TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
63.2K photos
1.62K videos
218 files
4.4K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

መረጃ እና መልዕክት ፦ 0919743630

ማርኬቲንግ ፦ 0979222111 ወይም
0979333111

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
ከዛሬ መስከረም 2 ቀን 1967 ዓ/ም ጀምሮ ቀዳማዊ ኃይለስላሴ ከስልጣናቸው ወርደዋል። #ETHIOPIA

አዋጅ ቁጥር 1/1967

1ኛ. ይህ አዋጅ የኢትዮጵያ ጊዜያዊ ወታደራዊ አስተዳደር አዋጅ ቁጥር 1/1967 ዓ/ም ተብሎ ሊጠቀስ ይችላል።
.
.
ይህ አዋጅ እስከፀናበት ድረስ "ኢትዮጵያ ትቅደም" የሚለውን አላማ የመቃወም አድማ የሚያደርግ፤ ስራ የሚያቆም፤ ያለ ፍቃድ ሰላማዊ ሰልፍ እና ስብሰባ የማድረግ በጠቅላላው የህዝቡን ፀጥታና ሰላም የሚነሳ ተግባር መፈፀም ክልክል ነው።

#TIKVAH_ETHIOPIA

@tsegabwolde @tikvahethiopia
#US_EMBASSY

አዲስ አበባ የሚገኘው የአሜሪካ ኤምባሲ በጋምቤላ ክልል ሁለት የግብረ-ሰናይ ድርጅት ሰራተኞች የገደሉ ታጣቂዎችን መንግሥት በአፋጣኝ በቁጥጥር ሥር አውሎ ለሕግ እንዲያቀርብ ጠየቀ። አክሽን አጌይንስት ኸንገር የተባለው ዓለም አቀፍ የግብረ-ሰናይ ድርጅት ሰራተኞች ጥቃት የተፈጸመባቸው በጋምቤላ ክልል ደቡብ ሱዳናውያን ስደተኞች ከሚኖሩበት ኙንዬል ከተባለ የመጠለያ ጣቢያ (Nguenyyiel Refugee Camp) ሥራቸውን አጠናቀው በመጓዝ ላይ ሳሉ እንደነበር ድርጅቱ አስታውቋል። በጥቃቱ የመስክ ሰራተኛ እና አሽከርካሪ ሕይወታቸውን አጥተዋል። የአሜሪካ ኤምባሲ በዛሬው ዕለት ባወጣው መግለጫ የግብረ-ሰናይ ሰራተኞች መሆኑን የሚጠቁም ምልክት በነበረው ተሽከርካሪ ላይ ባለፈው ሳምንት የተፈጸመውን ጥቃት አውግዟል።

Via #EsheteBekele
@tsegabwolde @tikvahethiopia
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
mwfellows.info/apply

በመጪው የአውሮፓ ዓመት ለሚካሄደው የ2020 የማንዴላ የወጣት አፍሪካዊያን መሪዎች ዋሽንግተን ፌሎውሽፕ መርሐ ግብር ምዝገባ ተጀመረ።

‘የማንዴላ ዋሽንግተን ፌሎውሽፕ’ የተባለው መርሃ ግብር ወጣት አፍሪካዊያንን በመመልመል በአሜሪካን አገር በሚገኙ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ለ6 ሳምንት የሚዘልቅ የአመራርነት ስልጠና የሚሰጥበት ነጻ የትምህርት እድል ነው።

በኢትዮጵያ የአሜሪካን ኤምባሲ ዛሬ በሰጠው ማብራሪያ በአውሮፓዊያን ቀመር በመጪው ዓመት ለሚሰጠው መርሐ ግብር ምዝገባው ትናንት ተጀምሯል። ምዝገባም እንደ አውሮፓ አቆጣጠር አስከ ጥቅምት 9 ቀን 2019 ይቆያል ተብሏል።

ተጨማሪ ያንብቡ👇
https://telegra.ph/ETH-09-13-5
#FAKE የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ማጠናቀቅያ ወይም የመሰናዶ መግቢያ #መቁረጫ ነጥብ ይፋ ሆነ እየተባለ በማህበራዊ ሚዲያ ሚሰራጨው። በዛሬው ዕለት ይፋ የተደረገው ተማሪዎች ውጤት ብቻ ነው። የመቁረጫ ነጥብ ይፋ አልተደረገም። በሚሰራጩ ሀሰተኛ መረጀዎች እንዳትታለሉ።

@tsegabwolde @tikvahethiopia
"ከዕገታው ጀርባ የእስራኤል የስለላ ድርጅት ሞሳድ እንደሚኖር ጥርጣሬያቸውን ገልፀዋል!"

ሐሰን ጃበር የተባሉ ሊባኖሳዊ የንግድ ሰው በሳምንቱ የመጀመሪያ ቀናት ትራንዚት በሚያደርጉበት አዲስ አበባ ቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ታግተው እንደተወሰዱ እና የደረሱበት እንዳልታወቀ ቤተሰቦቻቸው አስታውቀዋል።

በዕለቱ ከአፍሪካዊቷ አገር ጋቦን በመነሳት በአዲስ አበባ አድርገው ወደ ሊባኖስ ቤሩት በማምራት ላይ የነበሩት ሐሰን አዲስ አበባ ደርሰው ቀጣዩ ጉዟቸውን ለማድረግ በሚሰናዱበት ወቅት ለጊዜው ማንነታቸው ባልታወቁ ሰዎች ዕገታ እንደተፈፀመባቸው እና ሊሰወሩ እንደቻሉ የተገለፀው። የግለሰቡ ቤተሰቦች ከሊባኖስ ጋዜጣ አል አክበር ጋር ባደረጉት ቆይታ ከዕገታው ጀርባ የእስራኤል የስለላ ድርጅት ሞሳድ እንደሚኖር ጥርጣሬያቸውን ገልፀዋል።

እንደ ጋዜጣው ዘገባ ግለሰቡ ከዓመታት በፊት በፈረንጆች 2017 ከሒዝቦላህ ጋር ግንኙነት አለው በሚል በጋቦን የፀጥታ አካላት ምርመራ የተደረገባቸው መሆኑን አውስቷል። ይሁን እንጂ ሐሰን ከሒዝቦላህ ጋር ምንም አይነት ግንኙነት እንደሌላቸው ቤተሰቦቻቸው አስታውቀዋል።

በአሁኑ ሰዓት ሊባኖሳዊው ግለሰብ የት እና በምን ደረጃ ላይ እንደሚገኙ የሚታወቅ ነገር የለም። ስለጉዳዩ ኢትዮጵያ አየር መንገድ ምንም የሚያውቀው ነገር አለመኖሩን ለአዲስ ማለዳ ተናግረዋል።

የሊባኖስ የወጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በኢትዮጵያ በኩል የሚመለከታቸው የፀጥታ አካላት በጉዳዩ ላይ ግልፅ ምላሽ እስከ መጪው ሰኞ መስከረም 5/2012 ድረስ እንዲሰጥበት አሳስበዋል። ካልሆነ ግን ተመጣጣኝ እርምጃ እንደሚወስድ የሊባኖስ መንግስት አስጠንቅቋል።

Via #AddisMaleda
@tsegabwolde @tikvahethiopia
በደንብ ተመልከቱ⬆️

እኛ እንዲህ ነን፤ ተያይዞ፣ ተቻችሎ፣ ተዋዶ መኖር ካልቻልን ተያይዞ መጥፋት ነው የሚሆነው፤ አንዱን ጠጠር ብታነሱት ሁሉም ይፈርሳል፤ ለሁሉም መኖር የአንዱ መኖር ወሳኝ ነው።

#እንዋደድ #እንከባበር #እንፋቀር #ሰላም #ፍቅር #ተስፋ

ሀሳቡ ከማህበራዊ ሚዲያ ተወሰደ!


🚪መስከረም 2 ቀን 2012 ዓ/ም
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ማስታወቂያ!

ለዩኒቨርስቲ ተመዳቢ ተማሪዎች በሙሉ!

በ2012 የትምህርት ዘመን ለሚካሄደው የተማሪዎች/ተፈታኞች ምደባ፦

1. ከተፈጥሮ ሳይንስ ወደ ማህበራዊ ሳይንስ ትምህርት መስክ መቀየር የምትፈልጉ ተማሪዎች/ተፈታኞች እና

2. የዩኒቨርስቲ ምርጫችሁን ማስተተካከል (መቀየር) ለምትፈልጉ ተማሪዎች /ተፈታኞች የዩኒቨርስቲ ምርጫችሁን ማስተካከልም ሆነ የትምህርት መስክ ምርጫ (የመምህርነት መስክ ምርጫ መምረጥ) የሚቻለው በተማራችሁበት ት/ቤት (ፈተና በወሰዳችሁበት የፈተና ጣቢያ) በኩል መሆኑን እያሳወቅን የዩኒቨርስቲ ምርጫ ማስተካከያና የፊልድ መቀየሪያ ቀናት ከመስከረም 5/2012 እስከ መስከረም 12 /2012 ዓ.ም ድረስ ብቻ መሆኑን ኤጀንሲው እየገለፀ የመሰናዶ ት/ቤቶችም የተማሪዎችን ምርጫ ማስተካከልና የፊልድ ቅየራ /ከተፈጥሮ ሳይንስ ወደ ማህበራዊ ሳይንስ/ ጥያቄ በመቀበል እንዲታስተናግዱ ያሳስባል፡፡

ሀገር አቀፍ የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች ኤጀንሲ

በየዕለቱ የሚወጡ የትምህርት ነክ ጉዳዮችን በTIKVAH-MAGAZINE ማግኘት ትችላላችሁ👇
https://tttttt.me/joinchat/AAAAAEcez-UrldBjOpa-qQ
🥰1
#update ፕሬዚዳንት ኢሳያስ አፈወርቂ ለይፋዊ የስራ ጉብኝት ወደ ካርቱም ሊያቀኑ ነው። የሱዳን ሉዓላዊ ምክር ቤት ሃላፊ ሌተናል ጀኔራል አብድል ፋታ አል ቡርሃን ባቀረቡላቸው ግብዣ መሰረት በፕሬዚዳንት ኢሳያስ አፈወርቂ የሚመራ የኤርትራ ልኡካን ቡድን ለይፋዊ የስራ ጉብኝት ዛሬ ሱዳን ይገባል ተብሏል። ፕትሬዚዳንት ኢሳያስ በቆይታቸው የሀገራቱን የሁለትዮሽ ግንኙነት ማጠናከር በሚቻልባቸው ጉዳዮች እንዲሁም ባለፉት አመታት የነበረውን መልካም ግንኙነት ለማጠናከር ያለመ ውይይት ያደርጋሉ ተብሎ ይጠበቃል። ፕሬዚዳንቱ ለሁለት ቀናት የስራ ጉብኝት ከውጭ ጉዳይ ሚኒስትራቸው እና የደህንነት አማካሪያቸው ጋር በዛሬው ዕለት ሱዳን ካርቱም ይገባሉ ተብሎ ይጠበቃል። የሱዳን ሉዓላዊ ምክር ቤት ሃላፊ ሌተናል ጀኔራል አብድል ፋታ አል ቡርሃን በቅርቡ በኤርትራ ይፋዊ የስራ ጉብኝት ማድረጋቸው ይታወሳል።

ምንጭ ፦የሱዳን ዜና አገልግሎት/ebc/
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#ጥቆማ በአንዳድ የሀገሪቱ ከተሞች የ10ኛ ክፍል የብሄራዊ ፈተና ተፈታኝ ተማሪዎች ውጤታቸውን ለማየት እደተቸገሩ እየገለፁ ይገኛሉ። የሚመለከተው አካል ችግሩን እንዲፈታም ጠይቀዋል።

@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update በሚቀጥሉት ሁለት ዓመታት ውስጥ ዕውቀት እና ሃሳብ ያላቸውን ሰዎች ንድፍ ወደተግባር እንዲቀይሩ በማድረግ ቴክኖሎጂ እና ፈጠራን መሰረት ያደረጉ ሁለት ሺ አነስተኛ ተቋማት ሊያቋቋቁም መሆኑን የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር አስታወቁ።

የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ጀማል በከር በተለይ ለአዲስ ዘመን እንደገለጹት፤ በሚቀጥሉት ሁለት ዓመታት ውስጥ ሁለት ሺ አነስተኛ የሳይንስና ፈጠራ ንግድ እና አገልግሎት ተቋማትን በማቋቋም እና ድጋፍ ይደረጋል።

በስራቸውም 20 ሺ ሰዎችን በቀጥታ ተጠቃሚ ለማድረግ ሀገራዊ እንቅስቃሴ በሚኒስቴሩ ተጀምሯል። እንደ አቶ ጀማል ገለጻ፤በተለይ በተንቀሳቃሽ ስልክ እና በኮምፒውተር በመተግበሪያዎች፣ በሮቦት እና ሌሎች ፈጠራ ስራዎች እንዲሁም በማምረቻ እና አገልግሎት ዘርፉ ውስጥ ቴክኖሎጂን ተጠቅመው ችግር ፈቺ ንግድ ለሚጀምሩ ሰዎች የገንዘብ ድጋፍም ይደረጋል።

Via #EPA
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ዚምቧብዌ የቀድሞ ፕሬዝዳንቷን ሥርዓተ ቀብር ከመፈፀሟ በፊት፤ ሮበርት ሙጋቤን ለመሰናበት የአፍሪካ መሪዎች በዋና ከተማዋ ሐራሬ ይሰባሰባሉ ተብሎ ይጠበቃል። የደቡብ አፍሪካው ሲሪል ራማፎሳን ጨምሮ በርካታ በስልጣን ላዩ ያሉና የቀድሞ የአፍሪካ ርዕሰ ብሄሮችም በስንብቱ ላይ ይገኛሉ ተብሎ ይጠበቃል።

Via #BBC
@tsegabwolde @tikvahethiopia
መፍትሄ ያልተገኘለት የቴፒ ጉዳይ...

"እንደምታውቀው አመት ያለፈው የቴፒ ውጥረት እስካሁን መፍትሄ አላገኘም። በግጭቱ ሳቢያ ከቀያቸው የተፈናቀሉ ሰዎች ይኸው በአንድ አዳራሽ ውስጥ ተጠልለው ስምንት ወር አለፋቸው። ይህ ሁሉ ሲሆን አንድም የመንግስት አካል ሌላው ቀርቶ ሰብዓዊ እርዳታ እንኳን አላደረገላቸውም። በዚሁ ከቀጠለ የቡና ምርት ወቅት ስለደረሰ ተፈናቃዮቹ ወደቀያቸው ካልተመለሱ ሌላ ቀውስ መፈጠሩ አይቀሬ ነው።...የሚያሳዝነው ነገር ግጭቱ ከጀመረ አንስቶ ከቀን ቀን እየጨመረ የመጣውና እስከ ሰው ህይወት መጥፋት የተደረሰ የዝርፊያ ተግባር ነው። መጠኑ ይለያይ እንጂ አንድም ቀን የተኩስ ድምፅ ሳይሰማ ቀርቶ አያውቅም። ሰው ይሞታል፤ ንብረት ይዘረፋል።...አሁንም ቢሆን መንግስት ለጉዳዩ ትኩረት ሰጥቶ ነገሮች ካልተስተካከሉ ግጭቱ እንዳዲስ አገርሽቶ ሌላ ጥፋት እንዳያስከትል ስጋቴ ነው።" ከቴፒ የTIKVAH-ETH ቤተሰብ

@tsegabwolde @tikvahethiopia
ለማሳያነት⬆️

በሻኪሶ፣ በማጀቴ፣ እንዲሁም በምዕራብ ወለጋ ከተሞችና በሌሎችም አካባቢዎች የብሄራዊ ፈተና ተፈታኝ ተማሪ ወላጆች የልጆቻቸውን ውጤት ማየት እንዳልቻሉ እየገለፁልን ይገኛሉ። ከትላንት ጀምረው ተደጋጋሚ ሙከራ ቢያደርጉም ከድረገፁ የሚያገኙት መልስ "undefined" የሚል ነው።

•እኛም ይህንኑ የተለያዩ የመፈተኛ ቁጥሮችን በማስገባት አረጋግጠናል። ይህን መልእክት የምታነቡ የሚመለከታችሁ የስራ ኃላፊዎች ችግሩን ለይታችሁ #መፍትሄ ትፈልጉ ዘንድ በወላጆች ስም ጥሪ እናቀርባለን!

@tsegabwolde @tikvahethiopia
የደቡብ ክልል ጤና ቢሮ በ2011 በጀት ዓመት ብቻ 186 እና እስካሁን ደግሞ የ2011ዱንም ጨምሮ በጠቅላላው 425 አምቡላንሶች በላይ ተሰራጭተው አገልግሎት በመስጠት ላይ ቢሆኑም ችግሮች እየተስተዋሉባቸው ይገኛል፡፡

ተጨማሪ ያንብቡ👇
https://telegra.ph/ETH-09-14-3
የሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር!

በአዲሱ ዓመት በዩኒቨርሲቲዎች ሰላማዊ መማር ማስተማርን እውን ለማድረግ ቅድመ ዝግጅት መደረጉን የሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር አስታወቀ። ዩኒቨርሲቲዎች የ2011 የትምህርት ዘመንን በአስቸጋሪ ሁኔታ ማሳለፋቸውን ነው  ሚኒስትር ዲኤታ ፕሮፌሰር አፈወርቅ ካሱ የተናግረዋል። ተማሪዎች በሀሳብ ልዕልና በመከራከር መተማመን ሲችሉ ከውጭ የሚነሱ ፖለቲካዊ ሁኔታዎችን ምክንያት በማድረግ ትምህርታቸውን ማስተጓጎል፣ በቡድን መደባደብና መገዳደል አሳዛኝ ክስተት ነበርም ብለዋል።

“በኢትዮጵያ የከፍተኛ ትምህርት ታሪክ እንደ 2011 ዓ.ም የትምህርት ዘመን ብዙ ልጆቻችንን ያጣንበት ዓመት ታይቶ አይታወቅም” ያሉት ፕሮፌሰር አፈወርቅ፤ ከዚህ በመማርም ከሁሉም የክልል አመራሮችና ከዩኒቨርሲቲ የቦርድ ሰብሳቢዎች ጋር በ2012 የትምህርት ዘመን ሊወሰዱ በሚገቡ #ጥንቃቄዎች ላይ ውይይት መደረጉን ገልፀዋል። በዚህም እያንዳንዱ ወላጅ፣ ተማሪ፣ በየደረጃው ያለ አስተዳደር ለሰላማዊ የመማር ማስተማሩ ሃላፊነት ተጥሎባቸዋል ነው ያሉት።

ተጨማሪ ያንብቡ👇
https://telegra.ph/ETH-09-14-4
ኢዜማ ነገ በመቐለ ህዝባዊ ስብሰባ ያደርጋል!

የኢትዮጵያ ዜጎች ለማህበራዊ ፍትህ (ኢዜማ) የ2012 ዓ.ም የመጀመሪያ ህዝባዊ ስብሰባውን ነገ መስከረም 4 ቀን 2012 ዓ.ም በመቐለ ያካሂዳል፡፡ ህዝባዊ ስብሰባውን የፓርቲው ሊቀመንበር አቶ የሺዋስ አሰፋና የፓርቲው ም/መሪ አንዱዓለም አራጌ የሚመሩት ሲሆን ስብሰባውም ከጠዋቱ 4 ሰዓት ጀምሮ በመቐሌ ማዘጋጃ ቤት አዳራሽ እንደሚካሄድ የህዝብ ግንኙነት ኃላፊው ናትናኤል ፈለቀ ለአዲስ አድማስ ጋዜጣ ተናግረዋል፡፡ በዚህ ህዝባዊ ስብሰባ ላይ የፓርቲውን አላማና ግብ፣ ፕሮግራሙንና አጀንዳውን በስፋት ለህዝብ እንደሚያስተዋውቅ የገለፁት አቶ ናትናኤል፤ ከህዝቡ ለሚነሱ አስተያየቶችና ጥያቄዎችም ምላሽና ማብራሪያ ይሰጥበታል ብለዋል፡፡ ኢዜማ በመላ ሀገሪቱ በሚገኙ የተመረጡ ከተሞች ተመሳሳይ ህዝባዊ ስብሰባዎችን በተከታታይ እንደሚያደርግም ተገልጿል፡፡

@tsegabwolde @tikvahethiopia
#BAHIRDAR

የባሕር ዳር ሀገረ ስብከት በየአጥቢያዎቹ ለተከታታይ ሰባት ቀናት ጸሎተ ምህላ አወጀ፡፡ ሀገረ ስብከቱ ለመስከረም 11 ቀን 2012 ዓ.ም ሰላማዊ ሰልፍ ጠርቷል፡፡

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን የባሕር ዳር ሀገረ ስብከት ከፊታችን ሰኞ መስከረም 5 ቀን 2012 ዓ.ም ጀምሮ ለተከታታይ ሰባት ቀናት ጸሎተ ምህላ አውጇል፤ ለመስከረም 11 ቀን 2012 ዓ.ም ደግሞ ሰላማዊ ሰልፍ ጠርቷል፡፡ ሀገረ ስብከቱ ዛሬ በሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ እንዳመላከተው የፀሎተ ምህላው ዓላማ በቤተ ክርስቲያኗ እና በምዕመኖቿ ላይ የሚደርሰውን መከራ፣ ግፍ እና መሰደድ አስመልክታ ለፈጣሪዋ መልዕክት ለማቅረብ ነው፡፡

ከጸሎተ ምህላው እና ከሰልፉ በኋላ በእለቱ 10፡00 ሰዓት ላይ የኃይማኖት አባቶች፣ የሀገር ሽማግሌዎች፣ ወጣቶች እና የክልሉ ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች በተገኙበት ስለወቅታዊው የቤተ ክርስቲያን ጥያቄ ውይይት ይደረጋል ተብሏል በመግለጫው፡፡

ምንጭ፦ አብመድ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
በሀዋሳ ከተማ የሚኖሩ የአለታ ወንዶ የመረዳጅ #ዕድር አባላት በአለታ ወንዶ ከተማ ተከስቶ በነበረው ግጭት ጉዳት ለደረሰባቸው ወገኖች ከ800 ሺህ ብር በላይ የገንዘብ ድጋፍ አድርገዋል።

Via #SRTA
@TSEGABWOLDE @TIKVAHETHIOPIA
ፎቶ📸በእድሳት ምክንያት ላለፉት ሁለት ዓመታት አገልግሎት ሳይሰጥ የቆየው የአበበ ቢቂላ ስታዲዮም አሁን ላይ ዕድሳቱ ሙሉ በሙሉ በመጠናቀቁ ስራ እንደሚጀምር ተገለጸ። በተያዘው አዲስ ዓመት የውድድር ዘመን እስከሚጀመርበት ጊዜ ድረስ ስታዲዮሙ ለአገልግሎት ክፍት ይሆናል ተብሏል። የአበበ ቢቂላ ስታዲዮም በ1995 ዓ .ም ስራ ጀመረ ይሁን እንጂ ደረጃውን የጠበቀ አልነበረም። አሁን ላይ የአዲስ አበባ አስተዳደር ከፍተኛ በጀት በመመደብ ለስታዲዮሙ ሙሉ እድሳት አድርጓል።

Via #EPA

ስፖርታዊ ጉዳዮችን👇
https://tttttt.me/joinchat/AAAAAFb8M0pNEZTiGM68rg
‹‹ሁሉም ኢትዮጵያዊ በኢሬቻ በዓል ላይ እንዲገኝ ጥሪ አስተላልፋለሁ››

/የኦሮሚያ ክልላዊ መንግስት ም/ርዕሰ መስተዳድር፤ ሽመልስ አብዲሳ/

የኢትዮጵያ ሕዝብ ትልቅ #እድል አግኝቷል፤ ይሄን እድል በአግባቡ ካልተጠቀመ ትልቅ ኪሳራ ነው የሚሆነው። አገሪቱ ከፍተኛ ችግር ላይ ትወድቃለች።

ብዙ አገሮች እንደዚህ አይነት እድሎችን ባለመጠቀማቸው፣ የለውጥ እቅድ ተጨናግፎ፣ ብዙ ጥፋቶች ደርሰዋል፡፡ አገራቸው የማትወጣበት ማጥ ውስጥ ተዘፍቃ ኑሮ መከራ የሆነባቸው ብዙ አገሮችን መጥቀስ ይቻላል፡፡

በአገራችንም ብዙ ለውጦች ከሽፈዋል፡፡ አሁን ያገኘነው ለውጥ ግን ከፍተኛ ውጤት የተገኘበት ነው። ወደ ኋላ አንድ አመት ተኩል ተመልሰን ብናስታውስ፤ አስገራሚ የሆነ ለውጥ ተካሄዷል፡፡ ሁሉም ኢትዮጵያዊ ለውጡን ማስቀጠል ይገባዋል።

ሁላችንም፤ መንግስትም ሕዝብም ተባብረን በአንድ ላይ ይሄንን ለውጥ ማስቀጠል ከቻልን፣ የምንናፍቃትን ኢትዮጵያን እንፈጥራታለን፡፡ ሁሉንም እኩል የምታከብር፣ ብሔር ብሔረሰብ እኩል የሚከበርባት፣ ሁሉም የሚተሳሰብባት፣ ወንድማማችነት የሚጠነክርባት አገር መፍጠር እንችላለን፡፡

እኔን እንቅልፍ የሚነሳኝ ይሄንን እድል እየተጠቀምንበት ነው አይደለም? በየቀኑ ለውጡን የሚያስቀጥል ሥራ እያከናወንን ነው አይደለም? የሚለው ነው፡፡ ተግዳሮቶችን በትዕግስትና ከስሜት በፀዳ አስተሳሰብ እየተጋፈጥን ከሄድን፣ ነገሮች በፍጥነት ይቀየራሉ፡፡

ተጨማሪ ያንብቡ👇
https://telegra.ph/ETH-09-14-5