#AddisAbaba
የትምህርት ቤት ክፍያ ጭማሪ !
በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ሥር ሚገኙ 1,227 የግል ትምህርት ቤቶች በ2018 ዓ.ም. የትምህርት ዘመን እስከ 65 በመቶ ድረስ የትምህርት ቤት ክፍያ ጭማሪ እንዲያደርጉ እንደተፈቀደለቸው ተሰምቷል።
የጭማሪውን ጣሪያ 65 በመቶ መጨመር እንዲችል የተፈቀደለት ግን አንድ ትምህርት ቤት ብቻ ነው ተብሏል።
የከተማው ካቢኔ ባፀደቀው፣ " የግል ትምህርት አገልግሎት ክፍያ አሠራር ሥርዓት ረቂቅ ደንብ ቁጥር 194/2017 " መሠረት በ2018 ዓ.ም. የትምህርት ዘመን ከ1,585 የግል ትምህርት ቤቶች ውስጥ 1,227 ያህሉ እስከ 65 በመቶ ብቻ የትምህርት ቤት ክፍያ ጭማሪ ማድረግ እንደሚችሉ የአዲስ አበባ ከተማ የትምህርትና ሥልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለሥልጣን ዋና ሥራ አስኪያጅ አቶ ኢዘዲን ሙስባህ ለሪፖርተር ጋዜጣ ተናግረዋል።
በ2018 ዓ.ም. ጭማሪ ያደርጋሉ ተብለው የሚጠበቁ 1,227 ትምህርት ቤቶች አስቀድሞ የክፍያ ጭማሪ መነሻ ሐሳባችሁን አቅርቡ ሲባሉ " የዋጋ ግሽበት (Inflation) ጨምሯል " በሚል ያቀረቡት ጭማሪ አስደንጋጭ ነበር ብለዋል።
ከትምህርት ቤቶቹ ውስጥ 10 በመቶ የሚሆኑት ብቻ እስከ 50 በመቶ የጭማሪ ሐሳብ ያቀረቡ ሲሆን፣ ቀሪ 90 በመቶ ያህሉ ከ75 እስከ 263 በመቶ ጭማሪ ማቅረባቸውን ተናግረዋል።
ሆኖም ትምህርት ቤቶች ፣ ወላጆች፣ የከተማ አስተዳደሩ የትምህርት ቢሮ፣ የንግድ ቢሮ፣ የፕላንና ልማት ቢሮ፣ የፍትሕ ቢሮና የኢትዮጵያ ስታትስቲክስ አገልግሎት በተሳተፉበት ጥናት፣ ካለው ነባራዊ ሁኔታ ጋር አብሮ ሊሄድ የሚችልና በሚቀጥሉት 3 ዓመታት የሚኖር የዋጋ ማሪ ጣሪያ ይፋ መደረጉን አስረድተዋል።
የከተማ አስተዳደሩ ካቢኔ የክፍያ ጭማሪ ጣሪያውን ሲያስቀምጥ አንዱ መሠረት ያደረገበት ነጥብ የትምህርት ቤቶች ጥራት እንደሆነ ጠቁመዋል።
በዚህም ት/ቤቶች ከደረጃ አንድ እስከ ደረጃ አራት ተብለው በመሥፈርት መለየታቸውን ገልጸዋል። ከእነዚህም ውስጥ ጥራቱ የተሻለ የሚባለው ደረጃ አራት ትምህርት ቤት ነው ሲሉ ገልጸዋል።
" ደረጃ አራት የተሻለ ጥራት ያለው ትምህርት ቤት ነው፤ ጭማሪ ሲደረግም ከደረጃ ሁለት ጋር እኩል መሆን የለበትም፡፡ ስለዚህ ጭማሪውን በፐርሰንት (በመቶኛ) አለያይተነዋል " ብለዋል።
በዚህም ቅድመ መደበኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች የዋጋ ጭማሪ የሚያደርጉት እስከ 45 በመቶ ብቻ ነው ሲሉ ተናግረዋል። " 45 በመቶ ጨምሩ ማለት ሳይሆን ከዜሮ ጀምሮ 10 301 45 በመቶ ብቻ መጨመር ይችላሉ፡፡ ነገር ግን ከዚህ በላይ ማለፍ አይችሉም " ብለዋል።
- አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች እስከ 40 በመቶ
- መካከለኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች እስከ 45 በመቶ፣
- ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች እስከ 55 በመቶ ዋጋ መጨመር ይችላሉ ተብሏል።
በጣሪያው መሠረት ፦
° 144 ትምህርት ቤቶች እስከ 40 በመቶ፣
° 591 ትምህርት ቤቶች እስከ 45 በመቶ
° 378 ትምህርት ቤቶች እስከ 50 በመቶ፣
° 47 ትምህርት ቤቶች እስከ 55 በመቶ፣
° 66 ትምህርቶች እስከ 60 በመቶ ሊጨምሩ እንደሚችሉ ተገልጿል።
ከሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ውስጥ አንድ ትምህርት ቤት ብቻ የመጨረሻውን ጣሪያ ማለትም እስከ 65 በመቶ ክፍያ መጨመር እንደሚችል አቶ ኢዘዲን አመላከተዋል።
በከተማ አስተዳደሩ ከሚገኙ 1,585 ትምህርት ቤቶች መካከል 358 ያህሉ በ2016 ዓ.ም. የትምህርት ዘመን የጨመሩ ስለሆኑ በቀጣዩ ዓመት እንደማይጨምሩ ገልጸዋል። እነዚህ ትምህርት ቤቶች ክፍያ መጨመር የሚችሉት በ2019 ዓ.ም. እንደሚሆንም አክለዋል።
ይህ መረጃ ባለቤትነቱ የሪፖርተር ጋዜጣ ነው።
@tikvahethiopia
የትምህርት ቤት ክፍያ ጭማሪ !
በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ሥር ሚገኙ 1,227 የግል ትምህርት ቤቶች በ2018 ዓ.ም. የትምህርት ዘመን እስከ 65 በመቶ ድረስ የትምህርት ቤት ክፍያ ጭማሪ እንዲያደርጉ እንደተፈቀደለቸው ተሰምቷል።
የጭማሪውን ጣሪያ 65 በመቶ መጨመር እንዲችል የተፈቀደለት ግን አንድ ትምህርት ቤት ብቻ ነው ተብሏል።
የከተማው ካቢኔ ባፀደቀው፣ " የግል ትምህርት አገልግሎት ክፍያ አሠራር ሥርዓት ረቂቅ ደንብ ቁጥር 194/2017 " መሠረት በ2018 ዓ.ም. የትምህርት ዘመን ከ1,585 የግል ትምህርት ቤቶች ውስጥ 1,227 ያህሉ እስከ 65 በመቶ ብቻ የትምህርት ቤት ክፍያ ጭማሪ ማድረግ እንደሚችሉ የአዲስ አበባ ከተማ የትምህርትና ሥልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለሥልጣን ዋና ሥራ አስኪያጅ አቶ ኢዘዲን ሙስባህ ለሪፖርተር ጋዜጣ ተናግረዋል።
በ2018 ዓ.ም. ጭማሪ ያደርጋሉ ተብለው የሚጠበቁ 1,227 ትምህርት ቤቶች አስቀድሞ የክፍያ ጭማሪ መነሻ ሐሳባችሁን አቅርቡ ሲባሉ " የዋጋ ግሽበት (Inflation) ጨምሯል " በሚል ያቀረቡት ጭማሪ አስደንጋጭ ነበር ብለዋል።
ከትምህርት ቤቶቹ ውስጥ 10 በመቶ የሚሆኑት ብቻ እስከ 50 በመቶ የጭማሪ ሐሳብ ያቀረቡ ሲሆን፣ ቀሪ 90 በመቶ ያህሉ ከ75 እስከ 263 በመቶ ጭማሪ ማቅረባቸውን ተናግረዋል።
ሆኖም ትምህርት ቤቶች ፣ ወላጆች፣ የከተማ አስተዳደሩ የትምህርት ቢሮ፣ የንግድ ቢሮ፣ የፕላንና ልማት ቢሮ፣ የፍትሕ ቢሮና የኢትዮጵያ ስታትስቲክስ አገልግሎት በተሳተፉበት ጥናት፣ ካለው ነባራዊ ሁኔታ ጋር አብሮ ሊሄድ የሚችልና በሚቀጥሉት 3 ዓመታት የሚኖር የዋጋ ማሪ ጣሪያ ይፋ መደረጉን አስረድተዋል።
የከተማ አስተዳደሩ ካቢኔ የክፍያ ጭማሪ ጣሪያውን ሲያስቀምጥ አንዱ መሠረት ያደረገበት ነጥብ የትምህርት ቤቶች ጥራት እንደሆነ ጠቁመዋል።
በዚህም ት/ቤቶች ከደረጃ አንድ እስከ ደረጃ አራት ተብለው በመሥፈርት መለየታቸውን ገልጸዋል። ከእነዚህም ውስጥ ጥራቱ የተሻለ የሚባለው ደረጃ አራት ትምህርት ቤት ነው ሲሉ ገልጸዋል።
" ደረጃ አራት የተሻለ ጥራት ያለው ትምህርት ቤት ነው፤ ጭማሪ ሲደረግም ከደረጃ ሁለት ጋር እኩል መሆን የለበትም፡፡ ስለዚህ ጭማሪውን በፐርሰንት (በመቶኛ) አለያይተነዋል " ብለዋል።
በዚህም ቅድመ መደበኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች የዋጋ ጭማሪ የሚያደርጉት እስከ 45 በመቶ ብቻ ነው ሲሉ ተናግረዋል። " 45 በመቶ ጨምሩ ማለት ሳይሆን ከዜሮ ጀምሮ 10 301 45 በመቶ ብቻ መጨመር ይችላሉ፡፡ ነገር ግን ከዚህ በላይ ማለፍ አይችሉም " ብለዋል።
- አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች እስከ 40 በመቶ
- መካከለኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች እስከ 45 በመቶ፣
- ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች እስከ 55 በመቶ ዋጋ መጨመር ይችላሉ ተብሏል።
በጣሪያው መሠረት ፦
° 144 ትምህርት ቤቶች እስከ 40 በመቶ፣
° 591 ትምህርት ቤቶች እስከ 45 በመቶ
° 378 ትምህርት ቤቶች እስከ 50 በመቶ፣
° 47 ትምህርት ቤቶች እስከ 55 በመቶ፣
° 66 ትምህርቶች እስከ 60 በመቶ ሊጨምሩ እንደሚችሉ ተገልጿል።
ከሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ውስጥ አንድ ትምህርት ቤት ብቻ የመጨረሻውን ጣሪያ ማለትም እስከ 65 በመቶ ክፍያ መጨመር እንደሚችል አቶ ኢዘዲን አመላከተዋል።
በከተማ አስተዳደሩ ከሚገኙ 1,585 ትምህርት ቤቶች መካከል 358 ያህሉ በ2016 ዓ.ም. የትምህርት ዘመን የጨመሩ ስለሆኑ በቀጣዩ ዓመት እንደማይጨምሩ ገልጸዋል። እነዚህ ትምህርት ቤቶች ክፍያ መጨመር የሚችሉት በ2019 ዓ.ም. እንደሚሆንም አክለዋል።
ይህ መረጃ ባለቤትነቱ የሪፖርተር ጋዜጣ ነው።
@tikvahethiopia
❤1.1K😡1.05K😭69🙏58🤔32👏17😢15😱14🕊13💔12
#AddisAbaba #እንድታውቁት
ዛሬ ሰኔ 20 ቀን 2017 ዓ.ም ከሌሊቱ 6:00 ሰዓት ጀምሮ በአዲስ ሴንተር ወይም በሜክሲኮ ማከፋፈያ ትራንስፎርመር ላይ አስቸኳይ የጥገና ሥራ እንደሚከናወን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል አሳውቋል።
በዚህም ምክንያት ፦
- በሜክሲኮ፣
- በአፍሪካ ህብረት፣
- በቄራ፣
- በገነት ሆቴል፣
- በደንበል፣
- በመስቀል ፍላወር፣
- በወሎ ስፈር፣
- በመስቀል አደባባይ በባምቢስ እና አካባቢው ኤሌክትሪክ ተቋርጦ እንደሚቆይ አሳውቋል።
የጥገና ሥራው እስኪጠናቀቅ ድረስ ነዋሪዎች ከወዲሁ ተገቢውን ቅድመ ዝግጅት እንዲያደርጉ አሳስቧል።
#EEP
@tikvahethiopia
ዛሬ ሰኔ 20 ቀን 2017 ዓ.ም ከሌሊቱ 6:00 ሰዓት ጀምሮ በአዲስ ሴንተር ወይም በሜክሲኮ ማከፋፈያ ትራንስፎርመር ላይ አስቸኳይ የጥገና ሥራ እንደሚከናወን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል አሳውቋል።
በዚህም ምክንያት ፦
- በሜክሲኮ፣
- በአፍሪካ ህብረት፣
- በቄራ፣
- በገነት ሆቴል፣
- በደንበል፣
- በመስቀል ፍላወር፣
- በወሎ ስፈር፣
- በመስቀል አደባባይ በባምቢስ እና አካባቢው ኤሌክትሪክ ተቋርጦ እንደሚቆይ አሳውቋል።
የጥገና ሥራው እስኪጠናቀቅ ድረስ ነዋሪዎች ከወዲሁ ተገቢውን ቅድመ ዝግጅት እንዲያደርጉ አሳስቧል።
#EEP
@tikvahethiopia
❤782😭175😡86🙏73👏47😢17🕊15😱11🥰9🤔9
#AddisAbaba
" በዘንድሮ የግብር ማሳወቂያ እና መክፈያ ወቅት በገቢዎች ቢሮ 256 ቢሊየን ብር ለመሰብሰብ ታቅዷል " - ገቢዎች ቢሮ
ከሐምሌ 1/2017 ዓ/ም ጀምሮ እስከ ጥቅምት 30/2018 ዓ/ም ድረስ የ2017 ዓ/ም የግብር ማሳወቂያ ወቅት ነው።
በዛሬው ዕለት የደረጃ "ሐ" ግብር ከፋይ ደንበኞች ግብራቸውን ማሳወቅ የጀመሩ ሲሆን እስከ ሐምሌ 30/2017 ዓም ድረስ ግብር ግብራቸውን እያሳወቁ ይቆያሉ።
ከዚህ ቀደም ከነበረው አሰራር ለየት ባለ መልኩ በየደረጃው ያሉ ግብር ከፋዮች በወጣላቸው መርሃ ግብር መሰረት ግብራቸውን እንዲከፍሉ እንደሚደረግ የቢሮው የኮምዩኒኬሽን ዳይሬክተር አቶ ሰውነት አየለ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።
አቶ ሰውነት " ከዚህ ቀደም የደረጃ 'ለ' ግብር ከፋዮች ከሃምሌ 1 እስከ ጳጉሜ 5 ነበር የሚከፍሉት ዘንድሮ ይህ አሰራር ተቀይሮ ሃምሌን ለዝግጅት እንዲጠቀሙት እና ግብራቸውን ከ ነሐሴ 1 እስከ ጳጉሜ 5 ድረስ እንዲከፍሉ ተወስኗል አከፋፈላቸውም በስም ቅደም ተከተል ይሆናል " ብለዋል።
ዳይሬክተሩ በስም ቅደም ተከተል እንዲከፍሉ መደረጉ ግብር ከፋዩ ላይ መጨናነቆች እንዳይኖሩ እና ለብልሹ አሰራሮች እንዳይዳረጉ ያግዛል ነው ያሉት።
አቶ ሰውነት አየለ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በዝርዝር በሰጡት ሃሳብ ምን አሉ ?
" የደረጃ 'ለ' ግብር ከፋይ ደንበኞች በነሐሴ ወር የመጀመሪያው ሳምንት ላይ የስም ዝርዝራቸው ከ A-D ያሉ ግብር ከፋዮች የሚስተናገዱበት ፕሮግራም ወጥቷል፣ በዚህም መሰረት ግብር ከፋዩን በአራት ሳምንት በመከፋፈል አመታዊ ግብራቸውን እንዲያሳውቁ እና እንዲከፍሉ ይደረጋል።
የደረጃ 'ሀ' ግብር ከፋዮችን በሚመለከትም ከዚህ ቀደም ከሐምሌ 1 እስከ ጥቅምት 30 የአመታዊ ግብራቸውን የመክፈያ እና የማሳወቂያ ጊዜያቸው ነበር።
እነዚህ ግብር ከፋዮችም ሐምሌ እና ነሃሴን ለዝግጅት ተጠቅመው መስከረም እና ጥቅምትን ግብራቸውን የሚከፍሉበት ፕሮግራም ወጥቷል።
ቢሮው በተለያዩ ጊዜያት ከንግዱ ማህበረሰብ ጋር ባደረጋቸው ውይይቶች ወቅት የተነሱ የተለያዩ ችግሮች ነበሩ እነዚህን የተጠቀሱ ችግሮችን ለመቅረፍ የሚያስችሉ በጥናት የተለዩ 24 አይነት አዳዲስ አሰራሮችን ዘርግተናል ከዛሬ ጀምሮ ተግባራዊ ይደረጋል።
ለምሳሌ የኦዲት ጥራት ጋር ላይ ከአሰራር ጋር በተያያዘ ባሉ ክፍተቶች ምክንያት ሁለት ኦዲተሮች አንድ አይነት ፋይል ተመልክተው ውሳኔ ሲወስኑ ግን ሁለት አይነት ውሳኔ የሚወስኑበት አሰራር ነበር ይህንን ለማስቀረት የሚያስችል የአሰራር ስርአት ተዘርግቷል።
ከሂሳብ መዝገብ ጋር በተገናኘም የሂሳም መዝገብ መያዝ ያለባቸው ግብር ከፋዮች መዝገቡን ባለመያዛቸው በቁርጥ ግብር ሲስተናገዱ ነበር።
አፈጻጸም ላይ በነበረ ክፍተት ምክንያት በተለይም የደረጃ 'ሀ' እና 'ለ' ግብር ከፋዮች ያለ ሂሳብ መዝገብ ሲስተናገዱ የቆዩ ቢሆንም ከአሁኑ የ2017 ዓ/ም የግብር ማሳወቂያ ወቅት ጀምሮ ያለ ሂሳብ መዝገብ አይሰራም።
ሂሳብ መዝገብ ሳይዙ የሚመጡ ከሆነ ግን የሚወሰነው ውሳኔ አስተማሪ የሚሆን ይሆናል።
የግብር አሰባሰብ ስርአቱም ከእጅ ንክኪ በጸዳ መንገድ እንዲሆን በማሰብ የደረጃ 'ሐ' ግብር ከፋዮች በET-TAX በተሰኘ በተቋሙ በለማ መተግበሪያ እቤታቸው ተቀምጠው ግብራቸውን የሚያውቁበት እና የሚከፍሉበት ሁኔታ ተፈጥሯል።
በSMS በሚደርሳቸው መረጃም በTelebirr እና CBE Birr ግብራቸውን መክፈል ይችላሉ።
የደረጃ 'ሀ' እና የደረጃ 'ለ' ግብር ከፋዮችም በተመሳሳይ E-TAX በተሰኘ መተግበሪያ እንዲከፍሉ እያደረግን ያለንበት ሁኔታ አለ ነገር ግን ሁሉም ወደዚህ አሰራር ስርአት ገና አልገቡም።
ከፍተኛ ግብር ከፋዮች 100 ፕርሰንት ወደዚህ አሰራር ስርአት ገብተዋል ቀሪዎቹ በየቅርንጫፉ እቅድ ተይዞ አብዛኛው ግብር ከፋይ ወደዚህ አሰራር እንዲገባ እየተሰራ ነው።
የኦዲት ጥራትን የሚያረጋግጥ የስራ ክፍል ተደራጅቷል ኦዲተሩ የወሰነው ውሳኔ ምን ያህል ጥራት አለው የሚለውን ያረጋግጣል ከፍተኛ ልዩነት ከተፈጠረም ግብር ከፋዩ እንዲከፈል ይደረጋል፣ ይህንን የወሰነው አካልም ተጠያቂ ይሆናል።
የግብር ከፋዩን ሂሳብ መዝግብ የሚያዘጋጁ ባለሞያዎች በሚመለከት ከዚህ ቀደም ከግብር ከፋዩ ጋር በመደራደር ከፍተኛ የሆነ ግብር የመሰወር ስራ የሚሰሩበት እና የተሳሳቱ ሰነዶችን የሚያቀርቡበት ሁኔታ ነበር።
በዚህ ጊዜ ግብር ከፋዩን ኦዲት አድርገን ገንዘቡን ብናስከፍልም የሂሳብ ባለሞያዎቹ ተጠያቂ የምናደርግበት አሰራር አልነበረም አሁን የሂሳብ ባለሞያዎቹም ተጠያቂ የሚሆኑበትን አሰራር ዘርግተናል።
ኦንላይን ግብይትንም ለመቆጣጠር እና ግብር እንዲከፍሉ ለማድረግ የሚቻልበት የአሰራር ስረዓት ለመዘርጋት እየተሰራ ነው።
ከማዕከል ሁሉንም ቅርንጫፎች ለመቆጣጠር የሚያስችል ካሜራ አስገጥመናል።
በዘንድሮ የግብር ማሳወቂያ እና መክፈያ ወቅት በገቢዎች ቢሮ 256 ቢሊየን ብር ለመሰብሰብ ታቅዷል " ብለዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvahEthiopiaFamilyAddisAbaba
@tikvahethiopia
" በዘንድሮ የግብር ማሳወቂያ እና መክፈያ ወቅት በገቢዎች ቢሮ 256 ቢሊየን ብር ለመሰብሰብ ታቅዷል " - ገቢዎች ቢሮ
ከሐምሌ 1/2017 ዓ/ም ጀምሮ እስከ ጥቅምት 30/2018 ዓ/ም ድረስ የ2017 ዓ/ም የግብር ማሳወቂያ ወቅት ነው።
በዛሬው ዕለት የደረጃ "ሐ" ግብር ከፋይ ደንበኞች ግብራቸውን ማሳወቅ የጀመሩ ሲሆን እስከ ሐምሌ 30/2017 ዓም ድረስ ግብር ግብራቸውን እያሳወቁ ይቆያሉ።
ከዚህ ቀደም ከነበረው አሰራር ለየት ባለ መልኩ በየደረጃው ያሉ ግብር ከፋዮች በወጣላቸው መርሃ ግብር መሰረት ግብራቸውን እንዲከፍሉ እንደሚደረግ የቢሮው የኮምዩኒኬሽን ዳይሬክተር አቶ ሰውነት አየለ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።
አቶ ሰውነት " ከዚህ ቀደም የደረጃ 'ለ' ግብር ከፋዮች ከሃምሌ 1 እስከ ጳጉሜ 5 ነበር የሚከፍሉት ዘንድሮ ይህ አሰራር ተቀይሮ ሃምሌን ለዝግጅት እንዲጠቀሙት እና ግብራቸውን ከ ነሐሴ 1 እስከ ጳጉሜ 5 ድረስ እንዲከፍሉ ተወስኗል አከፋፈላቸውም በስም ቅደም ተከተል ይሆናል " ብለዋል።
ዳይሬክተሩ በስም ቅደም ተከተል እንዲከፍሉ መደረጉ ግብር ከፋዩ ላይ መጨናነቆች እንዳይኖሩ እና ለብልሹ አሰራሮች እንዳይዳረጉ ያግዛል ነው ያሉት።
አቶ ሰውነት አየለ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በዝርዝር በሰጡት ሃሳብ ምን አሉ ?
" የደረጃ 'ለ' ግብር ከፋይ ደንበኞች በነሐሴ ወር የመጀመሪያው ሳምንት ላይ የስም ዝርዝራቸው ከ A-D ያሉ ግብር ከፋዮች የሚስተናገዱበት ፕሮግራም ወጥቷል፣ በዚህም መሰረት ግብር ከፋዩን በአራት ሳምንት በመከፋፈል አመታዊ ግብራቸውን እንዲያሳውቁ እና እንዲከፍሉ ይደረጋል።
የደረጃ 'ሀ' ግብር ከፋዮችን በሚመለከትም ከዚህ ቀደም ከሐምሌ 1 እስከ ጥቅምት 30 የአመታዊ ግብራቸውን የመክፈያ እና የማሳወቂያ ጊዜያቸው ነበር።
እነዚህ ግብር ከፋዮችም ሐምሌ እና ነሃሴን ለዝግጅት ተጠቅመው መስከረም እና ጥቅምትን ግብራቸውን የሚከፍሉበት ፕሮግራም ወጥቷል።
ቢሮው በተለያዩ ጊዜያት ከንግዱ ማህበረሰብ ጋር ባደረጋቸው ውይይቶች ወቅት የተነሱ የተለያዩ ችግሮች ነበሩ እነዚህን የተጠቀሱ ችግሮችን ለመቅረፍ የሚያስችሉ በጥናት የተለዩ 24 አይነት አዳዲስ አሰራሮችን ዘርግተናል ከዛሬ ጀምሮ ተግባራዊ ይደረጋል።
ለምሳሌ የኦዲት ጥራት ጋር ላይ ከአሰራር ጋር በተያያዘ ባሉ ክፍተቶች ምክንያት ሁለት ኦዲተሮች አንድ አይነት ፋይል ተመልክተው ውሳኔ ሲወስኑ ግን ሁለት አይነት ውሳኔ የሚወስኑበት አሰራር ነበር ይህንን ለማስቀረት የሚያስችል የአሰራር ስርአት ተዘርግቷል።
ከሂሳብ መዝገብ ጋር በተገናኘም የሂሳም መዝገብ መያዝ ያለባቸው ግብር ከፋዮች መዝገቡን ባለመያዛቸው በቁርጥ ግብር ሲስተናገዱ ነበር።
አፈጻጸም ላይ በነበረ ክፍተት ምክንያት በተለይም የደረጃ 'ሀ' እና 'ለ' ግብር ከፋዮች ያለ ሂሳብ መዝገብ ሲስተናገዱ የቆዩ ቢሆንም ከአሁኑ የ2017 ዓ/ም የግብር ማሳወቂያ ወቅት ጀምሮ ያለ ሂሳብ መዝገብ አይሰራም።
ሂሳብ መዝገብ ሳይዙ የሚመጡ ከሆነ ግን የሚወሰነው ውሳኔ አስተማሪ የሚሆን ይሆናል።
የግብር አሰባሰብ ስርአቱም ከእጅ ንክኪ በጸዳ መንገድ እንዲሆን በማሰብ የደረጃ 'ሐ' ግብር ከፋዮች በET-TAX በተሰኘ በተቋሙ በለማ መተግበሪያ እቤታቸው ተቀምጠው ግብራቸውን የሚያውቁበት እና የሚከፍሉበት ሁኔታ ተፈጥሯል።
በSMS በሚደርሳቸው መረጃም በTelebirr እና CBE Birr ግብራቸውን መክፈል ይችላሉ።
የደረጃ 'ሀ' እና የደረጃ 'ለ' ግብር ከፋዮችም በተመሳሳይ E-TAX በተሰኘ መተግበሪያ እንዲከፍሉ እያደረግን ያለንበት ሁኔታ አለ ነገር ግን ሁሉም ወደዚህ አሰራር ስርአት ገና አልገቡም።
ከፍተኛ ግብር ከፋዮች 100 ፕርሰንት ወደዚህ አሰራር ስርአት ገብተዋል ቀሪዎቹ በየቅርንጫፉ እቅድ ተይዞ አብዛኛው ግብር ከፋይ ወደዚህ አሰራር እንዲገባ እየተሰራ ነው።
የኦዲት ጥራትን የሚያረጋግጥ የስራ ክፍል ተደራጅቷል ኦዲተሩ የወሰነው ውሳኔ ምን ያህል ጥራት አለው የሚለውን ያረጋግጣል ከፍተኛ ልዩነት ከተፈጠረም ግብር ከፋዩ እንዲከፈል ይደረጋል፣ ይህንን የወሰነው አካልም ተጠያቂ ይሆናል።
የግብር ከፋዩን ሂሳብ መዝግብ የሚያዘጋጁ ባለሞያዎች በሚመለከት ከዚህ ቀደም ከግብር ከፋዩ ጋር በመደራደር ከፍተኛ የሆነ ግብር የመሰወር ስራ የሚሰሩበት እና የተሳሳቱ ሰነዶችን የሚያቀርቡበት ሁኔታ ነበር።
በዚህ ጊዜ ግብር ከፋዩን ኦዲት አድርገን ገንዘቡን ብናስከፍልም የሂሳብ ባለሞያዎቹ ተጠያቂ የምናደርግበት አሰራር አልነበረም አሁን የሂሳብ ባለሞያዎቹም ተጠያቂ የሚሆኑበትን አሰራር ዘርግተናል።
ኦንላይን ግብይትንም ለመቆጣጠር እና ግብር እንዲከፍሉ ለማድረግ የሚቻልበት የአሰራር ስረዓት ለመዘርጋት እየተሰራ ነው።
ከማዕከል ሁሉንም ቅርንጫፎች ለመቆጣጠር የሚያስችል ካሜራ አስገጥመናል።
በዘንድሮ የግብር ማሳወቂያ እና መክፈያ ወቅት በገቢዎች ቢሮ 256 ቢሊየን ብር ለመሰብሰብ ታቅዷል " ብለዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvahEthiopiaFamilyAddisAbaba
@tikvahethiopia
❤971😡476😭89😱44🤔22🙏22🕊20😢10👏8💔7🥰6
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#AddisAbaba
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ገቢዎች ቢሮ የ2017 ዓ/ም የግብር ዘመን ግብር አወሳሰንና አሰባሰብ አሰራር ይፋ አድርጓል።
አዲሱ መመሪያ የሂሳብ መዝገብና የሂሳብ መግለጫ መሰረት በማድረግ የማሳወቅ፣ የመክፈል እና ሰነዶችን የመያዝ ግዴታ ተፈጻሚ የማይደረግባቸው ግብር ከፋዮችን በሚመለከት።
እንዲሁም የሂሳብ መዝገብና የሂሳብ መግለጫ መሰረት በማድረግ የማሳወቅ፣ የመከፈል እና ሰነዶችን የመያዝ ግዴታን ያልተወጡ ግብር ከፋዮችን በተመለከተ መደረግ ስላለበት ዝርዝር ሃሳብ የያዘ ደብዳቤ በቢሮው የታክስ ጉዳዮች ዘርፍ ምክትል ቢሮ ሃላፊ ወ/ሮ ወርቅነሽ ሰቦቃ ተፈርሞ ለሁሉም ለግብር ከፋዮች ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ተልኳል።
ደብዳቤው "የተወሰኑ ግብር ከፋዬች በህጉ የተጣለባቸውን ግዴታ ለመወጣት የተሰማሩበትን የስራ ዘርፍ ባለው የተለየ ባህሪ ምክንያት መቸገራቸውን በተለያየ ጊዜ በመጥቀስ አቤቱታ ያቀረቡ" መሆኑን ገልጿል።
ይሁን እንጂ የግብር ሕጉ ለየትኛውም የንግድ ዘርፍ በተለየ መልኩ የሂሳብ መዝገብና የሂሳብ መግለጫ መሰረት በማድረግ የማሳወቅ የመከፈል እና ሰነዶችን የመያዝ ግዴታን ቀሪ አለማድረጉንም አሳውቋል።
ይህንኑ ግዴታ አለመወጣትም አስተዳደራዊ ቅጣት የሚያስከትል መሆኑ እንደተጠበቀ ሆኖ የተለየ ባህሪ ያላቸው የተወሰኑ የሥራ ዘርፎች የግብር ህጉን ድንጋጌዎች በአስከበረ አግባብ የገቢ አሰበሰቡን እና የአገልግሎት አሰጣቱን ፍታሀዊነት ማዕከል ያደረገ የአሰራር ሥርዓት ለ2017 የግብር ማሳወቂያ ጊዜ ሂሳብ መዝገብ የማቅረብ ግዴታን ተፈጻሚነት በቅጣት ብቻ በማለፍ ማዘግየት አስፈላጊ መሆኑ ታምኖበታል ብሏል።
ስለሆነም የደረጃ "ሀ" እና የደረጃ "ለ" ግብር ከፋዬች የሂሳብ መዝገብና የሂሳብ መግለጫ መሰረት በማድረግ የማሳወቅ፣ የመከፈል እና ሰነዶችን የመያዝ ግዴታን ከዚህ በታች የተዘረዘሩ ግብር ከፋዬች በማይወጡበት ጊዜ ለደረጃ «ሐ» ግብር ከፋዬች የወጣውን ገቢ ግብር ደንብ ቁጥር 410/2009 የትርፍ ሕዳግ እና በግምት ግብር አወሳሰን መመሪያ ቁጥር 138/2010 በቁርጥ የወጪ ሰንጠረዥ መጠቀም ዘርፉ ግዴታውን በገቢ ግብር ሕጉ መሰረት እንዳይወጣ ከተማውም ማግኘት የሚገባውን ገቢ እንዳይሰበስብ ምክንያት ስለሚሆን ይህንኑ ክፍተት ለመዝጋት በገቢ ግብር አዋጁ ቁጥር 979/2008 አንቀጽ 80 መሰረት ግብር በግምት በሚሰላበት ጊዜ፦
ከግብር ከፋዮች ግንዛቤ የተለየ ድጋፍ የሚፈልጉ እና ሥራቸውም ከመንግስት ጋር በተገባ ውል ብቻ የሚያከናውኑ በማህበር የተደራጁ :-
- የትምህርት ቤቶችና የምገባ ማዕከላት መጋቢ እናቶች
- በከተማ ጽዳትና ውበት ደረቅ ቆሻሻ እና ገጸ-ምድር ማስዋብ ላይ የተሰማሩ
- ከንግድ ቢሮ ትስስር የተፈጠረላቸው የሸገር ዳቦን የሚሸጡ ማህበራት
ከመንግስት ተቋማት ጋር ያላቸውን ውልና በበጀት ዓመቱ ከአሰራቸው የመንግስት ተቋም ዓመቱን ሙሉ የተከፈላቸውን ክፍያ የሚገልጽ መረጃ ሲያመጡ መረጃን መሰረት አድርጎ በሠንጠረዥ "ሐ" መሠረት ግብሩን በማስላት ገቢው ተወስኖ እንዲሰበሰብ።
በተጨማሪም የሸገር ዳቦን የሚሸጡ በተጓዳኝ የሚከናውኑ የንግድ ስራዎች መኖራቸው በመስክ ምልከታ ተረጋግጦ በየዘርፉ የቀን ገቢ ግምት እንዲገመትላቸው ተደርጎ ግብሩ ተወስኖ እንዲሰበሰብ።
የንግድ ሥራ ፍቃድ ሳይኖራቸው በሞያ ፍቃድ ብቻ አገልግሎት የሚሰጡ ጠበቆች ፣የኢንሹራንስ ወኪሎች ፣ኢንሹራንስ ጉዳት ገማች ግለሰቦች በሚመለከት:-
➡️ ከግብር አመቱ አጠቃላይ እንደ ገቢ 35 በመቶ እንደ ወጪ 65 በመቶ ግብር የሚከፈልበት ገቢ ሆኖ በሠንጠረዥ "ሐ" መሠረት ግብሩን በማስላት ተወስኖ ገቢው እንዲሰበሰብ።
➡️ የንግድ ሥራ ያልሆነ ገቢ ያላቸው የመኖሪያ ቤት አከራዮች ከግብር አመቱ አጠቃላይ ገቢ 35 በመቶ እንደ ወጪ 65 በመቶ ግብር የሚከፈልበት ገቢ ሆኖ በሠንጠረዥ "ሐ" መሠረት ግብሩን በማስላት ተወስኖ ገቢው እንዲሰበሰብ።
➡️ በግል ኮድ 02 እና በንግድ ኮድ 03 ተሸከርካሪ የኪራይ አገልግሎት የሚሰጡ አጠቃላይ የኪራይ ገቢ ላይ በሠንጠረዥ "ሐ" መሠረት በመረጃ የሚወሰን በመሆኑ ግብሩን በማስላት ተወስኖ ገቢው እንዲሰበሰብ።
➡️ በህግ ደረሰኝ የመጠቀም ግዴታ ተፈጻሚ የማይደረግባቸው የከተማ ውስጥ የትራንስፖርት አገልግሎት ሰጭዎች /በቴክኖሎጂ ስምሪት የሚሰጣቸውን የሜትር ታከሲዎች ጨምሮ/ የገቢ ግብር ደንብ ቁጥር 410/2009 ሠንጠረዥ "ሐ" መሠረት ግብሩን በማስላት ተወስኖ ገቢው እንዲሰበሰብ መወሰኑን ይገልጻል።
(ተጨማሪውን ከተያያዘው ደብዳቤ ይመልከቱ)
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvahEthiopiaFamilyAddisAbaba
@tikvahethiopia
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ገቢዎች ቢሮ የ2017 ዓ/ም የግብር ዘመን ግብር አወሳሰንና አሰባሰብ አሰራር ይፋ አድርጓል።
አዲሱ መመሪያ የሂሳብ መዝገብና የሂሳብ መግለጫ መሰረት በማድረግ የማሳወቅ፣ የመክፈል እና ሰነዶችን የመያዝ ግዴታ ተፈጻሚ የማይደረግባቸው ግብር ከፋዮችን በሚመለከት።
እንዲሁም የሂሳብ መዝገብና የሂሳብ መግለጫ መሰረት በማድረግ የማሳወቅ፣ የመከፈል እና ሰነዶችን የመያዝ ግዴታን ያልተወጡ ግብር ከፋዮችን በተመለከተ መደረግ ስላለበት ዝርዝር ሃሳብ የያዘ ደብዳቤ በቢሮው የታክስ ጉዳዮች ዘርፍ ምክትል ቢሮ ሃላፊ ወ/ሮ ወርቅነሽ ሰቦቃ ተፈርሞ ለሁሉም ለግብር ከፋዮች ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ተልኳል።
ደብዳቤው "የተወሰኑ ግብር ከፋዬች በህጉ የተጣለባቸውን ግዴታ ለመወጣት የተሰማሩበትን የስራ ዘርፍ ባለው የተለየ ባህሪ ምክንያት መቸገራቸውን በተለያየ ጊዜ በመጥቀስ አቤቱታ ያቀረቡ" መሆኑን ገልጿል።
ይሁን እንጂ የግብር ሕጉ ለየትኛውም የንግድ ዘርፍ በተለየ መልኩ የሂሳብ መዝገብና የሂሳብ መግለጫ መሰረት በማድረግ የማሳወቅ የመከፈል እና ሰነዶችን የመያዝ ግዴታን ቀሪ አለማድረጉንም አሳውቋል።
ይህንኑ ግዴታ አለመወጣትም አስተዳደራዊ ቅጣት የሚያስከትል መሆኑ እንደተጠበቀ ሆኖ የተለየ ባህሪ ያላቸው የተወሰኑ የሥራ ዘርፎች የግብር ህጉን ድንጋጌዎች በአስከበረ አግባብ የገቢ አሰበሰቡን እና የአገልግሎት አሰጣቱን ፍታሀዊነት ማዕከል ያደረገ የአሰራር ሥርዓት ለ2017 የግብር ማሳወቂያ ጊዜ ሂሳብ መዝገብ የማቅረብ ግዴታን ተፈጻሚነት በቅጣት ብቻ በማለፍ ማዘግየት አስፈላጊ መሆኑ ታምኖበታል ብሏል።
ስለሆነም የደረጃ "ሀ" እና የደረጃ "ለ" ግብር ከፋዬች የሂሳብ መዝገብና የሂሳብ መግለጫ መሰረት በማድረግ የማሳወቅ፣ የመከፈል እና ሰነዶችን የመያዝ ግዴታን ከዚህ በታች የተዘረዘሩ ግብር ከፋዬች በማይወጡበት ጊዜ ለደረጃ «ሐ» ግብር ከፋዬች የወጣውን ገቢ ግብር ደንብ ቁጥር 410/2009 የትርፍ ሕዳግ እና በግምት ግብር አወሳሰን መመሪያ ቁጥር 138/2010 በቁርጥ የወጪ ሰንጠረዥ መጠቀም ዘርፉ ግዴታውን በገቢ ግብር ሕጉ መሰረት እንዳይወጣ ከተማውም ማግኘት የሚገባውን ገቢ እንዳይሰበስብ ምክንያት ስለሚሆን ይህንኑ ክፍተት ለመዝጋት በገቢ ግብር አዋጁ ቁጥር 979/2008 አንቀጽ 80 መሰረት ግብር በግምት በሚሰላበት ጊዜ፦
ከግብር ከፋዮች ግንዛቤ የተለየ ድጋፍ የሚፈልጉ እና ሥራቸውም ከመንግስት ጋር በተገባ ውል ብቻ የሚያከናውኑ በማህበር የተደራጁ :-
- የትምህርት ቤቶችና የምገባ ማዕከላት መጋቢ እናቶች
- በከተማ ጽዳትና ውበት ደረቅ ቆሻሻ እና ገጸ-ምድር ማስዋብ ላይ የተሰማሩ
- ከንግድ ቢሮ ትስስር የተፈጠረላቸው የሸገር ዳቦን የሚሸጡ ማህበራት
ከመንግስት ተቋማት ጋር ያላቸውን ውልና በበጀት ዓመቱ ከአሰራቸው የመንግስት ተቋም ዓመቱን ሙሉ የተከፈላቸውን ክፍያ የሚገልጽ መረጃ ሲያመጡ መረጃን መሰረት አድርጎ በሠንጠረዥ "ሐ" መሠረት ግብሩን በማስላት ገቢው ተወስኖ እንዲሰበሰብ።
በተጨማሪም የሸገር ዳቦን የሚሸጡ በተጓዳኝ የሚከናውኑ የንግድ ስራዎች መኖራቸው በመስክ ምልከታ ተረጋግጦ በየዘርፉ የቀን ገቢ ግምት እንዲገመትላቸው ተደርጎ ግብሩ ተወስኖ እንዲሰበሰብ።
የንግድ ሥራ ፍቃድ ሳይኖራቸው በሞያ ፍቃድ ብቻ አገልግሎት የሚሰጡ ጠበቆች ፣የኢንሹራንስ ወኪሎች ፣ኢንሹራንስ ጉዳት ገማች ግለሰቦች በሚመለከት:-
➡️ ከግብር አመቱ አጠቃላይ እንደ ገቢ 35 በመቶ እንደ ወጪ 65 በመቶ ግብር የሚከፈልበት ገቢ ሆኖ በሠንጠረዥ "ሐ" መሠረት ግብሩን በማስላት ተወስኖ ገቢው እንዲሰበሰብ።
➡️ የንግድ ሥራ ያልሆነ ገቢ ያላቸው የመኖሪያ ቤት አከራዮች ከግብር አመቱ አጠቃላይ ገቢ 35 በመቶ እንደ ወጪ 65 በመቶ ግብር የሚከፈልበት ገቢ ሆኖ በሠንጠረዥ "ሐ" መሠረት ግብሩን በማስላት ተወስኖ ገቢው እንዲሰበሰብ።
➡️ በግል ኮድ 02 እና በንግድ ኮድ 03 ተሸከርካሪ የኪራይ አገልግሎት የሚሰጡ አጠቃላይ የኪራይ ገቢ ላይ በሠንጠረዥ "ሐ" መሠረት በመረጃ የሚወሰን በመሆኑ ግብሩን በማስላት ተወስኖ ገቢው እንዲሰበሰብ።
➡️ በህግ ደረሰኝ የመጠቀም ግዴታ ተፈጻሚ የማይደረግባቸው የከተማ ውስጥ የትራንስፖርት አገልግሎት ሰጭዎች /በቴክኖሎጂ ስምሪት የሚሰጣቸውን የሜትር ታከሲዎች ጨምሮ/ የገቢ ግብር ደንብ ቁጥር 410/2009 ሠንጠረዥ "ሐ" መሠረት ግብሩን በማስላት ተወስኖ ገቢው እንዲሰበሰብ መወሰኑን ይገልጻል።
(ተጨማሪውን ከተያያዘው ደብዳቤ ይመልከቱ)
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvahEthiopiaFamilyAddisAbaba
@tikvahethiopia
1❤1.33K😡175🤔35🙏35🥰26😭24😢23🕊23😱18👏16
TIKVAH-ETHIOPIA
" ትምህርት ቤቶች ባቀረቡት የዋጋ ጭማሪ ፕሮፖዛል ላይከወላጆች ጋር መግባባት ላይ መድረስ ካልተቻለ ባለሥልጣኑ ውሳኔ የሚሰጥ ይሆናል " - የአዲስ አበባ ትምህርት ቢሮ በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ሥር የሚገኙ 1,227 የግል ትምህርት ቤቶች በ2018 ዓ.ም. የትምህርት ዘመን እስከ 65 በመቶ ድረስ የትምህርት ቤት ክፍያ ጭማሪ እንዲያደርጉ እንደተፈቀደለቸው መዘገቡ ይታወሳል። ጭማሪውን ተከትሎ የአዲስ…
#AddisAbaba
የትምህርት ቤት ክፍያ !
20 በመቶ ትምህርት ቤቶች በ2018 የትምህርት ዘመን አገልግሎት ክፍያ ጭማሪ ላይ ከወላጆች ጋር አለመስማማታቸውን የአዲስ አበባ ትምህርት ቢሮ አሳውቋል።
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ካቢኔ በቅርቡ ባጸደቀው የግል ትምህርት አገልግሎት ክፍያ አሰራር ስርአት ደንብ ቁጥር 194/2017 መሰረት በ2018 የትምህርት ዘመን አገልግሎት ክፍያ ላይ ከ ተማሪ ወላጅና አሳዳጊዎች ጋር ካልተስማሙ መንግስታዊ ካልሆኑ የትምህርት ተቋማት ጋር ውይይት መካሄዱን የከተማው ትምህርት ቢሮ አሳውቋል።
በውይይት መርሃ ግብሩ ፦
- የትምህርት ቢሮ ሃላፊ ዘላለም ሙላቱ (ዶ/ር) ፣
- የትምህርት እና ሥልጠና ባለሥልጣን ከፍተኛ አመራሮች
- የግል ትምህርት ቤቶች አሰሪዎች ማህበር ፣
- የግል ትምህርት ቤት ባለቤቶች እና የተማሪ ወላጅ ኮሚቴ ተወካዮች እንደ ተሳተፉ ቢሮው በማህበራዊ ትስስር ገጹ ገልጿል።
ውይይቱ የተካሄደው በጭማሪው ላይ መስማማት ላይ ያልደረሱ ትምህርት ቤቶች ደንቡ በሚያስቀምጠው መሰረት ባለስልጣን መስሪያ ቤቱ ውሳኔ ያሳለፈ በመሆኑ በዚህ ጉዳይ ላይ የጋራ አስተሳሰብ ለመያዝ እንዲቻል መሆኑን ተገልጿል።
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ኃላፊ ዶክተር ዘላለም ሙላቱ "በደንቡ መሰረት 80 ፐርሰንት ያህል ትምህርት ቤቶች ከወላጆችና አሳዳጊዎች ጋር በመስማማት የአገልግሎት ክፍያ መጨመራቸው የሚበረታታ ተግባር ነው" ብለዋል።
እንደ ትምህርት ቢሮ ሃላፊው ገለጻ 20 በመቶ የሚሆኑ ትምህርት ቤቶች ከክፍያ ጭማሪ ጋር በተያያዘ ከወላጆች እና አሳዳጊዎች መስማማት ላይ አለመድረሳቸውን አመላክቷል።
የትምህርትና ስልጠናና ቁጥጥር ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር አቶ ኢዘዲን ሙስባህ "በደንቡ ላይ በመግባባት ወደ ስራ መገባቱን በዚህም መሰረት በርካታ ትምህርት ቤቶች ከወላጆች ጋር በመስማማት መጨመራቸውን ፣ መመሪያውን መሰረት በማድረግም ባለስልጣኑ በተቀሩትና መስማማት ባልቻሉት ላይ ውሳኔ መስጠቱን" አሳውቀዋል ።
ባለሥልጣኑ ምን ውሳኔ እንዳሳለፈ በዝርዝር ባይገለጽም የወላጆችን የመክፈል አቅም እና የትምህርት ተቋማቱን የግብአት አቅርቦት ታሳቢ አድርጎ ተግባራዊ የሆነ መሆኑን ስለመናገራቸው ትምህርት ቢሮው አሳውቋል።
#AddisAbabaEducationBureau
@tikvahethiopia
የትምህርት ቤት ክፍያ !
20 በመቶ ትምህርት ቤቶች በ2018 የትምህርት ዘመን አገልግሎት ክፍያ ጭማሪ ላይ ከወላጆች ጋር አለመስማማታቸውን የአዲስ አበባ ትምህርት ቢሮ አሳውቋል።
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ካቢኔ በቅርቡ ባጸደቀው የግል ትምህርት አገልግሎት ክፍያ አሰራር ስርአት ደንብ ቁጥር 194/2017 መሰረት በ2018 የትምህርት ዘመን አገልግሎት ክፍያ ላይ ከ ተማሪ ወላጅና አሳዳጊዎች ጋር ካልተስማሙ መንግስታዊ ካልሆኑ የትምህርት ተቋማት ጋር ውይይት መካሄዱን የከተማው ትምህርት ቢሮ አሳውቋል።
በውይይት መርሃ ግብሩ ፦
- የትምህርት ቢሮ ሃላፊ ዘላለም ሙላቱ (ዶ/ር) ፣
- የትምህርት እና ሥልጠና ባለሥልጣን ከፍተኛ አመራሮች
- የግል ትምህርት ቤቶች አሰሪዎች ማህበር ፣
- የግል ትምህርት ቤት ባለቤቶች እና የተማሪ ወላጅ ኮሚቴ ተወካዮች እንደ ተሳተፉ ቢሮው በማህበራዊ ትስስር ገጹ ገልጿል።
ውይይቱ የተካሄደው በጭማሪው ላይ መስማማት ላይ ያልደረሱ ትምህርት ቤቶች ደንቡ በሚያስቀምጠው መሰረት ባለስልጣን መስሪያ ቤቱ ውሳኔ ያሳለፈ በመሆኑ በዚህ ጉዳይ ላይ የጋራ አስተሳሰብ ለመያዝ እንዲቻል መሆኑን ተገልጿል።
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ኃላፊ ዶክተር ዘላለም ሙላቱ "በደንቡ መሰረት 80 ፐርሰንት ያህል ትምህርት ቤቶች ከወላጆችና አሳዳጊዎች ጋር በመስማማት የአገልግሎት ክፍያ መጨመራቸው የሚበረታታ ተግባር ነው" ብለዋል።
እንደ ትምህርት ቢሮ ሃላፊው ገለጻ 20 በመቶ የሚሆኑ ትምህርት ቤቶች ከክፍያ ጭማሪ ጋር በተያያዘ ከወላጆች እና አሳዳጊዎች መስማማት ላይ አለመድረሳቸውን አመላክቷል።
የትምህርትና ስልጠናና ቁጥጥር ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር አቶ ኢዘዲን ሙስባህ "በደንቡ ላይ በመግባባት ወደ ስራ መገባቱን በዚህም መሰረት በርካታ ትምህርት ቤቶች ከወላጆች ጋር በመስማማት መጨመራቸውን ፣ መመሪያውን መሰረት በማድረግም ባለስልጣኑ በተቀሩትና መስማማት ባልቻሉት ላይ ውሳኔ መስጠቱን" አሳውቀዋል ።
ባለሥልጣኑ ምን ውሳኔ እንዳሳለፈ በዝርዝር ባይገለጽም የወላጆችን የመክፈል አቅም እና የትምህርት ተቋማቱን የግብአት አቅርቦት ታሳቢ አድርጎ ተግባራዊ የሆነ መሆኑን ስለመናገራቸው ትምህርት ቢሮው አሳውቋል።
#AddisAbabaEducationBureau
@tikvahethiopia
❤401😭57😡40🕊10🤔8😢8😱3
#AddisAbaba
ሽንኩርት ፣ ድንችና ሌሎች የአትክልት ምርቶች #ከቫት ነጻ እንደሆኑ የአዲስ አበባ ገቢዎች ቢሮ አሳውቋል።
ቢሮው " ማህበረሰቡ ዕለት በዕለት የሚሸምታቸው ያልተዘጋጁ የአትክልት ምርቶች ከተጨማሪ እሴት ታክስ ነፃ ተደርገዋል " ሲል ገልጿል።
ከሰሞኑን ለቅርንጫፍ ፅ/ቤቶች በወረደው ሰርኩላር ያልተዘጋጁ እንደ ሽንኩርት፣ ድንችና ሌሎች የአትክልት ምርቶች ከቫት ውጭ መደረጋቸውን አመላክቷል።
በሰርኩላሩ ላይ " የተጨማሪ እሴት ታክስ አዋጅ 1341/2016 አንቀፅ 10 እና አዋጅን ለማስፈፀም በወጣው ደንብ ቁጥር 570/2017 ዓ.ም መሰረት ያልተዘጋጁ እንደ ሽንኩርት፣ ድንችና ሌሎች አትክልቶች ያሉ ምርቶች ወደሀገር ውስጥ ሲገቡም ሆነ በሀገር ውስጥ ተመርተው ለግብይት ሲቀርቡ ከተጨማሪ እሴት ታክስ ነፃ መደረጋቸውን ተደንግጓል " በሚል ተቀምጧል።
በዚህም መሰረት ያልተዘጋጁ የአትክልት ምርቶች የሚያቀርቡ ግብር ከፋዮች ብቻ ከተጨማሪ እሴት ታክስ ነፃ የተደረጉ መሆናቸው ታውቆ ከሽያጭ መመዝገቢያ መሳሪያ አጠቃቀም ጋር በተያያዘ ተገቢው ክትትል በማድረግ እንዲፈፀም አዟል።
ይሁንና በአዋጁ ከታክስ ነፃ ከተደረጉ ውጪ የፍራፍሬ ምርቶች በሚያቀርቡ ግብር ከፋዮች የቫት አሰራሩ የሚቀጥል መሆኑን በመግለፅ ተገቢው ክትትል እንዲደረግ ቢሮው አሳስቧል፡፡
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
@tikvahethiopia
ሽንኩርት ፣ ድንችና ሌሎች የአትክልት ምርቶች #ከቫት ነጻ እንደሆኑ የአዲስ አበባ ገቢዎች ቢሮ አሳውቋል።
ቢሮው " ማህበረሰቡ ዕለት በዕለት የሚሸምታቸው ያልተዘጋጁ የአትክልት ምርቶች ከተጨማሪ እሴት ታክስ ነፃ ተደርገዋል " ሲል ገልጿል።
ከሰሞኑን ለቅርንጫፍ ፅ/ቤቶች በወረደው ሰርኩላር ያልተዘጋጁ እንደ ሽንኩርት፣ ድንችና ሌሎች የአትክልት ምርቶች ከቫት ውጭ መደረጋቸውን አመላክቷል።
በሰርኩላሩ ላይ " የተጨማሪ እሴት ታክስ አዋጅ 1341/2016 አንቀፅ 10 እና አዋጅን ለማስፈፀም በወጣው ደንብ ቁጥር 570/2017 ዓ.ም መሰረት ያልተዘጋጁ እንደ ሽንኩርት፣ ድንችና ሌሎች አትክልቶች ያሉ ምርቶች ወደሀገር ውስጥ ሲገቡም ሆነ በሀገር ውስጥ ተመርተው ለግብይት ሲቀርቡ ከተጨማሪ እሴት ታክስ ነፃ መደረጋቸውን ተደንግጓል " በሚል ተቀምጧል።
በዚህም መሰረት ያልተዘጋጁ የአትክልት ምርቶች የሚያቀርቡ ግብር ከፋዮች ብቻ ከተጨማሪ እሴት ታክስ ነፃ የተደረጉ መሆናቸው ታውቆ ከሽያጭ መመዝገቢያ መሳሪያ አጠቃቀም ጋር በተያያዘ ተገቢው ክትትል በማድረግ እንዲፈፀም አዟል።
ይሁንና በአዋጁ ከታክስ ነፃ ከተደረጉ ውጪ የፍራፍሬ ምርቶች በሚያቀርቡ ግብር ከፋዮች የቫት አሰራሩ የሚቀጥል መሆኑን በመግለፅ ተገቢው ክትትል እንዲደረግ ቢሮው አሳስቧል፡፡
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
@tikvahethiopia
❤1.93K🙏224👏109🤔74😡54🕊24😱20😢18🥰17😭17
#AddisAbaba
በመዲናዋ የተመረጡ የመንግሥት ተቋማት እስከ እሁድ ግማሽ ቀን ድረስ አገልግሎት ሊሰጡ ነው።
በአዲስ አበባ ከተማ በተመረጡ የከተማ አስተዳደሩ ተቋማት ላይ መደበኛ የሥራ ቀናት መራዘሙን የከተማው ፐብሊክ ሰርቪስና የሰው ሀብት ልማት ቢሮ አስታውቋል።
ቢሮው እንዳሳወቀው፥ አገልግሎት ፈላጊዎች በተመረጡ ተቋማት ከሰኞ እስከ ቅዳሜ ከጠዋቱ 2፡30 እስከ 11፡30 እና እሁድ እስከ ቀኑ 6፡30 ድረስ አገልግሎት ማግኘት እንደሚችሉ ነው የገለጸው።
አገልግሎቱም ከማዕከል መስሪያ ቤቶች ጀምሮ ክ/ከተማ እና ወረዳዎች ድረስ የሚዘልቅ መሆኑን አስታውቋል።
በተጠቀሱት ቀናት አገልግሎት የሚሰጡ ከማዕከል እስከ ወረዳ ያሉ ተቋማት የትኞቹ ናቸው ?
- ንግድ ቢሮ፣
- ገቢዎች ቢሮ፣
- መሬት ልማት አስተዳደር ቢሮ፣
- መሬት ይዞታ ምዝገባና መረጃ ኤጀንሲ፣
- ግንባታ ፍቃድ ቁጥጥር ባለስልጣን፣
- ህብረት ስራ እና የፐብሊክ ሰርቪስና የሰው ሀብት ልማት ቢሮ እና ቅርንጫፍ ፅ/ቤቶች ላይ በተጠቀሰው መሰረት አገልግሎት የሚሰጥ መሆኑን አሳውቋል።
@TikvahethMagazine @tikvahethiopia
በመዲናዋ የተመረጡ የመንግሥት ተቋማት እስከ እሁድ ግማሽ ቀን ድረስ አገልግሎት ሊሰጡ ነው።
በአዲስ አበባ ከተማ በተመረጡ የከተማ አስተዳደሩ ተቋማት ላይ መደበኛ የሥራ ቀናት መራዘሙን የከተማው ፐብሊክ ሰርቪስና የሰው ሀብት ልማት ቢሮ አስታውቋል።
ቢሮው እንዳሳወቀው፥ አገልግሎት ፈላጊዎች በተመረጡ ተቋማት ከሰኞ እስከ ቅዳሜ ከጠዋቱ 2፡30 እስከ 11፡30 እና እሁድ እስከ ቀኑ 6፡30 ድረስ አገልግሎት ማግኘት እንደሚችሉ ነው የገለጸው።
አገልግሎቱም ከማዕከል መስሪያ ቤቶች ጀምሮ ክ/ከተማ እና ወረዳዎች ድረስ የሚዘልቅ መሆኑን አስታውቋል።
በተጠቀሱት ቀናት አገልግሎት የሚሰጡ ከማዕከል እስከ ወረዳ ያሉ ተቋማት የትኞቹ ናቸው ?
- ንግድ ቢሮ፣
- ገቢዎች ቢሮ፣
- መሬት ልማት አስተዳደር ቢሮ፣
- መሬት ይዞታ ምዝገባና መረጃ ኤጀንሲ፣
- ግንባታ ፍቃድ ቁጥጥር ባለስልጣን፣
- ህብረት ስራ እና የፐብሊክ ሰርቪስና የሰው ሀብት ልማት ቢሮ እና ቅርንጫፍ ፅ/ቤቶች ላይ በተጠቀሰው መሰረት አገልግሎት የሚሰጥ መሆኑን አሳውቋል።
@TikvahethMagazine @tikvahethiopia
😡1.39K❤1.23K👏283😭124🤔44💔31🙏28🕊27😱23🥰14😢1
#AddisAbaba
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የፐብሊክ ሰርቪስና የሰው ሃብት ልማት ቢሮ የከተማዋ ካቢኔ በ4 ኛ አመት የስራ ዘመኑ በ11 ኛ መደበኛ ስብሰባው ላይ የጤና ባለሞያዎችን የጥቅማ ጥቅም ፓኬጅ በሚመለከት የተላለፈውን ውሳኔ ተግባራዊ እንዲሆን ውሳኔ አሳልፏል።
በቢሮው ሃላፊ ጀማሉ ጀንበር (ዶ/ር) ተፈርሞ ለ 11 ዱም ክፍለ ከተሞች የተላከው እና ቲክቫህ ኢትዮጵያ የተመለከተው ባለ አራት ነጥብ ደብዳቤ ከ2018 ዓ/ም በጀት አመት ጀምሮ ለጤና ባለሞያዎች ጥቅማ ጥቅሞቹ ተግባራዊ እንዲሆኑ ይጠይቃል።
በዚህም መሰረት ተግባራዊ እንዲሆኑ የተወሰኑት ጥቅማጥቅሞች :-
1. የትርፍ ሰዓት ክፍያን በሚመለከት የጤና ባለሙያዎች የትርፍ ሰዓት አገልግሎት ክፍያ አፈፃፀምን መሰረት ባደረገ እና በአገልግሎት አሰጣጥ ስታንዳርድ መሰረት ተግባራዊ እንዲሆን።
2. የጤና ባለሙያዎች፣ የትዳር አጋራቸው እና ከ18 ዓመት በታች የሆኑ ልጆቻቸው ቅድሚያ በሚሰሩበት የጤና ተቋም ፣ቀጥሎ በሌሎች የከተማ አስተዳደሩ የመንግስት ጤና ጣቢያዎች እና ሆስፒታሎች ነፃ የህክምና አገልግሎት እንዲያገኙ።
3. ከዚህ ቀደም በቀዳማዊ ልጅነት ልማት ፕሮጀክት በጊዚያዊነት የተቀጠሩ የቤት ለቤት፣ የወላጆች እና አሳዳጊዎች ምክር ሰጪ ሰራተኞች በቢሮው፣ በክፍለ ከተማ እና ጤና ጣቢያዎች ላይ የሚገኙ ሱፐርቫይዘሮች እና ኮኦርዲኔተሮች አሰራሩን ጠብቀው ቋሚ ሰራተኞች እንዲሆኑ።
4. የኑሮ ውድነቱን ጫና ለማቃለል በሁሉም የጤና ተቋማት ውስጥ የሸማቾች ህብረት ማህበራት ሱቆች በማቋቋም በመንግስት ድጎማ የሚቀርቡ ምርቶችን የጤና ባለሞያዎች በቀላሉ ማግኘት እንዲችሉ ሁኔታዎች እንዲመቻቹላቸው መወሰኑን ደብዳቤው ይገልጻል።
በመሆኑም ከላይ የተዘረዘሩት ጥቅማ ጥቅሞች ከ 2018 ዓም በጀት አመት ጀምሮ በከተማ አስተዳደሩ ስር ለሚገኙ የጤና ባለሞያዎች ተፈጻሚ እንዲሆንላቸው ለሚመለከታቸው የስራ ክፍሎች እና ሃላፊዎች መመሪያ መሰጠቱን ቲክቫህ ከደብዳቤው ተመልክቷል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvahEthiopiaFamily
@tikvahethiopia
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የፐብሊክ ሰርቪስና የሰው ሃብት ልማት ቢሮ የከተማዋ ካቢኔ በ4 ኛ አመት የስራ ዘመኑ በ11 ኛ መደበኛ ስብሰባው ላይ የጤና ባለሞያዎችን የጥቅማ ጥቅም ፓኬጅ በሚመለከት የተላለፈውን ውሳኔ ተግባራዊ እንዲሆን ውሳኔ አሳልፏል።
በቢሮው ሃላፊ ጀማሉ ጀንበር (ዶ/ር) ተፈርሞ ለ 11 ዱም ክፍለ ከተሞች የተላከው እና ቲክቫህ ኢትዮጵያ የተመለከተው ባለ አራት ነጥብ ደብዳቤ ከ2018 ዓ/ም በጀት አመት ጀምሮ ለጤና ባለሞያዎች ጥቅማ ጥቅሞቹ ተግባራዊ እንዲሆኑ ይጠይቃል።
በዚህም መሰረት ተግባራዊ እንዲሆኑ የተወሰኑት ጥቅማጥቅሞች :-
1. የትርፍ ሰዓት ክፍያን በሚመለከት የጤና ባለሙያዎች የትርፍ ሰዓት አገልግሎት ክፍያ አፈፃፀምን መሰረት ባደረገ እና በአገልግሎት አሰጣጥ ስታንዳርድ መሰረት ተግባራዊ እንዲሆን።
2. የጤና ባለሙያዎች፣ የትዳር አጋራቸው እና ከ18 ዓመት በታች የሆኑ ልጆቻቸው ቅድሚያ በሚሰሩበት የጤና ተቋም ፣ቀጥሎ በሌሎች የከተማ አስተዳደሩ የመንግስት ጤና ጣቢያዎች እና ሆስፒታሎች ነፃ የህክምና አገልግሎት እንዲያገኙ።
3. ከዚህ ቀደም በቀዳማዊ ልጅነት ልማት ፕሮጀክት በጊዚያዊነት የተቀጠሩ የቤት ለቤት፣ የወላጆች እና አሳዳጊዎች ምክር ሰጪ ሰራተኞች በቢሮው፣ በክፍለ ከተማ እና ጤና ጣቢያዎች ላይ የሚገኙ ሱፐርቫይዘሮች እና ኮኦርዲኔተሮች አሰራሩን ጠብቀው ቋሚ ሰራተኞች እንዲሆኑ።
4. የኑሮ ውድነቱን ጫና ለማቃለል በሁሉም የጤና ተቋማት ውስጥ የሸማቾች ህብረት ማህበራት ሱቆች በማቋቋም በመንግስት ድጎማ የሚቀርቡ ምርቶችን የጤና ባለሞያዎች በቀላሉ ማግኘት እንዲችሉ ሁኔታዎች እንዲመቻቹላቸው መወሰኑን ደብዳቤው ይገልጻል።
በመሆኑም ከላይ የተዘረዘሩት ጥቅማ ጥቅሞች ከ 2018 ዓም በጀት አመት ጀምሮ በከተማ አስተዳደሩ ስር ለሚገኙ የጤና ባለሞያዎች ተፈጻሚ እንዲሆንላቸው ለሚመለከታቸው የስራ ክፍሎች እና ሃላፊዎች መመሪያ መሰጠቱን ቲክቫህ ከደብዳቤው ተመልክቷል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvahEthiopiaFamily
@tikvahethiopia
❤823😡220🙏63😢25🤔22🕊9👏8😭6😱5💔5
#AddisAbaba
በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ስር ያሉ አንዳንድ የክፍለ ከተማ እና የወረዳ ጽ/ቤቶች ታጥፈዋል።
የከተማዋ የፐብሊክ ሰርቪስና የሰው ሃብት ልማት ቢሮ በ2017 በጀት አመት በከተማ አስተዳደሩ የማእከል ፣ የክፍለ ከተማ እና የወረዳ አደረጃጀቶች ውጤታማነት ላይ ጥናት ሲያካሄድ መቆየቱንና በጥናቱ መሰረት አንዳንድ አደረጃጀቶች እንዲታጠፉ መወሰኑን ውሳኔውን ለማስፈጸም ቢሮው ከጻፈው ደብዳቤ ላይ ቲክቫህ ኢትዮጵያ ለመመልከት ችሏል።
በጥናቱ መሰረትም አንዳንድ የክፍለ ከተማ እና የወረዳ አደረጃጀቶች ላይ ማሻሻያ መደረጉን አሳውቋል።
° በዚህም መሰረት በክፍለ ከተማ ደረጃ የኢኖቬሽን እና ቴክኖሎጂ ልማት ጽ/ቤት ታጥፎ በቡድን ደረጃ በዋና ስራ አስፈጻሚ ጽ/ቤት ስር እንዲደራጅ።
° የስራ አስኪያጅ ፑል እና የዋና ስራ አስፈጻሚ ሦስት አማካሪ መደቦች አደረጃጀታቸው እንዲታጠፍ።
° በወረዳ ደረጃም ስራ አስኪያጅ ጽ/ቤት ፣ መሬት ልማት እና አስተዳደር ቅ/ጽቤት ፣ባህልና ኪነጥበብ ጽ/ቤት፣ ቤቶች አስተዳደር ጽ/ቤት እና ግንባታ ፈቃድና ቁጥጥር ጽ/ቤት እንዲታጠፉና ስራው በክፍለ ከተማ ደረጃ እንዲከናወን።
° የወረዳው ጽዳት አስተዳደር ጽ/ቤት እና የከተማ ውበትና አረንጓዴ ልማት ጽ/ቤት በማዋሃድ በከተማ ውበትና አረንጓዴ ልማት ጽ/ቤት የሚከናወኑ ተግባራት በጽዳት አስተዳደር ጽ/ቤት እንዲከናወኑ እና የ ጽ/ቤቱ ስያሜ " የጽዳትና ውበት አስተዳደር ጽ/ቤት " በሚል እንዲደራጅ።
° የዋና ስራ አስፈጻሚው አማካሪ አደረጃጀት እንዲታጠፍ ተወስኗል።
ውሳኔው ከሃምሌ ወር ጀምሮ ተግባራዊ እንዲደረግ የሚያዝ ሲሆን እንዲታጠፉ ውሳኔ የተላለፈባቸው ጽ/ቤቶች እና አደረጃጀቶች መዘጋት መጀመራቸውን ቲክቫህ ኢትዮጵያ ከሰራተኞቹ ለማረጋገጥ ችሏል።
እንዲታጠፉ ውሳኔ የተላለፈባቸው ጽ/ቤቶች ተዘግተው ተገልጋዮችም ወደ ክፍለ ከተማ በመሄድ አገልግሎቱን እንዲያገኙ እየተነገራቸው ስለመሆኑ ስሜ አይጠቀስ ካሉ የግንባታ ፈቃድ እና ቁጥጥር ጽ/ቤት ባለሞያ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።
ባለሞያዋ በሌላ ክፍል ድልድል እስኪከናወንላቸው ድረስ ስራ ሳይገቡ በቤት እንዲቀመጡ የተነገራቸው መሆኑን ገልጸዋል።
በተጨማሪም " ከስራ አለመባረራችንን እና የሃምሌ ወር ደሞዝም እንደሚገባልን ተነግሮናል " ያሉ ሲሆን ድልድሉ እስኪከናወን በትዕግስት እንዲጠብቁ እንደተነገራቸው አመልክተዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ስር ያሉ አንዳንድ የክፍለ ከተማ እና የወረዳ ጽ/ቤቶች ታጥፈዋል።
የከተማዋ የፐብሊክ ሰርቪስና የሰው ሃብት ልማት ቢሮ በ2017 በጀት አመት በከተማ አስተዳደሩ የማእከል ፣ የክፍለ ከተማ እና የወረዳ አደረጃጀቶች ውጤታማነት ላይ ጥናት ሲያካሄድ መቆየቱንና በጥናቱ መሰረት አንዳንድ አደረጃጀቶች እንዲታጠፉ መወሰኑን ውሳኔውን ለማስፈጸም ቢሮው ከጻፈው ደብዳቤ ላይ ቲክቫህ ኢትዮጵያ ለመመልከት ችሏል።
በጥናቱ መሰረትም አንዳንድ የክፍለ ከተማ እና የወረዳ አደረጃጀቶች ላይ ማሻሻያ መደረጉን አሳውቋል።
° በዚህም መሰረት በክፍለ ከተማ ደረጃ የኢኖቬሽን እና ቴክኖሎጂ ልማት ጽ/ቤት ታጥፎ በቡድን ደረጃ በዋና ስራ አስፈጻሚ ጽ/ቤት ስር እንዲደራጅ።
° የስራ አስኪያጅ ፑል እና የዋና ስራ አስፈጻሚ ሦስት አማካሪ መደቦች አደረጃጀታቸው እንዲታጠፍ።
° በወረዳ ደረጃም ስራ አስኪያጅ ጽ/ቤት ፣ መሬት ልማት እና አስተዳደር ቅ/ጽቤት ፣ባህልና ኪነጥበብ ጽ/ቤት፣ ቤቶች አስተዳደር ጽ/ቤት እና ግንባታ ፈቃድና ቁጥጥር ጽ/ቤት እንዲታጠፉና ስራው በክፍለ ከተማ ደረጃ እንዲከናወን።
° የወረዳው ጽዳት አስተዳደር ጽ/ቤት እና የከተማ ውበትና አረንጓዴ ልማት ጽ/ቤት በማዋሃድ በከተማ ውበትና አረንጓዴ ልማት ጽ/ቤት የሚከናወኑ ተግባራት በጽዳት አስተዳደር ጽ/ቤት እንዲከናወኑ እና የ ጽ/ቤቱ ስያሜ " የጽዳትና ውበት አስተዳደር ጽ/ቤት " በሚል እንዲደራጅ።
° የዋና ስራ አስፈጻሚው አማካሪ አደረጃጀት እንዲታጠፍ ተወስኗል።
ውሳኔው ከሃምሌ ወር ጀምሮ ተግባራዊ እንዲደረግ የሚያዝ ሲሆን እንዲታጠፉ ውሳኔ የተላለፈባቸው ጽ/ቤቶች እና አደረጃጀቶች መዘጋት መጀመራቸውን ቲክቫህ ኢትዮጵያ ከሰራተኞቹ ለማረጋገጥ ችሏል።
እንዲታጠፉ ውሳኔ የተላለፈባቸው ጽ/ቤቶች ተዘግተው ተገልጋዮችም ወደ ክፍለ ከተማ በመሄድ አገልግሎቱን እንዲያገኙ እየተነገራቸው ስለመሆኑ ስሜ አይጠቀስ ካሉ የግንባታ ፈቃድ እና ቁጥጥር ጽ/ቤት ባለሞያ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።
ባለሞያዋ በሌላ ክፍል ድልድል እስኪከናወንላቸው ድረስ ስራ ሳይገቡ በቤት እንዲቀመጡ የተነገራቸው መሆኑን ገልጸዋል።
በተጨማሪም " ከስራ አለመባረራችንን እና የሃምሌ ወር ደሞዝም እንደሚገባልን ተነግሮናል " ያሉ ሲሆን ድልድሉ እስኪከናወን በትዕግስት እንዲጠብቁ እንደተነገራቸው አመልክተዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
❤533😡37🤔29🙏20🕊14😭13👏3😱3😢2💔1
#AddisAbaba
በዛሬው ዕለት የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የ4 ኪሎ ፕላዛን ፣ የ4 ኪሎ የገበያ ማዕከልን እና የመኪና ማቆሚያን በማስመረቅ ለአገልግሎት ክፍት አድርጓል።
ፕሮጀክቱ ምን ይዟል ?
- ከመሬት በታች የተገነቡ ዘመናዊ የሆኑ 102 የስጦታ እና የአልባሳት መደብሮች፣ ካፌዎች፣ ካፍቴሪያዎች፣ ማንበቢያ ስፍራዎች፣ ሱፐር ማርኬቶች፤
- ከ100 በላይ ተሽከርካሪዎችን በአንድ ጊዜ የሚያስተናግድ የመኪና ማቆሚያ፤
- በአንድ ጊዜ እስከ 5,000 ሰዎችን መሰብሰብ የሚያስችል የፕላዛ፣ የአንፊ ቴአትርና የተለያዩ የጥበብ ስራዎችን ማቅረቢያ ስፍራዎችን ይዟል።
የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ ወ/ሮ አዳነች አቤቤ " ፕሮጀክቱ የሲቪል ተሳትፎን፣ የባህል ዕድገትን፣ የእግር ጉዞን የሚያበረታታ፣ በዘመናዊ ቴክኖሎጂ የታገዘ፣ ሁሉንም የህብረተሰብ ክፍል በተለይም አቅመ ደካሞችና አካል ጉዳተኞችን ታሳቢ ያደረገ ነው " ብለዋል።
ፕሮጀክቱ ከ500 በላይ ለሚሆኑ ወጣቶች እና ሴቶች የስራ ዕድል መፍጠሩን አመልክተዋል።
#MayorOfficeofAA
@tikvahethiopia
በዛሬው ዕለት የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የ4 ኪሎ ፕላዛን ፣ የ4 ኪሎ የገበያ ማዕከልን እና የመኪና ማቆሚያን በማስመረቅ ለአገልግሎት ክፍት አድርጓል።
ፕሮጀክቱ ምን ይዟል ?
- ከመሬት በታች የተገነቡ ዘመናዊ የሆኑ 102 የስጦታ እና የአልባሳት መደብሮች፣ ካፌዎች፣ ካፍቴሪያዎች፣ ማንበቢያ ስፍራዎች፣ ሱፐር ማርኬቶች፤
- ከ100 በላይ ተሽከርካሪዎችን በአንድ ጊዜ የሚያስተናግድ የመኪና ማቆሚያ፤
- በአንድ ጊዜ እስከ 5,000 ሰዎችን መሰብሰብ የሚያስችል የፕላዛ፣ የአንፊ ቴአትርና የተለያዩ የጥበብ ስራዎችን ማቅረቢያ ስፍራዎችን ይዟል።
የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ ወ/ሮ አዳነች አቤቤ " ፕሮጀክቱ የሲቪል ተሳትፎን፣ የባህል ዕድገትን፣ የእግር ጉዞን የሚያበረታታ፣ በዘመናዊ ቴክኖሎጂ የታገዘ፣ ሁሉንም የህብረተሰብ ክፍል በተለይም አቅመ ደካሞችና አካል ጉዳተኞችን ታሳቢ ያደረገ ነው " ብለዋል።
ፕሮጀክቱ ከ500 በላይ ለሚሆኑ ወጣቶች እና ሴቶች የስራ ዕድል መፍጠሩን አመልክተዋል።
#MayorOfficeofAA
@tikvahethiopia
❤1.41K😡352👏96🙏29🤔22🥰21😢18🕊18💔18😱17😭3