን ተከትሎ ከሥራ ተነስተዋል። የፖላንድ ፀረ ሙስና ኮሚሽን መሥሪያ ቤቱ ላይ ምርመራ ካደረገ በኋላ ነው የተባረሩት።
የሕግ ክፍሉ ዳይሬክተርም ተባረዋል።
እ.አ.አ. ከ2011 ጀምሮ ለቪዛ ያመለከቱ ሰዎች ዝርዝር ላይ ኦዲት እንደሚደረግ ተገልጿል።
ተቃዋሚ የምክር ቤት አባል ፤ እስከ 250,000 ቪዛዎች ሕግ ሳይከተሉ ለእስያ እና አፍሪካ አመልካቾች ተሰጥተዋል ሲሉ ገልጸዋል።
መንግሥት ግን ቁጥሩ በጥቂት መቶዎች ብቻ የሚቆጠር ነው ሲል አስተባብሏል።
የተቃዋሚ ፓርቲ መሪ ዶናልድ ተስክ ፤ " ከአፍሪካ ፖላንድ መምጣት የፈለገ ሁላ ከኤምባሲያችን ቪዛ ገዝቶ አገራችን በቀላሉ ይገባል " ብለዋል።
የፖላንድ ጠቅላይ ሚኒስትር ግን ይህ ንግግር ቀውስ እንደሚያስከትል ገልጸው ችግሩ የተባለውን ያህል እንዳልሆነ ተናግረዋል።
" አገራችን ኃላፊነት የሚሰማት ዴሞክራሲያዊ አገር ሆና ሳለ የነጻውን ዓለም ደኅንነት አደጋ ውስጥ የምትከት ሆና እንድትታይ የሚያደርግ አካሄድ ስለሆነ በጥልቀት ሊብራራ ይገባል። ይህ የ21ኛው ክፍለ ዘመን ትልቁ ቅሌት ነው። ሙስና በመንግሥታችን ተንሰራፍቷል " ሲሉ የላይኛው ምክር ቤት አባል አሳስበዋል።
የፍትሕ ሚኒስተሩ ዚግኒው ዚዎብሮ ፤ ይህ አባባል የተጋነነ ነው ሲሉ ለብሔራዊ ቴሌቭዥን ጣቢያ ተናግረዋል።
ይህ ጉዳይ ከስደተኞች ጉዳይ ጋር በተያያ በቀጣዩ የፓርላማ ምርጫ ተጽዕኖ እንደሚያሳድር መገለፁን ቢቢሲ ዘግቧል።
@tikvahethiopia
👍435❤64😢13👎12🕊10😱9🥰4🙏2
#ሚዛን_ቴፒ_ዩኒቨርሲቲ #ኦዲት
የሚዛን ቴፒ ዩኒቨርሲቲ በ2014 ዓ / ም በጀት ዓመት ሲንከባለሉ የቆዩ የሒሳብ ጉድለት እንዳሉበት በሕዝብ ተወካዮች ም/ቤት የመንግሥት ወጪ አስተደደር እና ቁጥጥር ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ አስታውቋል።
ይህንን ያስታወቀው የዩኒቨርሲቲውን የ2014 ዓ/ም በጀት ዓመት የኦዲት ሪፖርት ሕጋዊነትን በተመለከተ ከባለድርሻ አካላት ጋር ውይይት ባደረገበት ወቅት ነው።
የዩኒቨርሲቲው የሒሳብ የኦዲት ጉድለቶች ተብለው በቋሚ ኮሚቴው የቀረቡት ምንድናቸው ?
- ለዩኒቨርሲቲው ማስፋፊያ ቦታ ለባለ ይዞታዎች ካሳ ቢከፈልም እስካሁን ከቦታው አልተነሱም። ለባለ ይዞታዎቹ የካሳ ክፍያ ቢፈጸምላቸውም ምንም ዓይነት ሰነድ (ካርታ) አላቀረቡም ፤ ግለሰቦቹ በመሬቱ ላይ ያላቸው ሀብትና ንብረት በሚመለከተው አካል ሳይረጋገጥ ክፍያ ተፈፅሟል። ተነሺዎቹ በገቡት ውል መሠረት የካሳ ክፍያው በተፈጸመ በ1 ወር ጊዜ ውስጥ ይዞታቸውን እንዲለቁ ቢጠበቅም፣ አንድም ግለሰብ ቦታውን አለቀቀም።
- ከተጋባዥ መምህራን ያልተሰበሰበ ቅድመ ግብር ፣ ለአካዴሚክ የሕክም እና ባለሙያዎች ከደንብና ከመመርያው ውጪ " ቶፕ አፕ " ተብሎ በድምሩ ከ41 ሚሊዮን ብር በላይ ማስተካከያ እንዲደረግ ቢጠየቅም እስካሁን ድረስ ግን አልተስተካከለም።
- በሥራ ገበታቸው እያሉ #ስብሰባ (ኮንፈረንስ) ለ2 ቀናት ለተሳተፉ ሠራተኞች የ18 ቀናት የውሎ አበል በቀን 171 ብር ተሠልቶ ያላግባብ ተከፍሏቸዋል።
- የተሟላ መረጃ ሳይቀርብ በወጪ መመዝገብ፣ ቀኑን በመጨመር ያላግባብ የውሎ አበል መክፈል፣ ከቀረበ ማስረጃ በላይ አስበልጦ መክፈልና የተሽከርካሪ ዕቃዎች ግዥ ሲፈጸም ያለ ደረሰኝ (በዱቤ) ሽያጭ ደረሰኝ 3,259,439 ብር ክፍያ ተፈፅሟል።
- በግባንታ ላይ ያሉ ' 12 ፕሮጀክቶች ' በተያዘላቸው የጊዜ ገደብ ተጠናቀው ለአገልግሎት አልዋሉም። ተቋራጮቹ በገቡት ውል መሠረት መሥራታቸውን ለማረጋገጥ ኦዲት ሲደረግ ከግንባታ ክፍል በተገኘው መረጃ መሠረት በርካታ ክፍተቶች ተገኝተዋል።
ከዚህ ውስጥ ፦
* ሉሲ ኮንስትራክሽን የተሰኘ የኮንስትራክሽን ኩባንያ 233,432,359.95 ብር ለቴፒ ካምፓስ የመማሪያ ሕንፃ ግንባታና ለመምህራን አዳራሽ ሚያዝያ 25 ቀን 2012 ዓ.ም. ጀምሮ ነሐሴ 21 ቀን 2014 ዓ.ም እንዲያጠናቀቅ በውሉ ቢገለጽም፣ እስከ ሰኔ 30 ቀን 2014 ዓ.ም. ግንባታው 56 በመቶ ላይ ብቻ ይገኛል።
* ኮንስትራክሽን ተቋራጩ (ሉሲ) በ73,652,906.05 ሳንቲም ለጂምናዚየም ግንባታ ሐምሌ 11 ቀን 2008 ዓ.ም. ጀምሮ እስከ ታኅሳስ 15 ቀን 2012 ማጠናቀቅ እንደሚገባው፣ ተቋራጩ በተሰጠው ጊዜ ውስጥ ሳይጨርስ ሌላ ፕሮጀክት ተሰጥቶታል።
* የውኃ አቅርቦት ግንባታ በ 300,283,120.83 ብር በጀት ሉሲ ኮንስትራክሽን ኩባንያ ሰኔ 28 ቀን 2013 ዓ.ም. ጀምሮ የካቲት 28 ቀን 2015 ዓ.ም. ግንባታውን እንዲያጠናቅቅ ፕሮጀክቱ ቢሰጠውም፣ ግንባታው እስካሁን አሥር በመቶ ላይ ይገኛል።
- ለግንባታና ለጥገና ለተደራጁ ማኅበራት ቅድመ ክፍያ ሲሰጥ ካደራጇቸው የመንግሥት ተቋማት የዋስትና ደብዳቤ ሳያቀርቡ 4,918,356.18 ብር ተከፍሏል።
በአጠቃላይ በዩኒቨርሲቲው ባለፉት ዓመታት ዕርምጃ ያልወሰደበት #ከ46_ሚሊዮን_ብር_በላይ የሚሆን የበጀት ጉደለት ቢኖርም ማስተካከያ የተደረገበት የበጀት ጉድለት አንድ በመቶ/1% አይሆንም ተብሏል።
ቋሚ ኮሚቴው ሚዛን ቴፒ ዩኒቨርሲቲ የኦዲት ግኝት አስተያየቶችን ለማረም እያደረገ ያለው ጥረት በቂ አለመሆኑን ከዚህ በኋላ ኃላፊነታቸውን በማይወጡ ኃላፊዎች ላይ ተገቢው ዕርምጃ መወሰድ እንዳለበት፣ ሕጎችንና መመርያዎችን ማክበር እንደሚገባ አሳስቧል።
የፌዴራል ዋና ኦዲተር መ/ቤ ምን አለ ?
- በዩኒቨርሲቲው ሕጋዊ ሒደትን ያልተከተለ የግንባታ ፕሮጀክቶች ውል፣ ተገቢ ያለሆነ የአበል ክፍያ፣ ለባለ ይዞታዎች ያለ በቂ መረጃ የተከፈለ የቦታ ካሳ ክፍያና ያለ በቂ የአዋጭነት ጥናት የተጀመሩ የገቢ ማመንጫ ሥራዎች በኦዲት ግኝት ተረጋግጧል።
- በተያዘላቸው ጊዜ ያልተጠናቀቁ ፕሮጀክቶች መኖር፣ በማዕቀፍ መከናወን የነበረባቸው ግዥዎች በግለሰብ መፈጸማቸው፣ ሕጋዊ ደረሰኝ ያልተገኘላቸው ግዥዎች መኖራቸውን ጨምሮ፣ በዩኒቨርሲቲው ዕርምጃ ያልተወሰደበት የኦዲት ግኝት ከ59 ሚሊዮን ብር በላይ እንዲደርስ አድርጎታል።
- ዩኒቨርሲቲው የውስጥ ቁጥጥርና የኦዲት ሥርዓት ደካማ በመሆኑ፣ ከ200 ሺሕ ብር በላይ ወደ ግለሰብ ኪስ እንደገባና ሕጋዊ ሒደቱን ባልተከተለ ግዥ መንግሥት ከ1.9 ሚሊዮን ብር በላይ አጥቷል።
የሚዛን ቴፒ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት ዶ/ር አህመድ ሙስጠፋ ምን አሉ ?
- የኦዲት ግኝቶችን ለማረም ጥረቶች በመደረግ ላይ ናቸው።
- በዩኒቨርሲቲው የሚገነቡ ፕሮጀክቶችን በተያዘላቸው ጊዜ ለማጠናቀቅ የበጀት እጥረት፣ የፀጥታ ችግርና የግንባታ ግብዓቶች ዋጋ መናር ምክንያቶችች ናቸው።
- የበጀት እና የንብረት አጠቃቀምን ለማስተካከል የዕውቀት ክፍተት አለ፤ ከሚመለከታቸው ተቋማት ጋር በመሆን የሰው ኃይል የማብቃት ሥራ በማከናወን ላይ ይገኛል።
- የካሳ ክፍያ የተከፈለባቸው ከ60 በላይ ይዞታዎች ውስጥ 46 ያህሉን ዩኒቨርሲቲው ተረክቧል። ሕግና ሥርዓትን በጣሱ ግለሰቦች ላይ የዕርምት ዕርምጃ እየተወሰደባቸው ነው።
መረጃው ከሪፖርተር ጋዜጣ የተገኘ ነው።
@tikvahethiopia
የሚዛን ቴፒ ዩኒቨርሲቲ በ2014 ዓ / ም በጀት ዓመት ሲንከባለሉ የቆዩ የሒሳብ ጉድለት እንዳሉበት በሕዝብ ተወካዮች ም/ቤት የመንግሥት ወጪ አስተደደር እና ቁጥጥር ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ አስታውቋል።
ይህንን ያስታወቀው የዩኒቨርሲቲውን የ2014 ዓ/ም በጀት ዓመት የኦዲት ሪፖርት ሕጋዊነትን በተመለከተ ከባለድርሻ አካላት ጋር ውይይት ባደረገበት ወቅት ነው።
የዩኒቨርሲቲው የሒሳብ የኦዲት ጉድለቶች ተብለው በቋሚ ኮሚቴው የቀረቡት ምንድናቸው ?
- ለዩኒቨርሲቲው ማስፋፊያ ቦታ ለባለ ይዞታዎች ካሳ ቢከፈልም እስካሁን ከቦታው አልተነሱም። ለባለ ይዞታዎቹ የካሳ ክፍያ ቢፈጸምላቸውም ምንም ዓይነት ሰነድ (ካርታ) አላቀረቡም ፤ ግለሰቦቹ በመሬቱ ላይ ያላቸው ሀብትና ንብረት በሚመለከተው አካል ሳይረጋገጥ ክፍያ ተፈፅሟል። ተነሺዎቹ በገቡት ውል መሠረት የካሳ ክፍያው በተፈጸመ በ1 ወር ጊዜ ውስጥ ይዞታቸውን እንዲለቁ ቢጠበቅም፣ አንድም ግለሰብ ቦታውን አለቀቀም።
- ከተጋባዥ መምህራን ያልተሰበሰበ ቅድመ ግብር ፣ ለአካዴሚክ የሕክም እና ባለሙያዎች ከደንብና ከመመርያው ውጪ " ቶፕ አፕ " ተብሎ በድምሩ ከ41 ሚሊዮን ብር በላይ ማስተካከያ እንዲደረግ ቢጠየቅም እስካሁን ድረስ ግን አልተስተካከለም።
- በሥራ ገበታቸው እያሉ #ስብሰባ (ኮንፈረንስ) ለ2 ቀናት ለተሳተፉ ሠራተኞች የ18 ቀናት የውሎ አበል በቀን 171 ብር ተሠልቶ ያላግባብ ተከፍሏቸዋል።
- የተሟላ መረጃ ሳይቀርብ በወጪ መመዝገብ፣ ቀኑን በመጨመር ያላግባብ የውሎ አበል መክፈል፣ ከቀረበ ማስረጃ በላይ አስበልጦ መክፈልና የተሽከርካሪ ዕቃዎች ግዥ ሲፈጸም ያለ ደረሰኝ (በዱቤ) ሽያጭ ደረሰኝ 3,259,439 ብር ክፍያ ተፈፅሟል።
- በግባንታ ላይ ያሉ ' 12 ፕሮጀክቶች ' በተያዘላቸው የጊዜ ገደብ ተጠናቀው ለአገልግሎት አልዋሉም። ተቋራጮቹ በገቡት ውል መሠረት መሥራታቸውን ለማረጋገጥ ኦዲት ሲደረግ ከግንባታ ክፍል በተገኘው መረጃ መሠረት በርካታ ክፍተቶች ተገኝተዋል።
ከዚህ ውስጥ ፦
* ሉሲ ኮንስትራክሽን የተሰኘ የኮንስትራክሽን ኩባንያ 233,432,359.95 ብር ለቴፒ ካምፓስ የመማሪያ ሕንፃ ግንባታና ለመምህራን አዳራሽ ሚያዝያ 25 ቀን 2012 ዓ.ም. ጀምሮ ነሐሴ 21 ቀን 2014 ዓ.ም እንዲያጠናቀቅ በውሉ ቢገለጽም፣ እስከ ሰኔ 30 ቀን 2014 ዓ.ም. ግንባታው 56 በመቶ ላይ ብቻ ይገኛል።
* ኮንስትራክሽን ተቋራጩ (ሉሲ) በ73,652,906.05 ሳንቲም ለጂምናዚየም ግንባታ ሐምሌ 11 ቀን 2008 ዓ.ም. ጀምሮ እስከ ታኅሳስ 15 ቀን 2012 ማጠናቀቅ እንደሚገባው፣ ተቋራጩ በተሰጠው ጊዜ ውስጥ ሳይጨርስ ሌላ ፕሮጀክት ተሰጥቶታል።
* የውኃ አቅርቦት ግንባታ በ 300,283,120.83 ብር በጀት ሉሲ ኮንስትራክሽን ኩባንያ ሰኔ 28 ቀን 2013 ዓ.ም. ጀምሮ የካቲት 28 ቀን 2015 ዓ.ም. ግንባታውን እንዲያጠናቅቅ ፕሮጀክቱ ቢሰጠውም፣ ግንባታው እስካሁን አሥር በመቶ ላይ ይገኛል።
- ለግንባታና ለጥገና ለተደራጁ ማኅበራት ቅድመ ክፍያ ሲሰጥ ካደራጇቸው የመንግሥት ተቋማት የዋስትና ደብዳቤ ሳያቀርቡ 4,918,356.18 ብር ተከፍሏል።
በአጠቃላይ በዩኒቨርሲቲው ባለፉት ዓመታት ዕርምጃ ያልወሰደበት #ከ46_ሚሊዮን_ብር_በላይ የሚሆን የበጀት ጉደለት ቢኖርም ማስተካከያ የተደረገበት የበጀት ጉድለት አንድ በመቶ/1% አይሆንም ተብሏል።
ቋሚ ኮሚቴው ሚዛን ቴፒ ዩኒቨርሲቲ የኦዲት ግኝት አስተያየቶችን ለማረም እያደረገ ያለው ጥረት በቂ አለመሆኑን ከዚህ በኋላ ኃላፊነታቸውን በማይወጡ ኃላፊዎች ላይ ተገቢው ዕርምጃ መወሰድ እንዳለበት፣ ሕጎችንና መመርያዎችን ማክበር እንደሚገባ አሳስቧል።
የፌዴራል ዋና ኦዲተር መ/ቤ ምን አለ ?
- በዩኒቨርሲቲው ሕጋዊ ሒደትን ያልተከተለ የግንባታ ፕሮጀክቶች ውል፣ ተገቢ ያለሆነ የአበል ክፍያ፣ ለባለ ይዞታዎች ያለ በቂ መረጃ የተከፈለ የቦታ ካሳ ክፍያና ያለ በቂ የአዋጭነት ጥናት የተጀመሩ የገቢ ማመንጫ ሥራዎች በኦዲት ግኝት ተረጋግጧል።
- በተያዘላቸው ጊዜ ያልተጠናቀቁ ፕሮጀክቶች መኖር፣ በማዕቀፍ መከናወን የነበረባቸው ግዥዎች በግለሰብ መፈጸማቸው፣ ሕጋዊ ደረሰኝ ያልተገኘላቸው ግዥዎች መኖራቸውን ጨምሮ፣ በዩኒቨርሲቲው ዕርምጃ ያልተወሰደበት የኦዲት ግኝት ከ59 ሚሊዮን ብር በላይ እንዲደርስ አድርጎታል።
- ዩኒቨርሲቲው የውስጥ ቁጥጥርና የኦዲት ሥርዓት ደካማ በመሆኑ፣ ከ200 ሺሕ ብር በላይ ወደ ግለሰብ ኪስ እንደገባና ሕጋዊ ሒደቱን ባልተከተለ ግዥ መንግሥት ከ1.9 ሚሊዮን ብር በላይ አጥቷል።
የሚዛን ቴፒ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት ዶ/ር አህመድ ሙስጠፋ ምን አሉ ?
- የኦዲት ግኝቶችን ለማረም ጥረቶች በመደረግ ላይ ናቸው።
- በዩኒቨርሲቲው የሚገነቡ ፕሮጀክቶችን በተያዘላቸው ጊዜ ለማጠናቀቅ የበጀት እጥረት፣ የፀጥታ ችግርና የግንባታ ግብዓቶች ዋጋ መናር ምክንያቶችች ናቸው።
- የበጀት እና የንብረት አጠቃቀምን ለማስተካከል የዕውቀት ክፍተት አለ፤ ከሚመለከታቸው ተቋማት ጋር በመሆን የሰው ኃይል የማብቃት ሥራ በማከናወን ላይ ይገኛል።
- የካሳ ክፍያ የተከፈለባቸው ከ60 በላይ ይዞታዎች ውስጥ 46 ያህሉን ዩኒቨርሲቲው ተረክቧል። ሕግና ሥርዓትን በጣሱ ግለሰቦች ላይ የዕርምት ዕርምጃ እየተወሰደባቸው ነው።
መረጃው ከሪፖርተር ጋዜጣ የተገኘ ነው።
@tikvahethiopia
😱142❤96😡45👏24🕊21🥰11😢11🙏6😭5
#ኦዲት
#ለተከታታይ_ዓመታት ለተገኘበት በርከት ያለ የኦዲት ክፍተት ማስተካከያ ማድረግ እንደተሳነው የተገለፀው የኢትዮጵያ አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን ከአመራር መቀያየር ባለፈ ጥብቅ ሪፎርም እንደሚስፈልገው የፌደራል ዋና ኦዲተር አስታውቋል።
ይህንን ያስታወቀው፤ የሕ/ተ/ምክር ቤት የመንግሥት ወጪ አስተዳደር እና ቁጥጥር ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የአደጋ ሥጋት ሥራ አመራር ኮሚሽን በ2014 / 15 በጀት ዓመት ሒሳብ ኦዲት ላይ የዋና ኦዲተር መ/ቤት የሥራ ኃላፊዎች በተገኙበት ውይይት ሲደረግ ነው፡፡
መስሪያ ቤቱ ምን አለ ?
ኮሚሽኑ ፦
📄ለሚፈጽማቸው ክፈያዎች ደረሰኝ ባለማቅረብ፣
📄ኮፒ ደረሰኝ መጠቀም፣
📃በኮፒ ደረሰኝ ሂሳብ ማወራረድ፣
📄ያልተፈቀደ ክፈያ በመፈጸም፣
📄ለተከፈለ ገንዘብ ማስረጃ ባለማቅረብ፣ እንዲሁም #በቢሊዮኖች ብር የሚቆጠር ተከፋይ እና ተሰብሳቢ ውዝፍ የኦዲት ሪፖርት ተገኝቷል።
- ከሳዑዲ ከስደት ለተመለሱ 102 ሺህ ኢትዮጵያውያን ለኪስ አበል እንዲሁም ለቤት ኪራይ 5.2 ሚሊዮን ብር ማስረጃ ሳይቀርብ ተከፍሏል። ተከፈለ ለተባለው ለዚህ ገንዘብ ሰነድ ማግኘት ባለመቻሉ ትክክለኛነቱን ማረጋገጥ አልታቻለም።
- ለምግብ ዝግጅት ድርጅት ተብሎ የተከፈለና በወጪ የተመዘገበ 2.9 ሚሊዮን ብር እንዲሁም ዋጋው ከ65.3 ሚሊዮን ብር በላይ የሆነ 14 ሺህ ኩንታል ዱቄት " ናህሊ ዱቄት ፋብሪካ " ለተስኘ ድርጅት የተከፈለ ተብሎ የቀረበ ቢሆንም የቀረበው ደረሰኝ ግን ኮፒ ነው።
- በወጪ ሒሳብ ለተመዘገበ 79 ሚሊዮን ብር ለኦዲት ሥራ የሚፈለጉ የወጪ ማስመስከሪያዎች (ቫውቸሮች) ከደጋፊ ሰነዶች ጋር እንዲቀርቡ በተደጋጋሚ ቢጠየቅም ማስረጃ ሊቀርብ አልቻለም።
- ያልተወራረደ 881.5 ሚሊዮን ብር ተሰብሳቢ ሒሳብ መኖሩ በኦዲት ሪፖርት ቢረጋገጥም፣ ከኦዲት ግኝት በኋላ የተወሰደ ማስተካከያ የለም።
➡️ በወቅቱ ያልተወራረደ 39.7 ሚሊዮን ብር ተከፋይ ሒሳብና ያልተከፈለ ሲሆን ከኮሚሽኑ መደበኛ በጀት 37.6 ሚሊዮን ብር በሥራ ላይ አልዋለም።
በተጨማሪም ፦
* ውኃ የሚያስገቡ እና ጣሪያቸው የሚያፈሱ መጋዘኖች ተገኝተዋል።
* በቆይታ ብዛት የተበላሸ ብስኩት ሳይወገድ በግምጃ ቤት ተገኝቷል።
* የቆይታ ጊዜያቸው የማይታወቅና በውስጣቸው ምን እንዳለ የማይታወቅ የታሸጉ 9 ኮንቴነሮች በመጋዘን ግቢ ውስጥ ተገኝቷል።
* የመጠቀሚያ ጊዜያቸው ያለፈ ፦
🔹ሴሪላክ የዱቄት ወተት፣
🔹የወይራ ዘይት፣
🔹የምግብ ዘይት፣
🔹ብዛት ያላቸውና ጊዜያቸው ያለፈባቸው ቴምሮች፣
🔹የንፅህና መጠበቂያ ሞዴስ ተገኝቷል።
* በእህል መጋዘኖች ውስጥ የመጠቀሚያ ጊዜያቸው ሊያልፍ #ሁለት እና #ሦስት ወራት የቀራቸው አልሚ ምግቦች፣ ሳሙናዎችና እህሎች ተገኝቷል።
◾የአደጋ ሥጋት ሥራ አመራር ኮሚሽነር አምባሳደር ሽፈራው ተ/ማርያም የኦዲት ሪፖርት ላይ ለመምክር በተጠራው ውይይት አለመገኘታቸው ቋሚ ኮሚቴውን አስቆጥቷል።
በወቅቱ ውይይቱ ላይ የተገኙት ሌሎች የሥራ ኃላፊዎች ኮሚሸነሩ የቀሩት ሌላ ተልዕኮ ስለነበራቸው እንደሆነ ተናግረዋል፡፡
የፌዴራል ዋና ኦዲተር ወይዘሮ መሠረት ዳምጤ ምን አሉ ?
° ኮሚሽኑ ኃላፊዎችን #ከመቀያየር ባለፈ መሠረታዊ የአስተሳሰብ ለውጥ ያስፈልገዋል።
° በ2014 ዓ/ም የዋና ኦዲተር መስሪያ ቤት ኦዲተሮች ለጊዜያዊ የኦዲት ሥራ የተረከቡትን ቢሮ ኦዲት አድርገው በሚወጡበት ጊዜ የኮሚሽኑ ሠራተኞች በመግባት #ሰነድ እያወጡ መሆኑን መረጃ አለኝ።
° ይህ ኮሚሽን ለፈጸማቸው ክፍያዎች ሰነድ ማቅረብ አለመቻሉ መሠረታዊ ችግሩ ነው።
° ከዚህ በፊት የበላይ ኃላፊው ቢታሰሩም ኮሚሽኑ ግን አሁንም ሰንኮፉ አልተነቀለም፣ በመሠረታዊነት ችግሩ አልተቀረፈም።
° በመጋዘኖች ውስጥ በሚገኙ ንብረቶች ከፍተኛ ችግር አለ። ገንዘቡ አንዴት እንደሚመጣ እናውቀዋለን ነገር ግን እዚህ ያለው ሥራ የተዝረከረከ ነው፡፡
° በ2013 ዓ.ም. #ድሬዳዋ እና #ሻሸመኔ በሚገኙ መጋዘኖች ከታዩ ችግሮች በመነሳት የኦዲት አስተያየት የተሰጠንባቸው ጉዳዮች በ2014 ዓ.ም በድጋሚ ኦዲት ሲደረግ በነበሩበት እንጂ ተስተካክለው አልተገኙም።
° " ደመወዝ የምንበላበት ተቋም ነው፣ ስለዚህ እዚያ ያለውንም ሥራ ልክ እንደ ቤታችን ማየት አለብን፡፡ ይህ ሁሉ ቁሳቁስ የሚገዛው በብድር ነው እናውቃለን፡፡ እዚህ አምጥተን በአግባቡ የማይውል ከሆነ፣ መሬት ላይ የሚደፋና ከጋዝ ጋር ተቀላቅሎ የሚበላሽ ከሆነ ሥራው ትርጉም አልባ ነው "
° በዚህ ውይይት ላይ ያልተገኙት #ኮሚሽነሩ የቀሩት ዕርዳታ ለማፈላለግ ሊሆን ይችላል ፤ ነገር ግን ተቋሙ የተገኘውን ንብረት በተገቢው መንገድ ማስተዳደር ካልተቻለ፣ ዕርዳታ ማፈላለጉ ብቻ ትርጉም የሌለውና በቀዳዳ በርሜል ውኃ እንደመሙላት የሚቆጠር ነው።
የገንዘብ ሚኒስቴር ፤ የኢንስፔክሽን መምርያ ኮሚሽኑ በኮፒ ደረሰኝ ሒሳብ እንደሚያወራረድ በተደጋጋሚ ቢነገርም ሊስተካከል ባለመቻሉ ይህንን ያደረገ ኃላፊ መጠየቅ አለበት ብሏል።
More - https://telegra.ph/Reporter-12-14-2
ቲክቫህ ኢትዮጵያ ይህ መረጃ ባለቤትነቱ የ "ሪፖርተር ጋዜጣ " መሆኑን ያሳውቃል።
@tikvahethiopia
#ለተከታታይ_ዓመታት ለተገኘበት በርከት ያለ የኦዲት ክፍተት ማስተካከያ ማድረግ እንደተሳነው የተገለፀው የኢትዮጵያ አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን ከአመራር መቀያየር ባለፈ ጥብቅ ሪፎርም እንደሚስፈልገው የፌደራል ዋና ኦዲተር አስታውቋል።
ይህንን ያስታወቀው፤ የሕ/ተ/ምክር ቤት የመንግሥት ወጪ አስተዳደር እና ቁጥጥር ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የአደጋ ሥጋት ሥራ አመራር ኮሚሽን በ2014 / 15 በጀት ዓመት ሒሳብ ኦዲት ላይ የዋና ኦዲተር መ/ቤት የሥራ ኃላፊዎች በተገኙበት ውይይት ሲደረግ ነው፡፡
መስሪያ ቤቱ ምን አለ ?
ኮሚሽኑ ፦
📄ለሚፈጽማቸው ክፈያዎች ደረሰኝ ባለማቅረብ፣
📄ኮፒ ደረሰኝ መጠቀም፣
📃በኮፒ ደረሰኝ ሂሳብ ማወራረድ፣
📄ያልተፈቀደ ክፈያ በመፈጸም፣
📄ለተከፈለ ገንዘብ ማስረጃ ባለማቅረብ፣ እንዲሁም #በቢሊዮኖች ብር የሚቆጠር ተከፋይ እና ተሰብሳቢ ውዝፍ የኦዲት ሪፖርት ተገኝቷል።
- ከሳዑዲ ከስደት ለተመለሱ 102 ሺህ ኢትዮጵያውያን ለኪስ አበል እንዲሁም ለቤት ኪራይ 5.2 ሚሊዮን ብር ማስረጃ ሳይቀርብ ተከፍሏል። ተከፈለ ለተባለው ለዚህ ገንዘብ ሰነድ ማግኘት ባለመቻሉ ትክክለኛነቱን ማረጋገጥ አልታቻለም።
- ለምግብ ዝግጅት ድርጅት ተብሎ የተከፈለና በወጪ የተመዘገበ 2.9 ሚሊዮን ብር እንዲሁም ዋጋው ከ65.3 ሚሊዮን ብር በላይ የሆነ 14 ሺህ ኩንታል ዱቄት " ናህሊ ዱቄት ፋብሪካ " ለተስኘ ድርጅት የተከፈለ ተብሎ የቀረበ ቢሆንም የቀረበው ደረሰኝ ግን ኮፒ ነው።
- በወጪ ሒሳብ ለተመዘገበ 79 ሚሊዮን ብር ለኦዲት ሥራ የሚፈለጉ የወጪ ማስመስከሪያዎች (ቫውቸሮች) ከደጋፊ ሰነዶች ጋር እንዲቀርቡ በተደጋጋሚ ቢጠየቅም ማስረጃ ሊቀርብ አልቻለም።
- ያልተወራረደ 881.5 ሚሊዮን ብር ተሰብሳቢ ሒሳብ መኖሩ በኦዲት ሪፖርት ቢረጋገጥም፣ ከኦዲት ግኝት በኋላ የተወሰደ ማስተካከያ የለም።
➡️ በወቅቱ ያልተወራረደ 39.7 ሚሊዮን ብር ተከፋይ ሒሳብና ያልተከፈለ ሲሆን ከኮሚሽኑ መደበኛ በጀት 37.6 ሚሊዮን ብር በሥራ ላይ አልዋለም።
በተጨማሪም ፦
* ውኃ የሚያስገቡ እና ጣሪያቸው የሚያፈሱ መጋዘኖች ተገኝተዋል።
* በቆይታ ብዛት የተበላሸ ብስኩት ሳይወገድ በግምጃ ቤት ተገኝቷል።
* የቆይታ ጊዜያቸው የማይታወቅና በውስጣቸው ምን እንዳለ የማይታወቅ የታሸጉ 9 ኮንቴነሮች በመጋዘን ግቢ ውስጥ ተገኝቷል።
* የመጠቀሚያ ጊዜያቸው ያለፈ ፦
🔹ሴሪላክ የዱቄት ወተት፣
🔹የወይራ ዘይት፣
🔹የምግብ ዘይት፣
🔹ብዛት ያላቸውና ጊዜያቸው ያለፈባቸው ቴምሮች፣
🔹የንፅህና መጠበቂያ ሞዴስ ተገኝቷል።
* በእህል መጋዘኖች ውስጥ የመጠቀሚያ ጊዜያቸው ሊያልፍ #ሁለት እና #ሦስት ወራት የቀራቸው አልሚ ምግቦች፣ ሳሙናዎችና እህሎች ተገኝቷል።
◾የአደጋ ሥጋት ሥራ አመራር ኮሚሽነር አምባሳደር ሽፈራው ተ/ማርያም የኦዲት ሪፖርት ላይ ለመምክር በተጠራው ውይይት አለመገኘታቸው ቋሚ ኮሚቴውን አስቆጥቷል።
በወቅቱ ውይይቱ ላይ የተገኙት ሌሎች የሥራ ኃላፊዎች ኮሚሸነሩ የቀሩት ሌላ ተልዕኮ ስለነበራቸው እንደሆነ ተናግረዋል፡፡
የፌዴራል ዋና ኦዲተር ወይዘሮ መሠረት ዳምጤ ምን አሉ ?
° ኮሚሽኑ ኃላፊዎችን #ከመቀያየር ባለፈ መሠረታዊ የአስተሳሰብ ለውጥ ያስፈልገዋል።
° በ2014 ዓ/ም የዋና ኦዲተር መስሪያ ቤት ኦዲተሮች ለጊዜያዊ የኦዲት ሥራ የተረከቡትን ቢሮ ኦዲት አድርገው በሚወጡበት ጊዜ የኮሚሽኑ ሠራተኞች በመግባት #ሰነድ እያወጡ መሆኑን መረጃ አለኝ።
° ይህ ኮሚሽን ለፈጸማቸው ክፍያዎች ሰነድ ማቅረብ አለመቻሉ መሠረታዊ ችግሩ ነው።
° ከዚህ በፊት የበላይ ኃላፊው ቢታሰሩም ኮሚሽኑ ግን አሁንም ሰንኮፉ አልተነቀለም፣ በመሠረታዊነት ችግሩ አልተቀረፈም።
° በመጋዘኖች ውስጥ በሚገኙ ንብረቶች ከፍተኛ ችግር አለ። ገንዘቡ አንዴት እንደሚመጣ እናውቀዋለን ነገር ግን እዚህ ያለው ሥራ የተዝረከረከ ነው፡፡
° በ2013 ዓ.ም. #ድሬዳዋ እና #ሻሸመኔ በሚገኙ መጋዘኖች ከታዩ ችግሮች በመነሳት የኦዲት አስተያየት የተሰጠንባቸው ጉዳዮች በ2014 ዓ.ም በድጋሚ ኦዲት ሲደረግ በነበሩበት እንጂ ተስተካክለው አልተገኙም።
° " ደመወዝ የምንበላበት ተቋም ነው፣ ስለዚህ እዚያ ያለውንም ሥራ ልክ እንደ ቤታችን ማየት አለብን፡፡ ይህ ሁሉ ቁሳቁስ የሚገዛው በብድር ነው እናውቃለን፡፡ እዚህ አምጥተን በአግባቡ የማይውል ከሆነ፣ መሬት ላይ የሚደፋና ከጋዝ ጋር ተቀላቅሎ የሚበላሽ ከሆነ ሥራው ትርጉም አልባ ነው "
° በዚህ ውይይት ላይ ያልተገኙት #ኮሚሽነሩ የቀሩት ዕርዳታ ለማፈላለግ ሊሆን ይችላል ፤ ነገር ግን ተቋሙ የተገኘውን ንብረት በተገቢው መንገድ ማስተዳደር ካልተቻለ፣ ዕርዳታ ማፈላለጉ ብቻ ትርጉም የሌለውና በቀዳዳ በርሜል ውኃ እንደመሙላት የሚቆጠር ነው።
የገንዘብ ሚኒስቴር ፤ የኢንስፔክሽን መምርያ ኮሚሽኑ በኮፒ ደረሰኝ ሒሳብ እንደሚያወራረድ በተደጋጋሚ ቢነገርም ሊስተካከል ባለመቻሉ ይህንን ያደረገ ኃላፊ መጠየቅ አለበት ብሏል።
More - https://telegra.ph/Reporter-12-14-2
ቲክቫህ ኢትዮጵያ ይህ መረጃ ባለቤትነቱ የ "ሪፖርተር ጋዜጣ " መሆኑን ያሳውቃል።
@tikvahethiopia
😡363❤170👏53😱47😭41😢36🥰17🙏17🕊16
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#ሲቢኢ #ዩኒቨርሲቲዎች #ኦዲት
" ባንኩ ላይ የሳይበር ጥቃት ደርሷል፤ ዝውውሩም አይታወቅም ብለው አስበው ነው ያደረጉት " - አቶ አቤ ሳኖ
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ፕሬዜዳንት አቶ አቤ ሳኖ በዩኒቨርሲቲዎች አካባቢ ስለነበረው የመጋቢት 6 ለሊት የገንዘብ ዝውውር እና አጠቃላይ ወጭ ስለተደረገው / አሁን ስለተመለሰው የገንዘብ መጠን ምን አሉ ?
አቶ አቤ ሳኖ ፦
" የተቋረጠውን አገልግሎት ካስጀመርን በኃላ ወደ ግብይቶች ምርመራ ነው የገባነው።
በዛ ያለ ግብይት ያደረጉትን ለይተናቸው የፍትሕ አካላት እንዲያውቁት አድርገናል። በብዛት በዛ ያለ ቁጥር ያለው እጅግ በጣም በሚያሳዝን ሁኔታ #በዩኒቨርሲቲዎች አካባቢ ነው።
ተማሪዎቹ (የዩኒቨርሲቲ ማህበረሰብ) ያሰቡት ባንኩ ላይ የሳይበር ጥቃት ደርሷል ብለው ነው። ስለዚህ የሚደረገው ግብይት (ወጭ / ዝውውር) አይታወቅም ብለው ነው ያደረጉት።
አሁን ላይ ግን ግብይቱ እንደሚታወቅ ሲያውቁ የወሰዱትን ገንዘብ እየመለሱ ነው ያሉት። አሁንም እንዲመልሱ ነው የምንፈልገው።
የወሰዱትን ገንዘብ ከመለሱ ወደ ክስ አንሄድም። የማይመልሱ ከሆነ ግን የህግ እርምጃ እንወስዳለን።
ዝርዝር ጉዳዩ (ከገንዘብ ዝውውር/ወጭ የተደረገ/የተመለሰ) ኦዲት ተደርጎ ሲያልቅ ይቀርባል።
የኦዲት ሂደቱ ስላላለቀ በዚህ መካከል ሌሎች ነገሮችን ማንሳት ከፋይናንሻል ኦዲት አካሄድ ጋር የሚሄድ ስላልሆነ አንዳንድ የህጋዊ እርምጃዎችም ሊከተሉ ስለሚችሉ ጥንቃቄ ስለሚፈልግ ነው። "
@tikvahethiopia
" ባንኩ ላይ የሳይበር ጥቃት ደርሷል፤ ዝውውሩም አይታወቅም ብለው አስበው ነው ያደረጉት " - አቶ አቤ ሳኖ
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ፕሬዜዳንት አቶ አቤ ሳኖ በዩኒቨርሲቲዎች አካባቢ ስለነበረው የመጋቢት 6 ለሊት የገንዘብ ዝውውር እና አጠቃላይ ወጭ ስለተደረገው / አሁን ስለተመለሰው የገንዘብ መጠን ምን አሉ ?
አቶ አቤ ሳኖ ፦
" የተቋረጠውን አገልግሎት ካስጀመርን በኃላ ወደ ግብይቶች ምርመራ ነው የገባነው።
በዛ ያለ ግብይት ያደረጉትን ለይተናቸው የፍትሕ አካላት እንዲያውቁት አድርገናል። በብዛት በዛ ያለ ቁጥር ያለው እጅግ በጣም በሚያሳዝን ሁኔታ #በዩኒቨርሲቲዎች አካባቢ ነው።
ተማሪዎቹ (የዩኒቨርሲቲ ማህበረሰብ) ያሰቡት ባንኩ ላይ የሳይበር ጥቃት ደርሷል ብለው ነው። ስለዚህ የሚደረገው ግብይት (ወጭ / ዝውውር) አይታወቅም ብለው ነው ያደረጉት።
አሁን ላይ ግን ግብይቱ እንደሚታወቅ ሲያውቁ የወሰዱትን ገንዘብ እየመለሱ ነው ያሉት። አሁንም እንዲመልሱ ነው የምንፈልገው።
የወሰዱትን ገንዘብ ከመለሱ ወደ ክስ አንሄድም። የማይመልሱ ከሆነ ግን የህግ እርምጃ እንወስዳለን።
ዝርዝር ጉዳዩ (ከገንዘብ ዝውውር/ወጭ የተደረገ/የተመለሰ) ኦዲት ተደርጎ ሲያልቅ ይቀርባል።
የኦዲት ሂደቱ ስላላለቀ በዚህ መካከል ሌሎች ነገሮችን ማንሳት ከፋይናንሻል ኦዲት አካሄድ ጋር የሚሄድ ስላልሆነ አንዳንድ የህጋዊ እርምጃዎችም ሊከተሉ ስለሚችሉ ጥንቃቄ ስለሚፈልግ ነው። "
@tikvahethiopia
🤔982❤327😡222😭129👏96🕊61🙏51🥰40😢40😱28
#ኢትዮጵያ #ኦዲት
የፌዴራል ዋና ኦዲተር የ2015 የፌዴራል መንግሥት መ/ቤቶች የፋይናንስና ሕጋዊነት ኦዲት እና የክዋኔ ኦዲት ሪፖርት ለምክር ቤት እያቀረበ ይገኛል።
በዚህም ወቅት ተከታዩን ሰምተናል ፦
በ2014 የበጀት ዓመት እና ከዚያ በፊት በፌዴራል መንግሥት መስሪያ ቤቶች በተከናወነው የኦዲት ሪፖርት መሰረት እርምጃ የተወሰደ እንደሆነ ማጣራት ተደርጎ ነበር።
በ92 መስሪያ ቤቶች ተመላሽ እንዲደረግ ተብሎ አስተያየት ከተሰጠበት 443 ሚሊዮን ብር እና በዶላር 23,230 ከ43 ውስጥ ተመላሽ የተደረገው 48.2 ሚሊዮን ብቻ እንደሆነ ታውቋል፤ ይህም ተመላሽ ሊደረግ ከሚገባው ጋር ሲነጻጸር 11 በመቶ ብቻ ነው።
ቀሪው 394.8 ሚሊዮን እና 23,230 ከ43 ተገቢው እርምጃ ያልተወሰደበት እና ተመላሽ አልተደረገም።
በተጨማሪ በ2014 #የተሟላ_የማስረጃ_ሰነድ ካልቀረበበት 5 ቢሊዮን 61 ሚሊዮን ማስረጃ የቀረበበት 508. 1 ሚሊዮን ብቻ ሲሆን በመቶኛ 10% ብቻ ማስረጃው ቀርቦ ትክክለኝነቱ ተረጋግጧል።
የተመለሰው ትንሽ ቢሆንም አሰተያየት ተቀብለው ተመላሽ ካደረጉት ተቋማት ውስጥ ፦
➡ የኢንፎርሜሽን ደህንነት መረብ አስተዳደር 5.9 ሚሊዮን ተመላሽ እንዲያደርግ ተብሎ 5.8 መልሷል።
➡ አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ 4.1 ሚሊዮን ተመላሽ እንዲያደርግ ተብሎ 3.5 ሚሊዮን መልሷል።
➡ የስፔስ እና ጂኦስፔሻል ስልጠና ኢንስቲትዩት ተመላሽ እንዲያደርግ ከተባለው 5.6 ሚሊዮን ውስጥ 4.4 ሚሊዮን መልሷል።
የሰነድ ማስረጃ አቅርቡ ከተባሉት ውስጥ ፦
☑ አዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ 124.25 ሚሊዮን ውስጥ ሁሉንም መልሷል።
☑ የአደጋ ስራ አመራር ኮሚሽን 150.2 ሚሊዮን ውስጥ ሁሉንም መልሷል።
☑ አዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ከ3.9 ሚሊዮን 2.2 ሚሊዮን መልሷል።
ሰነዶቹም ትክክለኛ መሆናቸው ተረጋግጧል።
#TikvahEthiopia
@tikvahethiopia
የፌዴራል ዋና ኦዲተር የ2015 የፌዴራል መንግሥት መ/ቤቶች የፋይናንስና ሕጋዊነት ኦዲት እና የክዋኔ ኦዲት ሪፖርት ለምክር ቤት እያቀረበ ይገኛል።
በዚህም ወቅት ተከታዩን ሰምተናል ፦
በ2014 የበጀት ዓመት እና ከዚያ በፊት በፌዴራል መንግሥት መስሪያ ቤቶች በተከናወነው የኦዲት ሪፖርት መሰረት እርምጃ የተወሰደ እንደሆነ ማጣራት ተደርጎ ነበር።
በ92 መስሪያ ቤቶች ተመላሽ እንዲደረግ ተብሎ አስተያየት ከተሰጠበት 443 ሚሊዮን ብር እና በዶላር 23,230 ከ43 ውስጥ ተመላሽ የተደረገው 48.2 ሚሊዮን ብቻ እንደሆነ ታውቋል፤ ይህም ተመላሽ ሊደረግ ከሚገባው ጋር ሲነጻጸር 11 በመቶ ብቻ ነው።
ቀሪው 394.8 ሚሊዮን እና 23,230 ከ43 ተገቢው እርምጃ ያልተወሰደበት እና ተመላሽ አልተደረገም።
በተጨማሪ በ2014 #የተሟላ_የማስረጃ_ሰነድ ካልቀረበበት 5 ቢሊዮን 61 ሚሊዮን ማስረጃ የቀረበበት 508. 1 ሚሊዮን ብቻ ሲሆን በመቶኛ 10% ብቻ ማስረጃው ቀርቦ ትክክለኝነቱ ተረጋግጧል።
የተመለሰው ትንሽ ቢሆንም አሰተያየት ተቀብለው ተመላሽ ካደረጉት ተቋማት ውስጥ ፦
➡ የኢንፎርሜሽን ደህንነት መረብ አስተዳደር 5.9 ሚሊዮን ተመላሽ እንዲያደርግ ተብሎ 5.8 መልሷል።
➡ አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ 4.1 ሚሊዮን ተመላሽ እንዲያደርግ ተብሎ 3.5 ሚሊዮን መልሷል።
➡ የስፔስ እና ጂኦስፔሻል ስልጠና ኢንስቲትዩት ተመላሽ እንዲያደርግ ከተባለው 5.6 ሚሊዮን ውስጥ 4.4 ሚሊዮን መልሷል።
የሰነድ ማስረጃ አቅርቡ ከተባሉት ውስጥ ፦
☑ አዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ 124.25 ሚሊዮን ውስጥ ሁሉንም መልሷል።
☑ የአደጋ ስራ አመራር ኮሚሽን 150.2 ሚሊዮን ውስጥ ሁሉንም መልሷል።
☑ አዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ከ3.9 ሚሊዮን 2.2 ሚሊዮን መልሷል።
ሰነዶቹም ትክክለኛ መሆናቸው ተረጋግጧል።
#TikvahEthiopia
@tikvahethiopia
❤130😱31😡20😭19🙏7🕊6🥰4🤔3😢3👏1
TIKVAH-ETHIOPIA
#ኢትዮጵያ #ኦዲት የፌዴራል ዋና ኦዲተር የ2015 የፌዴራል መንግሥት መ/ቤቶች የፋይናንስና ሕጋዊነት ኦዲት እና የክዋኔ ኦዲት ሪፖርት ለምክር ቤት እያቀረበ ይገኛል። በዚህም ወቅት ተከታዩን ሰምተናል ፦ በ2014 የበጀት ዓመት እና ከዚያ በፊት በፌዴራል መንግሥት መስሪያ ቤቶች በተከናወነው የኦዲት ሪፖርት መሰረት እርምጃ የተወሰደ እንደሆነ ማጣራት ተደርጎ ነበር። በ92 መስሪያ ቤቶች ተመላሽ እንዲደረግ…
#ኢትዮጵያ #ኦዲት
የ2015 በጀት ዓመት የፌዴራል የመንግስት መስሪያ ቤቶች የኦዲት ክንውን ላይ ማብራሪያ እየተሰጠ ነው።
ሂሳብ አቅራቢ የነበሩት 173 የፌዴራል መንግስት ባለ በጀት መስሪያ ቤቶች ሲሆኑ የ162 መ/ቤቶች እና 58 ቅርንጫፍ ፅ/ቤቶች በፌዴራል ኦዲተር መ/ቤት 11 ደግሞ በሂሳብ ምርመራ አገልግሎት ኮርፖሬሽን ኦዲት ሊደረጉ ታቅዶ ነበር።
10 መስሪያ ቤቶች 4 ቅርንጫፍ ፅ/ቤቶች በጸጥታ ምክንያት ኦዲት ተጀምሮ ተቋርጧል። 1 መ/ቤት ቢሮ አላቀረበም።
ከዚሁ ጋር በተያያዘ በጥሬ ገንዘብ ሂሳብ ላይ ታገቢው ቁጥጥር ይደረግ እንደሆነ ለማረጋገጥ ክትትል ሲደረግ ፥ በሁለት መስሪያ ቤቶች ብቻ ብር 383 ሺህ 238 ከ48 ሳንቲም ጉድለት ተገኝቷል።
#TikvahEthiopia
@tikvahethiopia
የ2015 በጀት ዓመት የፌዴራል የመንግስት መስሪያ ቤቶች የኦዲት ክንውን ላይ ማብራሪያ እየተሰጠ ነው።
ሂሳብ አቅራቢ የነበሩት 173 የፌዴራል መንግስት ባለ በጀት መስሪያ ቤቶች ሲሆኑ የ162 መ/ቤቶች እና 58 ቅርንጫፍ ፅ/ቤቶች በፌዴራል ኦዲተር መ/ቤት 11 ደግሞ በሂሳብ ምርመራ አገልግሎት ኮርፖሬሽን ኦዲት ሊደረጉ ታቅዶ ነበር።
10 መስሪያ ቤቶች 4 ቅርንጫፍ ፅ/ቤቶች በጸጥታ ምክንያት ኦዲት ተጀምሮ ተቋርጧል። 1 መ/ቤት ቢሮ አላቀረበም።
ከዚሁ ጋር በተያያዘ በጥሬ ገንዘብ ሂሳብ ላይ ታገቢው ቁጥጥር ይደረግ እንደሆነ ለማረጋገጥ ክትትል ሲደረግ ፥ በሁለት መስሪያ ቤቶች ብቻ ብር 383 ሺህ 238 ከ48 ሳንቲም ጉድለት ተገኝቷል።
#TikvahEthiopia
@tikvahethiopia
🤔62❤37😡11🕊6😱4😭4🥰2
TIKVAH-ETHIOPIA
#ኢትዮጵያ #ኦዲት የ2015 በጀት ዓመት የፌዴራል የመንግስት መስሪያ ቤቶች የኦዲት ክንውን ላይ ማብራሪያ እየተሰጠ ነው። ሂሳብ አቅራቢ የነበሩት 173 የፌዴራል መንግስት ባለ በጀት መስሪያ ቤቶች ሲሆኑ የ162 መ/ቤቶች እና 58 ቅርንጫፍ ፅ/ቤቶች በፌዴራል ኦዲተር መ/ቤት 11 ደግሞ በሂሳብ ምርመራ አገልግሎት ኮርፖሬሽን ኦዲት ሊደረጉ ታቅዶ ነበር። 10 መስሪያ ቤቶች 4 ቅርንጫፍ ፅ/ቤቶች በጸጥታ…
#ኦዲት #ኢትዮጵያ
ጤና ሚኒስቴር እና ትምህርት ሚኒስቴር ከፍተኛ ውዝፍ ተሰብሳቢ ሂሳብ ከተገኘባቸው ተቋማት መካከል መሆናቸው ተሰምቷል።
ለውሎ አበል እና ለመጓጓዣ እንዲሁም ለግዥ የተሰጠ ክፍያ ሰራተኛው ስራውን አጠናቆ ከተመልሱ በኃላ በ7 ቀናት መወራረድ እንዳለበት መመሪያ አለ።
ነገር ግን በ124 መስሪያ ቤቶች በጠቅላላው ብር 14.1 ቢሊዮን በወቅቱ ያልተወራረደ ወይም ያልተሰበሰበ ተሰብሳቢ ሂሳብ መኖሩ በኦዲት ታውቋል።
ጊዜው ሲታይም ከ1 ወር በላይ እስከ 1 ዓመት 1 ቢሊዮን 193 ሚሊዮን ብር ፤ ከ1 ዓመት በላይ እስከ 5 ዓመት 10.9 ቢሊዮን ብር ፤ ከ5 ዓመት በላይ እስከ 10 ዓመት 1.7 ቢሊዮን ብር ፤ ከ10 ዓመት በላይ 139 ሚሊዮን ነው።
ቀሪው ሂሳብ በቆይታው ጊዜ ያልተተነተነ ነው።
ውዝፍ ተሰብሳቢ ሂሳብ ከተገኘባቸው ተቋማት #ከፍተኛውን ድርሻ የያዙት እነማን ናቸው ?
➡ #ጤና_ሚኒስቴር 6 ቢሊዮን
➡ የመስኖ ቆላማ አካባቢ ሚኒስቴር 1.1 ቢሊዮን
➡ የትምህርት ሚኒስቴር 1 ቢሊዮን 12 ሚሊዮን
➡ በፌዴራል መንግስት የህንጻዎች ግንባታ ፕሮጀክት ጽ/ቤት 970.9 ሚሊዮን
➡ ቅዱስ ጳውሎስ ሆስፒታል ሚኒሊየም የህክምና ኮሌጅ 756.3 ሚሊዮን
➡ የጅግጅጋ ዩኒቨርሲቲ 433.5 ሚሊዮን
➡ የኢትዮጵያ ግብርና ምርምር ኢንስቲትዩት 286.8 ሚሊዮን
➡ የአደጋ ስራ አመራር ኮሚሽን 272.4 ሚሊዮን
➡ የመንግስት ግዥ አገልግሎት 265.2 ሚሊዮን
➡ የፌዴራል ፖሊስ ኮሚሽን 250.7 ሚሊዮን
➡ የውሃ እና ኢነርጂ ሚኒስቴር 218.3 ሚሊዮን ዋና ዋናዎቹ ናቸው።
በተጨማሪ የፕሮጀክት ሂሳብ በታየባቸው 4 መስሪያ ቤቶች 514.5 ሚሊዮን በወቅቱ ያልተወራረዳ ውዝፍ ተሰብሳቢ ሂሳብ ተገኝቷል።
እንደ የፌዴራል መ/ቤቶች የሂሳብ አያያዝ መመሪያ መሰረት የተሰብሳቢ ሂሳብ በቂ ማስረጃ ሲቀርብበት ብቻ ነው በተሰብሳቢ ሂሳብነት የሚመዘገበው። የተሰብሳቢ ሂሳብ ክምችት እንዳይኖር ቁጥጥር መደረግ አለበትም ይላል።
ነገር ግን በ15 መስሪያ ቤቶች በጠቅላላው 363.1 ሚሊዮን ማስረጃ ባለመቅረቡ የሂሳቡን ትክክለኝነት ማረጋገጥ አልተቻለም።
የተሰብሰቢ ሂሳቡን ትክክለኝነት ማረጋገጥ ካልተቻለባቸው መስሪያ ቤቶች መካከል ፦
🔴 የኢኖቬሽን እና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር 253.3 ሚሊዮን
🔴 የመንግስት ግዥ አገልግሎት 39.1 ሚሊዮን
🔴 ጤና ሚኒስቴር 28 ሚሊዮን ከፍተኛውን ድርሻ ይዘዋል።
#TikvahEthiopia
@tikvahethiopia
ጤና ሚኒስቴር እና ትምህርት ሚኒስቴር ከፍተኛ ውዝፍ ተሰብሳቢ ሂሳብ ከተገኘባቸው ተቋማት መካከል መሆናቸው ተሰምቷል።
ለውሎ አበል እና ለመጓጓዣ እንዲሁም ለግዥ የተሰጠ ክፍያ ሰራተኛው ስራውን አጠናቆ ከተመልሱ በኃላ በ7 ቀናት መወራረድ እንዳለበት መመሪያ አለ።
ነገር ግን በ124 መስሪያ ቤቶች በጠቅላላው ብር 14.1 ቢሊዮን በወቅቱ ያልተወራረደ ወይም ያልተሰበሰበ ተሰብሳቢ ሂሳብ መኖሩ በኦዲት ታውቋል።
ጊዜው ሲታይም ከ1 ወር በላይ እስከ 1 ዓመት 1 ቢሊዮን 193 ሚሊዮን ብር ፤ ከ1 ዓመት በላይ እስከ 5 ዓመት 10.9 ቢሊዮን ብር ፤ ከ5 ዓመት በላይ እስከ 10 ዓመት 1.7 ቢሊዮን ብር ፤ ከ10 ዓመት በላይ 139 ሚሊዮን ነው።
ቀሪው ሂሳብ በቆይታው ጊዜ ያልተተነተነ ነው።
ውዝፍ ተሰብሳቢ ሂሳብ ከተገኘባቸው ተቋማት #ከፍተኛውን ድርሻ የያዙት እነማን ናቸው ?
➡ #ጤና_ሚኒስቴር 6 ቢሊዮን
➡ የመስኖ ቆላማ አካባቢ ሚኒስቴር 1.1 ቢሊዮን
➡ የትምህርት ሚኒስቴር 1 ቢሊዮን 12 ሚሊዮን
➡ በፌዴራል መንግስት የህንጻዎች ግንባታ ፕሮጀክት ጽ/ቤት 970.9 ሚሊዮን
➡ ቅዱስ ጳውሎስ ሆስፒታል ሚኒሊየም የህክምና ኮሌጅ 756.3 ሚሊዮን
➡ የጅግጅጋ ዩኒቨርሲቲ 433.5 ሚሊዮን
➡ የኢትዮጵያ ግብርና ምርምር ኢንስቲትዩት 286.8 ሚሊዮን
➡ የአደጋ ስራ አመራር ኮሚሽን 272.4 ሚሊዮን
➡ የመንግስት ግዥ አገልግሎት 265.2 ሚሊዮን
➡ የፌዴራል ፖሊስ ኮሚሽን 250.7 ሚሊዮን
➡ የውሃ እና ኢነርጂ ሚኒስቴር 218.3 ሚሊዮን ዋና ዋናዎቹ ናቸው።
በተጨማሪ የፕሮጀክት ሂሳብ በታየባቸው 4 መስሪያ ቤቶች 514.5 ሚሊዮን በወቅቱ ያልተወራረዳ ውዝፍ ተሰብሳቢ ሂሳብ ተገኝቷል።
እንደ የፌዴራል መ/ቤቶች የሂሳብ አያያዝ መመሪያ መሰረት የተሰብሳቢ ሂሳብ በቂ ማስረጃ ሲቀርብበት ብቻ ነው በተሰብሳቢ ሂሳብነት የሚመዘገበው። የተሰብሳቢ ሂሳብ ክምችት እንዳይኖር ቁጥጥር መደረግ አለበትም ይላል።
ነገር ግን በ15 መስሪያ ቤቶች በጠቅላላው 363.1 ሚሊዮን ማስረጃ ባለመቅረቡ የሂሳቡን ትክክለኝነት ማረጋገጥ አልተቻለም።
የተሰብሰቢ ሂሳቡን ትክክለኝነት ማረጋገጥ ካልተቻለባቸው መስሪያ ቤቶች መካከል ፦
🔴 የኢኖቬሽን እና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር 253.3 ሚሊዮን
🔴 የመንግስት ግዥ አገልግሎት 39.1 ሚሊዮን
🔴 ጤና ሚኒስቴር 28 ሚሊዮን ከፍተኛውን ድርሻ ይዘዋል።
#TikvahEthiopia
@tikvahethiopia
😭158❤87😱32😡16🤔14😢9🕊7👏6🥰1
TIKVAH-ETHIOPIA
#ኦዲት #ኢትዮጵያ ጤና ሚኒስቴር እና ትምህርት ሚኒስቴር ከፍተኛ ውዝፍ ተሰብሳቢ ሂሳብ ከተገኘባቸው ተቋማት መካከል መሆናቸው ተሰምቷል። ለውሎ አበል እና ለመጓጓዣ እንዲሁም ለግዥ የተሰጠ ክፍያ ሰራተኛው ስራውን አጠናቆ ከተመልሱ በኃላ በ7 ቀናት መወራረድ እንዳለበት መመሪያ አለ። ነገር ግን በ124 መስሪያ ቤቶች በጠቅላላው ብር 14.1 ቢሊዮን በወቅቱ ያልተወራረደ ወይም ያልተሰበሰበ ተሰብሳቢ ሂሳብ…
#ኦዲት
የተሰበሰበው ገቢ #ትክክለኛነቱን ለማረጋገጥ ሂሳብ ኦዲት ሲደረግ በኢሚግሬሽን እና ዜግነት አገልግሎት #በዶላር የተሰበሰበ 1.3 ሚሊዮን ገቢ ትክክለኝነቱን ማረጋገጥ #አልተቻለም።
የፌዴራል ዋና ኦዲተር ማንኛውም ገቢ ተገቢ ማስረጃ ሳይሟላ በገቢ መመዝገብ ፍጹም ትክክል እንዳልሆነ አስገንብዝቦ የገቢ ማስረጃዎች በትክክል ተደራጅቶ እንዲያዝ ተገቢው ማስተካከያም እንዲደረግና እርምጃ እንዲወሰድ አሳስቧል።
@tikvahethiopia
የተሰበሰበው ገቢ #ትክክለኛነቱን ለማረጋገጥ ሂሳብ ኦዲት ሲደረግ በኢሚግሬሽን እና ዜግነት አገልግሎት #በዶላር የተሰበሰበ 1.3 ሚሊዮን ገቢ ትክክለኝነቱን ማረጋገጥ #አልተቻለም።
የፌዴራል ዋና ኦዲተር ማንኛውም ገቢ ተገቢ ማስረጃ ሳይሟላ በገቢ መመዝገብ ፍጹም ትክክል እንዳልሆነ አስገንብዝቦ የገቢ ማስረጃዎች በትክክል ተደራጅቶ እንዲያዝ ተገቢው ማስተካከያም እንዲደረግና እርምጃ እንዲወሰድ አሳስቧል።
@tikvahethiopia
😱189❤64👏25🙏23🤔22😭14😢8😡6🥰3
TIKVAH-ETHIOPIA
#ኦዲት የተሰበሰበው ገቢ #ትክክለኛነቱን ለማረጋገጥ ሂሳብ ኦዲት ሲደረግ በኢሚግሬሽን እና ዜግነት አገልግሎት #በዶላር የተሰበሰበ 1.3 ሚሊዮን ገቢ ትክክለኝነቱን ማረጋገጥ #አልተቻለም። የፌዴራል ዋና ኦዲተር ማንኛውም ገቢ ተገቢ ማስረጃ ሳይሟላ በገቢ መመዝገብ ፍጹም ትክክል እንዳልሆነ አስገንብዝቦ የገቢ ማስረጃዎች በትክክል ተደራጅቶ እንዲያዝ ተገቢው ማስተካከያም እንዲደረግና እርምጃ እንዲወሰድ አሳስቧል።…
#ኢትዮጵያ #ኦዲት
በ11 መስሪያ ቤቶች 43.5 ሚሊዮን ብር #ምንም ማስረጃ ሳይኖር ወጪ ተደርጓል።
በ2015 የበጀት ዓመት መ/ቤቶች የተፈቀደላቸውን በጀት በአግባቡ ወጪ ማድረጋቸውን / በአግባቡ መጠቀማቸውን ፣ ተገቢ ማስረጃ መቅረቡንና ሂሳቡ በትክክል መመዝገቡን ለማጣራት ኦዲት ተደርጓል።
በዚህም ፥ ምንም አይነት ማስረጃ ሳይቀርብ በወጪ የተመዘገበ ክፍያ / ሂሳብ ተገኝቷል።
በ11 መ/ቤቶች 43.5 ሚሊዮን ማስረጃ ሳይኖረው በወጪ ሂሳብ የተመዘገበ ሲሆን ማስረጃም ባለመቅረቡ ትክክለኛነቱን ማረጋገጥ አልተቻለም።
➡ የፌዴራል ፖሊስ ኮሚሽን 17.4 ሚሊዮን
➡ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅት ባለስልጣን 8.7 ሚሊዮን
➡ የመንገድ ደህንነትና መድህን ፈንድ አገልግሎት 8.7 ሚሊዮን
➡ ሚዛን ቴፒ ዩኒቨርሲቲ 4.4 ሚሊዮን
➡ የኢትዮጵያ አካል ድጋፍ አገልግሎት 3.3 ሚሊዮን ዋና ዋናዎቹ ናቸው።
ከዚህ ባለፈ ፤ በወጪ ለተመዘገቡ ክፍያዎች የተሟላ ማስረጃ መቅረቡን ለማረጋገጥ በተደረገው ኦዲት በ 48 መ/ቤቶች የተሟላ ማስረጃ ሳይቀርብ 44 ሚሊዮን 440 ሺህ በወጪ ተመዝግቦ ተገኝቷል።
የተሟላ ማስረጃ ሳይዙ ወጪ ከመዘገቡት መካከል ፦
🔴 ማዕድን ሚኒስቴር 5 ሚሊዮን 719 ሺህ
🔴 ጅግጅጋ ዩኒቨርሲቲ 5 ሚሊዮን 716 ሺህ
🔴 የጤና ሚኒስቴር 4 ሚሊዮን 677 ሺህ
🔴 ገንዘብ ሚኒስቴር 3 ሚሊዮን 34 ሺህ
🔴 በስራ እና ክህሎት ሚኒስቴር ገዋኔ የግብርና የቴክኒክ ሙያ ትምህርትና ስልጠና ኮሌጅ 2 ሚሊዮን 450 ሺህ
🔴 የኢትዮጵያ ጂኦሎጂካል ኢንስቲትዩት 2 ሚሊዮን 185 ሺህ ዋና ዋናዎቹ ናቸው።
የፌዴራል ኦዲተር መስሪያ ቤት ፤ ማስረጃ ካልቀረበ የሂሳቡን #ትክክለኝነት_ማረጋገጥ_እንደማይቻል ፤ የወጪ ማስረጃ ላልቀረበላቸው ክፍያዎች የወጪ ማስረጃ እንዲቀርብላቸው የማይቀርብላቸው ከሆነ #ገንዘቡ_ተመላሽ እንዲደረግ አሳስቧል።
#TikvahEthiopia
@tikvahethiopia
በ11 መስሪያ ቤቶች 43.5 ሚሊዮን ብር #ምንም ማስረጃ ሳይኖር ወጪ ተደርጓል።
በ2015 የበጀት ዓመት መ/ቤቶች የተፈቀደላቸውን በጀት በአግባቡ ወጪ ማድረጋቸውን / በአግባቡ መጠቀማቸውን ፣ ተገቢ ማስረጃ መቅረቡንና ሂሳቡ በትክክል መመዝገቡን ለማጣራት ኦዲት ተደርጓል።
በዚህም ፥ ምንም አይነት ማስረጃ ሳይቀርብ በወጪ የተመዘገበ ክፍያ / ሂሳብ ተገኝቷል።
በ11 መ/ቤቶች 43.5 ሚሊዮን ማስረጃ ሳይኖረው በወጪ ሂሳብ የተመዘገበ ሲሆን ማስረጃም ባለመቅረቡ ትክክለኛነቱን ማረጋገጥ አልተቻለም።
➡ የፌዴራል ፖሊስ ኮሚሽን 17.4 ሚሊዮን
➡ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅት ባለስልጣን 8.7 ሚሊዮን
➡ የመንገድ ደህንነትና መድህን ፈንድ አገልግሎት 8.7 ሚሊዮን
➡ ሚዛን ቴፒ ዩኒቨርሲቲ 4.4 ሚሊዮን
➡ የኢትዮጵያ አካል ድጋፍ አገልግሎት 3.3 ሚሊዮን ዋና ዋናዎቹ ናቸው።
ከዚህ ባለፈ ፤ በወጪ ለተመዘገቡ ክፍያዎች የተሟላ ማስረጃ መቅረቡን ለማረጋገጥ በተደረገው ኦዲት በ 48 መ/ቤቶች የተሟላ ማስረጃ ሳይቀርብ 44 ሚሊዮን 440 ሺህ በወጪ ተመዝግቦ ተገኝቷል።
የተሟላ ማስረጃ ሳይዙ ወጪ ከመዘገቡት መካከል ፦
🔴 ማዕድን ሚኒስቴር 5 ሚሊዮን 719 ሺህ
🔴 ጅግጅጋ ዩኒቨርሲቲ 5 ሚሊዮን 716 ሺህ
🔴 የጤና ሚኒስቴር 4 ሚሊዮን 677 ሺህ
🔴 ገንዘብ ሚኒስቴር 3 ሚሊዮን 34 ሺህ
🔴 በስራ እና ክህሎት ሚኒስቴር ገዋኔ የግብርና የቴክኒክ ሙያ ትምህርትና ስልጠና ኮሌጅ 2 ሚሊዮን 450 ሺህ
🔴 የኢትዮጵያ ጂኦሎጂካል ኢንስቲትዩት 2 ሚሊዮን 185 ሺህ ዋና ዋናዎቹ ናቸው።
የፌዴራል ኦዲተር መስሪያ ቤት ፤ ማስረጃ ካልቀረበ የሂሳቡን #ትክክለኝነት_ማረጋገጥ_እንደማይቻል ፤ የወጪ ማስረጃ ላልቀረበላቸው ክፍያዎች የወጪ ማስረጃ እንዲቀርብላቸው የማይቀርብላቸው ከሆነ #ገንዘቡ_ተመላሽ እንዲደረግ አሳስቧል።
#TikvahEthiopia
@tikvahethiopia
🤔286❤100😭95👏49😱38🙏28😢21😡20🥰18🕊12
TIKVAH-ETHIOPIA
#ኢትዮጵያ #ኦዲት በ11 መስሪያ ቤቶች 43.5 ሚሊዮን ብር #ምንም ማስረጃ ሳይኖር ወጪ ተደርጓል። በ2015 የበጀት ዓመት መ/ቤቶች የተፈቀደላቸውን በጀት በአግባቡ ወጪ ማድረጋቸውን / በአግባቡ መጠቀማቸውን ፣ ተገቢ ማስረጃ መቅረቡንና ሂሳቡ በትክክል መመዝገቡን ለማጣራት ኦዲት ተደርጓል። በዚህም ፥ ምንም አይነት ማስረጃ ሳይቀርብ በወጪ የተመዘገበ ክፍያ / ሂሳብ ተገኝቷል። በ11 መ/ቤቶች 43.5…
#ኦዲት #ኢትዮጵያ
(ከ2015 የበጀት ዓመት የፋይናንስ ሕጋዊነት ኦዲት እና የክዋኔ ኦዲት ሪፖርት)
➡️ የበጀት አጠቃቀም ፦
ኦዲት በተደረጉ መስሪያ ቤቶች የተፈቀደላቸውን በጀት በስራ ላይ ያዋሉት ሂሳብ ሲነጻጸር ከበጀት በላይ ወጪ የተደረገበት ፣ በርካታ ያልተሰራበት በጀት ተገኝቷል።
በ20 መ/ቤቶች በልዩ ልዩ የሂሳብ መደቦች በደንቡ መሰረት #ሳያስፈቅዱ ለእያንዳንዱ የበጀት ኮድ ከተደለደለው በላይ ወጪ የሆነ ሂሳብ ከመደበኛው በጀት ብር 524. 7 ሚሊዮን ፣ ከውስጥ ገቢ 288.9 ሚሊዮን ፣ ከካፒታል በጀት 489.4 ሚሊዮን በድምሩ 1.3 ቢሊዮን ብር ተገኝቷል።
በኮድ ከተደለደለው በጀት በላይ ውጭ ያደረጉ ዋና ዋና መ/ቤቶች ፦
🟠 ሚዛን ቴፒ ዩኒቨርሲቲ 322.5 ሚሊዮን
🟠 አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ እና ተጠሪ ተቋማቱ 267.9 ሚሊዮን
🟠 ጅግጅጋ ዩኒቨርሲቲ 173.2 ሚሊዮን
🟠 ወለጋ ዩኒቨርሲቲ 125.1 ሚሊዮን
🟠 የኢትዮጵያ ግብርና ምርምር ኢንስቲትዩት 109.5 ሚሊዮን
🟠 ዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ 91.3 ሚሊዮን
🟠 አምቦ ዩኒቨርሲቲ 83.3 ሚሊዮን
🟠 አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ 75.1 ሚሊዮን
ሁለት መስሪያ ቤቶች ደግሞ 9.7 ሚሊዮን ብር በጀት ስለመኖሩ ሳይረጋገጥ / ሳይፈቀድ ክፍያ ተፈጽሞ ተገኘቷል።
➡️ ከደንብ እና መመሪያ ውጭ የተከፈለ ፦
በ30 መ/ቤቶች ብር 16 ሚሊዮን 470 ሺህ ከደንብና መመሪያ ውጭ አላግባብ ተከፍሏል።
ዋና ዋናዎቹ መ/ቤቶች ፦
🔴 ኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር 3 ሚሊዮን
🔴 የመንግስት ኮሚኒኬሽን አገልግሎት 2 ሚሊዮን 889 ሺህ
🔴 ኮተቤ ትምህርት ዩኒቨርሲቲ 2 ሚሊዮን 42 ሺህ
🔴 መደወላቡ ዩኒቨርሲቲ 1 ሚሊዮን 156 ሺህ
➡️ በመስሪያ ቤት ለሌሉና ከስራ ገበታ ለተሰናበቱ ሰራተኞች የተከፈለ ደመወዝ ፦
በ16 መስሪያ ቤቶች በመስሪያ ቤት ለሌሉ እና ከስራ ለተሰናበቱ ሰራተኞች ብር 485 ሺህ 183 ከ56 ሳንቲም ደመወዝ ተከፍሎ ተገኝቷል።
➡️ በበልጫ አላግባብ የተከፈለ ወጪ ፦
በ32 መ/ቤቶች እና በ9 ቅርንጫፍ ፅ/ቤቶች በተለያዩ የግንባታና ግዥዎች 4.9 ሚሊዮንና ለውሎ አበልና ሌሎች ክፍያዎች 57.6 ሚሊዮን በድምር 62.6 በብልጫ ተከፍሎ ተገኝቷል።
➡️ የግዥ አዋጅ ደንብና መመሪያ ያልተከተሉ ግዥዎች ፦
በ73 መ/ቤቶች እና በ15 ቅ/ጽቤቶች ብር 2 ቢሊዮን 199 ሚሊዮን የመንግስት ግዥ አዋጅ ደንብ እና መመሪያን ሳይከተል ግዥ ተፈጽሟል።
° በጨረታ መግዛት ሲገባው ያለጨረታ በቀጥታ የተፈጸመ ግዥ 1.8 ቢሊዮን ብር
° መስፈርት ሳይሟላ በውስን ጨረታ የተገዛ 104.3 ሚሊዮን ብር
° ግልጽ ጨረታ መውጣት ሲገባው በዋጋ ማወዳደሪያ የተፈጸመ 96.1 ሚሊዮን ብር
° የዋጋ ማወዳደሪያ ሳይሰበሰብ በቀጥታ የተፈጸመ ግዥ 13.8 ሚሊዮን ብር
° ሌሎች የግዥ ሂደት ያልተከተሉ 134.6 ሚሊዮን ዋና ዋና ናቸው።
ዋና ዋና መስሪያ ቤቶች (ደንብና መመሪያ ሳይከተሉ ግዥ የፈጸሙ)፦
⚫ ገቢዎች ሚኒስቴር በዋናው መ/ቤትና በቅርንጫፍ ፅ/ቤት 1.4 ቢሊዮን
⚫ የኢሚግሬሽን እና ዜግነት አገልግሎት 91 ሚሊዮን
⚫ የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር 65.5 ሚሊዮን
⚫ የፌዴራል ፖሊስ ኮሚሽን 62.9 ሚሊዮን
⚫ የኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ 57.1 ሚሊዮን
⚫ ቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ 37.4 ሚሊዮን
⚫ የጉምሩክ ኮሚሽን ዋና መ/ቤት እና በድሬዳዋ ቅርንጫፍ ፅ/ቤት 34 ሚሊዮን
➡️ በአማካሪ መሃንዲሳ ሳይረጋገጥ የተከፈለ ክፍያ ፦
የግንባታ ክፍያ #በአማካሪ_መሃንዲስ ተረጋግጠው መከፈላቸውን ለማረጋገጥ በተደረገ ኦዲት በ2 መ/ቤቶች 170 ሚሊዮን 394 ሺህ በአማካሪ መሃንዲስ የክፍያ ማረጋገጫ የምስክር ወረቀት ሳይቀርብ ክፍያ ተፈጽሞ ተገኝቷል።
👉 ኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር 169.7 ሚሊዮን ብር ከፍሎ ተገኝቷል።
➡️ የተከፋይ ሂሳብ ፦
በ14 መ/ቤቶች 1.7 ቢሊዮን ብር በተከፋይ ሂሳብ ተይዞ ተገኝቷል። ለማን እንደሚከፈል እንኳን ተለይቶ አይታወቅም።
የተከፋይ ሂሳብ ለባለመብት መለየት ካልቻሉ መስሪያ ቤቶች ፦
🔵 የመስኖና ቆላማ አካባቢ ሚኒስቴር 1.5 ቢሊዮን
🔵 የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር 131.8 ሚሊዮን
🔵 ማዕድን ሚኒስቴር 29.9 ሚሊዮን ዋና ዋናዎቹ ናቸው።
#TikvahEthiopia
@tikvahethiopia
(ከ2015 የበጀት ዓመት የፋይናንስ ሕጋዊነት ኦዲት እና የክዋኔ ኦዲት ሪፖርት)
ኦዲት በተደረጉ መስሪያ ቤቶች የተፈቀደላቸውን በጀት በስራ ላይ ያዋሉት ሂሳብ ሲነጻጸር ከበጀት በላይ ወጪ የተደረገበት ፣ በርካታ ያልተሰራበት በጀት ተገኝቷል።
በ20 መ/ቤቶች በልዩ ልዩ የሂሳብ መደቦች በደንቡ መሰረት #ሳያስፈቅዱ ለእያንዳንዱ የበጀት ኮድ ከተደለደለው በላይ ወጪ የሆነ ሂሳብ ከመደበኛው በጀት ብር 524. 7 ሚሊዮን ፣ ከውስጥ ገቢ 288.9 ሚሊዮን ፣ ከካፒታል በጀት 489.4 ሚሊዮን በድምሩ 1.3 ቢሊዮን ብር ተገኝቷል።
በኮድ ከተደለደለው በጀት በላይ ውጭ ያደረጉ ዋና ዋና መ/ቤቶች ፦
🟠 ሚዛን ቴፒ ዩኒቨርሲቲ 322.5 ሚሊዮን
🟠 አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ እና ተጠሪ ተቋማቱ 267.9 ሚሊዮን
🟠 ጅግጅጋ ዩኒቨርሲቲ 173.2 ሚሊዮን
🟠 ወለጋ ዩኒቨርሲቲ 125.1 ሚሊዮን
🟠 የኢትዮጵያ ግብርና ምርምር ኢንስቲትዩት 109.5 ሚሊዮን
🟠 ዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ 91.3 ሚሊዮን
🟠 አምቦ ዩኒቨርሲቲ 83.3 ሚሊዮን
🟠 አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ 75.1 ሚሊዮን
ሁለት መስሪያ ቤቶች ደግሞ 9.7 ሚሊዮን ብር በጀት ስለመኖሩ ሳይረጋገጥ / ሳይፈቀድ ክፍያ ተፈጽሞ ተገኘቷል።
በ30 መ/ቤቶች ብር 16 ሚሊዮን 470 ሺህ ከደንብና መመሪያ ውጭ አላግባብ ተከፍሏል።
ዋና ዋናዎቹ መ/ቤቶች ፦
🔴 ኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር 3 ሚሊዮን
🔴 የመንግስት ኮሚኒኬሽን አገልግሎት 2 ሚሊዮን 889 ሺህ
🔴 ኮተቤ ትምህርት ዩኒቨርሲቲ 2 ሚሊዮን 42 ሺህ
🔴 መደወላቡ ዩኒቨርሲቲ 1 ሚሊዮን 156 ሺህ
በ16 መስሪያ ቤቶች በመስሪያ ቤት ለሌሉ እና ከስራ ለተሰናበቱ ሰራተኞች ብር 485 ሺህ 183 ከ56 ሳንቲም ደመወዝ ተከፍሎ ተገኝቷል።
በ32 መ/ቤቶች እና በ9 ቅርንጫፍ ፅ/ቤቶች በተለያዩ የግንባታና ግዥዎች 4.9 ሚሊዮንና ለውሎ አበልና ሌሎች ክፍያዎች 57.6 ሚሊዮን በድምር 62.6 በብልጫ ተከፍሎ ተገኝቷል።
በ73 መ/ቤቶች እና በ15 ቅ/ጽቤቶች ብር 2 ቢሊዮን 199 ሚሊዮን የመንግስት ግዥ አዋጅ ደንብ እና መመሪያን ሳይከተል ግዥ ተፈጽሟል።
° በጨረታ መግዛት ሲገባው ያለጨረታ በቀጥታ የተፈጸመ ግዥ 1.8 ቢሊዮን ብር
° መስፈርት ሳይሟላ በውስን ጨረታ የተገዛ 104.3 ሚሊዮን ብር
° ግልጽ ጨረታ መውጣት ሲገባው በዋጋ ማወዳደሪያ የተፈጸመ 96.1 ሚሊዮን ብር
° የዋጋ ማወዳደሪያ ሳይሰበሰብ በቀጥታ የተፈጸመ ግዥ 13.8 ሚሊዮን ብር
° ሌሎች የግዥ ሂደት ያልተከተሉ 134.6 ሚሊዮን ዋና ዋና ናቸው።
ዋና ዋና መስሪያ ቤቶች (ደንብና መመሪያ ሳይከተሉ ግዥ የፈጸሙ)፦
⚫ ገቢዎች ሚኒስቴር በዋናው መ/ቤትና በቅርንጫፍ ፅ/ቤት 1.4 ቢሊዮን
⚫ የኢሚግሬሽን እና ዜግነት አገልግሎት 91 ሚሊዮን
⚫ የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር 65.5 ሚሊዮን
⚫ የፌዴራል ፖሊስ ኮሚሽን 62.9 ሚሊዮን
⚫ የኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ 57.1 ሚሊዮን
⚫ ቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ 37.4 ሚሊዮን
⚫ የጉምሩክ ኮሚሽን ዋና መ/ቤት እና በድሬዳዋ ቅርንጫፍ ፅ/ቤት 34 ሚሊዮን
የግንባታ ክፍያ #በአማካሪ_መሃንዲስ ተረጋግጠው መከፈላቸውን ለማረጋገጥ በተደረገ ኦዲት በ2 መ/ቤቶች 170 ሚሊዮን 394 ሺህ በአማካሪ መሃንዲስ የክፍያ ማረጋገጫ የምስክር ወረቀት ሳይቀርብ ክፍያ ተፈጽሞ ተገኝቷል።
👉 ኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር 169.7 ሚሊዮን ብር ከፍሎ ተገኝቷል።
በ14 መ/ቤቶች 1.7 ቢሊዮን ብር በተከፋይ ሂሳብ ተይዞ ተገኝቷል። ለማን እንደሚከፈል እንኳን ተለይቶ አይታወቅም።
የተከፋይ ሂሳብ ለባለመብት መለየት ካልቻሉ መስሪያ ቤቶች ፦
🔵 የመስኖና ቆላማ አካባቢ ሚኒስቴር 1.5 ቢሊዮን
🔵 የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር 131.8 ሚሊዮን
🔵 ማዕድን ሚኒስቴር 29.9 ሚሊዮን ዋና ዋናዎቹ ናቸው።
#TikvahEthiopia
@tikvahethiopia
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
😭337❤142😱59🤔39😢28👏26😡25🕊17🥰16🙏5
TIKVAH-ETHIOPIA
#ኦዲት #ኢትዮጵያ (ከ2015 የበጀት ዓመት የፋይናንስ ሕጋዊነት ኦዲት እና የክዋኔ ኦዲት ሪፖርት) ➡️ የበጀት አጠቃቀም ፦ ኦዲት በተደረጉ መስሪያ ቤቶች የተፈቀደላቸውን በጀት በስራ ላይ ያዋሉት ሂሳብ ሲነጻጸር ከበጀት በላይ ወጪ የተደረገበት ፣ በርካታ ያልተሰራበት በጀት ተገኝቷል። በ20 መ/ቤቶች በልዩ ልዩ የሂሳብ መደቦች በደንቡ መሰረት #ሳያስፈቅዱ ለእያንዳንዱ የበጀት ኮድ ከተደለደለው በላይ…
#ኦዲት
ያልተሰራበት በጀት !
ገንዘብ ሚኒስቴር እና ጤና ሚኒስቴር የተመደበላቸውን በቢሊዮን የሚቆጠር በጀት ስራ ላይ ካላዋሉ ተቋማት ዋነኞቹ መሆናቸው ተሰምቷል።
በ2015 በጀት መስሪያ ቤቶች የተፈቀደላቸውን በጀት በአግባቡ ስራ ላይ ማዋላቸውንና መጠቀማቸውን ለማጣራት ኦዲት ሲደረግ በሂሳብ ኮዶች ከተደለደለው በጀት ከ10% በላይ #ያልተጠቀሙበትን ብቻ ተወስዶ 101 መስሪያ ቤቶች ፦
° መደበኛ በጀት 5.3 ቢሊዮን
° ከውስጥ ገቢ 207.6 ሚሊዮን
° ከካፒታል ብር 13.7 ቢሊዮን
በድምሩ 19.2 ቢሊዮን ብር #ያልተሰራበት_በጀት ተገኝቷል።
የተደለደለው በጀት ስራ ላይ እንዲውል #ካላደረጉት መስሪያ ቤቶች መካከል ፦
🔴 የገንዘብ ሚኒስቴር 8 ቢሊዮን ብር
🔴 ጤና ሚኒስቴር 1.9 ቢሊዮን ብር
🔴 የግብርና ሚኒስቴር 1.2 ቢሊዮን ብር
🔴 የፌዴራል ፖሊስ ኮሚሽን 818.4 ሚሊዮን
🔴 ወለጋ ዩኒቨርሲቲ 727 ሚሊዮን ብር
🔴 ትምህርት ሚኒስቴር 724.2 ሚሊዮን ብር
🔴 የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር 613.6 ሚሊዮን ብር ... ዋና ዋናዎቹ ናቸው።
#በጀት_ተፈቅዶ እያለ አለመጠቀም የታሰቡ ስራዎች እንዳይሰሩ ፤ መስሪያ ቤቱ አላማውን እንዳያሳካ ሊያደርግ ስለሚችል በበጀት ዝግጅት እና አጠቃቀም ላይ ጥንቃቄ እንዲደረግ ሲል የፌዴራል ዋና ኦዲተር መ/ቤት አሳስቧል።
#TikvahEthiopia
@tikvahethiopia
ያልተሰራበት በጀት !
ገንዘብ ሚኒስቴር እና ጤና ሚኒስቴር የተመደበላቸውን በቢሊዮን የሚቆጠር በጀት ስራ ላይ ካላዋሉ ተቋማት ዋነኞቹ መሆናቸው ተሰምቷል።
በ2015 በጀት መስሪያ ቤቶች የተፈቀደላቸውን በጀት በአግባቡ ስራ ላይ ማዋላቸውንና መጠቀማቸውን ለማጣራት ኦዲት ሲደረግ በሂሳብ ኮዶች ከተደለደለው በጀት ከ10% በላይ #ያልተጠቀሙበትን ብቻ ተወስዶ 101 መስሪያ ቤቶች ፦
° መደበኛ በጀት 5.3 ቢሊዮን
° ከውስጥ ገቢ 207.6 ሚሊዮን
° ከካፒታል ብር 13.7 ቢሊዮን
በድምሩ 19.2 ቢሊዮን ብር #ያልተሰራበት_በጀት ተገኝቷል።
የተደለደለው በጀት ስራ ላይ እንዲውል #ካላደረጉት መስሪያ ቤቶች መካከል ፦
🔴 የገንዘብ ሚኒስቴር 8 ቢሊዮን ብር
🔴 ጤና ሚኒስቴር 1.9 ቢሊዮን ብር
🔴 የግብርና ሚኒስቴር 1.2 ቢሊዮን ብር
🔴 የፌዴራል ፖሊስ ኮሚሽን 818.4 ሚሊዮን
🔴 ወለጋ ዩኒቨርሲቲ 727 ሚሊዮን ብር
🔴 ትምህርት ሚኒስቴር 724.2 ሚሊዮን ብር
🔴 የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር 613.6 ሚሊዮን ብር ... ዋና ዋናዎቹ ናቸው።
#በጀት_ተፈቅዶ እያለ አለመጠቀም የታሰቡ ስራዎች እንዳይሰሩ ፤ መስሪያ ቤቱ አላማውን እንዳያሳካ ሊያደርግ ስለሚችል በበጀት ዝግጅት እና አጠቃቀም ላይ ጥንቃቄ እንዲደረግ ሲል የፌዴራል ዋና ኦዲተር መ/ቤት አሳስቧል።
#TikvahEthiopia
@tikvahethiopia
😭618❤171😡155🤔81👏78🙏40😱30🥰21😢20🕊16
የገንዘብ_ሚኒስቴር_መመሪያ_ቁጥር_1063_2017.pdf
5.8 MB
#ታክስ #ኦዲት
የገንዘብ ሚኒስቴር፥ የታክስ ኦዲት የሚከናወንበትን ሥርዓት እና የታክስ ስሌት ማስታወቂያ የሚወጣበትን አኳኋን ለመወሰን መመሪያ አውጥቷል።
መመሪያው ከትላንትና በስቲያ ጀምሮ ስራ ላይ ውሏል።
መመሪያው ስለ አጠቃላይ ኦዲት ምን ይላል ?
የታክስ ባለስልጣን አጠቃላይ ኦዲት የሚያከናውነው ፦
- በስጋት ግምገማ ወቅት ታክስ ከፋዩ በህግ በተደነገገው መሰረት የሂሳብ መዝገብ የመያዝ ገቢውን የማስታወቅ እና ታክስ የመክፈል ግዴታውን ያልተወጣ መሆኑ ሲታወቅ እና ይህም ሁኔታ የተለያዩ ታክሶችን የሚመለከት ሲሆን፤
- ሌላ አይነት ኦዲት በመደረግ ላይ ባለበት ጊዜ የተገኙ ታክስ ከፋዩ የፈጸማቸው ተገቢ ያልሆኑ አድራጎቶች ኦዲቱ በማይሸፍናቸው በሌሎች ታክሶች ላይ ጭምር ውጤት ያላቸው መሆኑ ሲታወቅ፤
- ታክስ ከፋዩ ኦዲት እንዲደርግ ሲጠየቅ እና በታክስ ባለስልጣኑ አጠቃላይ ኦዲት አስፈላጊ መሆኑ ሲታመንበት፤
- አግባብነት ባላቸው በሌሎች የታክስ ህጎች በተገለጹ ሌሎች ምክንያቶች፤
- ታክስ ከፋዩ በጭብጥ ኦዲት ተደርጎ አከራካሪ ከሆነ እና በቅሬታ ጽ/ቤት በኩል አጠቃላይ ኦዲት እንዲደረግ ትዕዛዝ ሲሰጥ፤ ... ነው ይላል።
የታክስ ባለስልጣን አጠቃላይ አዲት በሚያከናውንበት ጊዜ ፦
° ተገቢ ያልሆነ የሂሳብ ስሌት፣ ግድፈት፤
° ገቢን ማሳነስ፤
° ተገቢ ያልሆነ የታክስ አሰያየም
° በታክስ ማስታወቂያ ወይም ስሌት ረገድ የተፈጸመ ሌላ ማናቸውም ጥፋት ያለመኖሩን ለማረጋገጥ፤ ሁሉንም ወይም የተወሰኑትን የታክስ አይነቶች በሚመለከት ዝርዝር እና ጥልቀት ያለው ምርመራ ማድረግ እንዳለበት መመሪያው ላይ ሰፍሯል።
ይህ የማጣራት ተግባር አግባብነት እስካለው ድረስ የህግ ድንጋጌዎችን ተከትሎ መፈጸም እንዳለበትም ይገልጻል።
(ሙሉ መመሪያው ከላይ ተያይዟል)
@tikvahethiopia
የገንዘብ ሚኒስቴር፥ የታክስ ኦዲት የሚከናወንበትን ሥርዓት እና የታክስ ስሌት ማስታወቂያ የሚወጣበትን አኳኋን ለመወሰን መመሪያ አውጥቷል።
መመሪያው ከትላንትና በስቲያ ጀምሮ ስራ ላይ ውሏል።
መመሪያው ስለ አጠቃላይ ኦዲት ምን ይላል ?
የታክስ ባለስልጣን አጠቃላይ ኦዲት የሚያከናውነው ፦
- በስጋት ግምገማ ወቅት ታክስ ከፋዩ በህግ በተደነገገው መሰረት የሂሳብ መዝገብ የመያዝ ገቢውን የማስታወቅ እና ታክስ የመክፈል ግዴታውን ያልተወጣ መሆኑ ሲታወቅ እና ይህም ሁኔታ የተለያዩ ታክሶችን የሚመለከት ሲሆን፤
- ሌላ አይነት ኦዲት በመደረግ ላይ ባለበት ጊዜ የተገኙ ታክስ ከፋዩ የፈጸማቸው ተገቢ ያልሆኑ አድራጎቶች ኦዲቱ በማይሸፍናቸው በሌሎች ታክሶች ላይ ጭምር ውጤት ያላቸው መሆኑ ሲታወቅ፤
- ታክስ ከፋዩ ኦዲት እንዲደርግ ሲጠየቅ እና በታክስ ባለስልጣኑ አጠቃላይ ኦዲት አስፈላጊ መሆኑ ሲታመንበት፤
- አግባብነት ባላቸው በሌሎች የታክስ ህጎች በተገለጹ ሌሎች ምክንያቶች፤
- ታክስ ከፋዩ በጭብጥ ኦዲት ተደርጎ አከራካሪ ከሆነ እና በቅሬታ ጽ/ቤት በኩል አጠቃላይ ኦዲት እንዲደረግ ትዕዛዝ ሲሰጥ፤ ... ነው ይላል።
የታክስ ባለስልጣን አጠቃላይ አዲት በሚያከናውንበት ጊዜ ፦
° ተገቢ ያልሆነ የሂሳብ ስሌት፣ ግድፈት፤
° ገቢን ማሳነስ፤
° ተገቢ ያልሆነ የታክስ አሰያየም
° በታክስ ማስታወቂያ ወይም ስሌት ረገድ የተፈጸመ ሌላ ማናቸውም ጥፋት ያለመኖሩን ለማረጋገጥ፤ ሁሉንም ወይም የተወሰኑትን የታክስ አይነቶች በሚመለከት ዝርዝር እና ጥልቀት ያለው ምርመራ ማድረግ እንዳለበት መመሪያው ላይ ሰፍሯል።
ይህ የማጣራት ተግባር አግባብነት እስካለው ድረስ የህግ ድንጋጌዎችን ተከትሎ መፈጸም እንዳለበትም ይገልጻል።
(ሙሉ መመሪያው ከላይ ተያይዟል)
@tikvahethiopia
❤362👏10😢4🙏4😭4😡4😱3🕊3
#ኦዲት
የመንግሥት ዩኒቨርሲቲዎች ለቋሚ የሥራ ቅጥር መደቦች የቀን ሠራተኞችን በመቅጠር ከ60 ሚሊዮን ብር በላይ ክፍያ መፈጸማቸው ተገለጸ፡፡
የፌዴራል ዋና ኦዲተር መሥሪያ ቤት የመንግሥት ተቋማት የ2016 በጀት ዓመት የበጀት ኦዲት አፈጻጸም ሪፖርት ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ሲያቀርብ ነው የተገለጸው፡፡
ዋና ኦዲተር መሥሪያ ቤት በሪፖርቱ እንደጠቀሰው 12 ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ሳይፈቀድላቸው ለቋሚ የሥራ መደቦች ላይ የቀን ሠራተኞችን ቀጥረው ተገኝተዋል ብሏል።
ተቋማቱ በጠቅላላው 61,882,081 ብር ለቀን ሠራተኞች ክፍያ እንደፈጸሙ የገለጸው የፌዴራል ዋና ኦዲተር ፦
➡️ ጅማ ዩኒቨርሲቲ 25,310,211 ብር፣
➡️ አምቦ ዩኒቨርሲቲ 10,938,834 ብር፣
➡️ ወለጋ ዩኒቨርሲቲ 7,888,374 ብር፣
➡️ ሐሮማያ ዩኒቨርሲቲ 5,170,600 ብርና ዲላ ዩኒቨርሲቲ 4,414,974 ብር በመክፈል ዋነኞቹ እንደሆኑ በሪፖርቱ ተጠቅሰዋል፡፡
እንዲሁም 17 የመንግሥት ተቋማት በጡረታ፣ በሞትና በሌሎች ምክንያት ከሥራ ለለቀቁ ሠራተኞች 408,462 ብር ያላግባብ ደመወዝ መክፈለቸው በሪፖርቱ ተገልጿል፡፡
የሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን ከግንቦት 30 ቀን 2014 ዓ.ም. ጀምሮ በልዩ ሁኔታ ካልተፈቀደ በስተቀር የሠራተኞች ቅጥር፣ የደረጃ ዕድገትና ዝውውር እንዳይፈጸም ቢከለክልም በስምንት መሥሪያ ቤቶችና በአንድ ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት በጠቅላላው 24,073,003 ብር የሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽንን ሳያስፈቅዱ ለቋሚ የሥራ መደቦች ሠራተኞችን በኮንትራት በመቅጠር ክፍያ ፈጽመዋል ተብሏል፡፡
ሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽንን ሳያስፈቅዱ የኮንትራት ቅጥር ከፈጸሙት ተቋማት መካከል ፦
- የቅደስ ጳውሎስ ሆስፒታል ሚሊኒየም ሕክምና ኮሌጅ፣
- ሐሮማያ ዩኒቨርሲቲ፣
- አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲና የአለርት ኮምፕሪሄንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ዋነኞቹ እንደሆኑ ተገልጿል፡፡
ይህ በዚህ እንዳለ በ2015 በጀት ዓመትና ከዚያ በፊት በተከናወኑ የኦዲት ሪፖርቶች መሠረት ዕርምጃ የተወሰደ መሆኑን ለማጣራት ኦዲት ሲደረግ በአጠቃላይ እንዲመለስ አስተያየት ከተሰጠበት 20.5 ቢሊዮን ብርና 23,230 ዶላር ውስጥ፣ የተመለሰው ሦስት ቢሊዮን ብርገደማ ብቻ መሆኑን የፌዴራል ዋና ኦዲተር አስታውቋል።
የፌዴራል ማረሚያ ቤት ኮሚሽን፣ የኢትዮጵያ አካል ጉዳተኞች አገልግሎትና የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቴአትር በአጠቃላይ 37,304,100 ብር የአገልግሎት ገቢ ተመናቸውና በሚመለከተው አካል ሳያፀድቁ ገቢ መሰብሰባቸውም ተገልጿል፡፡
እንዲሁም 28 የፌዴራል መሥሪያ ቤቶችና ሰባት ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤቶች የፈጸሙት 348 ሚሊዮን ብር ክፍያ የተሟላ የወጪ ማስረጃ አልቀረበበትም ተብሏል።
የተሟላ የወጪ ማስረጃ ሳይቀርብ በወጪ ከተመዘገቡት መሥሪያ ቤቶች መካከል የጤና ሚኒስቴር፣ አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ፣ የኢትዮጵያ ኅብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩትና የቤተ መንግሥት አስተዳደር ዋነኞቹ ናቸው።
በ70 የፌዴራል መሥሪያ ቤቶችና በሰባት ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤቶች ከ404 ሚሊዮን ብር በላይ የመንግሥትን የግዥ አዋጅ፣ ደንብና መመሪያ ያልተከተለ ግዥ ተፈጽሞ መገኘቱን ዋና ኦዲተር ገልጿል።
- ባህልና ስፖርት ሚኒስቴር፣
- የውኃና ኢነርጂ ሚኒስቴር፣
- የብሔራዊ ተሃድሶ ኮሚሽንና አርሲ ዩኒቨርሲቲ ደግሞ ከሕግ ውጪ ግዥ ከፈጸሙ ተቋማት መካከል ዋነኞቹ ናቸው።
ስምንት ተቋማት ደግሞ በጠቅላላው ከ6.5 ሚሊዮን በላይ ብር ዋጋ ያላቸውና ተገዝተዋል የተባሉ ንብረቶች እስካሁን ገቢ እንዳላደረጉ ሲገለጽ የሕዝብ ዕንባ ጠባቂ ተቋም፣ የቤተ መንግሥት አስተዳደርና የመቀሌ ዩኒቨርሲቲ ደግሞ ግዥውን ፈጽመው ዕቃዎቹን ገቢ ያላደረጉ
እንዲሁም በ2016 በጀት ዓመት 20 የፌዴራል መሥሪያ ቤቶች ከተመደበላቸው ዓመታዊ በጀት ውስጥ ከ14 ቢሊዮን ብር በላይ ሳይጠቀሙበት ወደ መንግሥት ካዝና ተመላሽ እንደሆነ ተገልጿል፡፡
የዚህ መረጃ ባለቤት ሪፖርተር ጋዜጣ ነው።
@tikvahethiopia
የመንግሥት ዩኒቨርሲቲዎች ለቋሚ የሥራ ቅጥር መደቦች የቀን ሠራተኞችን በመቅጠር ከ60 ሚሊዮን ብር በላይ ክፍያ መፈጸማቸው ተገለጸ፡፡
የፌዴራል ዋና ኦዲተር መሥሪያ ቤት የመንግሥት ተቋማት የ2016 በጀት ዓመት የበጀት ኦዲት አፈጻጸም ሪፖርት ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ሲያቀርብ ነው የተገለጸው፡፡
ዋና ኦዲተር መሥሪያ ቤት በሪፖርቱ እንደጠቀሰው 12 ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ሳይፈቀድላቸው ለቋሚ የሥራ መደቦች ላይ የቀን ሠራተኞችን ቀጥረው ተገኝተዋል ብሏል።
ተቋማቱ በጠቅላላው 61,882,081 ብር ለቀን ሠራተኞች ክፍያ እንደፈጸሙ የገለጸው የፌዴራል ዋና ኦዲተር ፦
➡️ ጅማ ዩኒቨርሲቲ 25,310,211 ብር፣
➡️ አምቦ ዩኒቨርሲቲ 10,938,834 ብር፣
➡️ ወለጋ ዩኒቨርሲቲ 7,888,374 ብር፣
➡️ ሐሮማያ ዩኒቨርሲቲ 5,170,600 ብርና ዲላ ዩኒቨርሲቲ 4,414,974 ብር በመክፈል ዋነኞቹ እንደሆኑ በሪፖርቱ ተጠቅሰዋል፡፡
እንዲሁም 17 የመንግሥት ተቋማት በጡረታ፣ በሞትና በሌሎች ምክንያት ከሥራ ለለቀቁ ሠራተኞች 408,462 ብር ያላግባብ ደመወዝ መክፈለቸው በሪፖርቱ ተገልጿል፡፡
የሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን ከግንቦት 30 ቀን 2014 ዓ.ም. ጀምሮ በልዩ ሁኔታ ካልተፈቀደ በስተቀር የሠራተኞች ቅጥር፣ የደረጃ ዕድገትና ዝውውር እንዳይፈጸም ቢከለክልም በስምንት መሥሪያ ቤቶችና በአንድ ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት በጠቅላላው 24,073,003 ብር የሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽንን ሳያስፈቅዱ ለቋሚ የሥራ መደቦች ሠራተኞችን በኮንትራት በመቅጠር ክፍያ ፈጽመዋል ተብሏል፡፡
ሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽንን ሳያስፈቅዱ የኮንትራት ቅጥር ከፈጸሙት ተቋማት መካከል ፦
- የቅደስ ጳውሎስ ሆስፒታል ሚሊኒየም ሕክምና ኮሌጅ፣
- ሐሮማያ ዩኒቨርሲቲ፣
- አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲና የአለርት ኮምፕሪሄንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ዋነኞቹ እንደሆኑ ተገልጿል፡፡
ይህ በዚህ እንዳለ በ2015 በጀት ዓመትና ከዚያ በፊት በተከናወኑ የኦዲት ሪፖርቶች መሠረት ዕርምጃ የተወሰደ መሆኑን ለማጣራት ኦዲት ሲደረግ በአጠቃላይ እንዲመለስ አስተያየት ከተሰጠበት 20.5 ቢሊዮን ብርና 23,230 ዶላር ውስጥ፣ የተመለሰው ሦስት ቢሊዮን ብርገደማ ብቻ መሆኑን የፌዴራል ዋና ኦዲተር አስታውቋል።
የፌዴራል ማረሚያ ቤት ኮሚሽን፣ የኢትዮጵያ አካል ጉዳተኞች አገልግሎትና የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቴአትር በአጠቃላይ 37,304,100 ብር የአገልግሎት ገቢ ተመናቸውና በሚመለከተው አካል ሳያፀድቁ ገቢ መሰብሰባቸውም ተገልጿል፡፡
እንዲሁም 28 የፌዴራል መሥሪያ ቤቶችና ሰባት ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤቶች የፈጸሙት 348 ሚሊዮን ብር ክፍያ የተሟላ የወጪ ማስረጃ አልቀረበበትም ተብሏል።
የተሟላ የወጪ ማስረጃ ሳይቀርብ በወጪ ከተመዘገቡት መሥሪያ ቤቶች መካከል የጤና ሚኒስቴር፣ አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ፣ የኢትዮጵያ ኅብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩትና የቤተ መንግሥት አስተዳደር ዋነኞቹ ናቸው።
በ70 የፌዴራል መሥሪያ ቤቶችና በሰባት ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤቶች ከ404 ሚሊዮን ብር በላይ የመንግሥትን የግዥ አዋጅ፣ ደንብና መመሪያ ያልተከተለ ግዥ ተፈጽሞ መገኘቱን ዋና ኦዲተር ገልጿል።
- ባህልና ስፖርት ሚኒስቴር፣
- የውኃና ኢነርጂ ሚኒስቴር፣
- የብሔራዊ ተሃድሶ ኮሚሽንና አርሲ ዩኒቨርሲቲ ደግሞ ከሕግ ውጪ ግዥ ከፈጸሙ ተቋማት መካከል ዋነኞቹ ናቸው።
ስምንት ተቋማት ደግሞ በጠቅላላው ከ6.5 ሚሊዮን በላይ ብር ዋጋ ያላቸውና ተገዝተዋል የተባሉ ንብረቶች እስካሁን ገቢ እንዳላደረጉ ሲገለጽ የሕዝብ ዕንባ ጠባቂ ተቋም፣ የቤተ መንግሥት አስተዳደርና የመቀሌ ዩኒቨርሲቲ ደግሞ ግዥውን ፈጽመው ዕቃዎቹን ገቢ ያላደረጉ
እንዲሁም በ2016 በጀት ዓመት 20 የፌዴራል መሥሪያ ቤቶች ከተመደበላቸው ዓመታዊ በጀት ውስጥ ከ14 ቢሊዮን ብር በላይ ሳይጠቀሙበት ወደ መንግሥት ካዝና ተመላሽ እንደሆነ ተገልጿል፡፡
የዚህ መረጃ ባለቤት ሪፖርተር ጋዜጣ ነው።
@tikvahethiopia
❤1.39K😱149😭71😡67🤔58👏27🙏22🕊20🥰19