TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
62.8K photos
1.61K videos
216 files
4.37K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

መረጃ እና መልዕክት ፦ 0919743630

ማርኬቲንግ ፦ 0979222111 ወይም
0979333111

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#Update የቤጉህዴፓ ማዕከላዊ ኮሚቴ #በተደራጀ_ሌብነት ተሰማርተው የክልሉን የተፈጥሮ ሀብት የመዘበሩ አካላት በምርመራ ተለይተው ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ #እርምጃ እንዲወሰድባቸው ወስኗል፡፡ በተጨማሪም ክልሉ በውስጥም ሆነ በውጭ የሚስተዋሉትን ማንነትን መሰረት ያደረጉ ጥቃቶች ከአጎራባች ክልሎችና ከፌዴራል መንግስት ጋር በመቀናጀት በአጭር ጊዜ እንዲያስቆም ወስኗል። ማዕከላዊ ኮሚቴው በኦሮሚያና በቤኒሻንጉል ጉሙዝ አዋሳኝ አካባቢዎች በተፈጠሩ ግጭቶች በጠፋው የሰው ህይወት፣ እንዲሁም በደረሰው የአካል ጉዳትና መፈናቀል የተሰማውን ጥልቅ #ሀዘን ገልጿል። የቤጉህዴፓ ማዕከላዊ ኮሚቴ ከቤት ንብረታቸው የተፈናቀሉ ዜጎችን መልሶ ለማቋቋም፣ አጥፊዎችን በህግ ለማስጠየቅ እና የፌዴራል መንግስት የሚወስዳቸውን እርምጃዎች ለማስፈጸም በትጋት የሚሰራ መሆኑን አረጋግጧል።

ምንጭ፡- የቤጉህዴፓ ማዕከላዊ ኮሚቴ ጽ/ቤት
@tsegabwolde @tikvahethiopia
👍1