TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
62.9K photos
1.61K videos
216 files
4.38K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

መረጃ እና መልዕክት ፦ 0919743630

ማርኬቲንግ ፦ 0979222111 ወይም
0979333111

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#እንድታውቁት

በአዲስ አበባ የህዝብ ትራንስፖርት አገልግሎትን እስከ ምሽት 4:00 በማይሰጡ አገልግሎት ሰጪዎች ላይ እርምጃ መውሰድ እንደሚጀምር የትራንስፖርት ቢሮ አሳውቋል።

ማንኛውም የህዝብ ትራንስፖርት አገልግሎት ሰጪ ከምሽቱ 4፡00 በፊት ፦
- የትራንስፖርት አገልግሎትን ማቋረጥ፣
- ከስምሪት መስመር ውጪ አገልግሎት መስጠት፣
- አቆራርጦ መጫንና
- ቢሮው ካወጣው ህጋዊ ታሪፍ ውጪ ህብረተሰቡን ማስከፈል እንደማይቻል በጥብቅ አሳስቧል።

ከዚህ አሰራርና መመሪያ ውጪ በሚንቀሳቀሱ የህዝብ ትራንስፖርት አገልግሎት ሰጪ #ባለንብረቶች እና #አሽከርካሪዎች ላይ የ5000 ብር (አምስት ሺህ ብር) ቅጣት እንደሚጣልበት አሳውቋል።

#TransportBureau

@tikvahethiopia
👏1.38K😡167153😭72🤔57🙏36🕊23😱12🥰10