TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
62.8K photos
1.61K videos
216 files
4.37K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

መረጃ እና መልዕክት ፦ 0919743630

ማርኬቲንግ ፦ 0979222111 ወይም
0979333111

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#አዲስአበባ #አሶሳ

➡️ " በስራ ዘመን ቆይታዬ ይህን ያህል ክብደት የሚመዝን ልጅ ሲወለድ የመጀመሪያው ነው " - ዶ/ር ረታ ትዕዛዙ (ዘውዲቱ መታሰቢያ ሆስፒታል

👉 " የ3 ቀን ጨቅላ ህፃን አንገቷ ላይ በአፈጣጠር ትልቅ እብጠት ይዛ የተወለደች ቢሆንም የተሳካ ቀዶ ህክምና ተደርጎላታል አሁን በተሻለ የጤና ሁኔታ ላይ ናት " - አሶሳ አጠቃላይ ሆስፒታል


በአዲስ አበባ ዘውዲቱ መታሰቢያ ሆስፒታል ቤቴልሄም አመኑ የተባለች እናት 6 ኪሎ ግራም የሚመዝን ወንድ ልጅ በተደረገላት የቀዶ ህክምና በሰላም ተገላገለች።

የሆስፒታሉ የማህፀን ስፔሻሊስት እና የዲፓርትመንት ኃላፊ የሆኑት ዶ/ር ረታ ትዕዛዙ ለኢቢሲ በሰጡት ቃል " በስራ ዘመን ቆይታዬ ይህን ያህል ክብደት የሚመዝን ልጅ ሲወለድ የመጀመሪያው ነው " ብለዋል።

ልጆች ከ5 ኪሎ በላይ ሆነው ሲወለዱ የሚደረግላቸው ህክምና መኖሩን የገለጹት ዶ/ር " ለልጁ የህክምና ክትትል እየተደረገለት ነው " ሲሉ ተናግረዋል።

በሌላ መረጃ በአሶሳ አጠቃላይ ሆስፒታል የተሳካ ቀዶ ህክምና ተደርጓል።

የ3 ቀን ጨቅላ ህፃን አንገቷ ላይ በአፈጣጠር ትልቅ እብጠት (Bilateral huge cystic hygroma) ይዛ የተወለደች ስትሆን  በእብጠቱ ምክንያት ጡት መጥባትም ሆነ እንደ ልቧዋ መተንፈስ አትችልም ነበር።

በ13/4/17 ዓ/ም በሆስፒታሉ የተሳካ ቀዶ ህክምና ተደርጎላት አሁን በተሻለ የጤና ሁኔታ ላይ እንደምትገኝ ተገልጿል።

አሁን እንደልቧ መተንፈስ ጡት መጥባትም ጀምራለች ተብኳል።

በህክምናው ላይ የተሳተፉ ባለሞያዎች ፦
🙏 Surgeons ፦ ዶ/ር ሮቤራ ተሾመ እና ዶ/ር መብራቴ ወ/መድህን
🙏 Anaesthesiologist ፦ ዶ/ር ሲሳይ እብስቱ
🙏 Anesthesia team: ደመቀ ወ/ኪዳን፣ ተሰፋዬ አሰፋ እና ሰለሞን አዳሙ
🙏 Scrub Nurse ፦ሲ/ር ሳይሽልዋል ወርቁ (ቹቹ)
🙏 Circulator Nrs ፦ አልሃጅ ሀሰን እንደሆኑ ሆስፒታሉ አሳውቋል።


@tikvahethiopia
🙏2.01K👏380269😭79😱44🕊34🥰27😢12🤔8
TIKVAH-ETHIOPIA
መታወቂያ መስጠት መቼ ይጀመራል ? " አሁን ማጣራት ጀምረናል የገቡትን መረጃዎች፣ አሰራሮችና ማኑዋሎች ጭምር ተዘጋጅቷል " - CRRSA የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የሲቪል ምዝገባና የነዋሪዎነት አገልግሎት ኤጀንሲ ከክልል ከተሞች መሸኛ ለሚያመጡ ዜጎች የአዲስ አበባ ከተማ የነዋሪነት መታወቂያ መስጠት መቼ እንደሚጀምር ጠይቀነው የሰጠንን ምላሽ በተደጋጋሚ አድርሰናችሁ ነበር። ኤጀንሲውን ከዚህ ቀደም…
#አዲስአበባ #መታወቂያ

“ ወደ 33 ሺሕ የሚሆን መረጃ ለሰላምና ጸጥታ ልከናል በየክልሉ ተጠርቶ እንዲመጣ በአንድ ወር ውስጥ ” - CRSSA

ከክልል ከተሞች መሸኛ ይዘው ለሚመጡ ተቋርጦ የቆየው የአዲስ አበባ መታወቂያ የመስጠት አገልግሎት መቼ እንደሚጀመር ቲክቫህ ኢትዮጵያ የሲቪል ምዝገባና የነዋሪነት አገልግሎት ኤጀንሲን በተደጋጋሚ መጠየቁ ይታወሳል።

ከዚህ ቀደም አገልግሎቱ መቼ ይጀመራል? ሲል ቲክቫህ ኢትዮጵያ የጠየቀው ኤጀንሲው፣ “ በጣም ባጠረ ጊዜ ውስጥ እንጀምራለን ” የሚል መስጠቱ አይዘነጋም።

አገልግሎቱ ባለመጀመሩ በድጋሚ መቼ እንደሚጀመር ስንጠይቀውም፣ “ ነሐሴ አጋማሽ 2016 ዓ/ም የትምህርት ምዝገባው ከተጠናቀቀ በኃላ እንሰጣለን ” ነበር ያለው።

ይሁን እንጂ ከዚያ በኋላም አገልግሎቱን የመስጠት ተግባሩ ሲጓተት ቆይቷል።  

አሁንስ አገልግሎቱ ተጀመረ ?

አሁንስ ከክልል ከተሞች መሸኛ ይዘው ለሚመጡ ተገልጋዮች የመታወቂያ አገልግሎት የመስጠት ስራው ተጀመረ ? ተብሎ የተጠየቀው ኤጀንሲው አገልግሎቱ እንደተጀመረ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጿል።

የኤጀንሲው ሥራ አስፈፃሚ አቶ ዮናስ አለማየሁ ምን አሉ ?

“ አገልግሎቱ ከተጀመረ ወር ሆኖታል። በሁለት መልኩ ነው ሥራውን እየሰራን ያለነው።

አንደኛው ቀርበው ሪፓርት እንዲያደርጉ፣ የፋይዳ ቅድመ ሁኔታ አደረግን። ከተጠሩት ውስጥ ቀድመው ሪፓርት ያደረጉት በጣም ጥቂት ናቸው።

ከዚያ ባሻገር ደግሞ ለሚዲያ በተደጋጋሚ እንደገለጽነው ክልል የመጡ መሸኛዎችን መልሰን ለክልል እንልካለን ማንነታቸውን ለማረጋገጥ ብለን ነበር። 

በዚህም በዛም መልኩ እንግዲህ እኛ ጋ ሪፓርት ያደረጉ ሰዎች ቁጥር ካመለከቱት ቁጥር ጋር ሲያያዝ በጣም አንሷል መጥተው ሪፓርት ያደረጉ ማለት ነው።

እናጣራለን ስንልም ሀሰተኛ ሰነድ ላይ ያለው ሁኔታ ትንሽ ፍርሃት ፈጥሯል መሰለኝ። ወደ 33 ሺሕ የሚሆን መረጃ ለሰላምና ጸጥታ ልከናል በየክልሉ ተጠርቶ እንዲመጣ በአንድ ወር ውስጥ።

ያ ማለት ሀሰተኛ መሸኛ ይዞ መጥቶ እንዲመዘገብ አስተዋጽኦ ያደረገውን፣ ሀሰተኛ መሸኛ ያስገባውንም ሰው ወደ ወንጀል ተጠያቂነት እናመጣለን የማይቀር ነው።

ዞሮ ዞሮ አገልግሎቱ ክፍት ነው ”
ሲሉ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።

ኤጀንሲው ከ42 ሺሕ በላይ ከክልል ከተሞች መሸኛ ይዘው ወረፋ እየጠበቁ ያሉ አገልግሎት ፈላጊዎችን መረጃ አጣርቶ አገልግሎት እንደሚሰጥ ከዚህ ቀደም አስታውቆ ነበር።

(በቀጣይ ተጨማሪ መረጃ እናቀርባለን)

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia
158🙏45😡30🤔22👏13🥰8🕊7😭7😱6😢4
#እንድታውቁት #አዲስአበባ

ከነገ ጀምሮ ከፊጋ - ወደ ሳፋሪ እንዲሁም ከሳፋሪ -ወደ ፊጋ የሁለቱም አቅጠጫ መንገዶች ላልተወሰኑ ቀናት ዝግ ይሆናሉ።

የአዲስ አበባ ትራፊክ ማኔጅመንት ባለስልጣን ፤ በአዲስ አበባ ከተማ በ2ኛው ዙር ከሚለሙት የኮሪደር መስመሮች መካከል የሲሚት- ጎሮ መንገድ አንደኛው መሆኑ አስታውሷል።

ከዚሁ ጋር በተያያዘ በለሚ ኩራ ክ/ከተማ የሲ ኤም ሲ- ፔፕሲ - ጎሮ - መንገድ  ልዩ ቦታው ሳፋሪ መብራት አካባቢ ብሪቲሽ ትምህርት ቤት አጠገብ የመንገድ ቆረጣ እንደሚከናወን ገልጿል።

ከነገ ጥር 20/2017 ዓ.ም ጀምሮ ከፊጋ - ወደ ሳፋሪ እንዲሁም ከሳፋሪ -ወደ ፊጋ የሁለቱም አቅጠጫ መንገዶቹ ላልተወሰኑ ቀናት ዝግ እንደሚሆኑ አሳውቋል።

አሽከርከሪዎች ይህንኑ አውቀው አማራጭ መንገዶችን  እንዲጠቀሙ ጥሪ አስተላልፏል።

@tikvahethiopia
😡734302🙏134👏67🕊43🤔41😭38😢36😱34🥰21
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
" ጨለማን ተገን በማድረግ የተፈፀመውን የማፍረስ ድርጊት በፅኑ እናወግዛለን " - ጠቅላይ ም/ቤቱ

በአዲስ አበባ ከተማ ፤ ቂርቆስ ክፍለ ከተማ ወረዳ  10 የሚገኘው የተባረክ መስጅድ አጥር በለሊት እንዲፈርስ የተደረገበትን ድርጊት በፅኑ እንደሚያወግዝ የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት አሳቋል።

ጠቅላይ ምክር ቤቱ ፥ " ከ1967 ዓ.ል ጅምሮ ለ50 ዓመታት መንፈሳዊ አገልግሎት እየሰጠ ባለው ተባረክ መስጂድ ላይ ከህጋዊ አሰራር ውጪ የተፈፀመውን የማፍረስ ድርጊት በፅኑ እናወግዛለን " ብሏል።

የአዲስ አበባ ከተማ እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት ከሚመለከታቸው የመንግስት አካላት ጋር በመነጋገር በህጋዊ መንገድ የመስጅዱ ቅጥር እንዲታጠር ቢያደርግም ትላንት ሌሊት ጨለማን ተገን በማድረግ ከመንግስት የስራ ሰዓት ውጪ እንዲፈርስ መደረጉ ጠቅላይ ምክር ቤቱን እንዳሳዘን ገልጿል።

ይህን ተግባር የፈፀሙ አካላት በህግ አግባብ እንዲጠየቁና መስጅዱ የደረሰበት ኪሳራ ተሸፍኖ ድጋሚ እንዲታጠር ለማድረግ ጠቅላይ ምክር ቤቱ ከአዲስ አበባ ከተማ እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት ጋር በቅንጅት እንደሚሰራ አመልክቷል።

ጠቅላይ ምክር ቤቱ ፥ " መስጅዶች የሙስሊሞች ቤተ አምልኮ ብቻ ሳይሆኑ እንደ ዐይን ብሌናቸው የሚጠብቋቸው መሰባሰቢያቸውና የልብ መርጊያቸው ጭምር በመሆናቸው ተመሳሳይ ድርጊቶች እንዳይፈፀሙም በዚሁ አጋጣሚ እናሳስባለን " ብሏል።

በሌላ በኩል የተባረክ መስጅድ ኢማም ሸይኽ ሙሳ አደም ለሃሩን ሚዲያ በሰጡት ቃል ፥
" ተባረክ (ጀርመን) መስጂድ ህጋዊ ካርታ ያለው ከ1967 ጀምሮ ሲሰገድበት የቆየ ነው " ብለዋል።

" ሙስሊሙ ማህበረሰብ ባላወቀበት ሁኔታ በህጋዊ መልኩ የተሰራን የመስጂድ አጥር እና ታፔላ በውድቅት ሌሊት መጥቶ ማፍረስ  ህገወጥ ተግባር ነው " ሲሉ ገልጸዋል።

" ለሰላማችን ትልቅ አስተዋፅኦ እያበረከተ ባለ አካል በዚህ መልኩ በውድቅት ለሊት የመስጂዱን አጥር እና ታፔላ ማፍረስ በእጅጉ አሳዝኖናል " ሲሉ አክለዋል።

" አሁንም የሚመለከተው የመንግስት አካል ህዝበ ሙስሊሙ ላይ የተፈፀመውን ትልቅ በደል በመልከት የመስጂዱን አጥር እና ታፔላ ወደነበረበት እንዲመለስ የበኩላቸውን አስተዋፅኦ እንዲወጡ " ሲሉ ጥሪ አቅርበዋል።

#ተባረክመስጂድ #አዲስአበባ

@tikvahethiopia
😡1.73K👏350😭192189💔79🤔43🕊41🙏33😢19😱13🥰11