TIKVAH-ETHIOPIA
" የሟቾች ቁጥር ከ8 ወደ 11 ከፍ ብሏል " - ኢስፔክተር ተስፋዬ ደምሴ ወደ ሐዋሳ ጉዞውን እያደረገ በነበረ ተሽከርካሪ ላይ በደረሰው አደጋ የሟቾች ቁጥር 11 መድረሱን የሐዋሳ ከተማ ፖሊስ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጿል። ትላንት ማምሻውን መነሻውን ከአርባ ምንጭ አድርጎ ወዘ ሐዋሳ እያመራ የነበረ ተሽከርካሪ በዎላይታ ዞን በዱጉና ፋንጎ ወረዳ ፋንጎ ኮይሻ ቀበሌ ልዩ ቦታው " ዞንጋ " በተባለው ቦታ አስከፊ…
#ሀዋሳ🕯
በቅርቡ ከአርባ ምንጭ ወደ ሐዋሳ ሲመለሱ በዎላይታ ዞን ውስጥ በመኪና አደጋ ህይወታቸዉ ላለፈ የሐዋሳ ከተማ ወጣቶች የሻማ ማብራትና የገቢ ማሰባሰቢያ ፕሮግራም በከተማ ደረጃ ከንቲባዉ በተገኙበት ተካሄደ።
በድንገተኛ የመኪና አደጋ ህይዎታቸዉ ያለፉ የጤና ቡድን አባላትን ለመዘከር ያለመ የሻማ ማብራትና የገቢ ማሰባሰቢያ ፕሮግራም የተጎጅ ቤተሰቦች ፣ የሀዋሳ ከተማ ከንቲባ የሀይማኖት አባቶች ፣ የሲዳማ ባህል ሽማግሌዎች በተገኙበት ተካሂዷል።
በሻማ ማብራት ፕሮግራሙ ላይ ንግግር ያደረጉት የሀዋሳ ከተማ ከንቲባ አቶ መኩሪያዬ መርሻዬ ፤ " እንደሀዋሳ ብቻ ሳይሆን እንደሀገር አልቅሰናል " ብለዋል።
ከዚህ አይነት አስከፊ የትራፊክ አደጋ ለመዉጣት ጥንቃቄ ብቻ ሳይሆን ጸሎትም ያስፈልገናል ሲሉ ገልጸዋል።
የተጎጅ ቤተሰቦችን ለመደገፍ ለተሰናዳዉ ፕሮግራም በከንቲባዉ ቢሮ 3 መቶ ሺህ ብር እንዲሁም በግላቸዉ 10 ሽህ ብር በማበርከት ድጋፉን አስጀምረዋል።
ፕሮግራሙን ለመካፈል ተደግፎ የመጣዉና ከአደጋዉ የተረፈዉ ወጣት ፋሲል በበኩሉ ሀዘኑን መቋቋም ከባድ መሆኑን በመግለጽ በእንባ ታጆቦ ወደቦታዉ ተመልሷል።
በእለቱ ከሁለት ሚሊየን ብር በላይ በጎፈንድሚና ለዚህዉ ተብሎ በተከፈተዉ የባንክ አካዉንት መሰብሰብ ተችሏል።
የገቢ ማሰባሰቢያ ፕሮግራሙን ያዘጋጀዉ ኮሚቴ " በድንገት ያጣናቸዉ ጓደኞቻችን ልጆችና ቤተሰቦች ለመርዳት ሁሉም ወጣት ድጋፍ እንዲያደርግ " ሲል ጠይቋል።
ለዚህ ሲባል የተከፈተዉ የባንክ አካዉንት ቁጥር 1000610475667 መሆኑን ገልጿል።
መረጃውን አዘጋጅቶ የላከው የሀዋሳው የቲክቫህ ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባል ነው።
@tikvahethiopia
በቅርቡ ከአርባ ምንጭ ወደ ሐዋሳ ሲመለሱ በዎላይታ ዞን ውስጥ በመኪና አደጋ ህይወታቸዉ ላለፈ የሐዋሳ ከተማ ወጣቶች የሻማ ማብራትና የገቢ ማሰባሰቢያ ፕሮግራም በከተማ ደረጃ ከንቲባዉ በተገኙበት ተካሄደ።
በድንገተኛ የመኪና አደጋ ህይዎታቸዉ ያለፉ የጤና ቡድን አባላትን ለመዘከር ያለመ የሻማ ማብራትና የገቢ ማሰባሰቢያ ፕሮግራም የተጎጅ ቤተሰቦች ፣ የሀዋሳ ከተማ ከንቲባ የሀይማኖት አባቶች ፣ የሲዳማ ባህል ሽማግሌዎች በተገኙበት ተካሂዷል።
በሻማ ማብራት ፕሮግራሙ ላይ ንግግር ያደረጉት የሀዋሳ ከተማ ከንቲባ አቶ መኩሪያዬ መርሻዬ ፤ " እንደሀዋሳ ብቻ ሳይሆን እንደሀገር አልቅሰናል " ብለዋል።
ከዚህ አይነት አስከፊ የትራፊክ አደጋ ለመዉጣት ጥንቃቄ ብቻ ሳይሆን ጸሎትም ያስፈልገናል ሲሉ ገልጸዋል።
የተጎጅ ቤተሰቦችን ለመደገፍ ለተሰናዳዉ ፕሮግራም በከንቲባዉ ቢሮ 3 መቶ ሺህ ብር እንዲሁም በግላቸዉ 10 ሽህ ብር በማበርከት ድጋፉን አስጀምረዋል።
ፕሮግራሙን ለመካፈል ተደግፎ የመጣዉና ከአደጋዉ የተረፈዉ ወጣት ፋሲል በበኩሉ ሀዘኑን መቋቋም ከባድ መሆኑን በመግለጽ በእንባ ታጆቦ ወደቦታዉ ተመልሷል።
በእለቱ ከሁለት ሚሊየን ብር በላይ በጎፈንድሚና ለዚህዉ ተብሎ በተከፈተዉ የባንክ አካዉንት መሰብሰብ ተችሏል።
የገቢ ማሰባሰቢያ ፕሮግራሙን ያዘጋጀዉ ኮሚቴ " በድንገት ያጣናቸዉ ጓደኞቻችን ልጆችና ቤተሰቦች ለመርዳት ሁሉም ወጣት ድጋፍ እንዲያደርግ " ሲል ጠይቋል።
ለዚህ ሲባል የተከፈተዉ የባንክ አካዉንት ቁጥር 1000610475667 መሆኑን ገልጿል።
መረጃውን አዘጋጅቶ የላከው የሀዋሳው የቲክቫህ ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባል ነው።
@tikvahethiopia
😭678❤132🙏52😢46🕊36🥰10👏7😱6😡3
TIKVAH-ETHIOPIA
#ሀዋሳ " ... በነዳጅ እጥረት ስራችንን መስራት አልቻልንም። ተሰልፈን ነው የምንውለው " - አሽከርካሪዎች " ባለፉት ሁለት ሳምንታት ከጅቡቲ የሚመጣው ነዳጅ መዘግየቱን ተከትሎ ነው ችግር የተፈጠረው " - የከተማው ገበያ ልማት በሀዋሳ ከተማ የነበረዉ ከፍተኛ የነዳጅ እጥረትና ሰልፍ ተስተካከለ ተብሎ ጥቂት ጊዜያት ሳይቆይ ድንገት ችግሩ ማገርሸቱን ተከትሎ መጨረሻ የሌላቸው የሚመስሉ ሰልፎች በየማደያዉ…
#ሀዋሳ
በሀዋሳ ከተማ የህዝብ ትንራንስፖርት አገልግሎት (ታክሲ) የሚሰጡ አሽከርካሪዎች ፤ " የነዳጅ ጉዳይ ስቃያችንን አበላን ፤ የመፍትሄ ያለህ !! " ሲሉ ድምፃቸውን አሰምተዋል።
ቃላቸውን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ የሰጡ የታክሲ አገልግሎት ሰጪ አሽከርካሪዎች ፤ "ሰርተን ከምንገባበት ለነዳጅ ሰልፍ ቆመን የምንውለበት እየበለጠ ነው " ብለዋል።
የነዳጅ ችግሩ ረጅም ጊዜ ያስቆጠረ ዛሬም ድረስ የቀጠለ ነው ሲሉ አስገንዝበዋል።
የቤተሰብ አስተዳዳሪ እንደሆኑም በመግለፅ "
ካልሰራን ልጆቻን ምን ይብሉ ? ፤ እኛስ ምን በልተን እንደር ? ይህ ጉዳይ መፍትሄ ይፈልጋል " ብለዋል።
ከሳምንታት በፊት በዚሁ በሀዋሳ ከተማ ያሉ አሽከርካሪዎች ፤ " በረዣዥም ሰልፍችና በነዳጅ እጥረት ሳቢያ ስራችን በአግባቡ መስራት አልቻልንም " በሚል ምሬታቸውን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ አሰምተው ነበር።
አሽከርካሪዎች ፤ ሁሉም ማደያዎች በአግባቡ አለመስራትና ከአገልግሎት ውጭ የሆኑ መኪኖች ለነዳጅ ሰልፍ ተገፍተዉ ከመግባት ባለፈ ከፍተኛ መጠን ያለዉ ሳልቫቲዮ ገጥመዉ መምጣታቸው ቀኑን ሙሉ ተሰልፈዉ እንኳን መቅዳት እንዳይችሉ ምክኒያት እንደሆነባቸው ገልጸው ነበር።
በወቅቱ እየተነሳ ላለው ቅሬታ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ምላሽ የሰጡት የሀዋሳ ከተማ ገበያ ልማት ቢሮ የስነልኬት ባለሙያው አቶ ሀብታሙ መኮንን ፤ ችግሩ መኖሩን አምነው ፤ ከጅቡቲ የሚመጣው ነዳጅ መዘግየቱን ተከትሎ የተፈጠረው ክፍተት ለችግሩ ምክንያት እንደሆነ ገልጸው ነበር።
ችግሩም " #ወደፊት_ይቀረፋል " የሚል ተስፋ እንዳላቸዉ ማመልከታቸው ይታወሳል።
@tikvahethiopia
በሀዋሳ ከተማ የህዝብ ትንራንስፖርት አገልግሎት (ታክሲ) የሚሰጡ አሽከርካሪዎች ፤ " የነዳጅ ጉዳይ ስቃያችንን አበላን ፤ የመፍትሄ ያለህ !! " ሲሉ ድምፃቸውን አሰምተዋል።
ቃላቸውን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ የሰጡ የታክሲ አገልግሎት ሰጪ አሽከርካሪዎች ፤ "ሰርተን ከምንገባበት ለነዳጅ ሰልፍ ቆመን የምንውለበት እየበለጠ ነው " ብለዋል።
የነዳጅ ችግሩ ረጅም ጊዜ ያስቆጠረ ዛሬም ድረስ የቀጠለ ነው ሲሉ አስገንዝበዋል።
የቤተሰብ አስተዳዳሪ እንደሆኑም በመግለፅ "
ካልሰራን ልጆቻን ምን ይብሉ ? ፤ እኛስ ምን በልተን እንደር ? ይህ ጉዳይ መፍትሄ ይፈልጋል " ብለዋል።
ከሳምንታት በፊት በዚሁ በሀዋሳ ከተማ ያሉ አሽከርካሪዎች ፤ " በረዣዥም ሰልፍችና በነዳጅ እጥረት ሳቢያ ስራችን በአግባቡ መስራት አልቻልንም " በሚል ምሬታቸውን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ አሰምተው ነበር።
አሽከርካሪዎች ፤ ሁሉም ማደያዎች በአግባቡ አለመስራትና ከአገልግሎት ውጭ የሆኑ መኪኖች ለነዳጅ ሰልፍ ተገፍተዉ ከመግባት ባለፈ ከፍተኛ መጠን ያለዉ ሳልቫቲዮ ገጥመዉ መምጣታቸው ቀኑን ሙሉ ተሰልፈዉ እንኳን መቅዳት እንዳይችሉ ምክኒያት እንደሆነባቸው ገልጸው ነበር።
በወቅቱ እየተነሳ ላለው ቅሬታ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ምላሽ የሰጡት የሀዋሳ ከተማ ገበያ ልማት ቢሮ የስነልኬት ባለሙያው አቶ ሀብታሙ መኮንን ፤ ችግሩ መኖሩን አምነው ፤ ከጅቡቲ የሚመጣው ነዳጅ መዘግየቱን ተከትሎ የተፈጠረው ክፍተት ለችግሩ ምክንያት እንደሆነ ገልጸው ነበር።
ችግሩም " #ወደፊት_ይቀረፋል " የሚል ተስፋ እንዳላቸዉ ማመልከታቸው ይታወሳል።
@tikvahethiopia
😢247❤86🙏30😭19🕊17😱13😡13🥰9👏7
#እንድታውቁት #ሀዋሳ #ክልከላ
በሀዋሳ ከተማ ከምሽቱ 3 ሰአት በኋላ ባለ ሦሰት እግር ተሽከርካሪ (ባጃጅ) እና የሁለት እግር ሞተር ሳይክል ማሽከርከር #ተከለከለ።
ሰሞኑን በሀዋሳ ከመዝናኛ መልስ እየደረሰ ያለውን የመንገድ ላይ የትራፊክ አደጋን ለመከላከል ሲባል ከምሽቱ 3:00 በኃላ ባለሦሰት እግር ተሽከርካሪ (ባጃጅ) እና ባለ ሁለት እግር ሞተር ሳይክል ማሽከርከር የተከለከለ መሆኑን የሀዋሳ ከተማ ትራፊክ ፖሊስ አስተባባሪው ኢንስፔክተር ተስፋዬ ደምሴ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ላይ አሳውቀዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያም ፦
° ምክንያት ?
° ክልከላው ለምን አስፈለገ ?
° በማህበረሰቡ የእለት ተእለት ህይወትስ ላይ የሚያሳድረዉ ጫና አይኖርም ? ወይ ስንል ኢንስፔክተሩን ጠይቋል።
ቃላቸውን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ የሰጡት ኢንስፔክተር ተስፋዬ ፤ " ሁሉንም ያደረግነው ለማህበረሰቡ ደህንነት ነው " ብለዋል።
" አሁን ላይ በሀዋሳ ከተማ ከፍተኛ የትራፊክ አደጋ እየተስተዋለ ነው " ሲሉ ገልጸው ከአደጋዎቹ አብዛኛዉ በባለሦሰት እግር ባጃጅና በባለሁለት እግር ሞተር ሳይክል የሚደርስ እንደሆነ አስረድተዋል።
" በዚህ አመት ብቻ በምሽት በሞተር ሳይክል የደረሰዉ አደጋ የሚያስገርም ቁጥር ያለው ነው " ያሉት ኢስፓክተር ተስፋዬ በቁጥር ስንት ? የሚለውን ወደፊት ዳታውን አጠናቅረዉ ለማህበረሰቡ የማሳየት እቅድ እንዳለቸዉ ጠቁመዋል።
ከአደጋዎቹ ውስጥ በአብዛኛው የሚከሰቱት በምሽት መሆኑን ጠቅሰው ፤ " ጠጥቶ ሞተር ሳይክል ማሽከርከር ትልቁ ምክኒያት ሆኖ ተገኝቷል። በተለይም በመንግስት ሞተር ሳይክሎች ሳይቀር ሶስትና ከዚያ በላይ ሆኖ መንቀሳቀስ አደጋ እየፈጠረ ነው ይህን ችግር ለመቀነስ ሲባል #ክልከላው ወጥቷል " ሲሉ ተናግረዋል።
በተጨማሪም ፤ " የባለ ሶስት እግር ተሽከርካሪዎች ከፍተኛ የወንጀል መፈጸሚያ እየሆኑ ነው " ያሉት ኢንስፔክተሩ ፤ " ለአብነት ኮንትራት ተብለዉ በሚንቀሳቀሱ አሽከርካሪዎች ላይ የሚደርሰው አደጋ እና የሌሎችም ወንጀሎች ምንጭ ሆነው ተገኝተዋል " ብለዋል።
" ጥንቃቄ ለራስ በመሆኑ ማህበረሰቡ ለራሱ ሲባል የወጣዉን ክልከላ አክብሮ እንዲንቀሳቀስ " ሲሉ አሳስበዋል።
" እለት ተእለት የሚከሰተው ዘግናኝ የትራፊክ አደጋ እንዲቆም የሁላችንም ትብብር ያስፈልጋል " ብለዋል።
ክልከላው የሚያበቃበትን ጊዜን በተመለከተ ምንም የተባለ ነገር የለም።
#TikvahEthiopiaFamilyHawassa
@tikvahethiopia
በሀዋሳ ከተማ ከምሽቱ 3 ሰአት በኋላ ባለ ሦሰት እግር ተሽከርካሪ (ባጃጅ) እና የሁለት እግር ሞተር ሳይክል ማሽከርከር #ተከለከለ።
ሰሞኑን በሀዋሳ ከመዝናኛ መልስ እየደረሰ ያለውን የመንገድ ላይ የትራፊክ አደጋን ለመከላከል ሲባል ከምሽቱ 3:00 በኃላ ባለሦሰት እግር ተሽከርካሪ (ባጃጅ) እና ባለ ሁለት እግር ሞተር ሳይክል ማሽከርከር የተከለከለ መሆኑን የሀዋሳ ከተማ ትራፊክ ፖሊስ አስተባባሪው ኢንስፔክተር ተስፋዬ ደምሴ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ላይ አሳውቀዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያም ፦
° ምክንያት ?
° ክልከላው ለምን አስፈለገ ?
° በማህበረሰቡ የእለት ተእለት ህይወትስ ላይ የሚያሳድረዉ ጫና አይኖርም ? ወይ ስንል ኢንስፔክተሩን ጠይቋል።
ቃላቸውን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ የሰጡት ኢንስፔክተር ተስፋዬ ፤ " ሁሉንም ያደረግነው ለማህበረሰቡ ደህንነት ነው " ብለዋል።
" አሁን ላይ በሀዋሳ ከተማ ከፍተኛ የትራፊክ አደጋ እየተስተዋለ ነው " ሲሉ ገልጸው ከአደጋዎቹ አብዛኛዉ በባለሦሰት እግር ባጃጅና በባለሁለት እግር ሞተር ሳይክል የሚደርስ እንደሆነ አስረድተዋል።
" በዚህ አመት ብቻ በምሽት በሞተር ሳይክል የደረሰዉ አደጋ የሚያስገርም ቁጥር ያለው ነው " ያሉት ኢስፓክተር ተስፋዬ በቁጥር ስንት ? የሚለውን ወደፊት ዳታውን አጠናቅረዉ ለማህበረሰቡ የማሳየት እቅድ እንዳለቸዉ ጠቁመዋል።
ከአደጋዎቹ ውስጥ በአብዛኛው የሚከሰቱት በምሽት መሆኑን ጠቅሰው ፤ " ጠጥቶ ሞተር ሳይክል ማሽከርከር ትልቁ ምክኒያት ሆኖ ተገኝቷል። በተለይም በመንግስት ሞተር ሳይክሎች ሳይቀር ሶስትና ከዚያ በላይ ሆኖ መንቀሳቀስ አደጋ እየፈጠረ ነው ይህን ችግር ለመቀነስ ሲባል #ክልከላው ወጥቷል " ሲሉ ተናግረዋል።
በተጨማሪም ፤ " የባለ ሶስት እግር ተሽከርካሪዎች ከፍተኛ የወንጀል መፈጸሚያ እየሆኑ ነው " ያሉት ኢንስፔክተሩ ፤ " ለአብነት ኮንትራት ተብለዉ በሚንቀሳቀሱ አሽከርካሪዎች ላይ የሚደርሰው አደጋ እና የሌሎችም ወንጀሎች ምንጭ ሆነው ተገኝተዋል " ብለዋል።
" ጥንቃቄ ለራስ በመሆኑ ማህበረሰቡ ለራሱ ሲባል የወጣዉን ክልከላ አክብሮ እንዲንቀሳቀስ " ሲሉ አሳስበዋል።
" እለት ተእለት የሚከሰተው ዘግናኝ የትራፊክ አደጋ እንዲቆም የሁላችንም ትብብር ያስፈልጋል " ብለዋል።
ክልከላው የሚያበቃበትን ጊዜን በተመለከተ ምንም የተባለ ነገር የለም።
#TikvahEthiopiaFamilyHawassa
@tikvahethiopia
👏665❤179😡151🤔63🙏39🕊25😭21😢17😱14🥰12
TIKVAH-ETHIOPIA
ፎቶ፦ ዓመታዊው የቅዱስ ገብርኤል የንግስ በዓል በቁልቢ ደብረ ኃይል ቅዱስ ገብርኤል ገዳም በተለያዩ ሃይማኖታዊ ስነ ሥርዓቶች በድምቀት እየተከበረ ይገኛል። ዛሬ ሐምሌ 19 እየተከበረ ባለው የዓመቱ የቅዱስ ገብርኤል ንግስ በዓል ላይ እጅግ ከፍተኛ ቁጥር ያለው ምዕመን ቁልቢ ተገኝቷል። #ቅዱስገብርኤል #ሐምሌ19 የፎቶ ባለቤት ፦ ኤፍኤምሲ @tikvahethiopia
ፎቶ፦ የሐምሌ 19 የቅዱስ ገብርኤል ዓመታዊ የንግስ በዓል በሀዋሳ ደብረ ምህረት ቅዱስ ገብርኤል ገዳም በታላቅ ድምቀት እየተከበረ ይገኛል።
በዓሉ ላይ እጅግ ከፍተኛ ቁጥር ያለው ኦርቶዶክሳዊ ምዕመን ተገኝቷል።
#ሐምሌ19 #ቅዱስ_ገብርኤል #ሀዋሳ
#TikvahEthiopiaFamilyHawassa
@tikvahethiopia
በዓሉ ላይ እጅግ ከፍተኛ ቁጥር ያለው ኦርቶዶክሳዊ ምዕመን ተገኝቷል።
#ሐምሌ19 #ቅዱስ_ገብርኤል #ሀዋሳ
#TikvahEthiopiaFamilyHawassa
@tikvahethiopia
4❤3.66K🙏401🕊82😡71🥰42💔24😭24🤔20😢18😱6