TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
62.8K photos
1.61K videos
216 files
4.37K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

መረጃ እና መልዕክት ፦ 0919743630

ማርኬቲንግ ፦ 0979222111 ወይም
0979333111

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#AddisAbaba

ሽንኩርት ፣ ድንችና ሌሎች የአትክልት ምርቶች #ከቫት ነጻ እንደሆኑ የአዲስ አበባ ገቢዎች ቢሮ አሳውቋል።

ቢሮው " ማህበረሰቡ ዕለት በዕለት የሚሸምታቸው ያልተዘጋጁ የአትክልት ምርቶች ከተጨማሪ እሴት ታክስ ነፃ ተደርገዋል " ሲል ገልጿል።

ከሰሞኑን ለቅርንጫፍ ፅ/ቤቶች በወረደው ሰርኩላር ያልተዘጋጁ እንደ ሽንኩርት፣ ድንችና ሌሎች የአትክልት ምርቶች ከቫት ውጭ መደረጋቸውን አመላክቷል።

በሰርኩላሩ ላይ " የተጨማሪ እሴት ታክስ አዋጅ 1341/2016 አንቀፅ 10 እና አዋጅን ለማስፈፀም በወጣው ደንብ ቁጥር 570/2017 ዓ.ም መሰረት ያልተዘጋጁ እንደ ሽንኩርት፣ ድንችና ሌሎች አትክልቶች ያሉ ምርቶች ወደሀገር ውስጥ ሲገቡም ሆነ በሀገር ውስጥ ተመርተው ለግብይት ሲቀርቡ ከተጨማሪ እሴት ታክስ ነፃ መደረጋቸውን ተደንግጓል " በሚል ተቀምጧል።

በዚህም መሰረት ያልተዘጋጁ የአትክልት ምርቶች የሚያቀርቡ ግብር ከፋዮች ብቻ ከተጨማሪ እሴት ታክስ ነፃ የተደረጉ መሆናቸው ታውቆ ከሽያጭ መመዝገቢያ መሳሪያ አጠቃቀም ጋር በተያያዘ ተገቢው ክትትል በማድረግ እንዲፈፀም አዟል።

ይሁንና በአዋጁ ከታክስ ነፃ ከተደረጉ ውጪ የፍራፍሬ ምርቶች በሚያቀርቡ ግብር ከፋዮች የቫት አሰራሩ የሚቀጥል መሆኑን በመግለፅ ተገቢው ክትትል እንዲደረግ ቢሮው አሳስቧል፡፡

ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ

@tikvahethiopia
1.93K🙏224👏109🤔74😡54🕊24😱20😢18🥰17😭17