" ዝግጅቱ ተጠናቋል " - ትምህርት ሚኒስቴር
ትምህርት ሚኒስቴር ፤ የመጀመሪያ ዲግሪ ተመራቂዎች የመውጫ ፈተና ዝግጅት #መጠናቀቁን አስታወቀ።
ፈተናው ከሐምሌ 3 እስከ ሐምሌ 8 ቀን 2015 ዓ.ም ድረስ ይሰጣል።
በሚኒስቴሩ የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት አገልግሎት ዴስክ ኃላፊ እዮብ አየነው (ዶ/ር) ለኢዜአ በሰጡት ቃል ፤ " የመጀመሪያ ዲግሪ ተመራቂ ተማሪዎችን እውቀትና ብቃት ለመለካት የሚሰጠው የመውጫ ፈተና ዝግጅት ተጠናቋል " ብለዋል።
የትምህርትና ስልጠና ባለስልጣን የትክክለኛ ተፈታኞችን ቁጥር እንዲያጣራ በማድረግ ከግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት 95 ሺህ 755 እንዲሁም ከመንግስት ዩኒቨርሲቲዎች 74 ሺህ 776 ተማሪዎች ለፈተና ይቀመጣሉ ሲሉ ገልጸዋል።
ፈተናውን ያላለፉ ተማሪዎቸ ዲግሪ እንደማይሰጣቸው እና የትምህርት ሚኒስቴር በሚያዘጋጀው የፈተና ጊዜ መሰረት ድጋሚ እንደሚፈተኑ አመልክተዋል።
ተማሪዎች በትምህርት ቆይታቸው ከተማሯቸው የትምህርት ዓይነቶች መካከል መሰረታዊ የሚባሉ ከ12 እስከ 17 የትምህርት ዓይነቶች ፈተና እንደሚወጣ ገልጸዋል፡፡
ለዚህም የፈተና ንድፍና የብቃት መመዘኛ መስፈርቶች መዘጋጀታቸውን አረጋግጠዋል፡፡
ከግንቦት 15 ጀምሮ ለ211 የትምህርት ፕሮግራሞች የፈተና ጥያቄዎች በማውጣት ለፈተናው ሙሉ ለሙሉ ዝግጁ እንዲሆን መደረጉን ተናግረዋል።
ፈተናው በኦንላየን የሚሰጥ በመሆኑም አስፈላጊ የቴሌኮም እና ሌሎች መሰረተ ልማቶችን ዝግጁ ለማድረግ እየተሰራ ስለመሆኑ ጠቁመዋል።
በሀገሪቱ ካሉ 325 የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት 161 እና ከመንግስት ደግሞ 44 ዩኒቨርሲቲዎች ተማሪዎቻቸውን እንደሚያስፈትኑ ጠቅሰዋል።
ዶ/ር እዮብ ፤ " ገበያው የሚፈልገውን ብቁ የሰው ኃይል ለማፍራት የመውጫ ፈተናው ከ2015 ጀምሮ በሁሉም የትምህርት መስኮችና መርሐ ግብሮች መስጠት እንዲቻል ስራዎች ከአንድ ዓመት በላይ ሲሰሩ ቆይቷል " ሲሉ አስታውሰዋል።
#ኢዜአ
@tikvahethiopia
ትምህርት ሚኒስቴር ፤ የመጀመሪያ ዲግሪ ተመራቂዎች የመውጫ ፈተና ዝግጅት #መጠናቀቁን አስታወቀ።
ፈተናው ከሐምሌ 3 እስከ ሐምሌ 8 ቀን 2015 ዓ.ም ድረስ ይሰጣል።
በሚኒስቴሩ የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት አገልግሎት ዴስክ ኃላፊ እዮብ አየነው (ዶ/ር) ለኢዜአ በሰጡት ቃል ፤ " የመጀመሪያ ዲግሪ ተመራቂ ተማሪዎችን እውቀትና ብቃት ለመለካት የሚሰጠው የመውጫ ፈተና ዝግጅት ተጠናቋል " ብለዋል።
የትምህርትና ስልጠና ባለስልጣን የትክክለኛ ተፈታኞችን ቁጥር እንዲያጣራ በማድረግ ከግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት 95 ሺህ 755 እንዲሁም ከመንግስት ዩኒቨርሲቲዎች 74 ሺህ 776 ተማሪዎች ለፈተና ይቀመጣሉ ሲሉ ገልጸዋል።
ፈተናውን ያላለፉ ተማሪዎቸ ዲግሪ እንደማይሰጣቸው እና የትምህርት ሚኒስቴር በሚያዘጋጀው የፈተና ጊዜ መሰረት ድጋሚ እንደሚፈተኑ አመልክተዋል።
ተማሪዎች በትምህርት ቆይታቸው ከተማሯቸው የትምህርት ዓይነቶች መካከል መሰረታዊ የሚባሉ ከ12 እስከ 17 የትምህርት ዓይነቶች ፈተና እንደሚወጣ ገልጸዋል፡፡
ለዚህም የፈተና ንድፍና የብቃት መመዘኛ መስፈርቶች መዘጋጀታቸውን አረጋግጠዋል፡፡
ከግንቦት 15 ጀምሮ ለ211 የትምህርት ፕሮግራሞች የፈተና ጥያቄዎች በማውጣት ለፈተናው ሙሉ ለሙሉ ዝግጁ እንዲሆን መደረጉን ተናግረዋል።
ፈተናው በኦንላየን የሚሰጥ በመሆኑም አስፈላጊ የቴሌኮም እና ሌሎች መሰረተ ልማቶችን ዝግጁ ለማድረግ እየተሰራ ስለመሆኑ ጠቁመዋል።
በሀገሪቱ ካሉ 325 የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት 161 እና ከመንግስት ደግሞ 44 ዩኒቨርሲቲዎች ተማሪዎቻቸውን እንደሚያስፈትኑ ጠቅሰዋል።
ዶ/ር እዮብ ፤ " ገበያው የሚፈልገውን ብቁ የሰው ኃይል ለማፍራት የመውጫ ፈተናው ከ2015 ጀምሮ በሁሉም የትምህርት መስኮችና መርሐ ግብሮች መስጠት እንዲቻል ስራዎች ከአንድ ዓመት በላይ ሲሰሩ ቆይቷል " ሲሉ አስታውሰዋል።
#ኢዜአ
@tikvahethiopia
👎1.87K👍960❤141😱48😢35🙏27🕊26🥰19🤔1
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
" በዓሉ #በሰላም ተጠናቋል " - ግብረ ኃይሉ
የ2016 የሆራ ፊንፊኔ የኢሬቻ በዓል የገዳ ስርአቱን በጠበቀ መልኩ #በሰላም መከበሩን የፀጥታ እና ደህንነት የጋራ ግብረ-ኃይል አስታውቋል።
ግብረ ኃይሉ ፤ በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ተሳታፊዎች ተገኝተውበታል ያለድ የዘንድሮው የሆራ ፊንፊኔ ኢሬቻ በዓል በሰላም ተከብሮ #መጠናቀቁን ገልጿል።
የነገው የሆራ አርሰዴ ኢሬቻ በዓለም በተመሳሳይ በሰላም ተከብሮ እንዲጠናቀቅ ሁሉም ህብረተሰብ የበኩሉን አስተዋጽኦ እንዲያደርግ እና ለፀጥታ ኃይሉ እገዛውን እንዲያጠናክር ተጠይቋል።
@tikvahethiopia
የ2016 የሆራ ፊንፊኔ የኢሬቻ በዓል የገዳ ስርአቱን በጠበቀ መልኩ #በሰላም መከበሩን የፀጥታ እና ደህንነት የጋራ ግብረ-ኃይል አስታውቋል።
ግብረ ኃይሉ ፤ በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ተሳታፊዎች ተገኝተውበታል ያለድ የዘንድሮው የሆራ ፊንፊኔ ኢሬቻ በዓል በሰላም ተከብሮ #መጠናቀቁን ገልጿል።
የነገው የሆራ አርሰዴ ኢሬቻ በዓለም በተመሳሳይ በሰላም ተከብሮ እንዲጠናቀቅ ሁሉም ህብረተሰብ የበኩሉን አስተዋጽኦ እንዲያደርግ እና ለፀጥታ ኃይሉ እገዛውን እንዲያጠናክር ተጠይቋል።
@tikvahethiopia
😡1.14K🙏548❤152🕊60🥰36😢30😱9
TIKVAH-ETHIOPIA
#AU #ETHIOPIA ትላንትና ምሽት ላይ ለ37ኛው የአፍሪካ ኅብረት የመሪዎች ጉባዔ ለመጡ መሪዎች በብሄራዊ ቤተመንግስት የእራት ግብዣ ተደርጎላቸው ነበር። ዛሬ የጠ/ሚኒስትር ፅህፈት ቤት ባሰራጫቸው ምስሎች የኬንያው ፕሬዜዳንት ዊሊያም ሩቶ ፣ የጅቡቲ ፕሬዝዳንት ኢስማኤል ኦማር ጌሌህን ጨምሮ የሌሎች የአፍሪካ ሀገራት መሪዎች በእራት ግብዣው ላይ ተገኝተው የነበረ ሲሆን የጎረቤት ሶማሊያው ፕሬዜዳንት ሀሰን…
#Update #ተጠናቋል
የአፍሪካ ሕብረት ጉባኤ በሰላምና በስኬት #መጠናቀቁን ኢትዮጵያ አስታውቃለች።
የሁሉም ሀገራት መሪዎች እና የጉባኤው ተሳታፊዎች ወደ አዲስ አበባ ሲገቡ ከዚህ ቀደም ከነበረው በደመቀ ሁኔታ ዓለም አቀፍ የዲፕሎማሲ ክብርን እና ፕሮቶኮልን በጠበቀ መልኩ አቀባበል እንደተደረገላቸው ፤ በአዲስ አበባ ቆይታቸውም በልዩ እንክብካቤ እንደተያዙ በኢትዮጵያ መንግሥት ተገልጿል።
ኢትዮጵያ ለዚህ ጉባኤ ስኬት ላለፉት 6 ወራት ስትዘጋጅ መቆየቷን የተገለጸ ሲሆን በተለይም ከሰላምና ደህንነት አንፃር በርካታ ባለድርሻ አካላት ሲሳተፉ መቆየታቸውን ተጠቁሟል።
በ10 ሺዎች የሚቆጠሩ የፀጥታ እና ደህንነት ኃይሎች ተሰማርተው እንደነበረም ተመላክቷል።
ለጉባኤው ስኬታማነት በተለይ በተለይ የአዲስ አበባ ህዝብ ከቅድመ ጉባኤው ዝግጅት አንስቶ ስብሰባው ተጀምሮ እስኪያልቅ ድረስ የትራፊክ፣ የመንገድ መዘጋጋት እና ሌሎች ጉዳዮችንም ታግሶ ፤ ከፀጥታ ኃይሉም ጋር በመተባበር እንግዶች ደህንነታቸው ተጠብቆ እንዲስተናገዱ ልዩ የእግዳ አቀባበል በማድረጉ መንግሥት ምስጋና አቅርቧል።
በተጨማሪ የፀጥታ እና ደህንነት ኃይሎች ፣ የትራፊክ ተቆጣጣሪዎች፣ የፕሮቶኮል ሰዎች፣ ሆቴሎች ፣ የሀገር ውስጥ እና የውጭ መገናኛ ብዙሃን .. ሌሎችም አስተዋፅኦ ያደረጉ ሁሉ ምስጋና ቀርቦላቸዋል።
@tikvahethiopia
የአፍሪካ ሕብረት ጉባኤ በሰላምና በስኬት #መጠናቀቁን ኢትዮጵያ አስታውቃለች።
የሁሉም ሀገራት መሪዎች እና የጉባኤው ተሳታፊዎች ወደ አዲስ አበባ ሲገቡ ከዚህ ቀደም ከነበረው በደመቀ ሁኔታ ዓለም አቀፍ የዲፕሎማሲ ክብርን እና ፕሮቶኮልን በጠበቀ መልኩ አቀባበል እንደተደረገላቸው ፤ በአዲስ አበባ ቆይታቸውም በልዩ እንክብካቤ እንደተያዙ በኢትዮጵያ መንግሥት ተገልጿል።
ኢትዮጵያ ለዚህ ጉባኤ ስኬት ላለፉት 6 ወራት ስትዘጋጅ መቆየቷን የተገለጸ ሲሆን በተለይም ከሰላምና ደህንነት አንፃር በርካታ ባለድርሻ አካላት ሲሳተፉ መቆየታቸውን ተጠቁሟል።
በ10 ሺዎች የሚቆጠሩ የፀጥታ እና ደህንነት ኃይሎች ተሰማርተው እንደነበረም ተመላክቷል።
ለጉባኤው ስኬታማነት በተለይ በተለይ የአዲስ አበባ ህዝብ ከቅድመ ጉባኤው ዝግጅት አንስቶ ስብሰባው ተጀምሮ እስኪያልቅ ድረስ የትራፊክ፣ የመንገድ መዘጋጋት እና ሌሎች ጉዳዮችንም ታግሶ ፤ ከፀጥታ ኃይሉም ጋር በመተባበር እንግዶች ደህንነታቸው ተጠብቆ እንዲስተናገዱ ልዩ የእግዳ አቀባበል በማድረጉ መንግሥት ምስጋና አቅርቧል።
በተጨማሪ የፀጥታ እና ደህንነት ኃይሎች ፣ የትራፊክ ተቆጣጣሪዎች፣ የፕሮቶኮል ሰዎች፣ ሆቴሎች ፣ የሀገር ውስጥ እና የውጭ መገናኛ ብዙሃን .. ሌሎችም አስተዋፅኦ ያደረጉ ሁሉ ምስጋና ቀርቦላቸዋል።
@tikvahethiopia
👏729❤137😡100🕊44🙏24😢17😭11😱7🥰6
TIKVAH-ETHIOPIA
#እንድታውቁት ነገ በአዲስ አበባ መንገዶች ይዘጋሉ። በአዲስ አበባ ' መስቀል አደባባይ ' ነገ #ቅዳሜ ከሚደረግ የድጋፍ ሰልፍ ጋር በተያያዘ መንገዶች እንደሚዘጉ የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን አስታወቀ። ከንጋቱ 11፡00 ሰአት ጀምሮ ሰልፉ እስኪጠናቀቅ ድረስ ፦ - ከቴዎድሮስ አደባባይ በብሄራዊ ቴአትር ወደ ወደ መስቀል አደባባይ ሚወስደው መንገድ ቴዎድሮስ አደባባይ - ከኡራኤል አደባባይ ወደ መስቀል…
#እንድታውቁት
በአዲስ አበባ ፤ #መስቀል_አደባባይ ከሚደረግ የመንግስት የድጋፍ ሰልፍ ጋር በተያያዘ ተዘግተው የነበሩ መገዶች ተከፍተዋል።
ሰልፉ #መጠናቀቁን ተከትሎ ተዘግተው የነበሩት መንገዶች ለተሽከርካሪ ክፍት ሆነዋል።
@tikvahethiopia
በአዲስ አበባ ፤ #መስቀል_አደባባይ ከሚደረግ የመንግስት የድጋፍ ሰልፍ ጋር በተያያዘ ተዘግተው የነበሩ መገዶች ተከፍተዋል።
ሰልፉ #መጠናቀቁን ተከትሎ ተዘግተው የነበሩት መንገዶች ለተሽከርካሪ ክፍት ሆነዋል።
@tikvahethiopia
😡1.23K👏212❤113🕊40🙏37😭29🤔17😢17😱10🥰6