#CustomsCommission
" ትልቁ ስህተት የተፈጠረው የጉምሩክ ኮሚሽን 'በርቀትና ኤክስቴንሽን የተመረቃችሁ ተወዳዳሪዎች አትካተቱም' ማለቱ ነው " - ቅሬታ አቅራቢ አመልካቾች
➡️ " የማጣራት ሂደቶች መደረጋቸው አይቀርም። ማንኛውም የቅጥር ማስታወቂያ ሲወጣ ሁሉም የተመዘገበው ያልፋል ማለት አይደለም " - ጉምሩክ ኮሚሽን
የጉምሩክ ኮሚሽን ለሥራ ቅጥር ከ2,000 በላይ ሥራ ፈላጊዎችን ክልሎችና የከተማ አስተዳደሮች መልምለው እንዲልኩለት በሰጠው ኮታ መሠረት የተመለመሉ ከ270 በላይ አመልካቾች መስፈርቱን ካሟሉ በኋላ " ኮሚሽኑ አልተካተታችሁም' አለን " ሲሉ ቅሬታቸውን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ አቀረቡ።
ለውድድሩ በቀረቡት 14 መስፈርቶች መሠረት በየወረዳ እንደተመለመሉ የገለጹት አመልካቾቹ፣ " ትልቁ ስህተት የተፈጠረው ጉምሩክ ኮሚሽን ' በርቀትና ኤክስቴንሽን የሆናችሁ ተወዳዳሪዎች አትካተቱም ' ማለቱ ነው " ሲሉ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።
" በኮሚሽኑ የሥራ ማስታወቂያ ላይ በማንኛውም የመንግስት ዩኒቨርሲቲ ከ2014 ዓ/ም ጀምሮ የተመረቀ፣ በግል ኮሌጆች ተመርቀው ትምህርት ሚኒስቴር ያረጋገጠላቸው መወዳደር እንደሚችሉ ተጠቅሶ እያለ በዚያ መሠርት ተመለመልን ስማችን ከተላከ በኋላ እየደወሉ አትካተቱም እያሉ ነው የነገሩን " ነው ያሉት።
ጉዳዩን ሲያጣሩ፣ " በመደበኛ ፕሮግራም የተመረቁ ብቻ ለፈተና እና ቅጥር ታሳቢ እንደሚደረጉ" መረዳታቸውን ገልጸው፣ "በመንግስትም ሆነ በግል ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት በኢ-መደበኛው ፕሮግራም (በእሁድና ቅዳሜ፣ በክረምት፣ በማታና በርቀት ፕሮግራሞች) የተመረቅን እንዲሁም ሁለተኛ ዲግሪ ያጠናቀቅን (በመንግስትና በግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት) ከውድድር ውጪ ሆነናል " ሲሉ መፍትሄ እንዲሰጣቸው ጠይቀዋል።
ቅሬታውን በዝርዝር በመግለጽ ምላሽ የጠየቅናቸው የጉምሩክ ኮሚሽን የኮሚዩኒኬሽን ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ዘሪሁን አሰፋ ቅሬታ አቅራቢዎቹ ያነሱት አጠቃላይ ሂደቱ ትክክል እንደሆነ፣ ሆኖም " አልተካተትንም " ማለታቸውን በተመለከተ ግን ጉዳዩን በደንብ ማጣራት እንዳለባቸው (እሳቸው ኮሚሽኑን) የሚመለከት ምላሽ ሰጥተዋል።
" የማጣራት ሂደቶች መደረጋቸው አይቀርም። ማንኛውም የቅጥር ማስታወቂያ ሲወጣ ሁሉም የተመዘገበው ያልፋል ማለት አይደለም። ተቋሙ ያስቀመጣቸው መስፈርቶች ይኖራሉ። ያን መሠረት ተደርጎ ምልመላ ይደረጋል " ብለው፣ በመዋቅራቸው በኩል የተቀጣሪዎችን መልምለው እንዲልኩ በዋናነት ተግባሩ ለክልሎች እንደተሰጠ አስታውሰዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ፣ አመልካቾቹ፣ ለውድድር ተመልምለው የክልል ኃላፊዎች ፈርመውበት ለፌደራሉ ጉምሩክ መላኩ እንደተነገራቸው፣ ሆኖም ከኮሚሽኑ ተደውሎ " በመደበኛው ለተመረቁ ነው ቅጥሩ” እንደተባሉ ነው የገለጹት፤ አሁን ትልቁ ነገር ኮሚሽኑ ይህን አድርጓል ? ለምን ? የሚል ጥያቄ አቅርቧል።
አቶ ዘሪሁን በምላሻቸው፣ መደበኛ ባልሆኑ የትምህርት መርሃ ግብሮች ተመርቀው የተወዳደሩ ሰዎች በውድድሩ ያቀረቡትን ቅሬታ በተመለከተ መረጃ ማጣራት እንዳለባቸውና የሚመለከተውን ክፍል ጠይቀው ማብራሪያ እንደሚሰጡ ቀጠሮ ሰጥተዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
" ትልቁ ስህተት የተፈጠረው የጉምሩክ ኮሚሽን 'በርቀትና ኤክስቴንሽን የተመረቃችሁ ተወዳዳሪዎች አትካተቱም' ማለቱ ነው " - ቅሬታ አቅራቢ አመልካቾች
➡️ " የማጣራት ሂደቶች መደረጋቸው አይቀርም። ማንኛውም የቅጥር ማስታወቂያ ሲወጣ ሁሉም የተመዘገበው ያልፋል ማለት አይደለም " - ጉምሩክ ኮሚሽን
የጉምሩክ ኮሚሽን ለሥራ ቅጥር ከ2,000 በላይ ሥራ ፈላጊዎችን ክልሎችና የከተማ አስተዳደሮች መልምለው እንዲልኩለት በሰጠው ኮታ መሠረት የተመለመሉ ከ270 በላይ አመልካቾች መስፈርቱን ካሟሉ በኋላ " ኮሚሽኑ አልተካተታችሁም' አለን " ሲሉ ቅሬታቸውን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ አቀረቡ።
ለውድድሩ በቀረቡት 14 መስፈርቶች መሠረት በየወረዳ እንደተመለመሉ የገለጹት አመልካቾቹ፣ " ትልቁ ስህተት የተፈጠረው ጉምሩክ ኮሚሽን ' በርቀትና ኤክስቴንሽን የሆናችሁ ተወዳዳሪዎች አትካተቱም ' ማለቱ ነው " ሲሉ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።
" በኮሚሽኑ የሥራ ማስታወቂያ ላይ በማንኛውም የመንግስት ዩኒቨርሲቲ ከ2014 ዓ/ም ጀምሮ የተመረቀ፣ በግል ኮሌጆች ተመርቀው ትምህርት ሚኒስቴር ያረጋገጠላቸው መወዳደር እንደሚችሉ ተጠቅሶ እያለ በዚያ መሠርት ተመለመልን ስማችን ከተላከ በኋላ እየደወሉ አትካተቱም እያሉ ነው የነገሩን " ነው ያሉት።
ጉዳዩን ሲያጣሩ፣ " በመደበኛ ፕሮግራም የተመረቁ ብቻ ለፈተና እና ቅጥር ታሳቢ እንደሚደረጉ" መረዳታቸውን ገልጸው፣ "በመንግስትም ሆነ በግል ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት በኢ-መደበኛው ፕሮግራም (በእሁድና ቅዳሜ፣ በክረምት፣ በማታና በርቀት ፕሮግራሞች) የተመረቅን እንዲሁም ሁለተኛ ዲግሪ ያጠናቀቅን (በመንግስትና በግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት) ከውድድር ውጪ ሆነናል " ሲሉ መፍትሄ እንዲሰጣቸው ጠይቀዋል።
ቅሬታውን በዝርዝር በመግለጽ ምላሽ የጠየቅናቸው የጉምሩክ ኮሚሽን የኮሚዩኒኬሽን ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ዘሪሁን አሰፋ ቅሬታ አቅራቢዎቹ ያነሱት አጠቃላይ ሂደቱ ትክክል እንደሆነ፣ ሆኖም " አልተካተትንም " ማለታቸውን በተመለከተ ግን ጉዳዩን በደንብ ማጣራት እንዳለባቸው (እሳቸው ኮሚሽኑን) የሚመለከት ምላሽ ሰጥተዋል።
" የማጣራት ሂደቶች መደረጋቸው አይቀርም። ማንኛውም የቅጥር ማስታወቂያ ሲወጣ ሁሉም የተመዘገበው ያልፋል ማለት አይደለም። ተቋሙ ያስቀመጣቸው መስፈርቶች ይኖራሉ። ያን መሠረት ተደርጎ ምልመላ ይደረጋል " ብለው፣ በመዋቅራቸው በኩል የተቀጣሪዎችን መልምለው እንዲልኩ በዋናነት ተግባሩ ለክልሎች እንደተሰጠ አስታውሰዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ፣ አመልካቾቹ፣ ለውድድር ተመልምለው የክልል ኃላፊዎች ፈርመውበት ለፌደራሉ ጉምሩክ መላኩ እንደተነገራቸው፣ ሆኖም ከኮሚሽኑ ተደውሎ " በመደበኛው ለተመረቁ ነው ቅጥሩ” እንደተባሉ ነው የገለጹት፤ አሁን ትልቁ ነገር ኮሚሽኑ ይህን አድርጓል ? ለምን ? የሚል ጥያቄ አቅርቧል።
አቶ ዘሪሁን በምላሻቸው፣ መደበኛ ባልሆኑ የትምህርት መርሃ ግብሮች ተመርቀው የተወዳደሩ ሰዎች በውድድሩ ያቀረቡትን ቅሬታ በተመለከተ መረጃ ማጣራት እንዳለባቸውና የሚመለከተውን ክፍል ጠይቀው ማብራሪያ እንደሚሰጡ ቀጠሮ ሰጥተዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
❤739😡55🙏27😭23🕊21😢9🤔6💔5😱4🥰2
TIKVAH-ETHIOPIA
#CustomsCommission " ትልቁ ስህተት የተፈጠረው የጉምሩክ ኮሚሽን 'በርቀትና ኤክስቴንሽን የተመረቃችሁ ተወዳዳሪዎች አትካተቱም' ማለቱ ነው " - ቅሬታ አቅራቢ አመልካቾች ➡️ " የማጣራት ሂደቶች መደረጋቸው አይቀርም። ማንኛውም የቅጥር ማስታወቂያ ሲወጣ ሁሉም የተመዘገበው ያልፋል ማለት አይደለም " - ጉምሩክ ኮሚሽን የጉምሩክ ኮሚሽን ለሥራ ቅጥር ከ2,000 በላይ ሥራ ፈላጊዎችን ክልሎችና…
#Update
#CustomsCommission
" ኮሚሽኑ በመደበኛው የትምህርት መርሃ ግብር የተማሩትን አመልካቾች ብቻ ወደ ቀጣዩ የቅጥር ሂደት መግባት የሚችሉብትን ሁኔታ ውሳኔ አሳልፏል " - ጉምሩክ ኮሚሽን
የጉምሩክ ኮሚሽን ባወጣው የቅጥር ማስታወቂያ ከ200ዐ በላይ ተወዳዳሪዎችን እንዲመለምሉ ለክልሎች እና የከተማ አስተዳደሮች በሰጠው ኮታ መሰረት የተመለመሉ አመልካቾች ዝርዝር ከተላከለት በኋላ በኢ-መደበኛው መርሃ ግብር የተመረቅነውን " ኮሚሽኑ በቅጥሩ 'አትካተቱም' አለን " የሚል ቅሬታ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ አቅርበው ነው።
ይህ ቅሬታ ያላቸው የተሰባሰቡት ብቻ ወደ 300 እንደሆኑ የገለጹ ሲሆን፣ ለምን ይህን እንዳደረገ ከቲክቫህ ኢትዮጵያ ጥያቄ የቀረበለት ጉምሩክ ኮሚሽን ጉዳዩን አጣርቶ ምላሽ ሊሰጥ ቀጠሮ ሰጥቶን ነበር፡፡
ኮሚሽኑ ለቀረበበት ቅሬታ ምን መለሰ ?
የኮሚሽኑ የኮሚዩኒኬሽን ዳሬክተር አቶ ዘሪሁን አሰፋ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ፣ " ኮሚሽኑ በመደበኛው የትምህርት መርሃ ግብር የተማሩት አመልካቾች ብቻ ወደ ቀጣዩ የቅጥር ሂደት መግባት የሚችሉበትን ሁኔታ ውሳኔ አሳልፏል። በመደበኛው የትምህርት መርሃ ግብር ትምህርታቸውን ያጠናቀቁ ናቸው በዚህኛው ቅጥር የተጋበዙት " ብለዋል።
ማስታወቂያው የመንግስት ዩኒቨርሲቲ፣ በግል ኮሌጆች ተመርቀው ትምህርት ሚኒስቴር ያረጋገጠላቸው ምሩቃን መወዳዳር እደሚችሉ በሚገልጸው መሰረት ካመለከቱ በኋላ " አትካተቱም " እንደተባሉና አሰራሩ ልክ እንዳልሆነ ነው አመልካቾቹ የገለጹት፤ ለዚህ ያላችሁ ምላሽ ምንድን ነው ? ስንል አቶ ዘሪሁንን ጠይቀናቸዋል፡፡
እሳቸውም፣ " ማስታወቂያ ላይ ዝርዝር ጉዳዮች ላይጠቀሱ ይችላሉ " ብለው፣ " ሌሎችን ዲቴይል መስፈርቶችን ኮሚሽኑ በኋላ ላይ ማጣራት አድርጎ ሁሉም ተመሳሳይ አካባቢ በመደበኛና ኤክስቴሽን የተማሩትን፣ ሌሎችን ደግሞ በሌላ መስፈርት ሳይሆን ለሁሉም ወጥ የሆነ ውሳኔ ነው የወሰነው " ብለዋል፡፡
ቲክቫህ ኢትዮጵያም ማስታውቂያው ወጥቶ ተወዳዳሪዎች ካመለከቱ በኋላ ኮሚሽኑ ይህን መወሰኑ ለምንድን ነው ? የገጠማችሁ ችግር ምንድን ነው ? በኢ-መደበኛው መርሃ ግብር የተመረቁት በቅጥሩ የማይካተቱ ከሆነስ ለምን ቀድማችሁ አላሳወቃችሁም ? የሚል ተጨማሪ ጥያቄ አቅርቧል፡፡
አቶ ዘሪሁን፣ " ኮሚሽኑ በኋላ ላይ አጠቃለይ የምልመላ ሂደት ይህን ብቻ ሳይሆን ሌሎች የማጣራት ሂደቶችን አድርጎ ካሉ ዝርዝሮች ውስጥ እነዚህ ወደቀጣዩ ዙር የምልመላ ሂደት ይለፉ ብሎ የወሰነው ወደ ቀጣይ ዙርም የተገባበት ሁኔታ አለ፡፡ ይህን ነው ልገልጽ የምችለው " ሲሉ አስረድተዋል።
ፕሮግራሙ ቢለያይም በሀገሪቱ ተመሳሳይ ይዘት ያለው ትምህርት ነው የሚሰጠው ስለዚህ መደበኛውን ብቻ ለይቶ ለመቅጠር ህጉ ይፈቅዳል ? ሁሉንም ምሩቃን ማካተት አልነበረባችሁም ? ለሚለው ጥያቄም፤ " ኮሚሽኑ ያስቀመጠው አሰራር ነው፡፡ መደበኛዎቹን ነው በዚህ የቅጥር ሂደት ውስጥ የማካትተው የሚል መስፈርት ወጥቶ ውሳኔ ተሰጥቶበት እየተሰራ ያለ ጉዳይ ነው " የሚል ምላሽ ተሰጥቷል፡፡
በሌላ በኩል፣ በክልሎች በኩል የነበረው የምልመላ ሂደት " በቢሮዎች ዘመድ ላላቸው ቅድሚያ እየተሰጠ ዘመድ የሌላቸው ከመንከራተታቸውም በላይ እድሉን እንዳላገኙ "፣ በአዲስ አበባ ያለው ምልመላም ኦፊሻል ወጥቶ እንዳልተመለከቱ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ቅሬታ ያደረሱ እንዳሉ በመግለጽ፤ ለዚሁ ቅሬታ ጉምሩክ ኮሚሽንን ምላሽ ጠይቀናል፡፡
አቶ ዘሪሁን " ቅሬታዎች የሉም ማለት አይደለም፤ እኛ ጋርም የመጡ ቅሬታዎች ነበሩ፤ ከተቀመጠው መስፈርት አንጻርም ይሁን በግለሰብ 'በዚህ ቀን ተመዝግበን፤ እኔ ማለፍ ሲገባኝ እከሌ/እከሊት ያላግባብ አልፋለች/ፏል' የሚል ቅሬታ አለ " ብለው፤ ፍትሃዊ እንዲሆን ጉዳዩን ወደ ክልል መልሶ ኮሚሽኑ ማጣራት እያደረገ ምላሽ እየሰጠ መሆኑን ተናግረዋል፡፡
ቅሬታ ያላቸው በክልል በኩል አጽፈው ቅሬታቸውን ቢያቀርቡ ኮሚሽኑ አጣርቶ ማስተካከያ የማያደርግበት ምክንያት እንደማይኖር፣ በዚሁ መሰረትም ምላሽ የተሰጣቸውና በሂደት ላይ ያሉም እንዳሉ ገልጸዋል፡፡
የአዲስ አበባውን ቅሬታ በተመለከተ በሰጡት ምላሽ አመልካቾች ተመልምለው እንደተላኩላቸው ተናግረው፣ " አይደለም አዲስ አበባ በሁሉም ወረዳዎች ተደራሽ መደረጉን ኮሚሽኑ ክትትል ሲያደርግ ነበር " ብለዋል፡፡
በዚህ የቅጥር ማስታወቂያ መሰረት ኮሚሽኑ የሚፈገውን ያህል የሰው ኃይል እንዳገኘና አመልካቾቹ በቀጣይ ስልጠና ወስደው ወደ ስራ የሚገቡበት እንቅስቃሴ እየተደረገ መሆኑን የገለጹት አቶ ዘሪሁን፣ በአጠቃላይ ምን ያክል ሰዎች አመልክተው እንደነበር ስንጠይቃቸው ለጊዜው ዳታውን እንዳልያዙና መግለጹ አስፈላጊ እንዳልሆነ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል፡፡
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
#CustomsCommission
" ኮሚሽኑ በመደበኛው የትምህርት መርሃ ግብር የተማሩትን አመልካቾች ብቻ ወደ ቀጣዩ የቅጥር ሂደት መግባት የሚችሉብትን ሁኔታ ውሳኔ አሳልፏል " - ጉምሩክ ኮሚሽን
የጉምሩክ ኮሚሽን ባወጣው የቅጥር ማስታወቂያ ከ200ዐ በላይ ተወዳዳሪዎችን እንዲመለምሉ ለክልሎች እና የከተማ አስተዳደሮች በሰጠው ኮታ መሰረት የተመለመሉ አመልካቾች ዝርዝር ከተላከለት በኋላ በኢ-መደበኛው መርሃ ግብር የተመረቅነውን " ኮሚሽኑ በቅጥሩ 'አትካተቱም' አለን " የሚል ቅሬታ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ አቅርበው ነው።
ይህ ቅሬታ ያላቸው የተሰባሰቡት ብቻ ወደ 300 እንደሆኑ የገለጹ ሲሆን፣ ለምን ይህን እንዳደረገ ከቲክቫህ ኢትዮጵያ ጥያቄ የቀረበለት ጉምሩክ ኮሚሽን ጉዳዩን አጣርቶ ምላሽ ሊሰጥ ቀጠሮ ሰጥቶን ነበር፡፡
ኮሚሽኑ ለቀረበበት ቅሬታ ምን መለሰ ?
የኮሚሽኑ የኮሚዩኒኬሽን ዳሬክተር አቶ ዘሪሁን አሰፋ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ፣ " ኮሚሽኑ በመደበኛው የትምህርት መርሃ ግብር የተማሩት አመልካቾች ብቻ ወደ ቀጣዩ የቅጥር ሂደት መግባት የሚችሉበትን ሁኔታ ውሳኔ አሳልፏል። በመደበኛው የትምህርት መርሃ ግብር ትምህርታቸውን ያጠናቀቁ ናቸው በዚህኛው ቅጥር የተጋበዙት " ብለዋል።
ማስታወቂያው የመንግስት ዩኒቨርሲቲ፣ በግል ኮሌጆች ተመርቀው ትምህርት ሚኒስቴር ያረጋገጠላቸው ምሩቃን መወዳዳር እደሚችሉ በሚገልጸው መሰረት ካመለከቱ በኋላ " አትካተቱም " እንደተባሉና አሰራሩ ልክ እንዳልሆነ ነው አመልካቾቹ የገለጹት፤ ለዚህ ያላችሁ ምላሽ ምንድን ነው ? ስንል አቶ ዘሪሁንን ጠይቀናቸዋል፡፡
እሳቸውም፣ " ማስታወቂያ ላይ ዝርዝር ጉዳዮች ላይጠቀሱ ይችላሉ " ብለው፣ " ሌሎችን ዲቴይል መስፈርቶችን ኮሚሽኑ በኋላ ላይ ማጣራት አድርጎ ሁሉም ተመሳሳይ አካባቢ በመደበኛና ኤክስቴሽን የተማሩትን፣ ሌሎችን ደግሞ በሌላ መስፈርት ሳይሆን ለሁሉም ወጥ የሆነ ውሳኔ ነው የወሰነው " ብለዋል፡፡
ቲክቫህ ኢትዮጵያም ማስታውቂያው ወጥቶ ተወዳዳሪዎች ካመለከቱ በኋላ ኮሚሽኑ ይህን መወሰኑ ለምንድን ነው ? የገጠማችሁ ችግር ምንድን ነው ? በኢ-መደበኛው መርሃ ግብር የተመረቁት በቅጥሩ የማይካተቱ ከሆነስ ለምን ቀድማችሁ አላሳወቃችሁም ? የሚል ተጨማሪ ጥያቄ አቅርቧል፡፡
አቶ ዘሪሁን፣ " ኮሚሽኑ በኋላ ላይ አጠቃለይ የምልመላ ሂደት ይህን ብቻ ሳይሆን ሌሎች የማጣራት ሂደቶችን አድርጎ ካሉ ዝርዝሮች ውስጥ እነዚህ ወደቀጣዩ ዙር የምልመላ ሂደት ይለፉ ብሎ የወሰነው ወደ ቀጣይ ዙርም የተገባበት ሁኔታ አለ፡፡ ይህን ነው ልገልጽ የምችለው " ሲሉ አስረድተዋል።
ፕሮግራሙ ቢለያይም በሀገሪቱ ተመሳሳይ ይዘት ያለው ትምህርት ነው የሚሰጠው ስለዚህ መደበኛውን ብቻ ለይቶ ለመቅጠር ህጉ ይፈቅዳል ? ሁሉንም ምሩቃን ማካተት አልነበረባችሁም ? ለሚለው ጥያቄም፤ " ኮሚሽኑ ያስቀመጠው አሰራር ነው፡፡ መደበኛዎቹን ነው በዚህ የቅጥር ሂደት ውስጥ የማካትተው የሚል መስፈርት ወጥቶ ውሳኔ ተሰጥቶበት እየተሰራ ያለ ጉዳይ ነው " የሚል ምላሽ ተሰጥቷል፡፡
በሌላ በኩል፣ በክልሎች በኩል የነበረው የምልመላ ሂደት " በቢሮዎች ዘመድ ላላቸው ቅድሚያ እየተሰጠ ዘመድ የሌላቸው ከመንከራተታቸውም በላይ እድሉን እንዳላገኙ "፣ በአዲስ አበባ ያለው ምልመላም ኦፊሻል ወጥቶ እንዳልተመለከቱ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ቅሬታ ያደረሱ እንዳሉ በመግለጽ፤ ለዚሁ ቅሬታ ጉምሩክ ኮሚሽንን ምላሽ ጠይቀናል፡፡
አቶ ዘሪሁን " ቅሬታዎች የሉም ማለት አይደለም፤ እኛ ጋርም የመጡ ቅሬታዎች ነበሩ፤ ከተቀመጠው መስፈርት አንጻርም ይሁን በግለሰብ 'በዚህ ቀን ተመዝግበን፤ እኔ ማለፍ ሲገባኝ እከሌ/እከሊት ያላግባብ አልፋለች/ፏል' የሚል ቅሬታ አለ " ብለው፤ ፍትሃዊ እንዲሆን ጉዳዩን ወደ ክልል መልሶ ኮሚሽኑ ማጣራት እያደረገ ምላሽ እየሰጠ መሆኑን ተናግረዋል፡፡
ቅሬታ ያላቸው በክልል በኩል አጽፈው ቅሬታቸውን ቢያቀርቡ ኮሚሽኑ አጣርቶ ማስተካከያ የማያደርግበት ምክንያት እንደማይኖር፣ በዚሁ መሰረትም ምላሽ የተሰጣቸውና በሂደት ላይ ያሉም እንዳሉ ገልጸዋል፡፡
የአዲስ አበባውን ቅሬታ በተመለከተ በሰጡት ምላሽ አመልካቾች ተመልምለው እንደተላኩላቸው ተናግረው፣ " አይደለም አዲስ አበባ በሁሉም ወረዳዎች ተደራሽ መደረጉን ኮሚሽኑ ክትትል ሲያደርግ ነበር " ብለዋል፡፡
በዚህ የቅጥር ማስታወቂያ መሰረት ኮሚሽኑ የሚፈገውን ያህል የሰው ኃይል እንዳገኘና አመልካቾቹ በቀጣይ ስልጠና ወስደው ወደ ስራ የሚገቡበት እንቅስቃሴ እየተደረገ መሆኑን የገለጹት አቶ ዘሪሁን፣ በአጠቃላይ ምን ያክል ሰዎች አመልክተው እንደነበር ስንጠይቃቸው ለጊዜው ዳታውን እንዳልያዙና መግለጹ አስፈላጊ እንዳልሆነ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል፡፡
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
❤1.17K😡172😭61🙏46💔37🤔21👏17😢14🕊13🥰12😱7